Telegram Web Link
  በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር “#የምግባራት ሁሉ ንግሥት  "በሚል ዐቢይ ርእስ ሃይማኖት  ባለበት ሁሉ ጾም እንዳለ፣የጾም  ጥቅም፣ እንዴት መጾም እንዳለብን፣በጾም ወቅት መጥነን መመገብ እንዳለብን ፣ዕለት ዕለት የማያቋርጥ ጾም ምን አይነት እንደሆነ በበቂ  ማስረጃ የተደገፈ  ትምህርት ይዛለች።
• ዐቢይ ጉዳይ  ዐምድ  ሥር  ደግሞ “ #የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተዋጽኦ  #በዐድዋ ጦርነት “ በሚል ርእስ   ታሪክ ብዙ ገንዘብ ከተከፈለባቸው ማስታወቂያዎች እና ገበያን ዓላማ አድርገው ከሚነገሩ ዲስኩሮች በላይ ድምፁ የሚያስተጋባ  እንደሆነ ፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያላትን ነገር ሁሉ ወደ አድዋ ጦርነት አንቀሳቀሰች ፡፡ ሕዝቧን ካህናቷንና ታቦቷን ይዛ ዘመተች ፡፡ ቆዳ እና ሌጦ የለበሱ ባሕታውያን ሳይቀሩ የዘመቻው ተሳታፊዎች ነበሩ፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያላትን ነገር ሁሉ ወደ አድዋ ጦርነት አንቀሳቀሰች ፡፡ ሕዝቧን ካህናቷንና ታቦቷን ይዛ ዘመተች ፡፡ ቆዳ እና ሌጦ የለበሱ ባሕታውያን ሳይቀሩ የዘመቻው ተሳታፊዎች  እንደነበሩ ያትታል ።
•  ክርስትና በማኀበራዊ ዐምድ ሥር  ደግሞ  " ከሚያለቅሱ ጋር አልቅሱ   “በማለት  የሚገባ ኅዘን እና የማይገባ ኅዘን እንዳለ ፣ በዘመናችን  በልዩ ልዩ ምክንያቶች ጩኸታቸው ያልተሰማላቸው ፤ዕንባቸው ያልታበሰላቸው ፤ከኀዘናቸው መረጋጋት ያልቻሉ ፣በረኅብ አልጋ የሚገረፉ  ወገኖቻችን ከዕለት ወደ ዕለት እየተበራከቱ እንደሆነ፣ የሰው ልጆች ለረኅብ የሚዳረጉባቸውን ዋና ዋና ምክንያቶች በዝርዝር ይዳስሳል፡፡  በዚህ ወቅት  እነዚህን ኀዘን የደረሰባቸውን ማጽናናት እንደሚገባ ይጠቁማል ።
•  በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር “#በእንተ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርዊ  ክፍል_፩ "  በሚል ርእስ ስለ ቅዱስ ኤፍሬም ልደትና ዕድገት ፣ስለ ቅዱስ ኤፍሬም አገልግሎትና የገጠሙትን ፈተናዎች  በስፋት ይዳስሳል ።
•  በነገዋ  ቤተ ክርስቲያን ዐምድ  ሥር “ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን ተረካቢ እናዘጋጅላት _ክፍል ፫ “ በሚል ልጆች በወላጆቻቸው ብቻ የሚያድጉ እንዳልሆነ ፣ጎረቤት፤ትምህርት ቤት ፣ማኅበረሰብ ወዘተ ሁሉ ለልጆች ዕድገት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሚና እንዳላቸው  ያስነብባል፡፡ 
•  በኪነ ጥበብ ዐምድ “ አጋዥነት “ በሚል ርእስ ሰፊና አስተማሪ ታሪክ ይዛለች ፡፡
•  የጥያቄዎቻችሁ መልስ ዐምድ “# ግብረ ሶዶማዊነትና ክፉቱ   ክፍል -፩ "   በሚል ርእስ ከመምህር ግርማ ባቱ የቅድስት ሥላሴ ዪኒቨርስቲ መምህር ጋር የተደረገ  ወቅታዊ ምላሽ ይዛለች  ።
        #መ/ር ግርማ ባቱ ".ሴት ከሴት ጋር ወንድም ከወንድ ጋር የሚፈጽሙት ኃጢአት እንደሆነ ገልጸዋል።
        #ማዕከላት፣የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ሐመር መጽሔት ፴፩ኛ ዓመት  ቁጥር ፫  ዕትም ለአንባቢያን እንድትደርስ  የድርሻችሁን እንደትወጡ  ምክንያቱም .ሐመር መጽሔት ትምህርተ ወንጌል ለመላው ዓለም ለማዳረስ አንዱ መሣረያ ናት፡፡

  አስተያየት ለመስጠት
magazine @eotcmk.org  ወይም በ0111540484/0944259014 ያግኙን

  ሐመር መጽሔት ፴፩ኛ ዓመት  ቁጥር ፫   በማሰራጨት ፡በማንበብና በማስነበብ የድርሻችን እንወጣ !
[email protected]  ሐመር መጽሔት  ዝግጅት  ክፍል
"ጾማችን በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት የሚኖረው የተፈናቀሉት ወገኖቻችን ወደ ቀያቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሮ መኖር ሲችሉ፣ የተራቡት ሲደገፉ፣ ፍትሕ ያጡት ፍትሕ ሲያገኙ ነው፡፡"
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ 2016 ዓ.ም ዐቢይ ጾምን አስመልክተው መልእክት አስተላልፈዋል።

ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት ሙሉ መልእክት እንደሚከተለው ቀርቧል።

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

በሀገር ውስጥና በዓለም ዙሪያ ሁሉ የምትገኙ ምእመናንና ምእመናት ልጆቻችን በሙሉ!

እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ስድስት ዓመተ ምሕረት የጾመ ኢየሱስ ሱባኤ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!

“ወእምዝ ኃደጎ ዲያብሎስ ወናሁ መጽኡ መላእክት ይትለአክዎ፡- ከዚህ በኋላ ዲያብሎስ ትቶት ሄደ፤ እነሆም ያገለግሉት ዘንድ መላእክት መጡ›› (ማቴ ፬፲፩)፡፡

በቀጣዮቹ ሁለት ወራት በከፍተኛ ሃይማኖታዊ ተመሥጦ የምንጾመው ጾም፣ ጾመ ኢየሱስ ተብሎ የሚታወቀው ነው፡፡ ይህ ጾም በጥንት ጊዜ ሰው በኃጢአት የወደቀበትን ምክንያት፣ እንደዚሁም ሰው ኃጢአትንና ዲያብሎስን እንዴት እንደሚያሸንፍ ጌታችን እኛን ያስተማረበት ጾም ነው፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በቅዱስ መጽሐፏ እንደምታስተምረን፣ ኃጢአትና ዲያብሎስ የአንድ ሳንቲም _ ሁለት ገጽታዎች ናቸው፤ ይህም ማለት ዲያብሎስ ባለበት ኃጢአት አለ ፤ ኃጢአት ባለበትም ዲያብሎስ አለ ማለት ነው፤ እነዚህ ሁለቱ የሚለያዩ አይደሉም፤ የመጨረሻ ግባቸው ደግሞ ሰውን መጣል ነው፡፡ዲያብሎስ የሰውን ደካማ ዝንባሌ ወይም በሆነ ነገር መጐምጀትን በሰው ሲመለከት ያንኑ የጐመጀበትን ክፉ ምኞት እንዲፈጽም፣ በረቂቅ የሰው ኅሊና ውስጥ ገብቶ በከፍተኛ ደረጃ ይገፋፋል፤ ሰውም በራሱ የመጐምጀት ዝንባሌና በዲያብሎስ ግፊት ለመንፈሳዊ ሕይወቱ ጐጂ የሆነውን ድርጊት ይፈጽማል ፤ ቀጥሎም ድርጊቱ በእግዚአብሔር ፊት በደል ይሆንና ከእግዚአብሔር ይለየዋል፡፡ ሰው ከእግዚአብሔር ከተለየ ደግሞ ዘለዓለማዊ ሕይወትንና ክብርን ጨምሮ ብዙ መልካም ነገርን ያጣል፤ ኃጢአት የሚባለውም ይህ ነው፤ በቀደሙት አባትና እናት ማለትም በአዳምና ሔዋን የተከሠተው ነገርም ይኸው ነው፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት

ኃጢአትን በጽድቅ፣ ዲያብሎስን በጾም በማሸነፍ የአሸናፊነትን መንገድ ሊያሳየን የመጣው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአዳምና በሔዋን የተፈጸመው ውድቀት እንዴት እንደሚቀለበስ በዚህ ጾም አስተምሮናል፡፡ ጌታችን ዐርባ ቀንና ዐርባ ሌሊት ከጾመ በኋላ ተራበ፤ ዲያብሎስም መራቡን አይቶ ይጐመጅልኛል ብሎ በምግብ ፈተነው፡፡ የጌታችን መልስ ግን ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ የሚል ነበረ፣ በተመሳሳይም በፍቅረ ንዋይና በአምልኮ ባዕድ ፈተነው የጌታ መልስ ግን በተቃራኒው ነበረ፡፡

ዲያብሎስ በሦስቱም የማስጐምጃ ፈተናዎች ጌታ ሊሸነፍለት ካለመቻሉም በላይ "አንተ ሰይጣን ከኋላዬ ሂድ" ብሎ ሲገሥጸው ተሸንፎ ትቶት ሂዶአል፡ በአሸናፊነቱ የተደሰቱ መላእክትም ወዲያውኑ መጥተው በክብረ አምልኮ አገለገሉት፤ በዚህ ድርጊት የምንመለከተው እውነታ ቀዳማይ አዳምን ባሸነፈበት ስልት ዳግማይ አዳም ክርስቶስን ለመጣል ዲያብሎስ የሄደበትን ርቀት በአንድ በኩል ስናይ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ዳግማይ አዳም ክርስቶስ የቀዳማይ አዳም ተሸናፊነትና ውድቀት ለመቀልበስ ያሳየውን ጥብዓት እናያለን፡፡

በዚህም የቀደመው ውድቀት በኋለኛው አሸናፊነት ሙሉ በሙሉ ተቀልብሶ፣ ዲያብሎስ ጓዙን ጠቅልሎና ተስፋ ተስፋ ቆርጦ መሄዱን እናስተውላለን።

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!

ጌታችን የአሸናፊነትን መንገድ በቃልና በተግባር አስተምሮናል፤ አሳይቶናልም፤ ይህንም ያደረገው እሱ አሸንፎልናል እያልን ለመኵራራት ሳይሆን፣ በእሱ ኃይል እየታገዝንና እሱ ባሸነፈበት ስልት እየተጠቀምን እንድናሸንፈው ነው፡፡ ሰይጣን የሚሸነፍበት ስልት በሌላ ሳይሆን፤ ሥጋዊ መጐምጀትን ከአእምሮአችን አውጥተን በመወርወር ነው፡፡

ሥጋችን በፍቅረ ንዋይ፣ በሥልጣን፣ በዝሙት እንደዚሁም በተለያዩ ሥጋዊ ምኞቶች ሊጐመጅ ይችላል፤ ያን ጊዜ ሰይጣን እነሱን እንድንፈጽም ሊገፋፋን ከበኋላችን እንደቆመ እናስብና "አንተ ሰይጣን ከኋላዬ ሃድ” እንበለው፡፡ በቃል ብቻ ሳይሆን በተግባር ያስጐመጁን ነገሮችን ከኅሊናችን አውጥተን በመጣል እሱን ማሸነፍ አለብን፤ በዚህ ጊዜ ሰይጣን ይሸሻል፤ መላእክትም ወደኛ መጥተው ይረዱናል፣ ይጠብቁናል፤ ያግዙናል፣ ያድኑናል፡፡ ዲያብሎስ የሰዎችን የመጐምጀት ዝንባሌን ተከትሎ በመገፋፋት ዛሬም ዓለማችንን ለከፋ ውድቀት እየዳረጋት ነው፣ ሀገራችንን ጨምሮ በየአካባቢው የሚቀሰቀሱት አለመግባባቶችና ግጭቶች መንሥኤያቸው ከመጐምጀት ውጭ ሊሆን አይችልም፡፡ ግማሹ በሥልጣን፣ ግማሹ በሀብት፥ ግማሹ በራስ ወዳድነት፣ ግማሹ ደግሞ የበላይ ለመሆን በሚል እሳቤ የሰው ኅሊና በክፉ ምኞት ይጐመጅና በዲያብሎስ ገፋፊነት ወደ ተግባራዊ ጥፋት ይገባል፡ በውጤቱም ሰው ይጎዳል፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት

ጾም ማለት እህልንና የእንስሳት ውጤቶችን ከመመገብ መከልከል ብቻ አይደለም፣ የእንስሳት ውጤት የሆኑትን ላለመመገብ ከምንወስነው በላይ እኩያት ፍትወታትንና ኃጣውእን ላለማስተናገድ በቁርጥ መወሰን ይጠበቅብናል፡፡ ስንጾም መገዳደልን፤ መጣላትን መለያየትን፤ መገፋፋትን በሆነ ነገር መጐምጀትን እርም ብለን በመተው ዲያብሎስን የምናሸንፍበት የአሸናፊነት ኅሊና መላበስ አለብን፣ ከክፉ ኅሊና እና ተግባር የተለየን ያህል በአንጻሩ ደግሞ በጎ ነገርን ለመስራት በእጅጉ መበርታት ይጠበቅብናል፡፡

ዲያብሎስ ተስፋ ቆርጦ የሚሸሸው ይቅር ይቅር ስንባባል፤ ለሰላምና ለአንድነት፣ ለፍቅርና ለስምምነት ስንቆም ነው! ከዚህም ጋር በእግዚአብሔር ፊት እጅግ ጸያፍ የሆነው ግብረ ኃጢአት በዚህች ምድር እንዳይፈጸም ማኅበረ ሰባችን በተጠንቀቅ ሲቆም ነው፤ እንደዚሁም ደም መፋሰስ፣ አለመተማመንና በሴት ልጆቻችን የሚደርስው አካላዊ፣ መንፈሳዊና ሞራላዊ ጥቃት ሲቆም ነው፡፡ ጾማችን በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት የሚኖረው የተፈናቀሉት ወገኖቻችን ወደ ቀያቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሮ መኖር ሲችሉ፣ የተራቡት ሲደገፉ፣ ፍትሕ ያጡት ፍትሕ ሲያገኙ ነው፡፡

ይህ ዓይነት መልካም ሥነ ምግባር በእያንዳንዱ የማኅበረሰብ አእምሮ ቦታ አግኝቶ ሲተገበር ትክክለኛውን ጾም ጾምን ማለት እንችላለን፣ ዲያብሎስም በእርግጠኝነት በዚህ ይሸነፋል፤ የሰው ጣዕመ ሕይወትም በዚህ ይለመልማል! ምድሪቱም በእግዚአብሔር በረከት ትሞላለች፡፡ ይህን ቅዱስ ተግባር በወርኃ ጾሙ በደንብ እንድንተገብረው ለመላው ኢትዮጵያውያን በተለይም ለኦርቶዶክሳዊው ማኅበረሰብ መንፈሳዊና አባታዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

በመጨረሻም

በሀገራችን ረሃብ የሚያጠቃቸው ወገኖች በበዙበት በአሁኑ ወቅት፤ ሳንመጸውት ጾምን ጾምን ማለት ማጣፈጫ ወጥ የሌለው ምግብ መመገብ ማለት ስለሆነ፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የቁርስ በጀቱን ለተራቡ ወገኖች በመለገስ ወገኖቹን በረሃብ ከመሞት እንዲታደግ ወቅታዊ ጥሪያችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡

መልካም የጾም ወቅት ያድርግልን! እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ !! ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! አሜን፡፡

አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መጋቢት ፩ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት

ዘወረደ


በዚህ ሳምንት የቃል ርደት፣ የወልድ ልደት፣ የአዳም ድኅነት ቢነገርም እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ከሰማይ የወረደ ሰማያዊ፣ በክብር ያረገ በኩረ ትንሣኤ መሆኑ አይዘነጋም፡። ለዚህም ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ “እውነት እውነት እልሃለሁ፥ የምናውቀውን እንናገራለን፤ ያየነውንም እንመሰክራለን፥ ነገር ግን ምስክርነታችንንም አትቀበሉትም። በምድር ያለውን ስንነግራችሁ ካላመናችሁኝ፥ በሰማይ ያለውን ብነግራችሁ እንዴት ታምኑኛላችሁ? ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፥ እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው። ሙሴ በምድረ በዳ እባቡን እንደ ሰቀለው የሰው ልጅ እንዲሁ ይሰቀል ዘንድ አለው፡፡ያመነበት ሁሉ ለዘለዓለም ሕያው ሆኖ እንዲኖር እንጂ እንዳይጠፋ፣ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘለዓለም ሕይወትን እንዲያገኝ እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ቤዛ አድርጎ እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶታልና” እንዳለ እርሱ ምድራዊ ያይደለ ሰማያዊ ነው። (ዮሐ.፫፥፲፩-፲፮)  “ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ” ስለ ፍቅሩ በፈጠረው የተጠመቀ ሰማያዊ ነው።

ጾመ ድጓው የሚጀምረውም እንዲህ በማለት ነው፤ “ዘወረደ እምላዕሉ፣ አይሁድ ሰቀሉ…. እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ በቃሉ፤ ….በቃሉ የሚያድነውን ከላይ የወረደውን የሁሉን ጌታ አይሁድ ሰቀሉት…”
ዘወረደ የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ነው። ስያሜውም የቅዱስ ያሬድ ነው። ትርጉሙም “ከሰማያት የወረደ” ማለት ነው። ቅድመ ዓለም ከአባቱ ከአብ የተወለደ ፣ድኅረ ዓለም ከድንግል ማርያም የተወለደ ነው። ስም አጠራሩ  ያለና የነበረ፣ እግዚአብሔር፣ በፈቃዱ ዓለምን ለማዳን የመምጣቱን ምሥጢር የምንረዳበት ሳምንት ነው። ይህ የመጀመሪያው ሳምንት ‹ጾመ ሕርቃል› እየተባለም ይጠራል፡፡ ሕርቃል (ኤራቅሊዮስ) በ፮፻፲፬ ዓ.ም የነበረ የቤዛንታይን ንጉሥ ነው፡፡ለክርስቲያኖች ባደረገው ርዳታ ምክንያት አንድ ሳምንት ጾመውለት ነበር፡፡ ዛሬም ድረስ ጾመ ሕርቃል እየተባለ ይጠራል፡፡ ሙሉ ታሪኩ በፍትሐ ነገሥት ትርጓሜ አንቀጽ ፲፭ ላይ ይገኛል፡፡

በዚህ ሳምንት ቤተ ክርስቲያን ስለ ጾም ጥቅምና እንዴት መጾም እንዳለብን ታስተምረናለች፡፡ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው “አከለክሙ መዋዕል ዘኃለፈ ዘተቀነይክሙ ለግዕዘ ሥጋክሙ፤ ለሥጋቸሁ ፈቃድ የተገዛችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃችኋል፤ ከአሁን በኋላ ግን ጹሙ፣ ጸልዩ ለእግዚአብሔር ተገዙ” እያለ የጾም አዋጅ ያውጃል። ጾም ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ፣ ፈቃደ ነፍስን ለፈቃደ እግዚአብሔር የምናስገዛበት መንፈሳዊ መሣሪያ ነው፡፡

ጾሙ በሚጀመርበት ሰንበት በሚሰበከው ምስባክ እንዲህ ብሎ ያሳስበናል፤ “ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ፣ በረዓድም ደስ ይበላችሁ” ጾም ከምግብና ከመጠጥ እንዲሁም ከሌሎች ምቾቶችና ደስታዎች ከመከልከል ያለፈ ጥልቅ ትርጉም ያለው ተግባር ነው። (መዝ.፪፥፲፩-፲፪) “ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ ከመ ያብርህ ብርሃነ ስብሐቲሁ በላዕሌነ፤ (የእግዚአብሔር) የክብሩ ብርሃን በላያችን ላይ ያበራ ዘንድ ጾምን እንጹም፤ወንድማችንንም እንውደድ” እንዲል። (ጾመ ድጓ)

በዘወረደ እሑድ የሚነበቡት ምንባባትም ይህንን የጾምን ጸጋ የያዙ ናቸው።

“ነገር ግን ፈጣሪያችን የምትበልጠውን ጸጋ ይሰጣል፤ ስለዚህም “እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፤ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል” ይላል፡፡ እንግዲህ እግዚአብሔርን እሺ በሉት፤ ሰይጣንን ግን እንቢ በሉት፤ ከእናንተም ይሸሻል፡፡ እግዚአብሔርን ቅረቡት፤ ይቀርባችሁማል፤ እናንተ ኃጥኣን እጆቻችሁን አንጹ፤ ሁለት አሳብም ያላችሁ እናንተ ልባችሁን አጥሩ፡፡ እዘኑና አልቅሱ፤ ሳቃችሁን ወደ ልቅሶ÷ ደስታችሁንም ወደ ኀዘን መልሱ፡፡ በእግዚአብሔር ፊት ራሳችሁን ዝቅ አድርጉ፤ እርሱም ከፍ ከፍ ያደርጋችኋል፡፡” (ያዕ.፬፥፮-፲)

“በውኑ እንግዲህ በስሙ እናምን ዘንድ የከንፈሮቻችን ፍሬ የሚሆን የምስጋና መሥዋዕትን በየጊዜው ለእግዚአብሔር ልናቀርብ አይገባንምን? ነገር ግን ለድሆች መራራትን፥ ከእነርሱም ጋር መተባበርን አትርሱ፤ እንዲህ ያለው መሥዋዕት እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋልና፡፡” (ዕብ.፲፫፥፲፭-፲፮)

በጾም የተጠቀሙ ቅዱሳንን እያሰብን ለጾም እንድንተጋም ወደ እነርሱ እንድንመለከት ቤተ ክርስቲያን ታስተምራለች፡፡“ ልባችሁ በመብል ያይደለ በጸጋ ቢጸና ይበልጣልና፤ በዚያ ይሄዱ የነበሩ እነዚያ አልተጠቀሙምና።” (ዕብ.፲፫፥፱) ሳምንቱ በሚጀምርበት ሳምንት የሚነበበው የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት እንዲህ ይላል፡፡ ጾመ ድጓው አባቶቻችን ያገኙትን በረከት እንደምናገኝበት ሲገልጽ “የእግዚአብሔር የክብሩ ብርሃን በላያችን ላይ ያበራ ዘንድ ጾምን እንጹም፤ ወንድሞቻችንም እንውደድ፤ ኤልያስ በጾም ወደ ሰማይ አርጓልና፤ዳንኤልም ከአናብስት አፍ ድኗልና፡፡”

ጾም ፈቃደ ነፍስን በፈቃደ ሥጋ ለማሠልጠን የአጋንንት ኃይል ለመቋቋም የሚያስችል የክርስቲያኖች ጋሻ በመሆኑ በሃይማኖት ለሚመሩ ምእመናን እጅግ አስፈላጊና ከምንም በላይ የሕይወታቸው መርሕ መሆን እንደሚገባ ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ እንዲህ በማለት   ያስተምራል፡፡ ” አሁንም ወንድሞቻችን በዚህ በሥጋችን ሳለን ፈቃደ ሥጋችንን ልንሠራ አይገባም፤ ፈቃደ ሥጋቸውን የሚሠሩ ሰዎች በወዲያኛው ዓለም ምውታን ናቸውና፡፡ የሥጋችሁን ፈቃድ በነፍሳችሁ ፈቃድ ድል ከነሣችሁት ለዘለዓለም ሕያዋን ትሆናላችሁ፡፡ የነፍሳቸውን ፈቃድ የሚሠሩ ሰዎች ሁሉ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና፡፡" (ሮሜ ፰፥፲፪-፲፬)

ጾም አበው ቅዱሳን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በጊዜ ቀምረው፣ በበታ ወስነው፣ በሁኔታ ገድበው... ባስቀመጡልን ወቅት ከእህልና ከውኃ በመከልከልና ሰውነትን በማድከም ብቻ ሳይሆን ለስሕተት ከሚዳርጉ ነገሮችና ቦታዎች ተቆጥቦ በጸሎት መትጋትም እጅጉን አስፈላጊ ነው፡፡ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊትም ይህንን እውነታ በተመለከተ እንዲህ ይላል፡፡ “እኔ ግን እዘንልን፤ ለምንልን ባሉኝ ጊዜ ማቅ ምንጣፍ ለብሼ አዘንኩላቸው፤ ሰውነቴን በጾም አደከምኩዋት፤ ልመናዬም እኔም ወደመጥቀም ተመለሰችልኝ፡፡” (መዝ. ፴፬/፴፭፥፲፫)

ጾም ከሥነ ምግባራት ሕግ አንዱ በመሆኑ እንኳንስ ያልተፈቀደውን የተፈቀደውም ቢሆን የማይጠቅም ከሆነ ፈጽሞ በመተው ለእግዚአብሔር ያለንን ፍጹም ፍቅር የምናስመሰክርበት ምሥጢር ነው፡፡

ጾም ከመብልና ከመጠጥ ጋር የተያያዘም በመሆኑ መብል ጊዜያዊ ስለሆነ ማለትም በዚህ ዓለም እስካለን ብቻ የምንገለገልበት እንጂ ዘለዓለማዊ ስላይደለ ለጊዜያዊ መብልና መጠጥ ምክንያት ከሃይማኖት ሥነ ምግባር እንዳንወጣ ቅዱሳን አባቶቻችን ሐዋርያት ሲመክሩ “መብል በእግዚአብሔር ዘንድ ግዳጅ አይፈጽምልንም ወደ እግዚአብሔር አያቀርበንም፤ ብንበላም አይረባንም፤ አይጠቅመንም፤ ብንተወውም አይጎዳንም” በማለት ሲመክሩን ቅዱስ ጳውሎስም የመብልና የሆድ ጊዜያዊነት አስመልክቶ እንዲህ በማለት አስተምሯል፡፡ (፩ኛቆሮ.፰፥፰)

“ሁሉ ነገር ተፈቅዶልኛል፤ ሁሉ ግን አይጠቅመኝም፡፡ ሁሉ ተፈቅዶልኛል በእኔ ላይ ግን አንድ ነገር እንኳን አይሠለጥንብኝም፡፡ መብል ለሆድ ነው ሆድም ለመብል ነው፡፡ እግዚአብሔር ግን ሁለቱንም ያሳልፋቸዋል”፤ (፩ኛቆሮ.፮፥፲፪-፲፫) “ለሚጠፋ ምግብ አትሥሩ፤ ይልቅስ የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ የዘለዓለም ሕይወት ስለሚሆን ምግብ ሥሩ” እንደ ተባለ (ዮሐ. ፮፥፳፯) ካለን ጊዜ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ጊዜ በመስጠት ቢበሉት የማያስርበውን፣ ቢጠጡት የማያስጠማውን፣ የዘለዓለም ሕይወት የምናገኝበትን ሥጋ እና ደሙን ተቀብለን መንግሥቱን እንድንወርስ ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን።

ሥርዓት ቅዳሴ
ከሠራኢ ካህን፣
ቅዳሴ፡
ዘእግዚእነ
“ዘበእንቲኣነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ፡ ወረደ እምሰማያት። ተሰብአ፡ ወተሠገወ እመንፈስ ቅዱስ ወእማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ስለ እኛ ስለ ሰዎች እኛን ለማዳን ከሰማይ ወረደ፤ በመንፈስ ቅዱስ ግብር  ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ፡፡”

ወንጌል፡ ዮሐ.፫፥፲-፳፬
የዕለቱ ምንባባት:-
•  በሠራኢ ዲያቆን (ዕብ.፲፫፥፯-፲፯)
•  በንፍቅ ዲያቆን (ያዕ.፬፥፮-ፍጻሜ)
•  በንፍቅ ካህን (የሐዋ. ፳፭፥፲፫-ፍጻሜ)

ምስባክ፡ “ተቀነዩ ለእግዚአብሔር በፍርሃት ወተሐሠዩ ሎቱ በረዓድ አጽንዕዋ ለጥበብ ከመ ኢይትመዐዕ እግዚአብሔር” (መዝ.፪፥፲፩)

ወንጌል፡ ዮሐ.፫፥፲-፳፬

ስብሐት ለእግዚአብሔር ኪያነ ዘፈጠረ ከመ ናምልኮ፤ እንድናመልከው እኛን ለፈጠረ ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን!
The Great Lent

The fast that Our Lord and Savior Jesus Christ fasted is known to be “The Great Lent.” The salvation done for all human beings is through His marvelous wisdom. The Lord’s Covenant vowed for His First Mankind and his heir has been made through The Holy Son becoming man and wearing flesh of humans.

The Lord’s work of salvation revealed upon the apostasy era, is done by His Birth, Words of Gospel, Baptism and Crucifixion. The Ethiopian Orthodox Incarnation Religion recognizes His work of salvation and in particular to His fasting, there are Eight known Weeks.

1. He Who Comes Down
The Almighty son of God, who can never be watched by the human’s eyes and touched with man’s hand has come down to be with mortals, wearing our flesh; ate; walked and talked like one of us. Even have washed human’s (the apostle’s) feet.
This is the reason our Holy Church recognizes and named the first week of the Great Lent that our Lord and Savior Jesus fasted Himself as “He who comes down.” Though He fasted for forty days, the days the King Heraclius fasted is added to the fast. Thus we fast 55 days, in commemoration of Our Lord’s fasting and enduring all the suffering

In this fasting season, all in the name of Orthodox Incarnation Religion believers, beginning the age of seven, are expected to fast in accordance to the time stated in the Book of “The Law Kings.”
The weeks of Great Lent have their own Liturgy of fasting and thus shall be known and performed accordingly. For instances, the time of abstaining from any kinds food and beverages in the first week is until 12 O’ Clock Local time. All the other weeks except passion week which is fasted until dawn, (One O’ Clock), are fasted till 11 O’ Clock.

The Significance of fasting this fast far more than just abstaining during the time duration since it the world’s salvation done by it. We shall make ourselves ready spirituality in order to embrace His mercy and cleanse our soul. We need to be engaged in all the good endeavors specially alms giving.

Saint Paul the apostle in his epistle to the romans said, “Therefore, brethren, we are debtors, not to the flesh, to live after the flesh. For if ye live after the flesh, ye shall die: but if ye through the Spirit do mortify the deeds.” (Romans 8:12-13) The Apostle has thought us to seize our bodily desire and do good for our soul.

Fasting has the power of strengthening us to pass all the predicaments in our spirituality and bestow us all the virtue in front of God. The prayer we do and the prostration we make during fasting seasons are accepted more than any other times. Our good endeavors are also recognized aside them.

May God bestow us mercy upon this fast, Amen!
‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ!››

ክፍል አንድ

ቤተ ክርስቲያን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደሙ ዋጅቶ የመሠረታት፣ በክርስቶስ ክርስቲያን ለተባልን በሙሉ መሰብሰቢያችን የተቀደሰች ቤታችን ናት፡፡ ቤተ ክርስቲያን ስንልም ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን፣ የክርስቲያን ወገን፣ የምእመናን አንድነት ወይንም ማኅበረ ምእመናን እያንዳንዱን ማለታችን ነው፡፡ (የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ቁጥር ፩)

ውድ አንባብያን! የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ስለ ቤተ ክርስቲያን ምንነት፣ ታሪክ ወዘተ መተንተን አይደለም፡፡ የነገዋ ቤተ ክርስቲያን ምን መምሰል አለባት? እንዴትስ ለትውልዱ እስከ ክብሯና ግርማ ሞገሷ ትሻገር? የሚለውን አሳሳቢ ጉዳዮችን መዳሰስ ነው እንጂ፡፡

ትውልድ ጅረት ነው፡፡ አንድ ትውልድ አልፎ ሌላ ትውልድ ይተካል፡፡ አንዱ አልፎ ሌላው ሲተካ ግን ተተኪው ትውልድ በቅብብሎሽ የሚተላለፉ ነገሮችን እየተቀበለና እየጨመረባቸው እንደ ዘመኑና እንደ ወቅቱ እያሳደጋቸው፣ እርሱም በተራው ለሌላው ትውልድ እያወረሳቸው ይተላለፋሉ፡፡

ቤተ ክርስቲያን ከትውልድ ወደ ትውልድ በበርካታ ትውልዶች ቅብብሎሽ ከዛሬው ትውልድ ከደረሱ ሀብቶች ዋናዋ ናት፡፡ ሀብት ብዙ ወገን ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ሀብተ ሥጋና ሀብተ ነፍስን የምታሰጥ ናት፡፡ በተጋድሎ በጠንካራ ሥራ፣ በብዙ ውጣ ውረድ ደምና ላብ ፈስሶበት የተገነባን ሀብት የተቀበለ ትውልድ ብቻውን ተጠቅሞ ጨርሶ ለተተኪው ትውልድ በተለይ መንፈሳዊ ውርስ ሳያተርፉ መሄድ ዕዳና በደል ነው፡፡ ይህ ሀብት የምንጠቀመው ብቻ ሳይሆን የምናስተላልፈው አደራ ጭምር ነው፡፡

አባቶቻችን ይህን አደራ አላፋለሱም፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ከተቀበሉት አብልጠው፣ ከተጠቀሙት አትርፈው ከጥፋትና ከብክነት ጠብቀው ከእኛ ዘመን ያደረሱልን መተኪያ የሌላት መንፈሳዊ ሀብታችን ናት፡፡
ቁም ነገሩ የዛሬዋ ቤተ ክርስቲያን ለነገው ትውልድ በምን ሁኔታ ነው የምትተላለፈው? ትውልዱስ እንዴት ነው የሚቀበላት? እኛ የዛሬዎቹ ትውልዶችስ እንዴት ለማስተላለፍ ለማውረስ አስበናል? አባቶቻችን ካወረሱን አጉድለን ወይስ አትርፈን ነው የምናስተላልፋት? የሚሉ ጥያቄዎች መጠየቅ ያለባቸው ናቸው፡፡

ከላይ እንደጠቀስነው ቤተ ክርስቲያን (ምእመኑን፣ ጉባኤውን ወይም አንድነቱን እና ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን እስከ ሥርዓትና ትውፊቱ) በጥቅል ቤተ ክርስቲያን ብለን ወስደን እንዴት ተቀበልናት እንዴትስ እናስተላልፋት የሚለውን ሐሳብ ማንሳት አስፈላጊ ነው፡፡

ቤተ ክርስቲያንን እንዴት ተቀበልናት?

አባቶቻችን ቤተ ክርስቲያን እንድትሰፋ፣ ዶግማና ቀኖናዋ እንዲጠበቅ፣ ምእመናን ወንጌል ሰምተው፣ ሃይማኖትን ጠብቀው፣ ምግባር ትሩፋት ሠርተው፣ በንስሓ በሥጋ ወደሙ ተጠብቀው መንግሥቱን ርስቱን እንዲወርሱ፣ ጉባኤው ሰፍቶ፣ አንድነቱ ጸንቶ አንዲኖር፣ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያንም በዓለም እንድትታነጽ፣ ጉባኤም እንዲ ሠራባት፣ ምእመናንም እንዲገለገሉባት ለማድረግ አገልግሉኝ ሳይሉ አገልግለው፣ ለራሳቸው ክብር ሳይሆን ለቤተ ክርስቲያን ክብር፣ ለራሳቸው ምቾት ሳይሆን ለምእመናን ምቾት፣ ለራሳቸው ሥጋዊ ጥቅም ሳይሆን ለቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ ጥቅም በትጋት ሠርተው አልፈዋል፡፡

‹‹ስለዚህም አንታክትም፤ ነገር ግን የውጭው ሰውነታችን ቢጠፋ እንኳን የውስጡ ሰውነታችን ዕለት ዕለት ይታደሳል›› እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ቤተ ክርስቲያን ስለ ወንጌል የማይታክቱ፣ አደራ ጠባቂ አደራ አስጠባቂ አባቶች ቤተ ክርስቲያንን እስከ ክብሯ ከትውልድ ትውልድ እያሸጋገሩ ከዚህ ትውልድ አድርሰዋታል፡፡ (፪ኛ ቆሮ. ፬፥፲፮፡) ሃይማኖት ለማጽናት፣ ምግባር ለማቅናት፣ ቤተ ክርስቲያንን ለማስፋት፣ ምእመናንን ለማብዛት፣ መናፍቃንን /ከሐድያንን ለመለየት፣ ሕግና ሥርዓት ለማውጣትና ለማስፈጸም በአጠቃላይ የቤተ ክርስቲያንን ሁለንተናዊ ጥቅም ለማስጠበቅ መብቷን ለማስከበር አስተምህሮዋን ለማስፋት እና ለማስቀጠል የጥረት የሚያደርጉ አባቶች በየዘመኑ ስለነበሯት ነው፡፡ በደሙ ለዋጃት ቤተ ክርስቲያን፣ በደሙ ለዋጃቸው ምእመናን /ለመንጋው/ እንዲሁም ለራሳቸው እንዲጠነቀቁ አደራ የተሰጣቸው ባላደራ ናቸውና የአደራቸውን አላጓደሉም፡፡ (ሐዋ.ሥራ ፳÷፳፰)

አባቶቻችን ቤተ ክርስቲያንን ከእኛ ለማድረስ ብዙ መከራን ተቀብለዋል፡፡ መከራው የጀመረው ገና ከሐዋርያት ዘመን ነው፡፡ ገና ከጅምሩም ነው፡፡ ‹‹በኢየሩሳሌም ባለችው ቤተ ክርስቲያን ላይ ታላቅ ስደት ሆነ›› ብሎ መጽሐፍ እንደነገረን (የሐዋ.ሥራ ፰፥፩)፡፡ ይህም የቅዱስ እስጢፋኖስን በድንጋይ ተወግሮ መሞት የጉባኤውን መበተን፣ በቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰውን ስደትና ሥቃይ የሚያስታውስ ቃል ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን በትውልድ ቅብብሎሽ ስትመጣ እንዲሁ አይደለም የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡ ብዙዎች በድንጋይ ተወግረው፣ በእሳት ተቃጥለው፣ በምሳር ተወግተው፣ በሰይፍ ተቀልተው፣ በገደል ተወርውረው በእስራት፣ በእርዛት፣ በረኃብ በጽም ተፈትነው ያቆዩን ናት ለማለት ነው፡፡ (ገድለ ሐዋርያት)

ከሐዋርያት ዘመንም በኋላ በሐዋርያት አበውም በሊቃውንትም ዘመን የቤተ ክርስቲያን ጉዞ አልጋ በአልጋ እንዳልነበር የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ምስክር ነው፡፡ ጥርሱ እንደወለቀው፣ ጺሙ እንደተነጨው፣ ፊቱ እንደተጸፋው እንደ ዲዮስቆሮስ፣ በፓትርያሪክነት ዘመኑ አምስት ጊዜ እንደተጋዘው አትናቴዎስ፣ ንግሥቲቱን በመዝለፉ፣ ሥርዓት አልበኛ ካህናትና ጳጳሳትን ከሹመታቸው በመሻሩ በስደትና በመከራ ሕይወቱ እንዳለፈው እንደ ዮሐንስ አፈወርቅ ያሉ አባቶችን ስናስብ ቤተ ክርስቲያንን ወደ እኛ ለማሸጋገር የተከፈለው ዋጋ ይገባናል፡፡ (የሃይማኖተ አበው ትርጓሜ መቅድም/የቤ ክርስቲያን ታሪክ)

በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ከመርቅያን ንጉሥና ከብርክልያ ንግሥት፣ መከራን ተቀብሏል፡፡ በጉባኤ ኬልቄዶን የተነሣውን ምንፍቅና በመቃወሙ፣ የሊቀ ጳጳሱን ደብዳቤ ባለ መቀበሉ፣ ንግሥቲቱና ደንገጡሮቿ ፊቱን ጸፍተው ጺሙን ነጭተው ጥርሱን ሰብረው ወደ ግዞት እንደላኩት የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ያስረዳል፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅም ሰነፍና ሥርዓት አልበኛ ካህናትንና ጳጳሳትን በመሻሩ፣ ከተማ ለከተማ የሚዞሩ መነኮሳትን በመገሠፁ፣ በሚሠሩት ግፍ ንግሥቲቱንና ባለ ሥልጣናቱን በድፍረት በመገሠፁ መከራ ደርሶበታል፤ በግፍም በግዞት ሞቷል፡፡ (የቤተ ክርስቲያን ታሪክ/ግንቦት ፲፪ ስንክሳር፣ ሰማዕትነት አያምልጣችሁ) ይህም ለራስ ክብር ሳይሆን ለቤተ ክርስቲያን የተደረገ ነው፡፡

ቤተ ክርስቲያን በዘመነ ሰማዕታት፣ ከዚያ በኋላም ሆነ በፊት እስከ ዛሬዋ ዕለት ቤተ ክርስቲያን እንድትቀጥል፣ ዘመናትን ተሻግራ ሙሽራዋ ክርስቶስ እስኪመጣ ተከብራ ትጠብቀው ዘንድ፣ ትውልዱ በየዘመኑ የበረከት ፍሬዋን ይመገብ ዘንድ፣ የጸጋ ግምጃዋን ይለብስ ዘንድ፣ የአጋንንትና ክፉ ሰዎችን ውጊያ የተዋጉላት ለክብሯና ለህልውናዋ ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡላት፣ ብርቱ የማይታክቱ አገልጋዮች፣ መሪዎች፣ አማኞች ስለ ነበሯት መሆኑን እንረዳለን፡፡ (፪ኛ ቆሮ. ፬፥፩)

ጠፍር ታጥቀው፣ ጥሬ ቆርጥመው፣ ውኃ ጠጥተው፣ ሰሌን አንጥፈው፣ ማቅ ለብሰው ቤተ ክርስቲያንን የጠበቋት ክፉ ቀንን ያሳለፏት፣ የዚህ ዓለም ሀብት፣ ሹመት ሽልማት፣ ሥጋዊ ደማዊ ጥቅም ያላበላሻቸው አባቶቻችንና እናቶቻችን ብዙ የብዙ ብዙ ነበሩ፡፡ ‹‹የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ዐሳብ ነው›› እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ የወንጌል አለመሰበክ፣ የምእመናን አለ መብዛት፣ የቤተ ክርስቲያን አለ መስፋት፣ የዕለት ዕለት ዐሳብ ሸክም የሆነባቸው፣ እየሠሩ የማይደክሙ፣ ትጉሃን ጽኑዓን አባቶቻችንና እናቶቻችን ለእኛ አደረሱልን፡፡ (፪ኛ ቆሮ.፲፩፥፳፰)

በዚህም የተነሣ ዳር ደንበሯ ሰፍቶ፣ ምእመኖቿ በዝተው፣ አጥር ቅጥሯ ተከብሮ፣ ጉባኤዋ ሰፍቶ፣ መንፈሳዊ ሀብት ንብረቷ ፋፍቶ ደርጅቶ፣ ክብሯ ገናንነቷ ዓለምን ናኝቶ፣ ለወዳጅ ትምክሕት፣ ለጠላት ኀፍረት ቁጭት ፈጥሮ፣ በየአህጉሩ ያለች ገናና ቤተ ክርስቲያንን አስረከቡን፤ እኛም ተረከብን፡፡

ውድ የዚህ ጽሑፍ ተከታታዮች! አምላካችን ቢፈቅድ በሕይወትም ብንኖር ክፍል ሁለትን ይዘንላችሁ እንቀርባለን፤ ቸር እንሰንብት!
ኑ! የከበረች ሕይወትን እናትርፍ !
መጋቢት 15 ቀን 2016 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ፣
+++
ገቢው በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች ባጋጠመው ማኅበራዊ ቀውስና ድርቅ የተጎዱ ወገኖቻችንን፣ ገዳማትና አብነት ት/ቤቶች ለመደገፍ የሚውል።
የመግቢያ ትኬቱን፡-
1. በማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 4ኛ ወለል (ቤተ አብርሃም)
2. በወረዳ ማእከላት ጽ/ቤቶች
3. በማኅበረ ቅዱሳን ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቆች
4. በማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ የዕለት ገንዘብ መሰብሰቢያዎች
5. በአሐዱ ባንክ ሁሉም ቅርንጫፎች
6. በሰ/ት/ቤት ጽ/ቤቶች
ለበለጠ መረጃ
• 09 44 71 82 82
• 09 42 40 76 60

ማኅበረ ቅዱሳን
አደራ አለብኝ!

የ 2016 ዓ.ም 2ኛ ዙር ጉባኤ

ዓለም ዓቀፍ የግቢ ጉባኤ ምሩቃን መርሐ ግብር

• ቀን፡ መጋቢት 08/2016 ዓ.ም
• ሰዓት፡ ከ 7፡00 ጀምሮ
• ቦታ፡ በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ
የጥናት መጽሔት ምርቃት

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት መጽሔት (The Journal of Ethiopian Church Studies/ JECS) በመስኩ ሰፊ ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች ግምገማ ተደርጎበት በማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማእከል ተዘጋጅቶ የሚታተም ነው።

ተቋሙ ከዚህ በፊት ተመራማሪዎች፣ መምህራንና ተማሪዎች የጥናት ሥራዎቻቸውን እንዲልኩ በመጋበዝ ተገቢውን የምርምር መሥፈርቶች ያሟሉ የጥናት ወረቀቶችን በመለየት በተከታታይ ለሰባት ጊዜ የጥናት መጽሔቱን አሳትሟል። አሁንም ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጋር በተያያዙ የተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ዙሪያ ተዛማጅ የሆኑ ሳይንሳዊ የምርምር ዘዴዎችን የተከተሉ የጥናት ውጤቶችን የያዘ ቁጥር ስምንት የጥናት መጽሔት ለኅትመት አብቅቷል።

የጥናት መጽሔቱ ቅዳሜ መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ምሁራንና ተመራማሪዎች፣ የጥናት መጽሔቱ ዋና አርታዒ እና ተባባሪ አርታዒያን በተገኙበት ይመረቃል።
ኑ! የከበረች ሕይወትን እናትርፍ !
መጋቢት 15 ቀን 2016 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ፣
+++
ገቢው በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች ባጋጠመው ማኅበራዊ ቀውስና ድርቅ የተጎዱ ወገኖቻችንን፣ ገዳማትና አብነት ት/ቤቶች ለመደገፍ የሚውል።
የመግቢያ ትኬቱን፡-
1. በማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 4ኛ ወለል (ቤተ አብርሃም)
2. በወረዳ ማእከላት ጽ/ቤቶች
3. በማኅበረ ቅዱሳን ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቆች
4. በማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ የዕለት ገንዘብ መሰብሰቢያዎች
5. በአሐዱ ባንክ ሁሉም ቅርንጫፎች
6. በሰ/ት/ቤት ጽ/ቤቶች
ለበለጠ መረጃ
• 09 44 71 82 82
• 09 42 40 76 60

ማኅበረ ቅዱሳን
አደራ አለብኝ!

የ 2016 ዓ.ም 2ኛ ዙር ጉባኤ

ዓለም ዓቀፍ የግቢ ጉባኤ ምሩቃን መርሐ ግብር

• ቀን፡ መጋቢት 08/2016 ዓ.ም
• ሰዓት፡ ከ 7፡00 ጀምሮ
• ቦታ፡ በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ
ቅድስት

የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት

የቅድስና ባለቤት የሆነው እርሱ እግዚአብሔር አምላክ ነው። እቀደስ አይል ቅዱስ፣ እባረክ አይል ቡሩክ ነው። በእርሱ የባሕርይ ቅድስና እኛን በአርአያውና በአምሳሉ ፈጥሮ ቡሩክ ሆኖ ባረከን፣ ቅዱስ ሆኖ ቀደሰን፣ሕያው ሆኖ ሕያዋን አደረገን። የጸጋ ቅድስናንም ከእርሱ አገኘን። ቅድስናው የተለየ፣ የከበረ፣ የሚመሰገን፣ የሚሰጥ/የሚያድል፣ የሚያነጻ፣ የሚባርክ እናም የሚያስተሰርይ ስለሆነ እንከን፣ ጉድለት የሌለበት ምሉዕ ነው። ለባለሟሎቹ ቢሰጠው የማይጎድል፣ ተከፍሎ የሌለበት ቅድስና ሆኖ እኛም የቅድስና በጸጋ ተካፋይ ሆነናል።

የተሰጠንን ቅድስና ገንዘብ እንድናደርግ እና እንድንጠቀምበት ደግሞ በጾም፣ በጸሎት፣ በስግደት፣ በምጽዋትና በሌሎች በጎ ምግባራት መትጋት ይገባናል። ‹‹እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ›› እንዲል፡፡ (ዘፍ.፪፥፫፣ ዘሌ.፲፱፥፪) የት መሄድ እንዳለብንም በግልጽ ልበ አምላክ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ‹‹ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ፤ ስለ ትምህርትህና ስለ እውነትህ ስምህን አመሰግናለሁ፤ በሁሉ ላይ ቅዱስ ስምህን ከፍ ከፍ አድርገሃልና›› ይላል። (መዝ.፻፴፯÷፪) የተቀደሰን መሥዋዕት በተቀደሰ ቦታ እንፈጽማለን። መቼ ቢሉ፣ በሰንበት፣ በበዓላት በማኅበረ ዐቢይ/ክርስቲያኖች በሚሰበሰቡበት፣ ስመ እግዚአብሔር በሚጠራበት፣ ታቦት  ባለበት፣ እግረ እግዚአብሔር በቆመበት ቅዱስ ስሙን ከፍ ከፍ በማድረግ ቅድስናን ገንዘብ እናደርጋለን።
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ለዐቢይ ጾም ሁለተኛው እሑድ በአዘጋጀው ምስጋና አማካኝነት ዕለቱ ‹‹ቅድስት›› የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ትርጉሙም ‹‹የተለየች፣ የተመረጠች፣ የከበረች›› ማለት ነው።  (መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ገጽ ፯፻፹፬) ቅድስት የሚለው ቃል ዕለቱ ‹‹ቅድስት›› ተብሎ የተሰየመበት ምክንያት ስለ ዕለተ ሰንበት እንዲሁም ስለ እግዚአብሔር አምላክ ፍጹም ቅድስና የሚያወሳ በመሆኑ ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክም ፍጥረታቱ የእርሱን ስም በማመስገን ይኖሩ ዘንድ ለቅድስና ሕይወት ፈጥሯቸዋልና በሰንበት እሑድ ክርስቲያኖች የቅድስና ተግባራትን ከሌላው ቀን አብዝተው ይፈጽማሉ፡፡ ዕለት ከተግባር፣ ስም ከክብር የተባበረባት ክብርት ሰንበት ቅድስት ስለሆነች ቅዱስ ያሬድ “ቅድስት” ብሎ ጠራት። ይኸውም የምትቀድስ፣ ከብራ የምታከብረን፣ አክብረናት የምንከብርባት በመሆኗ ነው።

ለዚህም ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓ “ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ፤ ሀቡ ስብሐተ ለስሙ፤ አክብሩ ሰንበተ ተገበሩ ጽድቀ፤ ዝግቡ ለክሙ መዝገበ ዘበሰማያት ኀበ ፃፄ ኢያማስኖ ወኢይረክቦ ሰራቂ፤ ድልዋኒክሙ ንበሩ ዘበላዕሉ ጸልዩ ኀበ ሀሎ ክርስቶስ” ትርጉም፦ “ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ስሙንም ጥሩ፤ ሥራውንም ለአሕዛብ ንገሯቸው፤ ለስሙም ምስጋናን አቅርቡ ሰንበትን አክብሩ፤ እውነትንም አድርጉ፤ ብል የማያበላሸው ሌባም የማያገኘው በሰማያት ያለ መዝገብን ለእናንተ ሰብስቡ፤ ተዘጋጅታችሁም ተቀመጡ፤ ክርስቶስ ወዳለበት ወደ ላይ አስቡ፡፡“  ስለዚህ ሰው ሰንበትን አክብሮ ጾሞ ጸልዮ፣ ቅድስናን ጠብቆ መኖር እንዲችል እግዚአብሔር የፍቅሩ መገለጫ የሆኑ ትእዛዛቱ ይነግሩናል።

 ቅዱስ ያሬድም ወቅቱን “ቅድስት” ብሎ ሲሰይም፦

፩.
የአርባ ቀን ጾም መጀመሪያ በመሆኑ፦ ዕለቱ ከዐቢይ ጾም ቀናት ውስጥ አርባው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመው ጾም መጀመሪያ ስለሆነች፣

፪. ቅድስት ሰንበት ላይ በመዋሉ፣ እንግዲህ “የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ” ተብሏል፡፡ (ዘፀ.፳፥፰) የሰንበትን ቀን አስቀድሞ የቀደሰ የባረከ ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ እግዚአብሔርም ሰባተኛውን ቀን ባረከው፤ ቀደሰውም፤ እግዚአብሔር ሊያደርገው ከፈጠረው ሥራ ሁሉ በእርሱ ዐርፎአልና፡፡” (ዘፍ.፪፥፫) 
“ከምእመናን ወገን አንድስ እንኳን በእሑድ ቀን ለገንዘብ መትጋት፣ ገንዘቤን አምጣ ብሎ መጣላት እና ዋስ መያዝ አይገባውም። ሁሉም ምእመናን ወደ ቤተ ክርስቲያን በንጽሕና በትሕትና ሆነው። ዳኛ ግብሬን፣ አበዳሪ ብድሬን፣ ኤጲስ ቆጶስ ዐሥራት በኵራት፣ ነጋ ድራስ ቀረጥ አምጡ ይሉናል ብለው ሳይፈሩ ይምጡ።

፫. ወቅቱ ወርኃ ጾም በመሆኑ፦ ምእመናን ይህንን ወቅት በጾም፣ በጸሎት፣ በእንባ፣ በስግደት፣ በአርምሞ፣ በመልካም ሥራ ቅድስናን የምናገኝበት፣ ጊዜው ሰው ወደ እግዚአብሔር አብዝቶ የሚተጋበት ወቅት በመሆኑ፣ ለእግዚአብሔር የሚገባ ነገር ለማድረግ የነገር ሁሉ መጀመሪያ፣ ለመልካም ነገር መነሻው በቅድስና በንጹሕ ልቡና መቅረብ ስለሆነ ቅድስት ብሏታል።  “እስመ ጾም እማ ለጸሎት ወእኅታ ለአርምሞ ወነቅዓ ለአንብዕ መቅድመ ኩሉ ግብር ሠናይት፤ ጾም ማለት የጸሎት እናት፣ የትሕትና እኅት፣ የእንባ ምንጭ፣የመልካም ሥራ ሁሉ መጀመሪያ ናት” እንዳለው ቅዱስ ያሬድ። ”ጾምን ቀድሱ፤ ጉባኤውንም ዐውጁ” የተባልን የተሰጠንን የጸጋ ቅድስና በእጃችን ላይ መኖሩን አመላካች ቃል ነው። (ኢዩ.፩፥፲፬)

፬. የወንጌል ትእዛዝ በመሆኑ ዕለቱን ተጠቅሞ ዓለምን አስተምሮበታል። “ዛቲ ዕለት እንተ ገብረ እግዚአብሔር ንትፈሣሕ ወንትሐሠይ ባቲ”  ትርጉም፡- “ይህች ዕለት እግዚአብሔር የሠራት ቀን  ናት፤ ሐሤትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን።” (መዝ.፻፲፯፥፳፬) ቅዱስ ዮሐንስም በራእዩ ሰንበት የጌታ ቀን ስለመሆኗ እንዲህ ይላል፤ “በጌታ ቀን በመንፈስ ነበርሁ፡፡” (ራእ. ፩፥፲)

ሊቃውንቱ በፍትሐ ነገሥት “ተጋብኡ ኵሎ ዕለት ኀበ ቤተ ክርስቲያን ወፈድፋደሰ በዕለተ ሰንበት ወበበዓላት ወበዕለተ ትንሣኤ ዘውእቱ ዕለተ እሑድ” ትርጉም፦ “ሁልጊዜ በቤተ ክርስቲያን ተሰብሰቡ፤ ይልቁንም በዕለተ እሑድ፣ በዕለተ ቀዳሚት፣ በጌታ በዓላት ወደ ቤተ ክርስቲያን ተሰብሰቡ” በማለት አዘውናል፡፡ (ፍትሐ ነገሥት፣ ገጽ ፪፶፬)

በትጋት ጾመን፣ ጸልየን ርስቱን እንድንወርስ የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃ፤ የቅዱሳን በረከት ይጠብቀን።

የዕለቱ መዝሙር (ከጾመ ድጓ)፦ግነዩ ለእግዚአብሔር

ምንባባት፡
(፩ኛ.ተሰ.፬÷፩-፲፫)፣ (፩ኛጴጥ.፩÷፲፫-ፍጻ.፣ሐዋ.፲÷፲፯-፴
ምስባክ “እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ:: አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ፣ ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ፤ እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ፈጠረ፡፡ እምነትና በጎነት በፊቱ፣ ቅድስናና የክብር ገናናነት በመቅደሱ ውስጥ ናቸው፡፡” (መዝ.፺፭÷፭)
ወንጌል (ማቴ.፮÷፲፮-፳፭)
ቅዳሴ: ዘኤጲፋንዮስ 

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
 
የ2016 ዓ.ም ሁለተኛው ዙር ዓለም አቀፍ የድኅረ ግቢ ጉባኤ መርሐ ግብር እየተከናወነ ይገኛል።

በጉባኤውም የማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን የበገና መዝሙር ያቀረቡ ሲሆን በዚህ ሰዓት በዲያቆን ኅሊና በለጠ  “ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው።” (ማቴ 4፥1) በሚል ኃይለ ቃል ትምህርተ ወንጌል እየተሰጠ ነው።
2024/09/29 18:25:45
Back to Top
HTML Embed Code: