Telegram Web Link
አባት ልጁን ለማግኘት ወደ ክፍሉ ጎራ ይላል፤ ልጁ ግን የለም። እንደለመደው አምሽቶ ሊመጣ እንደሆነ እያሰበ ክፍሉን ለቆ ሊወጣ ሲል የሆነ ነገር አስተዋለ።

አዎ ክፍሉ እንደወትሮው አልተዝረከረከም፤ በሚገባ ተፀድቶ ተስተካክሏል። አልጋውም በስርዓት ተነጥፏል፤ ወለሉ ሸልፉ ምኑ ሁሉ በወግ በወግ ሆኗል።

ግራ በመጋባት ክፍሉን እየቃኘ በመሃል ማጥኛ ጠረጴዛው ላይ ደብዳቤ ያገኛል፤ ከላይ ለ አባዬ ይላል በትልቁ።
ከፍቶ ማንበብ ጀመረ..

“ አባዬ ከትሬሲ ጋ ተያይዘን ጠፍተናል..አውቃለሁ እድሜዋ ከእኔ በ30 እንደሚበልጥ ፤ ቢሆንም እኔ ግን በጣም እወዳታለሁ። ለመጥፋት የወሰንነው እንዳረገዘችና ልጁ የኔ እንደሆነ ስትነግረኝ ነው።
ምንም ገንዘብ ስላልነበረን ከዋሌትህ ልሰርቅ ተገድጃለሁ።

ጥሩ ገንዘብ መስራት የጀመርን ጊዜ፤ የኤች አይ ቪ በሽታዋን ሆስፒታል እየሄድን ክትትል ማድረግ እንጀምራለን። ደሞ ብዙ ልጆችንም የመውለድ እቅድ አለን ፣ ጊዜው ሲደርስ ተሰብስበን መጥተን የምናይህም ይሆናል።

ቆይ ቆይ አባዬ የውሸቴን ነው ተረጋጋ፤ እዚሁ ሰፈር ነው ያለሁት የትም አሌድኩም። የኔ ፍላጎት ከፈተና ውጤቴ በላይ አስፈሪ ነገሮች እንዳሉ ለማስታወስ ነው ፤ ልታየው ከፈለክ ሌላኛው ጠረጴዛ ላይ አለልህ።
ስትረጋጋ ደውልልኝ ”

@wegoch
@wegoch
@paappii
ፀጉር ቆራጩ ደምበኛውን ያዝናናል ብሎ ያሰባቸውን ነገሮች በማጫወት ላይ ነው።
“ያ ይታይሃል?...አስፖልቱ ዳር የተቀመጠው ልጅ..?”
“አዎ”
“ከምታስበው በላይ ጅል ነው”
“እንዴት? ”
“ቆይ ላሳይህ” አለና ፤ወጣ ብሎ ልጁን ጠርቶ ወደ ውስጥ አስገባው።
“ተመልከት እንግዲህ..”

ከኪሱ አንድ የአምስት ብርና አንድ የአስር ብር ኖት አወጥቶ ሁለቱንም መሬት ላይ ጣላቸው ከዛ ልጁን “ ከሁለቱ ትልቁን ብር አንስተህ ሂድ” አለው። ይሄኔ ያ ልጅ አምስቷን ብር ብድግ አርጎ ወደ መጣበት ይመለሳል።
“አየህ ይሄን ደደብ?...በዚ እድሜው አምስት ብርና አስር ብርን መለዬት አይችልም!!”
“በጣም ሚገርም ነው” አለ ፀጉሩን ሊቆረጥ የመጣው ሰውዬ ባዬው ነገር የእውነትም ተገርሞ።

አስተናግዶት ከጨረሰ በኋላ ተሰነባብተው ተለያዩ። ይሁን እንጂ ያ ሰውዬ ቅድም ባየው ነገር ተገርሞ ብቻ ሊቀር ስላልፈለገ ልጁ ወዳለበት ሄዶ ያሳሰበውን ነገር ጠየቀው
“እውነት አንተ..አስር ብር እና አምስት' ብርን መለየት አትችልም?”
“አዪዪ..” አለ ልጁ
“አዪዪ..10 ብሩን ያነሳሁ ቀንማ ጨዋታው ያበቃል”

by Yosef Gezahegn

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሥዕል ለወዳጅ ዘመዶ ስጦታ ማበርከት የምትፈልጉ በ+251984740577 ይደውሉ።


ወይም @gebriel_19 ላይ  ፎቶ  በመላክ በ ተመጣጣኝ ዋጋ  ማዘዝ ይችላሉ!



@seiloch
@seiloch
ብርቅዬ ጎደኞቻችን

———
አብዛኞቻችን ከህይወት ዘመናችን አካል ከሆኑት ውስጥ የት/ቤት ጎደኞቻችን እና ትዝታችዎቻችን በእጅጉ ከምንናፍቃቸው እንዲሁም ወደኋላ ተመልሰን የመኖር ምርጫ ቢሰጠን በድጋሚ ያን ህይወት ለመኖር የምንመኘው እና የምንጎጎለት አንዳንዴም እንደእኔ ያለ የኋላውን ናፋቂ የሆነ ሰው በፈረንጆቹ ፊልም ውስጥ የሚያየውን በእነሱ አፍ  time travel  ወደኛ ስናመጣው ጊዜን ወደፊት እና ወደኋላ መመለሻ machine ለመስራት መመኘቱ አይቀርም ትግበራ ላይ ባንገባም (እውቀታችን ቢገድበንም) እና ስመለስ ወደእኛ አለም  የት/ት ቤት ህይወታችን ወርቃማው አስደሳቹ የህይወት ዘመናችን አካል ነው ብል ማጋነን አይሆንብኝም።የት/ት ቤት ትዝታዎቻችንን ስናነሳ ደሞ የሀይስኩል ህይወታችንን ሳናነሳ ማለፍ የሚታሰብ አይደለም የአብዛኞቻችን አስደሳች ሮማንቲክ አስቂኝ ህይወት ያሳለፍነው እዛ ውስጥ ነው ። ያ  ጊዜ ለብዝዎቻችን መፈንዳት የጀመርንበት (like volcano )ሴት መጥበስ ,መጀንጀን ትምህርቱን ከነጭራሹ መርሳት  ,ቤተሰብ ትልቅ ሰው መስማት ያቆምንበት እንደልባችን የምንሆንበት ከጎደኞቻችን ጋር ጥዋት ወተን ማታ ለማደር ወደቤት የምንገባበት አፍላ እድሜ። በዛ የጡዘት ጊዜ አይደለም ቁምነገረኛ ልጅ መሆን ቀርቶ ጥሩውን ከመጥፎ በቅጡ መለየት የምንቸገርበት እድሜ ነው ።ታዲያ እንዲህ ስል የሁሉንም የት/ት ቤት ህይወት የሚያጠቃልል አይደለም ሁላችንም አሉን ለየት ያሉ  ከልጅነት የምናቃቸው አንዳንዴም የቅርብ ጎደኞቻችን የሆኑ አሉን።  ከላይ የጠቀስኩትን life የማያቁት ከእድሜያቸው በላይ የበሰሉ አሁን ላይ ሆነው የወደፊታቸውን ዛሬ የሚቀርፁ,ሚያልሙ ትልቅ የማይዳሰስ የማይጨበጥ ለኛ ሲነግሩን እንድናሾፍባቸው የሚያደርጉን  ቁም ነገር የሚያበዙ በአብዛኛው ነገራቸው ለየት ያሉ ከኛ በተቃራኒ የቋሙ ውስጣቸው ሌላ ትልቅ ሰው አለ እስከምንል ንግግራቸው እና ሀሳባቸው የሚያስደንቀን እኛም የእነሱ አለም ገብቶንሞ ሆነ ሳይገባን እንዲሳካላቸው የምንመኝላቸው አሉን ብርቅዬ ጎደኞች ከዘፋኞች መሃል ያሉ ዘማሪዎች ከወረኞች መሃል ያሉ ዝምተኞች ከተደባዳቢዎች መሃል ያሉ አስታራቂዎች አሉን በትምህርት ብቻ ዕውቀታቸው ያለተገደበ ከኛ መሃል ምሁሮች አሉን። ታዲያ ይሄ ሁሉ ነገር እንዳነሳ ያስገደደኝ አንድ ነገር ነበር ተዕለታት በአንዱ ቀን ማታ ላይ ከቤተሰቦቼ ጋር ተሰብስበን  ቁጭ በልንበት ልጄ ለመዝናኛ የሚሆን ነገር ለመክፈት ከቻናል ቻናል ይቀያይራል በድንገት ግን አንድ  ከዚ ቀደም የማውቀውን ሰው በቲቪ መስኮት አየሁት በፍጥነት እንዲመልሰው ወደቻናሉ ልጄን አዘዝኩት ትዕዛዝ ይሁን ቁጣ አላቀውም እሱም ደንግጦል መለሰው እንዳልኩት አየሁት በድጋሚ ልቤ ደነገጠ የማውቀው ስሜት ተሰማኝ ልዩ ታሪክ አለኝ ከሱ ጋር ግን አልመጣል አለኝ ተብሰለሰልኩ አዕምሮዬን አስጨነቁት ጎልማሳውን ሰው ለማስታወስ የአዕምሮዬን የትውስታ ፋይሎች አገላበጥኩ ደከምኩ ከብዙ ድካም በኋላ የሆነ ሰው ያፋልጉኝ ማስታወቂያ ተለጥፏለት ሲገኝ እንዳለው ስሜት ተሰማኝ ተደሰትኩ አመሰገንኩ ወደራሴ ስመለስ  ቆሜ ነበር እና ተረጋግቼ ቁጭ አልኩ ሳቅኩ ከልቤ ተገረምኩ የደስታም እንባ አነባው ይሄ ሁሉ ሲከሰት ለካ እረስቻቸዋለው ቤተሰቦቼን ቁጭ ብለው እንደቲያትር ታዳሚ ይመለከቱኛል ከዛም ትወናው  አለቀ መሰለኝ ሚስቴ ልጆቼን ወደክፍላቸው አስገብታ ልታወራኝ መጣች መቼም ልጆጄ ዛሬ እንቅልፍ የላቸውም ምን እንደተፈጠረ ሲያሰላስሉ ሲጠይቁ እና ሲመልሱ ነው ሚያደሪት ።ወደሷ ስለመስ በአግርሞት እና በነዛ ስስ አይኖቾ በስስት እያየቺኝ ስፖንጅ በሚመስሉ እጆቾ እየዳበሰቺኝ ምን እንደተፈጠረ ጠየቀቺኝ ምኑን ብዬ ምን ልበልሽ ከየትኛው ልጀምርልሽ አልኳት አይን አይኖን እያየዋት እኔም በተራዬ ።ደስ ካለ የሷ ምላሽ ነበር  በሀሳብ ብዙ አመታት ተመልሼ ጀመረኩት ትረካውን አንድም ለሶ አንድሜ ለራሴ ።

ይቀጥላል part 2

@wegoch
@wegoch
@paappii
በውስጣችን ያለውን ሰውዬ እንዴት ተው እንበለው ?
(ሚካኤል አ )
እነሆ ለብርሀን ጨለማ ፣ ለወንድ ሴትን ፣ ለክፋት ደግነትን ተቃርኖ አድርጎ ሲፈጥር እንዴት ባንድ ገላ ውስጥ ሁለት ማንነት አብሮ ማቆየት ቻለበት ስል አስባለሁ !
ከዚህ ቀደም ሚካኤል አስጨናቂ (እኔ) ተቤራ በተሰኝ መፅሀፉ "ወይ ለከ!" በሚለው የአጭር ልበ ወለድ ክፍል ያነሳት እንስት ሁሌ ወደ አዕምሮዬ ትመጣለች ።
ያቺ ሴት ሰዎች በተለምዶ ሴተኛ አዳሪ የሚሏት ካራክተር ነች ።
ልቧ ሩህሩህ ፣ እምነቷ ፅኑ ነው ።
አታውቅም አይሏት ማንበብና መፃፍ ፣ መስማትም ትችላለች ። አንድ ጊዜ ዋነኛው ገፀ ባህሪይ ሊታዘባት ለገብርኤል ዕለት ሻማ ስታበራ አያት ።
የሱ አይደለም የሚገርመው ፣ የበዓል ዝክር አቀረበች ። ቡናው እጣኑ ፏ ብሎ ጠባቧ ቤት ድባቧ ፈካ ።
ያኔ “ይህን ለምን እንዳደረገች “ ጠየቃት ።
ያቺ ሩህሩህ እርግብ ። “ገብርእኤልን እወደዋለሁ ። ጠባቂ መልዓኬ” ነው አለችው ።
እሰየው አበጀች!
ቀጣይ ንግግሯ ግን መንፈስን በሁለት ገመድ የሚወጥር ፣ ግርምትን የሚጭር ነበር ።
“ አባቴ ዛሬም አንዱን ክልፍልፍ ያመጠልኛል ። መቼም ፆም አያሳድረኝ” አለች ።
አሁን ይህች ሴት እንዲህ ያለው እምነት እያላት ፣ እንዲህ ያለው ቀናኢነት እና የዋህነት እያላት ገላን ለዝሙት መስዋዕትነት ማቅረብ ሀጥያት መሆኑን እንዴት ሳታገናዝብ ቀረች ?🤔
ገብርኤልን ለዝሙቴ ተባባሪ አድርገኝ ብሎ በየዋህነት መለመንን ምን ይሉታል ?
ዋናው ገፀ ባህሪ ገረመችውም ፣ ስጋዋ ደግሞ አሳዘነችው ።
ዝም አለ ፣ ፅሞና ።
ዘመዴ እስቲ ሌላ ጨዋታ ላቀብልህ ደግሞ !
የዘመነ መሳፍንቱን ደጃች ማሩ ታውቃቸዋለህ አይደል ?
መቼም እኒህ ባላባት ዝክር አውጥተው ፣ እግዜርን ተለማምነው ፣ ለሀይማኖታቸው ቀንተው በቃኝ አይሉም ። አቤት እግዚሀርን ሲወዱት !
ለአንገት ሰይፍ መዘው ንሰሃ አባታቸው “ውጉዝ ከማሪዎስ” ካሉ ንዴት እና ደምፍላታቸውን ዋጥ አድርገው ሰይፋቸውን ወደ አፎታቸው ለመመለስ አይግደረደሩም ።
እናም አንደዜ ረዥም ፀሎት ይዘው አሽከራቸው ከጠሎት አናጥቧቸው እንዲህ አላቸው !
"ጌታዬ አስቸኳይ ጉዳይ አለን "
“እህ ምን ሆናችሁ ?”
“ስለ አያል ጉዳይ ነበር “
“አያል ምን ሆነ ?”
አሽከሩ እጅ ነስቶ ለጥ ማለት እየቀረው
“ጊታዬ እሱን አስሮ መግረፍና ማሰቃየት ደከመን አላቸው ። አንድ ነገር ይበሉት “
“ለዚህ ነው ፀሎቴን ያቋረጥከኝ ? አመዳም ወግድልኝ “ ብለው ተመናቅረው ሎሊያቸውን አባረሩት ።
ያ ሎሌ በልቡ እንዲህ ያለ ይመስለኛል ።
“እኒህ ምስጉን ትልቅ ፀሎተኛ መሪ እንዴት የአንድ ነፍስ ስቃይን እንዲህ በቀላሉ ንቀው ይተውታል ?”
(በነገራችን ላይ ደጃች ማሩ ደጃች ኃይሉን (የመይሳው ካሳን አባት) በክህደት ለረዥም ጊዜ ግዞተኛ አድርገውት መቆየታቸው በታሪክ ይወራል ። ይሄም ራሱን የቻለ ብዙ ጥያቄ የሚያስነሳ የክፉ ባህሪያቸው ምሳሌ ነው ። ክህደት !
በሌላ በኩል ደጃች ይማም በጎንደር ቅኔ ቤት ተማሪዎች ላይ በፈፀሙት ግፍ ምርር ብለው በሀዘኔታ ሲያነቡም ተስተውለዋል ። ሁለት ሰው ማለት ይሄ አይደለምን ?
ይሄን ሁሉ የምዘበዝበው ልጅ ሆነን ለፍስለታ ጾም ያጋጠመኝ ነገር ትዝ ብሎኝ ነው ።
ሁሌ መልክምነትን የሚያስተምረን ፣ በዛ ዕድሜ ካለን ልጆች በመልካምነት እና ዕውቀት አርአያ የምናደርገው ስንሻውን ነበር ።
ብዙ ልጆች አብረነው ፍልሰታ ፆምን እናስቀሳለን ።
ቄስ አምሀ ባዛ ስርቅርቅ ድምፃቸው አሀዱ ብለው አስጀምረው በሰላም ግቡ እስኪባል ድረስ በፍፁም መንፈሳዊነት እና ስክነት እናሳልፋለን ።
መቼም የቅዳሴ መዓዛው እና ጣዕሙን ያላጣጣመ ሰው ምንኛ ቀረበት ። የመቅደሱ እጣን ያን ሁሉ ፀሎት ቀጥ አድርጎ ወደ ሰማይ ሲያሳርግ በምናቤ ይታየኛል ።
የገነት መዓዛ !
ቅዳሴው ተፈፅሞ ወደ ቤት ስንሄድ ግን ስንሻው አድርጎ በመጣው ኤርገንዶ ጫማ ምትክ ዘናጭ እስኒከር አድርጎ አየሁት ።
ይሄ ልጅ መላዕክት ቀናነቱን አይተው ጫማ ገዝተው አምጥተውለት ይሆን ? ለማለት እየዳዳኝ
“እስኒከሩ?” አልኩት ።
“ አዎ ካንዱ ነፈዝ ላፍ አደረግሁት 😃"አለኝ
አጠገቤ የቆመው ያ የሰው መልዓኩ ስንሻው መሆኑን ተጠራጥሬ ትክ ብዬ አየሁት ።
በውስጣችን ሌላ ሰው እንዳለ ያሰብኩት ለዛን ቀን ይመስለኛል ።
በቃ የልጅ ልቤ በድንጋጤ አታሙዋን ደቃች ።
ዛሬም ድረስ ራሴንም ይሁን ሌላውንም ሰው እፈራለሁ ።
ውስጣችን ያለውን ሰውዬ መቼም አላምነውም 🙂


@wegoch
@wegoch
@wegoch
የመጨረሻው ቀን August 14 ነው። እድላችሁን ሞክሩ🙌
https://www.tg-me.com/dogshouse_bot/join?startapp=2H-hloxORHKMqDS8Gwvfbw
የሔዋን እናት... !

(ኤልቫን እንድታሸንፍልን የቋጠርንበት አንድ ዘመን🥰)

ዝም ብዬ ስለ ሲፋን ሐሰን እያሰብኩ... ድንገት ኤልቫን (ሔዋን) አብይለገሠ ትዝ አለችኝ። ያቺ ለቱርክ ትሮጥ የነበረችው፣ ልክ እንደ ሲፋን ቀጭን አንጀት የራቃት (አንጀት የምትበላ) ግን ጎበዝ፣ አይበገሬ፣ ፈገግተኛ አትሌት ነበረችንኮ። ብዙ ሰው እንደሚያስታውሳት አስባለሁ።

ያቺ ኤልቫንም እንደ ሲፋን ብዙ ድንቅ የሚባሉ የሩጫ ድሎች ነበሯት። በሆነ ወቅት የግማሽ ማራቶን ወርቅ ሜዳሊያን ወስዳ፣ እና የ5ሺ ይሁን የ3ሺ ሪከርዱን ሰብራ ሁሉ ነበረ። ልክ እንደ ሲፋን በየውድድሩ አትጠፋም ነበር ኤልቫንም!

ታዲያ ኤልቫን የደብረብርሃን ልጅ ናት። ያኔ.. የዛሬ 20 ዓመት አካባቢ ማለት ነው.. የንግድ ባንክ ነገረፈጅ ሆኜ የሰሜን ሸዋ፣ የመራቤቴ፣ የፍቼ፣ ወዘተ አካባቢዎች ጉዳዮችን በኃላፊነት ወስጄ ፍርድቤቶች እቀርብ ነበረ።

በዚያም ወቅት ብዙ ጉዳዮች በእንጥልጥል ላይ በመሆናቸው ለእነሱ በቶሎ እልባት እንድሰጥ ተብሎ (እና ተስማምቼ)፣ አለቆቼ አዲሳባ ሆነው፣ እኔ ደሞ ደብረብርሃን ላይ የማስተባበሪያ ቅርንጫፍ ቢሮ ተከፍቶልኝ፣ ለ11 ወራት ገደማ ለቆየ ጊዜ ሠርቼያለሁ።

በዚያ ወቅት፣ ያው ወጣትነትም አለ። ጭፈራውም። የጓደኞች መዓትም አለ። ብሩም ይመጣል። ይጠፋል። የሚገርም ዓለም ውስጥ ነበርን ከነጓደኞቼ። አንዳንድ ድሮ ሎውስኩል አብረን የተማርን ጓደኞቼም በደብረብርሃን በሚገኘው የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛው ፍርድቤት በዳኝነት ያገለግሉ ነበሩ። የሚገርም ጊዜን አሳልፈናል አብረን።

ታዲያ አንዳንዴ ኪሳችን የሚሞላውን ያህል፣ ስለማንሠርቅ ደግሞ፣ የዚያኑ ያህል በወሩ መጨረሻ ገደማ ደግሞ ኩ ኪሳችንን ድርቅ ይመታዋል። አንደኛችን ሌላኛችንን እስቲ ትንሽ ሳንቲም ይኖርሃል? የምንልበት ወሽመጥ ይቆረጥብናል። ምክንያቱም እንተዋወቃለና😀😊

እና በአንድ በጠብሽ በተወገርንበት አንዱ ክፉ ሰሞናችን፣ እግዜሩ አትሌት ኤልቫን ለገሠን በእጃችን ላይ ጣለልን። እንዴት? በየት በየት በኩል? ቀላል ነው። አስረዳለሁ።

የኤልቫን ወላጅ እናት የደብረብርሃን ከተማ ነዋሪ ነበሩ። ነዋሪ ብቻ ሳይሆኑ በከፍተኛው ፍርድቤት የመዝገቤት ሠራተኛ፣ እና የችሎት አስተናባሪ ሆነው ይሠሩ ነበረ። አሁን ስማቸው ተዘነጋኝ። ስማቸውን ስለረሳሁ በጣም ራሴን ወቀስኩ። አልዛይመሬን😊!!

እና ለቱርክ የምትሮጠዋ ኢትዮጵያዊት ቀጭኔ ተምዘግዛጊ አትሌት፣ ኤልቫን፣ የሆነ ዓለማቀፍ ውድድር ባሸነፈች ቁጥር፣ በቃ ለእናቷ ጫን ያለ ብር ትልክላቸው ነበር። እና ከመጠን በላይ ደስተኛ ነበሩ።

ደሞ እኛ ፍርድቤት አካባቢ ያለነው፣ የኤልቫን እናት መሆናቸውን ስለምናውቅ፣ ኢትዮጵያውያንን ቀድማ ወርቃችንን በመንጠቋ ቆሽታችን ቢያርር ራሱ፣ እናቷን ግን በማግስቱ ስናገኛቸው "እንኳን ደስ አለዎት! ጀግና ልጅ አለችዎት!..." እያልን የእናትነት ደስታቸውን ለመቋደስ (በአራዳ ቋንቋ እናትየውን ለማመቻቸት) እንጣጣር ነበር።

በሆነ ለደመወዝ በቀረበ አንዱ ሰሞናችን ታዲያ፣ ከየት እንበደር? እያልን መላ እየዘየድን እያለ... በድንገት አንድ የአትሌቲክስ ድል በጓደኛችን ቤት ቲቪ ላይ ተሰማ። ለቱርክ የምትሮጠው ትውልደ ኢትዮጵያዊት ኤልቫን አንደኛ ወጥታለች፣ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ደሞ ሁለተኛና ሶስተኛ ሆነው ጨርሰዋል። ያንን እንዳየን እኔና ዳኛው ጓደኛዬ (ስሙን ልጥራው ይሆን?) በደስታ እርስበርስ ተያየን!😀 ቆይ ሰው ሀገሩ ወርቅ ተነጥቃ ምን ፈገግታ ያለዋውጠዋል?

በማግሥቱ ይሁን በሳልስቱ "አንተ ጠይቃቸው፣ የለም አንተ ጠይቃቸው" ተባብለን ለኤልቫን እናት ሞቅ ያለ እንኳን ደስ ያለዎት መልዕክታችንን ካሰማን በኋላ... ፀጉራችንን እያከክን (አንደኛችን)... "ከሰሞኑ ደመወዝ ሲወጣ የሚመለስ ትንሽ ብር ይኖርዎት ይሆን... የኤልቫን እናት?" የምትለዋን ወሳኝ ጥያቄ እንደምንም አምጠን ተነፈስናት😀😀😀!

መልሳቸው ከጀት የፈጠነ እሺታ ነበር! እንዴታ! ደሞ ምን ችግር አለ? ስጦታ አልጠየቃችሁኝ? ያውም ብድር? ደሞ ልጄ ልካልኛለች ቤትሽን አሳድሺ ብላ! አይዟችሁ፣ ሲቸግራችሁ እናታችሁ ነኝ፣ ጠይቁኝ፣ አትፍሩ...!?" ተብለን በነፍስ ወከፍ በጠየቅነው ልክ ብድር ተለቀቀብን😊😀😀! አቤት ደስታ? አቤት ፌሽታ?! ከማጣት በኋላ የምትገኝ ሲሣይ... አቤት በረከቷ?!🥰😊😀

ታዲያ ሁሌ ስለ ኤልቫን ሳስብ... በእናቷ በኩል... ደብረብርሃን ላይ.. ለጠብሽ ሰሞናችን እንደ አንዳች ሲሣይ ከሠማይ ወርዳ የደረሰችልንን እያሰብኩ... ሁሌ ፈገግ እላለሁ!

ደሞ ጓደኞቼም ቀልደኞች ናቸው... አንዳንዴ ኧረ ሰሞኑን ድርቅ መታን እኮ... አሁንስ ሰበብ አጣን... ያቺ ኤልቫን ለገሠ ከሰሞኑ አንድ ውድድር አሸንፋ ይሆን? እንባባላለን። ሣቅ በሣቅ። ኧረ አልሰማሁም፣ አልሰማሁም ይላል ሌላው ሰው። ከዚያ ይቺ ጦልጧላ ማሸነፍ አቅቷት ነው አሁን? የማንን ጎፈሬ ስታበጥር ነው..? እኛ እሺ ምን እንሁን?? 😀😀😀 ሌላ ሳቅ! ብዙ ሳቆች!

ጊዜዎችህ፣ ዘመኖችህ፣ ወራቶችህ፣ የፍፍስሃና የሃዘን ሰዓቶችህ፣ የጠብሽና የሃላል ቅፅበቶችህ ሁሉ አብሯቸው የተያያዘ አንዳች የሰው ታሪክ አላቸው። በዐድሜህ ሁሉ የሆነ አብሮህ የሚደሰት፣ አብሮህ የሚከፋ፣ አብሮህ ምች የሚመታ፣ አብሮህ ከሲሣይህ የሚቋደስ አንድ ሰው፣ ብዙ ጓደኛ፣ ብዙ ሰዎች አሉ።

ይህ ነገር በተለይ ለእኛ ኢትዮጵያውያን በብዛት ተለይቶ የተሰጠን ትልቅ የጋራ ህይወት፣ ትልቅ የተባረከ ዕፁብድንቅ ሥጦታ ይመስለኛል።

ከሃገርህ ርቀህ ብዙውን ጊዜ፣ አጣህም አገኘህም፣ ተደሰትክም ከፋህም፣ ጨነቀህም አለፈልህም... ብዙ ጊዜ በብቻህ ጀልባ ላይ ነህ። ወቅቶችህ አኗኗሪ፣ ትዝታ ፈጣሪ፣ አዳማቂ ሰው የላቸውም። ሰው አልባ ህይወት፣ ትንፋሽ የለሽ ዕድሜ ይሆንብኛል።

እና ሳልወድ በግድ የድሮውን መከራና ደስታ እናፍቃለሁ። ሳልወድ በግድ በድሮ ትዝታዎች ውስጥ ስመላለስ አገኘዋለሁ ራሴን።

አሁንም ወደ ኋላ በትዝታ የመለሰኝ መነሻ ሃሳብ... የሲፋን ለኔዘርላንዶች መሮጥ ነበር። በሷ የተነሳ የጥንቷ የጠዋቷ ኤልቫን አብይለገሠ እና የደብረብርሃኗ ደግ፣ ደስተኛ፣ ትሁት እናቷ ትዝ አሉኝ! ጓደኞቼ ትዝ አሉኝ። ቀኖቻችን ትዝ አሉኝ።

ያ ሁሉ ወጣትነት። ተስፈኝነት። ሃቀኝነት። የጋራ ደስታችን። የጋራ ድብርታችን። የጋራ ጎጇችን። የጋራ ሀገራችን። የጋራ ዓለማችን። የጋራ ላይፋችን። ብዙ ወርቃማ ትዝታዎች ተግተልትለው ወሰዱኝ በሃሳብ።

የደብረብርሃን የኤልቫን እናት በዕድሜ፣ በጤና አሁንም እንደሚኖሩ ከልቤ ተስፋ አደርጋለሁ። ስለ ደግነታቸው፣ በአካል የራቀቻቸውን ልጃቸውን ድል በሰሙ ቁጥር፣ ደስታቸውን የሚጋራቸው ወገን ሲያገኙ... ከዓይኖቻቸው የሚፈልቁት የደስታ ጮራዎች አሁን ፊቴ ላይ ድቅን ይሉብኛል። ባሉበት መልካሙን ሁሉ እመኝላቸዋለሁ።

ለሁሉም። ለሁላችንም። የሰው ሃገር ባንዲራ ይዘው እንዲሮጡ ህይወትና ዕጣፈንታ ያስገደደቻቸውን የእናት ኢትዮጵያ አፈር ያበቀለቻቸውን ውድ ልጆቻችንን ሁሉ... ለእነሱም። ፈጣሪ መንገዳችንን እንዲያቀናልን። መልካሙን ሁሉ እንዲያመጣልን ምኞቴ ነው።

ፈጣሪ እናት ሀገራችንን፣ ሕዝባችንን፣ አብዝቶ ይባርክ!

በረካ ሁኑ! ♥️

መልካም ጊዜ!!🙏

by assaf Hailu

@wegoch
@wegoch
@paappii
ወግ ብቻ pinned «⌚️ በቀጣይ List የሚደረጉ ፕሮጀክቶች 👇👇👇 ትንሽ ጊዜ ነው ያላችሁ! #LOST_DOGS https://www.tg-me.com/lost_dogs_bot/lodoapp?startapp=ref-u_454803628__s_573809 1, MAJOR https://www.tg-me.com/major/start?startapp=454803628 2, BLUM🤢 https://www.tg-me.com/blum/app?startapp=ref_4AQg09PDzR 2,CATS 🐈 t.me…»
"እማዬኮ ሔዱ"
.
.
ባውሮፕላን ሔዱ። ጎረቤቶቻቸው አዋጥተው በአውሮፕላን አበረሯቸው።
ፎቶ እንኳ እንደሌለን ያወቅኩት ሲሔዱ ነበር። ሙሉ ጊቢውን ጠየቅኩ ማንም የለውም።
"ሳላገኘው ልሔድ ነው?" እያሉ ሳለ ትናንት ከአዲስ አበባ መጣሁ።
"እማዬ ማናቸው?"
የዩቲዩብ ትምህርቶቼን የሚከታተል ድምጻቸውን ሳይሰማ አይቀርም።
..
"ለምን ሔዱ?"
.
ምክንያታቸውን ሲናገሩ...
"ደከመኝ! የሽንት ውሀ ማንጠልጠል እያቃተኝ መጣ"
" ደጁ ላይ አስቀምጡልኝ ብለው አላቀብሎትም ያለ ሰው አለ? መሔድ ደስ ካላሎት ለምን አይቀሩም ?"
🥺 " ላዬ ላይ ሲያመልጠኝስ? ምን ታደርጋላችሁ?"
.
እማዬ ለምን በዚህ መሆን ፈለጉ?
.
1. ሀሜት አለ።
አራት አመት ገደማ ሆኗቸዋል ድሬዳዋ ከገቡ። የወሎ ሰው ናቸው።
ተመልሶ ወደ ልጆቻቸው መሔድ ደስ አላላቸውም። ስጋ እንደ ባዳ እንደማይደላ ደመነፍሳቸው ነግሯቸዋል። ዘመድ ስጋን እንጂ ስነልቦናን አይረዳም።
.
ባዳ መሀል ሀሜት አለ። ሀሜትኮ ንሰሀ ነው አይምሮን ያጸዳል። ቅርጥፍ አድርጎ ማማት ያልቻለ ሰው paranoid የመሆን እድሉ ሰፊ ነው። በአጭሩ ሀሜት #የአይምሮ_ሰገራ ይመስላል። ቆሻሻ ነው ግን መውጣት አለበት ልክ እንደ አር። አማናዊው ሰገራ በባለቤቱ ግፊት በምጥ ይወጣል! የአይምሮ ሰገራ ለማውጣት ግን #ባዳ ይፈልጋል።
.
#ባል ባዳ ነው። ለዛ ነው ሚስቱን #የሚበዳው። ባዳው ባል ከሚስቴ ጋር ይሕ #ስጋዬ ነው ይህ #ስራዬ ነው #ሳይል በሀሜት ከተንበለበለ አይምሮው ጤነኛ ይሆናል! ረጅም ይኖራል። "ሴትንኳ ስራዋ ነው" 🤭 አላልኩም ስርአት!!! ሚስትም ከጎረቤት ማማት ትታ ከባሏ ጋር በማማት ከተባበረች #እባብ ፈጣሪን የሚያሳማው ባዳ አያገኝም።
..
2. ትዕዛዝ አለ።
.
ዘመድ እንደባዳ እርጅናን አያከብርም። አሮጊቷን አንቺ ሲል ያቀረበ ይመስላል። ፍቅር ክብርን የሚበልጥ የሚመስለው ይኖራል። በፍቅር እንደልብ መታዘዝ የለም በክብር እንጂ። አልገባንም ከምናፈቅረው ለምናከብረው እንታዘዛለን። ከእናት በላይ ለአባት እንደማለት።
.
የምናፈቅረው ላይ የምናከብረው ነገር ከተገኘ አቤት መታደላችን።
.
#እማዬ ይከበራሉ። #ደም ለማየት ወራት የቀሯትን የደረሰች ልጅ ሲልኩ በሞገስ ነበር። ማንም የእርጅና ዘውዳቸውን እያየ ይታዘዝላቸዋል። ምናልባትምኮ ልጅቱን ከ 20 ሜትር የጠሯት አንድ እርምጃ ርቀት ላይ ያለች ከሰል እንድታቀብላቸው ነው። ፊቷን ቅጭም እንዳደረገች አቤት ሳትል ታቀብላቸዋለች። እግረመንገድ ለሚያወሯት ዝብዛብ አትመልስም! አቀብላቸው ስትመለስ እየተጉመጠመጠች ነው።
"አንቺ አስቀያሚ ስለምወድሽ ነውኮ!" ምናምን ይላሉ። "ኧረ ጎረመሰች" ይላሉ።
ሌላ ትእዛዝ እንዳይደግሟት እየጸለየች አጎንብሳ ትፈተለካለች። የልጅ ልጃቸው ብትሆንስ?😁
(አንድ የልጅነት ጓደኛዬ አጨባሽ አያቱ በመላክ አማረውት "ጂፓሱ ሸርተት ብሎ በወደቀባቸው" ይለኝ ነበር)
.
.
3. ሰላምታ ያገኛሉ።

ኦኦ እማዬ ሰላምታ ነፍሳቸው ነው። ማንም ሰላም ሳይል አያመልጣትም! በጊቢው 12 ተከራይ አለ። ከአንዱ ቤት ቢያንስ 2 ሰላምታ አያጡም። ሀያአራት ደና አደርክ እና ደና አመሸህ። አንዳንዴም እድል ከቀናም ስምንት ደናእደሩ ይደርሳቸዋል።
.
በሳቸው እድሜ ይሔ ቀላል ሀብት እንይመስልህ። ደሞ ትንሽ ስኳርና ሌላም በሽታ አላቸው/አለባቸው። ስለዚህ በትንሹ ሁለት ረዘም አድርጎ ጤናቸውን ጠያቂ ይገኛል። እግረመንገድህን ስለጤናህ ተመክረህ ታልፋለህ። ምናልባት ከትናንት ወዲያ አንዷ ጎረቤትህ እናትህ ከሪፍትቫሊ #የገዛችውን(ማነው ያገኘችውን! No ያመጣችውን! ይሔም አይሆንም ብቻ whatever u call it) የዲግሪ ወሬ ሰምተዋል።
"እንኳን ደስ አላት...ምን ተማረች...አንተን የመሰለ አድራሳ ምነው እስካሁን...😁" ብዙ ወሬ! ቲክቶክና ፌስቡክ የማይጠቀሙ ሰዎች መሰንበቻ የሚሆን ወሬና ጨዋታቸውን ከየት ያመጣሉ? እንደዚህ ነዋ የሚሸቃቅሉት። በስጋቸው መሀል ይሔም የለም።
.
.
5. ከሰል ይሸጣሉ።

ይሔ ደሞ እንድሜ ለመብራትሀይል መላ ሰፈሩን ወደሳቸው ይነዳዋል።
በህጻን አዋቂው "እማዬ የሉም" መባል ቀላል አይምሰላችሁ። በቀደም በመልክ የማያውቀኝ አንዱ
"የበሀይሉ መጸሀፍ አለ?" ሲሉት ጃፈር ጎን ቆሜ የተሰማኝን ሙቀት አልረሳም። 😊
ጃፊ በአይኑ አይኔን እያጠቀሰ "አልቃለች..." ሲልማ እዛው ገልቤ ልመታ ምንም አልቀረኝ።😁
እማዬ...
"ዝርዝር ይዛችሗል?
ማነው ስምህ አንተ? አባትህ ይቅማል? በል ቀጣይ ስትመጣ ፌስታል ይዘህ ከመጣህ ለበጎቻችሁ የተረፈ ሰላጣና ድንች አዘጋጅልሀለሁ። ምነው አጠርክብኝ ደሞ"
" ኧረ እናቴ ላጭታኝ ነው"
" በልሺ ሒድ አጭበርባሪ ቁመትህን የማላውቅ መስሎህ ነው አ?" (ይቺ ሁለት መስመር እንኳ ነገር አማረልኝ ብዬ ልቦለድ ሳደርጋት ነው። እማዬ አይሞጣሞጡም። አይናፋር አሮጊት ናቸው)
.
ልጆቻቸው ጋር ሲሔዱ ቅላታቸውን እና ክብራቸውን የሚፈታተን ከሰል መሸጥ አይችሉም። ከሰል መሸጥ እናት ማውረድ መስሏቸው። የዋህነታችን!
.
.
6. ትረባ
ትረባ አስለምጃቸው ነበር። የተለመደ ሰላምታቸው ሲያሰለቸኝ የፈጠርኩት መላ ናት። ለተፈሳው ለተገሳሁ ሁሉ ሊመክሩኝ ሲሞክሩ ቤት ገብቼ መሀል ጣት እስከማውጣት ስፈተን ትረባ አስለመድኳቸው።
.
"ምንስለሆኑ ነው እርሶ ሚካኤልን የማያስገቡት" ሙስሊም ናቸውና ይቀኑ ይሆናል ነጭ የለበሱ ጎረቤቶቻቸው ግቢውን አስታቅፈዋቸው ሲጠፉ። ሳቁ አይገልጸውም ፈነዱ! የወለቀ ሶስት ጥርሳቸው ፊት ሻሻቸውን ሳይጎትቱ። ተመልሰው ለመጡ አንጋሽ ጎረቤቶቻቸው እያወሯት ሰላምታቸውን አረዘሙ።
.
በቀደም ከውጪ ሲገቡ አይቼ..
"ከየት ነው?" ስላቸው ገቡልኝ
" ወክ ወጥቼ። ጠበስኩኮ!" 😂😂
ኦቲስቲኩ በሀይሉ ከውስጤ ምን ይላል...
"እንዴ በስተርጅና" ግም!
አፌ " መቼ ነው የሚያስተዋውቁን?"
አፋቸውን አፍነው 🤭 " በል አልችልህም ውጣልኝ"
.
ከሗላዬ...
"ሰላም ይመልስህ በል! ደና እደር..."
መቼም አመል ቶሎ አይለቅ።
.
እኚ ናቸው የሔዱት።

#በሃይሉ_ሙሉጌታ

@wegoch
‹‹አልተበላሸም››


÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷÷
1989 ዓ.ም.



አስራ ስድስት ዓመቷ ነበር፡፡ የአስረኛ ክፍል ተማሪ ነበረች፡፡ ድርስ ነፍሠ ጡር ነበረች፡፡



የልጇ አባት (የልጅሽ አባት ሲባል ደስ አይላትም፡፡ ያስረገዘኝ  ወንድ በሉ ትላለች) የሰባት ወር ቦይፍሬንዷ ነበር፡፡ ማርገዟን እንደሰማ ብን ብሎ ጠፋ፡፡



ለመጀመሪያ ጊዜ ያፈቀረችው ወንድ ነበር፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የሳማት፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰውነቷን የሰጠችው፡፡ 



ከብዙ ማባበል በኋላ ስትለምደውና ስትወደው በአንዱ ቀን እንዲህ አላት፤
‹‹አጎቴ ተከራይቶ የሚኖርበት ቤት እዚሁ ቤላ ጋር ነው፡፡ ለስራ ሐረር ሲሄድ ቁልፍ ሰጥቶኛል፡፡ ለምን እዚያ ሄደን በነጻነት ስናወራ አንውልም?››

‹‹አጎቴ ቤት ልወስድሽና ድንግልናሽን ልወሰደው ›› የሚል ወንድ የለ መቼስ፡፡ 



እጁን ይዛ ተከተለችው፡፡  የአጎቱ አንድ ክፍል ቤት በአግባቡ ከተነጠፈ ፍራሽ፣ ከብዙ መፅሐፍትና ከትልቅ ቴፕና አጠገቡ ከተዘረገፉ ካሴቶች በስተቀር ዐይን የሚገባ ነገር አልነበራትም፡፡



ፍራሹ ላይ አደላድሎ እንዳስቀመጣት ሰንደል ለኮሰ፡፡

‹‹ዘና እንድንል ነው፡፡ በዚያ ላይ ቤቱ ተዘግቶ ስለዋለ ይናፈስ ብዬ ነው›› ብሎ፡፡ 

‹‹ሰንደል በየት ሃገር ነው የታፈነ ቤት የሚያናፍሰው..?ይልቅ ለምን መስኮቷን አትከፍታትም?›› አላለችውም፡፡


‹‹አጎቴ ሙዚቃ በሃይል ይወዳል፡፡ የወጣ ካሴት አያመልጠውም፡፡ ቆይ ሰሞኑን የወጣ የፍቅራዲስ ካሴት አለ፡፡ እሱን ልክፈተው ለሙድ›› አላት ቀጥሎ፡፡
ለሙድ፡፡



ምንም አላለችውም፡፡


ከዚያ….



ፍቅርአዲስ ቤቱን በአስረቅራቂ ድምፅዋ ስትሞላው የእሱ ከንፈሮች አንገቷ ላይ ነበሩ፡፡


ሰላማዊት ተነክታ የማታውቀው ቦታ ስትነካ ፍቅርአዲስ አትርሳኝ እያለች በሚያባብል ድምፅዋ ታለቃቅስ ነበር፡፡

ፍቅርአዲስ ፣
‹‹ሄደሃል አሉ ብዙ ርቀህ እንደኔ ሆነህ አንተም ናፍቀህ
ምናለ ሆዴ ብትመጣልኝ ብታስብልኝ››  ብላ ስትለማመጥ
‹‹እንዲመችሽ ጃኬትሽን አውልቂው›› ብሎ እየተለማመጣት ነበር፡፡

በስልምልም ዐይኖቹ ሲለማመናት፣ በምትወደው ድምፁ ሲያባብላት ታዘዘችለት፡፡



በዚያ ላይ ቀኑን ሙሉ እህል አልበላችም ነበር፡፡ ከምሳ በፊት አስፎርፏት ስትወጣ ምሳቃዋን ረስታ፡፡
ሲገቡ ከሱቅ ካስመጣላት ሙቅ ሚሪንዳ በቀር ሆዷ ባዶ ነበር፡፡ 
እንደማቅለሽለሽ እያላት ነበር፡፡

እስከዛሬ ድረስ ሙቅ ለስላሳ አልጠጣም ብላ ስትከላከል ብዙ ሰዎች ‹‹ብርድ አይደል…ምን ማለትሽ ነው?›› ሲሏት አታብራራም፡፡ ግን ካልቀዘቀዘ ለስላሳ፣ በተለይ ሚሪንዳ አትነካም፡፡


እስከዛሬ ድረስ ፍቅርአዲስን ስትሰማ ዐይኖቿ በእምባ ይሞላሉ፡፡  ምን ሆንሽ ብሎ የሚጠይቃት ሲኖር መልሷ አንድ ነው፡፡

‹‹ድምጽዋ ደስ ስለሚለኝ ነው››
ግን ውሸቷን ነው፡፡ ፍቅርአዲስ በአትርሳኝ ሙዚቃ አጃቢነት በአንዲት ቀን አስረግዞ የረሳት የመጀመሪያ ቦይፍሬንዷን ስለምታስታውሳት ነው፡፡ ድምፅዋ ሃዘን የሃዘን በረዶ ያወርድባታል፡፡



ከሶስት ወራት በኋላ የኮከበ ፅባህን ግምብ ተደግፈው እያወሩ ‹‹አርግዣለሁ›› ስትለው አመዱ የጨሰው ሳሙኤል ብን ብሎ ጠፋ፡፡

ምስጢረኛ ጓደኞቿ ‹‹ድሮስ ከቅምቢቢት ዱርዬ ምን ይጠበቃል?›› ብለው አብረዋት አለቀሱ፡፡

አማራጭ ስላልነበራት ቤት ሄዳ የሆነችውን ስትናገር አባቷ ያለችውን የሰሙበትን ጆሯቸውን ማስቆረጥ ቢችሉ ደስ ይላቸው ነበር፡፡ እናቷም ከአንግዲህ ዐይኔ እንዳያይሽ አለቻት፡፡



ልብሷን ሸክፋ ወደ ብቸኛ መሸሸጊያዋ - ወደምትወዳት አክስቷ- ከመሄዷ በፊት ግን እናቷ ለሚቀጥሉት ሃያ አመታት ላትዘነጋው የወሰነችውን ነገር ተናገረቻት፡፡

‹‹ሕይወትሽን ጨርሰሽ አበላሽተሽዋል፡፡ ከእንግዲህ የትም አትደርሺም›› ብላ፡፡



እርግዝናዋ የኮከበጽባህ ትምህርት ቤት ርእሰ ሃሜት ሆኖ ቢከርምም በአክስቷ ፍቅርና ማበረታቻ ተደግፋ አስረኛ ክፍልን ከገፋ ሆዷ ጋር አገባደደችና ሰኔ 12/1989 ልጇን ወለደች፡፡


ሚካኤሏ አለቻት፡፡ የሰኔ ሚካኤል ልጅ ስለሆነች፡፡

አክስቷ ጥላ፣ አክስቷ ግድግዳና ማገር ሆናላት ሚካኤላን ከልጆቿ ጋር ስታሳድግላት መራር የእናቷን የእርግማን ቃል እንደምታመክን ቃል አስገብታት ነበር፡፡


‹‹ዛሬ ተሳስተሻል ማለት እስከወዲያኛው ሕይወትሽ ተበላሽቷል ማለት አይደለም፡፡ ይሄን እውነት ኖረሽ ካሳየሽኝ ልፋቴን ካስሽው ማለት ነው›› ብላ  የልጅነትእኩያ ልጇን ከጎኗ፣ የሰላማዊትን ጨቅላ በእቅፏ አድርጋ ስትመክራት ጉልበት ሆናት ነበር፡፡






ጥር 2016

የአርባ አራት ዐመቷ ሰላማዊት ከሃያ ስድስት ዐመት እኩያ ልጇ ሚካኤሏ ጋር እስክስታ ትወርዳለች፡፡
የሚካኤሏ ሰርግ ነው፡፡

በቅርበት የማያውቃቸው ሰው ሁሉ ደጋግሞ እንዲህ ይላል፡፡

ቀልዳችሁን ነው…እናቷ ልትሆን አትችልም፡፡ ታናሽ እህቷ ናት!
አይሆንም!
እውይ ደስ ሲሉ!
ታድለው!

ትንሽ ቆይቶ፣
ጭፈራው አድክሟት በሚዜና አጃቢዎቿ ታጅባ ከአዲሱ ባሏ ጋር የምትጨፍረውን ሙሽራ ልጇን እያየች ቁጭ ያለችው የሙሽሪት እናት ሙቅ ሚሪንዳዋን እየጠጣች ለራሷ-
‹‹ምንም የተበላሸ ነገር የለም፡፡ ሁሉም ነገር ግሩም ነው›› አለችና፤

ወዲያው በሰዎች ምርጫ ሙዚቃ ወደሚያጫውተው ዲጄ ለመሄድ ወሰነች፡፡


‹‹የፍቅርአዲስ ዘፈን ይኖረው ይሆን?›› ብላ እያሰበች፡፡

By Hiwot Emishaw

@wegoch
@wegoch
@paappii
ብ-ት-ን-ት-ን
-----------------------



ወላጆቼና አያቴ የጎረቤቶቻቸው ቤት ዘወትር በቦምብ እየተደበደበ፣ ጥይት እንደ ወፍ በጣራቸው ላይ እየበረረ ከዚህ ቦታ ሽሹ ብላቸውም አንገታችን ይታረዳል አሉ፡፡



ይሄ የወንድማማቾች ጦርነት ከተጀመረ አንስቶ ነጋ ጠባ ቀብር ላይ ናቸው፡፡ ባለፉት ጥቂት ወራት ማህበርተኞቻቸውን፣ አብሮ አደጎቻቸውን፣ ጎረቤቶቻቸውን፣ ዘመድ ወዳጆቻቸውን በየተራ፣ በሰልፍ ቀብረዋል፡፡ 



ትላንት ማታ ራሱ ወይዘሮ ታየች- የእማዬ የሴት ማህበር አጣጭ፣ የስንት ዘመን ባልንጀራና የታናሽ እህቴ የክርስትና እናት በሯ ላይ ተገድላ ተገኘች፡፡  ተባራሪ ጥይት ነው አሉ፡፡



‹‹በፈጠራችሁ ተለመኑኝ! አሁንም ከዚህ ሳይብስ ከዚህ እንሂድ›› ብዬ ተለማመጥኳቸው፡፡ ዛሬ ልመናዬ ውሃ ቢያነሳ ብዬ የደብራችንን ቄስ ለምኜ ይዤ መጥቻለሁ፡፡ አጠገቤ ቆመዋል፡፡



ካልሄድን ብዬ ልማለድ ስመጣ ይሄ አራተኛዬ ጊዜዬ ነው፡፡ ብዙ ሳትርቅ የምትገኘው ከተማ ውስጥ አነስተኛ አንድ ክፍል ቤት ተከራይቼ እኖራለሁ፡፡ ደልቃቃ ቤት አይደለችም ግን ቢያንስ ከጦር ሜዳው ሩቅ ናት፡፡



‹‹ልጄ! ቤታችን እዚህ ነው፡፡ ቀያችን ይሄ ነው፡፡ የት ነው ጥለነው የምንሄደው…?ለማን ጥለነው ነው የምንሄደው…? ጎጇችን ምን ይሆናል…እንስሶቻችንስ ማን ይይዝልናል?››  ብለው እንደ ሁልጊዜው አፍ አፌን አሉኝ፡፡




ቄሱ እምብዛም አላገዙኝም፡፡ ‘አረ እባክዎ እርዱኝ ! ›› ብዬ ብጠይቃቸው ይባስ ብለው፤
‹‹ተያቸው በቃ!  እንደ ፈቀዳቸው ይሁኑ፡፡ እዚሁ ይቆዩ›› አሉ፡፡
‹‹አባ! እዚህ ቆይተው ይሙቱ ነው የሚሉት?›› ብዬ እንደ መጮህ አደረገኝ፡፡ እማዬ አፍታም ሳትቆይ ቄሱን ልቆጣ በመድፈሬ ክፉኛ ተቆጣችኝ፡፡



ወዲያው ደግሞ ሁሉ ነገር ሰላም ይመስል ራት ሰርታ አብልታን ‹‹በይ አንቺ ነገ በጠዋት ወደ ሃገርሽ…ነገር ሳይጋጋል›› አለችኝ፡፡


እኔ እንድሄድ ይፈልጋሉ፡፡ እኔ እንዳልጎዳ ይፈልጋሉ፡፡


የአብዛኞቹ ከመንደሩ ወጥተው ከተማ የሚገኙ እኩዮቼ እጣ ፈንታ እንደሚደርሰኝ አውቀው ነበር፡፡ አንዱን ቀን ተደውሎ ቤታችሁ ጋዬ፣ እናት አባትሽ፣ አያትሽ ተገደሉ እንደምባል አውቀው ነበር፡፡


የእኔም ቤተሰቦች ተራ አሃዝ እንደሚሆኑ ልቦናዬ ያውቀው ነበር፡፡



ለመጨረሻ ልመናዬ ከመጣሁ ሳምንት እንኳን ሳይሞላኝ እንደማይቀርልኝ ያወቅሁትን መርዶ ተረዳሁ፡፡  ቤታችሁ በመትረየስ ተመቷል አሉኝ፡፡ እናትሽም.፣ አባትሽም፣ አያትሽም ሞተዋል አሉኝ፡፡



ከቀናት  ለቅሶ በኋላ ነገር ተረጋግቷል ሲባል እኔና ታላቅ ወንድሜ አውቶቢስ ይዘን ወደ ድሮ ቤታችን ተጓዝን፡፡


አይ ቤታችን እቴ! ቤታችን ወደነበረበት ባዶ ሜዳ ብል ይቀላል፡፡

ማልቀሱንስ ሳለቅስ ነው የከረምኩት፡፡



ነገር ግን እማዬ አባዬ እንደነገሩ አጣጥሮላት እንደ ጭስ ቤት የምትጠቀምበት ቦታ ላይ ያ የምወደውን ምስር ወጥ የምትሰራበት ሸክላ ድስት ብትንትን ብሎ ሳየው ግን ለአባባይ እስካስቸግር ማንባት ጀመርኩ፡፡



እኔ ልበታተንልሽ አባዬ፡፡  እኔ ብትንትን ልበል የኔ ዓለም፡፡

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Hiwot emishaw
"ትንሽ ቦታ"

ስሜታዊ ሆኖ ለተናገረን ፣ ሊረዳን ፈልጎ ለሳተ ፣ ኑሮ አስክሮት ለገፋን ፣ ንዴት ገፍቶት ላጠፋ ፣ ግዜ አጣሁ ብሎ ላልጎበኘን ፣ ስናሸንፍ ላላጨበጨበ፣ ስንወድቅ ላላነሳን ፣ ስናስብለት ላልተረዳን ፣ ማደጋችንን ላላየ ፦

"ትንሽ ቦታ ለይቅርታ" አኑረናል

አማረልን ብለን ላሳዘንን ፣ አጉል ተስፋ ለሰጠነው ፣ ውድቀት ላይ ለሳቅነው ፣ ብልግናን ላጎላናው ፣ ድድብናን ላነፈስነው ፣ ማድረግ ችለን ላላደረግነው ፣ ችለን ለተጣመምነው ።

ለራሳችን ይቅርታ አደርገናል...

ቺርስ ለአዲስ ዘመን
ቺርስ ለተስፋችን
ቺርስ🙏.


By Adhanom Mitiku

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሌሶቶ

በዝግታ የሚራመዱ ሰዎች ሃገር (Kingdom of the mountains ይላሉ ራሳቸውን ሲያቆላምጡ)
ከፍ ካለ ተራራማ ሃገር ስለመጣሁ "Kingdom of the slow walkers" እላቸዋለሁ እኔ ደግሞ።

ማሴሩ ተራሮች መሃል የከተመች ከተማ ።
ፀጥ ያለች
የተረጋጋች
ወከባ የማይታይባት።

እግረኞቿና አሽከርካሪዎቿ ብንሮጥም የትም አንደርስም የሚሉ ይመስላሉ።

በጠራራ ፀሃይ ብርድልብስ እና ቦት ያደረገ በግ ነጂ ከጂፕ ነጂ ጋር የሚተላለፍባት፣

ደረቅ፣ ነፋሻማና ቀዝቃዛ
(መዘዞ፣ መሃል ሜዳ ወዘተን የምታስታውስ)፣

ሁሉንም ሱቆቿን 12 ሰአት ላይ ዘግታ ወደ ቤቷ የምትከተት፣

በአንዱ የተራራ ጫፍ ትልቅ ነጭ መስቀል የሰቀለች፣ በዚህም አዲግራትን የምታስታውስ።

ባገሬ መስከረም መጋቢትን የመሰለ ደረቅ ወቅት ላይ ተገኘሁ።
እዚህ የክፍል ማሞቂያ 25 ላይ ይደረጋል ከቅዝቃዜ ለመሸሽ (እንደ ኳታር ባለ ሃገር ደግሞ ማቀዝቀዣ 25 ላይ የሚደረገው ከውጪው ሙቀት ለመሸሽ ነው።)

2800 ሜትር አናት ላይ አድጌ 1600 ሜትራቸውን ማድነቅ አልቻልኩም። በመጓዝ ብዛት የገባኝ ተራራ ለብዙ የአፍሪካ ሃገራት ብርቅ መሆኑ ነው /ደብረሲናን፣ ደሴን፣ አሰላን፣ አርሲ ቀርሳን፣ አዲስአበባን ላየ ሰው ማሴሩ የጉብታ ከተማ ነው/።

የዚህ ሃገር ሰዎች ንጉሳቸውን ይወድዳሉ።
ወይም የሚወዱ ይመስላሉ።

ከባድ ባለስልጣን የተባለው ብርድልብስ ለብሶ ስብሰባ ሊመጣ ይችላል።

ሁሉም በሚባል ሁኔታ ክብ ባርኔጣ ያደርጋሉ።

ዶላር ወደ ሌሶቶ ሎቲ መቀየር ፈልገን ካረፍንበት ሆቴል ፊትለፊት ወዳለ ካፌ ነገር መሩን። ሃበሾች ተሰብስበው ያወራሉ። የካፌውም ባለቤት፣ ዶላር ቀያሪውም የኛው ሰዎች ናቸው። ባልተለመደ ሁኔታ እዚህ የሚኖረው ሃበሻ አብዛኛው Expat ነው። የ አፍሪካ ህብረት፣ የ UN ሰራተኛ ወይንም በፕሮጀክቶች የተቀጠረ ሃኪምና ኢንጂነር።

" አንድ የሃበሻ ሬስቶራንት አለ ለበአል እዚያ እንወስዳችኋለን" አሉን።

ድሮ ድሮ የበአል መንገድ ያማርረኝ ነበርና
አንድ ቀን እናቴን
"መንገድ አማረረኝ የበአል ሰሞን ልቅርና በአዘቦት ቀን እየመጣሁ ልጠይቅሽ?" አልኳት።
መለሰች
" ስንት በአል የምናከብር ይመስልሃል ከዚህ በኋላ? ስሞት ትቀራለህ አትቸኩል።"

ዛሬ የአደይ አበባ፣ የበአል ግርግር፣ የመስከረም ምልክት አንዱም በማይታይበት ከተማ ሆኜ ንግግሯን አስታወስኩ።
እንቁጣጣሽ ሲያመልጠኝ ሁለተኛዬ ነው (የዛሬ አመት በጦርነት ምክንያት መንገድ በመዘጋቱ፣ ዘንድሮ በስራ)። ስንት እንቁጣጣሽ እንደቀረኝ ባላውቅም፣ ለኔ ለራሴ የበአል ጉጉቱ ባይኖረኝም ከቤተሰቤ ጋር(ከምወዳቸውም ሁሉ ጋር) የሚኖረኝ ጊዜ የተገደበ ነውና አለመገኘቴ አስደበረኝ።

የመንገዱ ሰልፍና ምሬት፣ የበአል ገበያ፣ የበአል ዘፈኖች፣ የእናቴንና እህቴን ቤት ውስጥ ወዲያ ወዲህ ማለት፣ የአባቴን ደጁን ለእርድ ማስተካከል፣ የወንድሜን ለቅዳሴ ለመሄድ መዘጋጀት፣ አልፌ የምሄድባቸውን አረንጓዴና አበባ የለበሱ ሜዳዎችና ተራሮች እናፍቃለሁ።

ከቤተክርስቲያን መልስ ስለምንበላው ጥብስ፣ ከፋዘር ጋር ተጋግዘን ስለምንገፈው በግ፣ በደምብ ስለማላውቃቸው ጎረቤቶች፣ ስለ ብዙ የስልክ ጥሪዎችና መልዕክቶች፣ ስለ ድፎ ዳቦ፣ ስለ ቡና አስባለሁ።

እዚህ ያለው ቡና በጣም ቢቀጥንብኝ ከኢትዮጲያ መሆኔን አውቃ "ሰላም ነው?" ያለችኝን አስተናጋጅ ፈልጌ ጠራሁ።
"This coffee is too weak I need somthing strong"
"Our coffee is not like yours".

የጀበና እጣቢ የሚመስል ነገር እየጠጣሁ አለሁ። ሆድ ለባሰው ....

ከበአል ድባብ ያላመለጠኝ ብቸኛ ነገር የፌስቡክ ፖስትና የቴሌግራም ስቶሪ ነውና ....

ሁላችሁንም እንኳን አደረሳችሁ።
መልካም አዲስ አመት።

ወንድማችሁ ነኝ ከጉብታዎች አናት ማሴሩ።

By haileleul Aph

@wegoch
@wegoch
@paappii
«ካባዬ»
(ከለእርቃን ሩብ ጉዳይ መፅሐፍ)

ክፍል አንድ

------------
ይሄንን ኮንዶሚኒየም ቤት ለማግኘት ከሦስት ወር በላይ ተንከራትቻለሁ።

ኪራይ ነው።
ዛሬ ዛሬ አዲስአበባ ላይ ፍላጎትንም፣ አቅምንም አጣጥሞ የሚገኝ የኪራይ ቤት
ማግኘት ሕልም ነው። እኔ ደግሞ የብር ችግር እንደሌለበት ሰው ስመርጥ ዐይን
የለኝም። ሀብታም ስላልሆንኩ ጠባብ ቤት መኖር ይፈረድብኝ፣ ግን ጠባብም
የተግማማም መሆን አለበት?



የለበትም።
ለዚህ ነው ይህንን አራተኛ ፎቅ ላይ የሚገኝ በጣም ጠባብ ግን ንጹህና ሰላማዊ
ስቱዲዮ ኮንዶሚኒየምለማግኘት ሦስት ወራት የፈጀብኝ። ከንጽሕናው ፀጥታው፣
አራተኛ ፎቅ ጥግ ላይ ክትት ብሎ መገኘቱ ማረከኝና ተከራየሁት።


ግን ይሄ ታሪክ ስለ ተከራየሁት ስቱዲዮ ኮንዶሚኒየም አይደለም።
ስለንጽሕናውና ስለፀጥታውም አይደለም። ስለሰፈሩ ከተማ መሀል መገኘትም
አይደለም። ስለ አዲሷ ጎረቤቴ እትዬ እማዋይሽ ነው።


ታኅሳስ ላይ ቤቱን ቀለም አስቀብቼ፣ እቃዎቼን ሸክፌ ገባሁ።


በገባሁ ዕለት ነው እትዬ እማዋይሽን ያገኘኋት እና የተዋወቅኳት።

ቅዳሜ ነበር። ከቀኑ ዘጠኝ ሰዐት ይሆናል።

እሷ፣ ፎቁን እያረፈች እንደወጣች በሚያስታውቅ ሁኔታ ትንፋሽዋ ቁርጥ ቁርጥ እያለና እያለከለከች በሬ አጠገብ የሚገኘው በሯ ጋር የቤቷን ቁልፍ እያንቀጫቀጨች ስትደርስ፣ እኔ ደግሞ ውስጥ ያለውን እስካስተካክል ውጪ የተውኳቸውን ኮተቶቼን ወደ ቤት ለማስገባት ስወጣ ነው፣ ፊት ለፊት የተገጣጠምነው።

እንዳየኋት የተሰማኝ ነገር ያለቦታዋ የምትገኝ ሰው መምሰሏ ነበር።

በዕድሜ ስልሳ ቤት ትሆናለች።

ነገር ግን ሙሉ በሙሉ የሸበተው ጸጉሯ ብዙ ጊዜ ዕድሜያቸው የሄደ ሰዎች ላይ እንደማየው ስስና እንክብካቤ ያጣ አልነበረም። ዘንፋላና በሥነ-ሥርአት የተተኮሰ ነበር። አለባበሷ አሁንም በእሷ ዕድሜ ያሉ ሴቶች እንደሚዘወትሩት ሰፊ ልብስ ላይ ሌላ ሰፊ ልብስ፣ ግራጫ ቀለም ላይ ቡናማ፣ ወፍራም ሹራብ ላይ ወፍራም የአንገት ልብስ ዓይነት አልነበረም።
ደልደል ያለና ውብ ሰውነት አላት።

በልኳ ግን ሳይጠብ የተሰፋ ቆንጆና ደማቅ ቢጫ ቀሚስ፣ አጠር ካለ ሰማያዊ ክፍት ሹራብ ጋር ለብሳለች። ተረከዙ አጭር፣ ፊቱ ሹል ጥቁር ጫማ አድርጋለች። የምታምር ትንሽዬ ቡናማ ቦርሳ አንግታለች።

ደርባባ ነች። ዘንጣለች።

“እንዴት ዋልሽ ልጄ?” ስትለኝ ነው ዕድሜዋን ከዝነጣዋ ያስታረቅኩት።

“ደህና ይመስገን” አልኩኝ ፈጠን ብዬ።

“ጎረቤትሽ ነኝ… እንኳን ደህና መጣሽ… እማዋይሽ እባላለሁ”
“አመሰግናለሁ… ኤደን እባላለሁ” መለስኩላት።
“ሳናግዝሽ ገባሽ… አሁን ምን ልርዳሽ?” አለች ዐይኖቿን ተመሳቅለው
የተኮለኮሉት ውጪ የተዘረገፉ እቃዎች ላይ አሳርፋ።

“ግዴለም ብዙ አይደለም ጨርሻለሁ” አልኩ አሁንም ፈጥን ብዬ።

“በይ ስትረጋጊ ቤቴ ነይና ቡና ጠጪ” አፈር አልኩና፣

“አይ…. እሱ እንኳን ሌላ ቀን” አልኩ። እያግደረደረችኝ ከሆነ መግደርደሬ ነበር።

“ኖንሴንስ… እያግደረደርኩሽ አይደለም… ጎረቤት መተዋወቅ አለበት። ቡና
ማፍላቴ ስለማይቀር እቃሽን ቦታ ቦታ አስይዢና እንጠጣለን”

አሁን ጥያቄ አልነበረም።

ትልቅ ሰውም ስለሆነች፣ ጥያቄም ስላልነበር ምርጫ አጥቼ እሺ አልኳት።
ዐሥራ አንድ ሰዐት ገደማ ላይ የብረት በሬ ተንኳኳች።

እማዋይሽ ነበረች።

“ነያ ቡናው ደርሷል” አለችኝ።

በሬን ቆልፌ ተከትያት ቤቷ ገባሁ።

ቤቷ፣ አዲስ በተቆላ የቡና ጠረንና ለአፍንጫ በሚጥም ዕጣን ጭስ ተጨናንቃ
ተቀበለችኝ።

ረከቦትና ስኒዎቹን በዐይኔ ብፈልግ የሉም። ዕጣን ማጨሻውን ለማግኘት ብሞክር
አልቻልኩም።

ከመቀመጤ፣ “ዛሬ ገብተሽ መቼስ ምግብ አልሠራሽም” ብላ ምን የመሰለ
ፍርፍር አበላችኝ።

ጎንደር ያለችውን ባለሙያ እናቴን አስታወሰኝ።

(ይቀጥላል)

By Hiwot Emishaw


@wegoch
@wegoch
@paappii
< "እናርግ" አለኝ እኮ፣ ያ ውሻ >

ምናለበት እሺ ብትዪው ? ምትወጂው ከሆነ ስሜቱ ለጋራ ነው ፣ አይደለም እንዴ?

< አንተ ሐይሚን አርገሀታል? ንገረኝ። >

"አድርገሀታል" ማለት? ምን አደረኳት? "

< ሒይ ! እያወክ አትገግም። >

"በድተሀታል ወይ ? ማለት ፈልገሽ ከሆነ ፣ በድቻታለሁ። ብድትድት ነው ያረኳት። ካንቺ ጓደኞች ያልበዳሁት የለም። "

< እህ ? ውሻ! ውሻ ነህ ።>

አዎ ነኝ ! ዉው ዉው ኣዉዉዉዉዉ ። ሀያትንም በድቻታለሁ።

ሀያት ነች ያስተዋወቀችን። ሀያት የጥቁር ቆንጆ ፣ እንደ እሳት ቅልብልብ ፈጣን ውልብልብ እጅግ ብልህና በትምህርትም ጎበዝ ተማሪ የነበረች ናት። ኤለመንተሪ ከሀያት ጋር ስንማር ጥያቄ ና መልስ ውድድር እኔና እሷ ከፍላችንን እየወከልን ዞረናል። ሀይስኩል እንደገባን ሀያት ናት ከዚህችኛዋ አለም ጋር ያስተዋወቀችን። ከአስረኛ ክፍል በሁዋላ ሀያት የት እንደገባች አናውቅም። እኔና አለም ግን አስር አመት ሆነን። በጓደኝነት። ንፁህ የሚባለው አይነት ጓደኝነት።

*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*

አለም

< ወዬ >

" አለም የሚል ስም ይዘሽ እንዴት መንፈሳዊት አማኝ ሆንሽ ? "

< አንተማ ለይቶልሀል። >

ሁሌም ከፍቅረኞቿ ምትለያየው የወሲብ ጥያቄ ሲያቀርቡላት ነው። እሷ "ከጋብቻ በሁዋላ" ትላቸዋለች። እነሱ ጥለዋት ሲሄዱ መጥታ እኔ ላይ ታለቅስብኛለች። ይበዳኛል ብላ ሰግታ አታውቅም።

እኔ ብበዳሽስ ? እላታለሁ።

ሁሌም < ሐይሚን አርገሀታል? እስካሁን ስንት ሴት አወጣህ? > ትለኛለች።

"ስንቷን ሴት ስንት ስንት ጊዜ እንዳወጣሁ ልንገርሽ ? ሐይሚን ...ሐያትን ደሞ እእእ ?"

< ኡህ! አንተስ ባልገሀል >

ትለኛለች።

*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*

በስጋ እናትም አባትም። ቤተሰቦቿ አሳዳጊዎቿ ናቸው። እና እኛ። እኛ ማለት እኔና ሌላ ማላውቃቸው ጓደኞቿ።

< አንተ ቤተሰብ ስላለህ እድለኛ ነህ > ትለኛለች።

" እኔ ቤተሰብ እዳ ነው " እላታለሁ።

*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*

ያኔ ሐያት ከእሷ ጋር ካስተዋወቀችን ማግስት ወደኔ ክላስ እየተጎተተች መጣች። ፀይም ነበረች ግን አመዳም። ፀጉሯ ረጅም ነው፣ ግን ደረቅ ነው። ጥቁር ሻርፕ አንገቷ ላይ ጣል ታደርጋለች ፣ ለምን እንደምታደርግ አይገባኝም። እናም ያግባባን ብቸኛ ነገር እኔ ብልህ እንደሆንኩ ማሠቧ ና እሷ ብርቱ ስለሆነች ከእሷ ጋር እንደምስማማ ስለምታስብ ነው።

እኔስ ? እኔ ትምህርት ላይ እየቀነስኩ አሪፍ መስሎ መታየት ላይ እየበረታሁ ነበረ። ቀንደኛ ቀልደኛ ሚባሉት ተማሪዎችን ጎራ ተቀላቀልኩ። ሁሉም ጓደኞቼ ድንግል ሆነው ሳሉ ቀድሜ ገርልፍሬንድ ያዝኩ፣ ቆንጆ ሴት፣ ከሌላ ክፍል፣ ሐይማኖትን ። በርግጥ ኤለመንተሪ እያለሁ የሔርሜላን አንገት ስሜያለሁ። ከነሱ መፍጠኔ ለእኔ አይገርመኝም።

እና ይህቺ አለም < ትምሕርትህ ይበጅሀል። እሷን ተዋት። ገና ልጅ ነህ። ደግሞም ቆንጆ አይደለችም።> ትለኝ ነበረ።

ግን ሁለታችንም በእድሜ እኩያሞች ነን። እሷን መካሪ እኔን ተመካሪ ያደረገን እሷን ለይቶ የመከራት ኑሮ ነው።

ኑሮ ያስተማራትን ትምህርት በደንብ ይዛዋለች። ፈተናውንም አልፋዋለች። አሁን ዘናጭ ነች። ፀይም መልኳም ፀጉሯም ወዝ ኖሮታል። ለስራ ሌላ ሀገር የሄደች ጊዜ ገንዘብ እኔ አበድራት ነበረ። ሁለት ጊዜ ሌባ ሙልጭ አድርጎ ዘርፏታል። አሁን እኔ ገንዘብ ሲቸግረኝ ከእሷ ነው የምበደረው። የወር ገቢዋ ከእኔ የወር ደመወዝ አስር እጥፍ ነው።

*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*_*

አስረኛ ክፍል ተዋወቅን ፣ አስር አመት አብረን አሳለፍን ። አሁን ልታገባ ነው። ሰርጓ በቅርብ ነው።

<አንተ መቼ ነው ምታገባው ? >

ብዙ ፍቅረኞች አሉኝ ። የቷን ላግባ?

< ባለጌ

ሐይሚን አሁን ብታገኛትስ ? >

አስር አመት ሙሉ ሐይሚን ያልረሳሻት ለምንድን ነው ?

< ሐይሚን አይደለም ያልረሳሁት። ያንን የግቢውን ቆንጆ፣ ብልህና ትንሽዬ ልጅን ልረሳው ያልቻልኩት። የአስራስድስት አመቱን ያንን ናሁ መሆን እፈልግ ነበር። አሁን ላይ ግን እዚህ ሆነን ደግሜ እሱ ራሱን ሆኖ ማየት እመኛለሁ >

" እመኚኝ። እኔ ምንም ከስሬ አላውቅም። እናም የራሴን መንገድ አገኛለሁ። ሚስትም አገባለሁ።

አንቺ ትንሽ ቀደም ብለሽ ሒጂ። አግቢ። እኔ ባንቺ መንገድ አልሄድምና። መልካም መንገድ። መልካም ጋብቻ።

ለባልሽ የምነግረው ነገር አለኝ ፦ " እሷን እቅፌ ላይ ለብዙ ቀን እንዳሳደርኳትና ከእሷ ገላ ላይ የወሰድኩት ምንም ነገር እንደሌለ ነው።

ስላልፈለኩ። ወይ ፈልጌ ስላልቻልኩ። ወይ ችዬም ታማኝ ሆኜ ይሆናል።

እኔ ባለቤቷ ነኝ። አሁን አንተ ባሏ ልትሆን ነው። ይትባረክ"


By Nahu senay

@wegoch
@wegoch
@paappii
የሄደበትን የመጨረሻ ቀን አስባለሁ።

ኩራቱን ተገፎ ሀፍረትን ተከናንቦ እርቃኑን እንደቆመ ሠው ዐይኔን ሽሽት አንገቱን ደፍቶ መሬት መሬት እያየ "እሜትዬ በድዬሻለሁ…" ያለበትን ቃና እሰማለሁ። ምህረት ፍለጋ ለይቅርታ አልመጣም ነበር። አንዳንድ ሀጥያቶች ስርየት የላቸውም፤ ስለአንዳንድ በደሎቻችን ከራሳችንም እርቅ አይኖረንም። ለዋለው ክህደት ይቅርን አልፈለገምና የኔ ይቅር ማለት ትርጉም አልነበረውም። የኔ ምህረት መስጠት ኩራትና ክብሩን ከወደቀበት ሊያነሳለት አቅም አልነበረውም። አንገቱን ደፍቶ በገባበት በር አንገቱን ደፍቶ ሲወጣ ቃል አልወጣኝም። አልተከተልኩትም በዐይኔ አልሸኘሁትም። ልቤ መመለሱን ቢሻ ከበደሉ ሊያልቀው ግን አልተቻለውም። በሰው ለውጦሻል ተይው ይሂድ አለ፡፡ ተውኩት፣ ሄደ…አልተመለሠም ።

ዘመናቶቼ መኸል ግን እጠብቀው ነበር። አንዱን ቀን ይመጣል ብዬ በር በሩን አማትሬያለሁ። ወሬውን ፍለጋ ጆሮዎቼ እልፍ ጊዜ ቆመው የደጁን ድምፅ ሲቃርሙ ኖረዋል። ብዙ ጠብቀዋል፤ ለማንም ሳልነግር በደሉን ውጫለሁ። ባሻዬ ከዳኝ ሳልል ይቅር ብዬ ነበር። ፍለጋ ባልወጣ የት ሄደ ባልል በልቤ በእየዕለቱ 'አንተ ትሻላለህ፤ ተመለስ ግድ የለም' እል ነበር።

እወደው ነበር፤ ኩራት በሸበበው ፈገግታ ቢደበቅም ቅሉ ሳየው ልቤ የፈካ ቀለምን ትፈነጥቅ ነበር። እንደነዛ የመጀመሪያ ቀናት ጠጁን እየተጎነጨ ጓዳውን ሲያማትር በዐይኑ ሲፈልገኝ ትንሿ ልቤ በመጋረጃ ተከልላ እያየች ትደልቅ እንደነበረው፤ እንዲያ…እንዲያ እወደው ነበር። እነዛ ጊዜ ሸምኗቸው ጋቢ ሆነው የለበሳቸው የጥጥ ማጎች ስለሱ እያሠብኩ ሳሾራቸው፤ ተበጥሰው እንደተንከባለሉ ስንት ወድቀው ስንት እንደተነሱ፤ ስንት እንዝርት እንደሰበሩ አያውቅም፤ አልነገርኩትም ለፍቅር ሰነፍ ነበርኩ ።

By Beza Wit

@wegoch
@wegoch
@paappii
አገባሁ...ወለድኩ...ደገምኩ...ሠለስኩ:: እሱን እያፈቀርኩ ከወንድሙ ሦስት ልጆች ወለድኩ:: እሱን እየተመኘው ወንድሙን አገባሁ:: ካሳለፍናቸው 3 የUniversity ጓደኝነት አመታት በኃላ እንደተመረቅን ነበር ላገኘው እንደምፈልግና ብቻውን እንዲመጣ የነገርኩት ገና ተደላድሎ ከመቀመጡ ነው " አፈቅርሀለው" ያልኩት ::ሳቀ በሀይል ሳቀ
"አንቺ ያምሻል እንዴ ለቁም ነገር ነው ምፈልግህ ስትይኝኮ ምን ሆነች ብዬ ስንት ነገር ነው ጥዬ የመጣሁት ትቀልጃለሻ አንቺ ሆሆ " አየሁት .. እነዛ መጀመሪያ ካየዋቸው ቅፅበት ጀምሮ ራሴን ያሳጡኝን አይኖቹን ትኩር ብዬ አየዋቸው ::ሚያረገው እየጠፋው ሁሌ እንደሚጠራኝ
" ቃሊ የምርሽን ነው እንዴ "
"አዎ አፈቅርሀለው" ፊቱን በአንዴ ወደ ግራ የተገባ ፊት ቀይሮ " ከመቼ ጀምሮ ቃሊ?"
"ከመጀመሪያው የሁለተኛ አመት የትምርት ቀናችን ከማክሰኞ ከመስከረም 22 ጀምሮ" ደነገጠ " ቃሊ please አታሹፊብኝ " ፊቱ ሲቀላ እየታወቀኝ መጣ
"ምንም እንድትለኝ አይደለም ብንጋባ ብታፈቅረኝ ምንምን በደስታ ልሞትብህ ስለምችል አላቅም ግን እህቴ ነሽ ምናምን እንዳትለኝ ደሞ" መንተባተብ ጀመርኩ ::
"ቃሊ"
"ወዬ" ልቤ በፍጥነት ስትመታ ይታወቀኛል
"ኤላኮ ያፈቅርሻል" ፊቱ ማላቀውን እሱን ሆነብኝ..ውስጤ ሲፈረከስ ተሰማኝ ኤላ ማለት? ኤላ የሱ ወንድም? ማለት መንታ ወንድሙ ኤላ ? ኤላ ጓደኛዬ? ኤላ ኤላ ውስጤ ተተራመሰ.....በመልክም በአመልም ምንም አለመመሣሠላቸው ሲገርመኝ ነበር ሶስቱን የጓደኝነት አመታት ያሳለፍነው :: ሁሌም አብረን ነበርን እሱም..ኤላም...እኔም :: በሁለት መንታ ወንድማማቾች መሀል ያለው ብቸኛ ጓደኛቸው በመሆኔ ጊቢ ውስጥ እንደኔ ደስተኛ ሰውም የነበረ መኖሩን እኔንጃ እኔን መሀል አርገው ሲተራረቡ መስማት...ሲበሻሸቁ...አንዳቸው እንዳቸው ላይ ሲቀልዱ ...እጄን የኔው ተፈቃሪ እንደቀልድ በቦክስ ሲመታኝ ኤላ ሲቆጣው...ተሸክመውኝ ሲሯሯጡ ላየን 3 መንታዎች እንጂ ማልዛመዳቸው መሆኔን ማንም አይጠረጥርም አንዳንዶቹ ደሞ የማንኛው ናት እንደሚሉም አቃለው :: የጊቢው ሴቶች ደሞ ኤላን ይወዱት ስለነበር እንዳጣብሳቸው ሚወተውቱት እኔን ነው ኤላ ግን ወይ ፍንክች ስለሚል ማጣበሱ አልተሳካልኝም ነበር :: ሲፈጥረኝ ከሴት አትዋደጂ ያለኝ ይመስል ከልጅነቴ ጀምሮ ሴት ጓደኛ ኖሮኝ አያውቅም ጊቢ ገብቼም የመጀመሪያውን freshman አመት ከማንም ጋር አልግባባም ነበር ከዛ ግን ሁለተኛ አመት ላይ ምንማረውን ትምርት መርጠን ስንመደብ እነሱን አገኘው ለዛም ነበር በጓደኝነታችን ደስተኛ የነበርኩት :: ከ6ኪሎ ጊቢ በታች ያሉ ማሚ ቤቶች ሄደን ምሳ ስንበላ በእጄ ከአንድ ጉርሻ በላይ ስጎርስ አላስታውስም በሁለቱ የፉክክር ጉርሻ ነበር ጠግቤ ምነሣው በዛ ላይ ሳየው ገና ልቤ የደነገጠለት ልጅ ጓደኛ ሆኜ ስስቅ መዋል ..ደስታ ማለት እኔ ነበርኩ:: "ጉድና ጅራት ወደ ኃላ ነው" አሉ....ያን ቀን "ኤላኮ ያፈቅርሻል " ሲለኝ ጉሮሮዬም ልቤም አይምሮዬም ደረቀብኝ ጎኔ ያለውን ግማሽ ኮካ አንስቼ ጨለጥኩት ::
"ኤላ የቱ" አይኖቼ ሲፈጡ ይታወቀኛል
"ቃሊ ኤላ የኛ ነዋ "ፊቱ የማላቀው ቋንቋ ፅሁፍ ሆነብኝ አየዋለው አይገባኝም ::
"ከመቼ ጀምሮ?" እሱ እንዳለኝ እኔም አልኩት ማወቄ ይቀይረው ያለ ነገር ይመስል
"ካየሽ ቀን ጀምሮ ቃሊ ትዝ ይልሻል class እንደጀመርን ካፌ አጊኝተንሽ ብቻሽን ከምትበዪ ከኛ ጋር ምሳ አብረን እንብላ ብዬሽ አብረሽን የዋልሽ ቀን " እንዴት እረሳዋለው ያን ቀን በአይን ካፈቀርኩት ሰውጋር አምላክ አገናኘኝ ብዬ በደስታ ስፈነድቅ ነበር የነጋው :: ፀጥ ብዬ ሳየው ወሬውን ቀጠለ "ያን ቀን ማለት ኤላ ካላስተዋወከኝ ብሎ ሲለምነኝ ነበር ታውቂያለሽ ቃሊ ኤላን ከማህፀን ጀምሮ ሳውቀው ከአፉ ወቶ ሚያውቀው የሴት ስም ያንቺ ብቻ ነበር :: ቃሊ ኤላ አንቺን ስለማግባት ካንቺ ስለመውለድ ብቻ ነውኮ ሚያልመው ደሞ እሱም ከዛሬ ነገ እነግራታለው እያለ ነውኮ የተመረቅነው ቃሊ ኤላን ያዢው ወንድሜ እስከነፍሱ የሚያፈቅራት ሴት ታፈቅረኛለች ብሎ ማሰቡ ለኔም በሽታ ነው ቃሊ ደና ዋይ ኤላን ያዢው" ብሎኝ ነበር በተቀመጥኩበት ጥሎኝ የሄደው "ኤላን ያዢው" ይሄን ነበር ያለኝ :: .....እኔም ኤላን በእጄ በልቤ እሱን ይዤ ይኸው ሶስተኛ ልጃችንን ወለድን:: .....ኤላ ህልሙን ኖረ እሺ እኔስ?? የሱ ህልም ማስፈጸሚያ ልሆን ነበር የተፈጠርኩት? ያፈቀሩትን ስለማግኘት ኤላ ያሟላው እኔ ያጎደልኩት መስፈርትስ ምን ነበር??? ልጆቼስ አጎታቸውን በልቤ አግብቼ እንደምኖር ያወቁ እንደሆነ እንዴት ይዳኙኝ ይሆን ? እንጃ....ሁሉም ያፈቀረውን አያገባም..ልክ እንደኔ::


By ቃል_ኪዳን


@wegoch
@wegoch
@paappii
God,have mercy! This woman is so obsessed with her life. With her home and her family.

በጠዋት ትነሳለች ቁርስ ትሰራለች ቤተሰቦቿን ታበላለች ታጠጣለች መጥገባቸውን ታረጋግጣለች ከዛም ወደየሚሄዱበት ትሸኛቸዋለች። ቀጥላ ወደቤቷ ጽዳት ፣ ወደእንጀራ ጋገራ ፣ ምሳ ማሰናዳት ወዘተ.... አቤት ያላት ፅናት! ለጉድ ነው! ቤት ጠርጋ ወልውላ አጫጭሳ ልብሶች አጥባ እቃዎቹ ታጥበው ደርቀው በየቦታቸው ተደርድረው።
ወጡ ችክን ብሎ ተሰርቶ፣ ቡናው ትክን ብሎ ፈልቶ እጣኑ እየጤሰ ምሳ 'ሳት ይደርሳል። በር በሩን እያየች የቤተሰቧን መምጣት ትጠብቃለች ሲመጡላት በሚገባ ታስተናግዳቸዋለች።

በፈገግታ እና በምግብ ከፈወሰቻቸው በኋላ መልሰው ወደየሩጫቸው! "አመሠግናለሁ"ን እንኳን ሳትጠብቅ በሳቅ በፈገግታ ሸኝታ ወደቤቷ! የተበላበትን የተጠጣበትን እቃ አጥባ፣ የተዝረከረከውን ቤት አበጃጅታ ስታበቃ ደግሞ ለእራት ዝግጅት ጉድ-ጉድታዋን ትጀምራለች። ጣፋጭ ምግብ አብስላ፣ ሙቅ ሾርባ ሰርታ ቤቷን አሟሙቃ ትጠብቃለች። ወዳሞቀችው ጎጆ ይሰበሰባሉ ከእጇ ፍሬም ይበላሉ።

ይሔ ብቻ አይደለም she is psychiatrist ,she is economist, she is event organizer, she is expert in negotiation and an incredible socialist!

ይህች ሴት እናቴ ናት❤️

ምኞትሽ ምንድነው ብባል " እንደሷ መሆን" እላለው።


By Magi

@wegoch
@wegoch
@paappii
2024/09/21 03:02:21
Back to Top
HTML Embed Code: