Telegram Web Link
ለሳምንት ያህል ከታጎርኩበት ቤቴ በአስገዳጅ ሁኔታ ወጣሁ (ያው የቢዴና ነገር 😉)
ባለቤቴ ወደ ቢሮ እንደሚሄድ ባል ሳይሆን በደርግ ጊዜ ለግዳጅ እንደተጠራ ሰው ቆጥራኝ እንባዋ በአይኖቿ ግጥም ብሎ ሸኘችኝ።
እኔም ዝናሬን አደግድጌ.. .(ማነው...ይቅርታ! )... የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ዶክተር ይመስል ይፕእጅ ዋንቴን ገርግጄ ...ፊቴን በጨርቅ ተሸፍኜ ወጣሁ ።
"HONEY! አይዞን ጨከን በል !" ...የውዲቷ ባለቤቴ ድምፅ ከጀርባዬ ተከተለኝ ።
።።።።
መንገዱ ከወትሮው ተለይቶ ረጭ ብሏል.. .ሜኪሲኮ ሞልቷል አቦ ሌላ ታክሲ ፈልግ! ብለው በጩኸት የሚያስበረግጉኝ የታክሲ ረዳቶች እንደ እንቁላል ተንከባክበው ጋቢና ከተቱኝ። ... (የተጓዡ ቁጥር ከማነሱ የተነሳ ከ ሰላሳ ደቂቃዎች በላይ ታክሲ ውስጥ ቁጭ አልን)...ታክሲዋ በቆመችበት ስትራፖ ሊይዛት ደቂቃዎች ሲቀሯት😊 እንቅስቃሴ ጀመረች።
ሰው ገብቶ...ሞልቶ...ተትረፍርፎ ...ፈሶ ...የሞላ የማይመስላቸው ረዳቶች በጣት የሚቆጠር ሰው ብቻ ጭነው...ሌላ ተጓዥ ሲያናግራቸው ለስለስ ባለ ድምፅ "ሞላ ...በቂ ነው። አምላክ ይህችንም ይባርክልን 😜" ይላሉ ።
ዘና ብለን ተጓዝን። መንገዱ ብዙ ሰው አይታይበትም...ሰዎች ርቀታቸውን ጠብቀው ይንቀሳቀሳሉ.. .በፊት የነበረው ቸልተኝነት አሁን ላይ ቀንሷል.. ፊትህ ላይ ጨርክ ስትልደርግ "ታካብዳለህ እንዴ?" ይልህ የነበረ ከተሜ ሁላ"አካብዳለሁ !..." የሚል መፈክር በልቡ ተሸክሞ ይውተረተራል ።
አዲስ አበባዬ እንደ ለቅሶ ቤት ተፋዛለች...ዘራ ...በረሮ ...ድንች በኪሎ ...ጫማዋን በሰላሳ ምናምን የሚሉ ሰቅጣጭ ድምፆች አይሰሙም።
ይሄን እያስተዋልሁ በአንዱ ክፋይ ልቤ እፎይታ ቢሰማኝም ...ሸገርዬ ውጭ ስትዞር ተይዛ አባቷ በቀበቶ እንደገረፋት ህፃን ልጅ ኩርምት ብላ ሳያት ደግሞ አንጀቴ በሀዘኔታ ተላወሰብኝ ።
"ወንድም ካላስቸገርሁህ ሂሳብ ልቀበልህ? "
ዞር አልኩኝ...ረዳቱ ነው ...
የኔ ትሁት! ምፅ

@wegoch
@wegoch
@wegoch

#Michael Aschenaki
እንዴት ናችሁ? ስንቶቻችን ነን ስለ COVID-19 ስናስብ ስለ ጤና ባለሞያዎቻችን ያሰብነው?
በምን መልኩ እንደምንረዳቸው አስበናል? ያሰብኩትን እንካቹ...ከአንድ መረጃ እንደተረዳሁት የአፍ መሸፈኛ (Mask) በይበልጥ N-19 በመባል የሚታወቀው ለእኛ በቤት ውስጥ ለምንቀመጥ ሳይሆን Hospital area በይበልጥም ከበሽተኞች ጋር ንክኪ ያላቸውና በተለይም የአየር ግፊት (pressurized air) የሚጠቀሙ የህክምና መሣሪያዎች ያሉበት ክፍሎች ውስጥ ለሚሰሩ እንደሆነ ሰማሁ።ታዲያ የሁሉም ሀኪም ጥያቄ የሆነው የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል (mask) እና glove እጥረት በምን እና ምን ታጥቀን የመጣውን ጉድ እንዋጋ እንደሆነ ከብዙኃኑ አንደበት እንደሰማችሁ ጥርጥ ር የለኝም። ታድያ እንዴት እንደግፋቸው? ጥሩ ጥያቄ ነው።
አብዛኞቻችን COVID-19 ወደ ሀገር ቤት የመግባቱ ዜና ከተሰማ ጀምሮ እንዴት፣ መቼ እና የት መጠቀም እንዳለብን ሳናውቅ ቤታችን አከማችተነዋል ፣አሁን ግን ቢያንሰ ሆስፒታል ገብተን በሽታውን ባንዋጋም ሊዋጉልን የገቡትን ሀኪሞቻችንን ትርፍ የለን ካለን ላይ በመስጠት በቂ የመከላከያ መሣሪያ አስታጥቀን እንሸኛቸው ።።።በነገራችን ላይ አንድ ሃሳብ አለኝ !! ነገሮች እየከፉ ሲሄዱ የማይዘጉ የንግድ ቦታዎች ይኖራሉ ለምሳሌ እንደ supermarket,pharmacy and banks.
የእናንተን አስተያየት እና መነሳሳት አይተን እነዚህ ከላይ የጠቀስኩዋቸው ቦታዎች ማንኛውም ካለው ላይ የማካፈል እድሉ ያለው ኢትዮጲያዊ መከላከያዎቹን የሚያስቀምጥልንን ጊዜአዊ ማከማቻ ቦታ እንዲተባበሩን እኔና መሰል ሀሳብ ያለን በመነጋገር የምንጠይቅ ሙሆኑን ለመግለጽ እወዳለሁ ።
በቅን አዕምሮ ቅን ለሆነ ሐሳብ እየተባበርን አንድም የጤና ባለሞያ በመሳሪያ ጉድለት ላለማጣት እንትጋ።
ገንቢ ሀሳብ ልታጋሩን ምትፈልጉ በ0953932279 ይደውሉ።
Share በማድረግ ሀሳቡን እንጋራው። share on pages

@wegoch
@wegoch
......
ካለንበት ሁኔታ ጋር የተያያዙ አንዳንድ የእንግሊዝኛ ቃላትን ወደ አማርኛ ለመመለስ የሚደረጉ ጥረቶችን አያለሁ ፤ ባህላችን ለበሽታ እንግዳ ባለመሆኑ ላዳዲስ በሽታዎችና ልምዶች ካልሆነ በቀር አዲስ ቃል መፍጠር አያስፈልግም ፤ የነበረውን ባግባብ መጠቀም ይበጃል፤ ለምሳሌ እኒህን እንሆ! plague = ቸነፈር ( የቃሉ ምንጭ ነፈረ ነው፤ በሽታው ያደረበት ሰው ገላው ላይ የመንፈር ምልክት ስለሚያሳይ ፤ ከዚያ የወጣ ስም ነው፤ ) Epidemic= ወረርሽኝ፤ ኩዋራንቲን የሚለውን ዘመኑ ፈትቶ የለቀቀብንን ቃል አንዳንዶች ወሸባ( sic) ብለው ተርጉመው ሲጠቀሙበት አያለሁ ፤" ውሸባ መግባት " ባንድ ክፍል ውስጥ ተቀምጦ መታጠብና መታጠን ነው፤ ከምቾትና ከፈውስ ያለፈ አላማ የለውም ! በዛሬ አጠራር steam bath ከምንለው ጋር ይቀራረባል፤ በተለይ ቁርጥማትና ሽፍንፍን በሽታ የነበረባቸው ጌቶችና እመቤቶች ውሸባ የመግባት ልማድ ነበራቸው ፤ ምናልባት ከምስራቃውያን የተቀዳ ባህል ሳይሆን አይቀርም ፤ አንድ የተጠመቀ የቱርክ ጥበበኛ፤ የሸዋ ባላባት ለነበሩት ሳህለስላሴ ውሸባ እሚጠመቁበት ባኞ እንደገነባላቸው ተነግሮናል፤ ኩዋራንቲን የሚለውን ቃል አማርኛ ፍቺ “ቀሳ “ ነው፤ ኩዋራንቲን ላይ ያለ ሰው ደግሞ” ቀሳ ወጣ” ይባላል፤ ጥቂት ወዳጆቼ ቃሉን በትክክል ሲጠቀሙበት አይቼ ተደስቻለሁ ! ጉዳዩን ለማጥራት አለቃ ደስታ ተክለወልድ ከዛሬ አምሳ አመት በፊት ባሰናዱት መዝገበቃላቸው ላይ ያሰፈሩትን ልጥቀስ “ ቀሳ፤ ብቻ ለብቻነት ፤ፈረንጆች ካራንቴን ከሚሉት ጋር ይስማማል” ( መዝገበ ቃላት፤ ገፅ 1119) ይላል ወንድማችሁ፤ ኢጆሌ ማንኩሳ ከቀሳ!

[በእውቀቱ ስዩም]
@wegoch
@wegoch
ከዓመታት በፊት ብዙዎች ወረርሽኝ ይነሳል ብዙ የዓለም ህዝብ ያልቃል ተዘጋጁ እያሉ አባቶች ሲናገሩ ይሄ ተረት ነው የደብተራ ወሬ ጥንቆላ ወዘተ እያሉ ያለምጡና ያጣጥሉ ነበር:: ዛሬ የተባለው ደረሰ:: አሁንም ይህን ፈታኝ ጊዜ ለማለፍ አባቶች የሚመክሩትን ምክር እየናቀ የ"CDC" መድኃኒት ይናፍቃል:: ልንገርህ : ከተፈጥሮ ውጭ የሆነ መድኃኒት የለም:: የኛ ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ደግሞ ተፈጥሮን ጠንቅቀው የተረዱ ናቸው:: የአበውን ቃል እንስማ! #ምክራቸውን_እንተግብር_እንጠንቀቅ :: መፍትሔ እየፈለጉ ያሉ የመድኃኒት ሊቃውንቶቻችንን በፀሎት እናግዛቸው::

@wegoch
@wegoch
የጤና ባለሙያ ነኝ!
ብዙ ራዕይ አለኝ!!
ትውልድ ላይ አሻራ ማሳረፍ ፈልጋለሁ።
ለሀገሬ በሙያዬ ማበርከት የምፈልጋቸው ብዙ ሀሳቦች አሉኝ። እጅግ የምወዳትና ተስፋዋ እኔ ላይ ያለ እናት አለችኝ በብዙ መዋደድና ደስታ አብሬ ማሳለፍ የምፈልጋቸው ፤ ስኬታቸውን ማየት የሚያጓጓኝ እህትና ወንድም አሉኝ። ወልደን ከብደን ቀሪ እድሜአችንን በመተጋገዝ እንድንኖር ቃል የሰጠሁት ባል አለኝ፤ ይሄ ሁሉ የሚሳካው ግን ስኖር ነው። ያንተ ትንሽ የጎደለች ጥንቃቄ እኔን ህይወት ልታስከፍለኝ ትችላለች። አንተ ብትታመም አንተን ለመርዳት እምቢ እንደማልልህ አንተም ቀድመህ ለመጠንቀቅ እምቢ አትበለኝ።
በአንተ ጥንቃቄ ጉድለት ወረርሽኙ ቢስፋፋ ከምወዳቸውና ከሚወዱኝ ተለይቼ ፤ እራሴን አደጋ ላይ ጥዬ አንተን ለመርዳት ግዳጅ የምወጣበት ቀን ሳይመጣ እኔም አንተም እንጠንቀቅ።
#ህልም አለኝ! #በመጠንቀቅ እርዳኝ!
#HealthProfessionalsChallenge !

@wegoch
@wegoch
#hiwi_ye_enatua_lih
#ኑርልኝ_የኔ_ኮሮና
#ለፈገግታ

ሰሞኑን ኑሮ በጣም ተስማምቶኛል። ባንድ ሳምንት ብቻ ሳልወፍር አልቀረሁም። አኗኗሬ ተቀይሯል። ሆቴል ስሄድ እንደ ድሮው በኪሴ ብር አልይዝም። ሶፍት ነው የምይዘው ከዚያም የፈለኩትን ምግብ አዛለሁ። ስለ ዋጋው አልጨነቅም። ምግቤን አጣጥሜ ከበላሁ በኋላ ሶፍቴን አውጥቼ እንዳላበው ሰው ግንባሬን እጠርጋለሁ። በተለይ ቢሉ ሲመጣ ዝም ብሎ አስነጥስ አስነጥስ ይለኛል ሁኔታዬ ያጠራጠራት አስተናጋጅ መጥታ
«ጌታዬ ምግቡ አልተስማማዎትም እንዴ? ችግር አለ ?» ትለኛለች «ኸረ የለም። ግን ከባድ ትኩሳትና ሳል ይዞኛል» ብየ ኡሁ ኡሁ ማለት እጀምራለሁ። አስተናጋጇ …በድንጋጤ ሁለት ሜትር ለመራቅ ትሞክራለች። 8335 ስትደውል እንደተለመደው መስመር ተይዟል ይላታል። «እሙ ሶፍት የለም? ሶፍቴን ጨርሼ ላበቴን በብር እየጠረኩ ነው ለማንኛውም ግን ሂሳብ » ብዬ ገንዘብ እንዳለው ሰው ከኪሴ ስገባ «በፈጠረህ ተወው ! ሂሳብ በቤቱ ነው» እባላለሁ። ደሞ እኔ ያጨማለኩትን ገንዘብ ማን ይነካል ? ኮራ ጀነን እያልኩ ወደ ቀጣዩ ሆቴል

( አቢ ጌቱ )

@wegoch
@wegoch
"በአንድ ዲንጋይ ሁለት ወፍ "

ቅድም ጠዋት ቤተክርስቲያን ስሜ እየመጣው መንገድ ላይ ሁለት
ትንንሽ ልጆች እድሜያቸው ከ 8-10 ውስጥ ያሉ ናቸው እየተሰዳደቡ ነበር የደረስኩባቸው አንደኛው አጭር ከሲታ ነው አንደኛው ነቃ ያለ መካከለኛ ሰውነት አለው መካከለኛው ልጅ እያከረረ ሊመታው ሲጠጋ ከሲታው እኮ ነው

"ስማ እርቀትህን ጠብቅ ! ስትጠጋኝ አታፍርም ኧረ
በድብድብ ሰበብ ፍጥረህ አጅሬ ኮሮናን ልታስተላልፍ እ ከተማ ለከተማ አትዙር ሲባል እየተንቀጀቀጅክ ያመጣኸውን ልትሰጠኝ 😂 ብሎ ፍራቻ ከኮሮና ስጋት ጋር ቀላቅሎ ተናገረው አንድም ይመታኛል ብሎ በኮሮና አሳቦ መሸሹ ነው ሌላም ሰሞኑን እየሰማ ያለው ነገር ጥሩ አይደለም እና ከኮሮና እራሱን መጠበቁ ነው ያኛው ተናዶ
ሊመታው ሲጠጋ ፖሊስ አጠገባቸው ቁሞ ይህን ትዕይንት ይከታተል
ነበር እና አንተ ብሎ ሲጮኽበት ሁለቱም በተለያየ አቅጣጫ ተፍተለኩ
እኔ እና ፖሊሱ እርቀታችንን ጠብቀን አሽካካን አይገልፀውም ፍሪውን
ልጅ ግን አድንቄዋለሁ በአንድ ዲንጋይ ሁለት ወፍ ነው ^ ጣ ^ ያደረገው ስለተመቸኝ እናንተም ዘና እንድትሉ ብዬ
አጋራዋቹ ።
ሸጋ ድምቅምቅ ያለች ቅዳሜ ተመኘውላችሁ !!
በቃለአብ

@wegoch
@wegoch
አንጋፋው ደራሲና የሐሳብ ሰው ስብሐት ገብረእግዛብሔር ለሰላምታ አምስት ጣቱን ዘርግቶ አይጨብጥም ነበር :: ከዚያ ይልቅ አምስቱንም ጣቶቹን የራሱ እጅ መዳፉ ላይ ጨብጦ ( እጅን ለቦክስ እንደማዘጋጀት ) እድርጎ ነበር እጁን ለሰላምታ የሚዘረጋው ::

እናም ይህ ልማዱን ያስተዋለው ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ እንዲህ ብሎ ጠየቀው

" ስብሐት ለምድንነው ለሰላምታ ግዜ በእጅህ ሰው የማትጨብጠው !? "

የስብሐት መልስ አጭርና ቅኔን ያዘለ ነበር ...


" ሰው እኮ የሚሄደው በእግሩ ሳይሆን በእጁ ነው "


( በስብሐት ገለጻ ' መሄድ ' ማለት ' መሞት ' ማለት ይሆን !? )

////

( ውድ ወገኖቼ እጃችሁን ጠብቁ :: ከልክሉም !! )
@wegoch
@wegoch
@wegoch
የታጋቹ ማስታወሻ
( በእውቀቱ ስዩም)

ዛሬ በጠዋት ተነሳሁ፤ አጠር ያለ ስፖርት ሰራሁ፤ ሳሎኔን አስር ጊዜ ዞርኩት፤ ከዚያ ሳሎኑ በተራው ዞረብኝ፤ ብዙ አልቆየሁም፤ በቁሜ ወደቅሁ፤ ከመድርደርያ ላይ እንደወደቀ የመርቲ ጣሳ እየተንከባለልሁ አራት ደረጃ ወደ ታች ! እምገርም ነው! እስከዛሬ አይቸው የማላውቀው ቤዝመንት አገኘሁ! ቤቱ ባለ ቤዝመንት እንደሆነ አከራዩ ለምን አልነገሩኝም? ተመስጌን ነው! የወደቅሁት ከቤቴ ውጭ ቢሆን ኖሮ አልቆልኝ ነበር፤ ይሄማ አናቱ ላይ ፊጥ ብሎበታል ይሉና በአንቡላንስ አፋፍሰው ይወስዱኝ ነበር! ከዚያ መርምረው ሲያጡብኝ “ ለዛሬ ኔጌቲቭ ነህ ! ይሁን እንጂ ቅድም አቅፎ የጫነህ የአምቡላንሱ ሾፌር ፖዘቲቭ መሆኑን አሁን ስለደረስንበት ከሳምንት በሁዋላ ተመልስህ ና” ሊሉኝ ይችላሉ ፡፡ በማስቀጠል፤ መስኮቴ ላይ ሆኘ ፤በጦር ሜዳ መነፅር አካባቢውን ቃኘሁት ፤ ፖሊስ የለም! ምፅ! ፖሊስ ራሱ ከቤት መስራት ጀመረ ማለት ነው! ያማሪካ ፖሊስ ከቤት ሲሰራ አስቡት!
ዜጋ- “ሄሎ ኦፊሰር ?
ፖሊስ- አቤት”
ዜጋ - ሌባ የቤቴን ሰብሮ ገብቱዋል
ፖሊስ - you kidding me?” እየቀለድህ መሆን አለበት
ዜጋ- ከምሬ ነው
ፖሊስ “- እስቲ አገናኘኝ
ከቤቴ ወጣሁ እና ፓርኩ ላይ በሚገኘው አግዳሚ ወንበር ቁጭ አልኩ! የተራቡ ርግቦች እግሬ ስር ተሰበሰቡ! ትናንት ከቁርስ እስከ እራት ድረስ ቅርፁን እየቀያየርሁ የበላሁትን በሶ በተነንኩላቸው፤ በሶው ኤክስፓየርዴቱ እንዳለፈ ያወቅሁት ሁለቱ ወፎች እዛው አረፋ ደፍቀው ሲሞቱ ሳይ ነው! ወገን! እና ጊዜው ያለፈበት በሶ በልቼ ያልሞትኩት ሰውየ የተበየደ ፍሬሽ ጉንፋን ይገለኛል ተብሎ ይታሰባል? እሱስ ድብን አድርጎ ሊገለኝ ይችላል! ብቻ የምችለውን ያክል ተጠንቅቄና አስጠንቅቄ ከሞትኩም አይደብረኝም! በሳልና በሳቅ መሀል ለመሞት ዝግጁ ነኝ፤ ድንገት በየነ ናፈቀኝ! ልደውልለት ስልኬን ካነሳሁ በሁዋላ መልሼ ተውኩት ፤ በዩማ (በየነ ሲቆላመጥ ነው) ከሶስት ቀን በፊት ስልኩ ከእጁ አምልጦ ተፈጥፍጦበታል ፤ በዚህ ዘመን ስልክህ ከወደቀ እጢህ ወደቀ ማለት ነው፤ አንደ ወትሮው ፤ ሞባይል ቤት ሄደህ ማሳከም አትችልም፤ በዚህ ብቸኝነት ላይ ስልክ ጎድሎበት አስበው! አስቢው! ስልኩ እንዴት እንደ ተፈጠፈጠበት በሚቀጥለው ክፍል እፅፋለሁ በዚህ ሳቢያ የበየነ አመል ከፋ !
ባለፈው በሜሴንጀር ደወልኩለት
“ ምን ፈለግህ? “ ብሎ አንባረቀብኝ!
“ ትርፍ ማስክ ካለህ እንድትልክልኝ ፈልጌ ነበር” አልኩት፤
“ ያንተን ፊት ማስክ አይመክተውም! መለስተኛ ድንኩዋን ሰፍተህ ጣል ብታረግበት ይሻልሃል”
በጣም ነቀልኩ! ለእልኩ ብየ፤ ከንፁህ አንሶላና ከሽራ ጫማ ማሰርያ የተደቀለ ቆንጆ ማስክ ሰርቼ ለብሼ ሰልፊ ተነስቼ ላክሁለት፤ ፎቶየን አይቶት ሲያበቃ እንዲህ እሚል ምላሹን ሰደደልኝ፤
“ በስመአብ! አላሙዲ አጥሮ የዘነጋውን መሬት መስለሀል ! ደሞ ያምርብሃል! ወረርሽኙ ከተወገደ በሁዋላ እንኩዋ እንዳታወልቀው ፓርኩ ውስጥ ያለው አየር በጣም ንፁህ ነው! የመኪና ፈስ የኢንዱስትሪ ግሳት አልበከለውም! ይሄ ንፁህ አየር ተመልሼ ላላገኘው እችላለሁ ! ለምንም ለምንም ብየ አንድ ጀሪካን ቀድቼ ወደ ቤቴ ገባሁ!

@wegoch
@wegoch
@wegoch
የታጋቹ ማስታወሻ(2)
ካለፈው የቀጠለ
(በእውቀቱ ስዩም)
“hi ”
የሚል መልክት ስልኩ ውስጥ ገባ! ገረመው! ካራት ወር በፊት ለላከላት ሰላምታ ዛሬ ምላሽ መስጠቱዋ ነው ፤ መልስ ትሰጠኛለች ብሎ ጠብቆ አያውቅም ፤ ዝነኛ ተዋናይት እና በተምሳሌትነት የታወቀች ሴት ናት ፤ እንደሱ ላለ ሰው ጊዜ አልነበራትም ! ዛሬ ግን ምላሽ ሲያገኝ ገረመው! ግን ብዙ ሊገርመው አይገባም! ቀሳ ወጥታለች! ውሎዋ ከስልኩዋ ጋር ነው! ለከረሙ መልክቶች ሁሉ በፅሞና ምላሽ የምትሰጥበት ጊዜ አላት: :
“ እንዴት እንደምወድሽኮ” የሚል ምላሽ ሰደደላት!
“ አመሰግናለሁ”
“ የህይወት ዘመን ፎንቃየ ነሽ ብልሽ አታምኚኝም”
“ አይ እንግዲህ ! ”
“ የሚገርምሽ ከመደወልሽ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ፤ ፕሮፋይ ላይ ያለውን ፎቶሽን እያየሁ ስመታ ነበር፤”
“ ምንድነው እምትመታው?
“ ከበሮ!”
“ ተው ባክህ!”
“ ቁመናየን ይንሳኝ”
ትንሽ ሲያወጉ ከቁዩ በሁዋላ ፤
“ ያው እንደምታቂው ሞት ከቦናል ! እኔ ከፋም ለማም አብይም እስካሁን ኖርያለሁ ! ከዚህ በሁዋላ በህይወቴ የምጠይቀው አንድ ነገር ነው ! ጡትሽን! ጡትሽን ፎቶ አንስተሽ ላኪልኝ! “
የላከውን አይታ ከድፍረት ቆጥራ asshole (ብሽቅ!) ብላ ብሎክ ታረገኛለች ብሎ ጠብቆ ነበር፤
“ ምን ይጠቅምካል ?” የሚል መልስ ላከችለት!
“ ለመጨረሻ ጊዜ ደስ ብሎኝ ልሙት ! ከተረፍኩ ደግሞ ባንች ሰበብ እንደተረፍኩ እቆጥረዋለሁ”
“አልገባኝም”
“ እውነቱን ንገረኝ ካልሽኝ በጣም ደብሮኛል! መሞት ፈርቼ እንዳይመስልሽ! ህይወቴንና ዶላሬን ለሀገሬ ስቆጥብ የኖርኩ ሰው ነኝ! አገሬ ገብቼ፤ ህዳሴው ግድብን ከግብፅ ወረራ እየተከላከልኩ ከመሰዋት ያለፈ አላማ ኖሮኝ አያውቅም! በቻይና ቫይረስ ተነድፌ ፤ ባሜሪካ ሆስፒታል ውስጥ መሞቴን ግን ልቀበለው እማልችለው አሰቃቂ ቅዤት ነው ! ደሞኮ እንዳገራችን ወግ በፍትሃት በፀሎትና በሙሾ መሸኘት በስንት ጣሙ ! ከሞትኩ፤ ብድግ አድርገው የቄራ ፍሪጅ የተገጠመለት ሲኖትራክ ውስጥ ይወረውሩኛል !
“ ያ እንዳይሆን በተቻለኝ መጠን አጥብቄ እጠነቀቃለሁ! ቤት ውስጥ ሳይቀር ማስክ አደርጋለሁ፤ ፈረንጅ ስለማላምን ራሴ የሰራሁት ማስክ ነው ነው እማደርግ ! ማስኬ ባለሶስት ገበር ነው! የፊትና የሁዋላ ኪስ ሳይቀር አለው፤ በርግጥ፤ ወፍራምና ክብ ፊቴ ለማስክ አልተፈጠረም! ቅድም በመስታውት ራሴን ስመለከት አዘንሁ! … ዳንቴል የለበሰ ግማሽ ድፎ መስያለሁ ፤ ደሞ ስተኛ ራሱ አላወልቀውም! ታፍኜ እንዳልሞት ፀልይልኝ”
“ የኔ ጡት መላክ ከዚህ ሁሉ ጋር ያለው ግኑኝነት አልገባኝም” አለቺው፤
“ ጡትሽን ብትኪልኝ በድብርትና በትካዜ ሳቢያ ስራ ያቆሙት ህዋሳቴ ይነቃቃሉ፤ ተነቃቅተው የተፈጥሮ ሞርታርና ባዙቃ ያመርታሉ፤ ኮሮናን ለወሬ ነጋሪ ሳያስቀር ይደመስሱታል፤ በመጣበት እግሩ ይመልሱታል”
ፀጥ ብላ ቆየች፤
ከዚያ
…typing typing
ዝም!
ከዚያ
...uploading picture
ትንፋሹን ዋጥ አድርጎ ጠበቀ!
ወድያው የስልኩ ስክሪን ወገግ አለ!
ጡት!
ማተብ የሚያነጥር ጡት!
እንኩዋን በዳበሳ፤ በመብረቅ የማያቀል-ጡት
ጡት!
ስልኩ ከጣቶቹ ላይ አመለጠ! ከደረጃው እየነጠረ ወርዶ ከታች ባለው የድንጊያ ንጣፍ ላይ ተኛ ! ከጥቂት ሰከንዶች በፊት ስልክ የነበረው አሁን ዝሆን የረገጠው የሰርዲን ጣሳ መስሎ ተጋደመ ! በየነ በድንጋጤ ውሃ ሆኖ፤ የስልኩን ስክሪን ገልብጦ ተመለከተው ! እውር ሸረሪት ያደራው ድር መስሎ ነበር!

@wegoch
@wegoch
ጓደኛዬ ነው

እጮኛ አለችው የምትወደው አንድ ቀን ቤተሰቦቿ ጋር እራት ልትጋብዘው ቀጠረችው፣ ሰው ለ እራት ግብዣ ወደ ግሮሰሪ ሄዶ ውስኪ ወይ ወይን ይገዛል እሱ ግን የሄደው ወደ ፋርማሲ ነው።
ለፋርማሲስቱ ሰውዬ ምን ይለዋል የውልህ እጮኛዬ ዛሬ እራት ጋብዛኛለች ከእራት በኋላ መኝታ ቤቷን ላስጎብኝህ ማለቷ ስለማይቀር አጋጣሚውን ለመጠቀም ኮንደም መያዝ አለብኝ አንድ ኮንዶም ስጠኝ አለና ገዝቶ ሊወጣ በሩ ጋር ከደረሰ በኋላ ተመልሶ... በነገራችን ላይ ሌላ አንድ ብትጨምርልኝ ደስ ይለኛል እጮኛዬ በጣም ቆንጆ እህት አለቻት እና ሁሌ አይኗ እኔ ላይ ነው ስለዚህ የሷንም ክፍል የምጎበኝበት አጋጣሚ ሊፈጠር ይችላል። አሁንም ሊወጣ በሩ ጋር ከደረሰ በኋላ ጌታዬ መቼም አትታዘበኝ የእጮኛዬ እናት እንዴት ያለች ቆንጆና አማላይ መሰለችህ በዛ ላይ ብዙ ጊዜ አስተያየቷ ሌላ ፍላጎት እኔ ላይ እንዳላት የሚናገር ነው የሷንም መኝታ ቤት ልጎበኝ የምችልበት አጋጣሚ ስለሚኖር አንድ ኮንደም ጨምርልኝ። አለና በተቀጠረበት ሰአት የእራት ግብዣው ላይ ተገኘ ሁሉም ቤተሰቦች ለእራት ተቀምጠው ደረሰ በጠረጴዛው ላይም እጮኛው በቀኝ በኩል የእጮኛው እህት በግራ በኩል የእጮኛው እናት ከእህትየው ጎን እና አባትየው ፊት ለፊት ተቀምጠዋል። ድንገት ጀለሴ እኔ ጸሎት ጸልያለሁ ከምግቡ በፊት ብሎ አቀርቅሮ ጸሎት ጀመረ
ሲጸልይ
ሲጸልይ
30 ደቂቃ አለፈው ሁሉም ግራ ተጋቡ ጸሎቱ ረዘመባቸው እጮኛው ወደ ጆሮው ጠጋ ብላ የኔ ውድ ይህን ያህል ጸሎተኛ መሆንህን አላውቅም ነበር እኮ ስትለው አንገቱን ቀና ሳያረግ የኔ ውድ እኔም እኮ አባትሽ ፋርማሲስት መሆኑን አላውቅም ነበር። 😊

@wegoch
@wegoch
@paappii

#biniyam behaylu
★★ሞቴን ቀማኝ…… ክፍል 1

"እግዜር የሰውን ልጅ የፈጠረው እንዲያመሰግነው ነው።" ይለኝ ነበር አባቴ … …

እንዳመሰግነው አንድስ እንኳን ሽራፊ ምክኒያት ያልተወልኝ ፈጣሪ የምስጋና ነዶ በምን ሂሳብ ከኔ ይጠብቃል?

የምኖርበት አንዳችም ምክኒያት የለኝም። …… አንዳችም የመኖር እንጥፍጣፊ ፍላጎትም የለኝም። …… ራሴን ላጠፋ ነው። ቢሆንም ከመሞቴ በፊት ወደ ደጁ እየሄድኩ ነው…… ነፍሴን እንዲምራት ልማፀነው አይደለም…… በፍፁም……… ቢሻው አይማራት። ……

ለብዙ ዓመታት ሀዘኔ ሲበረታ እንዳደረግኩት "በእሳት ውስጥ አንተ መንገድ አለህ፣ በውሃም፣ በወጀብም መሃል…… መውጫዬን አበጅልኝ……" ምናምን እያልኩ የማይሰማ ፀሎት ላደርስም አይደለም ደጁ የምገሰግሰው። …… ዛሬ ደጁን ለመጨረሻ ጊዜ የምጎበኘው ለምስጋናም፣ ለወቀሳም፣ ለልመናም…… ከእግዜሩ ጋር በተያያዘ አይደለም። …… ለፅድቁም ይሁን ለኩነኔው ልሄድለት አይደል?…… እዛው ለማገኘው ለደቂቃዎች ልዩነት እሱን ፍለጋ አልመጣም። ……………

የምሰናበተው ዘመድ አዝማድ የለኝም። ብሞት የምጎዳው አንድም ወገን የለም። ……… ግን የምሰናበተው ትዝታ አለኝ። የልጅነት ፣ የወጣትነት፣ የፍቅር… …… ትዝታ!!!

እናም ደጁ ተሰየምኩ። የእግሩን ኮቴ እንደሚቆጥር ሰው እግሮቼን እየጎተትኩ ደብሯን ዞርኳት። …… አንዱን ዛፍ ተጠግቼ ሳሩ ላይ ተቀመጥኩኝ። ………

"ኪዳነምህረት ምን በደልኩሽ ግን?" አልኳት… …… ድሮ ህፃን እያለሁ እንደማስበው ኪዳነምህረት በሴትነቷ ካዘነችልኝ ብዬ ነው መሰለኝ። ……

ደብሩ ከፈጣሪ ጋር መገናኛዬ ብቻ አልነበረም። ያለፈው ዝፍዝፍ 23 አመታት ህይወቴ ገፆች ነው። …… አባቴ እዚሁ ቄስ ነበር። ……… ሰባኪ ብቻ አይደለም። …… ቅንነት ያልተለየው የሰበከውን ሊኖር የሚታገል የዋህም ነበር። …… ሽንብራ ቆርጥሞ የጮማ የሚያመሰግን፣ ውሃውን ጨልጦ የወይን የሚያወድስ…… ልግስና ከእጁ፤ ፈዋሽ ፈገግታ ከፊቱ የማይለየው ቸር ሰው።

… የደብሩ ሳሮች ላይ የልጅነቴ ዳናዎች አሉ። ……… በአባዬ ትከሻ ላይ እንኮኮ ተቀምጬ እየተንጠራራሁ የዳበስኳቸው ዛፎች ላይ አሻራዎቼ አሉ።

…… እማዬ ልታቆርበኝ መስቀልኛ ባሰረችልኝ ነጠላዬ ውስጥ የእንጀራ ድርቆሽ ደብቄ ስኮረሽም አጠገባችን የቆሙት ሽማግሌ
"ይህችን ልጅ አታቁርቧት እህል ብጤ እያላመጠች ነው።" ሲሏት ሰምቼ የተፋሁት የላመ ድርቆሽ ሳሩ ላይ ትዝታው አለ።

ብዙም ሳይርቅ ከደብሩ ጀርባ የኔታ ሀ ሁ ሂ… …… ሲያስቆጥሩኝ

"በይ ይህቺን በያት" ሲሉኝ

"የኔታ ሽንቴ መጣ" ስመልስ

"በይ ሰበብ አትወሽክቺ በያት" ሲሉኝ

"ቀ " ስለመልስ

"በይ አሁን ዝለቂና ሸንተሽ ነይ" ሲሉኝ

"አይ…… የኔታ አሁንማ ይተውት ቀሚሴ ላይ አመለጠኝ" መልሼላቸው የፊደል ቤቱ ማቲ ሁላ በሳቅ ያውካካብኝ… ……
የኔታ ባለቀ ጥርሳቸው እየሳቁ ለአባዬ የነገሩብኝ።……… የልጅነት ትዝታዬ…
ሳቃቸው ጆሮዬ ላይ አለ።

ፍቅረኛዬ የአብስራም እዚሁ ደብር የአባቶች እግር ስር ሲማር ፣ አባቴጋ አሹቅ ላደርስ ስመጣ ነው የማውቀው… … ሁለታችንም ቤተሰቦቻችንም ሆነ እኛ ከደብሩ ውጪ ህይወት የሌለን ነበርና መገናኛችን እዚሁ ነበር። ደጁ ተሰይመን ፍቅራችንን እንዲያበዛልን ስንቴ ለምነነዋል? ……… "ኪዳነምህረትዬ ቶሎ እንዲያገባኝ አድርጊው" ብዬ የአብዬ ሳይሰማ የለመንኳትስ እዚሁ አይደል? ……

በዚያ አዝግም የህይወት ጎዳናዬ የማውቃቸው፣ የምኖርላቸው፣ የሚኖሩልኝ… … ሶስት ሰወች ከዚህ ደብር ጋር የተዛመዱ ናቸው። ……… ከመሞቴ ደቂቃዎች በፊት ልሰናበት የመጣሁት የነሱን ትዝታ ነው። እነሱን ነው። ………

አባዬን በሞት ሳጣው ፈጣሪን አላማረርኩም። ……

ለቤተሰቦቼ ተስለው በስተርጅና የወለዱኝ ብቸኛ ልጃቸው ነኝ። …… ከአድባር አድባር እየዞሩ ተስለው ፍሬያቸውን ለማየት ሳይታደሉ አመታት ተቆጠሩ። በስተመጨረሻ አባዬ ኪዳነምህረት መጥቶ ተሳለ… …… ልጅ ከሰጠችው እስከእለተ ሞቱ በደብሯ ሊያገለግል…… ሰማችው…… ዘመድ አዝማዴን ሳይል በወጣትነቱ ወደተወው ድቁንና ተመልሶ ሲማር ኖረ…… ሲያስተምር አረጀ። …… ሞተ።…… የሱን ሞት ተከትላ እማዬ ታመመች። ………

በአመት ልዩነት እናቴን ሲደግማትም… … "ምናለ እኔንም ብትወስደኝ?" ብዬ መመረሬን ደጁ ተነጥፌ ማረኝ ብዬዋለሁ። ………

ብቸኝነቴን በፍቅር የሞላው የአብዬ እንዳመሰግነው ብዙ ምክንያቴ ነበር። …… በየእለቱ ተመስገንን አላጎደልኩም። …… አሁን ግን የምስጋና ቋቴ ደረቀ። ……… የአብስራ ከአለምና ከኔ ፍቅር የፈጣሪው ፍቅር አየለበት። ……… "እኔ ሚስት አላገባም። የመድሀኒያለም ባሪያ ሆኜ መኖርን መርጫለሁ።" ብሎኝ ከአለም ጋር ክዶኝ ሄደ።

ለምን ባለፀጋ አልሆንኩም? ለምንስ ከፊደል ቆጠራ የዘለለ አዋቂ አልሆንኩም? ብዬ ጠይቄ አላውቅም። ………"……… ካንተ ምንም አልፈልግም በምድርም ያለ ሀብት፣ በተራሮች ያሉ ከብቶች፣ በሰማይም ያለ ሁሉ የኔ ነው" ያለ ባለፀጋ ፈጣሪ መበልፀግን እንደማይፀየፍ ባውቅም……… አሹቅ እየቃሙ ማመስገንን ተምሬያለሁና ከእለት እንጀራዬ ያለፈ ልመና የለኝም።

"ጤና ስላደረገሽ አመስግኚው" ይለኝ ነበር አባዬ

ጤንነት ምንድነው? ብቸኝነት ከካንሰር የበለጠ እንደሚያቆስል አያውቅማ!!
ፍቅርን ማጣት ከደም ብዛት በላይ ነፍስን ከስጋ እንደሚነጥል አያውቅማ!!!

ለምን ልኑር? ለማን ልኑር? …… ኖሬ የምሞላው የትኛውን ሽንቁር ብዬ? ኖሬ የምፈታው የትኛውን ቋጠሮ ብዬ? ……… ……
…………
…………
የስንብት ቃል የለኝም እና እንባዬ ብቻ ይፈሳል። ሳግ የሰማሁ መስሎኝ ዞርኩ። …… …… አልተሳሳትኩም። አምስት ክንድ በሚያህል ርቀት አየሁት። …… በጉልበቶቹ መሬቱ ላይ ተንበርክኮ አይኖቹን ወደሰማይ ሰቅሎ እጆቹን ደረቱ ላይ ወደ ትከሻው መስቀለኛ አጣምሮ በአራት መንገድ የሚፈሰውን እንባውን ሳይ የሰማሁት ሲታገል ያመለጠውን ሳግ እንደሆነ ገባኝ። የእኔንም እንባ እንዲያነባልኝ የሰጠሁት ይመስል …… እንባዬ ደርቆ አየው ጀመር። ……
ከሚፈሰው እንባው ጋር የምስጋና ናዳውን ያዥጎደጉደው ጀመር። ……… እንባው ከሃዘንም ጥልቅ መሆኑ ያስታውቃል። ግራ ገባኝ። …… እያመሰገኑ ለቅሶ
……… ተጠግቼ ብጠይቀው በወደድኩ። …… ፈራሁት። "ማነሽ? ወደየት ታውቂኛለሽ? ምንስ አገባሽ?" ያለኝ እንደሆነስ? ብዬ ፈራሁ። እውነትስ ምን አገባኝ? የኔን ሀዘን ማን ይዘንልኝ ብዬ ነው በሞቴ ጫፍ ላይ የማላውቀው ሰው እንባ የሚገደኝ? ፊቴን መለስኩኝ። ………… ሀሳቤን መመለስ ግን አልቻልኩም። ……

………
………
……
አልጨረስንም……


@wegoch
@wegoch
@paappii

#meri_feleke
© ዳንኤል ክብረት
አንዳንድ ሰው አለ ከጣና 'ሚሰፋ
ካባይ የሚጋፋ
ከዋርካ 'ሚፋፋ።
አንዳንድ ሰው አለ ሁሉ የሚሰጠው
ሁሉ 'ሚጨብጠው
ሁሉ 'ሚያዳምጠው።
አንዳንድ ሰው አለ
አንድ ቦታ በቅሎ ለሁሉ 'ሚበቃ
ሁሉን የሚያነቃ
ሁሉን የሚያበቃ።
አንዳንድ ሰው አለ የሁሉ ማረፊያ
ሁሉን መደገፊያ
ሁሉን መታቀፊያ።
በዘመናት መሐል ድንገት ተከሥቶ
ለሰው ሁሉ ታይቶ
ያንን ዘመን ዋጅቶ
ፈጣሪ መኖሩን ለሰው አመልክቶ
ወደላይ የሚሄድ ከወደ ላይ መጥቶ።
አንዳንድ ሰው አለ.....
.................................................................
"አላህ በከንፈር የሚሸነገል ሞኝ አይደለም! አላህ
የሚፈልገው ልብን ነው።"
(*ተቀዳሚ ሙፍቲህ፥ ዑመር ኢድሪስ)
===============
ክቡር ተቀዳሚ ሙፍቲህ የጸሎት መርኀ ግብር ላይ እንዲህ አሉ፡-
"ዱአ አድርግ ስትሉኝ 'አይኾንም' ያልዃችሁ
ወንድሞቻችን የኦርቶዶክስ አባቶች ሲጸልዩ
ኹላችንም ቁመን 'አሚን!' ብለናል። ያ ጸሎት በቂ
ነው ብዬ እንጂ ለሌላ አይደለም፤" አሉ ።
እኒህ ታላቅ አባት ንግግራቸውን ቀጠሉና፣ እንዲህ አሉ፥
"ከተመለስን ከልባችን እንመለስ! አላህ በምላስ
የሚሸኝ ጌታ አይደለም፤ አላህ በከንፈር የሚሸነገል
ሞኝ አይደለም።
አላህ የሚፈልገው ልብን ነው፤ አላህን
ምን እንዳስቀየምነው ታውቁታላችኹና
አልነግራችሁም።
አላህ የምንሠራውን ያውቃል!
ዛሬ ወንዱም ሴቱም ተጨመላልቋል፤ ወንዱ - 'ሴት
ካልሆንኹ' አለ፤ ሴቱም- 'ወንድ ካልሆንኹ' አለ፤
በቤተ ክርስቲያንም በመስጂድም ፈጣሪን በደልነው፤
በዘር ተከፋፍለን አስቀየምነው፤ በዚህም ምክንያት
'እናንተ አገልጋዮቼ አይደላችሁም ጠላቶቼ ናችሁ' ብሎ
ከቤተ ክርስቲያንም ከመስጂድም አስወጣን።
አላህ ቸር ነው!
በአንዴ ማጥፋት ይችል ነበር። ነገር ግን
አላደረገውም። በነፋስ አስፈራራን፤ በጎርፍ አስፈራራን፤
እኛ ግን አልተመለስንም።
አኹን ደግሞ መድኃኒት የሌለው በሽታ አመጣብን፤
አኹንም ከዚህ የባሰ መከራ እንዳይመጣብን
ከልባችን ኾነን ወደ አላህ እንመለስ!
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ፣ ኹሉም ፖለቲከኛ ከልብ
ኾኖ ሕዝብ ይስማ! የሃይማኖት አባቶችም ከልብ
አላህን እናገልግለው!
ሕዝብም የአባቶችን ምክር ይስማ! እርስ በርሳችንም
እንተዛዘን እንተሳሰብ! እንደዚህ የኾነ እንደኾነ አላህ
ይቅር ይለናል። መከራውንም ይመልስልናል።
ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር የሚሰደብበት፤ የሃይማኖት
አባቶች የሚሰደቡበት ወቅት ላይ ነው ያለነው። እኛ
ብንሞኛኝ አላህ አይሞኝም፤ ስለዚህ ከታች ጀምሮ ሥነ
ሥርዓት ይያዝ!
ወላጆች ልጆቻቸውን ሥነ ሥርዓት ያስይዙ!
መምህራንም ተማሪዎችን ሥነ ሥርዓት ያስይዙ!
መሪዎቻችንም ሕዝብ የሚላችሁን ስሙ!
እኛም እርስ በርሳችን እንተዛዘን!
የዚህ ወረርሽ መድኃኒቱ ይገኛል፤ ኢንሻ አላህ!!
ትንሹም ትልቁም 'ከእኔ በላይ የለም' የሚለው ኹሉ
ተንቀጥቅጧል። አላህ ከልባችን የምንመለስ
ያድርገን!" አሉ።
ለእኚህ ትልቅ ሰው አምላክ ረጅም ዕድሜ ከጤና ጋር ይስጥልን።
@wegoch
@wegoch
@wegoch
★★★ ሞቴን ቀማኝ ★★★
(ክፍል ሁለት)

አጠገቡ ተጠግቼ ተቀመጥኩ። …… አቅፌ ባባብለው በወደድኩ…… ስርቅታው እንዳይሰማ ሲያፍነው የፊቱ ገፅታ ልብን የሚሰብር ማሳዘን አለው፣ የአንጀቱ መንሰፍሰፍ ሆድ ያላውሳል…… የኔ መጠጋት ከለቅሶውም ከምስጋናውም አላናጠበውም። …… የጎረቤት ጨቅላ በአደራ እንደምትጠብቅ ባልቴት… የማደርገው ጠፍቶኝ… ዶፍ ለቅሶውን እስኪያባራ ፈዝዤ እጠብቀው ጀመር…… እንባዬ ደርቋል። ለመሞት ማቀዴ በጭላንጭል ትዝ ይለኛል……

ፊቱን በእጆቹ ደባብሶ ከተንበረከከበት ተነሳ…… እንዳልተንሰቀሰቀ…… እንዳልተከፋ… … ምንም እንዳልሆነ ሁሉ ሄደ…… ፈዝዤ ለቅሶውን እንደቅዳሴ እንዳልሰማሁት ከአይኔ ርቆ ሄደ… … ለምንድነበር የጠበቅኩት? …… ለምን እንደጠበቅኩት፣ ምን እንደምለው… ሳይገባኝ ተከተልኩት…… ማን ብዬ እንደምጠራው ስላልገባኝ በሩጫ ደረስኩበት። እጁን ስይዘው ከእንቅልፉ እንደባነነ ሰው ደነገጠ።……

የሞት ጫፍ ላይ የነበረ የህይወት ጎዳናዬን ችላ ብዬ ለምን በሰው ጎዳና እንደምቧችር አላወቅኩትም። ራሴን በማላውቀው ሰው ጎዳና ላይ ዶልኩት። …… ከብዙ ውትወታ በኋላ ውሃ ቅመስ ብዬ ከደብሩ ብዙ በማይርቅ ከደሳሳ መጠለያዬ ደጅ ሳሩ ላይ አሳረፍኩት። …… ውሃ አልሰጠሁትም። …… አይን አይኑን እያየሁ የሚያወራውን እሰማዋለሁ…… ከአፉ የሚወጡት ፊደላት ሳይሆኑ እንቁዎች መሰሉኝ። አፍሼ ብንቆጠቆጥባቸው ተመኘሁ።……

"ህይወት ሁሌም ስለሰዎች አይደለችም። …… ስለራስሽም ናት። ሁሌ ደግሞ ስለራስሽ አይደለችም ስለሌሎችም ናት" ያለኝ ከሀሁ ቆጠራ ላላለፈ የእውቀቴ ጥግ ከበደብኝ……

ከሶስት ሳምንት በፊት:— እንደምትሰበር ጌጥ የሚሳሳላት ሚስቱን ከወንድሙ ጋር ስትባልግ እንደያዛት ነገረኝ። …… በበነጋው ሁለት ልጆቻቸውን ይዛ ከወንድሙ ጋር ከቤት ከመውጣቷ በመኪና አደጋ ሁሉም ህይወታቸው ማለፉን ተረዳ። …… በአንድ ቀን ሁለት ልጆቹን፣ ብቸኛ ወንድሙን እና ሚስቱን የቀበረ እለት ራሱን ስቶ ሀኪም ቤት ገባ…… በህይወት ለመኖር የቀሩት ቀናት ብቻ መሆናቸው እንደተነገረው እያወራኝ በብዙ ሀዘን የታጀለ ፀዳል ፈገግታ ብልጭ አደረገልኝ። ……

"ጌታን የምታመሰግነው ምንም ስላሳጣህ ነው?" አልኩት ሰቆቃው ከሰቆቃዬ ሲነፃፀር ገለባ እየሆነብኝ

"በህይወት ብኖር በቁም ከመሞት የዘለለ እጣ ፈንታ አይኖረኝም ነበር። ሚስቴና ልጆቼን አጥቼ መኖር እንደሚከብደኝ የሚያውቅ አምላክ ሲጠራኝ ከማመስገን ውጪ ምን ይወጣኛል? ለንሰሃ ጊዜ ለሰጠኝ ፈጣሪ ከምስጋና ውጪ ምን ኩነኔ ከአፌ ይወጣል?" አለኝ አቀርቅሮ ለስላሳ እጆቹን እየፈተለ…… የምጠይቀውን አላውቀውም… … ቢመልስልኝ ግን ደስ ይለኛል። …… ምን እንደምመልስለት እንጃ… … ቢጠይቀኝ ግን ደስ ይለኛል።

"ራሴን ላጠፋ ነበር።" አልኩት። ባልገባኝ ምክንያት ስሜቴ ሁሉ የሚገባው ፍፁም መሰለኝ። …… አልደነገጠም። አይኖቹን አጥብቦ ሲያየኝ ሁሉንም ነገርኩት።

"ማንም ሰው ወደአንቺ ህይወት ጎዳና ሲቀላቀል ወይም አንቺ በሌሎች የመኖር ጎዳና ስትቀላቀዪ አንዲት ነገር ይቀበልሻል ወይ ይሰጥሻል። …… በመኖር ዘመንሽ ሁሉ አብሮሽ የሚኖር አንቺ ብቻ ነሽ። አየሽ ህይወት ስለሌሎች የሚሆነው ባጣሻቸው ሰወች መኖርሽ ሲመሰቃቀል ነው። ስለራስሽ የሚሆነው አሁንም ህይወትሽን የሚቀላቀሉ ሌሎች ኮከቦች እንዳሉ ስታውቂና መኖር ስትቀጥዪ ነው። ባለቀ ዘመኔ አንቺ እንደመጣሽው……" ሊለኝ የፈለገው በትክክል እኔ እንደገባኝ መሆኑን እንጃ… … የተናገራቸው ቃላት እውቀትን ይሁን መንፈስን የሰጡኝ እንጃ… … ከተራራ አናት ላይ ብቅ እንዳለች የጠዋት ፀሃይ የሩቅ ተስፋ ስሜት ሰጠኝ። ……

"ስንት ዓመት ይሆንሻል?" አለኝ

"ያለፈው ህዳር ሚካኤል 23 ዓመቴ"

"ካንቺ በሁለት ዓመት የሚበልጥ በልጅነቴ የወለድኩት ልጅ አለኝ። ምን እንደሚመስል አላውቅም። አይቼው አላውቅም። …… " የዳመነ አይኑን ለማስታገስ ዝም አለ።

በልጅነቱ እቤታቸው ከምትሰራ ሰራተኛ መውለዱን እና ቤተሰቦቹ ስላባረሯት ወደ ገጠር መምጣቷን ነገረኝ። …… በሞቱ አፋፍ ላይ አጠያይቆ ከኛ ደብር በእግር የ8 ሰዓት መንገድ ርቀት ላይ ያለ ገጠራማ ቦታ ከእናቱጋ መኖሩን ስለሰማ ሊያየው መምጣቱን ነገረኝ።

"ይቅርታ እንዲያደርግልኝ አልጠብቅም። …… አይኑን ብቻ አይቼው መሄድ ነው የምፈልገው።" አለኝ ፀፀቱ አይኖቹ ውስጥ እየጮኸ… …

ሲሄድ እያየሁት ልቡ ብቻ ሳይሆን እግሩም የተሰበረ፣ ከትከሻው የጎበጠ መሰለኝ። …… ብቻዬን ቀረሁ። …… ወደቅድሙ ብቸኝነቴ ግን መመለስ አልቻልኩም…… ላለቅስ ብፈልግ እንባ ራቀኝ፣ መከፋት ብፈልግም ልቤ በማያውቀው ተስፋ ይፈነጥዛል…… ምን አገኘሁ? ኸረ ምንስ ቢለኝ ነው? ለዚያውም ካለኝ ከግማሽ በላዩ ነው ያልገባኝ…… ከየት የመጣ ተስፋ ውስጤ ፈነጠቀ? …… የተናገረኝ ቃላት ህይወት ነበረው። ዓረፍተ ነገሩ ግልፅ ባይልልኝም…… ነፍስ እፍ ሲልበት ለነፍሴ መነቃቃት ሰጥቷታል። ……

በማላውቀው የደስታና የተስፋ ውሽንፍር እየተላጋሁ በሶስተኛው ቀን አመሻሽ ላይ የቆርቆሮ በሬ ተንኳኳች። …… ያ እየሞተ ለኔ መኖር የሆነኝ ሰው ነበር። …… አብሮት ያለው ወጣት ልጁ መሆኑን መናገር አይጠበቅበትም። …… የጠፋ ወዳጁን እንዳገኘ ሰው ተጠምጥሜ አቀፍኳቸው። …… የተሰማኝ እንደዛ ነው……የቅርብ ሰወች……

"እሰይ! እንኳን ኪዳነምህረት ተለመነችህ! …… " አልኩት ገብተው ከመደቡ እንዳረፉ
ከደቂቃዎች በኋላ መለወጡ ታየኝ

"ምነው? አመመህ እንዴ?" አልኩት

"ትንሽ አወን!"

አባዬ እያለ እንግዳ እቤታችን ሲያርፍ እንደሚደረገው ለእግራቸው የወዘፍኩትን ውሃ አቅርቤ ከብዙ እንቢታቸው በኋላ እግራቸውን ተራ በተራ አጠብኳቸው። ……

እኔና አባቱ ስንጫወት ምንም ቃል ሳይተነፍስ የቆየው ያሬድ
"ለምን ጠዋት አብረሽን አዲሳባ አትሄጂም?" አለኝ

"እውይ…… ምን አደርግ ብዬ?" መለስኩለት

"እኔ ከብቶቹን ጥዬ ብዙ መሰንበት ስለማልችል ታስታምሚዋለሽ።" አለ

አባቱ ላይ ያለውን ቅሬታ እንዳላነሳ ገባኝ። ከሁለት ሳምንት ያልበለጠ ጊዜ ለሚቆይ አባቱ ከብቶቹን ማስቀደሙ ቅያሜውን ማሳያ መሰለኝ።

"ትንሽ ራስሽን የምትደግፊበት ነገር ላደርግልሽ አስቢያለሁ።" አለኝ አባቱ… … ያሬድ ደስ አላለውም። የተከፋ ፊት አሳየ…… ……
……
……
አልጨረስንም……
………

@wegoch
@wegoch
@paappii

#meri_feleke
Forwarded from Mykey (Mikiyas Liyew Mykey)
''ጥንቃቄ ይጠብቅሃል  ÷
ማስተዋልም ይጋርድሃል''
ምሳሌ 2÷11

@Mykeyonthestreet
ተቃራኒ ለሚወዱ አንዳንድ ኢትዮጵያውያን መውጣት ያለበት ዐዋጅ።
#daniel_kibret

ስማ ስማ፣ ያልሰማህ ተሰማማ። ከዛሬ ጀምሮ ማንም ቤቱ እንዳይቀመጥ። የቻለ ከከተማ ውጭ፣ ያልቻለ ከተማ ውስጥ፣ ያልቻለም ሠፈር ውስጥ ያውደልድል። ቤቱ የተገኘ የ3 ወር ደመወዙን ይቀጣል። መብራትና ውኃም ይቋረጥበታል። እጅ መታጠብ ለአንድ ዓመት ተከልክሏል። እጁን ሲታጠብ፣ ሲፈትግ የተገኘ የታጠበበትን ውኃ እንዲጠጣው ይደረጋል። በሳሙና ከታጠበ ደግሞ ዐረፋ የሞላ በርሜል ውስጥ ውሎ ያድራል። ሰው ሁሉ ከቻለ ተዛዝሎ፣ ካልቻለ አንዱ ሌላውን አንጠልጥሎ፣ ያም ካልሆነ ተቃቅፎ ፣ ከባሰም ተደጋግፎ እንዲሄድ። ሲራራቅ የተገኘ ከፍ ብሎ አንገቱን ዝቅ ብሎ ባቱን ይቆረጣል። ይህ ዐዋጅ ቢወጣ፣ ሕዝቡ በተቃራኒው ስለሚሠራ የተፈለገው ለውጥ ይመጣ ነበር።

@wegoch
@wegoch
ቁጥርና ቅዳሜ
(ልዑል ሀይሌ)

20 ሰው ጭኖ ሲሄድ የነበረ ታክሲ እሷ ከታክሲው ስትወርድ እንዴት በቅፅበት ባዶ ሆነብኝ?... እንዴት አንድ ሴት በአንዴ 20 ሰው ልትሆንብኝ ቻለች? ...ተመለሺ ልላት ስልኳ ሊሆን የሚችል ቁጥር ለመገመት በማሰላሰል ላይ ሳለሁ "ሂሳብ!" ሲለኝ "ስንት ነው?" ስለው "4 ከ 50" ሲለኝ ስልኳ 45 ቤት ሊሆን እንደሚችል ጠረጠርኩ "መልስ ስጠኝ!" አልኩት ረዳቱን "ምን አስሬ ትጨቀጭቀኛለህ?" ሲለኝ 0945 ቀጣዩ ቁጥሯ 10 ሊሆን እንደሚችል ለመጠርጠር አፍታም አልፈጀብኝ 094510...ቀጣዮቹን የልጅቷ ቁጥር ለመገመት የሆነ አንዳች ጭቅጭቅ መፍጠር ስለነበረብኝ "ምንድነው ታክሲው መስኮት የለውም? ታግተን ነው? ወይስ ተሳፍረን?" ስል የሌሎቹም ተሳፋሪዎች ድጋፍ ተሰጠኝ..."አዎ ይከፈት!..ታፍነን እንሙት እንዴ?.." እኔ ይህን የጭቅጭቅ ርዕስ ያመጣሁት ቁጥር ቢጠሩና የልጅቷን ስልክ ለመገመት ቢረዳኝ ብዬ እንጂ ውጪ የሚጥለውን በረዶ የቀላቀለ ዝናብ እያየሁ...እንኳን መስኮቱ ይከፈት ልል ይቅርና ታክሲው ለያንዳንዱ ተሳፋሪ ብርድ ልብስ ቢኖረው
የመጀመሪያው ለባሽ እኔ እሆን ነበር የምሆነው... በመሃል አጠገቤ ያለው ተሳፋሪ ወደኔ ዞር ብሎ "ይገርምሃል ይሄ መንገድ ከተሰራ 15 ቀን አይሞላውም ግን ጎርፉ እንዴት እንዳጥለቀለቀው ተመልከት" ሲለኝ "ጥሩ ነዋ!" ብዬው የልጅቷን ቁጥር ግምቴን ገፋሁበት ……15 ቀን ካልሞላው 14 መሆን አለበት 09451014... ይሄን ቁጥር ፅፌ ካጠገቤ ያወራኝን ተሳፋሪ ተመልሼ ሳየው "ያመዋል እንዴ?!" በሚመስል የግርምት እይታ ሲያየኝ አስተዋልኩ...እኔም ምላሼን 'ጠረባ' በሚባል ክፉ እይታ አንስቼ አፈረጥኩት... ቀጣዩን የቁጥር ግምት የማገኝበትን ሰበብ እየፈለግኩኝ ባለበት ሰዓት ከኋላ ወንበር የነበረችው ተሳፋሪ "ወራጅ አለ!..አንዴ አሳልፈኝ" ስትል ጆሮዬ ውስጥ ጥልቅ አለ። እኔም የተሰጠቺኝን ቁጥር የስልኬ 'በተን' (ቁጥር መምቻ) ላይ ፅፌ ሰፊውን ህዝብ
ለማሳተፍ በሚል በግድ ባስከፈትኩት መስኮት ጆሮዬን አስግጌ ማዳመጥ በጀመርኩበት ቅፅበት አንድ ኬት እንደመጣ ያላወቅኩት አንድ ንፋስ የሆነ ቀማኛ ስልኬን ከነግምቴ እና ከገመትኳቸው ቁጥሮች ጋር ይዞት ሲጠፋ። ከገባሁበት የሐሳብ ባህር ወጥቼ ታክሲውን ባንድ እግሩ ባቆመውም የሄደው ላይመለስ በወጣበት ቀረ መውረጃችንም ሲደርስ ስወርድ ሌላኛው ረዳት እኛ ወደነበርንበት
ታክሲ መጥቶ ሹፌሩን "አንተ ቆይ በምን ፍጥነት ነው በዚህ ሰዓት ሁለት ቢያጆ ደርሰህ የመጣኸው?.." ሲለው 4 የልጅቷ ቀሪው ቁጥር 4 ሊሆን እንደሚችል ጠረጠርኩ ግን ደሞ ዜሮም ሊሆን እንደሚችል እየጠረጠርኩ በ 0 እና በ 4
መካከል እንደሆንኩ ወደቤቴ ተራመድኩ። ሁለቱንም ስልኮች የመሞከር ዕድሉ ቢኖረኝም ስልኬ በሌላ ሰው እጅ ትገኛለች። ስልክ ሲይዙ ቁጥሩ እየጠፋ ቁጥሩን አገኘሁ ሲሉ ስልኩ እየጠፋ ራስ ላይ ያለው ነገር እየተቀያየረ ቁጭት እየፈጠረ ህይወትን ያስቀጠላል። ...ግን ያቺ ልጅ እንዴት 20 ሰው ልትሆንብኝ ቻለች?...እስቲ በቀጣዩ ቅዳሜ ልፈልጋት ...ምርጡን ቅዳሜ
ተመኘሁላችሁ!!..

@wegoch
@wegoch
@wegoch
2024/09/25 07:22:59
Back to Top
HTML Embed Code: