Telegram Web Link
( የከሰመ - ፍቅር )
.
.
.
ካሊድ አቅሉ

ሳቅዋ ለዝብዋል ለወጉ ጥርሶችዋን ታሳያለች እንጂ እንዳረጀ አንበሳ ሞገሱ እንጂ መጉላት አይታይበትም ። " አንቺ ግን እንዴት ነሽ ሰው አይናፍቅሽማ ?" አልኳት ሀይል ባነሰው መነጠቁን ባወቀ ደካማ ድምፀት ። " አለው አረ ትንሽ እኮ busy ሆኜ . . . ." አልጨረሰችውም ተውጠው የቀሩ በጉጉት ምጠብቃቸው ቃላት ነበሩ ናፍቃኛለች ማያት በ ስስት ነው ግን ነፍስ አልባ እይታ ። የሚወዱት አካል አለ ብለው ላይሰረዝ የተፃፈ ቀስ በቀስ አሸዋ ላይ እንደተፃፈ ቃል ንፋስ እብስ ሲያረገው ታየኝ ማዘን ምንድነው ተስፋ መቁረጥስ . . . . በልብ መሰበር ከኔ ውጪ መልስ ይኖረዋል ብዬ ለማሰብ ይከብደኛል ። ዘመን ያከለብኝ ግን ገለልተኛ ሰው ሲያየው ከ ሶስት ደቂቃ ማይዘል ዝምታ " ቤት እንዴት ናቸው ?" በሚል ቃል ተሰበረ የሩቅ ዘመድ ማወራ እየመሰለኝ " ቤት ደህና ናቸው " ብዬ ነገር ማሳጠር ፈለኩ ፍቅሬን ለመራቅ በጓደኝነት ስም ዳር ዳር ስትሄድ አየዋት ። ወደ ውሃነት የተቀየረ ሻይ አጠገቤ ሞልቶ ይታያል ሁለት ቀን ሳላገኛት ካለፈ የሚቀየር መልኳ እንገናኝ ስላት መቀየሩ ደንቆኛል ። የሚያፈቅሩትን ሰው እንዴት የቅርብ እሩቅ ማረግ ይቻል ይሆን ? ህመሜን የቀነሰች መስልዋት ከ አስረኛ ፎቅ ከምወረውረው እየጎተትኩ ባወርደው ይሻላል ብላ ስቃዬን አበዛችው ። አልታወቃትም " የተፈቃሪ ትልቁ ስህተት ከእሱ አድማስ ባሻገር ጨለማ ነው ብሎ መደምደሙ ነው " " እና እያነበብሽ ነው ?" ለወንድምነት በቀረበ ቅላፄ ሀሳቤን አሻገርኩ . . . " እእ አዎ አንተን እራሱ ለማግኘት ከመምጣቴ በፊት ላይብረሪ ነበርኩ እነ ሳምሪ እራሱ እዛው እየጠበቁኝ ነው " መች ልሂድ የሚል ቃል አለመፈለግ ሚመራው ሚንቀሳቀስ ግኡዝ አካል ከፊቴ ታየኝ ።

" ግን እኮ ወዳታለው ከዘመን አግዝፌ
እሷን እንዳይጠባት ምሽት እየጠበኩ
ጨረቃን አርግፌ " ( አሁንም )

(ምልሰት) ሽምጥ ወሰደኝ ከአካሌ ቀድሞ አፌ ፍቅራችንን እያስታወሰ ጣረሞት ላይ ያለው ፍቅራችን ታየኝ ። ለመግደል ስትፍጨረጨር ለማትረፍ ሚደክመው ገላዬ ድንጋይ ላይ ውሃ እንደሚያፈስ ታወቀኝ ። " በቃ ሂጂያ እንደዛ ከሆነ አልያዝሽ ይቅርታ ከንባብ አቆርጬ ስለጠራሁሽ " የኑዛዝዬ ማሳረጊያ ነበር . . . . . . . . " ችግር የለውም " ፍቅራችን ከመሞቱ በፊት ገዳይዋ ያወጣችው የመጨረሻ ቃል . . . . .






ከፍቅራችን ሙት አመት ብሀላ ድንገት በሰፈራቸው ሳልፍ ግቢው ተከፍቶ ይጨፈራል እርምጃዬን ገታ አድርጌ ለሰከንዳች ለተከፈተው ሙዚቃ ጆሮዬን ለገስኩ . . . . " አትሸኘዋትም ወይ አትሸኘዋትም ወይ መሄድዋ አይደለም ወይ የዛሬ አመት የዛሬ አመት የማሙሽ እናት. . . . . " ሙዚቃው ቀጠለ እኔም ጉዞዬን ቀጠልኩ . . . . . . .

* * *
@wegoch
@wegoch
@paappii
የፈሪሳዊው መንፈስ
°°°°°°°°
አንዲት ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ተኮርምቼ፣ የቀኝና ግራ እጄን መዳፍ አላትሜ፣ በአውራ ጣቶቼ ድጋፍ አገጬን አሳርፌ፣ ሽቅብ ወደ ላይ አንጋጥጬ ተቀምጫለሁ፡፡ ዓይኖቼ በጨለማው መሀል የሰማዩን ሰማያት ሰነጣጥቀው ከእግዜር ዙፋን ፊት ዱለውኛል፡፡ አዕምሮዬ ህመሜንና ጉዳቴን በውስጥ ምላሱ ለአምላኬ ያንበለብላል፡፡ ብዙ የለምን ጥያቄዎች ያዘንባል፡፡

"ለምን ይህ በኔ ሆነ? ምን በድዬህ ነው? ለየትኛው ጥፋቴ ነው ይህ ቅጣት? ለምን ነው ምወደውን ማጣው? ምፈልገውን ማላገኘው? ለምን ፍቅሬን ባጭር ቀጨህ? ለምን የዘለዓለም ፍቅሬን ነጠቅከኝ? ፍቅርን በመሀላችን ማስፈንና ማርጋት እንዴት አቃተህ? ለምን ለእኔ ለልጅህ ማሰብ ተሳነህ? ከሀሊ እጆችህ እኔ የምሻውን ለማድረግ ለምን ታቀቡ? ለምን…?"

ጓደኛዬ እሌኒ ‹‹ምነው ብቻህን?›› በሚል ጥያቄ፣ ከማማረር ጥያቄዬ ገትታ፤ ከሰማይ መንበር ወዳለሁበት የድንጋይ ወንበር በቅጽበት መለሰችኝ፡፡
‹‹ብቻዬን አይደለሁም አምላክ ጋር እያወራሁ ነበር፡፡››
‹‹እያወራህ እንኳ አይደለም፤ ያው እንደለመደብህ እያማረርከው እንጂ! … እውነቱን ልንገርህ! ብቻህን ስትሆን እፈራለሁ፡፡ ፈጣሪን እንደጓደኛ እየገላመጥክ ምትወቅሰው ነው ሚመስለኝ…››
‹‹እንደ አባት እወደዋለሁ! እንደ አባት እለምነዋለሁ! እንደ አባት እጠይቀዋለሁ! እርግጥ ነው ጥያቄዬ ምሬትን ስለተሸከመ ወደ ወቀሳነቱ ያጋድላል… ››
‹‹እኮ! እሱ ነው ሚያስፈራኝ፡፡ ወቀሳና ምሬት ታበዛለህ፡፡ ካለህ ነገር ይልቅ የሌለህን፣ ካገኘኸው ይልቅ ያጣኸውን ነው ምታስበው፡፡ ያለህን ነገሮች አይተህ ለማመስገን ሞክረህ ምታውቅ አይመስለኝም፡፡ ሁሌም…!›› ልትናገር ያሰበችውን ከምላሷ እንዳይፈናጠር አቀበችው፡፡ ‹‹ነገ ምወስድህ ቦታዎች አሉ፤ ከዛ ለምስጋና አንደበትህን ታቀናለህ፡፡ አሁን ግባ ወደ ቤት! መሽቷል!!››

በጧት ቀስቅሳ ነጠላ አስለብሳ ቤተ ክርስቲያን ወሰደችኝ፡፡ ፀበል መጠመቂያ ስፍራው ጋር አጋንንት የሚጫወትባቸውና የሚጨፍርባቸው ምስኪን ፍጥረቶች በፀበል እና በፀሎት ኃይል ይለፈልፋሉ፡፡ ሆስፒታል ሂደን ጤና የናፈቃቸው ህሙማንን ጎበኘን፡፡ ወደ ሞት መንገድ እያዘገሙ ከኑረት ጋር በቀጭን ቱቦ የተሳሰሩ ሰዎችን አየን፡፡ በገዛ ወገናቸው ተፈናቅለው፤ ቤትና ሀብታቸውን ትተው በኬንዳ መጠለያ ስር የታጎሩ በርካታ ሰዎችን ቃኘን፡፡ ዘመድና ዞር ብሎ የሚያቸው ያጡ ጎዳና ላይ የተሰጡትንም እየተዘዋወርን ኮመኮምን፡፡

ልክ እንደጨረስን፤ ‹‹ይህን ሁሉ ያሳየሽኝ "ተመስገን" እንድል ነው›› አልኳት፡፡
‹‹አዎ›› ራሷን ላይና ታች ወዘወዘች፡፡
‹‹ይገርማል!››
‹‹ምኑ?›› በግርምት አየችኝ፡፡
‹‹አንድም የፈሪሳዊያን መንፈስ ተጣብቶን መኖሩ!! አንድም በራስ ወዳድነት አጉል መተብተባችን!!››
‹‹እንዴት?››
‹‹እኒህን ሁሉ ስታሳይኝ የዋልሽው የኔን ህመም በእነሱ ስቃይ ፍቄ… እንደፈሪሳዊው፤ "እንደነሱ ስላላደረግከኝ ተመስገን!" እንድል ነው፡፡ ራስ ወዳድ መሆን አልፈልግም፡፡ እንደውም እንኳን ተመስገን ልል… ስለነሱም አንስቼ የባሰ ልወቅሰውና ልጠይቀው ነው ምፈልገው፡፡›› ጥያት ሄድኩ፡፡ ወደ መቀመጫዬ!! ሽቅብ አንጋጥጬ፣ ሰማያትን ሰንጥቄ፣ ብዙ የለምን ጥያቄዎችን አዝዬ፣ ፈጣሪ ዘንድ ልቀርብ!!

#ኤልዳን

@wegoch
@wegoch
@wegoch
ፍቅርና ጦርነት

ክፍል 4

የማይነጋ ቀን የማያልፍ መከራየለም እንደሚሉት አበው ጨለማ ጊዜውን ለብርሃን ለቀቀ ፀሀይ የክረምቱን ደመና ሰነጣጥቃ ጨረሯን ወደምድር በትናለች ተስፋ ያለው ቀን ይመስላል ፤ ንጋት ላይ የመተኛት ልምድ የለኝም ዛሬም እንደልማዴ በጥዋት ተነስቻለሁ ።

ህመሙ እንዳገረሸበት ሰው ኩርምት ብዬ ቁጭ አልኩኝ ፀጋ ከእንቅልፏ ስትነሳ ያመመኝ እንዲመስላት ገና ካሁኑ እየተዘጋጀው ነው የዛሬውን ቀን አብራኝ እንድታሳልፍ ፈልጊለው ። ስዓት ስመለከት ገና 12:30 ነው ጊዜው አልሄድ አለኝ እንዴት ቀናችንን እንደምናሳልፍ ሳስብ ፀጋም ከእንቅልፏ ነቃች የእግዜር ሰላምታ ሰታኝ ሰውነቷን እያፍታታች መፀዳጃ የት እንደሆነ ጠይቃኝ ሄደች ።

ብዙም አልቆየችም ተመለሳ መታ የተኛችበትን እያነሳሳች እኔ በስስት እያየኋት ውስጤ ማዘን ጀመረ ማጣት ማጣት መሰለኝ ጭራሽ ማንተያይ ቻው ብላ ተለይታኝ በዛው ቀልጣ ምትቀር መሰለኝ ቢቸግረኝ ምነው አምላክ እህቴ ባደረጋት ብዬ ተመኘው አይ የጨነቀው ግራገባኝ እንዲህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ገብቼ አላቅም እንደዚህም ተሰምቶኝ አያውቅም ቤቴን ወደድኩት ፀሀይ እኔ ቤት ብቻ ያለች መሰለኝ አለም ሁሉ ጨለማ የኔ ቤት ብቻ ብርሀን ያለ መሰለኝ እድሜ ለፀጋማርያም የሷ ህይወት ጨልሞ የኔን አበራችው ፤

ድንገት ስራዋን ጨርሳ ወደኔ ስትዞር ግራገባኝ ተደናበርኩኝ ሳስበው የነበረው ያወቀችብኝ መሰለኝ ታማሚዋን እግሬን በእጄ ይዤው ማቃሰት ጀመርኩኝ ያካበድኩት መሰለኝ የዛኔ ስመታ ራሱ እንዲህ ያቃሰትኩ አይመስለኝም ። ፀጋ በፍጥነት መታ " ምነው አመመህ" ብላ ጠየቀችኝ ማቃሰቴን ሳላቆም ምወጋው መርፌ እንዳለኝና ሚወስደኝ ሰው እንደ ሌለ ነገርኳት ፤ አብረን መሄድ እንደምንችል ነግራኝ እሺ ተባብለን መኪና ያለውን አብሮ አደጌን ያሬድን ጠርቼው በሱ መኪና ሄድን ከቤት ጀምሮ ያሬድን እያየሁት ነበር በጣም ተገርሞል ሰረቅ ሰረቅ አርጎ ፀጋን ይመለከታታል እየተገረምኩኝ መኪናውን እንዲያቆም ነግሬው ፀጋን ተከተይኝ ብዬ ወረድኩኝ ፀጋ ምታየው ነገር ግራ አጋብቷታል ከሴቶች ልብስ ቤት ውጪ ህክምና አይታይም እጇን ይዤው ወደአንዱ ሱቅ ገባን ለሻጯ እንድታስወርጣት ነግሪያት እኔ ቁጭ አልኩኝ ። ልብሶች እየለካች ስታሳየኝ ለብቻዬ የውበት ውድድር ( ሞዴሊንግ ) ማይ መሰለኝ የለካችውን የተወሰኑትን ገዝተን ወደመኪናው ተመለስን ።ያሬድ ፀጋን ሲያያት አፉን ከፍቶ ቀረ ፤ መኪና መንዳት እስኪያቅተው ፈዞ ቀረ ፤

አሪፍ ቁርስ ወዳለበት ቤት ወስዶን እሱን ሸኘሁት ፤ ፀጋ ያሬድ ከሄደ በኋላ " ህክምናውስ መርፌ ምትወጋውስ " ብላ ጠየቀችኝ " ታከምኩ እኮ " ብያት ቦታ ይዘን ቁጭ አለን ።

የሰዓታት ፍጥነት ገረሙኝ ምግቡ ከመቼው ማለቁ ፀጋም እኔን ለሁሉ ነገር አመስግናኝ ቻው ብላኝ ለመሄድ መነሳቷ ሁሉም ነገር ፈጠነብኝ ጀርባዋን ሰታኝ ጉዞዋን ጀመረች የተሸናፊነት ስሜት ተሰማኝ አግኝቶ የማጣት ይዞ የመልቀቅ እያንዳንዱ የፀጋ እርምጃ ጆሮዬ ላይ አስተጋባ እራሴን አንድ ጥያቄ ጠየኩት " አግኝቶ ማጣት ያለ ቢሆንም ያጡትን ማግኘት አይቻልም ?" እራሴው ጠያቂ እራሴው መላሽ ሆኜ ከተቀመጥኩበት ተነስቼ " ፀጋማርያም አስመሳይ ነሽ " አልኳት ድምፄን ከፍ አድርጌ ድምፄን ስትሰማ መንገዷን አቁማ ወደኔ ዞራ አይን አይኔን እያየች "እንዴት " አለች ሲቃ ባለው ድምጽ ዞር ዞር ብዬ ያለንበትን ስመለከት ጥዋት ስለሆነ ከኛ ውጪ ማንም አልነበረም ጉሮሮዬን ጠራርጌ

" ችግር ውስጥ እንደሆንሽ አቃለው ምትሄጅበት አንድም ቦታ የለም ጓደኛሽም ጋር እንዳትሄጂ ባለቤቷ ደስ እንደማይለው ነግራሻለች ቤተሰብ ጋር እንዳትሄጂ አደጋውስጥ መመለስ ነው ታዲያ ይህን እያወቅሽ ምንም ችግር እንደሌለብሽ ቻው ብሎ መሄድ ምን ይሉታል እውነት እውነት እልሻለሁ ስተት ነው የሰራሽው ውፍፍፍፍፍፍ "

በደንብ ተነፈስኩኝ ሆዴ ውስጥ የቀረ ምንም ነገር ያለ አይመስለኝም አሁን ምጠብቀው የሷን ምላሽ ነው አይኔን አይኗ ላይ ተክዬ እሺ የትም አልሄድም እንድትለኝ መጠበቅ ጀመርኩ እሷ ግን
"ይህን ሁሉ እንዴት አወክ " አለችኝ
አይኗ እንባን አዝለዋል ቀስ ብዬ አጠገቧ ሄጄ
" ውሸት ነው " አልኳት ድምፄን ዝቅ አድርጌ ስሜቷን መቆጣጠር አቃታት እንኳን እናቴ ሞታብኝ እንዲያው አልቅስ አልቅስ ይለኛል አለ የመረረው እንባዋን እንዳላየው ፊቷን አዞረች፤

ማልቀሷን አላቆመችም እጇ ሳብ አድርጌ እቅፊ ውስጥ አስገባኋት እንድትፅናና መቀባጠር ጀመርኩ ግን ህመሟን ሚሽሩ አልነበሩም እንዳቀፍኳት ድምፄን ከፍ አድርጌ እግሬን ብዬ አቃሰትኩ ሀዘኗን ረስታ እንባዋን እየጠራረገች " ምነው አመመህ " አለች በእናትነት ርህራሄ ምንም ብትጎዳም የራሷን ረስታ ሰውን ምትረዳ ምናይነት ፍጡር ናት ። " አውቀህ ነው " አለችኝ ዝምታዬን አይታ ፀጥ ስላት ገባትና ህይወት ያለው ፈገግታን ለግሳኝ ና እንቀመጥ አለችኝ ።

በድርጊቴ እየተገረመች

" ምን አይነት ሰውነህ " አለችኝ

"ጠቆር ያልኩ" አልኳት

ጥርሷቿን ለመጀመሪያ ጊዜ አየኋቸው ከምር ሳቀች

" አይ ለሰው ትጨነቃለህ " ብላ ሁሉን እንድነግርህ ትፈልጋለህ አለች ልሰማት እንደምፈልግ ና ልረዳት እንደምፈልግ ነገርዃ
እሺ ብላ በረጅሙ ተንፍሳ

" እንደምታውቀው በጣም ትልቅ ችግር ውስጥ ነኝ ችግር ውስጥ የገባሁት ደሞ በኔ ስተት አይደለም በቤተሰቤ እንጂ ሙሉ ስሜ ፀጋማሪያም ኪዳኔ ነው አባቴ በቀድሞ መንግስት ብዙ መጥፎ ስራዎችን ሰርቷ ለመዘርዘር ሚያስጠላ ነው በዚህ ስራው ባገኘው ሀብት ቦሌ ላይ ህንፃዎች አሉት ይህ መጥፎ ስራው ጊዜ ሲያጋልጠው እኔን ልጁን ለባለ ስልጣን ሊድረኝ አስማማኝ ግን ከዚህ ሁሉ ሚያስጠላው ሚያገባኝ ሰውዬ virus በደሙ ያለበት መሆኑ ነው ይህን ሁሉ ቤተሰቦቼ እያወቁ ምንም አልመሰላቸውም ከቤት ከወጣሁ 4 ቀን ሆኖኛል ጓደኛዬ ጋር ለማረፍ ብሞክር ባለቤቷን አስደበደቡት ብቻ በጣም ችግር ውስጥ ነው ያለሁት "

አለችኝ ከቅድሙ አሁን የቀለላት ትመስላለች

" ጥያቄ ልጠይቅ"አልኳት እሺታዋን ገልፃልኝ

" መኖሪያ ቤት ካገኘሽ ስራ ካገኘሽ ሚጠብቅሺ ካገኘሽ ምን ታረጊያለሽ " አልኳት
እየሳቀች " ትቀልዳለህ በዚህ ሁኔታ ውስጥ አምላክ እራሱ እንዲህ አያደርግልኝም " አለች
"ቢገኝስ " አልኳት ቀጠል አድርጊ
" ደስ ይለኛል" አለች አቀርቅራ

"ተነሽ በቃ ካሁን በኋላ አንቺን ማንም ምንም አያደርግሽም እኔ እያለሁ ካሁን በኋላ ማዘን የለም እሺ ፀጋ" አልኳት እጇን ይዜ

"ተው ቃል አትግባ ሰዋቹን አታቃቸውም ምንም ከማረግ አይመለሱም እንድትጎዳ አልፈልግም ይቅርብህ "አለችኝ

ፈገግ ብዬ" እሱን ለኔተይው "ብዬ እጇን ይዤ ተነስተን ወደ ቤት መንገድ ጀመርን ለሀገሬ በውትድርና ጊዜ ቃል ከገባሁት በላይ ለፀጋ ቃል የገባሁት ከበደኝ ምክንያቱም ለሀገሬ የገባሁት ቃል ባፈርስ ከኔ ውጪ ሀገሬን ሚጠብቃት ሞልተዋል ለፀጋ ግን ከኔ ውጭ ማንም የላትም ማንም እኔ ብቻ .....

ክፍል 5..ይቀጥላል

@wegoch
@wegoch
@wegoch

#sem
አንድ ጆሮ
°°°°°°°°°

ከወደ ጥግ አንድ በካፖርት ላይ ካፖርት የጀቦኑ አዛውንት አረቂያቸውን እየተጎነጩ ቀና ብለው ለፈጣሪ ብሶታቸውን ይዘረግፋሉ፡፡ እኔ ካለሁበት ሁኜ ብሶት ካረቄ ጋር እጋታለሁ፡፡
‹‹ምን ነበር ፈጣሪ፣ የሰውን ጆሮ አንድ አርገህ ፈጥረህ ቢሆን ኖሮ፡፡ ያውም መልካሙን ብቻ የሚሰማ፤ መጥፎውን አግዶ የሚያስቀር፡፡ የዚህ ዘመን ትውልድ ጆሮኮ ሁለት የተለያዩና የተራቀቁ ነገሮችን እየሰማ፤ ከመስማቱም አልፎ እያጋጨ ነው፤ ተበጥብጦ ያበጣበጠነ፡፡ በአንዱ ጆሮ ፍቅር፣ በአንዱ ጥላቻ፣ በአንዱ መዝሙር፣ በሌላው ሙዚቃ፣ በአንዱ ዜና፣ በሌላው የመንደር ወሬ እየለቃቀመ፤ እውነቱን ከሀሰት፣ ጭካኔን ከደግነት፣ ጥሩን ከመጥፎ መለየት ሳይሳነው የቀረ አይመስለኝም፡፡…››
‹‹…ለነገሩ የሰው ልጅ ጆሮ በአንዱ እየሰማ በአንዱ ማፍሰስ የጀመረው አሁን አይመስለኝም፡፡ ሄዋን እራሱ ያንተን መራር የትዕዛዝ ቃልና የሰይጣንን አጓጊ ጣፋጭ ቃል ቱ! በጨለማ የጠላታችንን ስም አስጠራኸኝ፡፡››
የጠጡትን የተፉት መስሎኝ መሬቱን ባይ፤ ጠብታ ምራቃቸው ወለሉ ላይ ተለድፋ አየኋት፡፡ አረቂያቸውን ፉት አድርገው፤ ወጋቸውን ለአምላክ ማጫወት ቀጠሉ፡፡
‹‹ይኸውልህ የሁለታችሁ ቃል ውስጧ ጋር ተጋጭቶ በፈጠረው ስህተት፣ ራሷ ተሳስታ አዳምን አሳሳተችው፡፡ የራሳቸው መሳሳት አንሶ ሰዎችን ወደ ስህተት የሚዘፍቁ መናጢዎች የፈለቁት ዛሬ አይደለም፡፡ ያው የዛሬዎቹ በስልጣኔ ዘምነው፣ ስህተታቸውን እያወቁ ትክክል መሆናቸውን አምነው ለማሳመን መጣራቸው ለየት ያደርጋቸው ይሆናል እንጂ…››
‹‹የዋሁ አዳምም ያንተና የእሷን ቃል በሁለት ጆሮው ሰምቶ፤ ተምታቶበትና ተለያይቶበት ትክክለኛውን መምረጥ እስኪሳነው የቀባዘረ ይመስለኛል፡፡ ለነገሩ እኛንም፣ አምነን ያነገስናቸውና ወዳጅ መስለው የቀረቡን ናቸው የስህተት ኮምጣጤያቸውን በሀሰት ሰፍነግ ጨምቀው ያጠጡን፡፡›› ኮምጣጤውን የተጋቱ ይመስል፤ አረቂያቸውን ፊታቸውን አጨፍግገው በጉሮሯቸው ላኩት፡፡
‹‹ይኸው በዚህ ምክንያት አዳም ተሳሳተ፡፡ በመሳሳቱም ከመንግስትህ አባረርከው፡፡ እኛም ይኼው የምንሰማው ወሬ እየተዘበራረቀብን እድሜ ልካችን ከመንግስት ጋር እንደተጣላን ነው፡፡ ይቅርታ! እንደተቀያየምን፡፡ በምን አቅማችን ነው ምንጣላ? እኛ እንደሆን ከትቢያ ያነስን ነን፡፡…››
‹‹ይገርምኃል… ይህ ከሁለት አጽናፍ የሚመጣ ተቃራኒ ሀሳብና ወሬ ሁለት ጆሮ ላለው ፍጡር ጠንቅ እንደሆነ እንግዲህ እዚህ ዘመን ላይ ደርሷል፡፡…›› ካረቂያቸው ተጎነጩ፡፡ እኔም ተጎንጭቼ ጆሮዬን ወደሳቸው ቀሰርኩ፡፡
‹‹ይኼ ትውልድ እኮ አምላኬ… ሰላማዊ ሰልፍ በሰላም ጀምሮ በጦርነት ለመዝጋት የሚዳዳው፤ ወንድሙን ፊት ለፊት በፍቅር ቃል አሽቆጥቁጦ ዞር ሲልለት በሀሜት ጥርስ የሚቦጫጭቅ፤ ስለፍቅር ሰብኮ ጥላቻን ተግባራዊ ለማድረግ የሚሯሯጥ፤ ተደምሪያለሁ፣ አንድ ሁኛለሁ ሲል ውሎ ዘር እየዘረዘረ ሲያፈናቅል የሚያድር፤ በደምህና በመስቀልህ እንደተዋጀ አምኖ፣ ጧት ፀሎት አድርሶ ማታ ልክ እንደኔ የመጠጥ ዛር ላይ ሰፍሮ አንተን የሚያማርር ነው፡፡…››
አረቂያቸውን ከተጎነጩ በኋላ ጥርሳቸውን ብልጭ አድርገው የፌዝ ፈገግታ ለአምላክ እያሳዩ፤ ‹‹ያው እኔ ምጎነጨው ለበጎ ነው፡፡ የዚህ ትውልድ የህሊና ቁርጥማት ወደኔ እንዳይተላለፍ አስታግስበትና እረሳበት ዘንድ፡፡›› ሲሉ ማስተባበያ ሰጡ፡፡ ለካ እንዲህም ራስን ማሸሽ ይቻላል ብዬ፤ ፈገግ አልኩ፡፡
‹‹ይኼውልህ ይኼ ትውልድ… ሀገር ኖሮት ሀገሩን ሚያሳድግበትና ሚያስጠራበት አቅም ያጣ፤ ወንድም ኖሮት ወንድሙን የሚያከብርበትና ሚያፈቅርበት ልብ የተነፈገው፤ ቤት ኖሮት ቤት ገብቶ እንዳያርፍ የሰላም ሁኔታ ያሰጋው፤ እውቀት ኖሮት በተማረበት እንዳይሰራ የዘመድ ሰንሰለት ያማረረው፤ በቃ ምን ልበልህ እምነት ኖሮት እምነቱን የሚያምንበት እምነት ያልታደለው ነው፡፡ ግራ ገባኃ!? እኔም ግራ እንደገባኝ ነው፡፡›› እጃቸው መወዛገባቸውን እንዲያሳይ አወናጨፉት፡፡
‹‹አምላኬ ይኼ ትውልድ እኮ የመስማት ችግር የለበትም፤ የመለየት እንጂ፡፡ የሚሰማው የተለያየና ብዙ ሆኖበት መምረጥ ነው የተሳነው፡፡ የሀሰት ፍርድና የእውነት ሰነድን አግባብቶ ሰላማችንን የሚያደፈርስ፤ በጥቂት ሰዎች ልቦና ያደረ የሰይጣን ቁራጭ የሆነ ብትንታኝ ሀሳብ አለ፡፡ ያው አንተ በጥበብህ በረቀቀ መንገድ ብትንትኑን ካላወጣኸው እጇን ወዳንተ ስትዘረጋ የኖረች ሀገራችን፤ እጇን ወደ ኋላ ተጠርንፋ አይንህ እያየ በሀሳዊያን ፍርድ ከፍርድ ቀንህ በፊት የምትጠፋ እየመሰለኝ ነው፡፡ እግዚአብሔርን ስልህ!… አሃሃ! በስሜ አትማሉ ብለህ ነበር ለካ፡፡ ይቅርታ አምላኬ! በእኔም አትፈርድ! እንዲህ የምቀባጥረው እኮ እንደዚህ ዘመን ትውልድ እምነቴን የማሳርፍበትና የማምንበት እምነት ከውስጤ ተኖ ሄዶብኝ ነው፡፡ እስቲ በረቀቀ ጥበብህ መልስልኝ›› እጃቸውን አንከርፍፈው ወጉን ወደ ልመና ቀየሩት፡፡
‹‹ለትውልዱም ቀናውን ብቻ የሚሰማ አንድ ጆሮ ስጠው፡፡ ወይም…›› መጠጣቸውን ሊጎነጩ ብርጭቋቸውን ብድግ ሲያደርጉ፤ ይህ ፀሎታቸው ፀድቆ እዚሁ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት አፈትልኬ ወጣሁ፡፡
‹‹ወይም እውነቱን ከሀሰት፣ ጥሩውን ከመጥፎ መለየት የሚያስችል አዕምሮ አድለው፡፡›› ንግግራቸው በሁለቱም ጆሮዬ ጥልቅ ሲል ታወቀኝ፡፡ ተመስገን!! ሁለቱም ጆሮዎቼ ይሰማሉ፡፡


#ኤልዳን

@wegoch
@wegoch
@paappii
" መንገድ አስጀምረህ አልፈልግም ብሎ መመለስ ቃል አባይ አያደርግህም ሞት ነው ሚለየን ብለህ መኖር ሊለየን ?"

~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~
ካሊድ አቅሉ

አንዳንዶች ለምን አልገደልከኝም ብለው ይቀየሙሀል እንለያይ አልኳት " ለምን? " ብትሉኝ ስለማልበጃት የእኔ ህይወት መንገድ መፍሰሻ ጅማሮ ከእሷ መንገድ ጋር ሆድና ጀርባ ነው ። ለሚያፈቅሩት ደግ ደጉን አይደል ሚመኙት እኔ አጥታ ዛሬን ብታለቅስም ነገና ከነገ ወድያ ማያቆርጥ ሳቅ ከፊትዋ እንዳለ ተረድቻለው ።

"ታድያ እንዴት ተገናኛቹ በዚህ ሁሉ ልዩነት? " ብላቹ መጠየቃቹ አይቀርም ስንገናኝማ ያየነውን ቅዠት በህልም እየፈታን ቁሙ ሚለን አካል አተን በለጋ ጉልበት ዳገቱን ጀመርን በሳቅ ተጀምሮ ዳገቱ መሀል ስንደርስ መጀመሪያ ያልሰበሰብነው ሀይል ከየት ይምጣ ድካም ሲመጣ ጣት መጠቋቆም ተጀመረ . . .


ፍቅር ግን ይህን እንድናስተውል ፋታ አይሰጥም ቅርብ ቅርብን ብቻ ይገልጥልናል ። ማስታገሻ መድሀኒት ሳይሆን ነቃይ መድሃኒት እንደሰጠዋት አምናለው ። ሚያሽል መድሃኒት ደግሞ ብዙ ባህሪ ያሳያል ፊት ያሳብጣል ከቀናት ብሀላ ጤነኛ ሰው ያረጋል ። እንባዋ መንታ መንታ ይወርዳል ለሚያየን አልቃሽና አስለቃሽ እንመስላለን እኔን ልብ እንባ ግን ማን አየው ? አፌ መልስ ከሚሰጣት ግዜ በተግባር ሚያሳያትን ለመረዳት ይቀላል ።

" መንገድ አስጀምረህ አልፈልግም ብሎ መመለስ ቃል አባይ አያረግህም ሞት ነው ሚለየን ብለህ መኖር ሊለየን ? "

ላስረዳት ብዙ አልጣርኩም " ጠጣር እውነት መልኩን እስኪገልጥ ብዙ ጭጋግ ያልፋል "

ከፍቅር በላይ ብዙ ነገር ለየን " እኮ ምን?" አትሉኝም

" ሀይማኖት " ለየን . . .

አንድ ቤት ሁለት መንግስት አይነግስም እኔና እሷም ሁለት እውነታ ይዘን አንድ ትልቅ ተ ቋም ውስጥ አንገባም እንደዛ ካረግንማ ከሚያስማማን ሚለየን ገዘፈ ማለት ነው ። የሚታይ ሀዘን እኔን ባይ አያጣም በአፅናኝ ብዛት ይበረታል ።የእኔስ ሀዘን የስውር ስፌቱ ግድ የለም ይሁን እሷ ተፅናንታ ስትስቅ ካየው እሷን መታደጌ ነው የኔ የዘላለም ደስታ ።

ሶፍት አቀበልኳት ተቀብላኝ እንባዋን ስትጠርግ መውደድዋም አብሮ እየወጣ እንደሆነ ሲቃዋ ነገረኝ የቀላ አይን መንጣቱ አልነጋ ያለጭጋግ በብርሃን መተካቱ አይቀር . . . .

~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~ ~
@wegoch
@wegoch
@paappii
ብዙ የሀበሻ ወንድ በባህሪው ጦረኛ ነው። ተናካሽ ነው ። ሌላው ቢቀርና ጦር ሜዳ ባይዘምት እንኳ የራሱን ጦርነት ይፈጠራል።
ግሮሰሪ ኳስ እያየ ጠርሙስ ይወራወራል...የሞተር ውድድር ይገጥማል.. .ክንዱን እንደሱ ካለ ወንድ ጋር አጨባብጦ ጠረጴዛ ላይ ይታገላል.. . ።
በተለይ ገጠር ያሉ አባቶች ወንድ ልጅ ሲወልዱ ከልጅነቱ ባሻገር ጋሻ እና መከታ የመሆን ግዴታ ስላለበት በጀብድ ታሪኮች እና ተረቶች ልጃቸውን ሞልተውት ያሳድጉታል ።
ለምሳሌ የኔ አባት ልጅ ሆኜ ደፋር እንድሆን ስለሚፈልግ በምሽት ሽንቴ መጣ ስለው አቅራቢያ ፖፖ እያለ እንኳ ወደ አስፈሪው ጓሮ ያደርሰኝና ጥሎኝ ይመለስ ነበር ። ብዙ ጊዜ ለማለት ይቻላል ከጓሮዋችን የበቀለው ቀን በኮባነቱ የማውቀው ግንድ ሁሉ ሳይቀር ክንፍ ያበቀለ አውሬ መስሎኝ ብርርርር ብዬ ቤት እገባለሁ ። ተንደርድሬ እንደመጣሁ በራችን ስር ስደርስ ግን ያልፈራሁ የመምሰል ግዴታ ነበረብኝ ።
አንድ ቀን እንዲሁ አባዬ ጓሮ ጣለኝና ተደብቆ እኔን መከታተል ጀመረ ።
ብዙ ጊዜ ቡሪ የሚባል አጭር ጎረቤታችንን እንደምፈራው ከሁኔታዬ ይረዳ ነበር ።
ቡሪ ሽማግሌ ነው...በዛ ላይ አጭር ነው...ፂሙና ከአናቱ ላይ ጣል የሚያደርጋት ኮፍያ ጎደሎ ሰይጣን የሚመስል ገፅታ አላብሶታል ። እሱም እንደምፈራው ስለሚያውቅ አይወደኝም ። መንገድ ላይ ስሄድ እሱን ካየሁት ቀነኒሳ ነኝ። ዱካዬ አይገኝም ።
አንዳንዴ ባላሰብኩበት ቅፅበት ከኋላዬ ጎሸም ያደርገኛም። ዘወትር ካፉ የጫት ቅጠል አይጠፋም ። ዞር ስል ይገለፍጣል...አፉን ሳየው የገሀነም በር ተከፍቶ ሊሰለቅጠኝ ያሰፈሰፈ ስለሚመስለኝ እጄ ላይ የያዝኩትን ጥዬ እሸመጥጣለሁ። እሱን በማየት ብቻ ከጄ የወደቁ የአቡወለድ ብስኩቶችን ብዛት ሳስበው ዛሬም ድረስ ትልቅ ሆኜ እንኳ ይቆጩኛል።
ሽንቴን ጩርርርርርር እያደረኩ ወደ ነ ቡሪ ግቢ አሻግሬ አየሁ ።
አባዬ ተደብቆ ሁኔታዬን ይቃኛል ። ደግሞ ለክፋቱ ለዛን ቀን ቡሪ ሰክሮ ሲለፋደድ ድምፁን ሰማሁት።
መሽኛ ብዕሬን ወደ ሱሪዬ ሰገባ ዶልኩኝና እንደ እብድ እየጮህኩ ቤት ገባሁ ። በር ጋር መረጋጋት የለ ... ደፋር መምሰል የለ ... እናቴ ቡና የምታፈላበት ረከቦት ስር ከምኔው እንደደረስኩ ዛሬም ድረስ ፍጥነቱን ሳይንቲስቶች ለመገመት የሚችሉ አይመስለኝም።
ምን ልበላችሁ?
ባጭሩ ጋሽዬ አበደ ። ከእናቴ እግር ስር መንጭቆ አውጥቶ በቀበቶ ለጠለጠኝ። "የአስጨናቂ ልጅ ሆነህ የምን እንደ ሴት ሰፈርን በጩኸት መቀወጥ ነው ?" ብሎ ደህና አድርጎ አንቆራጠጠኝ ።
የልጅነት ጊዜያቶቼ በብዙ ፍቅርና ትራጄዲ የተሞሉ ናቸው ። ከአባዬ ጋር ልዝናና ስወጣ ሚሪንዳና ብስኩቴን ከላፍኩኝ በኋላ ወደ ሜዳ ይወስደኝና ከእኩያዎቼ ጋር ትግል ወይ ኳስ ያጋጥመኛል።
ብዙ ጊዜ ትግል የምጋጠመው ከቤቢ ጋር ነው...እሱ ደግሞ ደርሶ ወተት እየጠጣ ያደገ ልጅ ይሄንን ይመስላል ተብሎ ማስታወቂያ የሚሰራለት ድንቡጭ ያለ ወፍራም ነው።
እንደ ወረቀት አጣጥፎ ያነጥፈኛል...አፍንጫዬን ደም ደም የሚሸት ስሜት ሲሰማኝ ማልቀስ እፈልጋለሁ ።
ጋሽ አስጨንቅ ግን ድጋሚ እንድንታገል ቀጭን ትዕዛዝ ያስተላልፋል ...በሶስተኛው አልያም በአራተኛው ሙከራ ተሳክቶልኝ ታግዬ ካላሸነፍኩ አለቀልኝ!
አንዳንዴ ቤቢን ቀስ ብዬ በጆሮው አናግረዋለሁ ።
"አውቀህ ከወደክልኝ ነገ አስር ሳንቲም እሰጥሀለሁ" ስለው ቀስ ብሎ ከብለል ይልልኛል። ያኔ ታድያ ጋሽዬ ዓለም ዋንጫ እንደበላ አሰልጣኝ እሽኮኮ አድርጎኝ እየጨፈረ ቤት ይገባል።
ዛሬም ድረስ ያ የጀግንነት ስሜት ልቤ ውስጥ ስላለ ፍርሀት አያውቀኝም።
ወንዳወንድ ያደርጋሉ የሚባሉ ነገሮችን እከውናለሁ.. . ካፌ ውስጥ ቁጭ ብሎ በስትሮው ጁስ የሚጠጣ ወንድ ስመለከት ራሱ "ግሮሰሪ ሄደህ ድራፍትህን እየላስክ የማትዝናናው ምናባህ ነው ?" ብለህ ነርተው ነርተው ይለኛል ።
ይሄ ጥጋቤ ታድያ በቅርቡ ነበር የበረደው ። ወንድ ልጅ እንደ አውራ ዶሮ በጊዜ ገብቶ አልጋው ላይ መሰቀል የለበትም ብዬ ስለማስብ ግዳይ ጥሎ የነብር ቆዳ እንደለበሰ ዠግና ደረቴን ነፍቼ ስንጎማለል በእኩለ ለሊት ሿሿ ለመስራት ከተሰማሩ ዲቻዎች ጋር አይን ላይን ተጋጨው.. . በጆሮ ግንዴ በኩል ኮብልስቶን ሽው ብሎ አለፈ ...(የፑቲን ተዋጊ ጀቶች ይሄን ያህል ፍጥነት ያላቸው አይመስለኝም )
"ሂናቲን ሀንቴ ውሻ "ብሎ አንድ ወጠምሻ ወደኔ አቅጣጫ ተምዘገዘገ.. .አስማት ሆንኩበት ባገኘሁት መታጠፊያ ሾልኬ ተመምኩ ።
ቤቴ ስገባ እያለከለኩ ነበር ...
በጓሮ በር ገብቼ ...
"ሀኒዬ ዛሬ ለትንሽ ተቀልቤ ነበር ። ወንበዴዎች አሯሯጡኝ እኮ!" አልኳት ለሚስቴ ። ሚስቴ ሳሎን ስለነበረች
"አይዞህ ናማህን ጌታዬ" ...የሚል ምላሽ ሰጠችኝ ። ባለቤቴ ቀጠለች...
"ሆ ዛሬ እርማቸውን ቤተሰቦችህ ለእንግድነት ቢመጡ እንደዚህ ተሯሩጠህ እያለከለክ ትመጣ? "
ሳሎን ስደርስ አባቴ ቀበቶ ፈቶ አይገርፈኝ ነገር የልጅ አባት መሆኔ ታውሶት እያጉረመረመ ተመለከትኩት ።
"ወይኔ አስጨንቅ እንደዛሬም አልተዋረድሁ "
ጋሽዬ አንገቱን በሀዘኔታ እየወዘወዘ ነበር !
"ዎዜ" የሚለው ሙዚቃ ጆሮዬ ላይ አቃጨለብኝ :)

@getem
@getem
@paappii

#Mikael aschenaki
1,ስንቴ: 🎭
•••
ግንባሯ ላይ ግብዳ የመስቀል ንቅሳት አለ።ንቅሳቱ የቀይ ፊቷን ሲሶ የሚያክል ሸፍኖ መልኳን ክፉኛ ስላበላሸው ብዙ ጊዜ በሻሽ እና በነጠላ ትሸፍነዋለች።

ሁል ጊዜ ዘርፈፍ የሚል ቀሚስ አድርጋ ነበር ሰፈር የምትመጣው፤ፓንት ስለማታደርግ ቀሚሷ የቂጧ መካፈያ ውስጥ እየተሰገሰገ አስሬ ምዘዢኝ ይላታል።

*ይሄ የሰፈር ውሪ የእለት መዝናኛ ነበር*

ሁሌ አንድ አይነት ጫማ ነው የምታደርገው። ጥቁር፣በሁለት የእግር ጣቶች መሐል ማጥለቂያ ያለው...የግራ እግሩ ጫማ ማጥለቂያው የተገነጠለ ሲሊፐር... ጣ ጣ ጣ የሚል ድምጽ ከተሰማ ስንቴ ሰፈር መጥታለች ማለት ነው።

ስንቴ ሰፈር ከመጣች ለሶስት ነገር ነው ፡ አንድ ከኑሩ ሱቅ ስኳር ቡና እና ሰንደል ልትገዛ ፣ ሁለት ከቦኖ ውሃ ልትቀዳ ፣ ሶስት ደግሞ እኔን ለማየት።

ትወደኛለች።

•••

2,እኔ 🪢

ሶስት ጊዜ ራሴን ለማጥፋት ሞክሬ አልተሳካልኝም(እጄ ከሽርክት ብዛት ብሪጅስቶን ጎማ መስሏል)። እናቱ ከሞተች በኋላ ነው ወፈፍ ያደረገው ይሉኛል። ውሸታቸውን ነው! እናቴን አልወዳትም ነበር...የሞተች ቀን አሴ ፑልቤት ቦነስ ስጫወት ነው ያደርኩት። ዘጠነኛ ክፍል እያለሁ ሔለን የላኩላትን ቴክስቶች ስክሪንሻት አድርጋ ዋትሳፕ ግሩፕ ላይ ለቅቃ ለተማሪው ሁሉ ያሳየች ቀን ያለቀስኩትን ለቅሶ እንኳን አላለቀስኩላትም።

ሱስ የለብኝም ፤ ከጥንቃቄ ሳይሆን ከስንፍና ። አላጨስም፣አልቅምም፣አልጠጣም- ከቡና በስተቀር። ቡናውን እንኳን ያስለመደቺኝ መሲ ናት።

•••

3,መሲ 🌄

መሲ ከኳታር መጥታ እኛ ግቢ ተከራይታ የምትኖር ልጅ ናት ፤ ቆንጆ አይደለቺም- እንደውም ደቦልቦል ያለች ነገር ነች። ብዙ ነገር ያስለመደቺኝ እሷ ናት። በእኔ ሰው የመልመድ ችግር ጋግርታምነቴን እና ኮሶ ፊቴን ተቋቁማ በትግል ቀረበቺኝ። ቀስ እያልኩ ለመድኳት። የራሴ ክፍል ውስጥ አማትቤ የምገባ ልጅ የመሲ ቤት መዋል እና ማደር ጀመርኩ።

"...ጥርስህን ማነው የሸረፈህ??" ፈገግ እያለች...

"ኤሌትሪክ ልቀጥል ወጥቼ ከጣራ ላይ ወድቄ ነው" አንገቴን እንደደፋሁ።

ትስቅብኛለች 😂😂😂

ሌላ ቀን ደግሞ...

"...ቡቡ ግን ሳትዋሽ ንገረኝ ቺክ በ*ተህ ታውቃለህ??"

አይኔ ብልጥጥ ይልና ከአጠገቧ ብድግ ብዬ ወደቤት መራመድ እጀምራለሁ...ፍንጥር ብላ ትነሳና ይዛ ታስቀረኛለች...

"አባቴ ይሙት ስቀልድህ ነው...አታምርራ...ና ቁጭ በል በጌታ...ቡና እያፈላሁ አይደል? ብቻዬን ልታስጠጣኝ ነው??"

ቁጭ እላለሁ

የሆነ ቀን ደግሞ...

ስለባሏ ትነግረኛለች - "ባሌ አረብ ነበር። የናጠጠ ሀብታም!" የድሮ ባሏን ሃብት ልታሳየኝ አገጯን በአውራጣቷ ፍትግ ታደርገዋለች።(ቱጃር ነው ለማለት)... "... ይሄ የእናንተ ሼኩ... ከስድስት ወር አንዴ እኛ ቤት ይመጣ ነበር... አቤት የኔን ሽሮ ሲወዳት!... በየሄደበት ሁሉ የመሲ ሽሮ ካላለ ያወራም አይመስለው ነበር..."

"ከባልሽ ጋር በምን ተለያያችሁ?" ከሶስት ሰአት በፊት ካገኘኋት ጀምሮ ያወጣሁት የመጀመሪያ ዓ.ነገር ነው።

"እንዳንተ ያለ የሃገሬ ሸበላ ይሻለኛል ብዬ ፈታሁት!"... እንተያይና እንስቃለን...👀<>👀...😂😂

እውነተኛ ምክንያቷ ግን የአመሉ መብዛት ነው...አድርጊ የሚላትን ሁሉ ብትሞክርም ማድረግ ዳገት ሆነባት። ከአቅሟ በላይ ሲሆን ስትሄድ የያዘቻትን ሻንጣ ብድግ አድርጋ ጥላው መጣች።

ሐሙስ ለታ ደግሞ...

"አንተ ቡቡ"

"አቤት"

"ወዬ በለኝ ውሻ"

"ወዬ"

"ጎልደን ሻወር ታውቃለህ??"

👀

•••

4, ኑሩ 🕊️💸

ኑሩ ከወልቂጤ የመጣ የመንደራችን ባለሱቅ ነው። እናቴ በህይወት እያለች የዱቤ ደንበኛዋ ነበር። ምስጢረኛዋም ነበር...ከሃገሩ መጥቶ ታላቅ ወንድሙ ጋር እንዳረፈ መጀመሪያ ያወቃት የሰፈር ሰው እሷ ናት። ወንድሙ ትምህርት አላስተምረውም ስላለ ኑሩን ፊደል የማስቆጠር እዳ በእናቴ አዛዥነት እኔ ላይ አረፈ። ከጨዋታ ሰአቴ ላይ ቀንሼ ከማስጠናቴ በበለጠ ሁሌ ሲመጣ አብሮ ይዞት የሚመጣው የገነተረ ስጋ አይነት ሽታ ስላለ ኑሩን ማስጠናት ለእኔ 'ስቃይ' ነበር። አሁን ከዚህ ጋር ነው 'ሀሁ ፣ አቡጊዳ ፣ ኤቢሲዲ እያልኩ ስዳረቅ 'ምኖረው?' እያልኩ እበሳጭ ነበር። የኑሩ ተአምርነት የተገለጸልኝ ግን ገና በመጀመሪያው ቀን ነበር። ከፍጥነቱ ለማወቅ ያለው ጉጉት ፣ በዛ ላይ ታታሪነቱ ተጨምሮበት ከሳምንት በኋላ ደንደን ያለ መፅሐፍ የሚያነብ ደንበኛ አንባቢ ወጣው።

ያ ኑሩ ነው እንግዲህ ዛሬ ሃምሳ ብር ልፈልጠው ሱቁ ሄጄ አንዴ ታሪክ አንዴ ፍልስፍና እያወራ ቁም ስቅሌን የሚያሳየኝ።

"ደቡብ አፍሪካ ውስጥ አሁንም ድረስ ጥቁሮች እግራቸው ዝር የማይልበት ከተማ እንዳለ ታውቃለህ??"

"ኑሩ ደግሞ አሁን ይሄ እኔ ከጠየኩህ ሃምሳ ብር ጋር ምን ያገናኘዋል??"

"ላገናኝልህማ ነው ታግሰህ ስማኝ። ከተማዋ ስሟ ኦሬኒያ ይባላል... እናልህ..."

"ኑሩ በእትዬ ሞት ብሩን ስጠኝ...ስለቸኮልኩ እኮ ነው"

የእናቴን ስም ሲሰማ እባብ እንደወጋው ምላሱ ድርቅ ብሎ... ምንም ሳይናገር መሳቢያውን ከፈተና መቶ ብር አውጥቶ አቀበለኝ።

"ሹክረን ኑርሻ እንዳገኘሁ እመልሳለሁ" 🙌🏿

"አፍዋን" አለኝ ፍዝዝ እንዳለ...

ሄድኩ...

•••

5, አባቴ 🚫

ሳልወለድ ሞቷል!

•••

6,እንጀራ አባቴ 🪢

አልወደውም። አልጠላውም። በስሜ ነው የሚጠራኝ... ቃለአብ ይለኛል። አስራ ስድስት አመት አንድ ቤት ኖረን አሁንም 'እንግዳማቾች' ነን። እናቴ ከሞተች በኋላ ደግሞ ጭራሽ ተራርቀናል። ሳምንት ሳንተያይ የምንከርምባቸው ጊዜያት ጥቂት አይደሉም። እናቴ የፀሎት መፅሐፏን እና የቅዱሳንን ስዕል የምታስቀምጥበት ሙዳይ ውስጥ ለቀን የሚሆነኝን ብር አስቀምጦልኝ ወደስራው ይሄዳል። ያላስቀመጠልኝ ቀን ከኑሩ እበደራለሁ።

ያሳዝነኛል። እናትና አባቱን በተስቦ እንዳጣ እናቴ ነግራኛለች። ብቸኛ ወንድሙ ደግሞ በደርግ ጊዜ ለውትድርና ታፍሶ ተወስዶ የደረሰበት አይታወቅም።

እንጀራአባቴን ጮክ ብሎ ሲያወራ ሰምቼው አላውቅም። ድምፁን አጥፍቶ አንድ ቤት ለሰአታት መቀመጥ ይችልበታል... ማታ ከስራ ሲመጣ ሰራተኛዋ ለሶስታችንም ራት ታቀርብና በዝምታ እንበላለን... ስንጨርስ እኔ ብድግ ብዬ መሲ ጋር እሄዳለሁ... ሰራተኛዋ ደሞዟን አጠራቅማ የገዛቻትን ሚጢጢዬ ሳምሰንግ ስልኳን ይዛ ክፍሏ ትገባና ዱባይ ላለ ፍቅረኛዋ በኢሞ ትደውላለች... እንጀራ አባቴ ደግሞ ቴፑን ይዞ በረንዳ ላይ ይወጣና ቁጭ ይላል... በዚህ አሮጌ ቴፕ ከካሳ ተሰማ ውጪ ማንም ተከፍቶ ሰምቼ አላውቅም።

🎶...ያንቺማ ትዝታ ተቀርፆ በላዬ
ሳስብሽ ይረግፋል ሌት ተቀን እንባዬ...🎶

🎵...ውብዬ ውብዬ...🎵

•••

7. የእነ ታምራት ሱቅ

"ታሜ" ተጣራሁ

"ታሜ የለም" እህቱ ነች

"ቃል...ያንን ጁስ እና ሶስት የእንጀራ ላስቲክ ስጪኝ"... ሃምሳ ብር ሰጠኋት

"እሺ"

•••

8, እኔ እና መሲ 😵😵

"እሺ ላስቲኩ ምን ያደርጋል አልጋው ላይ!?"...

"ጎልደን ሻወር የሚባለውን ላሳይህ እኮ ነው ቡቡዬ።"

"ባለፈው እንዳደረግነው አልጋ ውስጥ ገብተን ብናደርግ አይሻልም?... እሱ እኮ አሪፍ ነው።"

"ይሄኛው ደግሞ ከዛ ይበልጣል።"

"እሺ እንዴት ነው የሚደረገው??"

"በመጀመሪያ ቅድም ያመጣኸውን ዋተርሜለን ጁስ ጠጥተሃል??"

"አዎ... ቁዝር አድርጎኛል ብታይ... ሸንቼ ብመጣ ራሱ ሙዴ ነው።"

"የትም አትሂድ... እዚሁ ሽናው"

"ኧ??"
-ልብሷን አወላልቃ በጡት ማሲያዣ ብቻ ሆና አልጋዋ ላይ ስትወጣ አልጋው ላይ ያለበሰቺው ነጭ ላስቲክ ተንኮሻኮሽ-

"እዚህ ጋር ሽናብኝ"...ወደ አንገቷ እየጠቆመቺኝ...

"መሲ ደግሞ ኩላሊቴን እንደሚያመኝ እያወቅሽ እንደዚህ አይነት ቀልድ ትቀልጂያለሽ??...ቶል ሸንቼ ልምጣና እንደባለፈው..."

"አይ የትም አትሂድ!" 🥺 ብላ ታፋዬን በእጇ ይዛ ወደላይ እያየቺኝ መስለምለም ጀመረች...

:ስታሳዝን:

|አምስት ደቂቃ - ጭቅጭቅ|

|አስር ደቂቃ - ጭቅጭቅ|

|አስራምስት ደቂቃ - ጭቅጭቅ|

ሃያ...

ሃያ አምስት...

"እኔ እኮ ግራ ገባኝ... ሰው እንዴት ሽንት ላዬ ላይ ሽኑብኝ ይላል?"

ሠላሣ

"በእትዬ ሞት"

"እምቢ"....የእምቢዬ ጥንካሬ እየሟሸሸ ሲሄድ ይታወቀኛል...

ሠላሣ አምስት

"እሺ እቃ ባበላሽስ?...አልጋሽስ?"

"ላስቲኩ አለ ችግር የለም!"

"እሺ ሽንቴ ቢሸትሽስ??"

"አይሸተኝም!"

"እሺ ቢዬቃጥልሽስ?"

"አያቃጥለኝም!"

"እሺ..."

"አያ...!"

"እሺ..."

"አያ...!"

እሽሽሽሽሽሽሽሽሽ

ሸናሁባት...

ሁለታችንም ድምፅ አወጣን...እኔ የግልግል እሷ የእርካታ

•••

9, የዛን ቀን 🩸

ከመሲ ጋር እንደወጣሁ ሰፈር ሁሌ ወደምቀመጥባት ድንጋይ (ስፓት) ሄድኩ። የህፃን መአት ስፍር ብሎባት ነበር... ሌላ ጊዜ ቢሆን ጠጠር አንስቼ ወደየአቅጣጫው እነዳቸው ነበር...ዛሬ ግን ባዶነት እየተሰማኝ ስለሆነ ከነሱ ጋር ቁጭ ብሎ መጫወት አማረኝ።

"ና...ና እኔ ስመጣ የታባህ ነው ምትሮጠው...ስይዝህ እጨምቅሃለሁ..."

ሁሉም እኔን ሲያዩ ከሮጡበት ተሰበሰቡ።

"ና ቁጭበል...ሁልህም ና...አንቺም ነይ..."

አጠገቤ ኩልኩል አሉ...ሞቀኝ...

"እጅህን ምን ሆነህ ነው??" አንዱ ፈላ በምላጭ ሸረካክቼ ጠባሳ በጠባሳ ወዳረኩት እጄ እየጠቆመ...

"ባለፈው እነ አብዲ ቤት ዲሽ ስሰራ ቆርቆሮ ቆርጦኝ"

"አይዞህ እሺ"🥺 ያቀፍኳት ህፃን ነች እንደዛ የምትለኝ...

እንባዬ ክብልል አለ...ፊቴን ሞቀኝ...

እንባዬን እንዳያዩብኝ ብድግ አልኩ...

"እናንተ ያቺ ስንቴ አይደለችም እንዴ???"

"አዎ ስንቴ ናት" ከህፃኖቹ ትንሽ ተለቅ ያለው...

"እየጠራችህ ነው ቡቡ"...ራሱ ህፃኑ...

"እሺ ግን እሷ ጋር ከመሔዴ በፊት የሆነ ጨዋታ መጫወት የሚፈልግ ከእኔ ጋር..."

ትልቁ ልጅ 'እኔ እፈልጋለሁ' አለኝ...

"እሺ ና በጆሮህ ምን እንደምታደርግ ልንገርህ"

🗣️👂"የሚገርም ፊልም ልጋብዝህ ነው..."

°°°

9.1,ከምትጠልቀው ፀሐይ ስር... 🥀⚱️

ሁለታችን ቆመን ነበር...

"ኧ ስንቴ ፈለግሺኝ?"

"አዎ ቡቡ አንድ ነገር ላማክርህ ነበር..."

"እሺ ንገሪኝ"

"ፊትህ ጠቋቁሯል... ያቺ የተሸረፈቺው ጥርስህም ሐኪም ቤት አልሄድ ብለህ በልዛ ቀረች አ?..."

"ስንቴ... እነግርሃለሁ ያልሺኝን ንገሪኝና ልሂድ እንጂ...መንገድ ላይ አቁመሽ ከሳህ ወፈርክ ትዪኛለሽ እንዴ??"

"እሺ እሺ ቡቡ..."

"በይ"

"... ቡቡዬ ሃገሬ ልገባ ነው"

"እንዴ ለምን!?" ትንሽ ደንገጥ ብያለሁ

" ... በቃኝ ይሄ ከተማ፡ ይኸው ስምንት አመት ከሃገሬ ወጥቼ እዚህ ከመጣሁ አንድ የኔ የምለው ነገር የለኝም... መማሰን ብቻ!"

"እሱማ አዎ።" የምለው ጠፋብኝ...

"መሄድ ካሰብኩ ስድስት ወር ሆኖኛል... ያንተ ነገር አልሆንልሽ ብሎኝ ነው እስካሁን የቆየሁት፣... አሁን ግን ግቢያችሁ ካለቺው ቀዩዋ ወፍራም ሴትዮ ጋር የጀመራችሁትን እንዳለ መቅደስ (ሰራተኛችን) ነግራኛለች።

"ኧረ እኔ እና መሲ ምንም..."

"ይገባኛል እኮ ቡቡዬ..." ማልቀስ ጀመረች... ስታለቅስ አንጀት ታንሰፈስፋለች እንባዋ እንደሰው እንባ ተከታትሎ ሳይሆን 'ሚወርደው እንደ ቧንቧ ውሃ ዥቅ ብሎ ነው 'ሚፈሰው

... "አንተ የከተማ ልጅ ነህ... እኔ ደግሞ ለቂጤ ፓንት እንኳን የሌለኝ የገጠር ልጅ..."

"ኧረ እንደዛ አይደለ..."

"እየወቀስኩህ አይደለም...ለምን ለአይንህ አልሞላሁምም አልወጣኝም...እንዲያው ነገሩን ነው..."...

እንባዋ ጭራሽ እየጨመረ መጥቷል...

"...አረቄ መሸጥ እንዴት ያስጠላል መሰለህ... ስንት ባለጌ ያገናኝሃል መሰለህ... እኔ ግን ሁሉንም ቻልኩት... ሰካራም እየተፋብኝ እኔ ትዝ የሚለኝ ጄርካን አንጠልጥዬ ውሃ ልቀዳ ስምጥ እዛች ድንጋይህ ጋር ቁጭ ብለህ ፀጉርህን ስትጠመልል ሳይህ የሚሰማኝ ደስታ ነው... እዚህ አንተን ላይ ስመጣ ህፃናቱ 'ፕላክፖርድ' ፊት ይሉኛል...እንግሊዝ አፍ ባላውቅም ንቅሳቴ ላይ እየቀለዱ እንደሆነ አልጠፋኝም... ቢሆንም አንተን የኑሩ ሱቅ በር ላይ ከነ አምሐ ጋር ስለኳስ ስትከራከር ሳይህ ሀዘኔ ሁሉ ይተናል..."

አሁንም እያለቀሰች ነው... እኔ በድን ሆኛለሁ...

"...ጋሽ ከበደን አወቅካቸው... ከዛ ከጥበቃ ቤቱ እልፍ ብሎ ትልቅ ግቢ ያላችው ሰውዬ? እንደውም ሁለት አይሱዙ አላቸው..."

ጭንቅላቴን ነቅንቄ አዎ አልኳት...

"አዎ እሳቸው... ልጆቼን ሁሉ ውጪ ልኬ በስተርጅና ብቸኝነት እፍግ አደረገኝ... ላግባሽና እያስተማርኩሽ እሺ ካልሽ ልጆችም ወልደሺልኝ እንኑር ብለውኝ ነበር... እኔ ግን ያንተ ነገር አለብኝ ቡቡዬ... እንዴት ብዬ እሺ ልበል? ተመላልሰው ተመላልሰው ተስፋ ሲቆርጡ በዛው ቀሩ። "

እንባዋ ቢቆምም ንፍጧ እንደውሃ እየወረደ አስሬ እንፍፍፍ ያስብላታል...

"እና መቼለት ነው አባቴ ደወለልኝ... 'አሁን እንዲህ አይንሽ እንደራበኝ ብሞት አባቴ አባቴ ብልሽ ታለቅሺያለሽ ወይ?' አለኝ። በጀ አልል ስለው በሰው ታሟል አስብሎ አስደወለልኝ... ይሄ ሁሉ ሲሆን ይሄን ሰፈር ጥሎ መሔድ ያቃተኝ አንተን ስለምወድህ ነው"

አሁን በተራዬ እኔ ማልቀስ ጀመርኩ...

"... ቅድም መቅደስ ስላንተና ስለተከራያችሁ ስትነግረኝ ቆረጠልኝ እንጂ አልደነገጥኩም... ውስጤ ቀድሞ ተስፋ ቆርጦ ነበር... ድሮስ የከተማው ልጅ እኔን የገጠሯን ለቂጧ እንኳን ፓንት የሌላትን..."

-ቀጭን የፍልፈል ድምፅ የመሰለ ሳቅ ሁለታችንም ጆሮ ውስጥ ጥልቅ አለ-

ተያየን... ማንም የለም አጠገባችን...ደንግጠናል... ሰይጣን ነው እንዴ??

ግራ ተጋብተን እንደተፋጠጥን ግን... ድንገት የሆነ ነገር ከቀሚሷ ስር በእግሮቿ መሐል አልፎ እግሬ አውጪኝ ማለት ጀመረ። ትንሽ እንደሮጠ የሆነ የአፈር ክምር ጋር ቆመ... አይኖቼን ጠራርጌ አየሁት... የቅድሙ ህፃን ነው።

"...ቡቡዬ ይመችሽ ምርጥ ፊልም ነው የጋበዝሺኝ። በስማም ጥግብ እስክል ነው የከለምኩት...ቡቡ ... "

ልቤ ከደረቴ ተንሸራቶ ወርዶ ሆዴ ውስጥ ገብቶ ሲመታ ተሰማኝ። ጢንንንንንንንንንን አለብኝ... መተንፈስ ጠፋብኝ....

ቀና ብዬ አየኋት... ቅድም አይኗ ውስጥ የነበረው ፍቅር በመዘግነን ስሜት ተቀይሯል... ሐዘኑ ግን አሁንም አለ... ቆሞ የነበረው እንባዋ እንደ አዲስ ፏ ብሎ ወረደ... መሸት እያለ ስለነበር የንግድ ዳሩ አፕል ብርሃን በእንባዋ ሲንፀባረቅ ደም እያለቀሰች መስሎ ታየኝ። ልይዛት ፈለግኩ...ፈራሁ። ድንገት ግን ዞር ብላ ፈትለክ አለች...

"ስንቴ!" ብዬ ተከተልኳት...

ሮጠች ... ተከተልኳት...ሮጠች...ተከተልኳት... ደረስኩባት...ደረስኩባት... ደረስኩባት.... ገጭ!!!

ስንቴ ወደላይ ብድግ አለች.. ከዛ ደግሞ... ወደታች ተምዘግዝጋ ፍርጥ!! የፍንዳታው ድምፅ ከየት እንደመጣ አላውቅም... ስንቴ ግን አይደለችም... ስንቴ እኮ ፍንዳታ አይደለችም... ጨዋ ናት።
የጣት ማስገቢያው የተገነጠለ ጥቁር ሲሊፐር ፊት ለፊቴ አረፈ... አየሁት...ሳቄ መጣ.... ከትከት ብዬ መሳቅ ጀመርኩ.... ሃሃሃሃሃ....ሳቄን ሳላቋርጥ ብድግ አደረኩት... አገላብጬ አየሁት...የተገነጠለው ጫፍ ላይ መርፌ ቁልፍ አለ፣... ስንቴ ተንሸራታ መኪና ውጥ እንዳትገባ ቆልፎ ያልያዘ መርፌ ቁልፍ... ድምፄን ከፍ አድርጌ ሳቄን ቀጠልኩ... ከትከት....

"ኡኡኡኡ..." ጩኸት ከሳቄ አቋረጠኝ... ወደጩኸቱ አቅጣጫ ስዞር ከነጭ መኪና ውስጥ ወጥቶ እየጮኸ ወደእኔ የሚመጣ ሰውዬ ታየኝ። የእንጀራ አባቴ ነው። ይሄን ሰውዬ ሲጮህ ሰምቼው አላውቅም... ጩኸቱ ያስቃል.... ከትክት .... ሃሃሃሃ.... አስፋልቱ ላይ ተንጋልዬ መሳቅ ጀመርኩ.... አባቴ ይጮሃል... ሰው አንድ ሁለት እያለ እየተሰበሰበ ነው... በሳቄም በጩኸቱም በግርግሩም መሐል ከአባቴ መኪና ውስጥ ክራር ተምዘግዝጎ ይመጣል... ካሳ ተሰማ እየዘፈነ ይከተላል...

🎶...ውብዬ ውብዬ ...

አንቺ መንገደኛ...ቀረሁ ተነጥዬ...🎶

-----

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Girum
|•

በተፈጥሮህ ሴቶች አይን የማትገባ ድውይ ነህ። ድንገት ብትገባ እንኳን ጠዋት ጫማህን ስታስጠርግ ጮርናቄ የምታቀርብልህ የውብዳር ወይ ደግሞ ከግንባር ያለግራ እግር የተመለሰቺው ምክትል አስር አለቃ አይንዬ አይን ውስጥ ነው። አንተ ደግሞ እነሱን አትፈልግም... ልብህ ፑል አጫዋቿ ሊሊ ወይም ኮፒ ቤት የምትሰራው መአዛ ጋር ነው የሚያሮጥህ።

[ካንተም ብሶ ትመርጣለህ!]

ግና(😂) ከተወሰኑ የብቸኝነት ወራት በኋላ (በላጤ ካላንደር ከዘጠኝ የሎሽን ብልቃጥ በኋላ) ያለችህን ድፍረት አሰባስበህ የሃምሳ ብር ሻይ ጠጥተህ መቶ ሃምሳ ብር ቲፕ የምታደርጋትን አስተናጋጅ ትጠይቃታለህ። ውለታ የሚሰራ ሰው ፊት እያሳየች(የምርም ውለታ እየሰራችልህ ነው 😂) 'እሺ ግን እ'ራት ብቻ ነው' ትልሃለች... 'አዎ ራጉኤልን' ብለህ እጇን ትመታላትና የታምራት ደስታን ዘፈን እያፏጨህ ወደቤትህ ትሄዳለህ።

[🎶...የ•ማ•ይ•ረ•ሳ•ው ጌታ-የ•ማ•ይ•ረ•ሳ•ው ጌታዬ...🎶]

-ከቀጠሮህ ቀን ቀደም ብሎ: ቅድመ ዝግጅት

°ሃሳቧን እንደምታስቀይራት እርግጠኛ ሆነህ ከአንገት በታች ጸጉር የሚባል ነገር ሳታስቀር ድምጥማጡን አጥፍተሃል።

°'የፍቅር ኬሚስትሪ' መፅሐፍን ሶስት ጊዜ አንብበሃል...ኖትም አውጥተህ ይዘሃል

°ቴክኖ ስልክህን በጫት ደንበኛህ አይፎን ሰባት ቀይረሃታል...

°ተረከዝህ ጋር የተቀደደቺው አንድ ለእናቷ ካልሲህን ተመሳሳይ ክር ሁለት ፌርማታ ተጉዘህ ገዝተህ ሰፍተሃል...

°ከግራጁዌሽን በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥርስህን ቦርሸሃል( ለዛሬ ጥርስ መቦረሽ የአፍ ጠረን አያመጣም)

-የቀጠሮህ ቀን ጠዋት: ደስጋት(ደስታ + ስጋት)

°እንዳቅሚቲ ዘንጠሃል ፣ አክስ ዲኦደራንትህን ብብትህ እና ብሽሽትህ ውስጥ ነስንሰሃል ፣ ጸጉርህን በጄል ፈርዘሃል ፣ የክትህን ለብሰሃል ፣ ቆዳ ጫማህን ገድግደሃል ። ፏ!👌🏿

°ምንም እንዳልረሳህ ደብል ቼክ አድርገህ ትወጣለህ።

-የቀጠሮ ቦታ: ዴት ናይት

ተጠብቃ ተጠብቃ ከች ትላለች ፤ ጨብጣ እየሳመችህ "አስቆየውህ እንዴ" በአፍህ ጉንጯን እየሳምክ በአፍንጫህ ከአንገቷ ጠረኗን እየሳብክ "ኧረ እንደውም...ከመጣው አራት ሰአትም አልሞላኝ አሁን ነው የመጣሁት!" ትላታለህ

መጀመሪያ አካባቢ ፍርሃት ሽባ ቢያደርግህም ፣ እየቆየ ሲመጣ ሪላክስ ማድረግ ትጀምራለህ ፣ ኧረ እንደውም ቀልድ እየፈጣጠርክ ታስቃታለህ። አስተያየቷ ደስ ይልሃል ፣ 'አዪዪዪ ዛሬ ይቺ ልጅ ወደቤቷ የምትሄድም አይመስለኝ' ትላለህ(ኦፍኮርስ በውስጥህ)።

ራት በአሪፉ ያልቃል

ዲዘርትም እንደዛው

ቅምቀማም እንደዛው

"እና ምንድነው ሃሳብሽ??"

"ከጠበኩት በላይ በጣም ደስ ብለኸኛል...ግን በመጀመሪያ ዴት ምንም ላላደርግ የራሴ ህግ አለኝ"

"እና ሌላም ዴት ይኖረናል እያልሺኝ ነው??" ሰፍሳፋነትህ ለራስህም ያስደነግጥሃል። 🤦🏾‍♂️

"እንዴ ታዲያስ!? በጣም ደስ የሚል ምሽት ነው ያሳለፍኩት።"

"እሺ" ትላለህ ሁለመናህ ቦግ ብሎ።

"በል መሽቶብኝ ጎዳና እንዳላድር ቶሎ ሸኘኝ" ትልህና ብድግ ብላችሁ ወደቤቷ ወክ ትጀምራላችሁ...

ከሬስቶራንቱ ወጥታችሁ ቤቷ እስክትደርሱ ሰባት ጊዜ አስቀሃታል፣ ሁለት ጊዜ እጅህን ነክታሃለች ፣ የውዲ አለን ፊልም ላይ እንዳየኸው ኮትህን ልትደርብላት አስበህ ከውስጥ ቀዳዳ መሆኑ ትዝ ሲልህ ሃሳብህን ቀይረሃል ፣ ሒሏ ተሰብሮ ቦርሳዋ ውስጥ ያለውን ጫማ ስትቀይር የተሰበረውን ሂል ይዘህላታል...[ ከሞላ ጎደል ስኬታማ ምሽት!]

-የግቢዋ በር ላይ: ልሳማት አልሳማት ከራስ ጋር ግብግብ

"በል እሺ ደህና እደር" ✋🏿 እጇን ብቻ ዘርግታልህ ወደቤቷ ትራመዳለች...

"እንትን"

"ጠራኸኝ?"

"እእእእ ጫማሽን ረስተሻል" እጅህ ላይ ያለውን ታኮው የተሰበረ ጫማ ትዘረጋላታለህ...

"ውይ" ትልና ተመልሳ መጥታ ትቀበልሃለች... ከዛ ቀስ ብላ ወደ ጉንጭህ ትንጠራራ እና በስሱ 'እምጱዋ'...

🎶...ደስ ደስ እያለኝ ነው እንጃ ደስ እያለኝ ነው...🎶

-ማታ ቤትህ: የደስታ ባህር ውስጥ ዋና...

ደስታ እንቅልፍ ስላሳጣህ አጠገብህ ያለውን ሬዲዮ ትከፍታለህ...

"ጤና ይስጥልኝ አድማጫችን የፍቅር ክሊኒኮች ነን ማን እንበል"

"እገሊት ነኝ"

የደዋዩዋን ስም ስትሰማ ድንግጥ ትላለህ...እሷ ትሆን? ትልና ትስቃለህ 😂😂 አንተ ሰውዬ ልታፈቅር ነው እንዴ? ሁሉ ሰው እሷን እየመሰለህ እኮ ነው።

"እሺ እገሊት ከየት አካባቢ ነው??"

"ከእንትን"

"ምንድን ነበር ህመምሽ እገሊት"

"በመጀመሪያ ዮኒዬ በጣም ነው የምወድህ በጣም ነው የማደንቅህ"

"ቴንክዩ አድማጫችን...አሁን ወደህመምሽ ቀጥይ"

"እኔ ችግሬ ኤክሴን መርሳት አለመቻሌ ነው። የተለያየነው በኔ ጥፋት ስለሆነ ራሴን ይቅር ማለት አልቻልኩም በዛ ላይ ፍቅሩ አልወጣልኝም...እሱ ግን ከነመፈጠሬ ረስቶኛል...በኔ ጥፋት ስለተለያየን ራሴን ለመቅጣት ብዬ ከሊጌ በታች ከሆኑ ሰዎች ጋር ዴት እወጣለሁ። እነሱን ከኤክሴ ጋር በማነጻጸር ያጣሁትን ነገር እያሰብኩ ቤት ገብቼ ስቅስቅ ብዬ አለቅሳለሁ...ራሴን ቶርቸር ማድረጌ ትንሽም ቢሆን ፀፀቴን ያስታግስልኛል...የሚገርምህ ዮኒዬ ዛሬ ራሱ ከዴት ተመልሼ ነው የምደውልላችሁ... የዛሬው ደግሞ ይለያል ብታይ ፍፁም የኤክሴ ተቃራኒ ነው... መልኩ የማይስብ ቁመቱ ቁመት አስተኔ...ቀልዶ የሚያስለቅስ... በቃ ምኑም የማይስብ ሰውዬ ነው...የምሰራበት ካፌ በመጣ ቁጥር የሚጥልልኝ ቲፕ ተጠራቅሞ የቤት ኪራዬን ስለሚችልልኝ እምቢ ብለው ደንግጦ በዛው እንዳይቀር ብዬም ቅድም ባልኩህ ምክንያትም እሺ ብዬው ዛሬ ራት በላን... ሰአቱ አላልፍልሽ ብሎኝ ምግቤን ራሱ በስርዓት አልበላሁትም... ቶሎ ቤቴ እንድደርስ ስጣደፍ ኤክሴ ለልደቴ የሰጠኝን ውድ ጫማ ሰብሬው አረፍኩ...እሱ ጫማ ብቸኛ የኤክሴ ማስታወሻ ነው ብታይ ዮኒዬ...እና ስጣደፍ ረስቼው ልገባ ስል ጠርቶ እንኪ ሲለኝ በደስታ ብዛት ሳላስበው ሳምኩት... ብታይ ከሳምኩት በኋላ እንዴት ሽምቅቅ እንዳልኩ...እና ብቻ ዮኒዬ ይሄንን ነገር እንድተው ከተቻለም ኤክሴን መልሼ እጄ እንዳስገባ ምን ትመክሩኛላችሁ?..."

•ስቱዲዮ ውስጥ የአራት ሰው ጫጫታ ይሰማል•

"የሚገርም ነው እህታችን... የህክምና የመጀመሪያው ስቴፕ ህመምን አምኖ ወደሀኪም ቤት መሄድ ነው... ያንን ደግሞ አድርገሻል...ቀሪው የእኔ የዶ/ር ዮናስ እንዲሁም የባልደረባዬ የዶ/ር ግዛቸው ስራ ነው... እና እኛ የምንልሽ ምንድነው...ኤክስሽን አግኚው...አዋሪው...እሱ ጋር ስትሄጂ በተቻለሽ አቅም አጋላጭ ልብሶችን ልበሺ...ጠዋት ጠዋት ፀበል ጠጪ ከሰአት ደግሞ አንዱ ፓስተር ጋር እየሄድሽ ይፀለይልሽ... ዱአሽን ደግሞ እንዳትረሺ እሺ አድማጫችን... በተጨማሪ ደግሞ ዮጋ ግድ ነው...ራስሽን ተንከባከቢ ፎከስ ኦን ዩርሰልፍ... በሐማስ ሲሸልስ ምናምን እየሄድሽ ችግርሽን ለአንድ ለሁለት ሳምንት እርሺ... ጆርናል ነገር ብትፅፊም አሪፍ ነው... አሮማቴራፒም አንድ አማራጭ ነው...ኤክስሽ ካንቺ ጋር መሆን አሻፈረኝ ካለ የቀረበት እሱ እንደሆነ ማሳየት አለብሽ... መሐል ቦሌ ላይ ጂ ፕላስ ፋይቭሽን ግትር... ከተማ ውስጥ አሉ የተባሉትን መኪናዎች ንድት...
ስራዬ አስተናጋጅ ነው አልነበር ያልሺኝ በቃ እንደውም ይሄንን ማድረግ እኮ ላንቺ ቀላል ነው ዘንድሮ የአስተናጋጅ ደሞዝ ከአንድ የፕሪሚየርሊግ ኳስ ተጫዋች ደሞዝ እኩል ነው። ከዛ በተጨማሪ ትሪት ዩርሰልፍ ቱ ኧ ናይስ ዲነር...ለብቻ ራት አይበላም ያለው ማነው?? አቅም ካለሽ ሆንግኮንግ ከሌለሽ ዱባይም ቢሆን እየሄድሽ ራስሽን ራት ጋብዢ... እየሰማሽን ነው እህታችን??"

"አዎ አዎ ዮኒዬ...ማለቴ ዶክተር ዮኒ" ቅቅቅቅ

"አዎ ጎበዝ...ያልንሽን ሁሉ ካደረግሽ ህመምሽ ሙሉ በሙሉ ነው ሚፈወሰው ከዛ በተጨማሪ እንደ ክኒን ነገርም እናዝልሻለን...የባልደረባችንን የዶ/ር ብርሐኔ ንጉሤ መፅሐፍ 'የፍቅር ኬሚስትሪ'ን አዘንልሻል...እሱን በቀን ሶስት ጊዜ ከምግብ በኋላ...እሺ አድማጫችን!??"

"እሺ ዮኒዬ በጣም ነው ማመሰግነው...እንዳላችሁኝ አደርጋለሁ... እሺ....እሺ...መልካም አዳር ለእናንተም"

°ስልኩ ይዘጋና ...ሰአት ስለደረሰ ዝግጅቱ ይጠናቀቃል°

ያንተ መተንፈስ የተጠናቀቀው ግን ገና ቅድም ነበር...😂😂

@getem
@getem
@paappii

#Girum
ሁለት ፡ ነጥብ
#ስርዓተነጥቦች 1

ጉሊት ነጋዴዋ የተበሳሱ ቲማቲሞች መርጣ እንድሸጥልኝ ስለጠየኳት ግራ ገብቷት ተፋጥጠናል። እኔ ኑሮዬን የማይመስል ነገር መሸመት አቁሜ ፤ እሷ እንከን ያለባቸውን ቲማቲሞች ከጤነኞቹ ጋር ሸውዳ መቀላቀል እንጂ፣ ተጠይቃ መሸጥ ላይ ልምድ ስላልነበራት። ዛሬ... እርማቸውን ፈላጊ ቢያገኙ፣ ትል የገጠባቸውን ቲማቲሞቿን በስስት አየቻቸው። የሷን ሀሳብና ሂሳብ ቸል ብዬ... አጎንብሼ ከቲማቲም መደቦቹ ውስጥ የተበሳሱትን እየለየሁ በጨምታራ ፌስታሌ ማስገር ጀመርኩ። ጎላቿ ጃንጥላዋን ዘርግታ ግድ እንደሌላት ሆና ታየኛለች።

ድንገት ከበስተጀርባዬ... ሞቅ ያለ የማለክለክ ድምጽ ሰምቼ ዞርኩ። አንድ ኑሮ ያፍተለተለው ጎልማሳ... ክምር ቄጠማ አዝሎ እየመጣ ነው። ሁለመናው የድካሙ ምስክር ነው። ገና እንዳየችው፣ ባለጉሊቷ ጃንጥላዋን ከበስተአናቷ ወደ ስር ዝቅ አድርጋ መደቧን በገሚስ ከለለችው።

ጎልማሳው በገዛ ላቡ ረስርሶ አጠገባችን እንደደረሰ... በድካም እያቃሰተ
"ቄጠማ ነበረሽ እንዴ?" አላት፤ በጃንጥላዋ በገሚስ የከለለችውን መደብ በዓይኖቹ እያሰሰ።
"ሞልቶ! ሊያውም ለምለም!" አለችው ፈገግ ብላ።
"አዬ እድሌ! ወይ እድሌ! እንደአህያ ልፋ ያለኝ ፍጡር! ድንገት ባይኖራት ብዬኮ... በሌለ አቅሜ... ልሳለምበት ከሄድኩት ከልደታ ቤተስኪያን ደጃፍ ድረስ ተሸክሜ መምጣቴ ነው... !"
እንባ አቅርሮ ወደላይ ቀና አለ
"ምነው መድኃኒዓለም? ካልሞትኩ አታሳርፈኝም ማለት ነው? ምነው ምነው? ደጃፌ ላይ እያለ... እንደአጋሰስ ከአገር ቂጥ ተሸክሜ መዛል አለብኝ? "

ቅርዝዝ ብሎ ወደ ጉሊት ሻጯ ዞረና...
"ድንገት አነሰ ካሉኝ ... አንቺ ጋር ተመልሼ ብመጣ አያልቅብኝም አይደል?" አላት በልምምጥ።

"ኧረ አያልቅም ብዙ ነው ያመጣሁት!" ግንባሯን ቋጥራ።

መልስ ሳይሰጣት እየተንፏቀቀ አልፎን ሄደ። መሄዱን አይታ ጃንጥላዋን መደቡን ከጋረደችበት ወደላይ ከፍ አደረገችው። ወዲያው መደቧን በፍጥነት አሰስኩ። ቄጠማ አልነበራትም!

"እንዴት የሌለሽን አለኝ ብለሽ፣ ምስኪን ለፍቶ አዳሪ ተስፋ ላይ ትቀልጃለሽ? ቆይ ተመልሶ ቢመጣስ?" በንዴት ቀና ብዬ ጮህኩ።

"ተመልሶ ቢመጣማ... አለቀ... ተሸጠ! እለዋለኋ!" በግድ የለሽነት ትከሻዋን አራገፈችብኝ...
ፈራኋት... !

ትበልጠኛለች...
እንደኔ መሰሎቿን አትሰበስብም!

ቲማቲሞቹን መምረጥ አቁሜ፣ ራሷ መርጣ እንደእግዜር እስክትሰጠኝ መጠበቅ ጀመርኩ...
ትበልጠኛለቻ...!
እንኳን የተበሳሳባትን፣ የሌላትንም ጭምር... አዋድዳ መሸጥ ታውቅበታለች ...

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Rediet aseffa
" ለካስ ፍቅር ለሁለት ፍቅር እየተሰጣጡ ሌላውን አለም ጆሮ ዳባ ልበስ ሚሉበት የስስታሞች አዙሪት ነው ። ቅፅበት ብቻ ሚታይበት የስሜት ጨዋታ . . . . . "

~  ~   ~   ~   ~    ~    ~    ~  ~  ~ ~    

(ቁስሉን የነኩበት አፍቃሪ )

በካሊድ አቅሉ

ትኩስ አፍቃሪዎች ፍቅራቸውን ያጋሉ መስሉዋቸው ለጋ ቁስልን በእንጨት ይሰዳሉ ።  ምናለ በአይን ቢያወሩ በልብ ቢደማመጡ አስራ ሁለት ሰው የያዘ ሚኒባስ ታክሲ ውስጥ ሚስቱን የፈታ ፣ ባልዋን የፈታች ፣ ባል የሞተባት ፤ ሚስት የሞተበት የተከዳ የተከዳች ይኖርበታል ብሎ ማሰብ እንዴት ይቸግራል ?

" ከአሁን ወዲህ እንዳትደውልልኝ ካንተ ጋር ያሳለፍኩት ግዜ ግዜዬን እንደገደልኩ ይሰማኛል "   መልዕክቱን ማመን አቅቶኝ ደጋግሜ ሳነበው ነው ለመሙላት አንድ ሰው ሚፈልግ ታክሲ ላይ እየተግተለተሉ ለሁለት ገብ ። " እንዴ አንድ ሰው እኮ ነው ሚይዘው " አልኩኝ ብሶቴን መተንፈሻ ሰበብ ፈልጌ የተቀመጥንበት ቦታ ሁለት ሆነው ሲመጡ አንድዋ ስልክ ተደውሎላት ስትወርድ ተመቻችተው ተቀመጡ ።

"ደከመሻ? "
አፍቃሪ በሚመስል ቅላፄ ሄዋኑን ያበረታል። የሄለንን ቴክስት ደግሜ ደግሜ አነባለው ከነሱ ፍትጊያ ለመሸሽ .  .  .  .

አንገትዋን ክንዱ ላይ አሳረፈች

ቁስሌ መጠዝጠዝ ጀመረኝ  (ህመም)

ፀጉሩን ማሻሻት ተቀጠለ . .  .

ቁስሌን ያደሙት ሳያንስ በህብረት ጨው ነሰነሱበት    (የፍቅረኞች ወንጀል)

" ለካስ ፍቅር ለሁለት ፍቅር እየተሰጣጡ ሌላውን አለም ጆሮ ዳባ ልበስ ሚሉበት የስስታሞች አዙሪት ነው ። ቅፅበት ብቻ ሚታይበት የስሜት ጨዋታ . . ."

ቅርፅ  ያለው ሳቅ  "ወደህነው"
ሁሌ እንከባከብሻለው ብልዋት ነው መሰለኝ ።

" እዚህ ትወርዳለህ? ችግር የለም ቤብ እኔ ቤት ገባለው ። "

ተስማምተው እንደመነሳት አለና ተመልሶ መቶ ስምዋት ወረደ ።

በፍቅር ህግ ግን እርስ በእርስ ፍቅር እየተሰጣጡ ሶስተኛ ወገንን አንቆ መግደል ይቻላል ?

ገነት ውስጥ እየተንጎማለሉ ነፍሴን ገሀነም ውስጥ አሽከረከርዋት . . .  .

" ኪያ በግዜ ቤት ግባ እኔ እንደገባው እደውልልሀለው "  ፌርማታው ደርሶ የወረደው ፍቅረኛዋ በእሺታ አንገቱን ነቀነቀ ።

ለመሰዋት እያንደረደረችው እንደሆነ እሱ  መች ገብቶት

እኔም ፈገግ አልኩና ወደ ውስጥ ለራሴ ቃል አሻገርኩ " እኛም እንዲህ ተብለን ነበር "
~   ~   ~   ~    ~   ~    ~   ~    ~    ~

@wegoch
@wegoch
@paappii
" የንፁህ ፍቅር ስጦታው ከስጋ አልፎ ነፍስ ላይ መገኘቱ ነው ። ወደታች ተራመድን ወደላይ የመንገዱ ማብቂያ መገናኘት ነው ። "

(ካሊድ አቅሉ)

~    ~   ~    ~     ~    ~     ~    ~    ~

ከሙዚቃ ቤቱ ዘፈን ተሻግሮ ጆሮዬን ጎበኘው ። ሞት ያጎላል አምናለው የተለመዱትን ሲያነሳ ለነገ አይልም ሳቅን ጨዋታን ጥርግ አርጎ በነበር መዝገብ ይከትበዋል ። አሊ ፊቱ ጠቁርዋል ያጣት እናቱን በሰበብ አስባብ ያስታውሳታል ።

እናቱ ለእሱ የአባትም ሚና የነበራት በሰው ማትተካ ለሙሉነቱ ምክንያት ለመጉደሉም ክፍተት ናት ። እናትና ልጅ በመንገዱ  ችብስ እየተጎራረሱ ሲሄዱ አይቶ ነው ትኩስ ቁስሉ የጠዘጠዘው ቁስል ሲያሳክክ ዳር ዳሩ ይነካል እንጂ ዘው ካሉበት ትርፉ መድማትና እንደ አዲስ ማገርሸት ነው ።  ለዛም ይመስላል አሊ ቶሎ መለስ አለና ቀልብን ለመግዛት ሞከረ ። የእናቱን ናፍቆት ግን በብርቱ እንዲያስታውስ ሁለተኛው አብይ ምክንያት ከሙዚቃ ቤቱ አልፎ ጆሮው የደረሰው የክብር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ዜማ ነው ።   
" ሞት እንኳን ጨክኖ ወስዶ
         ከሚያስቀረው
ምናለ ደጋጉን ዳግመኛ ቢፈጥረው "

ይላል ጥሌ ደግ ወዳጆቹን አስቦ በመብሰልሰል  የእናቴ ቅርብ ወዳጅ ይመስል በቀብርዋ ላይ ተገኝቶ ከእንባው ጋር ሚያንጎራጉር . . .

" ለተራበው አጉራሽ ላጣው ሰው ደጋፊ
  ሲሆን ያሳዝናል እንደ አፈር እርጋፊ "

ጥሌ ይንገበገባል አምላኩን በእርጋታ በሰከነ መንፈስ ስማኝ ለምን ይላል ቀስ ያለ አስመስሎ አምላኩ ላይ በቀስታ ይጮሀል እንደዚህ እያለ  . . .

" የሰራ ለሀገሩ ያልሰራም ሰነፉ
ያስኬዳል መንገዱ ለሞት ሲሰለፉ
ሞት ምርጫን ባወቀው እንዴት በወደደው
ስንዴን ከንክርዳዱ ለይቶ ቢያስቀረው "

አሊ ከስንኞቹ ጋር ከፍ ዝቅ እያለ እንባ አርሶታል ። አስተናጋጅዋ መታ የማክያቶ ቢል አምጥታ አጠገብ ስታኖር ብንን አለና አመሰግናለው ብሎ እጁን ወደ ኪሱ ለሂሳብ ሰዶ ሶፍትም አብሮ እውጥቶ እንባውን ጠረገ ።

" አምላክ የለየን የኔን ብርታት ለመታዘብና እናቴን ከመናፈቅ ነው  ። ማንንም አማልክት ቢወድ የእናቴን ጫፍ አያደርሳቸውም ። ለዛም አይደል ጀነት (ገነት ) ከእናት እግር ስር ናት ሚባለው ለዚች ሰናፍጭ ለምታክል አለም እናቴን ቀማህኝ ብዬ ከሱ ጋር ለምን ክርክር ልግባ ?    ሰማይ ቤት በባህር እየጠበቀኝ ለዚች ማንክያ ለማትሞላ አለምማ ዶሴ አላስከፍትም ።  " የንፁህ ፍቅር ስጦታው ከስጋ አልፎ ነፍስ ላይ መገኘት ነው ። ወደታች ተራመድን ወደላይ የመንገዱ ማብቂያ መገናኘት ነው ። "

~   ~     ~    ~     ~   ~     ~    ~    ~
@kalidakelu

@wegoch
@wegoch
@paappii
ውድ የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች,

አዲሱን መተግበሪያችንን El-Test(ኤል ቴስ) መለቀቁን ስናበስር በደስታ ነው።

ተማሪዎች የኢትዮጵያን ብሄራዊ ፈተና የበለጠ እንዲለማመዱ የሚረዳ መተግበሪያ ለማዘጋጀት ባለፉት ጥቂት ወራት ሳትታክት ስንሰራ ቆይተናል።

መተግበሪያችን ለፈተና የምታጠኑበትን መንገድ በመቀየር እና የሚገባዎትን ነጥብ እንድታገኙ ያግዛል። ባለፉት ዓመታት የወጡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ፈተናዎችን በጊዜ ቆጣሪ ይዉሰዱ እና የደረሱበትን ደረጃ ይገምግሙ። ለእያንዳንዱ ምዕራፍ በእርስዎ ውጤቶች ላይ ትንታኔያዊ መረጃ(analytical data) እና ምክረ ሀሳችን ያግኙ። ለአጠቃቀም ቀላል በሆነ መተግባሪያ ላይ ምንም አይነት ማስታወቂያ ወይም ብቅ ባይ ባነሮች ሳይረበሹ ፈተና በወሰዱ ቁጥር ለውጦትን እንገመግማለን።

የእኛን መተግበሪያ በቀጥታ ከ App Store እና Google Play ማውረድ ይችላሉ።
https://eltestapp.com/el-test.apk
ለበለጠ መረጃ: https://eltestapp.com/ ይጎብኙ።
ስልክ፡ 0923678876 / 0921484549
E-mail: [email protected]
--------------   ሸበላው -----------_

part-1

   ሴቶች ይወዱኛል። በጣም ። ከአንገት በላይ መውደድ አይደለም ። ከልባቸው ካለኔ መኖር እንደማይችሉ አይነት ። ብዙ ሰዎች እንደ ፀጋ ሊያዩት ይችላሉ ። ከእኔ ውጪ ማለት ነው ። በመልኬ ብቻ አይደለም የሚወዱኝ ታዲያ ።በእርግጥ ቆንጆ ነኝ ። ልቅም ያልኩ ሸበላ ። አውቃለው ትንሽ ስሙ ይደብራል ። ወንድ ብሎ ቆንጆ ሲባል እመኑኝ ግን የኔ ይለያል። ሁሉም ሴቶች ሳያፈጡብኝ አያልፉም ። እንደውም አብዛኞቹ ያነባሉ ። ለምሳሌ ከእንቅልፌ እንደተነሳው ፊቴን ሳልታጠብ ፣ ልብሴን ሳልቀይር፣ አይን አሬ ተዝረክረኮ ፣ በባዶ እግሬ የሆነ ሰርግ ቤት በስህተት ብገባ እንኳን ሴቶቹ አይናቸውን ከእኔ ላይ መንቀል ያቅታቸዋል። "ወይኔ ሲያምር" ፣ "አዪውማ አንትና " ፣ "ግርማ ሞገሱን አየሽው ... ውይይ ፎቶ አንሺው በናትሽ ስልኬን አልያዝኩም" ምናምን ይባባላሉ። ወጣቶች ብቻ አይደሉም እኮ በየትኛው እድሜ ያሉ ሴቶች እኔን ሲያዩ ያቅበዘብዛቸዋል ። ህፃናት ማሳደጊያም ሄድኩ አረጋውያን መርጃ ሴቶች ይጠመጠሙብኛል። ሌላው ቢቀር አራስ ልጠይቅ ሄጄ አራሷ ሴት ከሆነች "ጡት እሱ ካላጠባኝ" ብላ እሪ ትላለች ። ምኔን እንዳጠባት አስባ እንደሆነ እግዜር ይይላት። እንደፈረደብኝ ጡንጦ ደረቴ ላይ ሰክቼ ልጅቷ እስከምትተኛ ጠብቄ ነው የምወጣው። እሱንም በመከራ እናትየዋ
አራስ ገንፎውን በላይ በላይ አጉርሳኝ።

  ግን እንደተናገርኩት የሚወዱኝ ሴቶች ናቸው። ሴቶች ማለት ሴቶች ብቻ ። ወንዶች አይወዱኝም ። ይጠሉኛል በጣም ። እኔንጃ ለምን እንደሆነ ምንም ያጠፋሁት ነገር የለም ። በእርግጥ ከስድሳ በላይ ባለትዳሮች አፋትቻለው።  አስሩን ጠቅሼ ሀያውን አማግጬ ሲሆን ወደ ሰላሳ የሚጠጉትን ግን ምንም አላረኳቸውም። ካማገጥኳቸው ሴቶች ውስጥ አንደኛዋ አለቃዬ ነች። ያው አለቃዬም አይደለች የስራ እድገትና የደምዝ ጭማሪ ለማግኘት አብሪያት እንዳድር ጠየቀቺኝ ። አኔም አይኔን አላሸውም። በእርግጥ አብረን ያደርን ለት ልብሷን ስታወልቅ ሁለቴ ሙጭልፍ ሙጭልፍ አድርጌ አሽቻለው (አይኔን) ማለት ነው።
   ምንም ሳላደርጋቸው ባላቸውን ከፈቱት ውስጥ ትዝ የምትለኝ የጓደኛዬ ሚስት ነች። ቆንጅዬ ነች ። ያየቺኝ የዛን እለት መሆኑን ያወኩት እኔን ብቻ እየመረጠች ስታጎርሰኝ ነው። የዛን እለት ጓደኛዬ ያየኝ አስተያየት አይረሳኝም " እስካሁን ካንተ ደብቄ አቆይቻት መቼም በሰርጌ እለት ላይ ጉድ አታደርገኝም" የሚል መልዕክት ያለው አስተያየት ነበር። ተረድቼዋለው ግን አናዶኛል። ለምንድን ነው ወንዶች አስኮብላይ እንደሆንኩ የሚያስቡት። ሊያውም የጓደኛዬን ሚስት በሰርጉ እለት ላይ ምን ላደርግ እችላለው? ። ሊያውም አንደኛው ሚዜ ሆኜ ። ለማንኛውም የዛን እለት ከሙሽራዋ ጋር ነው ያደርኩት። አዎ ገንገበት ነኝ ፤ ትንሽ ጠጥቼ ነበር ግን ሚዜዋን ይዤ የገባው ነበር የመሰለኝ ። ጠዋት ስነሳ ነው የጓደኛዬ ጉድ መሆኗን ያወኩት። ሊያውም ካላገባኸኝ ብላ እየጮኸች። "እማ ትላንት እኮ ነው ያገባሽው እስቲ መጀመሪያ የበላሽው ይስማማሽ ቢያንስ እሱም ሰልስቱን ይብላ" ብላት አልሰማም ብላ እሪታዋን አቀለጠችው። እንዴት እንደወጣው ባላቅም ወደቤቴ ልደርስ አከባቢ ነው በሙታንቲ እንደሆንኩ ያስተዋልኩት።
.
.
@mikiyas_feyisa

@wegoch
@wegoch
@paappii
------------    ሸበላው -------------

(እራሱ የራሱን ትዳር ካልጠበቀ እንዴት ነው እኔ እራሴን ከሰከረው እራሴ ምጠብቀው?)

part-2 ❵

       እንደሰማሁት ከሆነ ከዛን እለት ጀምሮ ጓደኛዬ ምን የሚያክ ፍልጥ ይዞ እገለዋለው እያለ ሲዝት ነበር ። በማታ ወደቤት ልገባ ስል (እንኳንም አልገባውና) ግንድ የሚያክል ዱላው እያወዛወዘ ሲጠብቀኝ ከሩቅ አይቼ ከአንድም ሶስቴ ተደብቄው ነው ያመለጥኩት ። እኔ ቆይ ግን ምን አደረኩ  ... እህ ... ሳላያት መጥታ የተለጠፈቺኝ እሷው ። ባለ ትዳሯ እሷው ፤ አሱ የራሱን ትዳር ካልጠበቀ እንዴት ነው እኔ እራሴን ከሰከረው እራሴ የምጠብቀው።
  እሱ ብቻ አይደለም ወንዶች ሲሰበሰቡ የኔን ስም ሳያነሱ እና ሳይረግሙኝ አይለያዩም። የሆነ ጊዜማ የሀሰት ምስክር ሰብስበው ፍርድ ቤት አቆሙኝ። ምን ብለው ሊከሱኝ እንደሆነ ባይገባኝም ዳሩ። አቃቤ ህጓ እንደነገረቺኝ ከሆነ ግን "ሴቶችን ያለ አግባብ በማማለል ፣ በማስኮብለል እና የወንዶችን የማግባት መብት በመጋፋት" ብለው ነው የከሰሱኝ። እሷን በወንድ አቃቤ ህግ ሳያስቀይሯት በፊት። በዚ ክስ የመቅጫ ህግ እንዳለ ባላውቅም የወንዶቹን ህብረት ሳይ እና የዳኛውን ሚስት አማግጬ እንደሆን ስጋት ሲገባኝ ግን ደንግጬ ነበር። ዳኛዋ ሴት እንደሆነች እስከማውቅ ድረስ ፤ ወንዶቹም ይህን ሲሰሙ ነው ክሱን ያነሱልኝ።
    እስከዛሬ የሚገርመኝ ነገር ግን እስካሁን ለእናቴ እና ለአባቴ መፋታት እኔን እንደ ምክንያት ሲያዩኝ ነው። ቆይ እኔ ምን አደረኩ?። ገና ስወለድ ጀምሮ እናቴ ከኔ መለየት አልቻለችም። አዳር ላይም እንኳን ። አባቴ በዚህ ባህሪዋ በጣም እንደሚበግን አውቃለው ። መሀላቸው ስተኛ አይወድም እሷ ደግሞ "ብርድ ይመታብኛል " እያለች መሀላቸው ሸጉጣ ከአባቴ ደም ከመሰለ ፊቱ ጋር ታጋፍጠኛለች። ከአስተያየቱ በጣም እንደሚጠላኝ ብቻ ሳይሆን እኔን ከቤት ለማስወጣት የሚያስፈልገውን ሁሉ እንደሚያደርግ አውቃለው። ብዙዎቹን ለሊት እናቴ እንቅልፍ ሲወስዳት ጠብቆ እኔን አልጋ ስር ይከተኝና አቅፏት ይተኛል። እኔም ከመልመዴ የተነሳ አልጋው እንኳን እንደዛ አይመቸኝም። ግን የአባቴን ግፍ ያየሁት አልጋ ስር እንኳን አስተኝቶኝ ጫማውን እንዳነሳ ፍቃደኛ አይደለም። ልክ ሊነጋ ሲል (ሰዓቷን ያቃታል) የተንተራስኩበትን ካልሲ  መንጭቆ ይወስድና አድርጎ እኔን አልጋው ላይ ለጥፎኝ ወደስራ ይወጣል። ከአባቴ ጋር እንደዚህ ሆነን 18 አመት ሞለኝ።  የዛኑ እለት የራሴ አልጋ አዘጋጅቶልኝ "ሂድ ውጣ" ሲለኝ አባቴ እናቴ "አንገቴ በቢላ" በማለቷ እንደተፋቱ ሰምቻለው።
.
.
By mikiyas_feyisa

@wegoch
@wegoch
@paappii
-------------  ሸበላው ---------

Part-3 ❵
(የመጨረሻ ክፍል)

       ይኸው እስካሁን ድረስ ውጪ ባደርኩ ቁጥር እናቴ አየጮኸችብኝ 25 አመት ሞላኝ። ከሴቶች ጋር እንደ feminist ተሟጋች ስሞላፈጥ ህይወቴን መግፋት እየመረረኝ ሳለ እንዳጋጣሚ ሆኖ በስራ ምክንያት ከአንድ የሀብታም ልጅ ጋር ተገጣጠምኩ። እስቲ የእኔንም የእናቴንም ህይወት ልቀይር ፣ በዛውም ወግ ማዕረግ ላሳያት ብዬ ከልጅቷ ጋር ተጠቃለልኩ። ልጅቷ ልታብድልኝ ትንሽ ነው የቀራት። የርሷ ፍቅር ደግሞ እጅ እጅ ይላል ። ሀገር ሰላም ብዬ ተኝቼ ለሊት ላይ ተሳስቼ አይኔን ብገልጥ ቁጭ ብላ እያፈጠጠቺብኝ ነው ማገኛት። ስንት ጊዜ አስደነገጠቺኝ። ሁሌ ቁርስ ምሳ እራት አብሪያት ካልበላው ወይ ተሳስቼ ውጪ ከበላው ቤቱን መቅደላ ነው ምታደርገው። እንዴት እንደሆነ ባላውቅም ቢሮ ሆኜ ትን ሲለኝ እራሱ ውሀ ይዛ አጠገቤ ቆማ አገኛታለው። ከሁሉም ከሁሉም ደግሞ የከበደኝ ሁሌ ማታ ማታ ፍቅር መስራት አለብን የምትለው ነገር ነው። እንዴ .. ልገለኝ ነው ሀሳቧ? .. ፆም አትል ፣ ወርሀዊ ግዴታ አትል .. እንደ ሸማኔ እንዝርት ስውረገረግ እንዳድር ነው የምትፈልገው። የመጨረሻ ያንገሸገሸኝ ግን መፀዳጃ ቤት ብቻህን አትገባም ያለቺኝ ቀን ነበር። ለካ ፍቅርም ሲበዛ እንደዚህ ያንገሸግሻል። አልፀልይም እንጂ ብፀልይ ኖሮ "አቤቱ የዚህችን ልጅ ፍቅር በልኩ አርግልኝ" የሚል ቃል አክልበት ነበር።
   እንደመታደል ሆኖ ከዚህ ሁሉ ሴቶች በኋላ አንድ የምትጠላኝ ሴት አገኘው። እናቷ (ማለትም አማቼ) ። ባየቺኝ ቁጥር ደሟ ይፈላል። ከልጇ ጋር ስንጋባ ደስተኛ አልነበረችም እንድንፋታም የማትፈነቅለው ድንጋይ የለም። አጠላሏን በጣም ነበር ምወድላት (ተጠልቼ አላቅማ) ። ታዲያ በስተመጨረሻ የልጅቷም ፍቅር ሲበረታ የእኔም ትዕግስት ተሟጦ ሲያልቅ የእናቷም ነገረኛነት ሲታከልበት የፍቺያችን ቀን ደረሰና ተፋታን። የፍቺያችንን እለት ለማክበር ብዙ አንዕስቶች ተገኝተው ነበር። የሚገርመው ነገር ግን ከእነሱ ውስጥ በጣም ደስተኛ የነበረችው አማቼ ነበረች። አትታዘቡኝና የዛን እለት ከእርሷ ጋር ነበር ያደርኩት። የሚያበሽቀው ነገር ግን  ለሊት ላይ ተሳስቼ አይኔን ስገልጥ እንደ ሞኝ እያፈጠጠቺብኝ ነበር። አይ እድሌ!

አይቀጥልም

@wegoch
@wegoch
@mikiyas_feyisa
ይፈተኑ ይሸለሙ፡

ለ12ኛ ክፍል 10 ተፈታኞች እስከ ማክሰኞ ድረስ የሚቆይ የ 1.3GB የዳታ ፓኬጅ ሽልማት አዘጋጅተናል።

የኢትዮጵያን ብሄራዊ ፈተና እንዲለማመዱ የሚረዳችሁ መተግበሪያችን ምታጠኑበትን መንገድ ይቀይራል። ብሄራዊ ፈተናዎችን በጊዜ ቆጣሪ ይዉሰዱ እና የደረሱበትን ደረጃ ይገምግሙ። ለእያንዳንዱ ምዕራፍ በእርስዎ ውጤቶች ላይ ትንታኔያዊ መረጃ(analytical data) እና ምክረ ሀሳችን ያግኙ።

ሽልማቱን ለማግኘት ይህን ሊንክ በመጫን መተግበሪያውን  ያውርዱ👇👇
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.elevans.eltest

በመቀጠል መተግበሪያውን ተጠቅመው ሁለት የትምህርት አይነት ከ 90 በላይ ውጤት ካመጡ screenshot በማደረግ በቴሌግራም  @useryise ይላኩ ሽልማቶትን ይውሰዱ።

ለተጨማሪ መረጃ ቻናላችንን የቀላቀሉ
https://www.tg-me.com/eltest1


መልካም እድል 🚀
የመኖር አካፋይ የመሞት ሲሶ መንገድ መሃል........
(ሜሪ ፈለቀ)

ዓይኖቼን በቦዛዛው ስከፍት መጀመሪያ ያየሁት የጨለማ በር የመሰለ ሁለት ቀዳዳ ነበር። ቀዳዳው ውስጥ ጥቋቁር ሰበዝ የመሰሉ ነገሮች እጅብ ብለው ነገር………  እይታዬ እየጠራ ሲመጣ ነው የሰው አፍንጫ መሆኑን ያወቅኩት። የፊቴ ደፍ ላይ ይሄን የሚያህል አፍንጫ ምን ያደርጋል? ምን ሊሆን ነው እንዲህ የተጠጋኝ?

«ሜላት ትሰሚኛለሽ? የምለው ከተሰማሽ ዓይኖችሽን በጣቴ አቅጣጫ አንቀሳቅሺልኝ» ባለአፍንጫው ሰውዬ ፊቱን አሸሽቶ የሌባ ጣቱን ከአንዱ አቅጣጫ ወደሌላው ያወዛውዘዋል። ትንፋሹ የሚሰማኝ ቅርበት ላይ ሆኜ ምን ያስጮኸዋል? በአይኖቼ ጣቱን እየተከተልኩ ከቆየሁ በኋላ ዙሪያ ገባዬን ቃኘሁ። ሀኪም ቤት አልጋ ላይ ነኝ። ባለአፍንጫው ሰውዬ እና አጠገቡ የቆመችው በዓይኖቿ የምትስቅ ወጣት ሴት ከደረቡት ነጭ ጋውን በመነሳት ዶክተር ወይ ነርስ እንደሆኑ ገመትኩ። ዓይኔን ከጣቱ ጋር ስላዳከርኩት ደስ ያላቸው ይመስላሉ። ሴቷ ሰውነቴ ላይ እየተርመሰመሰች እንደሆነ ይታወቀኛል ግን የገዛ ሰውነቴ እንደባዕድ ነገር ነው የሚሰማኝ። ሽባ ሆኜ ነው? ለምንድነው ሰውነቴን የማልሰማው? አፌ ላይ የነበረውን የሆነ ፕላስቲክ ነገር ፈልቅቃ አንዳች የሚያህል ቱቦ ከአፌ ውስጥ እየመዘዘች ስትስብ የት ድረስ ዘልቆ እንደነበር ያልገባኝ ቱቦ ጉሮሮዬን እየፋቀው ሲወጣ ይታወቀኛል።

«ዌልካም ባክ ሜላት። ዶክተር ሀይሌ እባላለሁ። በቀስታ ለማውራት ሞክሪ እስኪ……. ዝምብሎ አንድ ቃል! የመጣልሽን» አለኝ በማባበል።

«ምን ሆኜ ነው ሀኪም ቤት የመጣሁት?» አልኩኝ ስሰማው የራሴ ባልሆነ ቀሰስተኛ ድምፅ።  ፈገግ አለ የሆነ ግልግል አይነት ስሜት በቋጠረ ፊት…………. ሴቷ ከግርጌዬ ዞራ የእግሬን መሃል በጣቷ እየነካካች።

«ጣቴ ከተሰማሽ እግርሽን አንቀሳቅሺልኝ እስቲ» አለችኝ። ጣቴን ይሁን ያንቀሳቀስኩት ሙሉ እግሬን ብቻ አንቀሳቀስኩላት። ተያይተው ያልገባኝን መልዕክት በግንባራቸው ተለዋወጡ። በደመነፍስ እጄ ይሰራ እንደሆነ ለማረጋገጥ ሳይጠይቁኝ እጄን አዘዝኩት። ይታዘዛል። ሰውየው የሆነች አንድ ቂጥ በአግባቡ የማታስቀምጥ መቀመጫ ነገር ስቦ በግራ ጎኔ አልጋው አጠገብ ተቀመጠ።

«ወይዘሪት ሜላት? አደጋ ደርሶብሽ ነው ወደዚህ የመጣሽው። ከደረትሽ ዝቅ ብሎ ሁለት ቦታ በመሳሪያ ተመትተሽ ነው። (እሱ እያወራ በእጄ ለመዳበስ ሞከርኩ።) ስለተፈጠረው ነገር የምታስታውሺው ነገር አለ?» በጭንቅላቴ ንቅናቄ እንደማላስታውስ ነገርኩት።

«እድለኛ ነሽ ጥይቱ ጉበትሽን ለጨረፍታ ነው የሳተው። በቀዶ ጥገና ወቅት ትንሽ ኮምፕልኬሽን ተፈጥሮ የነበረ ቢሆንም ቀዶ ጥገናው ስኬታማ ነበር። ነገር ግን ወደአዕምሮሽ ክፍል የሚሄደው ኦክስጅን ተቋረጦ ስለነበር የተወሰነው የእዕምሮሽን ክፍል ጎድቶታል። የዚህ ጉዳት ዋነኛው አካል ሜሞሪ ሎስ ነው።» ያለው ይግባኝ አይግባኝ እንጃ ብቻ በጭንቅላቴ የማስታውሰውን ነገር መበርበር ጀመርኩ። እሱ ማብራራቱን ቀጥሏል። ሀባ ምናምኒት ነገር ጭንቅላቴ ጓዳ የለም። አይ በደንብ ስላልነቃሁ ይሆናል፣ ድንጋጤ ላይ ስለሆንኩ ይሆናል፣ የሰጡኝ ማደንዘዣ አለቀቀኝ ይሆናል፣ ......... ምንም ምክንያት ይሁን ብቻ የሆነ ነገር ይሆናል እንጂ ዜሮ ዘጭ የሆነ ጭንቅላትማ አይኖረኝም።

«ጥያቄ አለሽ?» አለኝ ግማሹን ያልሰማሁትን ማብራሪያ ሲጨርስ።
«ማነው የተኮሰብኝ? ምን አድርጌያቸው ነው?» የሚለው ጥያቄ ከአፌ ወጣ!
«አልታወቀም። ማንም ይሁን ማን የተኮሰብሽ ሰው ፖሊሶች እቦታው ከመድረሳቸው በፊት አምልጧል። ዝግጁ ስትሆኚ ፖሊሶች ቃልሽን ሊቀበሉ ይመጣሉ። ምናልባት አገግመሽ ወደቤት ስትገቢ ፍንጭ የሚሰጥሽ ነገር ታገኚ ይሆናል።» ሲለኝ ቤቴን ለማሰብ ሞከርኩ።

«ቤት አለኝ? ቤቴ የት ነው? የሚያውቀኝ ሰው፣ ሊጠይቀኝ የመጣ ሰው የለም?»

«የቤት ሰራተኛዋ ነኝ ያለች ሴት ጠዋት መጥታ ነበር። ስልክ አስቀምጣ ነው የሄደችው። ደውለን እንደነቃሽ እናሳውቃታለን። አደጋው በደረሰብሽ ሰዓት መኪናሽ ውስጥ የእጅ ቦርሳሽ ተገኝቷል። ፖሊሶች በኤግዝቢትነት ይዘውት ነው። መታወቂያሽ ላይ ያለው አድራሻ አሁንም ድረስ የምትጠቀሚበት ከሆነ አራዳ ክፍለከተማ ነው የሚለው።» አለኝ ከተቀመጠበት እየተነሳ። የቤት ሰራተኛ ያለኝ ሴት ነኝ? እናት እና አባቴስ? አግብቼ ወልጄ ይሆን? ስንት ዓመቴ ነው? በወና ጭንቅላቴ ውስጥ መዓት ጥያቄዎች ሚሞሪ በሌለው ሰፊ ቦታ ተንቀዠቀዡበት።

«መቼ ነው አደጋው የደረሰብኝ?» አልኩኝ
«ከ27 ሰዓታት በፊት»
«ካላስቸገርኩኝ ትንሽዬ መስታወት ነገር ማግኘት እችል ይሆን? ፊቴ ምን እንደሚመስል ማስታወስ አልቻልኩም።» ስለው ግር በተሰኘ ሁናቴ ሲያየኝ እስከዛ ሰዓት እጇን ቆላልፋ ቆማ የነበረችው ሴቷ ሀኪም ፈጠን ብላ

«ቆይ ቦርሳዬ ውስጥ አለ» ብላ ወጣች። እንኳን የዘነጉትን ፊት አንድ ዓይን አጉልታ የማታሳይ ትንሽዬ መስታወት ይዛ ተመለሰች። መስታወቷን ቀረብ ራቅ እያደረግሁ ራሴን ላይ ሞከርኩ። ፊቴን አውቀዋለሁ። የሆነ 'የት እንደማውቀው ጠፋኝ እንጂ ይሄን ሰው አውቀዋለሁ' እንደሚሉት የሌላ ሰው ፊት አይነት እውቂያ ፊቴን አውቀዋለሁ። የሆነ ነገሩ የተቀየረም ይመስለኛል። ብቻ አላውቅም ቢዚ የሚያደርገው ሚሞሪ የሌለው ወና ጭንቅላቴ የፈጠረብኝ ቅዥብር ይሆናል። ያበጠ ከሚመስለው ዓይኔ ውጪ የተሸበሸበ ቆዳ ፊቴ ላይ የለም። አሮጊት አይደለሁም ማለት ነው።

«እድሜዬን መታወቂያዬ ላይ አግኝታችሁታል?»
«የትውልድ ዘመን 1980 ነው የሚለው።» ካለ በኋላ ያለንበትን ጊዜ ላላስታውስ እንደምችል አውቆ መሰለኝ «አሁን 2015 ላይ ነን!» አለ ቀጥሎ።

«እስከመቼ ነው ምንም የማላስታውሰው?» አልኩት ባወራሁ ቁጥር ሲደክመኝ እየታወቀኝ።

«አዝናለሁ! በእዚህ ጊዜ ብሎ ማለት አይቻልም። ወደኖርማል የበፊት እንቅስቃሴሽ ስትመለሺ ትውስታሽ በራሱ ጊዜ ሊነቃ ይችላል። ምናልባት እስከወዲያኛውም ላይመለስ ይችላል። ምናልባት ደግሞ የተወሰነ ትውስታሽ ተመልሶ የተቀረው ላይመለስ ይችላል። ቁስልሽ ድኖ ስትበረቺ የተለያዩ ቴራፒዎች እንድትሞክሪ እናደርጋለን። አዝናለሁ። » አለኝ አዝኖ ሳይሆን ማለት ስላለበት የስራ ግዴታው በሚመስል አነጋገር። ከዛ በኋላ ለረዥም ሰዓታት ዝም አልኩ። ብቻዬን ከተኛሁበት ክፍል በህመም ሲቃ በሚያዜሙ ታካሚዎች በተከበበ ክፍል ስድስተኛ ሆኜ ተደመርኩ። ሁሉም ታካሚዎች አስታማሚ አላቸው። የሚያጎርስ፣ የሚያገላብጥ፣ ምጽ ምፅ የሚል፣ ሲከፋም የሚያለቅስ፣ ሲበረታ አምላኩን የሚለማመንለት ብቻ ከጎናቸው ሰው አለ። ቀኑ የማላውቀውን የሰዓት ዙረት ቁጥር ዞሮ ምሽት እስኪሆን እኔን ብሎ የመጣ ሰው የለም። አደጋ እንደደረሰብኝ አልሰሙ ይሆን? ብቻዬን ይሆን የምኖረው? እሺ ይሁን ያቺ የቤት ሰራተኛ ነኝ ያለችውስ የት ገባች? ደውላ ለቤተሰቤ ወይ ለጓደኞቼ አትናገርም? ከአንዱ ሀሳብ ወደሌላው ስዘል፣ አናቴ ላይ የተንጠለጠለው ጉሉኮስ ሲያልቅ ሲቀየር ፣ በየመሃሉ መድሃኒት በክንዴ ሲሰጡኝ፣ ሳንቀላፋ ስነቃ ምሽቶ ነግቶ አረፋፈዱ ላይ የቤት ሰራተኛዋ ነኝ ያለችው ሴት በዶክተሩ እየተመራች መጣች። በትንሽዬ ዘንቢል የያዘችውን የምግብ ሰሃን እና ፔርሙዝ እያወጣጣች ከልብ ባልሆነ አጠያየቅ

«እንዴት ኖት እትዬ? ተሻሎት?» አለችኝ ባመጣችው ኩባያ ከፔርሙዙ እየቀዳች። ዓይኔን እንኳን አላየችንም። ዓይኖቼን ሽሽቷ የሀፍረት፤ የማክበር ወይም የፍራቻ አይደለም። የጥላቻ እንጂ! ሞቼም ቢሆን ግድ እንደማይሰጣት ታስታውቃለች። ወይኔ አምላኬ ክፉ ሴት ነበርኩ ማለት ነው?
2024/09/22 07:31:20
Back to Top
HTML Embed Code: