Telegram Web Link
ሥዕል ለማሳል በ+251984740577
ወይም @gebriel_19 ላይ  ፎቶ  በመላክ በ ተመጣጣኝ ዋጋ  ማዘዝ ይችላሉ!


@seiloch
@seiloch
ዝንቁል
።።።።።።

ከአያቴ ስድቦች ሁሉ ግንባሬ ላይ የተለጠፈ እስኪመስለኝ ሳስበው የሚያሳፍረኝ ስድብ ነው...ዝንቁል!ከሆነ ጊዜ በሁዋላ ከስድብነት ወደ ቅፅል ስምነት ተቀየረና ሳልወድ "አቤት" የምልበት መጠሪያዬ ሆኖ አረፈው።

"ዝንቁል ነይ አያ ከባዱ መጧል ሰላም በይው"ትለኛለች የምወደው አጎቴ ሲመጣ።
"ምነው እማ ስንቄ ካልጠፋ ስም?"ይላል አጎቴ እየሳቀ።ሰው ስሜን ሰምቶ ሲስቅ ለጉድ ነው 'ምሸማቀቀው!አንገቴን ወደ መሬት ትክል!በተለይ አጎቴ ከሳቀ!
"ምን ላርጋት እህ ብልጠት ያልሰራባትን!ነክሮ የተዋትን ከባድሰው!እንደው ፍርጃ ነውኮ እናንተየ!ሰው እንዴት በአስራ አምስት አመቱ እሳትና ውሀ አይለይም?ወይ አንች የአብማይቱ አታሳይኝ የለሽ!"ትላለች ሞኝነቴን ስታጎላ።በእርግጥ ሱቅ ስላክ ባለሱቆቹ ይከስራሉ ብዬ ስለማስብ መልስ አልቀበልም ብዬ አልቅሼ አውቃለሁ...አልክድም አምና አያቴ ለእንግዳ ሰርታ ያስቀመጠችውን ድንች ወጥ አሙቂ ያለችኝ ጊዜ እንዲጣፍጥላትና እንድትመሰገን ብዬ ብርጭቆ ሙሉ ስኳር ጨምሬበታለሁ።

"የሆነስ እንደሆን ስሙ ተዋህዷት አለቅጥ ቂል ያረጋታል እንጂ ምን ይበጃታል እማ ስንቄ?"ይሄኔ የእማ ስንቄ ቀይ መብራት ይበራል።ርዕስ ታስቀይራለች።በስሜ አልያም በጅልነቴ ዙሪያ ምክር ወይ አስተያየት ቢጤ ሊሰጧት ከቃጡ መስሚያዋ ጥጥ ነው።

"አንተ ከባዱ...እንደው ያች በቅሎህ ተሻላት አደራህ?"ትላለች የዝንቁልነቴን መዝገብ ትከድንና።እሷ ለመጣ ለሄደው የሞኝነቴን ነገር ተናግራ አልታክታት ቢልም እኔ ግን መስማቱ መረረኝና አንድ ቀን እንዲህ አልኳት።

"እማ ስንቄ"

"ኧ!ስንቋ አለቀኮ ብያለሁ እችን የቋቁቻም ዘር!እሰሰይ!የቆሎ ጓደኛዋ መሰልኳት?"

"ሁለተኛ ዝንቁል እንዳትይኝ!እናቴ ያወጣችልኝ ወርቅ የሆነ ስም አለኝ!ማንጠግቦሽ በይኝ"

"የጠገበ አህያ ይውጣብሽና ያላልኩሽ እንደሁ ትመችኝ?" አኩርፌ ወደውስጥ ስገባ የጎረቤታችንን የእማ ዝማምን ድምፅ ሰማሁ።ዘውትር  እየተጨናበሱ የሚመጡት እሳት ሊጭሩ ነው...የምጭርላቸው እኔ ብሆንም ...የአያቴ ጥሪ ተከተለ

"ዝንቁል ነይ ለዝማም እሳት ጫሪላት"

ማዕዶት ያየህ(ዘማርቆስ)
(
@gize_yayeh)

08/09/2015 ዓ.ም.


@wegoch
@wegoch
@paappii
አክስቴን እንዴት ፖለቲከኛ እንዳደረጉብኝ
።።።።።፡።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ጊቢያችን በሰጠን የ9ቀን  እረፍት ምን እንደምሰራበት ሳቅድ 5ኛው ቀን ላይ ደረስኩ...ያለ ቁምነገር!ወይ አላነበብኩ...ወይ ወግ ቢጤ አልሞነጨርኩ...ወይ ስካርፌን ጠምጥሜና ፀጉሬን አጎፍሬ የተነሳሁትን የአብዮተኛ ገጣሚት ፎቶ ፌስቡኬ ላይ አልለጠፍኩ...ብቻ የሆነ ቀን አክስቴ ዓይኔ ላይ ውል ስትልብኝ ተነሳሁና ቤቷ ሄድኩ።

"ቅንጭር ከየት ተገኘሽ?" አለችኝ።ከሲታነቴን ስታጋንን ነው "ቅንጭር"የምትለኝ።

"እታባ ደግሞ!እይ እስቲ እንዴት እንደወፈርኩ...ባህርዳርኮ ተመችቶኛል" ሰው ከሲታነቴን ሲነግረኝ ደሜ ነው ሚፈላው።

"አየሁት እቴ!ጣውላ ቂጥ!ምንሽ ነው የወፈረው?ያው የተላገ ጣውላ እንደመሰልሽ ነው!እንደው በምስክር ሞት ምናል ደህና ደህና ነገር ብትበይ?"

"ማነው ደግሞ ምስክር?"

"ምስክር ነዋ!"

"እኮ አላወቅሁትም"

"አይ እንግዲህ!አላወቅሁትም አይባልም አላወቅነውም ነው 'ሚባለው" ብላኝ እርፍ።ከመቀመጤ ሪሞቷን ቀሰረችና የጦፈ የፓለቲካ ክርክር ያለበትን ጣቢያ መርጣ ተደላድላ መከታተል ጀመረች።

"እታባ ኧረ ቀይሪው በማርያም!"

"ዝም በይ!ጁንታ!ምን ታውቂያለሽ ስለሀገር?ዝፈኝ አይበሉሽ እንጂ!"

"መቼስ ከሞት ዜና ዘፈን ይሻላል"

"እዬዬም ሲደላ ነው ቅንጭር!አታድርቂኝ !እዚሁ ደፍቼሽ መቃብርሽ ላይ ችግኝ እንዳልተክል!"

(ምንድነው ያስነኩብኝ ይችን ሴትዮ?ጊቢ ልሄድ ስል ልትቆርብ እያኮበኮበች አልነበር?ማነው የፖለቲካ ጋኔል ያስመታብኝ? 🤔🤔)

"እታባ ቆረብሽ አይደል?"

"ሲኖዶሱን ከፍለውት በየት በኩል?"( 🙄🙄 ምንም ብጠይቅ መልሷ ውስጥ ፖለቲካ አለ)
ወዲያው  4ዓመት የሞላው የልጅ ልጇ(የአክስቴ ልጅ) ወዲህ ወዲያ እያለ ሲጫወት ድመታቸው ላይ ቆመባትና አስጮሀት ።አክስቴ ብስጭት ብላ አምባረቀችበት

"የ20ሚሊየኑ  ባስ እላይህ ላይ ይውጣ!አፍርጠህ ትገድላት?" ለደቂቃዎች ክርክሩን ስትከታተል ቆየችና

"ቅንጭር...ጥሩ ቀን መጣሽ...ያች እምትወጃት አለችልሽ ሂጅ አቅርቢና ብይ"አለችኝ።መኮረኒ በአትክልቴን እየበላሁ ቤቱ ግድግዳ ላይ የተለጠፉትን አዳዲስ ምስሎች መታዘብ ጀመርኩ።ከፊት ለፊት ያለው ግድግዳ ላይ የዘመነ ካሴን ምስል ከነ ንግግሩ የያዘ መጠነኛ ባነር ተሰቅሏል።ከዓመት በፊት እዚሁ ግድግዳ ላይ የመድሃኔዓለም ስዕለ-አድህኖ ተሰቅሎ እንደነበር ትዝ አለኝና ደነገጥኩ።የቀኝ ግድግዳው ላይ የቀድሞው ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ምስል ተሰቅሏል።ከምስሉ በታች ያለውን ፅሁፍ ሳነብ ነው አክስቴ እንደለየላት የገባኝ።

"ባሏን ብታይ ውሽማዋን ጠላች ሆኖብኝ ነው ስትሞት ስለት ማስገባቴ!እሱ ቸሩ መድሃኔዓለም ነፍስህን በገነት ያኑራት!
                                     ያንተው ወይንሸት "


ወደሌላኛው ግድግዳ ስዞር አንድ ሱፍ ያጠለቀ ሰው  "ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ኢትዮጵያ ነን" ከሚለው ንግግሩ ጋር ተዘቅዝቆ ተሰቅሏል።

"እታባ ይሄን ሁሉ አንቺ ነሽ የለጠፍሽው?"

"ኋላስ ማን ሊለጥፈው ኖሯል!ግድግዳ ኬኛ!"

"በይ ደህና እደሪ ልሂድ"

"ልሂድ አይባልም ...እንሂድ ነው ሚባለው ቅንጭር"

(🙄🙄🙄🙄🙄🙄🙄🙄)

ማዕዶት ያየህ(ዘማርቆስ)
(@gize_yayeh)

10/09/2015 ዓ.ም.

@wegoch
@wegoch
@wegoch
ማንም በኬኔዲ እንዳይመጣብኝ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

   ኬኔዲ መንገሻን እንዴት እንደምወደውና ስስ ጎኔ መሆኑን ያወቁ አጠገቤ ሙዚቃውን ይከፍታሉ ።ተለክፌበት ነው መሰለኝ ድምፁን ከሰማሁ ጠላቴ ቤትም ሳልገባ አልቀርም።ለምን ቤተመንግስት አይሆንም?

  እና ኬኔዲን በተመለከተ የዛሬ ሁለት አመት ገደማ ያጋጠመኝ ትዝ አለኝ።ከቤታችን ጀርባ አንድ ፅድት ያለ ጊቢ ለብቻው ተከራይቶ የሚኖር የቅቤ ነጋዴ ነበር።ስሙን ቄስ ይጥራውና ቅዱስ ነበር ስሙ።

  ዘውትር ወደትምህርት ቤት ስሄድ ቪትዙን በአጠገቤ እያራመደ(ቪትዝ የያዘ ሰው እግረኛ ነው ሚመስለኝ😂 ተርቱብኝ ከፈለጋችሁ)

"ሄይ ቆንጆ" ይለኛል የሚያኝከውን ማስቲካ እስከ ሮቡዕ ገበያ እያስጮኸ።

"እንዴት አደርክ ቅዱስ?"

"አለሁልሽ...'ወደክላስ' ነሻ?ልሸኝሻ!"

"ውይ በጣም አመሰግናለሁ...ጓደኛዬ እየጠበቀችኝ ነው።"

"ታዲያ ምን ችግር አለው?ልሸኛችሁአ...ደውይላት" እንደማይተወኝ ሳውቅ ለጓደኛዬ ደወልኩ።ከቤት ትምህርት ቤት ያለው መንገድ በህይወቴ እንደዚያ ቀን ረዝሞቦኝ የሚያውቅም አይመስለኝም።ንግግሩ...ቀልዱ...ሳቁ...ወላ አተነፋፈሱ ይኮሰኩሳል።የሆነ parasite አንጀቴ ውስጥ የሚላወስ እስኪመስለኝ ነው ያቅለሸለሸኝ።

"ይገርማችሁዋል በጣም ሰቃይ ተማሪ ነበርኩ።ግን ከልጅነቴ ጀምሮ እኛ ኢትዮጵያውያን ቅቤ ላይ ያለን inspiration እንዳስደነቀኝ ነው።ቅቤ መነገድ አብሮኝ ያደገ ህልሜ ነበር..."አላለም?ቅርድድ!ማትሪክን 1.2 አምጥቶ ከትምህርት ጋር መቆራረጡን ያልሰማን መስሎት!

"By the way Gize...you is very talented...why not singing to me?"ሲል ትምህርት ቤታችን በር ላይ መድረሱን አላስተዋለም ነበር።RIP English!

  ከቀናት በሁዋላ  እንዲሁ ወደትምህርት ቤቴ ሳዘግም ከአጠገቤ ሲደርስ ቪትዙን አቁሞ

  "ሃይ ጊዜ"አለኝ።
ፀጉሩን እንደ ኬኔዲ መንገሻ ተቆርጧል።የሱን የሚመስል ሸሚዝ...ሱሪ...ጫማ...ከመኪናዋ ሙዚቃ ማጫወቻ የኬኔዲ ሙዚቃ ይንቆረቆራል።

  "ተው አአትከልክሏት
   ታንኳኳው በሬን
   ገብቷት ከመጣች
    ወዳ መውደዴን
    .........................
   እንደ ዱር ዝንጀሮ
    ጫካ እንደለመደ
   ቤት መግባት ይጠላል
    እሷን የወደደ..."

ቪትዙ ማርቼዲስ ሆና ታየችኝ ብላችሁስ?ከምኔው መኪና ውስጥ እንደገባሁና ክፍል ገብቼ እንደተቀመጥኩ አላውቅም።ብቻ የኒውተንን ህጎች እየተማርኩ ጭንቅላቴ ላይ የሚያቃጭል ዜማ ነበር።

"...ትዝብት ነው እቴ ትዝብት ነው
    ትዝብት ነው እቴ ትዝብት ነው
    ወዳጅ ከዞረ ፊቱ
     ከጨከነ አንጀቱ...."

በኬኔዲ አትምጡብኝ!

ማዕዶት ያየህ (ዘማርቆስ)
(
@gize_yayeh)
14/09/2015 ዓ.ም.


@wegoch
@wegoch
@paappii
ከተበሉስ አይቀር በጎጃም ቡዳ!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

   ጎጃሜ ነኝ።ያውም ማርቆሴ!የበላይ ዛር የሚያክለፈልፈኝ!እናላችሁ አምና እናት ከተማ ማርቆስን ለቅቄ ለአስኳላ ወደባህር   አዝግሜ ኖሮ ጠሀዩ ልብ ልቤን ሲጠብሰኝ ጊዜ በሳምንቴ ተመልሼ ወደማርቆስ!

  "ኧግ 'የኢንበርስቲ' ተማሪ!ይኸ ነው እንግዲህ ?በሳምንት ምላሽ ሆነ?"ኮብራ ምላሷ ጎረቤታችን ስንቴ ናት የምትለክፈኝ።

"የረሳሁዋቸው እቃዎች ስላሉ ትምህርት ሳይጀመር ልውሰዳቸው ብዬ ነው።''
  ''ነው?እምምምምም" ከንፈሯን አጣማ ትታኝ ሄደች።ከስንቴ ጋር ስሆን የETV ዜና ሳይቀር ይናፍቀኛል።የመሰለ ገ/ሕይወት ለንቦጭ ሁላ ውል ይልብኛል።ከያዘች አትፈታማ!ጥቃቅን ማብራሪያን ፍለጋ ልብህን እንደ ሎሊ ፖፕ ትጠባዋለች ነው 'ምልህ!!

አሁን በቀደም ዕለት ሱሪ ለብሼ የማላውቀው እኔ ቬል ሱሪዬን ወትፌ ስመናቀር አገኘችኝና

"ኧሯ!ሚጡ...ሱሪ ሲያምርብሽ አንቺ!"

"አመሰግናለሁ ...ያው የጊቢ ተማሪ እንምሰል ብለን ነው!"

"ኧራ!ልበሽ ኧረ!ለማናባቱ ብለሽ ደሞ!ይወጭቀው!ስንት ገዝተሽው ነው?"አለችኝ ሱሪዬን ቀለሙ እስኪለቅ እያየች።

"ቀላል ነው...950 "

"ዘጠኝ ከአምሳይ?ሸጋ ነው አንች!ተየት ነው የገዛሽው?ተአዲሱ ገበያ ነው?"

"አዎ ከዛው ነው"

"አምሮብሻል ነጋ ይሙት!ተንግዲህ ቀሚስ እንዳትለብሽ እንዲያውም...እና..."አቋረጥኳት

"በይ እሺ ሰላም ዋይ ስንቴ ጓደኞቼ እየጠበቁኝ ነው""ብያት ሄድኩ።'እህ ብዬ ከሰማሁዋት የገዛሁበትን ቀንና ሰዓት...ያጋዛኝን ሰው...የሸጠልኝን ሰው ...የልብሱን ብራንድ...መጠየቋ አይቀርም።ደሞ 'አምሮብሻል' ይባልልኛል!(😒😒ሰፈር ውስጥ "እናንተ!ያች የወለላ ልጅ ተበላሽታ አይል!ያችን የዶሮ ኩላሊት እምታክል ቂጧን በሱሪ ወትፋ ስትሞላፈጥ አይቻት..."እንደምትል መች ጠፍቶኝ?ዶሮ ኩላሊት ባይኖራት ራሱ የኔን ቅጥነት ለማጉላት ሲሆን እነስንቴ ቤት አላት)

የረሳሁዋቸውን እቃዎች ሸክፌ ወደ ባህርዳር ከተመለስኩ በሁዋላ ከዶርም ጓደኞቼ ጋር ብዙ ጊዜ እሰጥ አገባ ውስጥ የሚከተን ነገር ነበር።"ጎጃሜ ቡዳ ነው " የሚሏት ነገር!

"ጎጃሜ ቡዳ ነው
ብለሽ ያወራሽው
ሰው ሰውን ሲበላ
የታባሽ አየሽው?"  ከአፌ የማይጠፋ ግጥም ሆነ። በጨዋታችን መሀል አቦሰም ጥለን ዕድሉ የኔ ከሆነ "ድሮስ ጎጃሜ!"ይላሉ አፋቸውን ሸርመም አድርገው።ነገሮች በአንድም በሌላም መንገድ የዕድል ገፃቸው ወደኔ ከዞረ "ጎጃሜ አይደለች?"የሚሉት ጥቂት አይደሉም።አንዱማ እንዲያውም የሆነ ቀን  'ላማክርሽ እፈልጋለሁ'ብሎ በቁምነገር ቀጠረኝና ተገናኘን።

"እየውልሽ ጊዜ...እእ...እንትን ነው"
"ምን?"
"የሆነች ልጅ ወድጄ..."
"ኧረ?ማናት?"
"አታውቂአትም"
"እና አናግረሀታል?"
"ለሱ ነውኮ የፈለኩሽ"
"እንዳናግርልህ?"
"ኧረ በንግግር የሚገባት አይደለችም ልጅቱ"
"እና ምን ላርግልህ?"
"ያ...ው...ጎጃሜ አይደለሽ?እናንተኮ እዚህ ነገር ላይ አትታሙም...መ...ስተፋቅር እንድትሰሪልኝ ወይ እንድታሰሪልኝ ነበር" ብሎኝ እርርርርርፍ!
     ከዚህም ከዚያም የጎጄን ቡዳነት ሲደጋግሙብኝ መገንፈሉን እየተውኩ እኔው ራሴ በራሴ መቀለድ ጀመርኩ።

"ጎጃሜ ቡዳ ነው
  ብለሽ ያወራሽው
  ሰውን ሰው ሲበላው
  የታባሽ አየሽው ?"

እል የነበርኩት ልጅ

"ቡዳ ነው ይሉታል
  ጎጃምን በሙሉ
መች ጣዕሙ ሊታወቅ
ሰው ይዘው ካልበሉ"  ማለት ጀመርኩ።በሊታን መምረጥ ቢቻል ከተበሉስ አይቀር በጎጃም ቡዳ!ፍቅር ነዋ ምትለፈልፈው!!

  ማዕዶት ያየህ(ዘማርቆስ)
(
@gize_yayeh)

15/09/2015 ዓ.ም.


@wegoch
@wegoch
@paappii
...
ዝም ያለ መልክ ረጋ ያለ ሰውነት ያስደነግጣል?
ለምን እንደምደነግጥ እኮ ነው ያልገባኝ።
ልክ ሳየው ልቤ ምቱን ያፈጥነዋል፤ እጆቼ መንቀጥቀጥ ፊቴ መቅላት ይጀምራል። አይኖቼን ምን ለይ እንደማሳርፍ እንዴት ማውራት እንዳለብኝ ግራ እጋባለው። መንገድ ለይ ከሆንኩ ደግሞ ልክ ገና ከቤት እንደወጣ ሰው እግሬ ይማታብኛል፤ አየር ለይ የምረግጥ ይመስል እወላከፋለው። ስለ ራሴ የነበረኝ መረዳት ሚዛኑን ይስትና ፊቴ ለይ ያለች ትንሽዬ ነጥብ ትታየው ይሆን ብዬ ስጨነቅ ራሴን አገኘዋለው።

አይንን ያዝ በሚያደርግ መልኩ አይደለም አይኖቼን አስሮ ያቆያቸው፤ አንደበተ-ርትዑነቱም አይደለም ሲያወራ በሰማሁት የሚያሰኘኝ፤ በሩቅ በሚታየው ሞገሱም አይደለም ልቤን ሲያርደው የሚውለው።

እዩኝ በሚሉ መልኮች መሀል ነው የሱን ዝም ያለ ውበት ያየሁት፤ ከብዙ ተናጋሪዎች መሀል ገኖ ነው የሱ አድማጭነት እልፍ የሚያስወራኝ እልፍ የሚያፅፈኝ። ስክነት ያለው ህይወቱ ነው በሺህ ችኩል በሺህ ጥድፊያ መሀል ሁሉን አደብዝዞ እሱን ብቻ የሚያስመለክተኝ። የእውነቱን ኑሮ ነው ኑረቱን እንድወድለት ያስገደደኝ።

ያወራኝ እለት ቃላት ብቻ አልነበረም ከአንደበቱ የሰማሁት፤ ዝም ቢል እንኳን ብዙ መናገር የሚችል ገፅ ተችሮታል። እሱ ሲያወራ ስረታ እሱ ሲናገር ስርድ ይታወቀኛል። መቼ አምኜ መቼ እንደተቀበልኩት መቼስ ልቤን አሳልፌ እንደሰጠው እንጃ። ግን ከነበርኩበት ሁካታና ጥድፊያ አውጥቶ ሲያሰክነኝ ይሰማኛል። ዘመንን ማዘዝ ይችል ይመስል እሱ ጋር ስሆን የረሳሁት ሰላም የረሳሁት ፀጥታ በእርጋታ ከሚፈስ ጊዜ ጋር ዙሪያዬን ይከበኛል። ሰው ለመማረክ አለኝ የሚለውን የማንነት መልክ ይዞ ከውድድር አይሰለፍም ይልቁንስ ባለበት ይቆያል እንጂ። ከራሱ ጋር፤ የታይታ ካልሆነው ገዢ ስብዕናው ጋር።
እናም ሚዛን ልኬቱን ማጣት ይጀምራል። ከተናገሩት ሁሉ ይልቅ እሱ ይደመጣል፤ ከታዩት ሁሉ ይልቅ አይን ለማረፊያው እሱን ይናፍቃል፤ ከተገዳደሩት ሁሉ ይልቅ እሱ ሳይታገል ይጥላል። በቀደዱለት አይፈስም ነገር ግን በዙሪያው ያለውን ሁሉ ይዞ ወደ እራሱ መንገድ መሻገር ይቻለዋል።

"ይሄ ሰው ማንነው?" ያሰኘኛል፤ ማንነው? የጊዜው ኑረት እንዲህ የሚገላበጥለት። ማንስ ነው? ብቻውን ኑሮ በብዙ ሚረታው። እንዴት ሆኖለት ነው ሲያደምጥ መሰማት ሲመለከት ማውራት ለሱ የተቻለው። እንዴት ብረዳው እንዴት ቢገባኝ ነው ሚዛኔን በእሱ ተክቼ ሰው የማገዝፈው ከልኬት ማወረደው። ምኔን ቢያገኘው ምኔን ቢነካው ነው ዛሬ ገና መኖር የጀመርኩ ይመስል እጆቹ ካልያዙኝ የምንገዳገደው።

በዚህ ልክ የራስ ሰው በዚህ ልክ አዋቂ በዚህ ልክ አስተዋይ... ይሄ ሰው ማነው?

@wegoch
@wegoch
@paappii

By mahi
#ለወንዶች_ብቻ

ይኸውልህ።

ዋቴ ብልጽግና በሳይንስ ሳይሆን በጥንቁልናና በትንቢት የሚያስተዳድራት አገር በአምስት አመት ውስጥ 1.5 ትሪልዮን ዶላር የጦርነት ኪሳራ አምጥታ፣ አሁን አለም ላይ የሌለ 107% Hyperinflation ውስጥ ገብታ ሕዝቦቿን በኑሮ ውድነት እየለበለበች፣ በ15 ቢልዮን ዶላር ቅንጡ ቤተ መንግስት ትሰራለች። ላቲንም በለው ኤዥያ፣ አፍሪቃም ጭምር - Developing Countries የተሰኙ አዳጊ አገራት ውስጥ ቅንጡ ቤተ መንግስት አይሰራም፤ ድሃ ናቸዋ!

ስማ ስማ።

በቀጣይ ሁለት አመታት ኑሮ ከዚህ በላይ ይወደዳል። Anarchy ይሰፍናል። ደሞዝህ ከወር እስከ ወር ስለማያደርስህ ከሚስትህ ጋራ ትጣላለህ፣ ትዳርህ ይበጠበጣል። ''አላቅልሽም አብቃቂ'' እያልክ በየቀኑ ልትጨቃጨቅ ነው። እሷም ''ብሩን ጠጣህበት፣ ተዝናናህበት'' ብላ ልትበጠብጥህ ነው።

መፍትሄውን እንካ።

1 - ቆጥብ፣ ወጪህን በ60% ቀንስ። ስለ Minimalism አንብብ። ከካናዳዊው የF.I.R.E አቀንቃኝ Mr Money Mustache፣ ስለ ችጋራም አኗኗር እና ስለ Early Retirement የጻፋቸውን ከጉግል አጥና።

-

2 - ዝም ብለህ ውለታ አትዋል። ቢሮክራሲ አትቀንስ፣ መረጃ በነፃ አታቀብል። ኮሚሽን ጠይቅ። ደልል። አስከፍል። ክፈሉ ለማለት አትፈር። ሰው ሁሉ አስከፍሎ ነው ቀላልና ከባድ ጉዳይ የሚያሳልጠው።

-

3 - ስረቅ። አጭበርብር። ጉቦ ተቀበል። የእጅ ውረዱ ማለትን ተለማመድ። ስራ ላይ በኔትዎርክ ተደራጅተህ ስረቅ። (አትመፃደቅ - የብልጽግና መንግስት የሱን ብሔር ሰዎች ሰብስቦ ዝረፉ ብሎ ሲያሰማራ አንተ ጨዋ ጨዋ ከሰራህ ተግጠህ ታልቃታለህ)

-

4 - ውጪ አገር ወንድም፣ እህት፣ ጓደኛ ካለህ - ''ገንዘብ ካልላክልኝ ሁለተኛ እንዳትደውል'' በለው። ዳያስፖራ ጨለል ነው፣ ቀውሶች ናቸው። ብቸኝነት ሲያገረጣቸው በየሳምንቱ ይደውሉልህ እና ስለ ኑሮ ውድነት ጠይቀውህ ራሳቸውን ያጽናናሉ። አስር ብር ግን አይፈለጡም።

''ስንቴ ልንገርህ፣ ደህና ገንዘብ፣ ወይንም ወሳኝ እቃ ካልላክልኝ ሁለተኛ አትደውል፣ ቢዚ ነኝ'' ብለህ ጆሮው ላይ ዝጋበት።

-

5 - ቅጥረኛ አትሁን። ደሞዝተኛ አትሁን። በጠዋት ወጥቶ የታክሲ ወረፋ ተሰልፎ፣ ሙሉ ቀን ሰርቶ፣ የአለቃን Expectations አሟልቶ፣ በወር መጨረሻ የተመታ ደሞዝ መቀበል #ያደነዝዛል#ዶማ ያደርጋል። . . .ስራ ለቅቄስ? አትበለኝ። እሱማ ለራሴ ሰዎች የተያዘ ሚስጥር ነው፤ አልነግርህም።

-

ብቻ ይሄንን ጥሬ ሐቅ ልብ በል - በእነዚህ ሰዎች የስልጣን ዘመን እዚህ አገር ላይ ጠንክሮ መስራት #ያደኸያል

-

አትፍዘዝ፣
ታመጣለህ መዘዝ!

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Eyob mihretab
iPhone ባይኖርህ iPhone ያለው ጓደኛ ይኑርህ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

  "መልክ ይስጠኝ እንጂ ሙያ ከጎረቤት እማራለሁ" ትላለች እናቴ።

"Snapchat ይኑር እንጂ ሙያ ከጎረቤት እማራለሁ" ዘመን ላይ ሳንደርስ በፊት።ዕድሜ ለካሜራ ጥራትና ለSnapchat እኔና መሰል መልከጥፉአውያን መልክን ትተን ስለሙያ መጨነቅ ከጀመርን ቆየን!በቀደም አንዷ የሰፈሬ ልጅ ቴሌግራሟ ላይ የለጠፈችውን ፎቶዋን አይቼ ጉድ ብዬ አልበቃኝ አለ!ሳውቃትኮ ትል ያላመጠው ቲማቲም ነው ምትመስለው!እንዲያውም የአፍንጫዋን ትልቅነት በተመለከተ እናቷ ወ/ሮ አበሩ ሲቀልዱባት

  "ዝንጀር እስቲ ወጡን አሽትችና ጨውን ንገሪኝ" ይሏታል።ሰፈር ውስጥ ሁሉም "ዝንጀር" ነው የሚላት...ዕውነተኛ ስሟ "ጤና"እስኪረሳ ድረስ!ታዲያ ዝንጀር ዩኒቨርስቲ ስትገባ አጎቷ ከካናዳ IPhone ላከላት።በሄደች በሳምንቷ "ለእታባ አሳይልኝ"ብላ ጊቢ የተነሳቻቸውን ፎቶዎቿን በቴሌግራም ላከችልኝ።

  ወ/ሮ አበሩ ስልኬን እያገላበጡ ፎቶውን አዩትና

  "ሚጡ...የዝንጀርን ፎቶ አምጭው እንጅ"
  "ይኸው ዝንጀር ናትኮ"
   "ክይ!ቅማላም!...መሀይም ነኝ እንጅ መቀለጃ ነኝ?"
   "ኧረ ማርያምን አበርዬ!ይኸ ባለፈው የገዙላት ቲሸርት አይደል እንዴ?"
   "የት ገብቶ ነው ያ ለምቦጭ?ያ ሁላ ቡግር ምን ዋጠው?"
   "አገሩ ተመችቷት ይሆናላ"
   "በሳምንት?እኔ መልኳ መለስ ቢል ብየ በየሳምንቱ የቅቤ ስቀፈቅፍ ኖሬ እዛ ኸዳ በሳምንት ይኸን ያህል ወዝ?ይች በልቶ ካጅ!""

ዝንጀር ለእረፍት ስትመጣ በስልኳ የተወሰኑ ፎቶዎች አስቀረሁና ፌስቡኬ ላይ ለጠፍኩ።ከዚህ ቀደም ለፎቶዎቼ የተሰጡኝን አስተያየቶች መለስ ብዬ ቃኘሁ።

  ጥሎብኝ አንድ መፅሀፍ ባነበብኩ ቁጥር ከመፅሃፉ ጋር ፎቶ ተነስቶ የመለጠፍ ልምድ አለኝ።''የኢትዮጵያ ታሪክ ከኖኅ እስከ ኢህአዴግ"ከሚለው መፅሐፍ ጋር ፀጉሬን አጎፍሬ ለተነሳሁት ፎቶ አንዱ ተንከሲስ እንዲህ የሚል አስተያየት አስቀምጦልኛል።

  "የ77ቱ ድርቅ መልክ ቢኖረው አንቺን ይመስላል።ዘቅዝቄ እንደ መጥረጊያ ብጠቀምሽ ጉራንጉሩ ሁላ አይቀርሽም ስታፀጅው።"

ዝቅ ብሎ ደግሞ ሌላኛው

   "አንቀፅ 39 ፊት!ፊትሽ የመገንጠል ስሜቴን ቀሰቀሰው!ከኢትዮጵያ ውጣ ውጣ የሚለኝ መጣ!" ብሎኛል።ወረድ ስል ደግሞ

  "ፀሀዩ ከሮ ጥላ ተወዶ ፊት!ፊትሽ ህልም ይመስላል...አይቼው ልጮህም አማረኝ ልሮጥም አማረኝ ግን አልቻልኩም...ፍቺና ወይ አስፈቺና ገላግይን አቦ!" ሌላው ደግሞ

"ይኸን ግንባር ይዘሽ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብትሄጂ የራስሽ ክልል ይኖርሽ ነበር!"

  ከኔ ፎቶ በላይ 'ኮመንቶቹ' ናቸው ላይክ ያገኙት።በዝንጀር iPhone ታሪክ ሳይቀየር በፊት...ከአሁኖቹ "ኮመንቶች" በጥቂቱ

   "ፍንጭትሽ ደስ ስትል...ካንቺ ፍንጭት ከኔ ዲምፕል 'ሼር' አርገን ለምን አንዲት ቆንጅዬ ልጅ አንወልድም?"

  "ዓይኖችሽ  አንድነት ፓርክን ያክላሉ።ፍቀጂልኝና ሰልፊ ልነሳባቸው"
   
  

ወይ iPhone ወይ iPhone ያለው ጓደኛ ይኑርህ!

ማዕዶት ያየህ(ዘማርቆስ)
(
@gize_yayeh)

15/09/2015 ዓ.ም.


@wegoch
@wegoch
@paappii
ከቤት ስወጣ የሚያጋጥመኝ ሶስት አይነት ሰው ነው። ሙሉ በሙሉ የነቃ (ሞቲቬሽናል ስፒች ሚሰማ መሰለኝ) ሙሉ በሙሉ ያልነቃ (ከምኔው ታክሲ ውስጠሰ ገብቼ ያቋረጥኩትን እንቅልፍ በቀጠልኩ የሚል) እና በከፊል የነቃ ሰው ይገኙበታል። በከፊል የነቃውን ኢዜማ ልትሉት ትችላላችሁ🙂

ቅም አያቴ እስልምናን ከመቀበሉ በፊት መዳፍ ያነብ ነበር የሚል ታሪክ ሰምቻለሁ። እኔም የርሱ የልጅ ልጅ ልጅ ልጅ የሰው ፊት ማንበብ ቀኔን እጀምራለሁ።

ለታክሲ ከተሰለፉት ቁርሱን ቂንጬ የበላ ፣ ያደረ ሽሮ የበላና አሳር የበላን አብጠርጥሬ የመለየት ልዩ ተስጥኦ አለኝ። ከቤታቸው ፓንኬክ በልተው ሚወጡ ይኖሩ ይሆናል። የታክሲ ሰልፍ ላይ ግን አጋጥመውኝ አያውቁም።
ለአንድ ብጣሽ ቁርስ ወተት እንቁላል ዱቄት የሚያባክን ሰው ወይ መኪና አለው ወይ በራይድ ነው ሚንቀሳቀሰው። ድንገት ታክሲ ከተሰለፈ ይህንን ፅሁፍ እየፃፈ ነው😀

ጥሩ ቁርስ የጥሩ ቀን ማስጀመርያ ነው ይላል ኒቼ🙂 ኒቼ እንዲህ ያለ ነገር ይበል አይበል አላውቅም። ዮናስ ዘውዴ ይህንን ፖስት ካየው ግን ቀጣይ ብሔራዊ ቴአትር የሚዘጋጅ መድረክ ላይ ኒቼ እንዳለው ብሎ እንደሚጠቅሰው እርግጠኛ ነኝ🙂

ሰው የሆዱን በዝምታ ቢሸሽግ ግንባሩን ግን በፍፁም መሸሸግ አይቻለውም። ለሊቱን አለሙን ሲቀጭ ያደረና በትራስ እጦት አንገቱ የተቀጨ መለየት ለኔ በጣም ቀላል ነው።
አንዲት ቆንጆ በአጠገባችን ስታልፍ ዞሮ ካላየ ወይ ባለቤቱ አጠገቡ አለች ወይም አንገቱ ተቀጭቷል። አለዚያ ሌላ ነገር እንድንጠረጥር እንገደዳለን።

መጠርጠር ስል ሰሞኑን ሀገር እንደሚበጠብጡ የተጠረጠሩ ሰዎች እየታሰሩ ነው ተብሏል። አሁንም ግን የዘራ በረሮ ሚሸጡ ሰዎችና ጌታ መጣልህ እያሉ ሚያስደነግጡን ሰዎች ከተማው ላይ በነፃነት እየተንቀሳቀሱ ነው።ከቴም ሰላም ማስከበር¡

ትላንት ስራ ውዬ በድካም ተርከም ተርከም እያልኩ አስፋልት ስሻገር በግብዳ ስፒከር "ጌታ እየመጣ ነው" ብሎ አንባረቁብኝ። በድንጋጤ መኪና ውስጥ ተወርውሬ ነበር። ጌታ ሳይመጣ እኔ ወደርሱ ሄጄ ነበር😑

የሆነው ሆኖ "ቡና ጠጥቶ ከቤት መውጣት የብልሆች መገለጫ ነው ይላል ኒቼ"🙂

@wegoch
@wegoch
@paappii

By #Muaz jemal
Forwarded from ግጥም ብቻ 📘 (Leul M.)
ሥዕል ለማሳል በ+251984740577
ወይም @gebriel_19 ላይ  ፎቶ  በመላክ በ ተመጣጣኝ ዋጋ  ማዘዝ ይችላሉ!


@seiloch
@seiloch
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
   ዘርሽ ቢቆጠር ጉድፍ የለበትም።የጀግና ዘር ነሽ!በአባትሽ በኩል ቢኬድ ቅድመ አያትሽ የሚኒሊክ ዘብ ጠባቂ የቅርብ ወዳጅ ነበሩ።በእናትሽም በኩል ቢኬድ ምንጅላትሽ የሽምብራ ቆሬ ጦርነት ላይ የግራኝ አህመድን አሽከር በቀይ ጥይት ግራ ቂጡን ነድለውት ሲቅመደመድ ኖሮ መሞቱን አዲስ ዘመን ጋዜጣ የሆነ ጊዜ ላይ አስነብቧል።

  በማን እንደወጣሽ ባይታወቅም፣ዕድልሽ ይሁን ተፈጥሮሽ ግልጽ ባይሆንም፣ከአንድ ወንድ አትረጊም።ተረግመሽ ነው መሰል ከሚያጋጥሙሽ ወንዶች 25 % የሚሆኑት የጥሪ ማሳመሪያ ተጠቃሚዎች ናቸው። ልክ ስትደውይ
  "ወይ ሞልቶ ላይሞላ
   ለዚች ዓለም ኑሮ
   እኔ አልጨነቅም
   ከዛሬ ጀምሮ" የሚል መፈክር ይሁን ዘፈን ያልለየለት ብሶት ትሰሚያለሽ።(ሳትረገሚማ አትቀሪም!) ሌሎቹ 25 % የሚሆኑት ደግሞ የትንሽ ጣታቸውን ጥፍር የሚያሳድጉ ናቸው።ደህና መትረየስ እንዳነገበ ጀግና በጥፍራቸው አይን አ*ቸውን እየመነገሉ፣የከናፍራቸው ጫፍ ላይ የወጣችን ቡግር እየፈነቀሉ ቀንሽን ለሰማይ ለምድር የከበደ 'ትራጀዲ'ያደርጉብሻል።(በእርግጠኝነት ምንጅላትሽ የመቱት አሽከር ነው የረገመሽ!)

'እፎፎፎይ'ብለሽ ወደ ሌላኛው 25% ስትሮጪ መፈናፈኛ እስኪያጣ ሱሪውን የሚያስጠብብ፣ቀሪው 25% ደግሞ የሞተ ፍየል በብብቱ የያዘ እስኪመስል ድረስ አስጨናቂ ጠረን ያለው፣ላቡ ከብብቱ ስር እንደቀበና የሚወርድ ክልል-ዘለል የሆነ ፌደራላዊ ግማት ላይ ትወድቂያለሽ ።

"እና እንዴት ነው ኑሮው?"ይልሻል አፉ እንደተቀየደ ፈረስ ድዱን እያሰጣ።

  "ደህና ነው መቸም" ትያለሽ ሰው ያገኘሽ መስሎሽ።

"እናስ ተማሪ ነሽ ሰራተኛ?"ይልሻል  እንዳገጠጠ አንዴ ከላይ ወደታች፣አንዴ ደግሞ ከታች ወደ ላይ scan እያደረገሽ።

  አንድ ቀን አልፎልሽ በፀሃፊነት ወደምትሰሪበት ድርጅት ለጉዳይ የመጣ ነጋዴ ነኝ ባይ ትተዋወቂያለሽ...ቀጠሮ ትይዣለሽ።ደሞዝሽ በፈቀደው መጠን ለመዘነጥ ትሞክሪያለሽ።ከታች እናትሽ መሰረተ-ትምህርት ሲማሩ ለብሰውት ይሄዱ የነበረውን ቀሚስ ከወገቡ አስቆርጠሽ በሰውነትሽ ልክ አሰፍተሽ ለብሰሻል።ከላይ ከሰልቫጅ ተራ በ80 ብር የገዛሻትን ቲሸርት ጣል አድርገሻል።ባለፈው ወር እቁብ ሲደርስሽ የገዛሻትን የ 200 ብር ሽቶ "ምናባቱ!ሺህ ዓመት አይኖር!"ብለሽ የግራ ብብትሽ ስር አንዴ ረጭተሻታል። የቀኙንም'ኮ ልትረጭው ነበር ግን አሰብ አረግሽና "መቸስ ከጎኑ ስሄድ አንድ ጎኔ ነው በሱ በኩል የሚሆን"ብለሽ ተውሽው።ኤታባቱ!ሺህ ዓመት አይኖር!

  ፀጉርሽን በ 50 ብር ካስክ አፍሪካዊ ለዛውን ታሳጭዋለሽ።ተመስገን ነው!ሰሞኑን ማበጠሪያ አይሰበርብሽም!በፈቃደኝነት የሚያፈናቅል ሽታ ያለውን ሎሽንሽን መላ ሰውነትሽን ተቀብተሻል...ለእግርሽ ግጣም ከቆራሌው የተረፈች አንዲት ክፍት ጫማሽን ግጥም ታደርጊና ትሄጃለሽ !ወደ 'ዴትሽ'

ሰውዬሽም ከሞላ ጎደል ዘንጧል።

  "ምን ይምጣ የሚበላ?"
  "አንተ የተመቸህ ይሁን"
ጥብስ ይታዘዝና ጠበሳው ይቀጥላል ። ጥብሱ እስኪደርስ...

"እና...ደሞዜ 3000 ብር ነው አልሺኝ?"
"3200"
"ያው ነው...አሁን እኔ ወደዚህ ስመጣ የኮንትራት ታክሲ 200 ብር ነው የከፈልኩት" ብሎ ኩም ያረግሻል።ጥብሱ ደርሶ ከተበላ በሁዋላ
  "እና የቤት ኪራይ 600 ብር ነው የምከፍለው አልሽኝ?"
  "550"
  "ያው ነው 50 ብር ማለትኮ ለአስተናጋጅ የሚሰጥ 'ቲፕ' ነው"
  "እሱሰ ልክ ነህ"ከጥቂት ዝምታ በሁዋላ
"ተጫወች እንጂ ምነው?እኔ ዝም የሚል ሰው አልወድም...የምሬን ነው!የሚያስጨንቅሽ ነገር ካለ ንገሪኝ"
"ኧረ የለም!አመሰግናለሁ"
  "ምስጋና ስንቅ አይሆንም ...ባይሆን..."
  "ባይሆን ምን?"
  "ባይሆን ሌላ ጊዜ በደንብ ታጫውችኛለሽ እ?ሃሃሃሃሃ"
በኮንትሮባንድ የገባ ሳቅ ይለቅብሻል።
"እንሂድ እየመሸ ነው"ትያለሽ ሰዓትሽን አየት ታደርጊና።
"ኧረ ገና ምኑን ያዝነውና!አይዞሽ እኔ ራሴ ነኝ በኮንትራት ታክሲ ቤትሽ የማደርስሽ"ብሎ ሳይሰማሽ መጠጥ ያዛል ።'አልኮል አልጠጣም' ብለሽ ለመገገም ትሞክሪያለሽ።
"ምናይነቷ ናት ባካችሁ?ልንዝናና አይደል ወይ የመጣነው?እንደ ህፃን ፋንታ ልትጠጪ ነው?"ብሎ እንደምንም ቀበጣጥሮ አንድ ቢራ ያስከፍትልሻል።እየተሽኮረመምሽ መቀማመስ ትጀምሪያለሽ።ሞቅ ሲልሽ ፍርሀት ቢጤ ይሰማሽና

"እየመሸ ነው ብሄድ ሳይሻል አይቀርም"ስትይ ሰዓቱን አየት ያደርግና 
"ሆሆሆሆ እንዴት ያለችው ላይ ጣለኝ ባካችሁ?ገናኮ 3 ሰዓት ነው...ምን የሚያስቸኩል ነገር አለ?ገብተሽ አታበስይ ምናለሽ?"

"እሱስ አላበስልም...አከራዬ ደስ አይላቸውም እንጂ..."
"አአአአይ ...ለዛሬ የኪራይ ቤትሽን እርሻት...እዚሁ ቆንጆ room እይዝልሻለሁ" ሲልሽ መፍራት ትጀምሪያለሽ።

"ኧረረረረ አያስፈልግም ቤት እገባለሁ"ስትይ
"ለማንኛውም እየጠጣሽ "ይልሽና በተቀመጥሽበት ትቶሽ ወደ እንግዳ ተቀባዪአ ይሄዳል።ከቆይታ በሁዋላ አንድ ቁልፍ ይዞ ይመጣል።

"ምን...ባክሽ...' 'ሩሞቹ' ተይዘው አልቀዋል' አለችኝኮ...አይዞሽ double bed ነው የያዝኩት...መቼም የመሸበት አላሳድርም አትይም ሃሃሃሃሃ"
አሁን የምር...የምር...የምር ትፈሪያለሽ።ያቺ ተቆንጥጣ ያደገችዋ...ያቺ በዘመን ግሳንግስ ቀለሟን ያደበዘዝሽው አንቺነትሽ እየተፍገመገመች
"አምልጪ!...ተበላሽ! ትልሻለች።
"አአአአይ....ኧረ አትቸገር እዚሁ አካባቢ አንድ ጓደኛ አለችኝ እሷ ጋር እደውላለሁ..."
"ቆይ አላመንሽኝም ማለት ነው?ስታስቢው በጥብስና በቢራ የሴትን ገላ የምገዛ ርካሽ እመስላለሁ?I really feel sorry እንደዛ ካሰብሽኝ"
"ኧረ...እንደዛ ማለቴኮ አይደለም...አስቸገርኩህ ብዬ ነው እንጂ!እሺ በቃ" ትይውና

"እሳትና ጭድ አንድ ክፍል ውስጥ ያድሩ ዘንድ ደግ አይደለም...አንዳቸው የሌላቸው መጥፊያ ይሆናሉና " የሚለውን ቃል ጥሳችሁ አንድ ጣራ ስር ታድራላችሁ።

ጧት ለሰዓታት የተቃጠልሽበት ፀጉርሽ ፈርሶ...ጋኔል ያደረባት ጃርት መስለሽ ወደሰፈርሽ ትመለሻለሽ።ወደ መዳረሻሽ ገደማ ፋርማሲ ታይና ጎራ ትያለሽ።ሰው የተባለ ፍጡር ገና ከእናታቸው ማህፀን ሳሉ ጀምሮ የማያምኑት አከራይሽን ፋርማሲ ውስጥ ስታያቸው ልብሽ በአፍሽ ልትወጣ ትደርሳለች።በተጠራጣሪ አይኖቻቸው ከእግር እስከራስሽ አብጠርጥረው ያዩሽና
"አንች የኔ ዓለም የት ጠፍተሽ ነው ስታሸብሪን ያመሸሽ?"ይሉሻል።

"እንዴት አደሩ እትዬ?ማታ...ኮ አምሽቼ የምጨርሰው ስራ ኖሮኝ ሰዓት ስለሄደብኝ እንዳልረብሻችሁ ብዬ እዛው አድሬ ነው"

"ኧሯሯሯሯሯ!እና ስልኩ ቢከፈት ምን ይላል አደራሽ?...በዚህ በከፋ ዘመን እንደው ሰውስ ያስባል አይባልም?ጅብ በመውጫው አንችን ፍለጋ እንጉለሌ ልህድ?"

"ይቅርታ በጣም"

"የሆነው ሁኖ...ምን ልትገዥ ነው?"
ብለው እጅ ከፉ እንደተያዘ ሌባ ያፋጥጡሻል።

"እ...እንቅልፉ ነው መሰል ትንሽ ራሴን አሞኛል ማስታገሻ ልግዛ ብዬ"

"እህህህህም ነው?በይ...ደህና ዋይ"ብለውሽ ከፋርማሲው ሲወጡ የዘመናት ሀጥያትሽ የተፋቀልሽ ያህል ይቀልሽና "እፎፎፎፎፎፎይ!"ትያለሽ በሆድሽ።የምትገዥውን ገዝተሽ ስትወጪ አከራይሽ ፋርማሲው በር ላይ ቆመዋል።ስታያቸው ስቅቅ ብለሽ ታልፊያቸዋለሽ።ከማለፍሽ ወደ ፋርማሲው ድጋሚ ሲገቡ ታይና ጠጋ ብለሽ ለማየት ትሞክሪያለሽ።

"የኔ ዓለም...እንደው አሁን የወጣችቱ ልጅ የገዛችው ክኒና የምንድነው?" ይሉታል መድሀኒት ሻጩን።
"ምነው ማዘር ችግር አለ?"
"ኧረ የለም ዓለሜነህ!...አምና ቁርጥማት ያመኝ የነበር ግዜ ይኸን መሳይ ክኒና ነበር እምውጥ እንደው ሲያገረሽብኝ ግዜ ድጋምኛ ልዋጠው ይሆን ብየ ነው ...ሌላም አይደል"

"ኧረ...ተመሳስሎብዎት ነው 'ሚሆን ማዘር ይሄኮ post pill ነው"
"ምን pill?"
"postpill....postpill ማለት..."ብሎ ማብራሪያ ሲጀምርላቸው አንቺ እቃሽን እንዲያሻክፉሽ ወደ ጓደኞችሽ እየደወልሽ ነው።

ማዕዶት ያየህ(ዘማርቆስ)
(@gize_yayeh)
25/09/2015 ዓ.ም.

@wegoch
@wegoch
@paappii
"የሙሉቀን መለሰ ትዝታዎች"
(በዕውቀቱ ሥዩም)

ከብላቴናነቴ ጀምሮ ሙሉቀን መለሰን ስወደው ኑርያለሁ። አስቴር አወቀ፣ ኤፍሬም፣ ሙሉቀን እና አበበ ተካ በዜማ ባያጣፍጡት ኖሮ የጉብዝና ወራቴ ምንኛ እጅ እጅ ይል ነበር...!
"ስለምትመኘው ነገር ተጠንቀቅ አንድ ቀን ልታገኘው ትችላለህና" ይላል ጠቢብ...!
ታድያ አንድ ቀን ራሴን ሙሉቀን መለሰ ቤት አገኘሁት። በርግጥ ያገኘሁት በልጅነቴ የማልመውን ሙሉቀንን አልነበረም፤ ሙሉቀን የወጣትነት ሥራውን ሲኮንን ነበር የደረስኩበት። "የዘፈን ምንጭ ሰይጣን ነው" ይላል፡፡(ነገሩ እንዲህ ከሆነ፤ የኢትዮጵያ ባህል ሚኒስትር ሰይጣን ላገራችን ኪነጥበብ ያደረገውን አስተዋጽኦ አስታውሶ ቢሸልመው ደስ ይለኛል...ሰይጣን አይሸለምም ያለው ማነው?)🙄
ሙሌ የተራኪነት ተሰጥኦ አለው፡፡ ስለአማርኛ ዘፈን ታሪክ ሲነሣ ጠንከር ያለ ትንታኔ ያቀርባል፣ ለጊዜውም ቢሆን ዘፈን የሰይጣን መሆኑን ይረሳና በግሉ ስላበረከተው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይተርካል።
በርግጥ የታዋቂ ዘፋኞችን ችሎታ ያጣጥላል። አንዱን ስሙን የማልጠቀሰውን ዘፋኝ ሣነሳበት...
“እሱ እንዲያውም መዝፈን አይደለም ዘፈን እንዲያዳምጥ እንኳ ሊፈቀድለት አይገባም” አለኝ🤭 በተለይ ጥላሁን ገሠሠን ተችቶ አያባራም...
”እሱ እኮ የጉልበት ዘፋኝ ነው” ይለዋል።
ነገሩን ማስ ማስ ሳደርገው ከጥላሁን ገሠሠ ጋር ያለው
ግኑኝነት የፉክክር ብጤ ይመስላል። አልፈርድበት
“ሁለት አንበሶች ባንድ ዋሻ ውስጥ አይኖሩም ” ይላል ጎርኪ። በቅርቡ ሙሌ፤ “ናፍቆት ኢትዮጵያ” ከተባለ መጽሄት ጋር ዘለግ ያለ ቃለ-መጠይቅ አድርጓል።
ከምልልሱ ውስጥ ይቺን በፈገግታ ቀንጭቤ ልሰናበት...
ናፍቆት:- ለመሆኑ እስከ ስንተኛ ክፍል ተምረሃል?
ሙሉቀን፡- ረሳሁት እስከ ሦስተኛ ክፍል የተማርኩ ይመስለኛል።
ናፍቆት፡- ድምፃዊው ጥላሁን ገሠሠ በሁለት ክፍል ይበልጥሃላ!
ሙሉቀን፡- እሱ እዚያ ደርሷል እንዴ?
ናፍቆት:– አዎ፣ የምናውቀው እስከ አምስተኛ ክፍል ድረስ መማሩን ነው ….
ሙሉቀን፡- እንዲያውም አሁን ትዝ አለኝ አምስተኛ ክፍል ድረስ ነው የተማርኩት...🤭🤣🤣

(ቀንጭቤው ነው እንጂ ረጅም ነበር)

@wegoch
@wegoch
@paappii
ድሮ ድሮ ብሶት በወለደው በዘመነ ኢህአዴግ

¤¤¤¤

ድሮ ድሮ ከአድማስ ዩኒቨርሲቲ በዲፕሎማ ለተመረቀ ልጃቸው በሬ አርደው የሚደግሱ ቤተሰቦች ነበሩ

¤

ድሮ ድሮ ኑሮ ጥሩ ስለነበረ ህዝቡ ደረጄና ሀብቴ "ሙያሽ ይዘርዘርልሽ" እያሉ ሲዘፍኑ ሆዱን ይዞ ይስቅ ነበር

¤

ድሮ ድሮ ወደደብረ ማርቆስ የሚጓዝ አውቶቡስ ውስጥ የታደለ ገመቹን የነቀምት አውቶቡስ ውስጥ የሰማኸኝ በለውን ዘፈን መስማት ኖርማል ነበር

¤

ድሮ ድሮ ታመን ጤና ጣቢያ ስንሄድ ከመድኃኒቱ በፊት ወተትና ስጋ መመገብ እንዳትረሱ የሚል ማስጠንቀቂያ ይሰጠን ነበር

¤

ድሮ ድሮ አንድ ሱፍ ለመስፋት 30 ሜትር ጨርቅ እንጠቀም ነበር

¤

ድሮ ድሮ አዜብ መስፍን የተባሉ የቤት እመቤት ባለቤታቸው በሚከፈላቸው 7500 ብር ወርሃዊ ደመወዝ ድልቅቅ ብለው እንደሚኖሩ ከታይላንድ ጉብኛታቸው በዃላ ነግረውናል

¤

ድሮ ድሮ የመንግስት ሰራተኛው በወርሃዊ ቁጠባ ኮንዶሚኒየም ይደርሰው ነበር

¤

ድሮ ድሮ አርከበ እቁባይ የተባለ የብዙ የአዲስ አበባ ወጣቶችን ህይወት የቀየረ ከንቲባ ነበረ

¤

ድሮ ድሮ አበበ ተካ የሚባል ዘፋኝ የሆነች ቀሽት ዲያስፖራ አፍቀሮ "አለቅሳለሁ" የሚል ዘፈን አውጥቶ ሲያለቃቅስ ህዝቡ በጣም ስለተሰማው ገንዘብ ተሰብስቦ በአላሙዲን ድጋፍ አሜሪካ ሄዶ ልጅቷን እንዲያገኛት ተደርጓል

¤

ድሮ ድሮ ኃይሌ ገብረስላሴ 5 ኪሜ ውድድር ሲያሸንፍ ህዝቡ ከኮተቤ ፒያሳ ድረስ 10 ኪሜ እየሮጠ ደስታውን ይገልፅ ነበር

¤

ድሮ ድሮ ሰው ቤት ገብቶ መዘፍዘፊያ የሰረቀ ሌባ ፖሊስና ህብረተሰብ ቴሌቪዥን ላይ ቀርቦ ይወገዝ ነበር

¤

ድሮ ድሮ ከሰል ለማያያዝ አንድ ሌትር ጋዝ የሚጠቀሙ እናቶች ነበሩ

¤

ድሮ ድሮ ሀገሪቱ ውስጥ ከነበረው ህዝብ መካከል ስጋ በደንብ አያገኝም ተብሎ በፍለጋ የተገኘ አንድ አዛውንት አለቤ ሾው ላይ ቀርቦ ለ3 ዓመት ስጋ በነፃ እንዲወስድ ስሙን የረሳሁት ስጋ ቤት ቃል ገብቶላቸው ነበረ

¤

ድሮ ድሮ ተኽላይ ደምቢዶሎ ውስጥ አራርሳ ባህርዳር ላይ ሆቴል ነበራቸው

¤

ድሮ ድሮ ባለስልጣናትና አርቲስቶች የእግር ኳስ ግጥሚያ በህዝብ ፊት ያካሂዱ ነበር

¤

ድሮ ድሮ "ምግብማ ሞልቷል አምላክ መች ነሳኝ" የሚል ዘፈን ነበር

¤

ድሮ ድሮ ምግብ በተትረፈረፈበት ዘመን ከመመገባችን በፊት እጃችንን መታጠብ አንርሳ የሚል ተደጋጋሚ ማስታወቂያ ነበረ

¤

ድሮ ድሮ የ4ኛ ክፍል መምህር ካዛንቺስ ተከራይቶ ይኖር ነበር

¤

ድሮ ድሮ ማር ሲበዛ ይመራል የሚሉ ማር ያላቸው ወላጆች ነበሩን

¤

ድሮ ድሮ የቀበሌያችን ሊቀመንበር ልጆች አብረውን ደጃዝማች ወንድይራድ ት/ቤት ይማሩ ነበር

¤

ድሮ ድሮ መክሰስ የሚባል 10 ሰዓት ላይ የሚበላ ምግብ ነበረ

@wegoch
@wegoch
@paappii

By yihune ephrem
Audio
ፀሀፊና አንባቢ : ማዕዶት ያየህ (ዘማርቆስ)
@gize_yayeh

@wegoch
@wegoch
@wegoch
አነቃቂው መድረኩ ላይ እየተንጎራደደ "በህይወቴ ምርጡ ጊዜ ሚስቴ ያልሆነች ሴት እቅፍ ውስጥ ያሳለፍኩት ጊዜ ነው!" ሲል ተነገረ።

ለመነቃቃት አዳራሹ ውስጥ የተሰበሰበው ሰው በድንጋጤ ክውታ ተዋጠ።

አነቃቂው ንግግሩን በመቀጠል "እናም ያቺ ምርጥ ሴት፣ ዘጠኝ ወር በሆዷ፣ ከእዛም በጀርባዋ፣ ከእዛም በእቅፏ ያሞላቀቀችኝ ምርጥ ሴት፣ ያቺ ስጦታ ሳልሰጣት ያቀፈችኝ ምርጥ ሴት እናቴ ናት?!" ሲል ተናገረ።

አዳራሹ በሳቅ እና በጭብጨባ ተሞላ።

**
ከሳምንት በኋላ በእዚህ የአነቃቂ ንግግር ላይ የተገኘ ሥራ አስኪያጅ ድግስ ብጤ አዘጋጅቶ ዘመድ አዝማድ፣ ጓደኛ ቤቱ ጠራ። ዝግጅቱ ላይ ወዲህ ወዲያ እያለ ሰው ሲያስተናግድ፣ ሲጎርስ ከመጠጡ ሲጎነጭ ሞቅ ከማለት አልፎ ሰከረ።

ይሄኔ ነው እንግዳው ምግብ በልቶ፣ ጠጥቶ ሳይዝናና መሄድ የለበትም ሲል በአነቃቂ ንግግር ስልጠና ላይ ተገኝቶ የሰማውን ቀልድ ለታዳሚው ለመጋበዝ በመወሰን ድምጹን ጠራርጎ ንግግር የጀመረው።

"በህይወቴ ምርጡ ጊዜ፣ ሚስቴ ያልሆነች ሴት እቅፍ ውስጥ ያሳለፍኩት ጊዜ ነው!" ሲል ተነገረ።

ይሄኔ የሚስቱ ፊት፣ እንደመቅላት፣ አመድ እንደ መንዛት፣ አሸቦ እንደመምሰል ከእዛም ወደ ጥቀርሻነት ተለወጠ። ንግግሩን የሰማው የድግሱ ታዳሚ በድንጋጤ የጨው አምድ መሰለ።

ይሄኔ ባልየው በአነቃቂ ንግግሩ ወቅት የተነገረው የቀልዱ ሁለተኛ ክፍል ምን እንደሆነ ስለዘነጋ ለማስታወስ ለሀያ ሰከንዶች ያህል በዝምታ ከቆየ በኋላ ትዝ ሊለው ስላልቻለ ጎሮሮውን ጠራርጎ...

"...እናም ያቺ ሴት ማን እንደሆነች አላስታውስም!" ሲል ንግግሩን ደመደመ።
**
ማስታወሻ፣

ሰውየው ንግግሩን እንደጨረሰ ከሚስቱ በተሰነዘረበት የውስኪ ጠርሙስ ፍንከታ ምክንያት ኮማ ውስጥ ስለገባ አሁን ላይ ሆስፒታል ተኝቶ እስኪነቃ እየታከመ ይገኛል።

@wegoch
@wegoch
@paappii

By #Tilahun ango Girma
ኩርፊያህን ለምን እንደምናፍቀው ይገባህ ይሁን…… የምልህ አለአይደል ስትነጫነጭ ጊዜ …… ወይ ስትቆጣ ንዴትህን ግልፅ ስታደርግልኝ…… ትኩረቴን ፈልገህ ልክ እንደህፃን ሲያደርግህ በሆነው ባልሆነው ስታኮርፍ ኩርፊያህ ታስፈልጊኛለሽ የሚል መልዕክት ያለው ይመስለኛል እንክብካቤ ፈልገህ ትኩረቴን ሽተህ ይመስለኛል …… ሰዎች ፊት የነበረህን ኩራት አሽቀንጥረህ እኔ ዘንድ ብሶትህን ስትነፋረቅ…… ከጉያዬ ሽሽግ ስትል ፀጉርህን በጣቶቼ ዳበሳ ስበታትናቸው ጭንቀትህም አብሮ ቢበተን ……ትኩስ እንባህን በፈገግታዬ ባብስልህ…… እኚህን ሁሉ ሁነቶች እወዳቸዋለሁና ኩራትህን አሽቀንጥረህ መሸሸግን ፈልገህ ናልኝ…… በዚህች በጠበበችህ አለም ሳይታክትህ ትሸጎጥበት ዘንዳ እቅፌ ላንተ ሰፊ ነውና መሰልቸትን እኔ ጋር አታስበው…… የነፍስህ ጭንቀት ሲራገፍ የስስት አይኖችህ በፈገግታ ሲያበሩ እኔነቴን አንተው ውስጥ አየዋለሁ እናም አለም ሁሉ ብትጠብህ እቅፌ ላንተ ሰፊ ነው

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Fereha nuraddis
✍️ ሀገር ሰላም ብዬ የተቀመጥኩበት ታክሲ ውስጥ ጎኔ ያለችው ልጅ በሹክሹክታ ድምጽ ምን አለችኝ አባቱ ትወርድልኛለህ? ደሞ የአይኖቿ መስለምለምስ ትውልዱ አይን አውጥቷል ስትሉኝ አለማመኔ my dirty mind😏

✍️ባለፈው አዳነች አቤቤ ህገ መንግስታዊ ስርአቱን በሀይል ለመናድ ከአንድ ክልል ብቻ የሚደረግ ከፍተኛ ፍልሰት አለ ስትል ዲቻ ምንም እንዳልመሰለው ሳስብ ብቻዬን ሳቄ ያመልጠኛል ጦሶ🤦‍♂️

✍️ትናንት ምሳ የበላሁበት ስጋ ቤት ቆራጩ" የበሬን ምስጋና ወሰደው ፈረሱ" እያለ እየዘፈነ ነፍ ስጋ የሰጠኝ በደህና ነው ትላላችሁ😳 አሁን በጠዋት ችክክም ችክክም ችከክም በል በል እያለኝ እኮ ነው 🐎

✍️አርባ አመት ሙሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ለመሆን የታገለው ቀጨላ መርዳሳ የኦነግን የምስረታ በአል አብሮ ያከብራል ማለት ነው🤷‍♂️

✍️ በየ ለቅሶ ቤቱ ግን ከቀብር በኋላ የሚዘጋጅ የምሳ ግብአት ቀይ ምስር እና አልጫ አተር እንዲሆን ያወጁት ቀደምት እናቶች በማ ዘመነ መንግስት እንደነበሩ ዶክተር ሮዳስ ሲያብራራ ሰምቼው አላውቅም ወይስ አምልጦኝ ነው🤪

✍️ከአባታቸው ባገኙት አስር ሚሊየን ብር እና አምስት ተሽርካሪ ደሞ የሆነ የሆነ ሱቅ ተነስተው የሀብት ማማ ላይ የተቀመጡ ቃለ መጠይቅ ሲደረግላቸው እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ብለው ንግግር የሚጀምሩ  ቱጃሮች በወንጀል እንዲከሰሱልን ስል በትህትና አመለክታለሁ📯

✍️በቀደም እለት ዶፍ ዝናብ እየዘነበ ጣራችንን እንደ አታሞ ሲደልቅ ከዛ የዝናብ ኳኳታ ጋር በሚታገል ጮክ ባለ ድምጽ እናቴ
"እስቲ አንድ ልጅ ወልደህ አምጣልኝ" ብላ ያሳቀቺኝ ሳቅ አመቱን ሙሉ ከሳቅኩት ይበልጣል😂😂😂 እኔ እኮ እድሜዬን መቁጠር የረሳች መስሎኛል ለካ እስከዛሬ እየቆጠረች ነው Shame on you Mom እኔ ላንቺ ጊዜ ምን ብዬሽ አውቃለሁ🙄

✍️ያቺ በጣም ቆንጆ ሂጃቢ ያስሚን ወንድ አትጨብጥም 2 አመት እኮ አንድ መስሪያ ቤት አብረን ሰርተናል ሁሌም ስንገናኝ በርቀት እንደታቦት ብቻ ጎንበስ ቀና ብዬ ተሳልሜ ነበር ሰላም የምላት ምናል አንድ ቀን ከሀር የሚለዝብ የሚመስለኝ ለስላሷ እጇን ብታስነካኝ መዳፌ ላይ ያረፈ ጠረኗን ከሷ ተደብቄ አንድ ቀን ባሸተው ምነበረ😍😍😍

✍️በቀደም መንገድ ላይ እየሄድኩ በሀሳብ ጭልጥ ከማለቴ የተነሳ የማስበው ጠፍቶኝ ወደራሴ ስመለስ 801, 802, 803, 804 እያልኩ አገኘሁት ራሴን ምን ለምን እየቆጠርኩ እንደነበረ ግን ስካሁን ትዝ አላለኝም። እየጨለልኩ ነው እንዴ🧐

ከላይ ያልኩት ሁሉ አይረባም አውቃለሁ
አንዳንዴ እንዲ ነኝ
ወፈፍ ያደርገኛል እዘባርቃለሁ

By Binyam behaylu

@wegoch
@wegoch
@paappii
ውድ አልማዞች!
•••••••
የግመል ነጋዴው በገበያው ለሽያጭ ከቀረቡት ግመሎች መካከል በአንዱ እጅግ ስለተሳበ ከሻጩ ጋር ድርድር ጀመረ። በገዢና በሻጭ መካከል ብዙ ደቂቃዎችን የፈጀ የቀንስልኝ፣ አልቀንስም ክርክር ከተደረገ በኋላ ገዢው በዋጋ ተስማምቶ ግመሉን ገዝቶ ወደ ቤቱ ሄደ።

የግመል ነጋዴው ቤቱ እንደደረሰ አገልጋዩን ጠርቶ የግመሉን ኮርቻ እንዲያወርድ ይነግረዋል። አገልጋዩ የግመሉን ኮርቻ ሲፈታ ከኮርቻው ስር አነስተኛ መጠን ያላት የተቋጠረች ከረጢት ያገኛል። ከረጢቷን ሲፈታ በውድ የአልማዝ ማእድን ተሞልታለች።

አገልጋዩም "አለቃ የገዟት ግመል በነጻ ጭና ያመጣችውን በረከት ይመልከቱ!" ሲል በደስታ ተሞልቶ ጮኸ። ነጋዴውም በአገልጋዩ መዳፍ ላይ በጸሐይ ብርሀን የሚንቦጎቦጉ የአልማዝ እንክብሎች ሲመለከት እጅግ ተደነቀ።

ይሁንና "ግመሏን እንጂ አልማዞቹን አልገዛኋቸውም። አሁኑኑ ለባለቤቱ መመለስ አለብኝ" አለ - ነጋዴው።

አገልጋዩም "ምን የማይረባ አለቃ ነው ያለኝ?!" ሲል በሆዱ ካወራ በኋላ "ማንም ሰው የአልማዞቹን ትክክለኛ ባለቤት ሊያውቅ አይችልም! ሲል ተናገረ።

ይሁንና ነጋዴው ምክሩን ችላ ብሎ ጊዜ ሳይወስድ ባለቤቱን ፍለጋ ወደ ገበያው ተመለሰ። ብዙም ሳይለፋ የተቀሩ ግመሎችን ለመሸጥ ገዢ ሲጠብቅ የነበረውን የግመል ሻጭ አግኝቶ ትንሿን ከረጢት መለሰለት።

የግመል ሻጩም እጅግ ተደስቶ " እጅግ የከበሩ ማእድናቴን በኮርቻው ስር መደበቄን ዘንግቼ ነበር። አሁን ሽልማት እንዲሆንህ በከረጢቱ ውስጥ ካሉት አልማዞች ውስጥ ለዐይንህ ደስ ያሰኘህን ውሰድ!' አለ።

"ለከፈልኩት ገንዘብ ጥሩ ግመል ሽጠህልኛል። ተጨማሪ ሽልማትም ስጦታም አልቀበልም።" አለ - ነጋዴው። ነጋዴው ስጦታውን አልቀበልም ቢልም ግመል ሻጩ እንዲቀበለው ይወተውተው ጀመር።

በመጨረሻም ነጋዴው በፈገግታ ተሞልቶ "ከረጢቱን ልመልስልህ ስወስን ሁለት እጅግ የከበሩ አልማዞችን እራሴ ዘንድ አስቀርቻለሁ! ከእነርሱ የሚልቅ ሽልማት የለም!" አለው።

የግመል ሻጩ የነጋዴው የእምነት ቃል ሲሰማ እጅግ ተበሳጭቶ በከረጢቱ ውስጥ ያሉትን ውድ አልማዞች የጨርቅ እራፊ ላይ ደፍቶ ይቆጥራቸው ጀመረ። ይሁንና ቆጠራውን እንደጨረሰ በእፎይታ ተሞልቶ "በከረጢቱ ውስጥ ከነበሩት አልማዞቼ መካከል አንድም አልጎደለም። የትኞቹን ውድ አልማዞች ነው ለራሴ አስቀርቻለሁ ያልከኝ?"

ነጋዴውም በኩራት ተሞልቶ "እኔ ዘንድ ያስቀረኋቸው ውድ አልማዞች ታማኝነቴና ለእራሴ ያለኝ ክብር ናቸው!" ሲል መለሰለት።

ሻጩ የሰማውን ነገር ባለማመን ዐይኖቹን አፍጥጦ ነጋዴውን ከመመልከት ውጪ መልስ ሊሰጠው አልቻለም።

**
ሁላችንም ወደ እራሳችን መመልከትና እነዚያ ውድ አልማዞች እንዳሉን እንፈትሽ። ሁለቱ ውድ አልማዞች ያለው ማንኛውም ሰው የዓለማችን ባለጸጋው ሰው ነው።

@wegoch
@wegoch
@paappii
በአንድ የቴሌቪዥን ድራማ ላይ ሲሰሩ ነበር የተዋወቁት ፡ እና ተቀራረቡና ፡ አንድ ቀን እራት ልጋብዝሽ አላት ።

ጥሩ ቦታ ወሰዳት ፡ አሪፍ እራት በሉ ፡ እና ወደቤት ሊሄዱ ተነሱ ፡ ዴንዝል ዋሽንግተን የተጠቀሙበትን ሂሳብ ከፈለና ፡ ኪሱ ውስጥ የቀረውን ገንዘብ ሲያይ ደነገጠ ። በወቅቱ ሁለቱም መኪና የላቸውም ። ኪሱ ውስጥ የቀረው ገንዘብ ለታክሲ ላይበቃ ይችላል ። እና በባቡር እንሂድ ልበላት ? ወይስ ፡ ለምን ወክ አናደርግም ብዬ እስከቤት ልሸኛት ? የሚለውን እያሰበ እያለ ፡ ከሆቴሉ ወጥተው በሩ ላይ የተደረደሩት የሜትር ታክሲዎች ጋር ደረሱ ።

ፓውሌታ የአንዱን ታክሲ በር ከፍታ ገባች ። ዴንዝል ተከተላትና ፡ ወደቤቷ አቅጣጫ መጓዝ ጀመሩ ፡ እና እያወራት ፡ በመሀል ስንት እንደቆጠረ የታክሲውን ሜትር ያያል ።
ኬሎሜትሩ በጨመረ ቁጥር ፡ ብሩም እያደገ ሄደ ። ዴንዝል ዋሽንግተን ፡ ሀሳብ ገባው ፡ በመጀመሪያ ቀን ዴቲንግ ፡ የታክሲ መክፈል ያልቻለ ሰው ሆኗል ።
በመጨረሻም ቤቷ ደረሰች ። ዴንዝል ነገራት ።
ብር ጨርሻለሁ
ታዲያ ምን ችግር አለ ብላ የመጣችበትን እና እሱን ቤቱ ሊያደርሰው የሚችለውን ጨምራ ከፍላ ወረደች ።
......
ግንኙነታቸው እያደገ ሄዶ ፡ አንድ ቀን ቀለበት ገዝቶ ተንበረከከ
ፓውሌታ ፡ አብረን እንድንኖር እፈልጋለሁ ። ታገቢኛለሽ ? ሲል ጠየቃት
አላገባህም አለችው
ቀለበቱን ኪሱ ከቶ ተለያዩ ።
.....
ትንሽ ቆይቶ አንድ ቀን ይህንኑ ጥያቄ ደገመው ።
እኔና አንቺ ባልና ሚስት መሆን ያለብን ሰወች ነን ፡ አብረን እንድንኖር እፈልጋለሁ ፡ አለና ያንኑ ቀለበት አውጥቶ ለጋብቻ ጠየቃት ።
አዝናለሁ ዴንዝል አላገባህም ብላው ሄደች ።
እሱም ሄደ ።
....

ከወራት በኋላ አንድ ቀን ያችኑ የፈረደባት ቀለበት አውጥቶ ፡ ለሶስተኛ ጊዜ አግቢኝ ሲል ጠየቃት ።
ፓውሌታ ይህን ተስፋ የማይቆርጥ ሰው ፡ አትኩራ አየችው እና የቀለበት ጣቷን ዘረጋችለት ።
እሽ አገባሀለሁ ።
..........
ቆየት ብለው ሰርግ ደገሱ ፡ ትንሽ ሰርግ ነበር ። እና የሚበላ ነገር በጠሯቸው ሰወች ልክ ተዘጋጀ ።

እንግዶች እየተመገቡ እያለም ፡ ሙሽሮቹ ዴንዝል ዋሽንግተንና ፡ ፓውሌታ ፒርሰን ፡ በሰርጋቸው ላይ የተገኙትን እንግዶች ፡ እየዞሩ ሰላም ሲሉና አብረው ፎቶ ሲነሱ ቆይተው. . ምግብ ሊያነሱ ወደ ጠረጴዛው ሲሄዱ ፡ ባዶ ነው ።
ምግቡ አልቋል ።
......
እንግዶቻቸውን ሸኝተው በሰርጋቸው ቀን ሬስቶራንት ሄደው ተመገቡ ።

ይህ ከሆነ አሁን አርባ አመታት አለፈ ። በዚህ መልኩ የተገናኙት ጥንዶች አራት ልጆች ወልደው ፡ ሶስት መቶ ሚሊየን ዶላር በባንክ አጭቀው ፡ ሆሊውድን የሚያምሰው የመፋታት አባዜ ሳያገኛቸው ፡ እስካሁን አሉ ።
....
በዩቲዩብ ቻናላችን የሚቀርቡ ስቶሪዎችን መስማት ለፈለገ ፡ ከስር ያለው ሊንክ መገኛችን ነው ።

@wegoch
@wegoch
@paappii

By wasyihun
2024/09/21 22:47:20
Back to Top
HTML Embed Code: