Telegram Web Link
በጨዋታ መሃል ፦

<<በራስህ አትተማመንም አይደል>> አለቺኝ ?

እንዴት ልበ ሙሉነት የተጠናወተኝ ሰው እንደሆንኩ ከራሴ ጋ እየተሻማው አወራሁ... አብራራሁ... ዘበዘብኩ

በእርጋታ ከሰማቺኝ በኃላ
<<እንዴት እንደዚህ አልሽ ብትለኝ እና ያስተዋልኩትን ብነግርህ አይሻልም?>> አለቺኝ

<<ቀጥይ>> አልኳት ደስ ባላለው ፊት እያየኃት

<<ስላለህ፣ ስላስደመምከው ፣ስላደረከው ነገር ብዙ ሰአት ሁል ግዜ ታብራራልህ ። የተጣላኸውን የጠላኸውን ያናደደህን ሰው ስህተት እና ያንተን ቅድስና ታስረዳለህ ፣

ሰው ስለራሱ ሲያወራህ ቀጥለህ እኔ.. እኔም.. ብለህ ስለ ራስ ታወራለህ ምንም ነገር ስትሰማ ከራስህ ጋ እያወዳደርክ ነው መሰለኝ ።

ሰው ሲቃወምክ ስለምታወራው ነገር ሳይስማማ ሲቀር ቅር ይልሃል... ብዙ ታብራራለህ ። ያመንከው እና የሆንከውን እንዲመሰከርልህ እንዲጨበጨብልህ ጉንጭህ እስኪዝል ታስረዳለህ ።

ስላደረከው እና ስለሆንከው ነገር አስተያየት ትጠይቃለህ ደስታህ የሰው አስተያየት ላይ ተንጠልጥሎል።

እምቢ ማለት ይከብደሃል ። እምቢ ከማለት መዋሸት ትመርጣለህ ። ባላሳቀህ ነገር ትስቃለህ ፣

የአዲስ ሰው ቀልብ ለመሳብ እሱ የሚወደውን ነገር ለማውራት ለመሆኑ ጥረት ስታደርግ ብዙ ግዜ ያስተዋልኩ ይመስለኛል ።

ሰው እንዳይቀየም ስትል መጠየቅ ያለብህን አጠይቅም ።

ያበደርከውን ብደር እንኳን ስትጠይቅ ችግር እንዳጋጠመክ አብራርተህ ነው ።

ራስህን አታከብርም መሰለኝ እራስን አለማክበር አንደኛው በራስ ያለመተማመን ውጤት ነው !!

ከጠላት ሁሉ ጠላት የሚከፋው የውስጥ ጠላት ነው ። ከራስህ ጋ የታረክ ግዜ አለም ቢጣላህ እንኳን አትሸበርም ።

ስታወራ ረጋ ብለህ ተናገር !
ለመወደድ ስቃይ አትብላ !
ሰው አክብር እንጂ አክብደህ አትይ !
ሁሉንም እቅድህን ለሁሉም አታውራ!
የተሰማህን ሁሉ አትናገር !
እምቢ አልችልም ማለት ልመድ !
ስለተሳካልህ ነገር ሂደት በየሜዳው አታብራራ !

ያልተቀበልከው ማንነት ካለ የበታችነት ስሜት የሚያሰማህ ሁነት ካለ ረጋ ብለህ አጥናውና መላ ፈልግለት ።

ብቻህንም መሆን ልመድ ሁሌ አብሮ ሰው እንዲሆን አታስስ

ዝም ብዬ አየኋት ።

ልክ ካልሆንኩ፣ ያልኩት እውነት ከሌለው እንደቀባጠርኩ ከተሰማህ አፉ በለኝ
ካወራውት ፍሬ ነገር ካገኘህበት ደሞ ደግ >>

አሁንም ዝም አልኳት ። ዝምታዬ ውስጥ ግን መደነቅ እና ድብርት ነበረበት

By Adhanom Mitiku

@wegoch
@wegoch
@paappii
ጉድ በል🙊😂

⚡️ጥንዶቹ ለሰርጋቸዉ ቀን ያዘጋጁት የጥሪ ካርድ ማተሚያ ቤቱ ትልቅ ስህተት እንደሰራ ያወቁት ሁሉም ካርዶች ለተጋባዦች ተበትኖ ካለቀ በኋላ ነበር!

⚡️ማተሚያ ቤቱ እንዲያትም የተሰጠዉ ጥቅስ 1ኛ ዮሐ 4:18 ላይ ያለዉን ቢሆንም '1ኛ' የሚለዉን በመርሳታቸዉ ያተመዉ ዮሐ 4:18 ላይ ያለዉን ነበር። (1ኛ የምትለዋ በመረሳቷ መፅሐፉ ከ1ኛ የዮሐንስ መልዕክትነት ወደ የዮሐንስ ወንጌል ተቀየረ ማለት ነዉ።)

⚡️እንዲታተም የተፈለገዉ 1ኛ ዮሐንስ 4:18 "በፍቅር ፍርሃት የለም ፍፁም ፍቅር ፍርሃትን አዉጥቶ ይጥላል.." ይላል

⚡️ማተሚያ ቤቱ ያተመዉ ዮሐንስ ወንጌል 4:18 "አምስት ባሎች ነበሩሽ አሁን ካንቺ ጋር ያለዉም ባልሽ አይደለም..." ይላል!😂🤣

Via - simone dereje

@wegoch
@wegoch
@paappii
“አሳዳጅ በደጅ “
(በእውቀቱ ስዩም)

የጎጃሙ ገዢ ደጃዝማች ብሩ ደፋርና ሀይለኛ ተዋጊ ነበሩ፤ ተድላ ጉዋሉ የተባለ የስልጣን ተፎካካሪ ነበራቸው ፤ ከለታት አንድ ቀን፤ ተድላ ለደህንነቱ ስለ ሰጋ አባይን ተሻግሮ በሌሎች ገዥዎች ክንድ ስር ለመጠለል አሰበ፤ጥቂት ቦታዎች ያልተሳካ ጥረት ካደረገ በሁዋላ መጨረሻ ላይ ነገዎ ገመዳ የተባለ የጃርሶ(ሰላሌ) ጌታ ጥገኝነት ሊሰጠው ተስማማ፤

ደጃች ብሩ ይህንን እንደ ሰማ በንዴት ጤሰ! “ ጠላቴን ሸሽገህ ይዘሀልና መጣሁልህ “ ብሎ ለነገዎ ማስጠንቀቂያ ላከበት! ነገዎ ገመዳ ማስፈራርያው እንደደረሰው፥ ሰራዊቱን ከየቦታው ባዋጅ ጠርቶ ሰላሌ ሜዳ ላይ ጉግስ ጨዋታ አካሄደ፤ አላማው የፈረሰኞቹን ብዛት እና ንቃት ለጠላቶቹ ለማሳየት ነበር፤ በዛሬው አነጋገር ወታደራዊ ሰልፍ ማካሄዱ ነው፤ ይህንን የተመለከቱ የብሩ ሰላዮች ጉዳዩን ለጌታቸው አመለከቱ፤

ብሩ ግን ከውሳኔው ንቅንቅ አላለም፤ ወደ ሰላሌ ሄዶ የነገዎ ገመዳን ፈረሶች “ ቂጥለቂጥ እንደሚያማታ” ዛተ፤

መካሪ መኮንንኖች ግን እንዲህ አሉት’
“ ግዴለም ይቅርብን! አሳዳጅ በደጅ አንሁን! “

ዋናዋ ነጥብ “ አሳዳጅ በደጅ አንሁን “ የምትለው ምክር ናት! በሰፈራቸው፥ በሜዳቸው ብንገጥማቸው ያሸንፉናል ማለት ነው፤ (ናፖሊዮን ቦናፖርት እንዲህ የተባ መካሪ የነበረው ቢኖው ሩስያ ገብቶ አይዋረድም ነበር)

ደጃች ብሩ የመኳንንቱን ምክር ተቀብሎ ዘመቻውን አጠፈው፤

ፍቅር እስከመቃብር “ በተባለው የሀዲስ አለማየሁ ዝነኛ ልቦለድ ውስጥ ካሉት ዋና ታሪኮች አንዱ የባላገሮች አድማ ነው፤

ፊታውራሪ መሸሻ የተባሉት ጌታ የአመት በአል መዋያ የሚል አዲስ ግብር በባላገሮች ላይ ጣሉባቸው፤ ባላገሮች እምቢ አንከፍልም አሉ፤ ፊታውራሪ ጉልበታቸውን ተማምነው የሚንቁትን ያመጸ ባላገር በዘመቻ ለመቅጣት ቆረጡ፤

መካሮች ተሰበሰቡ፤ የድሮ መካር እንደ ዛሬ “ በለው ! በለው ! “ አይልም፤ ጌታው ፈረስ ከሆነ መካሩ ልጉዋም ይሆናል፤ መካሮች ተናገሩ፤

“ባላገር ሕይወቱንም ጥይቱንም ቆጥቦ ነው እሚዋጋ ፥ ጠላቱ እሱን በመፈለግና በራብና በጥም እስኪደክም ፊትለፊት ተሰልፎ አይገጥምም! ባገሩ እህል ውሃው የሱ ስለሆነ ዱር ገደሉ ተራራው ሸንተረሩ፥ ሁሉም የሱ ስለሆነ ፥ እህል ውሀውን ሸሽጎ፥ እሱ በዱር ገደሉ ተሸሽጎ ብዙ ሰው ሳይሞትበት ፥ ብዙ ጥይት እንኩዋ ሳይጠፋበት፥ ድል ያደርጋል! ያደመ ባላገርን አሸንፋለሁ ብሎ ማሰብ ውቅያኖስን ጠልቄ እጨርሳለሁ እንደማለት ነው “

ፊታውራሪ መሸሻ እንደ ደጃች ብሩ ምክር የሚሰሙ አልነበሩም፤ አሻፈረኝ ብለው ጦራቸውን አስከትለው ወደ አደሙት ባላገሮች ዘመቱ! ባላገሮች አበጀ በለው በተባለ ሽፍታ መሪነት የሚደንቅ ነገር አደረጉ፤ ፊታውራሪ መሸሻ ወደ ሰፈራቸው ዘው ብለው እንዲገቡ በሩን ከከፈቱላቸው በሁዋላ አዘናግተው ፥ ከብበው ፥ ከምክትል ሚስታቸው ጋር በተኙበት ማረኳቸው፤

የምንኖረው በቅራኔዎች በተሞላ አለም ውስጥ ነው፤ ከቅራኔዎች እሚገላግለን ምናልባት ሞት ሳይሆን አይቀርም፤ ፖለቲካ ማለት ቅራኔዎችን ከናካቴው ማስቀረት ሳይሆን ቅራኔዎችን ለከፋ ጉዳት እንዳይዳርጉ አድርጎ ማርገብ ነው፤ የሆነ አካባቢ ማህበረስብ ሲያምጽ የአመጽ ምንጭ የሆኑትን ሮሮዎች እህ ብሎ መስማት፤ ችግሮችን ማዳመጥ እና ለመፍታት መፍቀድ የመንግስት ዋና ስራ መሆን አለበት ፤ ለገበሬ ማዳበርያ በጊዜው ማቅረብ፤ ህዝቡ አስተዳዳሪዎቹን ራሱ እንዲመርጥና እንዲሽር መፍቀድ፥ በሰላም ተዘዋውሮ እንዲኖር ፥ እንዲሰራና የቤት ንብረቱ ባለቤት እንዲሆን ማገዝ፤ ወዘተረፈ...

በተረፈ በገዛ መንደሩ ላይ ወታደር አሰማርቶ ብሶቱን ለማፈን መሞከር ከታሪክም ከስነጽሁም አለመማር ነው፤ ቅራኔዎችን ማራገብ ትተን ቅራኔዎችን ማርገብ ይልመድብን!

By: bewuketu seyoum

@wegoch
@wegoch
@paappii
በጽኑ ህመም ውስጥ ከነበረች ልጃቸው ጎን ለ38 ዓመታት ያልተለዩ እናት

ኤድዋርዳ ኦባራ የተባለች የስኳር ህመምተኛ አሜሪካዊት ታዳጊ በ16 ዓመቷ በፈረንጆቹ 1969 የሳንባ ምች ሰለባ ስትሆን በሽታው ተደራራቢ እና ጽኑ ስለሆነም ቤተሰብ ወደሆስፒታል ቢወስዷት ሊሻላት አልቻለችም፡፡

በዚህ ጭንቅ ውስጥ ልጅ የእናቷን አይን እያየች ‘’እናቴ ከጎኔ አትለይ’’ ስትል ትጠይቃለች፡፡የእናት አንጀት እንስፍስፍ ነውና በፍጹም ከጎንሽ አልለይም በማለት እናት ለልጃቸው ቃል ገቡ።

ኤድዋርዳ ህመሟ ይጸናባትና በጽኑ ህመም (ኮማ) ውስጥ ሆና ቀናት፣ ሳምንታት፣ ወራት ተቆጠሩ፤ ዓመታትም አልፈው ኤድዋርዳ ከገባችበት ጽኑ ህመም ውስጥ ሳትወጣ ለ42 ዓመታት ቆይታ ህይወቷ አለፈ።

በእነዚህ ዓመታት ውስጥም እናት ልጃቸውን ከተኛችበት አልጋ ሳይርቁ የሚችሉትን ሁሉ እንክብካቤ አደረጉ። እንቅልፍ ከ90 ደቂቃ በላይ ተኝተው የማያውቁት እናት ለልጃቸው ሙዚቃ በማንጎራጎር፣ መጽሃፍት በማንበብ እና ታሪኮችን በመንገር ያሳልፉ ነበር።

ቤተሰቡን ይደጉም የነበረው አባትም ልጁን መንከባከብ ግድ ሲለው ስራውን ተወ፤ ለችግርም ተጋለጡ፤ በመጨረሻም ብዙም ሳይቆይ በልብ ህመም በሽታ ለህልፈት ተዳረገ፡፡

እናትም በ2008 ማለትም በ81 ዓመታቸው ከልጃቸው በፊት አለፉ፡፡ ከዚያ በኋላ እህቷ እየተንባከበቻት ለአራት ዓመታት ቆየች፡፡

ሆኖም በሽታውና ስቃዩ በርትቶባት መንቃት ባለመቻሏ እናቷ ከሞቱ ከአራት ዓመት በኋላ ከ42 ዓመታት የጽኑ ህመም ቆይታ በኋላ በ59 ዓመቷ ህይወቷ ሊያልፍ ችሏል፡፡

በዚህም የዓለም ጊነስ ሪከርድስ ኤድዋርዳን ራሷን ስታ (ኮማ) ውስጥ ለረጅም ጊዜ በመቆየት ሲል መዝግቤያታለሁ ብሏል ሰሞኑን፡፡

ዶ/ር ዌይን ዳየር ከማርሴለን ዳየር ጋር በመሆን “A Promise Is A Promise: Unbelievable Story of a Mother’s Unconditional Love and What It can Teach Us’’ በሚለው መጽሃፍ ውስጥ የኤድዋርዳን ታሪክ ከትቧል።

ጸሃፊው እንዳለውም ይህ ሴራ ቀመስ የሆነ ታሪክ አይደለም፤ ወይንም በፍቅር ስለከነፉ ጥንዶች የሚያትት ልብ ወለድ መጽሃፍ አይደለም፡፡ እውነተኛ ጽናትና ፍጹም ፍቅር የታየበት እናትነት ነው፡፡

በየሬድ ዘ

@wegoch
@wegoch
@paappii
"ብታዪ ጠይም ነው አይኖቹ አይኖቼ ላይ ሲያርፉ ሰውነቴ ይርዳል ከዛ ደግሞ በነዛ አለንጋ ጣቶቹ ተሣስቶ እንኳን እጁ ሰውነቴ ላይ አርፎ ከነካኝ  ከነካኝ ስልሽ ደግሞ መጨበጥንም ያካትታል ልክ ያኔ ሴት መሆኔን ሁላ እረሣለው ኧረ የምን ሴት ሰው መሆኔ ለሆኑ ሰአታት ይጠፋኛል ፣ በጣም ትኩር ብዬ ካየሁት ቡኀላ አይኖቼን ከሱ ላይ ነቅዬ ሌላ ነገር ላይ ባሣርፍም ሚታየኝ እሱ ብቻ ነው አለ አደለ ጣፋጭ ነገር ቀምሠሽ እስከሆነ ጊዜ ጣእሙ ከአፍሽ እንደማይጠፋ ሁሉ የሱ ምስልም ከአይኔ አይጠፋም..............ሚያምሩ አበቦች ፣ ሚያምሩ ቦታዎች ፣ ሚያምር ሰማይ ፣  ሚያምሩ ህፃናት ራሱ ከእሱ ሚሠሩ ነው ሚመስለኝ ምንም ሚያምር ነገር ባይ አይኔ ላይ የሚመጣው የእሱ ምስል ነው ማንም ሰው ስለወንዳወንድነት ቢያወራ የወንድ መለኪያዬ እሱ ነው ። ደረቱን መንተራስ ልክ ገነትን እንደመውረስ ያህል ህልሜ ነው ተሳስቶ እንኳን ወደኔ ዞሮ ካወራ አይኔን ከከንፈሩና ከጥርሶቹ መንቀል አልችልም ።ደሞ ልክ ሲያወራኝ ምንም አላወራም ምንም ፀጥ ፣ ፀጥ ነው ምለው ተሳስቼ ቃል ከአፌ ባወጣ እንኳን 'እሺ ' ብቻ ነው ምለው ምንም ቢለኝ እሺ ብቻ አንደበቴ ራሱ ይተሣሠራል ግን ..ግን እሱ ይሄን አያውቅም................"ብዙ በጣም ብዙ ስለሱ ጉንጮችዋ እየቀሉ እጆችዋ እየተንቀጠቀጡ  እንዴት እንወደደችው ታወራልኛለች ብዙ ስላላጣጣመችው ስላልቀመሰችው ገላ አይንዋን በእንባ ሞልታ ታወራልኛለች ።  እሱ የእስዋን ፍቅር እንደማያውቀው ሁሉ እሷም የእሷን እንጂ የኔን አታውቅም ........ከተፈጠርኩ የተሳምኩት በሱ ከንፈር እንደሆነ አታውቅም....... ጡቶቼ የተዳበሱት ልክ ተሳስተው ሲነኳት በሚነዝሯት ጣቶቹ መሆኑን አታቅም.......... የሴትነት ደሜ የፈሰሰው እግሮቼ መሀል የነበረው መጋረጃ የተገለጠው በሱ እንደሆነም አታውቅም ........ከንፈሮቹ ግንባሬ ላይ ሲያርፋ ዘውድ  እንደተሠጣት ልዕልት እንደምሆን አታውቅም....... የፍቅር ልኬ መሆኑን አታውቅም....... ደረቱ ላይ ተኝቼ ጨረቃ በፀሀይ እንደተተካች አታውቅም  እሷ ይሄንን ሁሉ አታውቅም .....የሷ ተስፋ የኔ ግን ትዝታ መሆኑን አታውቅ .......። እሱ የሌለበትን ወጣትነቴን እንጂ ለሱ የተሰዋውን ልጅነቴን፣ ወጣትነቴን እንጂ ሳፈቅረው ውስጤ እንዳረጀ አታውቅም ........አታውቅም ።

By ቃልኪዳን ሰለሞን

@wegoch
@wegoch
@paappii
ጭራሽ አልተሰማውም አይደል? ምንም ሳይመስለው ተቀበለሽ አይደል? የፍቅርን ትርጓሜ በሙሉ ዘረፍሽና ላገባሽው ሰው ኮንዶም አድርገሽ ሰጠሽው ይኸው ከዛ ጊዜ ጀምሮ የሰው ልጆች ሁሉ ኑሯችን ጥላቻ ሞታችን ጥላቻ
'ቢያንስ ራስህን ጠብቅ' 'ቢያንስ ራስህን ጠብቅ' 'ቢያንስ ራስህን ጠብቅ'  የገደል ማሚቶ ከአንጀትሽ ነጥቃ በአግራሞት ለመላው ተፈጥሮ ስታስተጋባ ድፍን ህልውና ዓይኑን ከከደነበት ገለጠና ከሰማዩ ላይ አፈጠጠብሽ እንደጸሃይ ሆኖ እንደጨረቃ ሆኖ እንደመኖርም እንዳለመኖርም ሆኖ
ግን አንቺ ይሄንን ሁሉ ተዓምር ጀምሮ ሲጨርስ መች አየሽ? ወደውስጥሽ ከፈትሽና የሴትነት ክብርሽ፤ ምሰሶው በገዛ እጅሽ ተገንድሶ ሲወድቅ ተመለከትሽ
ምናልባት በሌላ ዓለም ቋንቋ ይሄ ነገር ደስ የሚል ስም ወጥቶለት ይሆናል ከውልደቱ አስቀድሞ የተነገረለት ሞቱ ተቀድሶለት ህልውናው አስመልኮም ይሆናል።
በዚህኛው ዓለም ግን ዕለቱ ደሞዝ ከገባ አራተኛው ሃሙስ ነበር ጓዳው ባዶ ነበር ጎረቤት መቀላወጥ ሰልችቶሽ ያልበላ ሆድሽ ሲጮኽብሽ እሳት ጠቅልለሽ አጎረስሽውና ጥቅልል ብለሽ ተኛሽ አንዳንድ እሳት አለ ሲለኮስ ገላሽን እንደፈረንጅ በረዶ ቡንንን የሚያደርግ እየነፈሽ በየመጠጥ ቤቱ ስታስሺው በጽድቅሽ ተሰውረሽ ቀረሽ
ግና
ገድልሽን ሊጽፍልሽ ማን መጣ? ማን የፍቅር ሃይማኖተኛ ሊሰብክልሽ ተገኘ?
ሁሉን የሚያይ አምላክ እንኳን በባልሽ ቀንቶ ወይም አጋፔውን ስለሰረቅሽው ተቆጥቶ በነበልባሉ እንድትጋዪ ተወሽ እኔም አይቻለሁ ማዕበል የሚጋልብ የነበልባል ማዕበል በሩ ጋር እያደረሰ የሚያላትምሽ ዳርቻ ሊያወጣሽ ይልና እጀታው ላይ ስትደርሺ ጌታሽ ሰምቶ ማዕበሉን ቀጥ ሊያደርገው ይመጣል እየዘፈነ ጎረቤት እየረበሸ የወላለቀ ጥርሱን ያባበጠ ፊቱን ይዞልሽ አንጀትሽን ሊበላ
ከዛም እሱ ምን አደረገ ዝም ብሎ ተቀበለሽ ደግሞም ሌላ ቀን እንዳይረሳ ክተችልኝ አለሽ ወንድ ልጅ ያን ያህል....ያን ያህል ደደብ እንስሳ ነው አይደል
ወይስ ወይስ እኔ ስለወንድ ልጅ ምንም አላውቅም ተሳስቻለሁ
ተንገዳግዶ ወደቀ እንዴ አውሬ እንዳየ ሰው ሮጦ አመለጠሽ  የሙት መንፈስ እንዳየ ሰው ተርበተበተ ምንነትሽን አላውቅ ብሎ ተንፈራገጠ ፊቱ እንደሙሴ ከእድሜው አርባዓመት የጨመረ ፊቱ ተጨማደደ ጸጉሩ በአንድ ዕለት ሸበተ የእግዚአብሔርን ጀርባ ፊትሽ ላይ አይቶ...
አይ እንደሱ አላደረገም እንደዛም አልተሰማውም ምንም አልተሰማውም
ረስቶት በነበረ ትንሽዬ ሳንቲም ሌላ ኮንዶም ገዛና የሰጠሽውን ኮንዶም አስቀመጠው አለመግዛት ይቀል ነበር ሌላ ገላ አለመንካት ይቀል ነበር ከመጀመሪያው እንዲህ ዓይነት ፍቅር አለመቀበል መተው ይቀል ነበር ግን ቀላል መስሎት አጉል ቀላል ሸክም ተሸከመ የአዳምን ልጅ ሲረግመው በዘመንህ አቀበት እንጂ ቁልቁለት አትውደድ አለው እሱም ቀላል መስሎት ተንደረደረ ተንደረደረ መውረድ ማለቂያ ያለው መስሎት

@wegoch
@wegoch
@paappii
ወንዳላጤዎች ላይ ያለ መንፈስ
(ሚካኤል አ)
እንዲህ እንደዛሬው የትዳርን ጣፋጭ ፍሬ ከመጉረሳችን በፊት በወንደላጤነት ዘመናችን ሳለን ለትዳር የነበረን አመለካከት ይህን ይመስል ነበር ...
.
ጀማው አምስት ትዳርአጤዎችን ያቅፋል ።
ከአምስቱ ሲንግል ወንደላጤዎች ደግሞ ሁለቱ እጅግ በጣም ሰነፎች ነበርን ።
እኔና አሚር... አንድ ቤት ተጋርተን ህይወትን ስንገፋ ስንፍናችን በአይን ከመታየት ልቆ በጆሮ ይሰማ ነበር :)
ጥቂት የልግምና ባህሪያቶች ከበታች ተጠቅሰዋል
....
ስራ 1 ፦ የበሉበትን ሳህን ማጠብ
መፍትሄ ፦ ስስ ፌስታል ሳህኑ ላይ አድርጎ ከበላዩ እንጀራ በመጣል መጠቀምና ምሳው ሲያልቅ ፌስታሉን መጣል
ስራ 2 ፦ ካልሲ ማጠብ
(እዚህ ጋር በተለይ የአሚር ካልሲን መኮቸር እንጠቅሳለን ።
'መኮቸርን ' የወንደላጤዎች መዛግብት ፦ ካልሲ ውሀ ከማጣቱ የተነሳ እንደ ኮብልስቶን መድረቅ የሚል ፍቺ አለው ።
እንደውም አንድ ጊዜ ተጣልተን ካልሲውን ወርውሮብኝ ግንባሬን ስንት ቀን እንዳመመኝ ሳልጠቅስ ማለፍ አልፈልግም ።
መፍትሄ ፦ አዲስ ካልሲ መግዛት እና ኮቾሮውን ካልሲ መጣል
ስራ 3 ፦ መጋረጃ ማጠብ
መፍትሄ ፦ ክፍፍል
የመጋረጃውን ከወገብ በላይ አሚር ያጥባል
የመጋረጃውን የታችኛውን ክፍል ካልተጠላን እኔ አጥበዋለሁ ። በሁኔታዎች ከተደባበርን የታችኛውን ጨርቅ አላጥብም ብዬ ሙዱን እከንተዋለሁ
ስራ 4 ፦ ድስት ማጠብ
መፍትሄ ፦ እንግዳ ሲመጣ የድስቱን የላይኛው ገፅ በደንብ አድርጎ ማፅዳት (ውስጡን ለቄስ)
እናቴ ለእረፍት አዲስ አበባ ዘለቀችና ቤታችን ጎራ አለች ። እኔና አሚር መስሪያ ቤት ሄደን ነበር ።
ማሚ የቤታችንን ንፅህና አይታ ተደነቀች።
የወለሉ ፅዳትና የመጋረጃው መፍካት እጅግ ውብ ነበር ።(የመጋረጃው የታችኛው ክፍልን
የአልጋችን ጠርዝ በመሸፈን ያገለግለናል )
እናም ይሄ ጉብዝናችን ያስደመማት እናቴ የምንሰራውን ወጥ አይታ ለመመዘን ድስቱን ከፈተችው ።
ድስቱ ነጭ ፀጉር አውጥቶ አርጅቷል ። ብዙ ጊዜ ሽበት ስለማያጣው እኔና አሚር ለድስቱ ስም አውጥተንለታል
ችሮታው ከልካይ :)
ማሚ ለዛን ቀን በስልክ እንዴት እንዳንባረቀችብኝ ሳስበው ዛሬም ድረስ ስንፍናዬን እረግመዋለሁ ።
...
በመንፈቅ ልዩነት ከአምስቱ አባላት ሁለቱ ላይ ውሳኔ ለማሳላፍ ፓርላማው የአስቸኳይ ጊዜ ስብሰባ ጠራ ።
የስብሰባው አላማ ሁለቱ ወጣቶች የትልቅ ሰው ስራ የመስራት ሙከራ በማድረጋቸው እነሱን ከጓደኝነት መሰረዝን ይመለከታል ።
ሙሉቀንና ዮሀናን ያስባረራቸው ተግባሮች ከበታች ተጠቅሰዋል ።
ጥፋት 1 ፦ ሙሉቀን እንደ ትልቅ ሰው መሬት ለመግዛት ከደላላ ጋር ሲወያይ በመሰማቱ
(ሰው እንዴት የክለብ መጨፈሪያ ጠርሮብን መሬት ይገዛል? ፤ የሚል ብሶትም አለበት)
ጥፋት 2 ፦ ዮሀና ለአንዲት ለወደዳት ፍቅረኛው ሽማግሌ ለመላክ ማሰቡ ሲደረስበት
(ዮሀና እንደሚለው ሁኔታው በድንገት የተፈጠረ ፅንስን ለመታደግ ፍቅረኛውን በወግ ማዕረግ ለማግባት የተወሰነ አማራጭ የሌለው ግዴታ ነበር )
ቢሆንም ዮሀና ኮንዶምን በጥንቃቄ ካለመገልገል አልፎ ማስረገዙ ሳያንስ በዛ ላይ የማግባት ሙከራን ማድረጉ በወንደላጤው ኮሚቴ በቸልታ የሚታይ ነገር አልነበረም።
ሁለቱም ታገዱ ።
ከእግዱ ወዲያ ሶስት ወንደላጤዎች አሸሸ ገዳሜያችንን ቀጠልን ።
ይሄ ጉዞዋችን ዓመት ሲቆይ ግን እኔ በተለይ ሁኔታዎችን ማነፃፀር ጀመርኩ።
ሁለቱ የተለዩ ጓዶች በትዳር በረከት ወዛቸው ችርፍፍ ብሎ በሀብትና ልጅ ተባረኩ።
ሶስቱ ወመኔዎች ዛሬም ድረስ ዩንቨርስቲ ያለን ይመስል ነበር። ወዝ አልባ አመዳሞች ነን።
ደግሞ ከባለትዳሮች የተሻለ ገንዘብም አልነበረንም ።
ያን ጊዜ እኔ አንዲት ሸጋ ወድጄ ቀስ ብዬ ከጀማው ተሸበለልኩ ።
ፓርላማው ለአስቸኳይ ውሳኔ ሁለቱ አባላቱን ጠራ :)

By Mikael aschenaki

@wegoch
@wegoch
@paappii
<<አልነግረውም >>

ናርዶስ ጓደኛዬ ናት ለምን በተደጋጋሚ ስልክሽን ታጠፊያለሽ ፣ትደበቻለሽ ሙድሽ ፍላክቹዬት ያደርጋል ?

እ ?

<<በፍቅር ሂወቴ ደስተኛ አይደለሁም>>

ታድያ ለምን ችግሩን ለመፍታት አትሞክሪም ፣ለምን ቅር ያለሽን ጉዳይ ለፍቅረኛሽ አትነግሪውም ።

<<አ .ል .ነ .ግ. ረ. ው. ም !!>>

ለምን ???

<<አልነግረውም ኣ ! >>

በንግግር እመኚ እንደ ዘመናዊ ሰው በጠረቤዛ ዙርያ ማውራት ልመጂ ። ልብሽ ውስጥ የተሰማሽን ቅሬታ ካልተወያየሽበት ተጎጂዋ አንቺ ነሽ ?

<<አልነግረው...ም ! >>

መውደዱን እንዲነግረኝ ነው የምነግረው?!
በዙርያው ላሉ ሴቶች ፍቅረኛ እንዳለው እንዲናገር ነው የምነግረው ?!
የጓደኛዬ ፍቅረኛ ቆንጆ ቦርሳ ስጦታ ገዛላት ስለው ለኔም እጮኛዬ ስጦታ በገዛልኝ እያልኩ እንደቀናው ልንገረው ?!

ስለ ነገ ስለ ትዳር ሳወራው ወሬ ሲቀይርብኝ አትቀይርብኝ ወሬ ብዬ ነው የምነግረው ?!

ቤተሰቦቼ እንዳገባ ይወተውቱኛል አንተ ደሞ የጋብቻ ሃሳቡም ውልብም አይልብህም ብዬ ነው የምነግረው?!
ወሲብ ሲያምር ብቻ እንደምትወደኝ እንደናፈከኝ አታስመስል ብዬ ነው የምነግረው ።

አንተ ጋ ስመጣ ፀጉሬን ቦርጬን ፣ዳልዬን መቀመጫዬ ለማየት መስታወት ጋ ተገትሬ አማረብኝ አላማረብኝ ብዬ ነው እምመጣው

ዋው! ፓ ! አምሮብሻል አንዳንዴ እኮ በለኝ ነው ብዬ የምነግረው ?!

ፔሬድ ሲያነጫንጨኝ እና ሲያጠወልገኝ ፣ቅናት ሲያስዶክከኝ ተረዳኝ የኔ መሆንክን አስዳስሰኝ ብዬ ነው የምነግረው ??

አልነግረውም !!

ድሮ የምሆንለት ፣የምነግረውን ፣ የማደረግለትን ችላ ማለቴን ሁኔታዬ ገብቶት ብዙ ሳይረፍድ ከጠየቀኝ ካሳሰበው ብቻ ነው የምነግረው

አድራጎቱ እንደማያፈቅረኝ ምስክር ነው ። ልብ ላይ የሌለ ፍቅር በውይይት የሚመጣ አይመስለኝም !!

ሰው አስፈልጎት ስትሰጠው፣ እገዛ ፈልጎ ስታግዘው፣ ጠይቆ ስትመልስለት በተሻለ ሁኔታ አሰጣጥህን እውቅና ይሰጠዋል ፣በተሻለ ሁኔታ ያገዝከው እገዛህን ይረዳል ፣በተለየ መንገድ የነገርከው ይገበዋል ።

ካለዝያ ዝም ብዬ እርባን ለሌለው ነገር አልደሰኩርም !!>>

ታድያ ለምን አትተይውም ? !

<<እየተውኩት ነው እኮ አብሮ ሆኖ መተውን
መለማመድ እና እርም ማውጣት የመሰለ ቆንጆ ነገር የለም ።

ልክ ስተወው ይመጣል ያኔ እንደተላለፍን የጨከነ ፊቴን አሳይቼ ልመናውን እራመዳለሁ ።
ስተወው ባይመጣም አይገርመኝም አንዳንድ ሰነፍ ብዙ ከዘገየ በሆላ ነው አድራጎቱ የሚገለጥለት !!

የሆነው ሆኖ

ያኔ ከሱ የያዘኝ ሱስ ሙሉ ለሙሉ ስለሚራገፍ ደስታ ከኔ ጋ ይሆናል !!>>

በAdhanom Mitiku

@wegoch
@wegoch
@paappii
ከምታነብ ሴት ጋር አትከራከር!

ካደኩበት ሀይቅ ዳር አካባቢ ከሁሉ የተለዩ የሚመስሉኝ አንድ አሳ አጥማጅ ባልና እጅግ በጣም አንባቢ የሆነች ሚስቱን አውቅ ነበር፡፡ አንድ ቀን ታዲያ አሳ አጥማጁ ባል ደክሞት ለማረፍ ወደ ቤቱ መጣና ከሶፋው ላይ ወድቆ እያንኮራፋ እንቅልፉን ይለጥጠው ጀመር፡፡ ሚስት ማንበብ አልቻለችም ስለዚህ ለየት ያለ ነገር ማድረግ አሰበችና መጽሃፏን ይዛ ከቤት ወጣች፡፡
የባሏን ጀልባ ወደ አንድ ጸጥተኛ የሀይቁ ክፍል ቀዘፈችና በስሱ በሚዳብሰው ነፋሻማ አየር እየተዝናናች መጽሃፏን ገልጣ ማንበቧን ቀጠለች፡፡
ከጥቂት ቆይታዎች በኋላ በድንገት የባህሩ ላይ ጠባቂዎች ጀልባ ከች አለ፡፡ ኮስታራው ፖሊስም ማይክራፎኑን በእጁ አንከርፍፎ ይለፈልፍ ጀመር
‹‹ምን እያደረጉ ነው እመቤቴ!››
‹‹መጽሃፍ እያነበብኩ!›› (ምን እንደማደርግ አይታየውም እንዴ! በማለት እየተገረመች!)
‹‹ እመቤቴ በተከለከለው የሀይቁን ክፍል ላይ ስለሚገኙ በፍጥነት አካባቢውን ይልቀቁ!››
‹‹ምን አጠፋሁ ጌታው!›› አለች ደርባባዋ እመቤት
‹‹በዚህኛው የሀይቁ ክፍል አሳ ማጥመድ አይፈቀድም እመቤት!››
‹‹እሱን አውቃለሁ ጌታው! ሆኖም እንደሚያዩኝ አሳ እያጠመድሁ ሳይሆን መጽሃፍ እያነበብኩ ነው!››
ፖሊሱ ፈገግ ብሎ ‹‹እንደማየው ጀልባዎ በአሳ ማጥመጃ መሳሪያዎች ተሞልቷል፤ ስለዚህ እኛ በሌለንበት በማንኛዋም ደቂቃ መረብዎን ጥለው እንደሚያጠምዱ እገምታለሁ፡፡ ስለዚህ አሁኑኑ አካባቢውን ጥለው የማይሔዱ ከሆነ ባልተፈቀደ ቦታ አሳ በማጥመድ በሚለው አንቀጽ መሰረት በቁጥጥር ስር የማውሎት መሆኑን ይገንዘቡ!››
ሴትየዋም ፈገግ ብላ አየችውና ‹‹ጌታው እንዲያ የሚያደርጉ ከሆነ እኔም ጾታዊ ትንኮሳና አስገድዶ መድፈር በሚለው አንቀጽ መሰረት የምከስዎ መሆኑን ይወቁ!›› አለች ኮምጨጭ ብላ
‹‹አይቀልዱ እመቤቴ ይህ የስራ ጉዳይ ነው! እንኳን ልተነኩስዎና ልደፍርዎ ቀርቶ አጠገብዎ እንኳን እንዳልደርስኩ ያውቃሉ!››
‹‹ እውነት ነው አውቃለሁ፡፡ ሆኖም ያንን ለማድረጊያ (መድፈሪያና መተንኮሻ ይሆን!) የሚያገለግል ማንኛውንም አይነት መሳሪያ እንደያዙና ጭር ሲልልዎ በማንኛዋም ደቂቃ ያን ሊያደርጉ እንደሚችሉ እገምታለሁ!›› አለች ደፋሯ እመቤት
ፖሊሱም ጥቂት አሰብ አደረገና ‹‹ መልካም ቀን ይሁንልዎ እመቤቴ! ይጠንቀቁ!›› የጀልባውን ሞተር ኮርኩሮ ጉዞውን ቀጠለ፡፡
ከአንባቢ ሴት ጋር አትከራከር!
ብልህና አስተዋይ ስለምትሆን ትቀጣሃለች!

(አብይ ተስፋዬ ከ7 አመት በፊት እንደተረጎመው)

@wegoch
@wegoch
@paappii
«… አምስት፣ ስድስት፣ ሰባት …»

አንድ ወቅት ላይ ለተወሰኑ ቀናት … ወደኾነ የሀገራችን ክፍል የመሄድ ዕድል አገኘኹ።

ከመሄዴ በፊት …ስለቦታው አንድ ኹለት ያኽል ደስ የሚሉ ዘፈኖች ሰምቼ ነበርና …ቦታውን ለማየት በጣም ጓጓኹ።

እንዲኽ የተዘፈነለት፣ ግጥምና ዜማ የተሠራለት ቦታ እንዴት ያለ ቢኾን ነው የሚልን ሀሳብ እያሰብኹ፣ ወደ መንገድ ዳር ወጥቼ ባጃጅ ተሳፈርኩ።

«እስቲ እንትን የሚባለው ቦታ አድርሰኝ»

«እሺ ግባ»

የተወሰኑ ደቂቃዎች እንደነዳ የመንገዱን ጥግ ይዞ ቆመ።

«ምነው?»

«ደረስንኮ»

«እንትን የሚባለው ቦታ ይኼ ነው እንዴ?» ማመን አልቻልኹም…

«አዎ»

ወርጄ ሳይ ወዲያና ወዲኽ ተራርቀው አምስት ቤቶች፣ ስድስት ዛፎችና፣ ሰባት ሰዎች ብቻ ይታዪኛል። … የቀረው ቁጥቋጦ የወረረው በረሃና የተራቆተ ተራራ ነው። ክው ነው ያልኹት። በጉጉት የተሞላው ልቤ በኩርፊያ ኩምሽሽ አለ።

«በቃ ይቺው ናት?» አልኹት ባለማመን

«ምን ፈልገኽ ነበር?» አለኝ እየሳቀ …


አንዳንድ ደስታዎች እንዲኽ አይደሉም ወይ? አብዛኛው መሻትና ፍላጎታችን ጉም እንደመጨበጥ አይደለም ወይ? አንዳንድ ነገሮች በጥበብ ስም፣ በዕውቀት ስም፣ በፋሽን ስም፣ በሥልጣኔ ስም፣ በወጣትነት ስም፣ በሀገር ስም የተጋነኑ ናቸው። እዚኽ ካልደረስክ «ፋራ» የሚያስብሉ … ስንደርስ ግን ኹሉም በጋራ መስማማት እውነት የተደረጉ ውሸቶች መኾናቸውን እንረዳለን። ሀቀኞች ሮጠው ወደመጡበት ይመለሳሉ። ፈሪዎች ግን ራሳቸውን እየዋሹ መኖር ይቀጥላሉ።

አንዳንድ ሰዎች ሲታዪ ረዥም ይመስሉና ደርሳችኹ አጠገባቸው ስትቆሙ አያጥሩባችኹም? ስብዕናቸውም እንደዚያው የኾኑ አሉ። ስታውቋቸው ወርደው ተዋርደው ቅልል የሚሉ እንደገለባ … ምነው ባላውቃቸው ኖሮ የሚያስብሉ አሉ።

አንዳንዴ የኾነን ነገር ደርሶ ከማየት በጉጉት መኖር የተሻለ ነው። አስቡት ዕድሜ ልካችኹን አንድን ነገር ስታሳድዱት ከርማችኹ የደረሳችኹበት ቀን ምንም ሲኾን? … አምስት ምንም፣ ስድስት ከንቱ፣ ሰባት ባዶ … ሲኾን

እና ጥቂት የጥርጣሬ ሥፍራ መተው አሪፍ ነው መሰለኝ።

—————


By 𝙷𝙴𝚗𝚘𝚌𝚔 𝙱. 𝙻𝚎𝚖𝚖𝚊

@wegoch
@wegoch
@paappii
የእንጀራ ዋጋ

የለውጡ ሰሞን: የአንድ እንጀራ ዋጋ : ከአምስት ብር ተነስቶ የመሸጫ ዋጋው በፍጥነት ስምንት ብር ሲገባ ለውጥ ነው እና ብዙም ሳይከፋን በዋጋ ሳንማረር እንገዛ ነበር። እንጀራውም - ወፍራም እና የጤፍ መሆኑ ብዙም የማያከራክር ነበር።

ከሁለት አመት በፊት : የእንጀራ ዋጋ አሁንም አሻቀበ እና አስራ አምስት ብር ሲደርስ : እንጀራው ራሱ ዋጋውን ሰምቶ ሳይሆን አይቀርም ክው ያለ መሰለ ። ይህ እንጀራ ደረቅ ያለ እና ቀለሙም ጥውልግ ያለ ቢሆንም : እንጀራ በመሆኑ ፤የጤፍ እንጀራነቱ ቢያጠራጥረንም : ስንቱን ጠርጥረን እንዝለቅ ብለን ገዛን በላን።

የዛሬ ዓመት ከመንፈቅ አካባቢ ደግሞ : አስራ ሰባት ብር ገባ።' ንጣቱ የሩዝ ይመስላል' እያልን በላን።

የዛሬ ዓመት ደግሞ: ሃያ ሁለትብር ሆነ :-' ሃያ ሁለት' የሰፈር ስም እንጂ የእንጀራ ዋጋ ሆኖ አያውቅም' እያልን :- መከፋታችንን በቀልድ አዋዛን እንጂ አልተከራከርንም ። :'የዩክሬን እና የሩሲያ ጦርነት ከዓድዓ ጤፍ ጋ ምን ያገናኘዋል ? እንዳንል ማን ይሰማናል? ሲገናኝ ውሎ ሲገናኝ ቢያድር 'እንጀራ''ም. መኖር' ም' በአንድነት መወደድ ነበረባቸው?

አሁን በሁለትሺ አስራ ስድስት መባቻ ላይ : የአንድ እንጀራ ዋጋ : ሃያ አራት ብር የገባ ሲሆን : ይሄ እንጀራ ንፁህ ጤፍ መሆኑ ከማጠራጠሩ በላይ :የሚገርመው ነገር : በእዚህ ውድ በሆነ ዋጋ የተገዛው የእንጀራ ዓይኖች ውስጥ የምናየው :እንጀራውን ሳይሆን ትሪውን ሆኗል።

የእንጀራዎቹ ዓይኖች መሳሳታቸው በዚህ ከቀጠለ :ያ ያሳደገን እንጀራ : ዓይኖቹ ቀዳዳ በቀዳዳ ሆነውበት: ባለቀለበቶች እንጀራ እንዳይሆን እየሰጋሁለት ነው።

ሁሉ ነገር በዚሁ ከተባባሰ: ወደፊት ጤፍ ዋጋው እጅግ ከመወደዱ የተነሳ አንድ ኩንታል ጤፍ የገዛ ሰው ጤፉን እራሱ ቆሞ አስፈጭቶ::ወደ ቤቱ ለመውሰድ በአካባቢ ፖሊሶች ጥበቃ እና እጀባ እንዲደረግለት: ከወሳኝ ኩነት ጤፉን በግል ንብረትነት አስመዝግቦ: ከወረዳው የድጋፍ ደብዳቤ ሊያፅፍ ይችላል ።

ቡሽራ
ከሠንጋ ተራ

@wegoch
@wegoch
@paappii
የመንገደኚት መጣጥፍ(ፍናማርያም)

“I know why a caged bird sings”
ህይወት ውሰጥ ተነግሮን ከምንረዳው ይልቅ ኖረናቸው የሰረፁን ነገሮች ይበረታሉ፡፡ አንዳንዴ ሰዎችን ከመረዳት ርቀን የምንገኘው፣ህመማቸው የማይሰማን በራሳችን የህይወት መስመር ውስጥ ከህመም ጋር ስላልተዋወቅን ነው፡፡ አሊያም እንደዚህ መኖር(ጠብቆ) አለበት ብለን ካስቀመጥነው የራሳችን ልክነትን ካዘነፉ ከመረዳት እንርቃለን፡፡
እግሬ ሽሬን ከረገጠበት ቀን አንስቶ በተለይም አያቴን ይዤ የስነ-አዕምሮ ህክምና ከመጣንበት ቀን ጀምሮ በሀሣቤ የምጥለው የማነሳው፣ስለህይወት ለመረዳት ከራሴ ጋር የምነዛነዘው በዝቷል፡፡ በስንት ስንክሣሮች በተከበበች ዓለም ጋር እየተላተሙ፣ጭነቷን መሸከም ከከበዳቸው ሰዎች፣ጥሰው ወጥተው አዕምሮና ሀሳባቸው ታፍኖ ከሰመጡ፣ ወደ ልክነት ለመውጣትና ለመተንፈስ ከሚነገዳገዱና ከሚፍጨረጨሩ ሰዎች ጋር ለአያቴ ስል መሰንበት ኑባሬዬ ከሆነ በኋላ ህመም ሰርፆኛል፤ህመም ገብቶኛል፡፡ ታዲያ ግቢውን ከረገጥኩበት የመጀመሪያዋ ሰዓት አንስቶ ልጅ እያለን ሰፈራችን ውስጥ ስለሚታወቁት አዕምሮአቸውን የታመሙ ሰዎች ታሪክ ማውጠንጠን ጀምሬ ነበር፡፡

# አሻግሬ እብዱና ውሸት ታንቃ ትሙት
አሻግሬ ድሮ ድሮ እጅግ ያተረፈ ነጋዴ ነበር ይላሉ የኋላ የኋላ ከሚያምናቸው የሽርክ ጓደኞቹ ተከድቶ ከከሰረ አንስቶ በሰፈራችን መንገድ ላይ  “ውሸት ታንቃ ትሙት” ብሎ በመጮህ ሌላ አሻግሬን ይዞ ተከሰተ፡፡ አምኗቸው የከዱትን፣እውነቱን በሀሰት ገልብጠው የጣሉትን በግሉ ሸንጎ ለመፋረድ ሲል፣ በእርግጥም ለዚህ ሰው እምነትን ማጉደል፣ሀሰትን መንገር ህመም ሆኖበታል ውሸት ታንቃ ትሙትለት፡፡

# እማማ ኡኡ
የሰፈራችን ትላልቅ ሰዎች የሊበን እናት ይሏቸው ነበር እኛ ደግሞ እማማ ኡኡ፡፡ የሊበን እናት እማማ ኡኡ የተባሉት ኡኡ ብሎ የሚጮህ ሰው ከሰሙ ድንጋይ ይዘው በማሯሯጣቸው ነው፡፡ እማማ ያቺን ቃል አምርረው የጠሏት የአንድ ልጃቸውን ሊበን መርዶ ከሰሙት ቀን ጀምሮ ነው፣ምናልባት ሲያረዷቸው የሰሟት የመጀመሪያ ቃል ሆና ኡኡ ሲባል የልጃቸውን አለመመለስ እየደጋገመች ስለምትነግራቸው ነው፡፡
አንዳንዴ ሰዎች ሊሉን የፈለጉትን ነገር ሊነግሩን ባሰቡ ሰዓት አንረዳቸውም፤እንተላለፋለን፡፡ ስንኖር፣፣ስናጣ፣ስንወድቅና ስንሰበር ህመሙን እናውቀዋለን፡፡ አያቴ ከመጣሁ ጀምሮ ብዙ ቃላት አላወራችም ብቻ በየመሀሉ ደረቷን እየደቃች ከምሕላ ጸሎቶች አንዱን ትደጋግማለች፡፡

"አንቲ ማርያም አክሱም ጽላተ ሙሴ
ተዓረቅና እንዶ መሬት ከይመሴ
ሕራይ በልናዶ መሬት ከይመሴ"

ከሁለት ዓመታት በኋላ ሽሬ ስመለስ ለወትሮ በሰዎች የሚከበበው የአያቴ መሪጌታ ወልዳይ ቤት ባዶ ነበር፣አክስቴ አብረኸት የለችም፣ዘርዓ ዳዊትና ክብሮም የሉም፣አባ ክብረቅዱሳንና እማሆይ ሣህለማርያም የሉም፣ ምንምና ማንም የለም ምስኪኗ አያቴ ዕንበባ(አደዬ) ብቻ፣ ቤት ማለት ጣራና ግድግዳ ብቻ ነው እንዴ አይመስለኝም አያቱን ከተኛችበት አልጋ ላይ በራስጌዋ በኩል ተቀምጬ ስለቤተሰባችን ማሰብ ጀመርኩ፡፡እውነት ግን እነዚህን ሰዎች ሀቅ አልነበራቸውም ጦርነትን ይፈልጉ ነበር ?? አላውቅም!!!

#መሪጌታ ወልዳይ
አያቴ መሪጌታ ወልዳይ የአቋቋም መምህር ሲሆን እሱ ለቤተሰቡ ባወጣው ቀጭን ትዕዛዝ መሰረት ከልጅ እስከ የልጅልጅ የአብነት ትምህርት የመማር ግዴታ ነበረብን፡፡ ለእኔም የመጀመሪያ የግዕዝ ቃላቶችን በቃሌ ያስጠናኝ አያቴ ነበር፣ አቡነ ሳልል የሰዓታት መግቢያ ላይ ያለችዋን ነበር የህይወት ስንቅ ናት እያለ ያሸመደደኝ፣ በእግዚአብሔር ታምኛለሁ፣ብወድቅም በእርሱ እነሳለሁ የምትለዋን

"ሠለስተ አስማተ ነሢእየ እትመረጎዝ
እመኒ ወደቁ እትነሣእ
ወእመኒ ሖርኩ ውስተ ጽልመት
እግዚአብሔር ያበርህ ሊተ"

ታዲያ ይሄ ሰው ከዜማው ና ከአቋቋሙ፣ ከመቋሚያና ጽናጽሉ ውጪ ጠመንጃ የጨበጡ እጆች እንዳልነበሩት  ተረድተውለት ይሆን ? አላውቅም፡፡

#አክስቴ አብረኸት
ለሁላችን አምባሻና ህብስት እየጋገረች ከሻይ ጋር የምትሰጠን፣በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ሄዶ በቀረው ባሏ ሁሌ የምታለቅስ ናት ፡፡ምናልባት ለእርሷስ ባሏን የነጠቃትን ጦርነት አምርራ ትጠላ እንደነበር ያውቁላት ይሆን? እንጃ

#ዘርዓዳዊት
የአክስቴ አብረኸት የመጀመሪያ ልጅ ነው ወንድሜ ዘርዓ፣ ልጅ እያለሁ አያቴ ወንጌለ ዮሐንስን እንዲያስቀጽለኝ ነግረውት፣በምገድፋቸው ቃላት እየተናደደ፣ወይቤላና ወይቤሎ ማለት ከብዶኝ በ አይደለም ቨ በይ እያለ እስከ ምዕራፍ አራት እየተነዛነዝን ገብተን ወአውስአ ኢየሱስ ወይቤላ እንዳልኩ  መሳሳቴ ገብቶኝ የተለመደው ቁጣውን ስጠብቅ እያነበብሽ ያለውን ተረድተሸዋል ግን ብሎኝ ከተቀመጠበት በሀሳብ ሲጓዝ እኔም ምን ይሆን ብዬ መሳቱን ትቼ ወንጌለ ዮሐንስ ምዕራፍ አራትን ከላይ እስከታች ስደጋግም፣ አይ ዘርዓ … እሺ የሱንስ በዛች ምዕራፍ የተፃፈውን ሣምራዊ አይሁዳዊ የማያስብል አንድ የሆነ የዘላላም መጠጥን ሊጠጣ የወደደ፣እንኳን ሰው ማጥፋት ይቅርና ቃላትና ዜማ ስሰብር የሚቆጣ ወንድሜ እንደነበር ገብቷቸው ይሆን? እንጃ አላውቅም፡፡

# አባ ክብረቅዱሳን
በአያቴ ደብር አብረው የሚያገለግሉ መነኩሴናየቅዳሴ መምህር ናቸው፣አባ ክብረ ቅዱሳን(የኔታዬ)፡፡ እንደሌሎቹ የቤተሰባችን ሴቶች የቅኔ ትምህርትን ትቼ ለነፍሴ የቀረበውን ዜማ ለመቀፀል በማሰቤ ነበር አያቴ በደስታ ከእርሳቸው ስር እንድማር ሲወስደኝ በቅርበት ያወኳቸው፡፡ በደብረአባይናዋልድባ ናፍቆታቸው እኛም የማናቀውን ደብር አስናፍቀውናል፣ስለተቀደሰው የምንኩስና ህይወት ሲነግሩን ዜማውና ካስባሉን በኋላ በኋላ በሚነግሩን የነፍስ ትምህርቶች ስንት የጨለማ ቀናቶቼን ወጥቼባቸዋለሁ፡፡እና የኔታዬ ከቅዳሴ ጸሎት ሀበነ ንኅበር(አንድ መሆንን ስጠን) የምትለዋን እንደሚወዷት በቅዳሴያቸው ለአንድነት እንጂ ለጠብ ዜማ እንደሌላቸው ተሰምቶላቸው ይሆን? አላውቅም፡፡

# እማሆይ ሣህለማርያም
የአያቴ ዕንበባ ታናሽ እህት ነበሩ እማሆይ፣ቁጣቸውና የአቡነ አረጋዊ ዝክራቸው አይረሳኝም፣ አይ እማሆይ ሁሉም ነገር መሰተር እና ትክክል መሆን አለበት የሚሏት ነገር፣ ምስለ ሥዕላቱን የሚቀቡት ሽቶ ሲያልቅባቸው የሚያዝኑት ሀዘን አንድ የሆነ ሰው ሲገዛላቸው እየፈነደቁ ቀድመው ሥዕለ ማርያምን የሚቀቧት ነገር፣ ጠንቅቀው የተማሩ ቢሆኑም የሚደጋግሟት አንድ ጸሎታቸው የሆነው ይትቀደስ ስምከ፣የሆነ ቀን የአቡነ አረጋዊ ዝክር ደርሶባቸው እንዳስለመዱት እኔና ረዊና የበሶ ዱቄት ስለአቡነአረጋዊ እያልን ጠይቀን ከበረከት እንድንካፈል ለመጀመሪያ ጊዜ ሲልኩን እንዴት በየሰው ቤት እንሄዳለን ብለን ስንነጫነጭ በቁጣ እንኳን እናንተ ይቺ እናት ብለው ሥዕለማርያማቸውን እያመለከቱ በየሰው ቤት ሀሜት ሳትፈራ እንጀራ ለምናለች ብለው ሲያበሩን ከንቱነታችንን አምነን በሶ ሰብስበን ስንመጣ የመረቁን ምርቃትና ለቁጣቸው የነገሩን የአንድ ሊቅ ቅኔ

"ማርያም ድንግል ዘኢትፈርሀ ሐሜተ
ፍርፈራተ ሕብስተ ሰአለት በፍና እንዘ ትፀውር ሕብስተ"

እማሆይስ ታዲያ ከዝክራቸውና በደስታ ቅዱሳኖቻቸውን ከሚቀቡት ሽቶ በቀር ሌላ ሀቅ እንዳልነበራቸው ታውቆላቸው ይሆን እንጃ አላውቅም፡፡

# ክብሮም
አንዳንዴ ሰዎች ሰርግና ሞት አንድ ነው ሲሉ ፍቅርም አንድ እንደሆነ ማን በነገራቸው እላለሁ፡፡ ክብሮም የመጀመሪያም የመጨረሻም ፍቅሬ ነበር ፡፡ ለእርሱ ደብዳቤ መፃፍ ሰበብ ትግርኛ መጻፍ የተለማመድኩበት፣ከደብዳቤ ፍቅር ተጣብቄ የቀረሁበት ክብሮም፣ አዲስአበባ

ይቀጥላል

በ@markrylos

@wegoch
@wegoch
@paappii
ክፍል ሁለት

ስመለስ ሌላ ነገር እንደሌለ ሁሉ ክረምት እስኪደርስ ስሙን ዘርዓ እንዳስጠናኝ ወንጌለ ዮሐንስ የምደጋግምለት ክብሮም፣አያቶቼ ጋር አስሬ በመደወልና ዘርዓን ፈልጌው ነው እያልኩ ጥያቄዬን ትቼ ስለእርሱ ቀን ውሎ ወንድሜን  የምነዘንዝለት ክብሮም፡፡ የሆነ ጊዜ ከስድስተኛው ጽጌ ማኅሌት አዳር በኋላ የትላልቆቹን አቋቋምና እሱ ከበሮውን ይዞ እንዴት ሲያጅባቸው እንደነበር ከዜማው ጋር ለእኔና ዘርዓ እያሳየ ተመየጢ ተመየጢ ወይትጎንድኢ ብሎ ሳናስበው ተንሸራቶ ሲወድቅ እኔና ዘርዓ ልባችን እስኪፈርስ የሳቅነው ተመልሶ እግሩን እያመላከተ ስለተፈጠረው የቴክኒክ ስህተት ይቅርታ ብሎ በቀደመው ሀይሉ ተመየጢ ብሎ ሲጀምር ዘርዓ ተቀላቅሎት ተመየጢ እያልን ያመሸንበት፡፡ ክብሮም ናተይ፤እሱንስ ተመየጢ(ተመለሺ) እያለ እንዳትዘገይ የሚለማመናት፣ማኅሌቷን ቀጥ ብሎ የሚቆምላት ፣ልጅነቱን ለውዳሴዋ የሰጠላት ርኅርኂት እመቤት እንዳለችው ይረዱ ይሆን  ከወንዞች ማዶ ይሄንን እያሰበች የምትፅፍ፣ወደፊት ስለእርሱና እሷ ስታስብ የነበረ፣ክረምት አልፎ ልታየው የምትናፍቅ አንዲት ሴት እንዳለችው ይገባቸው ይሆን እንጃ
ስለሁሉም አሰብኩ አብርሃና ክራሩ፣ንግስቲና የኪሮስ አለማየሁ (አንዕጓይ ፍስስ) ዘፈኖች፣ እነቅሳነትን፣ረዊናን ፣ አነ ደሊናና ሸዊትን፣ የኖሩባቸው ቤቶች የተመላለሱባቸው የሽሬ ጎዳናዎች የዋህነታቸውና ሀቃቸው ይነግሩላቸው ይሆን? አላውቅም፣አላውቅም፣አላውቅም
Mahmoud darwish እንዳለ “I don’t know who sold our homeland, but I saw who paid  the price” የከፈለውን አውቃለሁ፣ለምን ሰዎች ሰላምን አብዝተው እንደሚፈልጓት አውቃለሁ፣ለምን ስለሁሉም ባሰብኩ ጊዜ እንደ ሚፋጅ እሳት ውሃ በጉንጮቼ ላይ እንደሚወርድ አውቃለሁ፡፡ አያቴም ለምን ያንን ዜማ እንደምትደጋግመው አሁን አውቃለሁ:: ጦርነት እንደ ሙሽራ ለሁሉም በየተራ ይድረሰው ተብሎ የሚዜምለት አይደለም፣ይበቃል፡፡
ጉንጮቼን እጆች ሲዳብሷቸው ከሄድኩበት ብንን አልኩ አያቴ ነበረች ጓለይ ጓለይ እያለች አብራ እያነባች የምጠርግልኝ ቀስ ብላ እጆቼን ይዛ “ማርያም ታውቃለች “ አለችኝ ፣እንባ ባረገዙ አይኖቼ እያየኋት እጆቿን አጥብቄ አንገቴን እየነቀነኩ አዎ ማርያም ታውቃለች አልኳት፡፡ እጆቿን ወደደረቷ መልሳ እየደቃች በድጋሚ ማዜም ጀመረች
አንቲ ማርያም አክሱም ጽላተ ሙሴ
ተዓረቅና እንዶ መሬት ከይመሴ
ሕራይ በልናዶ መሬት ከይመሴ

ዶክተር ማያ አንጄሎ ለግልታሪኳና ለጥቁሮች ጭቆና ለማመልከት “I know why a caged bird sings”
  እንዳለች ሁሉ እኔም የታሰረች፣የተዘጋባት ወፍ ለምን እንደምትዘምር አውቃለሁ፡፡ አያቴን ተቀላቅዬ ማዜም ጀመርኩ፡፡ አንቺ የሙሴ ጽላቱ የምትባይ ማርያም፣መሬት ሳይመሽ ታረቂን፣ እሺ በይን፣ተለመኚን፡፡
            ተጻፈ በፍናማርያም
          ነሐሴ 16 2015 ዓም
by @markrylos

@wegoch
@wegoch
@paappii
"በፈጠረህ ይዤሀለሁ ትልቁ...በፈጠረህ....የምትወዳት ከሆነ 'በ ዳኋት' አትበለኝ በቃ።"
"እኔ እኮ እንዲህ አይነት ነገር መስማት ትወዳለህ ብዬ ነው ስከንፍ ወዳንተ የመጣሁት።"
"እውነት ነው እወዳለሁ። የምትወዳት ከሆነ ግን 'ተኛን' ወይ 'ወሲብ ፈፀምን' በለኝ። ያው ያደግነው ከሬዲዮ ስር አይደል?! ንግግርህ አዕምሮዬ ላይ ቁልጭ ያለ ምስል መፍጠሩ አይቀርም። ያን ቃል በተጠቀምክ ቁጥር ሲገባ ና ሲወጣ ሁሉ ይታዬኛል..."

"ህክምና ያስፈልግሀል አንተ!"

"ተው አልኩህ...አልሰማ አልከኝ...ምን ልበልህ?...በዛ ላይ ብዙዬ እኮ የሁለታችንም አብሮአደግ ነች። ለሌላ ሴት የምትጠቀመውን ቃል ለሷም ስትጠቀመው ደስ አይልም።"
"ይቅርታ ግን እንደዚህ ተደስቼ ስለማላውቅ እኮ ነው። እንዲያውም ይሔንን ደስታ በግዕዝኛ ነበር... 'ፍስሀ...ሀሴት...ስርፀት' ምናምን በሚሉ ቃላቶች እየታጀቡ መግለፅ!"
"ኧረ ተረጋጋ"
"የምሬን ነው። ታውቃለሀ ከሷ በፊት ሴክስ እንደ ሴክስ አዝናንቶኝ እንደማያውቅ?"

"ምን ማለት ነው እሱ ደሞ?"

"በቃ መዋሰቡ አልነበረም የደስታዬ ምንጭ! ምኗን ስነካት ምን እንደምትሆን እያዬሁ በመገረም ብቻ ነበር ሌቱን የምገፋው። ልክ ቲቪ የመጣልን ሰሞን ሪሞቱን አንስተን አንዱን አንዱን እየነካካን ምኑ ምን እንደሆነ ለመረዳት ስንሞክር እንደነበረው ማለት ነው!"
"እእእ ገባኝ። ህእ!...ባይዘዌ...የመጀመሪያ ቀን ቀዩን ተጭነህ ስዊችድ ኦፍ ሲሆንብህ ደንግጠህ ከአክስታችን ቤት ያደርከውን ዛሬም ድረስ ባስታወስኩት ቁጥር ነው የምስቀው!"
"ሂሂ እጄ የማያርፈውን?...በዛ ሳምንት ብቻ አራቴ ነው ያበላሸሁት...ቡኃላ እንደዛ ሊሰለቸኝ ያን ያህል ሙጥኝ ማለቴ ይገርመኛል!"

"ለምንድን ነው ግን እንደዛ የሆንከው?"

"ምን የሆንኩት?"
"ማለቴ..ሁሌም የሆነን ነገር ስታገኝ ለመጎርጎር የምትጣደፈው? ሬዲዮኗንም እንዲሁ ነካክተህ ነካክተህ ሲበቃህ ጣልካት። ቲቪውንም እንደዛው። በቃ አንድን ነገር የምትወደው እስክታውቀው ብቻ ነዋ?!"
"ሂሂሂ ...... ብዙዬንም ነካክተህ ትጥላታለህ እያልከኝ ነዋ አንተ ሴታሴት?"

"ጂሰስ!!...የመስማት ነው የመረዳት ችግር ያለብህ?"
"ትንሹዬ...ካወቅኩት ቡኃላ ያልተውኩት አንድ አንተ ብቻ ነህ። 'ንዲህ አይነት ድብብቆሽ እኔ ላይ ደስ አይልም።"
"ስለምን መደባበቅ ነው የምታወራው?"

"ጠይቀሀት ነበራ ብዙዬን?"

"እንዴ? በጣም ድሮ እኮ ነው። የታችኛው ፀጉር ራሱ..."
"ጭገር?!"
"ስነስርዓት ይኑርህ እስኪ..."
"እሽ ምን እንበለው?"
"በቃ ተግባባን አይደል? የግድ እስከ አያቱ ድረስ መጠራት አለበት?"
"ቀጥል እሺ!"
"ብቻ እሱን ነገር ራሱ ገና አላበቀልኩም ነበር! እሺ ብትለኝ ምን ላደርጋት አስቤ እንደነበር እንኳን አላውቅም። ካጠገቤ ስላገኘኋት ብቻ ነው የጠዬቅኳት።"
"እንግዲያውስ ይቁረጥልህ ከእንግዲህ ስለሷ እንዳታስብ። አንዴ ተባድ ተናል እኛ!"
"አባቴ ይሙት ካሁን ቡኃላ ይሔን ቃል ከተጠቀምከው...."
"በድ ቻታለሁ.....ብ ድትድት አድርጌያታለሁ ምን ታመጣለህ እስኪ?!"

"አይይይይይይ እ!....ጌታን የምታሳዝን ሰው ነህ!!"

"እንዴዴ?....ምን እየሆንክ ነው?...ኧረ...ኧረ ውሀ መቋጠር ምናምን!! ልታለቅስ ነው? እና መጀመሪያውኑ እንደምትወዳት በግልፅ አትናገርም ነበር እንዴ?"
"አልወዳትም። አንተን ይንሳኝ አልወዳትም.....ኧህህህህህ!....ሁለት በጣም የምትቀርቡኝን ሰዎች አ'ምሮዬ ውስጥ እንደዛ ላስባችሁ ስለማልፈልግ ብቻ ነው...ok?! እንደ አባዬ እና እማዬ እናንተም አድርጋችሁት የማታውቁ እንዲመስለኝ ብቻ ነው ማሰብ የምፈልገው። የምለው ገብቶሀላ?"
"ማለት?! አባዬ እና እማዬም እኮ ይባ..!"
"እንዳትጨርሰው!"
"እሺ በቃ ይቅርታ!....ሆሆሆ!...ቆይ አንተ ግን እስከመቼ ነው እንደዚህ ከተግባሩ በላይ ቃሉን እየፈራህ የምትኖረው?"

"የሌለ ችግር ፈጥረህ አታውራ!"

"ኧረ ተው? መናገር የፈለግከውን ሁሉ እየተናገርኩልህ፤ መብላት የፈለግከውን 'አምሮኛል' እያልኩልህ ማደግህን ረሳኸው?...መልስልኝ እስኪ?!...ቆይ የምታስበውን ነገር 'እንዲህ አስቤያለሁ' ብሎ መናገር ለምንድን ነው ወንጀል የሚመስልህ? በተግባር እንዳንተ ክፉ የለም። አሁን ራሱ እድሉን ብታገኝ ብዙዬን ከኔ ነጥቀህ ታገባታለህ። ለአፍህ ግን የማይከብደው ነገር የለም።"

"ሁሉም እንዳንተ አይደለም ትልቁ። እንዲያውም እኔ ባንተ ቦታ ብሆንና የፍቅር ጥያቄ ጠይቀሀት እንደምታውቅ ብሰማ ኑሮ ከአጠገቧ ድርሽ አልልም ነበር። እንኳን ልጠይቃት!!"

"አታካብድ...ከበዳ...አይይይይ እ!....ግብረ ስጋ ግኑኝነት ከፈፀምን ቡኃላ ነው የነገረችኝ!"

"ሲጀመር እኔ እንደምወዳ...ማነው እንደጠየቅኳት የማያውቅ አንድም የሰፈር ሰው የለም።"
"አንድ እኔ አለሁ አልኩህ እንግዲህ..."
"ለማመን ይከብደኛል እሱን!"
"ያንተ ማመን እና አለማመን ምንም ትርጉም የለውም ትንሹ። ህይወት ለማመን በሚከብዱ ገጠመኞች የተሞላች ነች። እኔ ግን ህሊናዬ ንፁህ ነው።"
"ህሊናቸው ንፁህ በሆኑ እና ባልሆኑ ሰዎች መሀል ያለው ልዩነት ምን እንደሆነ ታውቃለህ?"
"ምን?"
"ንፁህ የሆኑት ሁሌም እንደቆሸሹ ነው የሚያስቡት። የቆሸሹት ደግሞ ፃድቅ እንደሆኑ!"

"ብ ዳታም ፓስተር! ከነ እውቀትህ ገደል ግባ እሺ። አሁንስ ይሔ ሾካካነትህ በጣም ነው ምርር ያለኝ!! እንዲያውም ለአንድ ለሁለት ሳምንት ላገኝህ አልፈልግም። ቻው!"

"ግዴለም አታስብ!!...ለሁለት ሳምንት ብቻ ሳይሆን ለሁለት አመት ያህል አታገኘኝም። ክፍለሀገር ስራ ልጀምር ነው።"
"ማ...ማለት...ክፍለሀገር የት?"
"ጂማ ዩንቨርስቲ!"
"አንተተተተተ ውሻ!!! አውቀሀለሁ ውሻ ነህ ማሪያምን!!"

"ምንድን ነው የሚያስጮህህ? እስኪ ተረጋጋና አውራኝ?"
"እጄን ምታ? እስኪ 'አባቴ ይሙት...ብዙዬ ጅማ ስራ መጀመሯን አላውቅም' በለኝ!!"
"በእየሱስ ስም?! የምርህን ነው?..."

"ሌላ ምንም አትበል። አላውቅም ነበር ብለህ አንዴ ብቻ ማልልኝ። ከዛ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከህይወትህ ወጥቼ እሔድልሀለሁ።"

"ለኔም እኮ ማወራረድ ከበደኝ የሰማሁትን ነገር!"
"ማልልኝ አልኩህ!!".
"እሺ አትጩህ! ይሔው በአባቴም በእናቴም ስም እምላለሁ አላውቅም ነበር።.....እህህህህህ...ምንድን ነው እንደዚህ የምታፈጥብኝ? ጌታን አላውቅም አልኩህ......እንዴዴዴዴ ኧረ አይንህን ንቀል ሰውዬ!!.......እንደዛ ከተሰማህ ወይ ስራው ያምልጠኝ በቃ...መቅረትም እኮ እችላለሁ..."

"አያይ...አያስፈልግም እሱማ።....እንደው ነገሩን ተራ መገጣጠም ነው ብዬ ለማመን ትንሽ ስለከበደኝ ብቻ ነው!!"

"ያንተ ማመንና አለማመን ምን ትርጉም አለው ትልቁ? ህይወት እንደሁ ለማመን በሚከብዱ ገጠመኞች የተሞላች ነች። እኔ ግን ህሊናዬ ንፁህ ነው።"

"👀"

(ርዕስ:- ቃዬል እና ቃዬል)

@wegoch
@wegoch
@paappii

By mickel Azmeraw
ኤየር ባስ 380 የተባለው ግዙፍ አይሮፕላን በመቶዎች የሚቆጠር ተሳፋሪዎችን ጭኖ በ800 ኪሎ ሜትር በሰአት ፍጥነት 30,000 ጫማ ከፍታ ላይ እየበረረ ነው

ከየት መጣ በሚያስብል ፍጥነት ደግሞ የተዋጊ ጄት ከጎኑ ተከሰተ - ከትልቁ አውሮፕላን ትይዩ ሆኖ በመገናኛ ሬዲዮ የትልቁን አይሮፕላን ፓይለት አገኘው

"ኤየር ባስ 380 መንዳት ድብርትን የሚያጭር ይመስለኛል"

የትልቁ አውሮፕላን ፓይለት አልመለሰለትም

"እስኪ አሁን የማደርገውን አዝናኝ ትርኢት ተመልከት” ብሎ የሚያበረውን ጄት በጀርባው በመገልበጥ በብርሃን ፍጥነት ወደ ሰማይ ሽቅብ ወጥቶ እየተገለባበጠ ወደ ምድር ተምዘግዝጎ በድጋሚ በቄንጠኛ ሁኔታ ፍጥነቱን ጨምሮ ወደ ላይ ተምዘግዝጎ ከትልቁ አውሮፕላን ጎን ቆመ

"እንዴት ነበር ትርኢቱ?" በድጋሚ በሬድዮ ጠየቀው

"በጣም አስደናቂ ነበር! እስኪ የእኔን ደግሞ ላሳይህ" ብሎት ሬድዮኑን ዘጋው

የጄቱ አብራሪ ቢጠብቅ ቢጠብቅ ምንም የለም

ከ15 ደቂቃ በኃላ የትልቁ አውሮፕላን አብራሪ ተመልሶ መጥቶ "እንዴት አየኸው?" ብሎ ጠየቀው

"ምኑን? ምን አደረግክ?" የጄቱ አብራሪ ጠየቀው

"ከወንበሬ ተነስቼ እግሮቼን አፍታትቼ ወደ አውሮፕላኑ የኃላ ክፍል ሄጄ ተሳፋሪዎቹን ሰላም ብዬ ሽንት ቤት ተጠቀምኩኝ:: በዚያውም ደግሞ ቡና እና የቸኮሌት ኬክ ይዤ ተመለስኩኝ" 🤷🏽‍♂️🤷🏽‍♂️

👇🏾

ወጣት እያለህ ፍጥነት: ስሜት: ለመታየት መቅበዝበዝ እና ተቀባይነት ለማግኘት መጋጋጥ ያለ ነው

እድሜህ ሲገፋ እና ህይወት ሲገባህ ግን ምቾት: ሰላም እና እርግት ስክን ማለት ትልቁ መገለጫህ ሊሆን ይገባል

@wegoch
@wegoch
@paappii

By zemelak endris
የነዳጅ ነገር

ወገን ሰሞኑን መገናኛ አካባቢ ሄዳችዃል? ድልድዩ ስር ክራር ይዘው የሚለምኑ ባለተሰጥኦ ለማኞች አልበዙባችሁም? የኑሮ ውድነቱና የነዳጅ ዋጋው በዚሁ ከቀጠለ ዋሽንትና ከበሮ ይዘን የምንቀላቀላቸው ብዙ ወገኖች እንኖራለንና የሙዚቃ መሳሪያ ገዝቶ መዘጋጀቱ ይበጃል።

እኛ ስንቀላቀላቸው ልመናው በሙሉ ባንድ ይታጀባል። ቢያንስ ቢያንስ ምፅዋት ሰጪ "እስኪ ያሁኗን ልመና ድምፅህን ወረድ አደርገህ ድገምልኝ፤ በሙዚቃ መሳሪያ ብቻ ለምነኝ" እያለ ዘና ብሎ መመፅወት አለበት። 32 ቁጥር አውቶቡስን የሚጠብቁ የኮተቤ ነዋሪዎችም ባሷ እስክትመጣ ነገር እየበሉ በባንድ የታጀበውን ልመና እየሰሙ ቢቆዩ ይመርጣሉ።

I came from the future ብዬ አልሰክሳችሁም ከላይ የፃፍኩት ቀልድ አይደለም በቅርቡ በሰፊው የምንመለከተውና ብዙሃኑ ህዝብ ደግሞ የተመለከተው እውነታ ነው። የነገውን የኢትዮጵያ ገበያ ለመገመት Time traveller መሆን አይጠበቅንም። ከባዱ ነገር ኑሮ ከበደኝ እንኳን ብትል የሚሰማህ የለም። ከወራት በፊት መንግስት ለነዳጅ እሰጥ የነበረው ድጎማ ካዝናዬን ስለጎዳው አቁሜያለሁ ሲል ኢኮኖሚስቱ ሙሼ ሰሙ መንግስት ድጎማ ማድረግ ከበደኝ ካለ ህዝብስ በምን አቅሙ ሊሸከመው ይችላል ብሎ ጠይቆ ነበር። መልስ የሰጠው የለም። መንግስት ዝርዝር ሳይዝ ነው የሚንቀሳቀሰው መሰለኝ ብዙ ጊዜ መልስ አይሰጥም።

ወዳጆች ከዚህ ቀደም እንዳልኳቹህ ኑሮ ውድነቱ በዚህ ስለሚቀጥል ግሮሰሪ ገብቶ ከለር ፕሪንት አላቹህ ብሎ የሚጠይቅ ተማሪ፣ ወደገበያ ሲሄድ ወታደራዊ አሸኛኘት የሚደረግለት ሸማች፣ ሽንኩርት ገዝቶ ወደቤቱ ሲገባ የታየ አባወራ "የሽንኩርቱ ጌታ" ተብሎ ሲዘፈንለት መስማታችን አይቀርም። እኔ ለቅድመ ዝግጅት 1 ኪሎ ሩዝ ምን ያህል ፍሬ እንዳለው ጎግልን መረጃ እየጠየቅኩ ነው። ከዛ ቆጥረህ ትቅላለህ፤ 12 ፍሬ ለቁርስ 12 ፍሬ ለምሳ ለመተኛት እንኳን መመገብ አያስፈልግም።

@wegoch
@wegoch
@paappii

By yihune Ephrem
ደባሌ ነች። የስራ ባልደረባዬም ነች። አብረን ነው የምንውለው። አብረን ነው የምናመሸው። የምንለያዬው....ለመኝታ ብቻ ነው። "አትሰለችህም ወይ?" ይለኛል ጓደኛዬ። ስንተኛም የማንለያይበትን መንገድ ለማግኘት እየጣርኩ እንደሆነ አያውቅም።

እንደምወዳት እኮ ልነግራት ነበር። ግን ድንገት ስለምትፈልገው የወንድ አይነት ስታብራራ ሰምቼ ጉሮሮዬ ተዘጋብኝ። ፀጥ አልኩ። ውሸት ምን ያደርጋል? መስፈርቷ ውስጥ በከፊል እንኳን የለሁም። ድሮ ድሮ ኮራጅ ተማሪዎች ጎበዝ ተማሪ ሲያጡ ከሰነፉ ላይ ይኮርጁ ነበር...እሱ "True" ሲል እነሱ "False" እያሉ...እሷም መስፈርቷን ያወጣችው እንዲህ እያደረገች ሳይሆን አይቀርም....እኔ ስስ ስሆንባት "ደንዳና"...እኔ ፀይም ስሆንባት "ደማቅ ቀይ" እያለች!

አንዳንዴ እንደዚህ ነው...የማይፈልጉት ነገር መሆንህን የሚሳውቁህ ስለሚፈልጉት ነገር እያወሩ ነው።

ስለዚህ በዝምታ መውደዴን ቀጠልኩ። መውደዴን ያልተውኩት ሞኝ ስለሆንኩ አይደለም። መውደዴን ያልተውኩት እሷ ያስቀመጠችውን መስፈርት የሚያሟላ አንድም ወንድ እንደማታገኝ ስለማውቅ ነው።
አውቃለሁ አለም እንደኔ ባሉ መካከለኛ ሰወች የተሞላች እንደሆነች። አውቃለሁ ህይወት ኮርኩማ ኮርኩማ ስታንዳርዷን እንደምታወርድባት። ከኔ የሚጠበቀው ያ ቀን እስኪመጣ ድረስ ከስሯ ሳልጠፋ መቆዬት ብቻ ነው።

የሴት ጓደኛም የላትም። ረጅም ስለሆነች ከነሱ ጋ ስትቆም ቀውላላ ያስመስሏታል። ስለዚህ እኔ እኩያዋ ጋ መሔድን ትመርጣለች። "እንደዚህ ረጅም ሴት ወይ ከአማልክቱ ወገን ነች...ወይ በስህተት ሴት ሁና የተፈጠረች ወንድ ነች!" ይላል ጓደኛዬ። እስማማለሁ በአባባሉ። በስህተት ሴት ሁና የተፈጠረች ወንድ እንዳልሆነችም አውቃለሁ።

ማታ ማታ የሆነ ቲቪ ሸው እናያለን። ትንሽ እንዳዬን እናቋርጠውና "Grey Anatomy" የሚለውን ተከታታይ ድራማ ለአስረኛ ጊዜ እንጀምረዋለን። ወይ "Friends" እናያለን። ጓደኛማቾቹ ሲሳሳሙ ዞር ብዬ አያታለሁ። እሷ ግን አታዬኝም። መልሼ እዞራለሁ።

ታዲያ ሁኔታችንን ሁሉ የሚገርመው የስራ ባልደረባችን "እንደኛ ባለትዳር ለመባል እኮ በሶስት ወር አንዴ ሴክስ ማድረግ ነው የቀራችሁ" እያለ ሙድ ይይዛል። ቀልዱ ቀልድ ነው እኔ ግን.... "ሜሪ" ብዬ ለሌላ ነገር በጠራኋት ቁጥር...በዛው "ሜሪ ሚ?" ብዬ ልንበረከክላት የሚያምረኝ ቀን ጥቂት አይደለም።

እሱም ነው ትልቁ ፍርሀቴ። የሆነ ቀን ኩሽና ውስጥ፣ ወይ ፊልም ስናይ፣ ወይ የሆነ ሒሳብ ሳስረዳት፣ ወይ ስለምናዬው ድራማ ስታብራራልኝ...ድንገት ደፍሬ እስማታለሁ። ከዛ ትክ ብላ ታዬኝና ተነስታ ወደ ከፍሏ ትገባለች። ዘግታኝ ልትውል ነው ብዬ ስጨናነቅ ተመልሶ በሯ ይከፈታል። ከዛ እንደገና ልትስመኝ ነው ብዬ መጓጓት ስጀምር በአንደኛው እጇ ሻንጣዋንም ይዛ እየወጣች ነው። በስማም!!.....ላብ በላብ ሁኜ ከእንቅልፌ እነሳለሁ። "ህልም እልም" "ህልም እልም" ብዬ አማትቤ እተኛለሁ።

ተይዣለሁ። ተይዣለሁ በጣም። በርግጥ እስከ ምን ድረስ እንደተያዝኩ ያወቅኩት አንድ ቀን አሟት ቀርታ ቢሮ ብቻዬን የሔድኩ ዕለት ነው።  "አንቺ ስትሔጅ ስንቶች ተጋለጡ" የሚለው የአብርሽ ግጥም እንዳዲስ ትርጉም ሲሰጠኝ ዋለ!
ከቤት እስከ ቢሮው ያለው መንገድ ለካስ እንደዚህ ሩቅ ነበር?! ምን ብርታት ሰጥቶን ነው በ'ግራችን ስንመላለስበት የከረምነው?
ለካስ ስራዬን እጠላዋለሁ!! አለቃዬስ ምንድን ነው እንዲህ የሚያስጮኸው? ቢሯችን ለምንድን ነው ሆስፒታል ሆስፒታል የሚሸተው? ሰራተኛው ሁሉ ለምንድን ነው የማያስቅ ቀልድ የሚቀልደው?
ከተማው ላይስ መቼ ነው ሰው እንደዚህ የበዛው? ሮፍናንን ማነው ዘፋኝ ያደረገው? ፀሀዩዋ እንዴት እንዴት ነው የሚሰራራት?

የምወደው ነገር ሁሉ አስጠላኝ። የምጠላውን ሁሉ ማጥፋት አማረኝ። ይሔን ሁሉ ሁኘ ምርር ብሎኝ ሰዓቱን ሳዬው ደግሞ ገና አራት ተኩል እያለ ነው። በርግጥ ሀያ ደቃቃ ይቀረዋል ለተኩልም። ራሴን አመመኝ። ስራውን ትቼው ወደቤት ተመለስኩ።

በሩን ከፍቼ ስገባ...!

ሜሮን በድንጋጤ ከላዩዋ ላይ ያለውን ወንድ ገፍትራው ተነስታ ቆመች። አይኔን ማዬት ከብዷት ተሸማቅቃ አንገቷን ሰበረች። እኔም የሰማኒያ ሚስቴ ስትማግጥብኝ የያዝኳት ያህል ግርጥት ብዬ ዝም አልኩ። ከተወሰነ መፋጠጥ ቡኃላ ነበር ሚስቴ አለመሆኗ ትዝ ያለኝ። ብንን ብዬ ይቅርታ ጠይቄያቸው ተመልሼ ልወጣ ስል ሩጣ እጄን ያዘችው።  "ምነው?" አልኩ ድምፄ እንዳይንቀጠቀጥ እየተጠነቀቅኩ።

"ጊዜ ማሳለፊያ መስሎህ እንዳትቀዬመኝ" ብላ ጀመረች!...እጆቿን እያፍተለተለች...."ያው ነገሩ ትንሽ ሲሪዬስ እስኪሆን ደብቄህ ነው እንጂ...ስመኘው የኖርኩትን ልጅ'ኮ  አግኝቸዋለሁ!" አለችና በፈገግታ አዬችኝ። ከልቧ ደስ እንዳላት ታስታውቃለች። ሁኔታዋም ለሚወዳት ልጅ ሳይሆን ለታላቅ ወንድሟ እንደምትነግር...ሀፍረት እና ኩራት የተቀላቀለበት ነው። አይኖቿ የደስታ እንባ አቅርረዋል። እርግጠኛ ሆናለች። የኔም አይኖች ረጠቡ።
አንዳንዴ ደግሞ እንደዚህ ይሆናል....የምስራቻቸው ውስጥ መርዶህን ትሰማለህ!

By michel Azmeraw

@wegoch
@wegoch
@paappii
“እኔኮ አፌ እንጂ ልቤ ንጹሕ ነው…” የምንል ብዙዎች ነን —ጀብድ እንደኾነ ነገር፤ መርዘኛ ምላስ ከክፉ ልብ ይቀልል ይመስል ነገር።

“እኔ ሲፈጥረኝም መደባበቅ አላውቅም፣ ሲፈጥረኝም ግልጽ ግልጹን ነው የማወራው” እያልን ሰው የምናቆስል አለን። ግልጽነትን መረን ከመኾን ለመለየት ዕድሜና ብስለት ያልሰጠን —ስናሳዝን።

ሰው ግን በልቡ ከሞላው በቀር በአፉ ሊወጣ የሚችል ምንም ነገር የለም —ሐቅ ነው። እርግጥ ነው አንዳንዴ ሰው በብስጭት ከአፉ ያልተገቡ ቃላት ሊወጡ ይችላሉ። ደጋግሞ ደጋግሞ የታቀደ በሚመስል መልኩ ሰውን የሚሰብር ሰው ግን “እኔም ሰው ነኝ” ብሎ ሊመሳሰል አይችልም።

“ይቅርታ” ማጣፊያው ሲያጥረን የምንመዘው ራስን የመከላከያ መሣሪያ አይደለም። “ይቅርታ” ማለት ድጋሚ ያንን ጥፋት ላለማድረግ መወሰን እንጂ፤ “የቀደመ ጥፋቴን እርሱልኝ” የሚል የብልጣ ብልጦች ይግባኝ ሊኾን አይገባም። ብዙዎች ግን ያለ ምንም ማመዛዘን ከአፋቸው አጥንትን የሚሰብር ቃል እያወጡ ደግመው ደግመው “ይቅርታ” በማለት የቃሉን ጉልበት ይፈትናሉ።

ይቅርታ” ማለት ግን “ቀጣይ በደንብ አስቤ አወራለኹ” ማለት ጭምር ነው። ይቅርታ ማለት ግን “ቀጣይ በቂ መረጃ ሳይኖረኝ አላወራም” ማለት ጭምር ነው። ይቅርታ ማለት ግን “የማወራው ነገር የሚያመጣውን ቅጣትና ወቀሳ ሙሉ ለሙሉ እቀበላለኹ” ማለት ነው። ካልኾነ ግን “ይቅርታ” የፍቅር መግለጫ፣ የሕግ ፍጻሜ የኾነውን ያሕል … የመሠሪዎች መሹለኪያ የማርያም መንገድ ኾኖ ይቀጥላል።
————————————

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Henock Bekele
ፍቅር ይሞታል
*

ፍቅር እንደ ሰው ልጅ ይጸነሳል፣ ይወለዳል፣ ያድጋል፣ ይሞታል። በህይወት ውስጥ ይኼን ዑደት ከውኖት ያልፋል። ምናልባት መች እንደሚሞት ማን እንደሚገድለው ይሆናል ማይታወቀው። ከመሞት እጣ ፈንታው ግን አፈንግጦ ነጻ መውጣት አይችልም።

ልብ የፍቅርን ዘር በጉያው ሸጉጦ ሊያጸድቅ ይነሳል። ዘር ሁሉ ማረፊያው የተለያየ ስፍራ እንደሆነ ሁሉ ፍቅርን የተሸከመ የልብ ማህጸንም መክተሚያው ይለያያል።

በመንገድ ላይ የተበተነ ዘር አፈር እንኳ በቅጡ ሳይለብስ በእንጭጩ በወፍ አፍ እድገቱን እንደሚቀጭ ሁሉ፤ አንዳንድ ፍቅርም ገና እንዳልተወለደ ጽንስ በልብ ማህጸን ውስጥ ሳያቆጠቁጥ አፈር ድሜ ይበላል። ሳይዙት ይተናል። ሳይጨብጡት ይበተናል።

አንዳንድ ፍቅር የታጨው ሳይጀምር ለማለቅ ነው። ሳይወለድ እንደመውረድ። ልብህ ለሽንፈት ዘነፍ ማለት በጀመረበት ወቅት ብዙ ምክንያቶች የእድገት ጸር ወፍ ሁነው ይለቃቅሙታል። ድንገት አይተኃት ልብህ እየተንፈራገጠች ወደ መውደድ ባህር ልትደፍቅህ ስታብሰለስል...

ምታፈቅረው ሰው፣ ባል፣ ትዳር፣ ልጆች እንዳሏት ትሰማና አንጀትህ ቁርጥ ሊል ይችላል።
ነገ ከነገ ወዲያ ሀገር ለቃ ልትከንፍ ክንፏን እያርገበገበች ያለች፤ አሊያም አንዳች እርጉም ህመም ከጥቂት ቀናት በኋላ ይዟት ወደ ሞት ደጃፍ ሊያሸከትፍ መሆኑን አውቀህ ... ላለመጎዳት፣ በተስፋ ጉም ላለመጨበጥ፣ በማጣት ሰደድ ላለመንደድ በእንጭጩ ልትደፈጥጠው ትችላለህ።

ጽንሰቱን አጽድቆ ለውልደት የሚንደረደር ፍቅርም በጭንጫ መሀል እንደተዘራ ዘር ጥልቅ መሬት በማጣቱ ምክንያት ... ፀሐይ እሳት ሚተፋ ጥርሷን አግጥጣ የወጣች ጊዜ እንደደረቀ ሁሉ፤ በቅጡ ሳያቆጠቁጥም ሆነ ለማደግ በሚፍጨረጨርበት ወቅት ... ልበ መሬቱ ጥልቅ መሆን አቅቶት ስረ እምነቱ ስር መስደድ ሲሳነው ... እንደ ቅናት እና ጥርጣሬ ያሉ አጠውላጊ ፀሐዮች በእሳት አናትህን እየደቁ የፍቅርህን እድገት ገትተው ለሞት ይዳርጉታል።

"ከብዙ ሴቶች ጋር ያለህ ቅርበት ደስ አይልም" በሚል ... ርካሽ ቅናት በተጠናወተው መንፈስ ልታለመልም ያቀድከውን ፍቅር አድርቃ ልትርቅህ ትንደረደራለች። እንደ ሂሳብ ድምር አንተን አንድ አለኝ ብላ ጥግ ላይ አኑራህ፤ "የተሻለ ሰው በህይወቴ ሊመጣ ይችል ይሆናል" በሚል ኦና የተስፋ ጥርጣሬ እየወላወለች መሀል ቤት አንሳፋህ ግራ ስታጋባህ ከርማ ... አደገ እያልክ አንተ ደስታህን ስትምግ፤ ድንገት ተፈትልካ... ከስርህ አፈንግጣ ስርህን አድርቃ ትሸሻለች።

እሾህ መሀል ወድቆ እድገቱን እያናረ ... ራሱን ለትልቅ ምርት ሊያጭ ሲያኮበኩብ በእሾኹ ታንቆ እንደሚከስም ዘር፤ አንዳንድ ፍቅሮችም በጥሩ ሁኔታ እያደጉ ሂደው ... ጥሩ መንገድ አበጅተው ተጉዘው ... ለፍሬ ሊበቁ፣ ሊደነቁ፣ ሊመሰገኑ ነው ሲባል፤ ድምጹን አጥፍቶ በውስጣቸው ሲያደባ የነበረ ያልታወቀ አመለ እሾህ ደርሶ ወጥቶ እንቅ አድርጎ እዛው አኮስምኖ ለሞት አፍ ይገብራቸዋል።

ስንት አመት ተጠናንተህ ኑረህ... ለሰርግ ስትዘገጃጅ፤ ራስክን ለትዳር ተቋም ስታደረጅ፤ ከዓመታት በፊት የሰራኸው ስህተት ልጅ ሆኖ መጥቶ እንደ እሾህ አንቆ የፍቅርህን ግንድ አጥመልምሎ ይደፋዋል።

ከዛሬ ነገ ቀለበት ልሰርላት እያልክ ያደገ ፍቅርህን እስከ እርጅና ለማጽናት እየታተርክ ባለህበት ወቅት፤ ሀብት የሚያንገበግባቸው ቤተሰቦቿ... እልፍ አስገዳጅ ምክንያቶችን ደርድረው ውዷን ፍቅርህን እንደ ባሪያ ለራሳቸው ጥቅም ይሸጡብህና ተስፋ ላይ ያነጽከውን ቤት ብን አድርገው ከነፍቅርህ ያቀጭጩታል።

ለትዳር በቅተህ እስከ እርጅና ዘመንህ... መልካም መሬትን ተጣብቆ ለፍሬ እንደበቃ ዘር ፍቅርህን አጽድቀህ ጣፋጭ ፍሬዎቹን እየተመገብክ ይሆናል። ግን ህይወት ፍቅርን ለዘላለም የሚያኖር የዋህ ልብ አትሻምና ውድህን በሞት ትነጥቅኃለች። አንተ መውደድህን በልብህ አጽድቀህ እጅ ባለመስጠት ልትሟገታት ትፍጨረጨራለህ፤ እልዃ እስከ ጥግ ነውና አንተን ከነፍቅርህ ትደመስሳለች። ትገድላለች!

ፍቅር መሞቻው... እንደ ሰው ልጅ የመሞቻ ቀን አይታወቅም፤ ግን ከመሞት አያመልጥም። ሲጸነስ፣ በጽንስ ውስጥ፣ እንደተወለደ፣ ተወልዶ ጥቂት ኖሮ፣ እያደገ፣ በደንብ አድጎ፣ ጎርምሶ፣ ጎልምሶ፣ ለእርጅና በቅቶ ... ብቻ የሆነ የኑረት ኡደት ውስጥ ለሞት ተላልፎ ይሰጣል። ፍቅርም እንደ ሰው ልጅ ይሞታል። በሰው ልጅ ልብ ውስጥ ፍጹም ሆኖ ለመኖር እየታገለም ቢሆን... አብሮ ካኗሪው ጋር በአፈር ይቀበራል።

#ኤልዳን
@eldan29

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሌባዋ ሴት ነበረች!
(አሌክስ አብርሃም)

ስልክ ምናምን እያልን ስለመሰረቅ ስናወራ ወዳጀ ዴቭ ትዝ አለኝ!" መገናኛ የገጠመውን እየነገረኝ ነው ...

" አንተ ስልክ ትላለህ እንዴ! የኔን ልንገርሃ ...መገናኛ ልክ ታክሲ ውስጥ ልገባ ስል የሆነ ፈጣን እጅ ኪሴ ውስጥ ዘው አለና ወዲያው ወጣ ፤ ዞር ስል ብዙ ሰው አለ ፣የማን እጅ እንደሆነ አላወኩም ...ግን ሳስበው ሳስበው ሴት ሳትሆን አትቀርም..."

"እንዴ ! ካላየኻት ሴት መሆኗን እንዴት አወክ?"
"የእጇ ልስላሴ ....በስማም! እንደዛ አይነት ፈጣንና ለስላሳ እጅ አጋጥሞኝ አያውቅም"
"እጁ ገብቶ የወጣው ኪስህ ውስጥ፤ ልስላሴውን እንዴት ...'ሴንስ' አደረከው ?"
"ባክህ ኪሴ ቀዳዳ ነበር ፣ በዛ ላይ ፖንት አለበስኩም! አፈፍእኮነው ያደረገችኝ እንትኔን ፣ማርያምን! ከመደንገጤ የተነሳ እጀን ልኬ ሁሉ መኖሩን ቸክ አደረኩ፤ መገናኛ ምኑ ይታመናል?!ሆሆ!"

ቆይቶ ዴቭ ከፍቅረኛው ጋር ተጣላና ሌላ ሴት ጋር ጀመረ ... እና ኤክሱ ብስጭት ብላ ምን አለች? ..."ደግሞ ከሌባ ለተረፈ እንትኑ!" ውይ ሴቶች 😀

@wegoch
@wegoch
@paappii
2024/09/21 19:58:21
Back to Top
HTML Embed Code: