Telegram Web Link
ስብሰባው
=======+++++=====
አንዱ አብዮታዊ ፈጣሪን ከሰይጣን ጋር ሊያስታርቅ እቅድ አዘጋጅርና ሽማግሌዎችን መርጦ ውይይት እያደረገ ነው። (መግለጫ መስጠቱ ነው)

ሰብሳቢው:- የስብሰባው አጀንዳ ሰይጣንን ከፈጣሪ ጋር እንዴት ማስታረቅ አለበን የሚል ነው። እንደምታውቁት የሰይጣንን ቦታ መላእኩ ከተረከበ በሁዋላ ሰይጣን እንቅልፉን አልተኛም። እንደምታዩት እርስ በእርሳችን ጠብ ጭቅጭቅ ንትርክ ሁኗል ተግባራችን። ስለዚህ እሄን ነገር ሰላም ለማድረግ ሰይጣን ከፈጣሪ ጋር መታረቅ አለበት። በዚህ ጉዳይ ሰፊ ማብራሪያ እንድትሰጡበት እንፈልጋለን '' ሲል ስልኩን መነካካት ጀመረ
*
ሽማግሌ ተመረጠ (ሉካን ቡዱን መሆኑ ነው)
****
ሰይጣን እንቅልፉን ተኝቶ አገኙት
***
ሠው:- ሰይጣን የተመቸህ ትመስላለህ ?
ሰይጣን:- እድሜ ለናንተ ሰላሜን ሰጣችሁኛል ዛሬ ምን እግር ጣላችሁ?
ሠው:- ፈቃድህ ከሆነ አንተን ከእግዚአብሄር ጋር ለማስታረቅ አስበን ነበር
ሰይጣን:- አይሆንም! አትልፉ! ከናንተ ጋር የታረቅኩት ይበቃል። እሱ እኮ ካንዴ ሁለት ጊዜ ከስልጣኔ አስለቅቆኛል። እንደምታዩኝ እንቅልፋም አድርጎኛል። ስሜን ስልጣኔን እና ማንነቴን ቀይሮ አንኮታኩቶኛል። እና እንዴት እታረቀዋለሁ?
ሰው:- ደግሞ ከየትኛው ስራህ ነው ያስለቀቀህ ?ለሚካኤል ከሰጠው ውጭ
ሰይጣን:-አዎ! ለዘመናት ብቻየን ስፈነጥዝበት የነበረውን ዝሙትና ተንኮል ንትርክና ጭቅጭቅ ውሸትንና ክህደት አብዝቶ ለሚሰራው ሰው ለተባለው ፍጡር አሳልፎ ሰጠብኝ። ሰዎች በኔ ስም እየተጠሩ እርስ በእርሳቸው ይናከሳሉ። እኔ ለመስራት የሚከብደኝን ሀጢያት እናንተ እንደጽድቅ ትቆጥሩታላችሁ። እኔ እስካሁን ሰው አልገደልኩም። እናንተ ግን ሰውን አርዳችሁ ትበሉ ጀመር: እኔ እስካሁን ከሴት ጋር አልተኛሁም ለናንተ ግን ዝሙት ስራችሁ ነው ሰዎች ሰይጣን አሳሳተኝ ትሉኛላችሁ እኔ ግን እንኳን ላሳስታቸው በስራችሁ ታስቀኑኛላችሁ:: እግዚያብሔር እኔን የሚያሸንፈኝ በቃሉ ነው: ሀይሉ ያንበረክከኛል: እኔ የእግዚብሄርን ወንበር የደፈርኩት በወቅቱ ከኔ በላይ ስላልነበር ነው: እናንተ ግን ካለቃችሁ በላይ አለቃ መሆን ያምራቹሃል: ከባሏ በላይ የቤቱ አባወራ ትሆናላችሁ: ከሻጩ በላይ ትርፋማ ትሆናላችሁ: ካረ'ባው ይልቅ ወተት ትጠግባላችሁ: ጠዋት ማታ ስርቆት: ሌት ተቀን ዝሙት: ሰርክ ጭቅጭቅ: ነጋ ጠባ ጦርነትና ሀሜት!! ያንተ ያለህ እኔ የማላውቀውን ሀጢያት ሁሉ አሳያችሁኝ እኮ
ሠው:-እና አንተ እያሳሳትክን እኮ ነው
ሰይጣን:- በቀር ለሀሜትማ ምን ተይዞላቹሀል: እኔ አመንዝሩ ስረቁ ቀሙ ተጋደሉ ተጣሉ ብዬ አማልኳቹህ? ካለአመነዘራችሁ ብልታቹሁን እቆርጣለሁ: ካልሰረቃችሁ እጃችሁን እሰብራለሁ አልኳቹሁ? ካላማቹህና ካልገደላችሁ ዘራችሁን አጠፈዋለሁ አልኳቹሁ? በነጻ የሚጠጣውን ጸበል ንቃችሁ በብር የሚገዛውን አልኮል የምትጋቱ እናንተ! ሚስታችሁን ህጻን እያስታቀፋቹህ የምትሴስኑ እናንተ! የሠራን የምትቀሙ የሠረቀን የምትሸልሙ: የቀማን ጀግና የገደለን ታጋይ እያላችሁ ስላንድነት የታገለውን በፍላጻ የምትቆራርጡ እናንተ! ከከቅቤ ላይ ሙዝ ከእንጀራ ላይ ሳጋቱራ ጨምራቹሁ የምትሸጡ እናንተ! ከወደቀ እንጨት ላይ ምሳር ይበዛበታል ሁኖ ነገሩ ጥፋታችሁን ሁሉ በኔ ስታላኩ የማይሰቀጥጣቹሁ እናንተ! ደግሞ እኔሳ ስልጣኔን ተቀምቼ አርፌ በተኛሁ ምን አረኩ?
ሰው:- እሹ አሁን ወቄስታውን ተወውና የመጣነው ከእግዚአብሄር ጋር ልናስታርቅህ ነው
ሰይጣን:- (ከትከት ብሎ ስቆ) 'ልናስታርቅህ ነው' ነው ያላችሁ? ትገርማላቹሁ እኮ! መታረቅን እንጂ ማስታረቅንማ ትወዱት የለ! አስታራቂማ እንደምድር አሽዋ በዝቶ የለ! የጠፋው እኮ የሚታረቀው ነው! ከሲኦል ይልቅ የሚያስፈራችሁ እኮ ይቅርታ ነው! ይቅርታ የሚባለው ነገር አይደለም ተግባሩ ስሙ በራሱ ያንቀጠቅጣቹሃል! እናንተ እርስ በእርሳቹሁ ሳትታረቁ ሰው ለማስታረቅ ጉባዬ ትጠራላችሁ! በስድብና በቂም ልባቹህ ተሞልቶ ጸጉራቹህ ስለሸበተ ብቻ እናስታርቅ ትላላችሁ! ለመሆኑ እስካሁን ከወጡት ሙዚቃ ስለእርቅ የተዘፈነ አለ? ''እያየህ በለው: ገዳይ ና ገዳይ ና: ነይ ማታ ማታ: ልቡን ልበለው: አምጡት ምንሽሬን' የሚለውን ከመሥማት ውጭ ስለእርቅ አድምጠን እናውቃለን? ሰው ከገዛ ህሊናው ጋር ተጣልቶ ያስታራቂ ያለህ እያለ እየጮህ እናንተ ከዚህ እኔን ትረብሻላቹሁ' ሲል ትቷቸው ሄደ
=====
ሰብሳቢው:- ሰይጣንን አገኛችኛችሁት?
ሽማግሎች:- አግኝተነው ነበር ነገር ግን ሰድቦ ሰደደን
ሰብሳቢው:- ባይሆን አስማት አላስተማራችሁም?
''እየተከዘ''

Mezin worku

@wegoch
@wegoch
@gebriel_19
ወረፋ
(ቡሩክ ካሳሁን)
አናሳዝንም ወይ? ኸረረረረረ
የቴዲ ዘፈን መስሎህ ለእስክታ እንዳትነሳ ጎበዝ፡፡ ይህ የታክሲ ናፋቂ ህዝብ ድምፅ ነው፡፡ ከሜክሲኮ ወደ አራት ኪሎ ለማቅናት ያኔ ሙሴ እስራኤሎችን ለማሻገር ያሰለፈውን ሰልፍ የሚያስንቅ የታክሲ ሰልፍ ተሰልፈናል፡፡ እንደው አንድ አፈ ቀላጤ ሰው ‹እስኪ 1፣ 1 ብር› እያለ እዛ የተሰለፈውን እየዞረ ቢጠይቅ እኔ ነኝ ያለ ቅጥቅጥ ይገዛ ነበር ዳሩ ምን ያደርጋል ቀጥቃጣ ብቻ ነው የተሰበሰበው፡፡ በዚህ ጊዜ ወዳጄ፣ ተራ አስከባሪ ማወቅ አንድ ትልቅ ባለስልጣን ከማወቅ አይተናነስም፡፡ ተራ አስከባሪዎችም ጊዜ የሰጠው ቅል ሆነው የተከበሩ ሰዎችን ሚስት ስልጣንን ተገን በማድረግ (ያቺም ስልጣን ሆና ማለት ነው) ፆታዊ ጥቅም ያሳድዳሉ፡፡ እኔ በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ተራ አስከባሪ መሆን ተመኘው፤ ቀናሁ ;-) ፡፡ እዛ የተሰለፈች ሴት ሁላ ለተራ አስከባሪው ደማቅ ፈገግታ ታሳያለች፡፡ እነ እገሌ እቺን ሰልፍ እየቀረፁ ይመስለኛል በእንትን ፊልም ሰልፍ አገር ሲጨናነቅ ምናምን የሚሉት፡፡
ሰልፉ ላይ ከታክሲ ይልቅ አዳዲስና አሮጌ ሃሳቦች ቶሎ ቶሎ ይመጣሉ፡፡ ‹ቃና ይዘጋ› እያለ አንዱ ከጓደኛው ጋር ሲያወራ ከፊቱ የተሰለፈ ባለ ጥቁር ፂም ጎረምሳ ‹ ምነው ብራዘር የከሰረ የፊልም ደራሲ ወይ ዳይሬክትር ዘመድ አለክ እንዴ ወይስ ኢ.ቢ.ኤስ ነው ምትሰራው?› ብሎ መለሰለት
‹ ትውሉዱ እኮ እየተበላሸ ነው ባህሉንና ወጉን እየረሳ ነው ቃና መዘጋት አለበት›
‹እና ታዲያ ትውልዱን ወደ ባህሉና ወጉ ምትመልሰው ምርጫ ቢስ በማድረግ ነው እንዴ? ከቻልክ አስተምረህና አስረድተህ እንጂ አስገድደህ ነው እንዴ? ደግሞስ የትኛው የሀገራችን ፊልም ነው ለወጉና ለባህሉ ሲጨነቅ ያየከው? እቺ እቺ ማምታቻ ናት፤ ባይሆን ሰዉ ፊልምን ማጣጣምና መገምገም ጀመረ፤ ገበያችንን ዘጋው በለኝ በግልፅ› እየተባባሉ ሲጨቃጨቁ ‹ኸረ ወንድሞቼ የቸገረን ታክሲ ነው የኢትዮጲያ የፊልም ደረጃ አንድ እርምጃ ወደፊት ወደኋላ ስትሉ አደናቅፎት እንዳይከሰከስ› በመሀል ሰላላ ድምጽ ተወረወረች፤
በድንገት ተራ አስከባሪው አንዲት ቆንጆ ልጅ ስልክ ቁጥሯን ተቀብሎ መጀመሪያ ሰልፍ ሲወስዳት
‹በህግ አምላክ ወደሰልፏ መልሳት› አሉ ከራሰ በራነት የተረፈ ፀጉራቸው ፈትል ጥጥ የመሰለ ሰውዬ
ተራ አስከባሪው ልጅቱን እርጉዝ ናት ብሎ ደረቀ… ሰውየውም ‹እንኳን እርግዝና የረባ ቦርጭ የላትም ባይሆን ዛሬ ማታ ታረግዝ እንደሆን ንገረን› አሉ የፊታቸው ደምስር እንደተገተረ
ተራ አስከባሪውም ‹ዉ…ይ ፋዘርዬ በሁለትሺ አስርም እንደዚ ኖት አልተለወጡም?¡› አፌዘ
‹ኸረ ፌደራል ይዘዝብህ ሌላ ምንም አልልህም› ሰልፈኛው ፈገግ አለ፡፡
.
አንድ ነጭ ሚኒባስ ያንን ሰልፈኛ ሊታደግ ከተፍ አለ፡፡ ዲጄው(ወያላው) ሰልፉን ሲያይ ልቡን አወረው፤ ‹አምስት አምስት ብር ይመቻችኋል?› አለ ወደሰልፈኛው እየተመለከተ
‹አዎ ይመቸናል 2ብር ከሀያ አምስት መልስ ምትሰጠን ከሆነ› የሆኑ አሮጊት መለሱለት
‹ጥሩ ይቀልዳሉ ቃና ላይ እርሶ ኖት እንዴ 300ሺ ብር ያሸነፉት? 5 ብር ሚመቸው ይግባ› ወያላው ተናዶ መለሰላቸው
ሰልፉ ያታከተው ተሯሩጦ ገባ፡፡ እንደምንም እኔም ትርፍ ሆኜ ገባሁ፡፡ ወያላው ሂሳብ መሰብሰብ ሲጀምር ታምረኛ እኮ ነው የኢትዮጵያ ህዝብ ባዘቦቱ ዝርዝር የለኝም ሚል ሁላ ሁለት ከሰባ አምስት፣ ሁለት ከሰባ አምስት እያወጣ ለወያላው ይሰጥ ጀመር፡፡ ጦርነት ተነሳ አምስት ብር ነው ያልኳቹ አምስት ብር አምጡ ወያላው ደነፋ፡፡ ‹እሺ አትልማ› ሚል ድምጽ ከኋላ ተወረወረ ዞር ብዬ ሳይ ቅድም 2ብር ከሀያ አምስት ከመለስክልን ያሉት ሴትዮ ናቸው፡፡
‹ካፌ እና ሬስቶራንት ገብተህ 5 ብርና 10 ብር ቲፕ ሰጥተህ ትወጣለህ ታክሲ ላይ ግን ለ25 ሳንቲም መልስ ትንገበገባለህ› ወያለው በንዴት መለሰ ከኋላ ኪሱም ‹እቺም እንጀራ ሆና ሚጥሚጣ በዛባት› የሚል ጥቅስ አውጥቶ መኪናው ላይ አንጠለጠለ፡፡ 4ኪሎ ደርሰን መውረድ ስንጀምር የቅድሟ ሴትዮ ‹ይኸውልህ ልጄ ጊዜ ሰጠኝ ተብሎ አይመፃደቅም እራሱ ጊዜ ይጥላልና› ሲሉት ለወያላው
‹ኸረ ስራዬን ልስራበት በሰላም ግቢ› ለትልቋ ሴትዮ መለሰላቸው
አውርዶን እንደጨረሰም መኪናውን ወደ ሜክሲኮ አዙሮ ሱዳን ድረስ በሚሰማ ‹ሜክሲኮ ሜክሲኮ› እያለ ጮኸ ግን ተሳፋሪ አላገኘም፡፡


ጥቅምት 2010 ዓ.ም
ቡሩክ ካሳሁን ቴሌግራም ቻናል ለመቀላቀል
@burukassahunc


@wegoch
@wegoch
//ሕይወት እንደ ተረት/// (1)
(ጆኒ ፀጋዬ)

..ህይወት እንደ እመት ቦቦሊና አሮጊት ናት፡፡ ግን ሁሌም ጨርቅ
አስጥሎ ለማሣበድ የሚያስችል አንዳች መላ አታጣም.. ይላል፤
አሌክሲስ ዞርባ፤ የካዛንታኪስ ገፀ ባህርይ፡፡ ከእነዚህ መላዎችዋ
አንዱ አዲስ ዓመት ነው፡፡ ህይወት ሰርክ አዲስ ናት፡፡ በመደጋገሟ
ኃይሏ አይቀንስም፡፡ ሁሌም ልባችንን እንደ ሰቀለች ታኖረናለች፡፡
ህይወት ሰማያዊ፤ በደም በሥጋ ትተርከናለች፡፡ የሰው ልጅ መሬታዊ፤
በቃል፣ በዜማ፣ በቀለም፣ በኪነ ቅርፅ ኮርጆ ይተርካታል፡፡ አንዳንዴም
በትረካው እርሷን ለማስናቅ ይዳዳናል፡፡
ህይወት፤ ሁሌም ቢነበቡ ከማይሰለቹ ..ታላላቅ ተረቶች.. አንዷ ነች፡፡
እንደ ኤዞፕ ወይም እንደ ተራኪዋ - የአላዲን? ልጃገረድ ባለ ጥበበኛ
እጅ ስትገባ፤ ተደጋግማ ብትነገርም ሁሌም እንደ አዲስ የምንሰማት
ውብ ..ተረት.. ናት፡፡ ህይወትን ..ተረት.. በሚያደርግ ጠቢብ ትርጉም
ታገኛለች፡፡ ትከብራለች፡፡ህይወት ..ተረት.. ከመሆንዋ በፊት ትርጉም
የለሽ ናት - ዝብርቅርቅ የዕብድ ቃል፡፡ ወደ ትረካ ስትመጣ ትርጉም
ትይዛለች፡፡ የሰው ልጅ ህይወት ከእንስሳት እድር ወጥቶ ማዕረግ
የሚያገኘው በትረካ ነው፡፡ በቦታ እና በጊዜ ተበታትኖ የነበረ ህይወት
ትርጉም በሚሰጥ መንገድ ትቀመራለች፡፡ ምርጥ ታሪክ ትሆናለች፡፡
ህንዳዊቷ የልቦለድ ደራሲ አሩንዳቲ ሮይ በአንድ ጽሁፍዋ ..ምርጥ
ታሪክ ማለት፤ ትናንት ሰምተናቸው፤ ዛሬም ደግመን ለመስማት
የምንፈልጋቸው ናቸው፡፡ ከየትኛውም የታሪኩ አንጓ ብትጀምሩ
ይመቻችኋል፡፡ ምርጥ ታሪኮች፤ ያልታሰበ ወይም ያልተገመተ -
አስደንጋጭ? አጨራረስ የመከተል ጮሌነት ያላቸው አይደሉም፡፡
እንደምንኖርበት ቤት ወይም እንደ ወዳጅ ጠረን የምታውቃቸው እንጂ
አዲስ አይደሉም፡፡
..ታሪኩ እንዴት እንደሚጠናቀቅ እናውቃለን፡፡ ግን እንደማናውቅ
ዓይነት ጆሮአችንን ከፍተን፤ ልባችንን ሰጥተን ታሪኩን ለመስማት
ዝግጁ ነን፡፡ ነገሩ፤ አንድ ቀን እንደምንሞት ስናውቅ፤ ሞት የሌለብን
ሆነን መኖር ነው፡፡ በታላላቅ ታሪኮች ውስጥ ማን እንደሚሞት፣ ማን
እንደሚኖር፣ ማን አፍቃሪውን እንደሚያገኝ ማን እንደማያገኝ
ታውቃላችሁ፡፡ ግን እንደገና እንዲነገራችሁ፤ እንደገና እንድታውቁት
ትፈልጋላችሁ፡፡ ይኸ ነው የምርጥ ታሪኮች ምትሃት፣ አስማት፣
እንቆቀቅልሽ.. ትላለች ሮይ፡፡
ህይወትም እንዲህ ዓይነት ድንቅ ታሪክ ናት፡፡ በአዲስ ዓመት መንፈስ
አሙቃ፤ በተደጋጋሚ ባየነው አስማቷ አፍዝዛ፤ አሮጌውን አዲስ አድርጋ
አሳይታ ልታሰክረን ትመጣለች፡፡ ሽርጉድ ታሰኘናለች፡፡
በህፃናቱ አንደበት፤ እያዜመች ከፊታችን ቆማለች፡፡ ይኸው አሁን፤
..አበባዬ ሆይ ለምለም፤ ባልንጀሮቼ ለምለም.. እያለች፤ እንደ ገና
ልባችንን ታሞቀው ይዛለች፡፡
..ህይወት እንደ እመት ቦቦሊና አሮጊት ብትሆንም፤ ... ሺህ ጊዜ
ከአልጋ ተጋድማ፤ ሺህ ጊዜ በድንጋሌ -ሀሳብ - እይታ? ከመደብዋ
ትነሳለች፡፡ ዳግም ትወለዳለች፡፡ ምትሃት ነች፡፡
..ለምን? እንዴት?.. የሚል ጥያቄ በማንሳት ለዛዋን፣ ጣዕሟን
ማበላሸት ትርፍ የለውም፡፡ ይልቅስ በተስፋ ዝናብ ያጨለጨለ ምናብ
አድላ፤ በአዲስ ዓመት እንደገና ልትሞሽረን ከመጣችው ምትሃተኛ
ህይወት ጋር መተቃቀፍ ነው፡፡ እኔ ስታቀፋት እንዲህ ሆነ፤
..ከየት መጣሁ ሳልል ከአንድ ሥፍራ ዱብ አልኩ፡፡ በመደነቅ ፈንታ
የሚያሳስበኝ ክፉ ነፋስ ዱብ አለ፡፡ ህይወት ድግግሞሽ መሆኗን
የሚያስታውሱኝ ትናንሽ ቀበሮዎችን ታሰሩ፡፡ የፅጌ መስኩን
የሚያማስኑ ቀበሮዎች ታገሱ፡፡ በዘላለም ሜዳ እና ሰማይ፤ በጊዜ
ማሣ ዳር ከበቀለች እና ፍፃሜው በማይታወቅ ህዋ ውስጥ ብቻዋን
ካለች ዛፍ ላይ ከሰራችው ጎጆ እንቁላልዋን ታቅፋ የተቀመጠች ርግብ
ሆኜ ነቃሁ፡፡ እኔው ራሴ፤ ከእንቆቅልሽ እንቁላል ውስጥ ክሌውን ሰብሬ
እንደ ጫጩት ብቅ ስል እራሴን አየሁት፡፡
ይኸን ተዓምር ለማወደስ ፈለግኩት፡፡ ከሰው ዕድሜ የላቀ ዕድሜ
ያለው ..ቋንቋ.. ለመንኩ፡፡ የተወሰደ ልሳኔ እንዲመለስልኝ ጠየቅኩ፡፡
በኃያሉ አምላክ ዙፋን ፊት ቆሜ ውዳሴውን እንዳወርድ ይፈቀድልኝ
ዘንድ ማለድሁ፡፡ የተዘረጋ እጄ ሳይታጠፍ፤ ምስጋና የተራበ ልቤ
ዘመረ፡፡ የምስጢር ወይንጠጅ ተጎነጨሁ፡፡ ታላቁን ውቂያኖስ
የምትውጥ አንዲት ጠብታ ከፍቅር ላምፋ ላይ እንደ ጤዛ ጠብ ስትል
አየሁ፡፡
ድንገት ደግሞ፤ ኃይለኛ ውሽንፍር የቀላቀለ የጥርጣሬ ወጀብ ተነሳ፡፡
ወጀቡም የነፋስ ድንኳኔን ካስማ ሊነቅለው ታገለ፡፡ ያኔ ልቤ በእምነት
ጀልባ ተሳፈረች፡፡ ይኸው በፍቅር አምባ፤ የተስፋ ድንኳን ተተክሏል፡፡
ልቤም ወደዚያው እየቀዘፈች ስትሄድ ተመለከትኳት፡፡ አራቱም
አቅጣጫዎች ጠቀሱኝ፡፡ አዜብ፣ መስእ፣ ሊባ እና ባህር ጠሩኝ፡፡ የዕፀ
በለስ ማዕበል ተነሳ፡፡ ጀልባዋን ሊውጣት አገሳ፡፡ የትዕቢት ባህር
ፎገላ፡፡
ያኔ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፈረሱን እየጋለበ መጣ፡፡ በእረፍት ውሃ ዳርቻ
ለመቀመጥ የሚታገለውን መሬታዊ ፍጡር ሊታደገው በነጩ ፈረሱ
ጋለበ፡፡ የትዕቢት ባህር ፀጥ አለች፡፡ የእፀ በለስ እሣት ተዳፈነች፡፡
የክፋት አፍንጫ ተፎነነች፡፡ ጀንበር ገብታ እስክትወጣ ድረስ ህይወት
ሰልፍ ሆኖ ቆየ፡፡
ቀንም ሆነ፤ ማታም ሆነ፤ ሁለተኛ ቀን፡፡ የማለዳ ፀሐይ ስትወጣ፤
የፍቅርን ሰረገላ የሚስቡት ነጫጭ ፈረሶች እየተቅበጠበጡ መጡ፡፡
የሌቱ የሀሳብ ዝርፊያ ተገታ፡፡ ፈረሶቹ በማለዳው ጮራ
እያብለጨለጩ ይታዩኛል፡፡ ክፉዎች ሊነኩት በማይችሉት የፍቅር
ልጓም፤ እየኮለኮለ የሚጋልበው አምባላይ ፈረስ መጣ፡፡ ..የወይኑን
ተክል ከቀበሮዎቹ ጠብቁ፡፡ የወይኑን ማሣ እንዳያማስኑት ትጉ..
የሚል ድምፅ ተሰማ፡፡ ነቃ አልኩ፡፡ ግን ስለሆነው ነገር ከማወቄ በፊት
ሁሉም ነገር ፀጥ አለ፡፡ ከሩቅ ስፍራ እንደሚመጣ ነፋስ እየተውጀበጀበ
ከጆሮ የገባው፤ በልስላሴው እያዘናጋ ኪሶቼን በረበራቸው፤
ካህን የነፍሴ አገልጋይ
እንቅልፍ አትተኛም ወይ፤ የሚል ዜማ ነው፡፡
ሃሌ - ሃሌ ሉያ፤ ፀባኦት - ኤልሻዳይ፤ ሃሌሉያ፤ ዛሬ ህይወት ታሪክ
መሆን አልፈለገችም፡፡
ከተራራው ጀርባ፤ ከወንዙ ባሻገር
የተጨዋወትነው፤ ብዙ ምስጢር ነበር..
እያለ ያዜመው ማን ነበር? ህይወት የሮማንቲካዊ ቅርጽ የያዘ ተረክ
ስትሆን እንዲህ ነው፡፡
የፈረሰው የእውን እና የህልም ዓለም ግድግዳ እንደ ገና ቆመ፡፡
ህይወት እንዲህ ትዘፍናለች፡፡ እንዲህ ትተረካለች፡፡ ህይወት እንዲህ
በቀለም ተስላለች፡፡ ነገ በሌላ ካንቫስ ሌላ፣ በሌላ ሰዓሊ እጅ በአዲስ
ቀለም እንደ አዲስ ዘመን በልምላሜ አጊጣ ታድሳ ትመጣለች፡፡
ህይወት ትንግርት ናት፡፡ እንኑራት፡፡ አበባዬ ሆይ ለምለም፡፡
ጨፍር ጎበዝ ደንስ ጎበዝ
ህይወት የምትፈቷት እንቆቅልሽ አይደለችም፡፡
በድንቅ ተጥለቅልቃችሁ የምትኖሯት ተዓምር ነች፡፡ በፍርሃት እና
በፍቅር የምንዘምራት የሞት እና የትንሣዔ መዝሙር ናት፡፡ አሁን
ባግዳድ ልውሰዳችሁ፡፡ ተረት ልንገራችሁ፡፡ የሃማሉን ቁጥብ እና
የሦስቱ የባግዳድ ወይዛዝርት ታሪክ የዘመን መለወጫ ስጦታዬ ነው፡፡
ከዘመናት በአንዱ ዘመን፤ ባግዳድ ውስጥ ሚስት ሳያገባ በላጤነት
ብቻውን የሚኖር ቁጥብ የሚሉት ሐማል ነበር፡፡ ከዕለታት በአንዱ ቀን
በጎዳናው ዳር ቦዝኖ፤ ቅርጫቱንም ደገፍ ብሎ እንደ ቆመ አንዲት
ወይዘሮ መጣች፡፡ በወርቅ የተጠለፈና የወርቅ ጉንጉን ጥለት ያለው
ሙሉ ሐር ቀሚስ እንደለበሰች ከፊቱ ቆመች፡፡ ጫማዋ ወርቅ፤
ፀጉሯም በወርቅ የተጌጠ ነው፡፡ ዓይነ ርግብ ያደረገች ይህች ሴት፤
ብርሃን የሚረጩ ጥቋቁር ዓይኖች ያሏት ናት፡፡



ይቀጥላል

@wegoch
@wegoch
📌 ሳይክ-ኢንፎ

የምክርና የንግግር ህክምና (Counseling and Therapy) በ Online Chat ፣ በ Video Call ወይም በ Phone Call በማንኛውም ሰዓት እና ቦታ ላይ ሆነው በነፃ ማግኘት ይችላሉ ። 100% ሚስጥሮት ተጠብቆ የሚፈልጉትን እርዳታ አሁን ያግኙ !
//ህይወት እንደ ተረት // (2)
(ጆኒ ፀጋዬ)

እይታዋ ቅዝዝ ልስልስ
ያለው፤ ፍጹም የተዋበችው ያቺ ሴት እንደ ሙዚቃ በአማረ ድምፅ
..ቅርጫትህን ይዘህ ተከተለኝ.. አለችው፡

ሐማሉ ቁጥብ ፍፁም ተደንቆ እና የሚሰማውንም ማመን አቅቶት፤
..ያአላህ! እንዴት ያለች የተባረከችና ዕድላም የሆነች ቀን ነች.. አለ፡፡
ያንን ብሎ ቅርጫቱን አፈፍ አድርጎ ከትከሻው ጣለ፡፡ከአንድ ቤት ደርሳ
እስከ ቆመች ድረስ ተከተላት፡፡ በዚያም በሩን አንኳኳች፡፡ የናዛሪው
ሽማግሌ ፈጥነው ብቅ አሉ፡፡ የወርቅ ሳንቲም ተቀበሉ፡፡ በእሱም እንደ
ወይራ ዘይት ኩልል ያለ የወይንጠጅ አምጥተው ሰጥዋት፡፡ እርሷም
ቀስ አድርጋ ከቅርጫቱ ውስጥ አስቀመጠችው፡፡ ..አንሳና ተከተለኝ..
አለችው፤ ሐማሉን ቁጥብ፡፡ ..ሰው ያሰኘውን ሁሉ የሚያገኝበት አላህ
የባረከው ቀን ይሄ ነው.. እያለ ቅርጫቱን ተሸከመ፡፡ አሁንም ከአንድ
የአትክልት መሸጫ ሱቅ በር ደርሰው እስኪቆሙ ተከተላት፡፡ በዚያም
የሻሚ አፕል፣ የኦስማን ኩንች፣ የአማን ኪሽኒት፣ የአባይ ወንዝ
ያበቀለው ዱባ፣ የግብፅ ሎሚ፣ የሱልጣኒ ብርቱካን እና ትርንጎ
ገዛች፡፡ ከቅርጫቱም አኖረች፡፡ ደግሞ መልካም ማዕዛ ያላቸው የአደስ
ፍሬዎች፤ ሽታው የሚያውድ የአልፓይን ሐረግ፣ የደማስቆ ኔኑፋረስ እና
ከሞሜላ፣ እንደ ደም ቀይ የሆነ ፅጌሬዳ፣ የቫዮሌት፣ የኢግላንታይን፣
የፈካ የሮማን እና የአደይ አበባዎች በቅርጫቱ ተጨመረ፡፡ ከዚያም
..በል አንሳ.. አለችው፡፡ አንስቶ ተከተላት፡፡TN> እልፍ ብሎ ደግሞ
ከሉካንዳ ቤቱ ቆመች፡፡ ..አምስት ኪሎ ሥጋ ቁረጥልኝ.. አለች፡፡
ከፈለች፡፡ በሙዝ ቅጠል ጠቅልሎ ሰጣት፡፡ ከቅርጫቱ ጨመረች፡፡
አሁንም ..በል አንሳ.. አለች፡፡ ሃማሉ ተሸከመ፡፡ ተከተላት፡፡ደግሞ
ከአንዱ ግሮሰሪ ቆመች፡፡ ከዚያም ደረቅ ፍራፍሬዎችን ገዛች፡፡
ለውዙን፣ ዘቢቡን ጨመረች፡፡ ከምግብ በኋላ የሚቀርቡ ጣፋጭ
ተከታዮችንም አከለች፡፡ ..ሐማል አንሳ ተከተለኝ.. አለች፡፡ ቅርጫቱን
አነሳ፡፡ ተሸከመ፡፡ ተከተላት፡፡
ከጣፋጭ መሸጫ ሱቅ ገብታ፤ ዝርግ የሸክላ ሰሃን ገዝታ፤ እንደ ዝባድ
ያሉ ለዓይን እና ለአፍንጫ የጣመ ጠረን ያላቸው መዋቢያ ዕቃዎችን
በሰሃኑ አስቀምጣ፤ ከቅርጫቱ ጨመረች፡፡ ..ሃማል አንሳ.. አለች
ቀጠለች... ቀጠለች...በዚህ ጊዜ፤ በፍፁም ደስታ የተጥለቀለቀው
ሐማል፤ ..ይሄን ሁሉ ዕቃ እንደምትገዢ አስቀድመሽ ብትነግሪኝ ፈረሴን
ወይም ግመሌን ይዤ እመጣ ነበር.. አላት፡፡ እሷም ፈገግ አለችና
..ወሬውን ተወው፤ በልማ እንሂድ አይዞህ፤ ኢንሻ አላህ፤ ጠቀም ያለ
አስብ ታገኛለህ.. አለችው፤ ማጅራቱን በእጇ መታ እያደረገች፡፡
ደግሞ ከሽቱ መሸጫ ሱቅ ገባች፡፡ የፅጌሬዳ፣ የብርቱካን፣ የአደይ፣
የቫዮሌት፣ አበቦች መዐዛ ያላቸውን ፈሳሾች ገዛች፡፡ አንድ የሽቱ
ማርከፍከፊያ ጠርሙስም ገዛች፡፡ እጣኖችን፣ ሰንደሎችን ገዛች፡፡
በእስክንድሪያ የተሰሩ ሻማዎችን ሸመተች፡፡ ከዚያም በቅርጫቱ
ጨምራ ..አንሳና ተከተለኝ.. አለች፡፡ ሄዳ ከአንድ ሰፊ ግቢ ቆመች፡፡
በግቢው የሚታየው ቤት እጅግ ያማረና አምዶቹ ሞገስ የሰጡት ቤት
ነው፡፡ ባለ ሁለት ተካፋች የሆነው እና ከጥቁር እንጨት የተሰራው
የቤቱ በር ላይ ቀይ የወርቅ ቅጠል ተለብጦ ይታያል፡፡ ከበሩ እንደ
ደረሰች ዓይነ እርግቧን ወደ ጎን አደረገች፡፡ እናም በቀስታ አንኳኳች፡፡
ሐማሉ ከኋላዋ እንደ ቆመ፤ ስለ እመቤቲቱ ቁንጅና፣ ተወዳጅነት እና
የደስደስ በስተቀር ሌላ የሚያስበው አልነበረውም፡፡ በሩ ተከፈተ፡፡
ጉድ ነው፡፡ በሩን የከፈተችው ረዘም መለል ያለች ወጣት ናት፡፡
የቁንጅና አብነት የምትሆን፤ የአዕምሮ ብሩህነትን የታደለች ፍጹም
ግርማ ሞገስ ያላት ወጣት ናት፡፡ ግንባሯ እንደ ነጭ አበባ ሆኖ
ጉንጮቿ እንደ ቀይ ፅጌሬዳ የቀሉ ናቸው፡፡ ብሩህነትን የተላበሱት
ዓይኖቿ እንደ ጊደር ወይም እንደ ሜዳ ፍየል ስክት ያሉ ናቸው፡፡
ቅንድቦቿ የአዲስ ጨረቃ ቅርፅ የያዙ ናቸው፡፡ አፏ የጠቢቡ ሰለሞንን
ቀለበት የመሰለ ሲሆን ከንፈሮችዋ ፍም ናቸው፡፡ ጥርሷም በክር
ተለክቶ የተደረደረ ሉል ይመስላል፡፡ አቤት አንገ አንገትዋ እንደ ሚዳቋ
አንገት መለል ያለ ነው፡፡ ጡቶቿ ሞላ ያለ ሮማን ይመስላሉ፡፡
ስትራመድ፤ ሰውነቷ በለበሰችው ቀሚስ ውስጥ እንደ ፀጉር ጉንጉን
ይሽመለመላል፡፡ እምብርቷ፤ አንድ ብልቃጥ የወይራ ዘይት ይይዛል፡፡
በጥቅሉ የምድር ባለቅኒያት ሁሉ በቅኔያቸው ያወደሷት ሴት
ትመስላለች፡፡ ቁጥብ፤ በዚህች ሴት እልፍኝ ገብቶ በሚያየው እና
በሚሰማው ነገር ሁሉ እየተደመመ ቆየ፡፡ ከወይዛዝርቱ ጋር ተላመደ፡፡
ተፈቀደ፡፡ እናም ግጥም በወይንጠጅ እየተጎነጨ ጥያቄ
አቀረበ፡፡ ..በአላህ ብቻችሁን ናችሁ፡፡ እኔ በዚሁ ብቆይ ምን
ይመስላችኋል?.. ብሎ ጠየቀ፡፡ ጥያቄውን ከመቀበላቸው በፊት
ከሦስቱ ሴቶች አንዷ ጥያቄ አቀረበች፡፡ ጥያቄውም ..ምንም ነገር
ብታይ አንድም ጥያቄ ላታነሳ ማሃላ ታደርጋለህ?.. አለችው፡፡ ሐማሉ
ቁጥብ ..እምላለሁ.. አለ፡፡ ከመሃላው በኋላ ..ወዲያ ሂድና እዚያ
ከበሩ ላይ የተፃፈውን ነገር አንብብ.. አሉት፡፡ በወርቅ ፊደል ከበሩ
የተፃፈው ቃልም እንዲህ የሚል ነው፡፡ ..የማይኮነስረውን ነገር
የሚያወራ ሰው፤ የማያስደስተውን ነገር ይሰማል.. ተረቱ ይቀጥላል፡፡
ህይወት የምንፈታት እንቆቅልሽ ሳትሆን የምንኖራት ትንግርት እንደ
ሆነች ስንቀበል የማይኮነስረንን አናወራም የማንወደውንም
አንሰማም፡፡ ከፍ ሲል ቀንጨብ ያደረኩት የሪቻርድ በርተን ተረት
ይቀጥላል፡፡ ተረቱም የኛ ህይወት ነው፡፡ ህይወት እንደ ቁጥብ
እመቤት ነች፡፡ እኛም ሐማሎቿ ነን፡፡ እመቤት ህይወት፤ መጪውን
ዘመን እንደ ቁጥብ በሸክሟ፣ በስጦታዋ፣ በፀጋዋ አምበሽብሻ ታሳድረን ።

(ጆኒ ፀጋዬ)

@wegoch
@wegoch
Forwarded from ቅንድል ኢትዮጵያ (Ermiyas Dejene)
ቅንድል ዲጂታል መፅሔት

#አዝናኝ #አስተማሪ #ወቅታዊ #ሀገርኛ መፅሔት👇👇

#ቅፅ 1 - #ቁጥር 4

@KendelM
@KendelM
Forwarded from ቅንድል ኢትዮጵያ (Ermiyas Dejene)
ቅንድል Digital መፅሔት.pdf
4.3 MB
ቅንድል ዲጂታል መፅሔት

#በአዲስ እና በአማረ አቀራረብ‼️

ቅፅ 1 - ቁጥር 4

💵ፓኬጅ ከገዙ 50 ሳንቲም ብቻ💵

@KendelM
@KendelM
ቆዳ እና ባለቆዳ(ልዑል ሀይሌ)

በሬው እግር እግሬን እያየ ይጮሃል "እምቧ!!..." እኔም የሱ እንደዛ ማፍጠጥ እየገረመኝ እግሮቼን እንደ አዲስ እመለከታቸው ጀመር። "ምናባቱ አይቶ ነው ይሄ በሬ እንዲህ እያፈጠጠ የሚጮኸው?" እላለሁ አንዳችም አዲስ ነገር ከእግሮቼ ሳጣ ....ነገር ግን በሬው
ጩኸቱን ቀጥሏል "እምቧ!!..." ምን አይቶ ይሆን ይሄ ከብት እንዲህ የሚጮኸው?..." እያልኩ እየተነጫነጭኩ እርምጃዬን ስጀምር በሬውም እየተከተለኝ ሲጮህ ሳይ ተገርሜ እኔም እግር እግሩን አየው ጀመር። ሁለታችንም እግር እግራችንን እየተያየን ከቆየን በኋላ የበሬው እረኛ ደርሶ ሲቆም እኔም የእፎይታ ትንፋሼን እየለቀቅኩ "ምን ሆኖ ነው ባክህ እግር እግሬን እያየ የሚጮኸው?...ምነው ሊጠርግልኝ
አስመሠለውሳ..." ስለው በሬው የታሰረበትን ገመድ አጥብቆ እየያዘ "አመሉ ነው...ማለቴ ከቆዳ የተሰራ ነገር ሲያጋጥመው ሳያስወልቅ አይተውም። እርሶም ቆዳ ጫማዎትን ቢያወልቁት ከዚያ በኋላ ፊቱን አዙሮ ይሄዳል" ሲለኝ የተጫማሁትን አንበሣ ጫማ እያየሁ "አይ ዕድሌ የአያ ጎበዜ እንዳይበቃኝ አንተም ትቀናብኝ?!..ስንት ዕድር ዕቁቡን
በኩራት እየተራመድኩ ያቋረጥኩበትን ስንቱን ምቀኛ ዓይኑን ያቀላሁበትን ጫማ የኔ ነው አልክ?!..እንግዲህ አንተንስ ምን ገዶኝ አወልቅልሃለሁ...እንኳን ጫማዬ እግሬም የኔ አይደለ!!...ተውሸውም አይደል የዚህችን ዓለም ግሳንግስ እጓዝበት ዘንድ የሆነው?...ይሁና!!"
ብዬ ጫማዬን አውልቄ ወደሱ ሳስጠጋለት እረኛው እንዳለው ፊቱን አዙሮ ሄደ። ...እውነት ነው ያስጮሃል ቆዳህን ሌላው እንደጫማ እየረገጠው ሲሄድ ያማል!!...ነገህን በሌሎች ላይ ስታይ ካልነቃህ ዕጣ ፈንታህን እያበላሸኸው እንደሆነ አትጠራጠር
.
.
...(ይቀጥላል)

15-09-11
አሶሳ ኢትዮጵያ


@wegoch
@wegoch
የጋሽ እርገጤ ልጅ ባረገዘች ማግስት
(ቡሩክ ካሳሁን)
ጋሽ እርገጤ ከተኙበት በ11፡30 በሚስታቸው ወይዘሮ የሻሽ ወርቅ አማካኝነት ከእንቅልፋቸው ተቀስቅሰው ወደ ሳሎን እንዲመጡ ተደረጉ፡፡ ጋሽ እርገጤ ብስጩ እና ቁጡ ሰው ቢሆንም ወደ ሳሎን ሲያመሩ ግን በጣም ደንግጠዋል፡፡ ጋቢያቸውን አገልድመው ሳሎን ሲደርሱ ሶስት ሱፍ የለበሱ ሽማግልዎች ከፊታቸው ቆመው አገኟቸው፡፡ ይበልጥ ደነገጡ አፋቸው እየተሳሰረ ‹ምነው ምን ተፈጠረ?› ሲሉ ሶስቱን አዛውንት ጠየቋቸው፡፡ ሆኖም ግን መልስ አላገኙም ጋሽ እርገጤም እግራቸውን ብርክ ብርክ ይላቸው ስለጀመር ከሶፋው ላይ ተቀምጠው ‹እሺ ተቀመጡና እንነጋገር› አሏቸው፡፡ ሶስቱ አዛውንትም ‹የመጣንበትን ሳንናገር አንቀመጥም› ብለው መለሱ፡፡ ጋሽ እርገጤ ትግስታቸው ሞለቶ ሞለቶ ፀጉራቸው ጋር የደረሰ ይመስላል፡፡ ወይዘሮ የሻሽ ወርቅም በሳሎኑና በመኝታ ቤቱ መሀል ቆመው ‹አንቺ ታውቂያለሽ› እያሉ ወደሰማይ ያንጋጥጣሉ፡፡ ጋሽ እርገጤም ‹ታዲያ ምን ይሁን ትሉኛላቸው አመጣጣቹ እንደ መርዶ ነጋሪ በለሊት፤ አኳኳናቹ ልጅህን ለትዳር ስጠን አይነት፤ እንዴት ነው ነገሩ?› ቁጣ ቀላቅለው መናገር ጀመሩ፡፡
.
ከሶስቱ ሽማግሌዎች አንድኛው እየፈሩና እየተቡ ‹እእ እኛ የመጣነው እእ ልጆት ኤደን…› መጨረስ ተሳናቸው ከኪሳቸው መሀረባቸውን አውጥተው ግንባራቸው ላይ የተቸፈቸፈውን ላብ ይጠርጉ ጀመር፡፡ ‹እኮ ልጄ ኤደን ምን ሆነች?› ጋሽ እርገጤ ጠየቁ
ከሽማግሌዎቹ በእድሜ አነስ ሚሉት ‹እንዴ እኛ አላስረገዝናት የምን መርበትበት ነው፡፡ ያስረገዛት እዛ ተንጋሎ እንቅልፉን ይደቃል እኛ በምን ሀጥያታችን እንሽማቀቅ› ለራሳቸው ብለው ልባቸውን አጀገኑና ‹ልጆት ኤደን አርግዛለች› ነገሩን አፈረጡት፡፡ ነገሩን ሲያፈርጡት ጋሽ እርገጤ አይናቸው ፈጦ ነበር፤ ሁለቱ ሽማግሌዎች መሬት መሬት እያዩ መሬትን ሲያሽኮረምሙ ነበር፤ ወ/ሮ የሻሽ ወርቅ በሁለት እጃቸው ጆሯቸውን ደፍነው ነበር፡፡
.
ጋሽ እርገጤ ለረጅም ሰዓት አይናቸውን ካፈጠጡ በኋላ ‹ወይኔ እርገጤ› ብለው አንባረቁ፡፡ ሶስተኛ ጎረቤት ያለ ህፃን ልጅ በድምፃቸው ባኖ ማልቀስ ጀመረ፡፡ ሁሉም ተጨንቀዋል፡፡ ማነው ያስረገዛት? እገላለው ብለው የድሮ ጠብመንጃቸውን ሊያመጡ ሲነሱ ሚስታቸው ተንደርድረው እግራቸው ላይ ወደቁ ሽማግሌዎቹም ይለምኗቸው ጀመር፡፡
‹ኸረ ግዴሎትም ይረጋጉ፤ ቁጭ ብለን አውርተን መፍትሄ እናመጣለን፤ መቀጣትም ካለበት በህግ እንዲቀጣ እናደርጋለን እንጂ መንግስት ባለበት ሀገር ደም መፋሰሱን ምን አመጣው?› ከሽማግሌዎቹ አንዱ ሊያረጋጋቸው ሞከረ
‹መንግስት በኔ ልጅ ምን አገባው? ያገባኛል ካለም መንግስትን እራሱ አስረግዤ ነው ማሳየው› ለያዥ ለገላጋይ አቃቱ፡፡
.
እንደምንም ተለምነውም ተሸንግለውም ከተረጋጉ በኋላ በወጉ መሰረት ለጋብቻ እንዲበቁ ሽማግሌዎቹ ጥያቄ አቀረቡ፡፡
ጋሽ እርገጤም ‹ስለየትኛው ወግ ነው ምታወሩት? ከጣልያን ነው እንዴ የመጣችሁት እናንት ሰዎች? ጭራሽኮ ግራ እያጋባችሁኝ ነው፡፡ ቆይ ከሰርጉ በፊት ያረገዘችው ጥሎሽ መሆኑ ነው? እኔ አይኔ እያየ ይሄ ወሮበላ ልጄን አያገባትም› አሉ፡፡
በዕድሜ ትንሹ ሽማግሌ ‹በቃ አይኖትን ጨፍነው ልጆቹ ይጋባሉ› ለማለት ቃጣቸው ነገር ግን እሳት ላይ ቤንዚን አርከፍክፈው ነገሩን የብሔር ፀብ ላለማስመሰል ብለው ተዉት፡፡ ጋሽ እርገጤ ቢለመኑ ቢሰሩ ፍንክች ያባ ቢላዋ ልጅ አሉ፡፡
‹ታዲያ ምን ቢሆን ይሻላል› አሉ እስካሁን ዝም ብለው የነበሩት ሽማግሌ
‹ቀልድ…ቀልድ ቢሆን ይሻላል› ጋሽ እርገጤ ፈጠን ብለው መለሱ::
.
.
.


ጥቅምት 2010 ዓ.ም

ቡሩክ ካሳሁን ቴሌግራም ቻናል ለመቀላቀል👇
@burukassahunc


@wegoch
@wegoch
Forwarded from አንድነት ይሻላል ፨ ፍቅር ያሸንፋል
የእውነተኛ ፍቅር ትርጉም የገባው ሰው እንኳን ብሔር ቆጥሮ ሰውን ከሰው ለይቶ ሊጎዳ ይቅርና እንስሳት ላይ እንኳን አይጨክንም።
ያኔ በኛ ጊዜ
(ቡሩክ ካሳሁን)
እንደ ዛሬ ፈታና ማይሰረቅበትና ጃዋር ማይፈነጭበት ያኔ የኛ የትምህርት ጊዜ ዋነኛ የፈተና ፀር ገጀራው ነበር፡፡ አስረኛ ክፍል እያለን ገጀራው ለፈተና ጊዜ ሚያወጣው አሰላለፍ ሞሪኖን ሚያስንቅ አሰላለፍ ነው፡፡ እሱ ካወጣው የፈተና አቀማመጥ ማንም ወለም ዘለም አይልም፡፡ (ምን ያደርጋል ማትሪክ ላይ መንግስት በራሱ አሰላለፍ አስቀመጠንና ተበላ እንጂ፡፡) ለሁላችንም የምንቀመጥበትን ቦታ ከነምናልባት አስተማሪ ‹ተነስ› ቢለን ምናቀርበው ምክንያት ይነግረናል፡፡
አሁን ለምሳሌ መስኮት ዳር ላስቀመጠው ልጅ አስተማሪ መጥቶ ከቦታህ ልቀይር ቢለው ከልጁ ሚጠበቀው ገጀራው እንዳለው ‹ ብዙ ብርሀን ከሌለ አይነበበኝም› ማለት ብቻ ነው ከዛ በኋላ ገጀራው ጣልቃ ገብቶ ‹ታዲያ ማይታይህ ከሆነ እዛው ተቀመጣ› ብሎ ውሳኔ ያስተላልፋል፡፡
ገጀራው በጣም ብልጥ ነው፡፡ ራሱን ከክፍላችን ጎበዝ ተማሪ ኋላ ያስቀምጣል፡፡ እኔና ዱባለን የሰፈሩ ልጆች ስለሆንን ያው የጎሳ ፖለቲካ አደል ሀገሪቱን በ4ቱም አቅጣጫ ሚያዋስናት?¡ ከእሱ አቅራቢያ ያደርገንና ለሱ ከተላኩት መልሶች ርዝራዡ ይደርሰናል፡፡ ሳሮን በዚ ጊዜ ከገጀራው ጋር እጅና ጓንት አይገልፀውም ምናልባት ስጋና አጥንት ከገለፀው ትሆናለች፡፡ ሁል ጊዜ ሳሮንን ከጀርባው ነው ሚያስቀምጣት፡፡ አንድ ጊዜ ትዝ ይለኛል ዱባለ ከገጀራው ትይዩ ተቀምጦ መልስ ስጠኝ ብሎ እንባ ቀረሽ ልመና ሲለምነው ፅፎ ካዘጋጀ በኋላ ዞሮ ለሳሮን ሳትጠይቀው ሰጣት፡፡ የዱባለ ሀሞት ሲፈስ ፊቱ ላይ ይነበብ ነበር፡፡እጁን ሁላ አውጥቶ ቢናገር ምንኛ አንጀቱን ባራሰ ነበር፡፡ ምን ያረጋል ገጀራው ነዋ፡፡ ገጀራው ለፈተና ሰሞን ፂሙን አለቅጥ ያሳድጋል፤ አንገቱ ላይ ስካርፕ ጣል ያረጋል፡፡ ባጭሩ የዘመኑን ገጣሚዎች ይመስላል፡፡ ታዲያ እንዲ ሆኖ ከሩቅ ላየው ባንክ ሊዘርፍ እንጂ ፈተና ሊፈተን ሚመጣ አይመስልም፡፡ እሳት የለበለበው ብርጭቆ ወረቀት የመሰለ ፊቱ እንኳንስ ተቆጥቶና ተኮሳትሮ ፈገግታው ራሱ ቀልብ ይገፋል፡፡ የፊቱ ጥቅም የሚገባህ በፈተና ሰዓት ነው፡፡ በፈተና ሰዓት ፈታኛችን እኔና ሌሎች ተማሪዎች ላይ አራስ ነብር ሆኖ ለመተንፈስ ራሱ ሲያሳቅቀን ይቆይና ገጀራው ጋር ሲደርስ ግን የትዳር ጥያቄ የቀረበላት ልጃገረድ ይሆናል፡፡ በሙሉ አይኑ ገጀራውን አያየውም፤ አይኑን ይሰብራል፣ ያስለመልማል፡፡ ያኔ ገጀራው ጋቢናውን ተማምኖ ካፅናፍ እስከ አፅናፍ ፈታ ብሎ ይኮርጃል፡፡ አስተማሪው በጣም ሲመረው ገጀራው አጠገብ ይሄድና ስለ ኑሮ፣ ኳስ፣ ንግድ ይቀባጥራል፡፡ በአጭሩ አንድ ያልታወቀ ጋዜጣን ይመስለኛል፡፡ በዚህ ሰዓት ገጀራው ፈተናውን ሰርቶ ካልጨረሰ ‹ይቅርታ እየሰራው ነው ሀሳቤን እየሰረቅከኝ ነው› ብሎ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ አስተማሪውን ወደ ጥጉ ይመልሰዋል፡፡ በአጭሩ ገጀራው ማለት የፈተና ሰዓት ባልቻ አባ ነፍሶ ማለት ነው፤ ድል ሳያረግ አይመለስም፡፡
ያን ሁሉ ጀብዱ የሰራ ሰው ታዲያ ምን ያደርጋል በ11ኛው ሰዓት መንግስት ጉድ አደረገው፡፡ ማትሪክ በምንፈተንበት ሰዓት የክፍላችን ጎበዝ ልጅ ክፍል ሞልቶ ተቆርጦ ሌላ ክፍል ገባ፤ ገጀራውን ውሀ በላው፡፡ ፈታኙ ገጀራውን እንደልቡ እንዲፈነጭ ቢፈቅድለትም ‹መልስ ካልተሰጠ ምርጫ ምን ያደርጋል?› አደል ኤፍሬም ስዩምስ ያለው፡፡ አንድ ሙሉ ክፍል ተዟዙሮ ኮርጆ አንድ ሙሉክፍል አይነት ስህተት ከፍንጥርጣሪ መልስ ፈተናው ላይ አሰፈረ፡፡ ገጀራው በአስደማሚ ውጤት በዝረራ 10ኛ ክፍል አቋረጠ፡፡ የኢትዮጵያ የትምህርት ጥራት ተስፋ ማንሰራራት የጀመረው ያኔ ይመስለኛል፡፡

መስከረም 2010 ዓ.ም

ቡሩክ ካሳሁን ቴሌግራም ቻናል ለመቀላቀል 👇
@burukassahunc


@wegoch
@wegoch
Forwarded from Melkam74 Digital Magazine
መልካም74 ቅፅ ፩ ቁጥር 6 እነሆ ወቅታዊ ጉዳዮችን እና መዝናኛን አካቶ ለንባብ በቅቷል።
Forwarded from Melkam74 Digital Magazine
Melkam74 ቅፅ ፩ ቁጥር 6.pdf
4.3 MB
📠 መልካም74 ቅፅ ፩ ቁጥር 6

💰 ፓኬጅ ከገዙ በብር 1.20 ብቻ 💰
‹‹ሄይ…አልተኛሽም አይደል…?››
---------------------------------------
ከበፊት ጀምሮ የዚህ የመብራት ፈረቃ ነገር ሊያሳስበው የሚገባው መብራት
ሃይልን ብቻ ሳይሆን ቤተሰብ መምሪያም ነው ስንል በነሲብ ሳይሆን ምክንያት
ነው፡፡እንዲሁ በወሬ በወሬ መብራት በብዛት ሲጠፋ ብዙ ህፃናት ይፈጠራሉ የሚል ነገር አውቅ ነበር፡፡ የመብራት ፈረቃ ዳግም ሲጀመር ግን ሆነ ብዬ ጨለማ እና የህዝብ ቁጥር መጨመር ቁርኝት ካላቸው ብዬ ትንሽ ዳሰሳ አደረግኩ፡፡ አላቸው! ብዙ ምሳሌ አገኘሁ፡፡….ለምሳሌ የዛሬ 11 አመት ዛንዚባር ለአንድ ወር መብራት ድርግም አድርጋ ከርማ በአስረኛው ወር ላይ የሚወልዱ እናቶች ቁጥር በሃያ በመቶ እንደጨመረ አነበብኩ፡፡ስለዚህ….ያው… ሌላ ጊዜ ቲቪ የሚያዩ ባልና ሚስት መብራት ከሌለ እርስ በርስ ስለሚተያዩ…ሌላ ጊዜ ራዲዮ የሚያደምጡ ባልና ሚስት መብራት ከሌለ ስሜታቸውን ስለሚያዳምጡ…ሌላ የሚያዝናና ነገር ስለማይኖር በ‹‹እንትን›› ብቻ ስለሚዝናኑ…እንቅልፍ አልወስድ ብሏቸው ሲገላበጡ ቆይተው ‹‹እ…አልተኛህም እንዴ?›› …‹‹ሄይ…አልተኛሽም አይደል…?›› በሚል ለፍቅር ድግስ ስለሚዘጋጁ….የመብራት ሃይልን ብስጭት ለመወጣት አንዳቸው ላንዳቸው ብቸኛ የደስታ ምንጭ ስለሚሆኑ….ሁለት ሆነው ተኝተው ሶስት ሆነው ስለሚነሱ…..….የካቲት 2012 ላይ ወላ ጋንዲ፣ ወላ ጤና ጣቢያ፣ ወላ በፀጋህ….፣ በየመብራት ፈረቃ ልጆች ምጥ ተይዘው በሚመጡ ነፍሰጡር እናቶች ባይጣበቡ
ምን አለች በሉኝ!ለሁሉም፣ የዚህ የመብራት ፈረቃ ነገር ሊያሳስበው የሚገባው መብራት 😄

@wegoch
@wegoch
@paappii

#by_hiwot_emishaw
ሰላም ጤና ይስጥልኝ. አርቲስት #በረከት_ግርማ (አቢቹ) እባላለው የአዲስ አበባ ነዋሪ ስሆን የተለያዩ የኪነ #ቅርፅ እና ኪነ #ቅብ ስራዎችን እሰራለው። ስራዎቼን @artbekiyechalal ገፅ ውስጥ በመቀላቀል እንድትጎበኙልኝ በ አክብሮት ጠይቃለው።.................

@artbekiyechalal @artbekiyechalal

አመሰግናለው!!

@seiloch @seiloch
እንኳን ለ 1440 ኛው የ #ኢድ_አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሰን!

መልካም በዓል

@seiloch
@getem
@wegoch
Forwarded from Mykey (Mikiyas Liyew (Mykey))
Eid-Mubarak
@Mykeyliyew
ሰዶማዊነት፤
።።።።።።።።።። ።።።።።።።።።።
(ቡርሐን አዲስ)
በአጭሩ ከነብዩ ሎጥ (ዐ›ሰ) ጋር አያይዘን ከኃይማኖታዊ አንድምታው መነሳት ይቻላል፤
ሰዶማዊነት በዋናነት የቁሳዊነት ስልጣኔ አንዱ ጀብድ ነው፤ ከጥንት እስከዛሬ ሰዶማዊያንን
የምናገኘው… ከተነሱ ስልጣኔዎች አኳያ ነው፤ የአንድ ስልጣኔ ህልፈት መዳረሻም ምልክት
ነው፤ ታላቁ የስነ-መንግስት ምሁር ጀነራል ሰር ጆን ግለብ ፌት ኦፍ ኢምፓየርስ በተሰኘ
ጥናቱ ስድስት የአንድ ስልጣኔ ኡደቶችን አቅርቧል፡፡ የትኛውም ስልጣኔ እነዚህን ኡደቶች
ያልፋል፤ ስድስተኛው ኡደት ላይ ከደረሰ የዚያ ስልጣኔ ህልፈት ጫፍ መሆኑን ያስረግጣሉ፤
ከጥንት ግሪክ እስከአሁን የተነሱ ስልጣኔዎችን በዚህ ቅኝት መዳሰስ ይቻላል፡፡ በአማካይ
እስከ 250 አመታት እድሜ ይቆያሉ ስልጣኔዎች፡፡ ከዚያ ሌላ መልክ ለሚኖረው ስልጣኔ
ተሸናፊ ይሆናሉ፤ ግሪኮ ሮማን የስልጣኔያቸው መጨረሻ ሰሞን ሴሰኝነትን አቅፈው
እናገኛለን፤ ሴተኛ አዳሪዎች የነገስታት አማካሪ እስከመሆን ደርሰው ነበር፡፡
ታላቁ የኦቶማን ሱልጣኔት … ሀረም የሚሉት ባዕደ-ልማድ ማጓን ሲጀምሩ ስልጣኔው
መዉደቂያው ላይ ነበር፤ ይኼው አንግሎ አሜሪካን የሚቃኘው የዘመናችን ስልጣኔም
ያለበትን እውነት ማየት ቀላል ነው፤ ከተሞች አደጉ ስንል የነሱን መልክ ይይዛሉ፤ ወዲያው
ሞራል መክሳት ይጀምራል፤ ሴሰኝነት፣ ስርቆት፣ ዘረፋ፣ ግድያና መሰል ኢ-ፍትሃዊ፣ ኢ,-
ሰብዓዊ ክዋኔያት በዝተው ይጎርፋሉ፤
አዲስ አበባ ከአስርና ሀያ አመት በፊት ከነበራት የዋልጌነት ጠባይ አሁን በብዙ እጥፍ ብዙ
ዋልግነቶች አልበዙባትም? ሴሰኝነቱ፣ ዝርፊያው፣ ቀማኛው፣ ወሲብ ለባሹ፣ ሱሰኛው ደባሉ
ወዘተ… እየጋተን ያለውን የሞራል ዉርደት ማሰብ አይከብድም፡፡
ስለሰዶማዊነት፤
በሞራል የታነጸ ህዝብ ከሚገለፅባቸው መለያዎች አንዱ ሰዶማዊነትን መቃወሙ ነው፤
ከለመደው ቤተሰባዊ ባህሉ መዉጣት አለመፈለጉ ነው፡፡ ይህን ስርዓት ለማፍረስ
ከሚያስችሉ የቁስ አምልኮ ስልጣኔዎች አንዱ ሰዶማዊነት ነው፤ የሎጥ ህዝቦች እኮ
በጊዜው ንቃት ነበራቸው፤ ሰዶማዊ ሆነው ከሰሙ እንጂ፤ በ14ኛው ክፍለ ዘመን በጣሊያን
ፖምፔ ተመሳሳይ ሰዶማዊያን በዝተው እንደነበር ይታወሳል፤ ዛሬ ከባድ ዝማሬ የተነገበለት
አንዱ አጀንዳ ይኼው ሆኗል፡፡
በነገራችን ላይ ባዮሎጂካዊ እንደሆነ ጭምር የሚቀርቡ ጥናቶች አሉ፤ ፍጹም የተጋነና
የሳይንስን ክብር ያጎደፈ ነው፤ ራሳቸው ሰዶማዊ የሖኑ ሳይንቲስቶችና ከፍተኛ ክፍያን ድጋፍ
ያደረጉ የሙያ ሙሰኞች ጎባጣ ሳይንሳዊነት እንጂ እውነተኛ ሳይንስ ሆኖ አይደለም፡፡ ሌላ
ጊዜ አስፈላጊ ሲሆን የምለው ይኖር ይሆናል፡፡
….
ሰዶማዊነት አንዱ የቤተሰብ ዋጋን ማርከሻ አብዮት ነው፤ ሰዎች ቤተሰብ ሆነው እንዳይኖሩ
የማስቻል ነውጥም ነው፤ ወሲብን የማጮህና በሴስ የተቋጠረ ልቅ ስርዓትን የማንሰራፋት
የማህበረሰብ ጅምላ መቆጣጠሪያ እንከን ነው፡፡ ይህ ብቻ አይደለም በርካታ እውነቶችን
ማውሳት ይቻላል፡፡
ሶስተኛው ሞገድ የሚባለውን የአክራሪ ፌሚኒስቶች እንቅስቃሴ ካየን እንዲሁ ቤተሰብን
ማፍረስ የሴቶችን መብት በህያውነት ለማስከበር ይረዳናል የሚሉ፡፡ ይህም ሌዚቢያንነትን
እስከማስፋት መድረሱን ይታዘቧል፡፡ ብዙ ጉዳዮችን በድፍረትና ባልታዩበት አዉድ መታዘብና
ማጥናት ካልቻልን ከባድ ፈተና ውስጥ ነን፡፡
“ጋብቻ ወንድን ለማገለግል የሚጠቅም መሳሪያ ነው፤ ስለዚህ ጥረታችን ሁሉ ጋብቻን
ማፍረስ ላይ ይሁን ሴቶችን ነጻ ለማዉጣት አይነተኛ መሳሪያችን ጋብቻን ማፍረስ ነውና
ሴቶች ባላቸውን እንዲተው ማድረግ አለብን”
ዲክለሬሽን ኦፍ ፌሚኒዝም 1971
የተከበረ ጋብቻን ማፍረስ ለምን አስፈለገ? ሰዶማዊነትን መዝመርስ ጠቀሜታው ምን
ይሆን? እንቀጥለው ይሆናል፤ ግን ሁላችንም በየራሳችን መንገድ መፈተሸ ብንችልስ?

@wegoch
@wegoch
@wegoch
ዘረኝነት ራሱ ግብረ-ሰዶምነት ነው!!
የራሱን አይነት ብቻ የሚያስከጅል። ሁለቱም ጥንቦች ናቸውና አንፈልጋቸውም!!"
----
ደግ ደጉን
((ጀማል አማን ዘወሎ ))

@wegoch
@wegoch
@balmbaras
2024/09/28 07:21:53
Back to Top
HTML Embed Code: