ሁመራ ማእከል በሁመራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ ጉባኤ ሲያስተምራቸው የቆዩትን የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ለመጀመሪያ ግዜ ማስመረቁ ተገለጸ
ሰኔ ፳፬/፳፻፲፯ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን ሁመራ ማእከል በሁመራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ ጉባኤ ሲያስተምራቸው የቆዩትን የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ለመጀመሪያ ግዜ ማስመረቁ ተገልጿል።
በምርቃት መርሐ ግብሩ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቢ ሐዲስ መ/ር ዜናዊ አሸተ፣ የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ መጋቢ ሰላም መ/ር ኃይሌ አምዴ እንዲሁም የሀገረ ስብከቱ ዋና ኦዲትና ኢንስፔክሽን ገንዘብ ቁጥጥር እና የደብረ ፀሐይ ቅ/ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት ሰብሳቢ የሆኑት ዲ/ን ዳኛቸው ሰው ዓለም እና የተመራቂ ወላጆች ተገኝተዋል።
ኮሌጁ ለመጀመሪያ ጊዜ በዲፕሎማ ሰኔ 21/2017 ዓ.ም ካስመረቃቸው ምሩቃን መካከል 23 የሚሆኑት በግቢ ጉባኤ አገልግሎት ውስጥ ሲከታተሉ ቆይተዋል።
ከተመራቂ ተማሪዎች ውስጥ የግቢ ጉባኤው ሰብሳቢ የነበረችው ተማሪ ሕይወት ደመወዝ በኮሌጁ አጠቃላይ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የዋንጫ እና የብር ተሸላሚ መሆኗ ተገልጿል።
በመርሐ ግብሩ ያሬዳዊ ዝማሬ በተመራቂዎችና በማእከሉ መዘምራን የቀረበ ሲሆን ለተመራቂ ተማሪዎች የአደራ መስቀል ተበርክቶላቸዋል፡፡
ሰኔ ፳፬/፳፻፲፯ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን ሁመራ ማእከል በሁመራ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ ጉባኤ ሲያስተምራቸው የቆዩትን የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ለመጀመሪያ ግዜ ማስመረቁ ተገልጿል።
በምርቃት መርሐ ግብሩ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቢ ሐዲስ መ/ር ዜናዊ አሸተ፣ የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ መጋቢ ሰላም መ/ር ኃይሌ አምዴ እንዲሁም የሀገረ ስብከቱ ዋና ኦዲትና ኢንስፔክሽን ገንዘብ ቁጥጥር እና የደብረ ፀሐይ ቅ/ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት ሰብሳቢ የሆኑት ዲ/ን ዳኛቸው ሰው ዓለም እና የተመራቂ ወላጆች ተገኝተዋል።
ኮሌጁ ለመጀመሪያ ጊዜ በዲፕሎማ ሰኔ 21/2017 ዓ.ም ካስመረቃቸው ምሩቃን መካከል 23 የሚሆኑት በግቢ ጉባኤ አገልግሎት ውስጥ ሲከታተሉ ቆይተዋል።
ከተመራቂ ተማሪዎች ውስጥ የግቢ ጉባኤው ሰብሳቢ የነበረችው ተማሪ ሕይወት ደመወዝ በኮሌጁ አጠቃላይ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የዋንጫ እና የብር ተሸላሚ መሆኗ ተገልጿል።
በመርሐ ግብሩ ያሬዳዊ ዝማሬ በተመራቂዎችና በማእከሉ መዘምራን የቀረበ ሲሆን ለተመራቂ ተማሪዎች የአደራ መስቀል ተበርክቶላቸዋል፡፡
ጎንደር ማእከል ለግቢ ጉባኤያት ተተኪ ሥራ አስፈጻሚዎች ሥልጠና መሰጠቱ ተገለጸ
ሰኔ ፳፭/፳፻፲፯ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን ጎንደር ማእከል ለግቢ ጉባኤያት ተተኪ ሥራ አስፈጻሚ ሥልጠና መሰጠቱ ተገልጿል።
በሥልጠና መርሐ ግብሩ የኔታ መዝገበ ቃል ገብረ ሕይወት የሰቆጣ ወለህ ነቅዐ ሕይወት የ4ቱ መጽሐፍተ ጉባኤያት ምሥክር መምህር "የዓላማ ሰው በአብሮነት" በሚል መነሻ ርእስ የግቢ ጉባኤ ሥራ አስፈጻሚዎችን መንፈሳዊ ሕይወትና የአገልግሎት አፈጻጸም የሚያሳድግ ሥልጠና ሰጥተዋል።
በዕለቱም የማእከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ሥልጣናት ቆሞስ አባ ዮሴፍ ደስታ የተገኙ ሲሆን ለተተኪ ሥራ አስፈጻሚዎች ምክርና መልእክት አስተላለፈዋል።
ሰኔ ፳፭/፳፻፲፯ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን ጎንደር ማእከል ለግቢ ጉባኤያት ተተኪ ሥራ አስፈጻሚ ሥልጠና መሰጠቱ ተገልጿል።
በሥልጠና መርሐ ግብሩ የኔታ መዝገበ ቃል ገብረ ሕይወት የሰቆጣ ወለህ ነቅዐ ሕይወት የ4ቱ መጽሐፍተ ጉባኤያት ምሥክር መምህር "የዓላማ ሰው በአብሮነት" በሚል መነሻ ርእስ የግቢ ጉባኤ ሥራ አስፈጻሚዎችን መንፈሳዊ ሕይወትና የአገልግሎት አፈጻጸም የሚያሳድግ ሥልጠና ሰጥተዋል።
በዕለቱም የማእከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ሥልጣናት ቆሞስ አባ ዮሴፍ ደስታ የተገኙ ሲሆን ለተተኪ ሥራ አስፈጻሚዎች ምክርና መልእክት አስተላለፈዋል።
ያሬዳዊ ዜማ ተጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ መተላለፍ እንዲችል ሥራዎች እየተሠሩ እንደሚገኝ የዜማና የኪነ ጥበብ ማእከል አስታወቀ
ሰኔ ፳፮/፳፻፲፯ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የዜማና የኪነ ጥበብ ማእከል ያሬዳዊ ዜማ ተጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ መተላለፍ እንዲችል ሥራዎች እየተሠሩ እንደሚገኝ አስታውቋል።
በማኅበረ ቅዱሳን የዜማና የኪነ ጥበብ ማእከል ምክትል ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ምሕረቴ እንደገለጹት ማኅበረ ቅዱሳን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ያሬዳዊ ዜማ ተጠብቆ መልኩን፣ ጸባዩን ሳይቀይር እንዲቀጥል ለማድረግ የኅትመት ሥራዎችን እያዘጋጀ ለምእመናን ተደራሽ ለማድረግ እየሠራ እንደቆየ ገልጸው አሁንም የበኩሉን ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ምክትል ኃላፊው አክለው በተለይ ምእመናን፣ ሰንበት ትምህርት ቤቶች፣ ማኅበራት ጋር ግቢ ጉባኤያትን በተመለከተ አመለካከት ላይ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን በተለያየ ጊዜ በመስጠት፣ ማእከላት ራሳቸውን እንዲችሉ ተተኪ መምህራንን ከማፍራት አንጻር ላለፉት ሦስት ወራት የአሠልጣኞች ሥልጠና እየተሰጠ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በተጨማሪም በሥልታዊ ዕቅዱ መሠረት በአገልግሎት ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶችንና መፍትሔዎችን የሚያሳይ ጥናቶችን በማጥናት በተለይ ሽብሻባን፣እንቅስቃሴን፣የመሣሪያ አጠቃቀምን በተመለከተ 25 ሰ/ት/ቤቶች በተገኙበት ጥናቱን ማቅረብ ተችሏል።
ተግዳሮቱንና መፍትሔውን በተመለከተ የተጠናው ጥናት በዋናነት ለውይይትና ለውሳኔ የሚሆኑ 12 አጀንዳዎችን በመለየት ከዋናው መዋቅር ከቤተ ክህነት ታይተው ውሳኔ እንዲሰጥባቸው ለማድረግ እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።
ሰኔ ፳፮/፳፻፲፯ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የዜማና የኪነ ጥበብ ማእከል ያሬዳዊ ዜማ ተጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ መተላለፍ እንዲችል ሥራዎች እየተሠሩ እንደሚገኝ አስታውቋል።
በማኅበረ ቅዱሳን የዜማና የኪነ ጥበብ ማእከል ምክትል ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ምሕረቴ እንደገለጹት ማኅበረ ቅዱሳን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ያሬዳዊ ዜማ ተጠብቆ መልኩን፣ ጸባዩን ሳይቀይር እንዲቀጥል ለማድረግ የኅትመት ሥራዎችን እያዘጋጀ ለምእመናን ተደራሽ ለማድረግ እየሠራ እንደቆየ ገልጸው አሁንም የበኩሉን ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ምክትል ኃላፊው አክለው በተለይ ምእመናን፣ ሰንበት ትምህርት ቤቶች፣ ማኅበራት ጋር ግቢ ጉባኤያትን በተመለከተ አመለካከት ላይ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን በተለያየ ጊዜ በመስጠት፣ ማእከላት ራሳቸውን እንዲችሉ ተተኪ መምህራንን ከማፍራት አንጻር ላለፉት ሦስት ወራት የአሠልጣኞች ሥልጠና እየተሰጠ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በተጨማሪም በሥልታዊ ዕቅዱ መሠረት በአገልግሎት ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶችንና መፍትሔዎችን የሚያሳይ ጥናቶችን በማጥናት በተለይ ሽብሻባን፣እንቅስቃሴን፣የመሣሪያ አጠቃቀምን በተመለከተ 25 ሰ/ት/ቤቶች በተገኙበት ጥናቱን ማቅረብ ተችሏል።
ተግዳሮቱንና መፍትሔውን በተመለከተ የተጠናው ጥናት በዋናነት ለውይይትና ለውሳኔ የሚሆኑ 12 አጀንዳዎችን በመለየት ከዋናው መዋቅር ከቤተ ክህነት ታይተው ውሳኔ እንዲሰጥባቸው ለማድረግ እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።
ከሰ/ት/ቤቶች ጋርም የመግባባትና አብሮ የመሥራት ለውጥ እየመጣ ሲሆን በተለይ የተወሰኑት በተግባር በሚታይ መንገድ ከሕትመት ጀምሮ መሳሪያ አጠቃቀምን ጭምር ለውጥ የታየባቸው ቢሆንም በቂ ነው ማለት ግን አይቻልም ስለዚህ ከዚህ በላይ አስቦ፣ ተናቦ፣ ተቀናጅቶ እንደ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ዘርፍ የሚያገለግል የትኛውም አወቃቀር ጋር በጋራ መወያየት ያስፈልጋል በማለት የማእከሉ ም/ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ምሕረቴ አመላክተዋል።
በመጨረሻም አቶ ፍቃዱ ከሰ/ት/ቤቶችና ከሚመለከተው አካላት ጋር በጋራ በመሥራት፣ በመተጋገዝ፣ በመረዳዳት ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ያለውን አገልግሎት ሰፊ ተደራሽነት እንዲኖረው ለማድረግ ሁሉም አካል የበኩሉን መወጣት ቢችል ለውጥ ማምጣት ይቻላል በማለት መልእክት አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም አቶ ፍቃዱ ከሰ/ት/ቤቶችና ከሚመለከተው አካላት ጋር በጋራ በመሥራት፣ በመተጋገዝ፣ በመረዳዳት ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ያለውን አገልግሎት ሰፊ ተደራሽነት እንዲኖረው ለማድረግ ሁሉም አካል የበኩሉን መወጣት ቢችል ለውጥ ማምጣት ይቻላል በማለት መልእክት አስተላልፈዋል።