Telegram Web Link
🎨 የስራ ቦታዎን በ wallart ማስዋብ  ይፈልጋሉ?
ይደውሉልን!
በተጨማሪም
🟠LOGO
🟡ለ ካፌ እና ሬስቶራንት
🟡ለ ጌም ዞን
🟡ለ ህፃናት ክፍል  እንዲሁም ማንኛውንም የ ግርግዳ ላይ ሥዕል እንስላለን!
@gebriel_19
+251984740577
ይደውሉ

@seiloch
@seiloch
አትዩኝ አለቅም!


በአሁኑ ወቀት ካለው የኑሮ ደረጃ በመካከለኛ የኑሮ ዘዬ ውስጥ እንደ ሚኖር አለባበሱ ያመለክታል። በግምት 24 ዓመት ይሆነዋል። ጠይምነቱ ኢትዮጵያዊነቱን ያበራል፤ እንደከሰል የጠቆረ ጂንስ ሱሪ ሃጫ በረዶ በመሰለ ነጭ ሸሚዝ ለብሷል፤ ቡኒ ጫማ እንደ ተጫማ አይኔ አይክድም፤ ለዝነጣ ልበለው ለፀሀይ ጠቆር ያለ መነፅር አጥልቋል፤ በክንዱ ላይ ያንጠለጠለውን ሰማያዊ ሹራብ ሲለብስ ከቅጥነቱ ደርባባነቱ ጎላ። የስራ መውጫ ሰዓት ስለሆነ ሰዉ ወደ ጎጆው ለመገስገስ ወደ ትራንስፖርት ሰልፍ እንጂ ማን ምን ይሁን እያየ አይደለም፤ ይህን ወጣትም ያየሁት የባስ ሰልፍ ላይ ነው። አንድ ወዳጁ"ይስሀቅ እንዴት ነህ" ብሎ ሰላምታውን ከፊቱ ፈገግታ ጋር ለገሰው፤ ከተሰለፈ እንኳንስ ለመሳቅ ፈገግም ያላለው ሰልፈኛ ከወዳጁ ሲገናኝ ከንፈሩ ተላቆ ጥርሶቹን ማስቆጠር ጀመረ። ሲመስለኝ ከተገናኙ ሰነባብተዋል የባጡንም የቆጡንም እያወጉ ሰዓታቸውን ገፉ፤ ባሲቷ ሰዓቷ ሲደርስ እያጋፈረች መጣች። ይስሀቅ በሰልፉ 3ኛ ላይ ስለሆነ ሲያወጋው የነበረውን ወዳጁን ተሰናበተው። አዛውንቶች በቦታው ነበሩ አብዛኛዎቹ ለማምነው ለመግባት ቢሞክሩም ሰዉ ፍቃደኛ ስላልሆነ መግባት አልቻሉም። ታዲያ የሁሉም አይን ግን እንደተማክሮ እሱ ላይ አርፏል፤ እሱም ፊቱን ሲጨፈግገው "ይቺ ጠጋ ጠጋ....." ሳይል አልቀረም። ትኬተሯ መጥታ እንደየአመጣጣችን ትቆርጥልን ጀመር ባሱ ሞልቶ በሞተሩ እያጓራ ጭሱን እንደ እጣን ወደ ሌላ መስመር የተሰለፉትን ተሰላፊዎች እያጠነ ጉዞአችንን ጀመርን። እኔ ለትዝብት ይመቸኝ ዘንድ ከመጨረሻው ወንበር ተስፈንጥሬ ሁኔታውን እየተከታተልኩ ነው። አዛውንቶቹም ገብተው ከልጁ አካባቢ ያንዣብቡ ጀመር፤ አይናቸውን ከሱ መንቀል ተሳናቸው። እኔም በተመስጦ መከታተልን በጀ ብዬ ዘልቄበታለ። ለካስ ይስሀቅ በጥቁሩ መነፅር ውስጥ ሁኔታውን እየቃኘ ነበር፤ ለእነዚህ እይታዎች መልስ መስጠት አለብኝ ብሎ አስቀድሞ ፈገግ አለና በጎርናና ድምፁ "እባካችሁ አትዩኝ! የእናንተ እይታ አያስለቅቀኝም፤
ይችን ወንበር ለማግኘት ብዙ ለፍቻለሁ፣
ደም ባላፈስም ፀሀይ ተግቻለሁ፣
እጄን ጨብጬ ሌላውን ባልጨብጥም ተራዬን ጠብቂያለሁ። አሁን እኔን ከምታዩኝ በጊዜ አትሮጡም፤ ከማጭበርበር ይልቅ ህግን አትጠብቁም፤ እንደ አብርሃም ብላቴና ይስሀቅ በጊዜዬ በመታዘዜ ይኸው ለዚህ ዙፋን ታጭቻለሁ። ብታዩኝ ባታዩኝ እኔን አያገባኝ። ያገኘሁት በሀቄ፤ የተቀመጥኩት በልፋቴ ነው። እናም "አትዩኝ አለቅም!" በድጋሚ አትዩኝ ወንበሬን አለቅም! " በማለት እሱ ፈገግ እያለ የሰውን ሁሉ አይን ወደ ፊት ከማንጋጠጥ ወደ ቁልቁል ሰበረው። እኔም በንግግሩ ቅኔውን ለፈቺ ብዬ እንደተረዳሁት ተረድቼ በንግግሩ ተደምሜ ጉዞዬን ቋጨሁ።


ተፃፈ በኢማን አብዲ(ረዱ)


ታኅሳስ 7,2015ዓ.ም
@redu_30

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሰው ሂያጅ ነው!🚶

የሰው ልጅ መሄድ የሚጀምረዉ ገና ከእናቱ ማህፀን ጀምሮ ነው። በእናቱ ማህፀን ሳለ  ከእንቁላልነት ወደ ትንሽ ፍሬነት ይቀየራል። ከዚያም ከ 9 ወራት ትግልና ፅናት በኃላ ሰው ሆኖ ይወለዳል። ነገር ግን በዚህ ብቻ አያበቃም በእግሩ ይጓዛል በእግሩ ሲሰላች እንስሳትን አዘጋጀ። በበቅሎ በአህያ ወዘተ ይጓዝ ጀመረ። ግን አልበቃውም።

ወቸ ጉድ ከዚህ በላይ ደሞ በምኑ ሊጓዝ ነው?

ገና ምኑ ተጀምሮ የሰው ልጅ ድንቅ ፍጥረት ነው። ብሎ ብሎ ባለ ሞተሩን መኪና ሰራና በመኪና ከሀገር ሀገር መጓዝ
ጀመረ። ግን አሁንም መድረስ የፈለገበት አልደረሰም።

እና የት ለመድረስ ቀጥሎ ምን ሰራ?

በቀጣይ ደግሞ ባቡርን ሰራ ረጅሙን ተሳቢ። በዚህም አላበቃም የሰው ልጅ ይህን በነካሁት ብሎ የሚመኘውን ሰማይ አውሮፕላን ሰርቶ  አጠገቡ እንደ ቀልድ ይንሳፈፍበት ጀመር። አየርን ለመተንፈስ ብቻ ስንጠቀምበት ድንቄ ሰው ግን አየርን ለመጓጓዛም ተጠቀመበት።

በቃው ይሄን ያህል ከሄደ  በአየር ሀገር ለሀገር ዞረ

ምን ይበቃዋል ጨረቃ ላይ ለመሄድ መንኩራኩርን አበጀ ከዚያም ፕላኔቶች ጋር ደረሰ።


ፈጠራውም ገና ይቀጥላል።
ሰው ራሱን እስኪያገኝ መሄዱን አያቆምም።

እራሱን ለማግኘት ደግሞ በሞተር ነገሮችን መስራት ሳይሆን ያለበት 'ራሱን በመስራት 'ራሱን መሆን ነው። ስለዚህም ራስህን ለማግኘት በቅድሚያ ራስህን ሁን። ከዚህ በኃላ "ሰው ሂያጅ ነው" የሚባለዉ ነገር አንተ ላይ ታሪክ ሆኖ ይቀራል ማለት ነው።
ለዚህም ነው አባቶቻችን ''እንቁላል ቀስ በቀስ በእግሩ ይሄዳል'' የሚሉት። ከእንቁላል ተነስቶ እስካሁን መሄድ ያላቆመዉ አጅሬ ሰው ግን ምነኛ ድንቅ ፍጥረት ነዉ?


የሰው ልጅ ሂያጅ ነው መሄጃውን የማያውቅ ከንቱ፣
ለፍተህ ጥረህ ግረህ ብላ ቢለው አባቱ፣
መዳረሻም የለው የመሄጃው ማብቂያ፣
ራሱን ሲያገኝ ነው የፍሬው መለኪያ።


አንተ  ግን  መሄድህን  መቼ  ታቆማለህ  /እስከየት  ትሄዳለህ...?  እኔ  እልሃለው  ምቾት  ሞልቶ  እስኪተርፍልህ    ሳይሆን  ራስህን  እስክታገኝ  ሂድ  ፡፡
          
         ተፃፈ በኢማን አብዲ(ረዱ)

       ጥቅምት 04,2015ዓ.ም
@redu_30

@getem
@getem
@getem
አየህ ወንድሜ ካልጠፋ ሀገር የት እንደተፈጠርን?


እንደትላንት ተወልደን ዛሬ ላይ እድሜያችን ስንት ደረሰ? ወጣትነታችን ወደ ፊት የሚያራምደን መስሎን ተሞኘን። ዕቃቃችንን ስንጥል፥ ጨዋታችንን አልጠገብንም ነበር። ድክ፥ ድክ ያልነው በወጉ ዳዴ ሳንል ነው። ልባችን ላይ የሚነደው የጉርምስና እሳት ደረታችንን ሲፋጅ ሰፊ መንገድ ያለ መስሎን ነበር።


አየህ ወንድሜ ካልጠፋ ሀገር የት እንደተፈጠርን?


ከአባታችን ወገብ የተከፈለው ዘር፥ በእናታችን ማኅጸን እንቁላል ሳይመታ፤ ፅንስ ሳንሆን፥ ሥጋችን ሳይቦካ፥  አጥንታችን ሥር ሳይሰድ፥ ጅማታችን ሳይዘረጋ፥ ሽል ሳንሆን በፊት. . . ክፉ ዕጣ ቀድሞናል። አንዳችን ለአንዳችን ጠላት ተደርገናል። ለሞትም ታጭተናል። ሳንመርጥ ወግነናል። ደርሰን ባልበደልነው፥ ባልሠራነው ታሪክ. . . አክ እንትፍ ተብለናል።


አየህ ወንድሜ ካልጠፋ ሀገር የት እንደተፈጠርን?


እኔና አንተ ምንም እንኳ ወደ ፊት መጓዝ ብንፈልግም፤ ይሄ ሀገር የሚሄደው ወደ ኋላ ነው። ዳገቱን ወጣን፥ አቀበቱን አሸነፍን፥ ተራራውን ረታን ስንል. . . እየተንሸራተተ መቀመቅ ይዞን ይወርዳል። በየቀኑ ትርጉም አልባነትን እንድናንከባልል ተፈርዶብናል።


አየህ ወንድሜ ካልጠፋ ሀገር የት እንደተፈጠርን?


አናምንም። ግን ዕውቀት የማይዘልቀው የድንቁርና እና የአረመኔነት ዘረመል ሥጋ ለብሶ ያለው እዚህ ሀገር ነው። ኅዘንተኞች ሳለን መጽናኛ የለንም። ፍርፋሪ እሴት ሳይቀር ነጠቁን። ረክሰው አረከሱን። የሤራ ፖለቲካው ጉንጉን ፈጣሪ ዓለምን ከፈጠረበት ጥበብ በላይ ሳይረቅቅ አይቀርም። እግዚዖ!


አየህ ወንድሜ ካልጠፋ ሀገር የት እንደተፈጠርን?


ከተወለድን ጀምሮ አላስተኙንም። ታዲያ  ሕይወታችን ስለምን ቅዠት በቅዠት ሆነ? ማለት  መቼ አስተኝተውን? መቼስ ተደላድለን? እስከ መች እንደምንኖር አናውቅም። ሕይወት አጭር ናት፤ እዚህ ሀገር ደግሞ እጅግ በጣም አጭር ናት። ሕልውናችን ከእኛ ቁጥጥር ውጪ ነው። ብንነቃም፥ ብናንቀላፋም ሕይወት ጭራቅ መልኳን ለአፍታ አትቀይርም። የቸገረ ነገር!


አየህ ወንድሜ ካልጠፋ ሀገር የት እንደተፈጠርን?


እንዴት እንደሆነ ባናውቅም እንደ ትውልድ አምክነውናል። ሳንወለድ ገድለውናል። የእናት ጡት ሳንጠባ አስረጅተውናል። ቆምረውብናል። ቅያሜውን ሳናውቅ፥ ጦርም ሳንገጥማቸው፥ ያለ ወግ ድል አድርገውናል። ያረፈብን የጀግናም አይደለ፥ የፈሪ ዱላ ነው!


አየህ ወንድሜ ካልጠፋ ሀገር የት እንደተፈጠርን?


ዳሩ ምርጫ አልነበረንም።

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Esubalew abera
.....
ይህ ቀን ግን እንደተለመዱት ቀናት አይሆንም።

መነሻህ ለይ ስራዎችህን ሰዎች እንዲረዱትና ትኩረት እንዲሰጡት ትሻለህ፤ ቢያበረቱህ፣ ቢያደንቁህ፣ ከጎንህ ቢቆሙ ምነኛ በወደድክ ግን የነገሮች መልክ ሌላ ነው። ሲደክምህ ከማንም ምንም መጠበቅ ታቆምና የተለመደው ስራህን ትቀጥላለህ ብዙ አንድ አይነት ቀናት በአንድ መልክ ያልፋሉ። ከብዙ ቀናት መካከል ግን በሆነችዋ ቀን ነገሮች ይለዋወጣሉ፤ ይህቺ ቀን ላንተ የቀደመውን ተግባርህን የምትፈፅምባት የተለመደች እለት ለሰዎች ግን አንተን አጥርተው የሚያዩባት ልዩ ቀን። ድንገት ሰዎች ለአንተ ትኩረት መስጠት፣ ስራዎችህን ማድነቅ፣ ማሞገስና ማክበር ይጀምራሉ ትደነግጣለህ!
"ልክ እንደተለመደው እኮ ነው" ማለት ይቃጣሀል ግን ለፈጣሪ ስራውን የሚሰራባት ቀን ናትና ለብዙ የትላንት የድካም ቀናቶችህ በዚች አንዲት እለት እጥፍ ድርብ አድርጎ ይክስሀል፤ በዝምታ የሆነውን ሁሉ ትቀበላለህ።

ይህ ቀን ግን እንደተለመዱት ቀናት አይሆንም።

ላደረከው ክፋት ምላሹ ዝምታ ሲሆን ልብህ እየደነደነ ይመጣል፤ የቀድሞ "ምን ይመጣብኝ ይሆን?" የሚለው ፍርሀትህ "ማን ምን ያመጣል?" ወደሚለው ድፍረት ይሸጋገራል ክፋትን በትንሽ ትንሹ ትለማመዳለህ። ለስራህ በጩኽት ይቀጣህ የነበረው ህሊናህ ልክ ምንም ያላደረክ ይመስል ዝም ይልሀል፤ እናም ልክ ካንተ በላይ ሰው ከምድር በላይ ገዢ የሌለ ይመስል ትታበያለህ። የተለመደውን በደል በምትፈፅምባት አንዲት ቀን ግን ፈጣሪ የስራህን ሁሉ ማብቂያ ያደርገዋል።
እንደ ተራራ የገዘፈው እንደ ሰናፍጭ ያልታየህን ቁልል ባልጠበከው ጊዜና ቦታ ይንደዋል፤ በራስህ የክፋት ካብ ፍራሽ ስር ምንምና ማንም ሆነህ ትቀራለህ፤ ይህ ቀን እንደተለመዱት ቀናት አይሆንም።

የፈጣሪ አንዲት እለት አንተ በጠበከው ጊዜና ቦታ አትመጣም የተለየ ፅድቅ ወይ የተለየ ክፋት ባልሰራህባት በአንዷ ቀን ግን የስራህ ሁሉ ማጣፊያ ይሆናል።

ፈጣሪም ሰውም ያላየህ ሲመስልህ ልብህን ከቶ አይክፋው በመልካም ጎዳናህ ለይ ሆነህ በዝምታ አምላክህን ጠብቀው።

ፈጣሪም ሰውም ያላየህ ሲመስልህ በክፋት ጎዳናህ ለይ በማን አለብኝነት እንዳሻህ አትረማመድ አይደለም ቆሞ መሄድ አጎንብሶ እንኳን ምህረት ማግኘት  ለታደሉት ብቻ ይሆን ይሆናል።
ለክፋትህም ልክ አበጅለት ምክንያቱም ይህ ቀን እንደተለመዱት ቀናት አይሆንም።

@wegoch
@wegoch
@wegoch

By mahlet
ትዝታ ዘ Elementary (፰)
_____

ወ/ሮ መስከረም ወደ ክፍል ገባች! ... 'አርት' አስተማሪያችን (እድሜዋ በአንቺና አንቱ መሐል ሆኖ ተቸገርን!!) ... አጭር ወፈር ያሉ ሴትዮ ናቸው! ... አጭር ሰው ነገረኛ ነው ይባላል! እሳቸውም የተለዩ አይደሉም! ... በየሳምንቱ አዳዲስ የግርፋት አይነት ያስተዋውቃሉ። ... ግርፊያው በደረጃ የተደለደለ ነው፣ አርት ደብተር ረስቶ/ትቶ የመጣ፣ የተሰጠ የቤት ስራ ያልሰራ፣ እያስተማረች የሳቀ/ች፣ እያስተማረች ያወራ እያለ በቅደም ተከተል ይወርዳል! ...

ዛሬ እኔና ዮሐንስ አርት ደብተር ይዘን አልመጣንም! ... ከግርፋት እንዴት እንደምናመልጥ ከሰልፍ ላይ ጀምሮ እያውጠነጠንን፣ እየተከራከርን ነው የቆየነው! ... በስተመጨረሻ ተስማማን- "አሞናል ብለን እንውጣ" !! ...

⨳⨳

«አርት ደብተራችሁን አውጡ !!»
ክፍሉ ተንኮሻኮሸ ... ተማሪው ደብተሩን እያወጣ ጠረጴዛው ላይ ይዘረጋል! ...
እኔና ዮሐንስ ትወናችንን ልንጀምር ነው! ...
«ያላመጣችሁ ኑ ውጡ!»
ትወናችን ተጀምሯል ...
ዮሐንስ ጠረጴዛው ላይ ተኛ! ... እኔ ከዳሁት! ... ወ/ሮ መስከረም በሁለቱ መደዳ መሐል ሆነው ነው የሚያረጋግጡት ከፊት ወደኋላ ከመሄዳቸው በፊት ጎን ለጎን ያሉትን ቼክ ያደርጋሉ! ... ሀሳቡ ብልጭ ያለለኝ ድንገት ነው (ዮሐንስ ይቅር በለኝ!!) ... ወ/ሮ መስከረም ከኛ ፊት የሚቀመጡትን ዴስክ ቼክ አድርጋ ከጎን ወዳሉት ስትዞር ቼክ ተደርገው ከታለፉት ተማሪዎች ደብተር ተቀበልኩና ፊቴ ዘረጋሁት ! ...

⨳⨳

አሁን እኛ ጋር ደርሳለች!
«ተነስ አንተ ውሪ!» ዮሐንስን ነው!
ዝም ጭጭ! ወይ ፍንክች!
«ምናባቱ ሆኖ ነው?!» ጥያቄው ለኔ ነው ...
«አሞት ነው!»
«አሁን ነው ከቅድም ጀምሮ?»
«ከቅድም ጀምሮ!»
መምህሯ ዮሐንስን መነቅነቅ ጀመሩ ...
«ተነስ! ደብተርህን አሳይና ተኛ!»
አዪዪ! ... አይሁንልህ የተባለ ልጅ!
ዮሐንስ ሆዬ ወይ ፍንክች! ...
«ተነስ ነግሬሃለሁ! ... ተኝተህ ሞተሃል!»
ዮሐንስ ተነሳ ... ፊቱን አጨፍግጎ ዓይኑን እያሸ ነው ...
«ደብተርህን አውጣ!»
አሁንም ዓይኑን እያሸ ነው ...
«እስከወዲያኛው ሳላጋድምህ ደብተርህን አውጣ!»
የዮሐንስ "እንቅልፍ" ብን ብሎ ጠፋ! ...
«አ....ላ...መ...ጣ...»
ዷዷ! ... ቿቿ! ...ጯጯጯጯ! ...

@wegoch
@wegoch
@paappii

By abdu s aman
Forwarded from ❀ርብቂ Ribki Photography (Ribka Sisay)
እየተደገሰልህ ነው!!!

ሽር ጉድ ...ጉድ ጉድ...ጉድ ሽር

እንደ ገብስ ቆሎ ገባ ወጣ ያለ
ሱፍ የተጣለበት

ቀንህን ለማድመቅ ..ለማሞቅ ተነስተው

መሰሉህ??

እየደገሱልህ አሻሮ ባሻሮ
ጌሾ
የሙሾ ጠላ

ድግስስስስ ላዘን ጥንስስስስ ....
...........
Apr 21,2021
©Ribka Sisay
..........
@ribkiphoto
ጃሃ
.
.
.
ፀሀፊ እንኳ አልነበርኩም... ነገር ግን ይሁዳነቴን አምኖ የሀጢያት ባልደረባዬ የሆነኝ ሰው ያጋራኝን ታሪክ እውነት እና ውሸትን ባንድ መደርደሪያ ላይ አስቀምጦ በግማሽ ብርጭቆ አረቄ ከሚጠፋ እኔነቴ መሀል ተራ ሰጥቼው ልሰድረው አልፈለኩም። እርግጥ ፊያሜታን በዓሉ የገለፃትን ግማሽ የአዳም ተባረኪን እሩብ ልገልፅለት አልችልም እንደ ዴዝዴሞናም እያጎን ፈጥሬ ኦቴሎዋን አላሳጣለት ይሆናል። ቢሆንም የልጅነት ልቤ የግጥም ዛሩ ወጥቶለት የቄሳርን ለቄሳር ግጥምን ለነበእውቀቱ ብሎ እንደ ጲላጦስ እጁን ታጥቦ ብዕር ጥሎ ሲጋራ ካነሳ  ከዓመታት በኋላ እህ ማለት አሰኘኝ። ......"እኔ ምልህ"አለኝ ሲጋራ አጫጫሴን በትኩረት ካየ በኋላ ሲጋራ ምን ያህል እንደምወድ ቢያውቅም ምክንያቴን ግን ጠይቆኝ አያውቅም እኔም መልስ አልነበረኝ።

"እኔ ምልህ የውሀ አይነት ስሜት ታወቃለህ?"
ማለት የተረጋጋ ማለትህ ነው? አልኩት
"NO መልክ የሌለው ይሄ ነው ልትለው የማትችለው ዓይነት"
"እኔንጃ እእእ....." ምን እንደምመልስለት እያሰላሰልኩ ወገቧ ላይ የደረሰችውን ትንባሆ አቀበልኩት ጨዋታችን እንዲቋረጥ አልፈለኩም ሲያወራ ደስ ይላል። ታሪኩ ያለፍኩበትን ያስታውሰኛል። ሀሳቡ ዞሬ ላላየው የማልኩትን ትናንቴን እንድቃኘው ደጀን ሆኖኝ ያውቃል።

"ስለሷ ሳስብ ውሀነት ነው የሚሰማኝ" አለ ሁለቴ ስቦ ሲጋራውን ቂጡ ጋር ካደረሰ በኋላ......."በማይታይ ውበት..በሚረብሽ ፀባይ....ሴትነት ባልጎላበት ለዛ የተደበቀ ውብ እና አሳዛኝ ነብስ እንዳላት የተረዳው ቀን ክርስቶስ ሳይመጣ ይሁዳን ለመሆን ለምን ቸኮልሽ? ልላት አስብና "ዋ ይሄን ግራ የገባው ወሬህን እዛው" የሚል መልሷ እንደሚከተለኝ ስለማውቅ መልሼ እተወዋለሁ ።ሁሌም እንዲ ናት ጥያቄው ካልገባት ወይም መመለስ ካልፈለገች ቁጣ ይቀናታል።እና ስለሷ ባሰብኩ ቁጥር ስሜቴ ውሀ ይሆንብኛል።
አንዳንዴ ወድጃቸው ከነበሩት ሴቶች ዝርዝር ውስጥ እፈልጋት እና ከግርጌ አካባቢ እንኳ ሳጣት ግራ እጋባለው።

እንደምጠላትም ማመን አልችልም። መቼም ማፍቀሬን በግላጭ አግኝታ ከእግር ጥፍሬ እስከ ራስ ፀጉሬ ያለተቀናቃኝ መጣ ከጣለችው ይሁዲት ጋር ላወዳድራት አልችልም። ብቻ ጎኗ ቆሜ አለው ማለት በከበባት ጦር መሀል ገብቶ መፎከር ያምረኛል። እንድትስቅ እፈልጋለው...ጥሎባት ደሞ አትስቅም ፈገግ ካለችም ከስንት አንዴ ነው። የልጅ ነፍስ አላት ..ንፁህ መዓዛ ያለው..የሚጣራ አይነት.......
ሳያት ይቀለኛል.. ለብ ባለ ውሀ ሻወር የመወሰድ አይነት የመታደስ ስሜት ይሰጠኛል። ለስላሳ ሙዚቃ የመስማት ያህል እርጋታ ይከበኛል በናት ጉያ ስር እንደመወሸቅ ያለ ድፍረት ማንም የማይደርስብኝ ያህል ልበሙሉ ሆናለው ።
ስሰማት የአለም እውነት ሁሉ ውሸት ይሆንና ሀቅ ከሷ ወዲያ ላሳር ስል እውላለው። የፍቄ ትረካና የጂጂ ዘፈን ለጆሮዬ ያስጠላኛል ። ማርያምን አልወዳትም!!! ማታ ስገባ አላልማትም ሳያት ልቤ ምቱን አይቀይርም አትናፍቀኝም ላያት አልራብም። ሳያት ግን በሰራችው የሾክ አጥር ስር ሾልኬ ማራኪ ነፍሷን ሳይ እውላለሁ እገረማለሁ እራሴን እረሳለሁ ...እጠፋለሁ አ.ይ.ገ.ባ.ት.ም እላለው... ከዚ የተሻለ ይገባታል... ያለችበትን ቦታ የከረመችበትን ህይወት ቃኘውት አዲስ አልሆነብኝም የኔ አለም ውሰጥ ያለች ይመስለኛል ..አይገባትም ነበር በፍፁም!! ...."
በመጨረሻ ቃሉ ማብቂያ ራሴን አሰብኩ ዘመን ወደ ኋላ መለሰኝ እሷን የኔን አሰብኳት ወዲያው አዲስ ሲጋራ ለኮሰ ።ተቀበልኩት አይገባውም ነበር.....
ምንአልባት የሚገባው ......

@ wegoch
ቃለመጠይቁ___

ጥያቄ: ሀገሪቷ ዳግም ኢጣሊያንን ያሸነፈችው መቼ ነው?

መልስ: ትግሉ ለአምስት አመታት እየተደረገ ቢቆይም በ1933 ዓ.ም. በድል ተደምድሟል።

ጥያቄ: በእዚህ ጦርነት ከፍተኛ ሚና የተጫወቱ ሰዎችን ስም ዝርዝር ጥቀስ?

መልስ: በሂደቱ ውስጥ በርካታ ሰዎች አስተዋጽኦ አድርገዋል። ስም መዘርዘር ከጀመርኩ አንዱን አንግሶ ሌላውን አንኳስሶ ይሆንብኛል።

ጥያቄ: ሙስና የሀገሪቱ ዋነኛ ጠላት ነው ብለህ ታስባለህ?

መልስ: ይሄንን ጉዳይ እያጣራ ያለ መንግስት ያቋቋመው ኮሚቴ አለ። ኮሚቴው የሚያወጣውን ሪፖርት ካየሁ በኋላ መልስ ልሰጥበት እችላለሁ።

ቃለመጠይቅ አድራጊዎቹ የሥራ አመልካቹ በሰጠው መልስ እጅግ በመርካትና በመደነቅ ውጤቱን ደጅ ሆኖ እንዲጠባበቅ እንዲሁም ለሌሎቹ የሥራ አመልካቾች ጥያቄዎቹን እንዳይነግራቸው አስጠንቅቀው አሰናበቱት።

••••

ወጣቱ የሥራ ተወዳዳሪ ከክፍሉ እንደወጣ ከእርሱ ቀጥሎ የሚገባው አመልካች ምን ምን ጥያቄ እንዳቀረቡለት እንዲነግረው ይነዘንዘው ጀመር። ወጣቱም "ለቃለመጠይቅ አድራጊዎቹ ጥያቄውን ለሌላ አመልካች እንደማልናገር ቃል ገብቻለሁ።'" ሲል ይመልሳል።

ሌላኛው ተወዳዳሪ ጥቂት አሰብ ካደረገ በኋላ "እሺ መልሶቹን ነገረኝ?!" ብሎ ይጠይቀዋል።

ወጣቱም ቃለመጠይቅ አቅራቢዎች "ጥያቄዎቹን ለማንም እንዳትናገር!" ብቻ ብለው እንዳስጠነቀቁት በማስታወስ "መልሶቹን አትንገር አላሉኝም!" ብሎ ለእራሱ ካወራ በኋላ የመለሳቸውን ሶስት መልሶች ለሌላኛው አመልካች ይነግረዋል። የተነገረውም አመልካች መልሶቹን በልቦናው መዘገበ።

•••

ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ሁለተኛው አመልካች ለቃለመጠይቁ ወደ ውስጥ ተጠርቶ ገባ።

ጥያቄ: መቼ ነው የተወለድከው?

መልስ: ትግሉ ለአምስት አመታት እየተደረገ ቢቆይም በ1933 ዓ.ም. በድል ተጠናቅቋል።

ቃለመጠይቅ አድራጊዎች በመልሱ እንደተደናገሩ ወደ ሁለተኛው ጥያቄ ይሄዳሉ...

ጥያቄ: የአባትህ ስም ማን ይባላል?

ሙልስ: በሂደቱ ውስጥ በርካታ ሰዎች አስተዋጽኦ አድርገዋል። ስም መዘርዘር ከጀመርኩ አንዱን አንግሶ ሌላውን አንኳስሶ ይሆንብኛል።

ቃለመጠይቅ አድራጊዎቹ ግራ ተጋብተው..

"ያምሀል እንዴ ሰውዬ?!"

"ይሄንን ጉዳይ እያጣራ ያለ መንግስት ያቋቋመው ኮሚቴ አለ። ኮሚቴው የሚያወጣውን ሪፖርት ካየሁ በኋላ መልስ ልሰጥበት እችላለሁ!"
••••

ምንጭ: ድረገጽ


@wegoch
@wegoch
@paappii
ይሉኝታ(ክፍል 1)


  እግዜሩ ያለ የሌለ አቅሙን ሙጥጥ አድርጎ የሰራውን ይሉኝታ ሁሉ የሆነ ጊዜ ላይ መሸከም ከብዶት ሳለ ወደ ቀራንዮ ጫፍ መስቀሉን ሲጎትት ቀረብ ብሎ እንዳገዘው ምስኪን እኔም ጠጋ ብዬ"አባት ሆይ! ይህን ሁሉ ይሉኝታ ብቻህን?ባይሆን ትንሽ ላግዝህ !"ብዬ ያንን ለምድር ለሰማይ የከበደ ይሉኝታ ተቀበልኩት።እሱም በይሉኝታ መቅረቤን አይቶ "ላለው ይጨመርለታል"በሚለው መርህ በእገዛ ሰበብ የተቀበልኩትን ይሉኝታ መልሶ ሳይወስድልኝ ቀረ።እነሆ እኔም ከዛ ወዲህ ትልቅ ትንሹ  ሲያሻው እንደ ስጋጃ እየረገጠ፣ሲፈልግ እንደማስቲካ እያላመጠ፣ባስ ካለም እንደ እንቧይ እያፈረጠ በይሉኝታዬ እኔው ላይ ዳንኪራውን ይመታል።

  "ልጅ ደስታ!እስቲ ና ወዲህ" ይሉኛል እማ አልጣሽ ከመንገዱ ጫፍ ወገባቸውን ይዘው ይቆሙና።

  እማ አልጣሽን ሳያቸው አስማተኛ አሮጊት ይመስሉኛል።በፈገግታቸው ተሸፍኖ ያለውን ከባድ ቁጣ ከእግዚአብሔር በላይ ሳልፈራው አልቀርም።እንደው አንዲት ነገር አዝዘውኝ እምቢ ብላቸው  ፈገግ ያለ ገፃቸውን በቅፅበት ክስክስ ያደርጉና በቅርባቸው ያለ ጭራሮ ቢጤ አንስተው ድግምት ነገር እያነበነቡ መሬቱን ጫር ጫር ቢያደርጉት ሽንቴን ልሸና ምናምኔን አውጥቼ ባንከፈረርኩበት እንደ እንጨት አድርቀው የሚያስቀሩኝ ይመስለኛል።ወይ ስፈራቸው!🙆

  "አቤት እማ አልጣሽ" እላለሁ አጠገባቸው ስደርስ።

"ደስታየነህ...እንደው መቸም አንዴ ሲፈጥርህ የአሮጅትና የሽማግሌ መጫወቻ ሁን ብሎሀል...አንተም ጣድቅ ነህ መቸም አልታዘዝም አትልም...እንደው እሱ መድሀኔዓለም ምቀኛህን ውጋት ይዘዝበት!"

"አሜን እማማ"

"እንደው ያችን እላይ መንደር ያለችዋን አትጠገብን አወቅሀትም አይደል?"

"እትየ አትጠገብ የጋሽ ባህሩን ባለቤት አይደል?"

"እ...የባህሩ ምሽት!ሰልስትና እለታ ቸግሮኝ 50 ሳህኔ ማሽላ ተበድሬአት ነበር...አሁን የሻለቃ(ሻለቃ ማለት በደርግ ጊዜ በውትድርና ያገለግል የነበረ ባለቤታቸው ነው።)  ጡረታ ሲመጣ ሸምቸ መግባቴ ነው...ንስማ አድርሰህላት ና ጀታየነህ እመርቅሀለሁ"አሉኝ እግራቸው ስር በማዳበሪያ ታስሮ ወደተቀመጠው እህል እያዩ።የእትዬ አትጠገብን ቤት ርቀት ሳስብ ማዳበሪያው ገና ሳልሸከመው ደከመኝ።በመንገዴ የማገኛት ክፉ አቀበት ከጦሳ ተራራ ገዝፋ ብትታየኝም 'እምቢ' ግን አልልም።ይሉኝታዬን ለማን ሸጬው?

  እንደፈረደብኝ ያንን በግምት 65 ኪሎ የሚሆን ማዳበሪያ ተሸከምኩትና መንገዴን ጀመርኩ።እትየ አልጣሽ ከሁዋላዬ ሲመርቁኝ አልፎ አልፎም በሞኝነቴ ሙድ ቢጤ ሲይዙብኝ ይሰማኛል።

"ተባረክ ደስታየነህ ብሩክ ሁን!አሁን የማን ልጅ እሽ ብሎ ይታዘዛል በዚህ ዘመን?እድሜ ይስጥህ!ወገብህን ተውልቃት፣እጅህን ተቁርጥማት ይሰውርህ!"ይሉና ደሞ ድምፃቸውን ዝቅ አድርገው

"አይይይ እንደው መድሃኔዓለም!እንደው እንዲህ ማንም የሚጭነው አህያ ሆኖ ይቅር!ኧረ አህያስ ሲበዛባት ትለግማለች..." ሲሉ ከነሸክሜ ዞር ስል እንደገና ድምፃቸውን ሞቅ ያደርጉና

"እንጀራ ይውጣልህ ደስታየነህ!ምቀኛህን እግሩን ያልምሸው የኔ ዓለም!ውለህ ግባልኝ ክፉ አይንካህ!" ይሉኛል።

ይቀጥላል

ማዕዶት ያየህ

17/07/2015 ዓ.ም.

@wegoch
@wegoch
@paappii
ይሉኝታ(ክፍል 2)

  ያገኘኝ ሁሉ ሲልከኝና ሲያዘኝ ውዬ የዛለ ሰውነቴን እየጎተትኩ ቤቴ እገባለሁ።እናቴ የቡና እቃዎቿን እያቀራረበች በመሀል ቀና እያለች ስታስተውለኝ ትቆይና

"አዋጥተው እንደገዙት መጋዣ ሲጭኑህ ይውላሉ አይደል?እንደው እምቢ አልፈጠረብህም አቡሽ?እምቢ አትልም?"

"ይረግሙኛል ብዬ ነውኮ"

"ኤዲያ!የረገሙህስ እንደው?አንድ ሳህን  ጤፍ ይገዙልህ መሰለህ?አዬ አለመታደል!እንዲህ እብን ሆነህ ትቀር?አድገሀልኮ ደስታ!18 ሞላህኮ!ልጅ አትባል ከንግዲህ"
ስትለኝ በመሀል አንድ ድምፅ አቋረጣት

"እንዴት ውላችሁዋል እናንተ?"እያሉ ወደውስጥ ዘለቁ እትየ አትጠገብ።እኚህን ሴትዮ ሳያቸው ያጥወለውለኛል።በነገር ሰው ሲወጉ ወደርም የላቸው።በቀደም ከመሸ ተልኬ ስወጣ ከማህሌት(የሰፈሬ ልጅ) ጋር ሱቅ ተገናኘንና የሆነ ያልሆነውን እያወራን ስንራመድ እትየ አትጠገብ በዛ ረጅም ቁመታቸው ሀውልት መስለው ከፊትለፊታችን ተገነጨሩ።ማህሌት ትከሻ ላይ ጣል ያረኩትን እጄን በፍጥነት አውርጄ ሰላምታ አቀረብኩላቸው።በውሉ ያልተሰማኝን ነገር አልጎምጉመው ሄዱ።በነጋታው ቤታችን መጡና

"እንዴት ውላችሁዋል ቤቶች?"አሉ በጎንዮሽ እያገረመረሙኝ።ወዲያው ወደኔ ዘወር አሉና

"ደስታ...ምነዋ ዛሬስ የጋሽ አለሙ ልጅ የት ሄዳ ነዋ?"አሉኝ።በአስማት እንዳደረቁኝ ሁላ ቀጥ ብዬ ቀረሁ።አባቴ

"ኧ?ደሞ የጋሽ አለሙ ልጅ እዚህ ምን ታረጋለች ?" ጥያቄአዊ አስተያየቱን እያነጣጠረብኝ።

"አብረው አያጠኑም እንዴት?ትናንት እዚህ አምሽታ ስትወጣ ያየሁዋት መስሎኝ"ብለው እርርርፍ!ምን ያልተመኘሁላቸው እርግማን አለ?ሙሴ በበትሩ ለድድ ሩብ ጉዳይ የሆነ ጥርሳቸውን ቢያረግፈው ደስታዬ! ኢያሱ ያቆማት ፀሀይ እንትናቸውን ለምች ትስጠው!ሌላ ክፉ አልመኝም!

"ኧረ ማታኮ ሱቅ ተገናኝተን እየሸኘሁዋት ነው ያዩን እዚህ አላመሸችም"አልኩኝ እየተርበተበትኩ።

እናቴ 'ለዚህም ደርሰሀላ?!'አይነት አስተያየት አየችኝ።እየተጎተቱ መጥተው የነገር መርዛቸውን አርከፍክፈውት ሄዱ።ከዛ ወዲህ ቤታችን ሲመጡ በጤና አይመስለኝም።እስኪወጡ ሱባኤ እይዛለሁ።ዛሬ ደግሞ ምን ሊሉኝ ነው እያልኩ ስብሰለሰል

"ደስታየ...ነገ ትምህርት አለህ?"አሉኝ።

ይቀጥላል

ማዕዶት ያየህ(ዘማርቆስ)
(gize_yayeh)

@wegoch
@wegoch
@paappii
ጠላ እየጠጣን ከጓደኞቼ ጋ ተሰባስበን እየቀደድን ሳለ ፦

ምድር ላይ የትኛውን ገጠመኝህን በይበልጥ ትወዳዋለህ የሚል ቀደዳ ጀመርን

ፍሬንድ ቀጠለ

"አንድ እለት እሁድ ጠዋት እናቴ ቡና እየጠጣች ፣ እየመከረችኝ ፣ እየመረቀችኝ ፣ እየሰደበችኝ ሳለ

በጣምምም ደስስ የሚልሽ ምን ብታገኝ ነው  አልኳት  አጠያየቄ ድንገት ነበር

ላሊበላ ፣  አክሱም ጽዮን ፣ ውቅሮ ማርያም ካዲ ብሄድ ደስ ይለኛል አለቺኝ

ፊቷ ላይ ያለው ምኞት የደስታ ዳር ይመስል ነበር።  ። በነጋታው ስጣደፍ ሄጄ ቢሮ አንድ መቶ ሺ ብር  ተበደርኩ ፍቃድ ወሰድኩ

ሎተሪ ደረሰኝ ብያት  ላሊበላ ፣  አክሱም ጽዮን ፣ ውቅሮ ማርያም ካዲ ወሰድኳት   ደስስ አላት ፀለየች  ፣ ለነዲያን መፀወተች ፣ እጄን ይዛ መረቀቺኝ ። 

ከዛ ከተመለስን በኋላ ሶስት ወርም አልቆየች ትንሽ አሞት ሞተችብኝ። ሳለቅስ ፣ ሳዝን ያፅናናኝ እና ያበረታኝ ህልሟን ማሳከቴ ነበር

ቀጠለ ሌላ ፍሬንድ ፦

"አንድ ቀን ክላስ ቀጥቼ ዩኒፎርሜን እንደለበስኩ  ጠላ ቤት ደቅ ብዬ አባቴ ከጓደኞቹ ጋር  ከች አለ ሳየው ስካሬ ጠፋ ።

ልጄ ነው ብሎ ለፍሬንዶቹ  አስዋወቀኝ ። ሃይለኛ ስለነበር እዛው ካልገደልኩ ይላል ብዬ ነበር። ምንም አላለኝም ። እንደውም የጠጣሁበትን ከነ ፍሬንዶቼ ከፈለልኝ ። ቀድሜው ወጣሁ ፦

አላመንኩትም የሚገድለኝን አገዳደል እያሰብኩ  ስፈራ ስቸር እቤት አምሽቼ ገባሁ ። እሱ ምንም አላለኝም ።

በሳምንቱ "ጋሻው ዛሬ ትምህርት የለህም አይደል "

"አዎ"
"በቃ ዛሬ አብረን እንዋል አለኝ" እሺ ብዬው የሚሰራበት
አብረን ሄድን

ውሎውን አዋለኝ ። የሆነ ህንፃ ይጠብቃል ፣ ህንፃው ጋ የሚቆም መኪና ይጠብቃል ፣ መኪና ያጥባል ።

የጠበቀበትን እና ያጠበበትን  ብር እንዲሰጡት ደጅ ይጠናል ፤ ትንሹም ትልቁም ይጠራዋል ፣ ያዙታል ያን ቀን አባቴ በጣም አሳዘነኝ

ከፊቱ ገሸሽ ብዬ አለቀስኩ

እንዴት እንደሚያሳድገኝ ያኔ ነው የገባኝ ። ምን እያለ እንደመከረኝ ፣ በእኔ ጉዳይ ለምን እንደሚናደድ ገባኝ

የዛ ቀን ህይወቴ ተቀየረ ።

ሌላ ፍሬንድ ቀጠለ ፦

"አንድ ቀን  እቃ ጠፍቶኝ ቤታችንን ሳምሰው
የታናሽ እህቴ ዲያሪ አገኘሁት በማላውቀው ምክንያት የማስሰውን ነገር ትቼ ደቅ ብዬ ማንበብ ስጀምር ።

ጥጋቤ ፣ ድፍረቴ እልሄ ተነፈሰ ። የግሩፕ ጠብ አጓጉል ውሎዬ ጣጣ  ለመጀመሪያ ጊዜ ገባኝ። ለመጀመሪያ ጊዜ መፍራት ጀመርኩ ፤ ለቤተሰባችን ምን ያህል እንደማስፈልግ ማስታወሻዋ ነገረኝ" 

ለካ አንዳንድ ቀን ብቻውን ዘመን  ያህላል !!

   by Adhanom Mitiku

@wegoch
@wegoch
@paappii
ወግ ብቻ pinned «ጠላ እየጠጣን ከጓደኞቼ ጋ ተሰባስበን እየቀደድን ሳለ ፦ ምድር ላይ የትኛውን ገጠመኝህን በይበልጥ ትወዳዋለህ የሚል ቀደዳ ጀመርን ፍሬንድ ቀጠለ "አንድ እለት እሁድ ጠዋት እናቴ ቡና እየጠጣች ፣ እየመከረችኝ ፣ እየመረቀችኝ ፣ እየሰደበችኝ ሳለ በጣምምም ደስስ የሚልሽ ምን ብታገኝ ነው  አልኳት  አጠያየቄ ድንገት ነበር ላሊበላ ፣  አክሱም ጽዮን ፣ ውቅሮ ማርያም ካዲ ብሄድ ደስ ይለኛል አለቺኝ…»
የምወድደው አለቃዬን ዛሬ አገኘሁት፣ ከዓመታት በኋላ። ያለፈውን ጊዜ አንስተን እንደ አዲስ ተሳሳቅን። በተለይ የሚከተለውን ገጠመኜን።
*
ባንክ ተቀጥሬ አመት ያህል እንደሆነኝ አንድ እሁድ እለት ከጓደኞቼ ጋር ኳስ ለማየት ከቤት ወጣን። ይሁንና ኳስ እያየን ድራፍት እየጠጣን የነበርን ጎረምሶች ባላሰብነው ሁኔታ በከተማው የሚገኙ አንድ ባለሀብት ባስወረዱልን ውስኪ እስከ እኩለ ሌሊት ስንራጭ አመሸን።

ጠዋት ላይ አንድ ጓደኞዬ ቤት ስነቃ ፣ እራሴን መሸከም አቅቶኛል። ቤቱ በመጠጥ ሽታ ተሞልቷል። በእርግጠኝነት በእዚህ መልኩ ሥራ መሄድ እንደማልችል ስለገባኝ ወደ አለቃዬ ስልክ ደውዬ...

"ዘመድ ስለሞተ ለመቅበር ወደ ገጠር እየሄድኩ ስለሆነ ፍቃድ ፈልጌ ነበር..." ስል ፈቃድ ጠየቅኩ።

ተፈቀደልኝ።

መሀል ላይ ሌላ መስሪያ ቤት የሚሰራ ጓደኛዬም ከእንቅልፉ ነቅቶ ወደ ቢሮው ደውሎ ለቅሶ ገጥሞኛል በማለት ሥራ ካስፈቀደ በኋላ የእኔን ጠየቀኝ።

"እንዲህ ሀንጎቨር ሳይለቅቀኝ ሥራ ገብቼማ የመጠጥ ሽታ ስጋብዛቸው አልውልም። እኔም አለቃዬ ጋ ደውዬ ዘመድ ሞቶብኛል ብዬ ዋሸሁ። ጌታ ይቅር ይበለኝ!" አልኩት።

"እኔማ አሁን ላይ ዘመዶቼን በሙሉ ጨርሼ በጎረቤት ሞት ምናምን ማስፈቀድ ጀምሬአለሁ" አለኝ። ተሳሳቅን።

ይሁንና እየተሳሳቅን ሰዐት ለማየት ስልኬን ሳነሳ ሳላውቅ ነክቼው ኖሮ አለቃዬ ጋ ደውሎ እየቆጠረ አገኘሁት። በእርግጠኝነት ንግግራችንን ሰምቷል። ቆሌዬ ተገፈፈ፣ መሬት ተከፍታ እንድትውጠኝ ተመኘሁ። ነግቶ አለቃዬን እንዴት ፊቱን እንደማየው ሲጨንቀኝ ዋለ፣ ማታም በሐሳብ ስገላበጥ፣ እንቅልፍ ባይኔ ሳይዞር ነጋ።

በማግስቱ ጭንቀት እየተጫጫነኝ፣ ልቤ እየደለቀ፣ አንገቴን ደፍቼ ወደ ምሰራበት ባንክ ሄድኩ። አለቃዬ እንደወትሮው በጠዋት ቢሮ ገብቷል። በጭንቀት እንደተዋጥኩ ፊቴን ከስክሼ ይቅርታ ለመጠይቅ ወደ እርሱ ሄድኩ።

ልክ እንዳየኝ ፊቱ ከንዴት ይልቅ በፈገግታ እንደተሞላ "ቀብር ደረስክ?!" ሲል ጠየቀኝ። ዝም አልኩ። ከፊቴ ላይ መሳቀቄን አንብቦ ነው መሰለ የእኔን ምላሽ ሳይጠብቅ...

"አይዞህ! አትጨነቅ። እኔም የሆነ ጊዜ ላይ እንዳንተው ጎረምሳ ነበርኩ። እረዳለሁ። ሌላ ጊዜ እንዳትዋሸኝ። አሁን ወደ ሥራህ ሂድ" አለኝ።
***

@wegoch
@wegoch
@paappii
በዚህ ዘመን ሰው ሆድ እንዲብሰው እንደማድረግ ቀላል ነገር የለም ። ሰዉ እንዳለ ስስ ሆኗል ። ቀኑ እንዲጨረብ ትንሽ ምክንያት ይበቃዋል ።

አጠገብህ ያለውን ስራ ፈት በብሄርህ ምክንያት ነው ስራ ያላገኘኸው ብትለው ሲብሰከሰክ ይውላል ።

አንዱ ጓደኛህ ሲደውልልህ "እየነዳሁ ነው መልሼ እደውልልሃለሁ" ብትለው ቀኑን ሙሉ ይቆዝማል ።

የሆነችን ልጅ "በጣም ወፍረሻል" ብትላት ለጊዜው የሆነ የሆነ ነገር ትልህና መስታወት ፊት ቆማ ትብሰለሰላች ። 

እስኪ አንዱ ሲስቅ ጠብቀህ  "ሳይኖርህ አትሳቅ" በለው ፤ ወዲያው ይከስማል።

እፊቱ እንግሊዘኛ ስታወራ የሚከፋው ሰውም አለ።

አፍቅሮ የተጎዳ ሰው "እህህህ" እንዲል የፌስቡክ ጨለምተኞች ከblack and white ፎቶ ጋር የሚለጥፉት አጭር ጽሑፍ ይበቃዋል ።

ናፋቂውን ምንም አትበለው ፤ ገና ደመና ሲያይ ውስጡ ይረበሻል ።

ለማልቀስ "ፍቅርሽ ነው የጎዳኝ" የሚል ዘፈን ብቻ የሚበቃው አለ ።

ደህና ነሽ ? ስትላት እንባዋ ግጥም የሚል አለች ።

ህልምህ ምን ነበር ? ብለህ ብትጠይቀው የማይከፋው አለ ? ።

ፀሐይ ሲመታው ብቻ ኑሮ የሚመረው አለ ።

ሰዉ እንደ ድሮው ረጅም የታክሲ ሰልፍ የመጠበቅ አቅም የለውም ። መኪና የለኝም ወይም የራይድ የለኝም ብሎ ያዝናል ።

እና ይሄ በሆዱ እንባ ያጠራቀመ ህዝብን ማስለቀስ ምን ሞያ ይጠይቃል ?

ከባዱ ነገር ተስፋ መስጠት ነው ። ተስፋ  ስጠው ስልህ ምክረው ማለቴ አይደለም ። ከምር ተስፋ ስጠው ። አስቀው ። አለሁ በለው ። ራሱን እንዲችል አድርገው ። ባዶ ሆዱን አትሰክሰው ። አብልተህም አትሰክሰው ። ዕድል ስጠው ። እመነው ። እቀፋት ። ተቃቀፉ ። ምናምን...

Via: Hab HD

@getem
@getem
@getem
ውርስ!
•••
ቅርንጫፌ ውስጥ ካሉ ቆጣቢ ደንበኞች መካከል ትልቅ ተቀማጭ ገንዘብ ያለው ደንበኛ ነው። በየጊዜው የሚያስቀምጠው ገንዘብ ሲጨምር እንጂ ሲቀንስ አይቼ አላውቅም። ታታሪ ሰራተኛ፣ ባተሌ እንደሆነ ገንዘብ ሊያስገባ ለብሶት የሚመጣው የቆሸሸ የሥራ ቱታ ምስክር ነው። አንድ ትልቅ ጋራዥ እንዳለው አጫውቶኛል።
ለተወሰኑ ወራት ዐይቼው ስለማላውቅ አሳስቦኝ ስልኩ ላይ በተደጋጋሚ ስደውል ስልኩ አይሰራም።
                             *
አንድ ቀን ጠዋት አዳፋ፣ ለሐዘን ቀለም የተነከረ ነጠላ የለበሱ፣  እጅግ የተጎሳቆሉ እናትና ፊቷ በማድያት የጠቆረ ሴት ከእኔ ቀድመው ቢሮ ጠበቁኝ።
ወንበሬ ላይ ተደላድዬ እንደተቀመጥሁ የፍርድ ቤት የውርስ ውሳኔ እንዲሁም ከባንኩ ዋናው መሥሪያ ቤት የህግ መምሪያ የተሰጠ አስተያየትና የባንክ ደብተር አቀበሉኝ። የባንክ ደብተሩን ስገልጸው ከታታሪው ደንበኛዬ ፎቶ ጋር ተፋጠጥኩ።
"ምን ሆኖ ነው?!"
"ሥራ ቦታ አደጋ ደርሶበት አረፈ ልጄ!" አሉኝ - አሮጊቷ።
የሰማሁትን ለማመን አልቻልኩም። እጅግ ደነገጥሁ። የፍርድ ቤት ውሳኔውን አነበብኩት የውርስ ውሳኔው በቅርንጫፋችን ያለው ገንዘብ ለእናቱና ለእህቱ እንዲካፈል የሚያዝዝ ነው። እንዲህ የተጎሳቆሉት ሴት በእርግጥም የእዚያ የባተሌ፣ የእዚያ በየሳምንቱ በብዙ ሺህ ብሮች ሂሳቡ ላይ የሚያስገባ፣ የእዚያ ሚሊዮን ብሮች ሒሳቡ ላይ ያጠራቀመው ደንበኛዬ እናት መሆናቸው እጅግ ገረመኝ።
"እግዚአብሔር ያጽናዎ እናቴ! ነፍስ ይማር! እጅግ የማከብረው ደንበኛዬ ነበር። እጅግ ታታሪ ሰው ነበር። ስልኩ ላይ ደጋግሜ ስደውል የማይነሳው ለካ ለእዛ ነበር ለካ?! ወይኔ ወንድሜ!" አልኋቸው።
"ይኸው እንዲህ ጥሎ ለሚሞተው ገንዘብ 'ሥራ፣ ሥራ!' ሲል የት ወደቅሽ ሳይለኝ፣ ታምሜ ሳይጠይቀኝ፣ ቁራሽ ተቸግሬ ሳይረዳኝ፣ እህቱን ሳይረዳ፣ የዘመድ ለቅሶ በልቶ፣ ከዘመድ ተቆራርጦ ማንም ሳያስበው በድንገት ሞተ። ሲሞት ተደወለለኝ፣ መጥቼ ቀበርኩት። የማህጸን ማሟሻዬ፣ የበኩሬ ነበር፣ ሙት አይወቀስም ይሉኛል፣ እኔ ግን ስወቅሰው እኖራለሁ።" አሉኝ በእንባ ብዛት የሞጨሞጨ አይናቸውን በአዳፋ ነጠላቸው ጫፍ እየጠረጉ።
"አይዞዎት እናቴ! በርታ ይበሉ! እርሱስ ቢሆን ይሄ ይመጣል ብሎ አለች አሰበ?! ያው ህይወት ሩጫ ናት፣ ምናልባት አልሞላ ብሎት..."
አላስጨረሱኝም።
"እድሜዬ ካለቀ፣ መቃብሬ ከተማሰ ብር አውርሶኝ፣ የልጅነት ፍቅሩን ነፍጎኝ፣ መኖሬን እንድጠላ አድርጎኝ ሞተ። በህይወት መኖሩ ብቻ መጽናዬ ነበር። ልጄ እናት አለችህ?!"
"አዎን እማ!"
"ዛሬን ጠይቃት፣ 'እንዴት አደርሽ' በላት። ሞት መምጫው ስለማይታወቅ ለነገ ምንም አታሳድር ልጄ። ልጄ ሲለፋበት የኖረውን፣ እኔን ያስተወውን ብሩን ወረስኩ፣ ፍቅሩን ግን ሳያወርሰኝ ሞተ። እኔ እንደምወድደው አውቃለሁ እርሱም ያውቃል፣ ወጣትነቴን ሰውቼ ያለአባት አሳድጌዋለሁ። እንደሚወድደኝ ሳያሳየኝ፣ እንደሚወድደኝ ሳላውቅ ሞተ" አሉኝ።
                               ****
የውርስ ገንዘቡን አካፍያቸው እንደጨረስኩ ከጓደኞቼ ጋር ዱባይ ሄጄ ልዝናና ከቆጠብኩት ብር ወደ ላይ ግማሹን አውጥቼ ለእናቴ ከላኩላት በኋላ ስልክ ደውዬ "እማ በዓል አብሬሽ ነው የማከብረው፣ ለበዓል ጨምርልኝ ያልሽኝን ብርም አስገብቼልሻለሁ፣ አወድሻለሁ እማ!" አልኳት።
ባልተለመደ ባህሪዬ የተገረመችው እናቴ "ምን ነው ጥልዬ በቀን መጠጣት ጀመርክ እንዴ?!" ስትል ጠየቀችኝ።
እንደምወዳት የምነግራት ሞቅ ሲለኝ ብቻ ስለነበረ አልተቀየምኳትም።
                           •••••
ሐሳብ ወለድ ታሪክ!

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Tilahun Girma Ang
አባቴ እናዝናለን ፡ ካሁን በኋላ በምድር ላይ የሚቆዩት ግፋ ቢል ለስድስት ወራት ያህል ነው ።
........

እኚህ በምስሉ ላይ የሚታዩት አባት  Stamatis Moraitis የሚባሉ በወጣትነት ዘመናቸው ሀገራቸው ግሪክን በወታደርነት ያገለገሉ ሰው ናቸው ።
እና በአንድ ወቅት ልጆቻቸውን እና የልጅ ልጆቻቸውን ለመጎብኘት በሄዱበት አሜሪካ ትንሽ ህመም ይሰማቸውና ወደ ሆስፒታል ይሄዳሉ ።
ሀኪሙ  ግሪካዊውን ሰው በተለያየ አይነት የህክምና ዘዴ ከመረመረ በኋላ ፡ ሰውየው በማይድን የሳንባ ካንሰር እንደተያዙና ፡ ካሁን በኋላ በህይወት የሚቆዩት ለስድስት ወራት እንደሆነ ነገራቸው ።  የዶክተሩን  የምርመራ ውጤት ካዩ በኋላም ዘጠኝ አባላት ያሉት የዶክተሮች ቡድን ፡ ስለውጤቱ ትክክለኛነት ፈረሙበት ።

ይህን የሰሙት ሚስተር Stamatis አዘኑ ፡ ወደልጆቻቸው ቤት ከተመለሱ በኋላም መርዶውን ነግረዋቸው ተያይዘው ተላቀሱ ።
እንግዲህማ ወደ ሀገሬ ግሪክ ልሂድ ፡ ሞቴ እዛ ይሁን ቀብሬም  አባት አያቶቼ ባረፉበት ቦታ ይፈፀማል በማለት ፡ ከጥቂት ቀናት ቆይታ በኋላ ወደ ሀገራቸው ግሪክ ተመለሱ ።

Stamatis Moraitis ወደ ግሪክ ከተመለሱ በኋላ ምንም እንኳን ከስድስት ወራት በኋላ እንደሚሞቱ ፡ በአስር ሀኪሞች የተፈረመ ፡ ወረቀት ቢይዙም ፡ ለወትሮ ከሚሰሩት ስራ አልታቀቡም ።
በህይወታቸው ውስጥ የተከሰተ ምንም አይነት ለውጥ እንደሌለ ቆጥረው ፡ እንደድሮው አትክልቶቻቸውን ይንከባከባሉ ፡ ወራት ለቀረው እድሜ ፡ ለመድረስ አመታትን የሚፈልጉ ፍራፍሬዎች ይተክላሉ ፡

እንዲህ እንዲህ እያሉ ፡ ሳይታወቅ ያቺ የቀጠሮ ወር ደረሰችና ፡ ለመሞት ቀናትን  መቁጠር ጀመሩ ። ግን  ምንም የለም ። ሰውነታቸው ደክሞ ከዛሬ ነገ ድንገት እወድቅ ይሆን እያሉ በስጋት በመጠባበቅም  ፡ ስድስት ወሩን አለፉት ።
ሰባተኛ ወር ገባ ። ምንም የለም ።
አመት አለፈ ። ሰውየው ጭራሽ ንቁና ብርቱ መሆን ጀመሩ ። ሁለት ሶስት አመት አለፈ ። እንዲህ እንዲህ እያለ ፡ አስር አመት ሆናቸው እንደውም  ፡ በፊት አልፎ አልፎ ይሰማቸው የነበረው የህመም ስሜት ራሱ ጠፋ ።

እናም በአስረኛ አመታቸው ፡ ልጆቻቸውና ፡ የልጅ ልጆቻቸው ወደ ሚኖሩበት አሜሪካ ሄደው ሊያዩዋቸው ፈለጉና ወደዛ ተጓዙ ።
ካሁን አሁን መርዶ እንሰማ ይሆን ብለው ለአመታት የጠበቁት ዘመዶቻቸው ጋር በአካል ተገናኙ ።
...........
ከቀናት ቆይታ በኋላ ፡ ከዛሬ አስር አመትበፊት ፡ ለመሞት ስድስት ወራት ብቻ እንደሚቀራቸው የነገሯቸው ዶክተሮች ያሉበት ሆስፒታል ሄደው ሰላም ሊሏቸው በዛውም አስሩም ዶክተሮች የፈረሙበትን ወረቀት ለዶክተሮቹ  ሊያሳዩዋቸው ያዙና ወደ ሆስፒታሉ ሄዱ ።
ነገር ግን በሚያሳዝን ሁኔታ ፡ አንድም ዶክተር ማግኘት አልቻሉም ። ሁሉም ሀኪሞች በተለያየ ጊዜ በህመም አልፈዋል ።
......
ግሪካዊው Stamatis Moraitis ከአስር አመታት በፊት ይህን ምርመራ ሲያደርጉ የስልሳ አመት አዛውንት ነበሩ ። እና ይሞታሉ ከተባሉ በኋላ ለሌላ ለ42 አመታት በህይወት ኖረው ፡ በ102 አመታቸው ከጥቂት አመታት በፊት አልፈዋል ።
.............
ጥያቄው  አስር ዶክተር ፈረመ ?  ሳይሆን ፡  ከላይ ተፈርሟል ወይ ነው  ።

@wegoch
@wegoch
@wegoch

By wasihun
ለመሆኑ ለትዳር እንዴት ተመራረጣችሁ? ሲባሉ

“ያው አስተሳሰቡ
ህልሙ
እውኑ
ምናምን የሌለ ተመቸኝ።" ብለው ያዝጉሃል።

ይቺ መልስ ግን deep inside የምርጫ ቅስቀሳ እንደሆነች ሁላችንም እናውቃታለን።

እርግጠኛ አደለሁም
ብቻ 2009 ላይ ይመስለኛል
አዲስ አበባ ውስጥ ለፍርድ ቤት ከቀረቡ ክሶች መካከል ከ57 በመቶ በላይ የሚሆኑት የፍቺ መሆናቸውን አስታውሳለሁ። ጊዜው ስለረዘመ ቁጥሩ ላይ ስህተት ልፈጥር እችላለሁ

አንዳንዴ የተጋነነ impression ይዞ ወደ ትዳር መግባት የማታ የማታ የሚያመጣው መዘዝ ይህ ነው አይባልም።

በቀደም አንድ ጓደኛየን ልጠይቀው ቤቱ ሄጄ ነበር።
ሚስቱ አንድ የሚንቦራች ልጅ እየጠበቀች የቤተሰብ ጨዋታን ስታይ ደረስኩ።

ባልሽ የለም እንዴ?

ፊቷን ሀዘን እየመተረው ፈልፈላውን እያሳየችኝ
"እሱ 'ኮ ነው።”

ምን ተፈጥሮ ነው?

“በቃ ነጋ ስጭኝ ነው!
ጠባ ስጭኝ ነው!
ምግብ ላቀርብ ጎንበስ ካልኩ ዘሎ ጉብ ነው!
ተው ብለው አልሰማኝ አለ።
አሁን እንደምታየው ነው እየመነመነ እየመነመነ እየመነመነ ሄዶ የትልቁ ልጃችንን እኩያ መስሎ አረፈው። እስኪ አንተ ፍረደኝ አሁን ይሄ ባል ነው መጥገር?"

አናደደኝ
ገላመጥኩት
እዛው ሚስቱ ክንድ ላይ ሽጉጥ እንዳለ
"ካቹፓራ ሳያት አያስችለኝም” አለኝ

በሌላ ቀን ደግሞ
ሚስቱ ደጅ ላይ ኩርሲ ላይ ተቀምጣ አንድ አራስ ራቁቱን ጭኗ ላይ አስተኝታ ሰውነቱን በቅባት እያሸች ፀሀይ ታሞቀዋለች።

ባልሽስ?

እንባዋ ዠደደደደ እያለ ጭኗ ላይ የተኛውን አራስ ቂጡን ቸብ ቸብ አደረገችው

ባሏ ነበር
አደነጋገጤ

ባል ቀና ብሎ የእንጀራ እናቱን እየጠባ
ምን አለኝ?

“ጉጉጋጋ”

እንባየ ደርሶ ግጥም አለ🥴

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Tamiru temesgen
ከሚያነበው መጽሐፍ ገጽ ውስጥ የሰርግ ወሬ ሲነፍስበት ላፍታ ንባቡን ገታ አድርጎ፤ ሶፋ ላይ ተደላድላ ስልክ ላይ ያፈጠጠችውን ልጁን አያት። የእድሜዋ መናር አሳሰበው። ደግሶ ድሮ የመመረቅ እና የመጎረር፣ የመደነቅ ስሜት በአምሮት ናጠው።

"ለምን ነው ፍቅረኛ ይዘሽ ወደ ትዳር ጎዳና ማትራመጂው? እስከመቼ እንዲሁ በዋል ፈሰስ ትባክኛለሽ?" አላት።

ዐይኗን ከስልኳ ሳትነቅል "መች አለና" የሚል መልስ አሽቀነጠረች።

"ምኑ?"

"ፍቅርም፣ ሁነኛ ፍቅረኛም"

መልሷ ከነከነው። ህልምን ፈርቶ እንዴት ከመተኛት ያፈገፍጋል ሰው? "ፍቅር ላንቺ ምንድን ነው?"

"ክርስቶስ"

መልሷ ግማሽ ልቡን ሀሴት አጠጣው፤ ግን ድፍን መልስ አይወድም። "አብራሪው!"

"በቃ ለሚወዱት ሰው እስከሞት ድረስ ታምኖ መጓዝ፤ ያውም ያለማፈግፈግ፣ አሁን ያለው ወንዱም ሴቱም ታምኖ ሚሄደው ተቃቅፎ የልቡን እስኪያደርስ፤ ስጋውን እስኪያስደስት፣ ኪሱን እስክታልብ ነው። ስሜት እና ብልጠት እንጂ ፍቅር የለም አባ" ምርር አለች።

"ምን ያህል የፍቅር ሰው ነኝ ትያለሽ? ፍቅርንስ በገለጽሽው መንገድ ለመኖር ምን ያህል ዝግጁ ነሽ?"

ጨነቃት!
መልስ ከውስጧ ተሰለበ።
ዝም አለች!
ዝምታዋን ታክካ ራሷን መመርመር ያዘች።

#ኤልዳን
by @eldan29

@wegoch
@wegoch
@paappii
ድቅድቁ መሀል ያሉ ፋኖሶች
(ካሊድ አቅሉ)

የቦሌ መድሃኒያለም ቤተክርስትያንን አጥር ይዤ ቁልቁል አዘግማለው ፀሀይዋ እየሸሸች ለምሽት ምድርን ልታስረክብ ሽር ጉድ እያለች ነው ። የቤተክርስትያኑ አስተምሮት ለመስማት በጉዞዬ መሀል ጆሮዬን ለባለ ግርማ ሙገስ ድምፅ ባለቤት አባት ሰጠው " እውነተኛ  ደግ ጎተራው ሞላ አልሞላ እንብላ ብሎ ለምስኪን የቤቱን በር በሰፊው ሚከፍት ነው ። በሩን ዘግቶ አቅሉን እስኪስት ከተመገበ ብሃላ የከመረው መብል አላልቅ ሲለው ካደረማ ይበላሻል ለምስኪን እንስጠው ያሉት ደግ ነን ለማለት ሲዳዳቸው ይታያል ፤ ሞኞች ምስኪኑማ ተርቦ በራቹ ላይ እያለ ከርችማቹ መለሳቹት እኮ ያለ ሰዓቱ የመጣ ፈውስ ይባስ ቁስሉን ያመረቅዘዋል ። በጥሙ ሰዓት ያልደረሰ ውሃ ህይወቱ ካጣ ብሃላ እንደ ወንዝ ብታዘንቡለት አስክሬኑን ከማጠብያነት ውጪ ምን መላ ፈይዶ ? ስትሰጡ ኪሳቹ እስኪሞላ አትጠብቁ 'የመቅዶንያ ሰዎች ካላቸው ጥልቅ ድህነት ላይ ይሰጣሉ ' ይልም የለ ቃሉ"


ከመቅደሱ  ስለ ደግነት ሚማርክ ትምህርት ሲሻገር የኔዋ ደግ ባለቤቴ ፌቴ ላይ ድቅን አለችብኝ ሁሉን ነገርዋን ተቆጣጠረች ድግነትዋን ግን እንዴት ፋታ ትስጠው እጅዋ እና ልብዋ በምንም ቢከረቸሙ ከመከፈት አይታቀቡም ልግስና የመኖርዋ ዋስትና ነው ካልሰጠች የመኖርዋ ትርጉም ይጠፋታል ። አስተነፋፈስዋ ሚስተካከለው በቻለችው አቅም ክንድዋን ስትዘረጋ ነው ውይ ታድላ የነደደው ማፍቀሬ ላይ ቤንዝል አርከፈከፈችበት ቸርነትዋ አንገበገበኝ ከሷ ሌላ ማሰብ ተሳነኝ ። አንዳንድ ሰው አለ ደግሞ ክፉ ሰው እራሱ ደግ ሚለው ፍጥረተ አለሙን ሚያነቃቃ በመራር ከማጣፈጥ አልፎ ድባቡን በሙላ ሚቀይር አፍንጫችንን ይዘን በምንሄድበት መንገድ "ውይ ደስ የሚል ሽታ " ብለን የጠላነውን መንገድ በፍቅር ደጋግመን እንድንመላለስ ሚያረጉን እህቶች, አባቶች , እናት ,አክስት , ጓደኛ ጎረቤት ወዘተ . . . . .  አሉ አበቃልን ብለን የቁም ሞት ሊወርሰን ሲሰናዳ ከመንጋጋው ሚያድኑን . . . ህይወትን በእንባ ብቻ እንዳንከትባት የሳቅን ዙፋን ይዘው ከተፍ ሚሉልን ጭንቅን መውጫ መሰላሎች ድቅድቁ መሃል ያሉ ፋኖሶች  . . . . ።

~    ~    ~   ~   ~

@wegoch
@wegoch
@wegoch
2024/09/21 20:30:00
Back to Top
HTML Embed Code: