Telegram Web Link
<<ኤርትራ ውስጥ ብትወለድና እትብትህ እዛ ቢቀበር እትብትህን የበላው ምስጥ ግን አፋር ላለመድረሱ እርግጠኛ አትሁን። ጋምቤላ ተወለድ እትብትህን ጋምቤላ ውስጥ የበላው ምስጥ ግን አፋር ላለመድረሱ እርግጠኛ አትሁን። ለምን ከምስጡ ለመሻል አትሻም ? ለምን ትጠባለህ?.......ሰፊ አገር እያለህ ለምን ጠባብ ክልል አገርህ እንዲሆን ትመኛለህ?.....አህያ እንኳ ጋጣው ሲጠበው ይራገጣል። አትጥበብ። የማያሳፍርህ ነገር ቢኖር በኢትዮጵያነትህ ማመንህ ብቻ ነው በቃ። >>

<>ዴርቶጋዳ <>
©ይስማዕክ ወርቁ

@wegoch
@wegoch
@Bebra48
Forwarded from ቅንድል ኢትዮጵያ (Ermiyas Dejene)
ቀንዲል ዲጂታል መፅሔት.pdf
6 MB
ቀንዲል ዲጂታል መፅሔት

#አዝናኝ #አስተማሪ #ወቅታዊ #ሀገርኛ መፅሔት

ቅፅ 1 - ቁጥር 3

💵ፓኬጅ ከገዙ 70 ሳንቲም ብቻ💵

@KendilM
@KendilM
"ማሰብ፣መናገር፣ማድረግ" እነዚህ ሶስት አብይ አሳቦችን አፅኖት ሰጥተን እንመልከት የሰው ልጅ የሚፈጠረው ፣በሕይወቱ ዘመኑ ፅድቅም ሆነ ሀፅያት የሚሰራው በነዚህ ሶስት ነገሮችነው፡፡ 1 እንዴት የሰው ልጅ ይፈጠራል? እልፍ አመት ተጉዘን ቁዱስ ቁርሃን እና መፀሀፍ ቅዱስ ገልጠን ብንመለከት ይሄን የጥያቄያችንን መልስ እናገቻለን ግን ቀላል በሆነ መንገድ ለመመለስ ያህል "ሁለት ጥንዶች አብረው በአንድ ጎጆ በፍቅር ይኖራሉ፡፡ በነዚህ ጥንዶች መካክል ጊዜውን ጠብቆ የሚመጣ የቀጣይ ሕይወታቸውን ያማረ ፣ተድላ የሆነ ምኞታቸውን ላምባ የሚያሳይ ልጅ የመውለድ አሳብ በአይምሮአቸው ይቀረፃል፡፡ ይህ አሳባቸውን እውን ለማድረግ በመነጋገር ይፈታል ከዛ የአሰቡት፣ የተነጋገሩት ሁሉ በሁለቱም ዘንድ ተቀባይነት ካገቸ ወደ ተግባር ይገባሉ፡፡ ከዛ ከዘጠኝ ወር በኦላ የሰዉ ልጅ ይፈጠራል 2እንዴት የሰው ልጅ ሀፅያት ይሰራል? "ሰው ሆነን ስንፈጠር ፣ወደ ዚህ ስንቀላቀል ከፍት ፣ተንኮልን ይዘን የተፈጠረ ማንም ሰው የለም፡፡ ጊዜ እድሜን፣ ማንነትን፣ አሰተሳስብን፣ እውቀትን፣ ደረጃን.... ብዙ ነገር ቀያራ ነው፡፡ በምንኖርበት፣ በምንሰራበት፣ በምንማርበት ቦታ ከእኛ ቅንፁል ደረጃ ከፍ ያለ ጓደኛ ይኖረናል፡፡ ለዛ ሰው በውሰጣችን የሚሰማን ሰሜት ይኖራል፡፡ እንዴት በለጠን? ፣ከእኔበምንተሽሎነው? እያልን ሌትም በማህልትም የተቃረነ አሳብ በውሰጣች ገብቶ እንብከነከናለን፡፡ ሰሚ አገቸንም አላገቸንም ለብዙ ጊዜ በውሰጣችን የሚመላለሰውን አሳብ ለምናውቃቸው ናለሚያውቁን ሰለዛሰው እያነሳን እናወራለን፡፡ ከዛ የዛ ሰውን እድገት ለማደናቀፍ የውሸት መረብ በማዘጋጀት ከሰራው፣ ከትምሕርቱ፣ ከማሀበራዊሕይወቱ እንቅፍት እንዲገጥመው እንጥራለን፡፡ ጥረታችን እውን ሲሆን የዛ ሰው ሕይወት መና ሲሆን እኛ እንደሰታለን ሕልማችንም እልባት ያገኛል፡፡ 3እንዴትየሰው ልጅ ፅድቅ ይሰራል? "የመልካምነት ዋጋዋ ትንሽ ናት፡፡ ግን ቱርፍቱ ብዙነው፡፡ የምናሰበው አላማ ፍሬውን ማግቸት ባንችልም በሌላ ሰው ዘንድ ማየት ስንችል ለእኛም ተስፍ ይሰጠናል እና ልንደሰት ይገባል፡፡ ብዙ ሰዋች በአዮት፣ በሰሙት ነገር ተነሰተው ለሰዋች አድናቆት ይሰጣሉ፡፡ መልካም ነገር መናገር ደግሞ የመልካምነት አሰተሳሰብ ውጤትነው፡፡ ብዙ ሰዋች ለሰው ያላችውን ከብር ለመግለፅ ለዛሰው የሰራእድልበመፍጠር፣ የትምሕርትእድል በማመቻቸት ፣ሽልማት ፣እውቅና፣እርዳታ በመሰጠት መልካምነትን ያደርጋሉ" በሕወታችን ውሰጥ በሚጠቅሙሞ በማይጠቅሙም አሳቦች ተዘፍቀናል እንከርዳዱን ከንፁሁ እህል ለመለየት ደግሞ የሰው ልጅ የጊዜ እሰረኛ ነው ፡፡ትናንት መጥፎ ያልከው ዛሬመልካምነው ፣ዛሬ መልካም ነው ያልከው ነገ መጥፎ ሊሆን ይችላል፡፡ ግን ለሁሉም ነገርመልካምነት ይሻላል፡፡

5/8/2011 የተፃፈ
ከአሸናፊፍቃዱ/1050/

@wegoch
@wegoch
@wegoch
..........................................
ያመለጠው ዶሮ እና አመላለጡ(ልዑል ሀይሌ)
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
አመለጠ!!...እውነቴን ነው አመለጠ!!...ለስንት ነገር ያሰብኩት ዶሮ
ለስንት ነገር ሳያስበኝ ከእጄ አፈትልኮ አመለጠ!!...እኔም በድንጋጤ
በመንገዱ ስታልፍ ከነበረች ባልቴት በእጇ ይዛው የነበረችውን
መዘፍዘፊያ ነጥቄ ዶሮዬን ባሯሩጠውም በቅያሱ በኩል ታጥፎ
አመለጠኝ። ...ፍጥነቱ ሲገርም ይሄማ የኡሴን ቦልት እጅ አለበት እንጂ
ሰው (ማለቴ ዶሮ) እንደዚህ አይሮጥም። ወይም ልክ እንደተሸጠ
ከገዢው አምልጦ እንዲመለስ ሻጮቹ አለማምደው ተልዕኮ
ሰጥተውታል እንጂማ ሰው (ማለቴ ዶሮ) እንደዚህ አይሮጥም።
ከዶሮው ማምለጥ በኋላ ቆም ብዬ ዙሪያ ገባውን ስቃኘው ከኋላዬ
ሁለት ቆመጥ(አጭር ዱላ) የያዙ ፖሊሶች መቆማቸውን አየሁና
"በዚህ ነው!...በዚህ ነው ያመለጠው!!..ኧረ ድረሱበት..." ብዬ ገና
ብሶቴን ከመጀመሬ አንደኛው ቆመጥ(ማለቴ ፖሊስ)..ጀርባዬን
ሲነርተው 'ከዶሮው ጋር ተመሳሰልኩበት ይሆን?' ብዬ የተገነጠለውን
(ማለቴ የተመታውን አካሌን) ማሻሸት ጀመርኩ።
"ባንተ ቤት አምልጠህ ሞተሃል...ከኔ እንኳን አንተ አንድ ወመኔ ንፋስ
ውስጥ የምትንገላታ አንዲት ስንጥር ልታመልጥ አይቻላትም!.." አለኝ
ከቁመቱ በላይ እየነጠረ እኔም ከድንጋጤዬ ለመውጣት እየታገልኩ
'ምነው ይሄ ሰውዬ አክቲቪስት ነኝ አለ!!..'(አልኩኝ በውስጤ)..."ኧረ
ዶሮዬ እየራቀች ነው እባክህን በዚህ ሞራልህ በቁጥጥር ስር
አውልልኝ ...እውነት ከደረስክባት እና ከያዝካት ከአንቀፅ 39 በኋላ
(ማለቴ ከግንጠላው በኋላ) እግሯንና አንገቷን..." ብዬ ሳልጨርሰው
ሁለቱ ፖሊሶች እየተከታተሉ በንፋስ ፍጥነት ከአጠገቤ ሲርቁ ሳስተውል
ክው ብዬ ራሴን መጠየቅ ጀመርኩ "በቃ ጆሮ ቀረ ማለት ነው?...አሁን
የዶሮ አንገትና እግሯ ምን ያደርግላቸዋል?...ዘንድሮኮ ከማዳመጥ
መሮጥ እየቀደመ ተቸገርን...ወይ ሳላስበው አንገቷ ላይ ጩባ
አድርጋለች ብያቸው ይሆን እንዴ?...ከተገንጣይ ላይ ለመካፈል
እንደዚህ መሮጥ አግባብ ነው?..ኦ ኦ!..ሳላስበው ቡተሊካን ነካካሁ
መሠለኝ...የኔ ጥያቄ የዶሮዬ ማምለጥ ነው እኔ እንደሌሎቹ ዶሮዬን
አስታክኬ ቡተሊካ አላወራም የስንት ዘመን መጠጫዬን
አጠራቅሜ..ስንት ዕቁብ ዕድሩን አዳርሼ የገዛሁት ዶሮዬ የሚገኝ ከሆነ
ግን ፓርቲ ባቋቁምም አይቆጨኝም። እንደውም ላቋቁም ይሆን
እንዴ?...የ.ዶ.ብ.ፓ.(የጠፋችው ዶሮዬ ብትገኝልኝ ፓርቲ)...12
ብልቶቹ ክልሎችን እና አዲሱን የዶሮ ማደሪያ ሽቦ... የሚወክል ሆኖ
(አይ የኔ ነገር አፈርኩ እኮ!...እንዴት ግን ሐበሻ ለራሱ አንድ ብልት
ወስዶ ዶሮን ብልት በብልት አደረገው?..አሁን ፈረሰኛ እንዴት ብልት
ሊሆን ይችላል?...ኦ..ኦ..እንደውም ይህቺን ጥያቄ በፓርቲዎች ስብሰባ
ላይ አንስቼ ጉድ ካላስባልኩ ምናለ በሉኝ..ተከታይ እንደሆነ
አላጣ...ስንቱ ማንን እንደሚከተል ጠፍቶት ሲያዛጋ አይደል
የሚውለው?)...ወይኔ ዶሮዬ ግን የት ደርሶ ይሆን?...ኧረ መኪና
እንዳይገጭብኝ ሌላውስ ሌላ ነው። ለነገሩ እንደዛ ከሆነስ ከቴሌቪዥን
ጣቢያዎች በአንዱ በዜና ሳላየው አላመሽም..'በዛሬው ዕለት 600 ብር
የተገዛ ዶሮ ሊያመልጥ ሲሞክር በመኪና ተገጭቶ ሆስፒታል ገብቶ
የሕክምና እርዳታ እየተደረገለት ይገኛል::'..ብሎ አንዱ ሲዘግብ
አላጣውም። ..ወይ አፋልጉኝ ልለጥፍ ይሆን?..እንዲህ ብዬ ልፃፈው?
'ተፈላጊ:-አንድ መልከ መልካም ነጭ እና ጥቁር ዶሮ...አካባቢውን ዞር
ዞር ብዬ ንፋስ ልውሰድ በሚል ተልካሻ ሰበብ ከገዢው መደብ(ማለቴ
ከገዢው እጅ) አፈትልኮ ከአካባቢው ተሠውሯል። ይሄንን ዶሮ አግኝቶ
ለባለቤቱ ላስረከበ ወገን ፈረሰኛው ጊዮርጊስ ውለታውን ይክፈለው።
ፈላጊ ባለጡሩምባው....''አይ ዶሮዬ ምነው የበላህ ሰውዬ አልጮህ
አለ?''...ለነገሩ ይሄንን የመሰለ ለበግ ሩብ ጉዳይ የሆነ ዶሮ ሰልቅጦ
እንደምን ይጮሃል?...እህህ...እስቲ ተዉኝ!!...ከራሴ ጋር አስፓልት
ዳር ቆሜ እንዲህ ስወዛገብ ..አንዲት ባልቴት መጥታ በእጄ የያዝኩትን
መዘፍዘፊያ ነጥቃኝ "ሌባ!!..ሰርተህ አትበላም?..ትልቅ ሰው
አይደለህ?..." ብላ በጩኸት ከገባሁበት ሐሳብ ስታናትበኝ
እያገላበጥኩ አያት ጀመር የአወራሯ ፍጥነት ከጠፋው ዶሮዬ ጋር
ተመሳስሎብኝ...ምናልባት ተቀይራ ብትሆንስ ይኸው ሴትዮዋ
እንደማያት ብልት በብልት ነች 12 ይሙላ አይሙላ እርግጠኛ
ባልሆንም...አይቼ ሳልጨርሳት ቂን ቂን እያለች እየለፈለፈች ዶሮዬን
ወደገዛሁበት አቅጣጫ ስትሄድ ተከትያት መሄድ ጀመርኩ...ጉዷን
ልየው ብዬ!!...ስትሄድ ስከተላት የሚለው የጋሽ ጥላሁን ገሠሠ ዘፈን
እንዳጋጣሚ ከአንድ ቡቲክ ሲያጅበኝ ምናልባት ግምቴ ትክክል ሊሆን
እንደሚችል እያሠብኩ ...መዘፍዘፊያዋን..ማለቴ ሴትዮዋን ወደ ዶሮ
እስክትቀየር በጉጉት እየተጠባበቅኩ እየተራመድኩ ነው። ዘንድሮ
ሁሉም እንደ እስስት በሚቀያየርበት ጊዜ ይህቺ ሴትዮ ወደ ዶሮነት
ብትቀየር ምኑ ያስገርማል?..ሴትዮዋ አንድ የዕንቁላል ሻጭ ጋር ዋጋ
ስትደራደር ሳይ ይበልጥ ጥርጣሬዬን ጨመረችው። እንዴት ይሄንን ሁሉ
ዕቃ ዘልላ ዕንቁላል ልትጠይቅ ቻለች?..ዕንቁላሉን እያገላበጠች
ስትፈትሽ ሳይ ለምን እንደሆነ እንጃ.. ልጇን ከገበያ እየፈለገች እንደሆነ
ተሰማኝ...አገላብጣ ካየች በኋላ አላገኘችውም መሰለኝ ጉዞዋን
ስትቀጥል እኔም መጨረሻዋን ልይ ብዬ ተከተልኳት...ሴትዮዋ አየሩን
በመዘፍዘፊያው እየቀዘፈች ከአንድ የሸቀጣ ሸቀጥ ሱቅ ስትገባ ጠጋ
ብዬ ማማተር ጀመርኩ..ከሴትዮዋ ፊት ለፊት ያየሁትን ነገር ግን ማመን
አልቻልኩም። ቁርጥ የጠፋውን ዶሮዬን የሚመስል ዶሮ አንድ እግሩ
ላይ ካሰርኩለት ከቤት ይዤ ከወጣሁት ቀይ ማሠሪያ ገመድ ሳይ
በድንጋጤ የማደርገው ጠፋኝ..የኔ ነው ብዬ ሐገር ምድሩን በአንድ
እግር ስለማቆም አሰብኩ ነገር ግን ታርጋ የለው ነገር በምናባቴ የኔ
መሆኑን ማሳመን እችላለሁ?.. ያ ዶሮዬ አይን ዓይኑን ትክ ብዬ ሳየው
እንዳጋጣሚ ሲጮህ ተስረቅራቂው ድምፁም የኔ ዶሮ መሆኑን
አረጋገጠልኝ። ሆኖም እንዴት እንዴት ብዬ የኔ የጠፋው ዶሮ እንደሆነ
ላሳምናቸው?...ወይ ስም የለው..ወይ መታወቂያ የለው...ወይ ብሄር
የለው ነገር...እንደጨነቀኝ እዛው ተገትሬ ፊት ለፊቴ የሚካሄደውን
ትንግርት እያየሁ ከቆየው በኋላ ቤት የሚጠብቀኝ ጭቅጭቅ በሃሳቤ
ውልብ ብሎ ሲያልፍ አንዳች ኃይል ገፍቶኝ ሱቁ ውስጥ ተገኘሁ።..ያቺ
መዘፍዘፊያዋ የኔን መግባት ስታይ በአሽሙር መሸርደድ ጀመረች..."አይ
እቴ!...ምነው ጥላ በዛብኝ...ይህቺን መዘፍዘፊያ ገዛች ተብሎ
ሲ.አይ.ኤ. ይመደብብኝ?..አዪ ዕድሌ...ዕድሌ ነው.." ...እኔም
የምናገረው ጠፍቶብኝ ዓይኔን ከዶሮዬ ሳልነቅል "እዚህ ሱቅ ካርድ
ይኖራል?"ስል...የመዘፍዘፊያዋ ድምፅ ድጋሜ አስተጋባብኝ "ወይ
ጉድ?!..ዶሮ በየት ሐገር ነው ካርድ የሚጠየቀው?..."...ሳላስበው
አንድ ቃል አሟልጮኝ ወጣ..."ይሄ ዶሮኮ..." ብዬ ከመጀመሬ ከሱቁ
ጓዳ ውስጥ አዲሷ ፍቅረኛዬ ስትወጣ ሳይ ሐሳቤን በእንጥልጥል
ተውኩት...መዘፍዘፊያዋም ከአፌ ያመለጠውን ቃል እስክቋጨው
እንደሚጠባበቅ በሚያሳብቅ ሁኔታ ስትገላምጠኝ
ብመለከትም...በፍቅረኛዬ ውብ ፈገግታ ተረትቼ አረፍተ ነገሩን መቋጫ
ሳላበጅለት ቀረሁ....አዲሷ ፍቅረኛዬም በአይኗ ጥቅሻ እንደማላውቃት
እንድሆን አሳወቀቺኝ(ስለቤተሠቦቿ ወግ አጥባቂነት ደጋግማ
ስለነገረቺኝ እኔም ወዲያው ነበር ምልክቷን የተረዳሁት)..."እ...ካርድ
ይኖራል?"..."አለ...ግን ባለመቶ ብቻ ነው...ልስጥህ?.." ስትለኝ
የሞት ሞቴን "አ...አዎ ስጪኝ" አልኳትና የሷንና የቤተሰቦቿን ማጅራት
መቺነት እየረገምኩ ከሱቁ ወጣሁ...እንግዲህ አንዳንዴ እንዲህ ነው።
ስጦታ መስጠት እንደማልወድ የገለፅኩላት ፍቅረኛዋ እኔ ብቻ
የማውቀው 700ብር ለሷና ለቤተሰቦቿ ሰጠሁኝ ግን ዕድሌ ሆነና
ተነጥቄ እንዳበረክት ተገደድኩ!!...እንኳን አደረሠሽ ውዴ!!..እንኳን
አደረሠሽ ውዴ!!...እንኳን አደረሠሽ ውዴ!!...እያልኩኝ የዶሮውን ገበያ
አቋርጬ ወደ ቤቴ ተመለስኩ...አይጣል...የአንዳንድ ቀን አዋዋል..!!

@wegoch
@wegoch
@wegoch
Forwarded from ግጥም ብቻ 📘 (👋ገብረዬ)
እግዚአብሔርን የሚያምንና የሚወድ ቢኖር፥ እርሱ በዚህ አንፀባራቂና የደስታ በዓል ደስ ይበለው፡፡ ብልህ አገልጋይ ቢኖር፥ እርሱ ወደ ጌታው ሐሴት ገብቶ ዕልል ይበል፡፡

በጾም የደከመ ቢኖር፥ አሁን ደመወዙን ይቀበል፡፡ በመጀመሪያው ሰዓት ወደ አምላኩ የቀረበ ቢኖር፥ ዛሬ ሽልማቱን ይውሰድ፡፡
በሦስተኛው ሰዓት የመጣ ቢኖር፥ እርሱ በዓሉን በምስጋና ያክብር፡፡ በስድስተኛው ሰዓት የደረሰ ቢኖር፥ አይጎድልበትምና አይጠራጠር፡፡ እስከ ዘጠነኛ ሰዓት የዘገየ ቢኖር፥ ሳይጠራጠር ይቅረብ፡፡ እስከ ዐሥራ አንደኛዋ ሰዓት የዘገየ ቢኖር፥ ስለ መዘግየቱ አይደንግጥ፡፡ ጌታ ቸር ነውና፤ በመጨረሻ የመጣውንም እንደ መጀመሪያው አድርጐ ይቀበሏልና፡፡ በዐሥራ አንደኛው ሰዓት ለመጣው ከመጀመሪያው ሰዓት አንሥቶ ሲደክም ከነበረው ጋራ እኩል ይሰጧልና፡፡
መጨረሻ ለመጣው ጌታ ምሕረቱን ይለግሰዋል፤ መጀመሪያ ለመጣውም ያስብለታል፡፡ ለአንደኛው ይሰጠዋል፤ ለሌላኛውም ጸጋውን ያድለዋል፡፡ ለአንደኛው መልካም ምግባሩን ይቀበልለታል፡፡ ለሌላኛውም መልካም ፍቃዱን ይቀበልለታል፡፡ ለአንዱ ምግባሩን ያከብርለታል፤ ለሌላኛውም በቅን ልቡና የሚያደርገውን ጥረት ያደንቅለታል፡፡ ስለዚህ ኹላችሁም ወደ ጌታችሁ ደስታ ግቡ፡፡

ፊተኞች ኋለኞችም ሆይ! እኩል ደመወዛችሁን ተቀበሉ፡፡ ባለጸጐች ድኾችም ሆይ! በአንድነት ዘምሩ፡፡ እናንተ ብርቱዎች ደካሞችም ሆይ! በዓሉን አክብሩት፡፡ እናንተ የጾማችሁ መጾም ያልቻላችሁም ሆይ! ዛሬ ላይ ደስ ይበላችሁ፡፡
መሠዊያው ሙሉ ነውና ኹሉም በማዕዱ ደስ ይበለው፡፡ ፍሪዳው የሰባ ነውና አንድ ሰው ስንኳ እንደ ተራበ እንዳይሔድ፡፡ ኹላችንም የእምነት በዓሉን እንካፈል፤ ከቸርነቱና ከፍቅሩ ሀብትም እንቋደስ፡፡

ማንም ስለ ድኽነቱ አይዘን፥ ኵላዊቷ መንግሥት ተገልጣለችና፡፡ ማንም በኃጢአቱ አያንባ፥ ከመቃብሩ የይቅርታ ብርሃን ተንቦግቧልና፡፡ ማንም ሞትን አይፍራ፥ የመድኃኒታችን ሞት ከዚህ ነጻ አውጥቶናልና፡፡ ለእርስዋ በመታዘዝም ጌታ አጥፍቷታልና፡፡
በሞቱ ሞትን ገደለው፡፡ ወደ ሲዖል በመውረድ ሲዖልን በዘበዘው፡፡

ኢሳይያስም አሰምቶ እንደ ተናገረ ሲዖል ከጌታችን ጋር ፊት ለፊት ተገናኘች፤ መረራትም! ከንቱ አድርጓታልና መረራት! ሸንግሏታልና መረራት! ሽሯታልና መረራት!
ነፍሳትን ይዛ እንዳታስቀር አስሯታልና መረራት!
[መቃብር የዕሩቅ ብእሲ] ሥጋ አገኘሁ ብላ ዋጠችው፤ ስትውጠው ግን እግዚአብሔር ኾኖ አገኘችው - መረራትም!

ሞት ሆይ! መውጊያህ ወዴት አለ? ሲዖል፥ መቃብርም ሆይ! ድል መንሣትህ ይዞም ማስቀረትህ ወዴት አለ?
ክርስቶስ ተነሣ፤ ሞት ሆይ፥ አንተም ጠፋህ!
ክርስቶስ ተነሣ፣ አጋንንትም አዘኑ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መላእክትም ሐሴት አደረጉ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ የሰው ሕይወትም ነጻ ወጣች!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መቃብርም ባዶ ኾነች!
ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ ለአንቀላፉት ኹሉ በኵር ኾኖላቸዋልና፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

@getem
@wegoch
ለመከራ የፈጠረኝ! Re
«ዘውድአለም ታደሠ»
ኮንዶሚኒየም መኖር ችግር ነው! ሁሉም ዶሮና በጉን በሩ ላይ አስሮ ብሎካችንን ኤልፎራ አስመስሏታል። እኔም ትናንት ሚስቴ በግ ካልገዛህ እያለች ስትነተርከኝ ጥቂት ብር ይዤ በግ ልገዛ ብወጣ አንድ ቀውላላ በግ ነጋዴ ሁለት ፊታቸው ላይ ከባድ ድብርት የሚታይባቸውን ከሲታ በጎች ይዞ ቆሞ አገኘሁና ጠጋ ብዬ
«ልትሸጣቸው ነው?» አልኩት
«እና ሐገር ላስጎበኛቸው ነው ካገሬ ይዣቸው የወጣሁት?» አለኝ
«እንደው ኩነኔ አይሆንም እነዚህን መግደል?» ስለው ፈጠን ብሎ
«አንቀህ ነው እንዴ ምትገድላቸው?» አለኝ
«አይ ያው በቢላም ቢሆን ...» ብዬ ሳልጨርስ
«ወንድሜ ካሳዘኑህ ውሰድና በጉዲፈቻ አሳድጋቸው» አለኝ
«እሺ ስንት ነች እቺ?» አልኩት ወደአንዷ እየጠቆምኩ
«በግ ታውቃለህ ማለት ነው። በጣም አስተዋይ በግ ነች እሷ» ብሎ ጀርባዋን መታ መታ ሲያደርጋት ወደጎን ፍንግል አለችና አቧራዋን አራግፋ ተነሳች።
«እኔ አስተውሎቷ ምን ይሰራልኛል ላስተምራት አይደለም እኮ ምወስዳት» ስለው
«ሁለት ሺ ብር ክፈል» አለኝ
«ሁለት ሺ ብርማ አታወጣም»
«በርግጥ ላታወጣ ትችላለች ነገር ግን እኔ ሁለት ሺ ብር ነው የሚያስፈልገኝ»
«ቀንስና ልውሰድልህ» አልኩት
«አይ ወዳጄ በጓን ግን አይተሃታል? ውስጠ ወይራ እኮ ነች። መፍዘዟን አትይ። በዚያ ላይ በእንክብካቤ ነው ያደለብኳት»
«ጭራሽ ደልባ ነው እንዲህ የከሳችው?»
«አዎና! በርግጥ እኔ ስብእናዋ ላይ ነው የሰራሁት። በጥሩ ስነምግባር ነው ያሳደግኋት» አለኝ ቆፍጠን ብሎ። ሳቄን ለመቆጣጠር እየሞከርኩ
«አንድ ሺ ብር ትሸጥልኛለ ...?» ብዬ ሳልጨርስ
«ውሰዳት!» አለኝ በደስታ ተሞልቶ።
ምነው ዝም ባልኩ ብዬ በይሉኝታ አንድ ሺ ብር ሰጥቼው በጓን ይዤ ልሄድ ስል መራመድ አቅቷት በቀስታ ስታዘግም
«ቃሬዛ ቢኖርኮ ደግ ነበር» አለኝ ሰውዬው በጉን በሃዘን እየሸኘ።
ተበሳጭቼ ዝም ብዬው ስሄድ
«ወንድሜ እንደው ለነፍስ ትሆንሃለች መጀመሪያ የህክምና እርዳታ አርግላት» አለኝ
መንገድ ላይ በጓን ያየ ሁሉ ከንፈሩን እየመጠጠ ያልፋል። አንዳንዱ እኔን እያየ አንገቱን በሃዘን ይነቀንቃል። በግ ላርድ ሳይሆን እንደአብርሃም ልጄን ልሰዋ ይዤ እየሄድኩ ነው ያስመሰሉት። ሽምቅቅ እንዳልኩ ቤት ደረስኩ። ሚስቴ በጓን እንዳየቻት
«ምንድነው ይዘህብኝ የመጣኸው?» ብላ ጮኸች። በጩኸቷ ከኔ ይልቅ የደነገጠችው በጓ ነች። አይኗን አስለምልማ መሬት ወደቀች! የመጀመሪያ ደረጃ እርዳታ ላደርግላት ሞከርኩ። አልነቃ ስትለኝ በአፌ ትንፋሽ ልሰጣት ሳጎነብስ ሚስቴ
«በዚህ አፍህ እኔ ከንፈር ጋር ድርሽ እንደማትል እወቀው!» ስትለኝ ቀና ብዬ መጨረሻዋን ማየት ጀመርኩ ..
ውይይ! አረፈች! በጣም የሚያሳዝን ሁኔታ ነው የገጠመኝ ጎበዝ።
ለሚስቴ «ያ ሙታን አስነሳለሁ ሚለው ነብይ ጋር ይዘናት እንሂድ ይሆን?» ስላት
«እሱ አክስቱ ሞታ ክፍለሐገር ሄዷል» አለችኝ። እሺ ምን ተሻለኝ ጓዶቼ?
«ቆይ ግን ...የግድ ስጋዋን ለመብላት እኛ ልንገድላት ይገባል እንዴ? ያው ሞት ሞት ነው። በቢላም ሞተች በድንጋጤ ያው መሞቷ አይቀርም!» ስል ሚስቴ ሶስት ግዜ አማትባ «በል አውጥተህ ጣል» አለች።
እኔ ግን ተስፋ አልቆረጥኩም! እቺን በግ እኮ ስጋዋን ፈልጌ ሳይሆን እንደበግ እንድትተውን ነው የገዛኋት። አክተር ደሞ አይሞትም
ኦህህህህህ! ተመስገን!
ነቅታለች ጎዶች «እልልልል ...» (አሉ እትዬ ዘርፌ የቤት እቃ (ማማሰያ ሳይቀር) እየሰረቀ ያሰለቻቸው ልጃቸው ሲታሰር)
እንዲህ ነው እንጂ በግ! ዝም ብሎ መሞት አለንዴ? እኛ ሳንፈቅድላትማ አትሞታትም! አልኩ ለሚስቴ (አንዳንዴኮ እንደ አፍሪካ መሪዎች ሚያደርገኝ ነገር አለ)
ሚስቴ መንቃቷን ስታይ «በል ቶሎ እረድልኝ» ብላ የአሉላ አባነጋን ሻሞላ የሚያህል ቢላ ይዛ መጣች።
«አሁን ለዚች በግ ይሄን የሚያህል ቢላ መጠቀም ተመጣጣኝ እርምጃ ነው ብለሽ ታስቢያለሽ?» አልኳት
«ወሬውን ተወውና ሳትሞት እረዳት» የሚል ቀጭን ትዛዝ ሰጠችኝ! ሻሞላውን ተቀብዬ ወደበጓ ስጠጋ አይኗን ከፈት አርጋ ቢላውን አየት አረገችና እንደሰው እንባዋ ባይኗ ሞልቶ ፀጥ አለችላችሁ! በቃ ሞተች!
ብቻ በጣም የሚያሳዝን ጉዳይ ነው የገጠመን ወገን! ከሚስቴ ጋር ያደርኩትን አዳር አዳር አትበሉት። ለሊት ላይ ጠጋ ብዬ እያቀፍኩ
«አይዞን እኛ ጤና የሚቀጥለው ፋሲካ ምን የመሰለ ሙክት ነው ምናርደው» ስላት እንደአለቃ ገብርሃና ገፍትራ ከግድግዳ ጋር አጋጨችኝ!
ኤጭ አሁንስ መረረኝ! ጌታ ሆይ ትመጣለህ ወይስ እኔ ልምጣ?

@wegoch
@wegoch
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from Melkam74 Digital Magazine
Melkam74 ቅፅ ፩ ቁጥር 5.pdf
3.2 MB
📠 መልካም74 ቅፅ ፩ ቁጥር 5

💰 ፓኬጅ ከገዙ በ 0.70 ብር ብቻ 💰
አንዳንድ ቀን
(ቡሩክ ካሳሁን)

እረፋዱ ላይ ኢንተርኔት ካፌ ገብቼ ፌስቡኬን ስፈሰቡክ ቆየውና ከፍዬ ተነስቼ ከወጣው፡፡ በኋላ ቅር ቀልቤን ስለቀፈፈኝ ተመልሼ ወደ ኢንተርኔት ካፌው ስገባ፤ ለካ አካውንቴን ሎግ አውት አላረኩትም ነበር፤ አንዱ ነውረኛ በእኔ አካውንት ገብቶ የመንግስት ባለስልጣናትና ሹማምንት ተሰብስበው የተነሱት ፎቶ ላይ ‹አስመሳይ ሌቦች› ብሎ ሊኮምት ሲል እጅ ከፊደል ያዝኩት፡፡ ከዛም በድንጋጤ
‹ኡኡኡኡ ብዬ ሳልጮህ በህግ አምላክ የጀመርከውን ነገር አቁም፤ በህግ፣ ለውጥ አደናቃፊ ነው ብዬ አሲዝሀለው› ስላልኩት ፈርቶ ለቀቀልኝ፤ እኔም ሎግ አውት እያረኩኝ ‹‹በራስህ አካውንት እንዲደረግ ማትፈልገውን በሰው አካውንት አታድርግ ነው፡፡› ሚለው መፅሃፈ ማርክ ዙከርበርግ ከመነሻው እስከ መድረሻው› ብዬ ገስጬው ወጣሁ፡፡ እስኪ አንድ ጊዜ የማርክ ወዳጅ አሜን ይበል እዚጋ!!! ፡-)
ከኢንተርኔት ካፌው ወጣሁና መንገድ እንደጀመርኩ ዝናብ ጀመረ፡፡ ተሯሩጬ አንድ ካፌ ገባሁ፡፡ ካፌው ውስጥ በጣም ብዙ ሰዎች ስለነበሩና የመቀመጫ እጥረት ስለነበረ አንድ ጠረቤዛ ላይ ለመጠቀም ሳይሆን ከበረከቱ ለመሳተፍ በሚመስል ሁኔታ በጣም ብዙ ሰዎች ተሰበሰብን፡፡ ሁሉም የየግሉን ይሰራል፤ ስማርት ፎን የያዙ ከስልካቸውጋ ሲያወሩ፤ ስማርት ፐርሰን የያዙ ደግሞ እርስ በእርስ ያወራሉ፡፡ ከሁለት ጓደኛሞች ጎን የነበረ አንድ ወጣት ስልኩን እየተጠቀመ ሁለቱ ጓደኛሞች እያወሩ በድንገት ተበሳጭቶ ስልኩን መጠቀም ያቆምና ‹ጀለሴ ወይ ዣንጥላ ይዤ ልቁም እንዴ አበሰበሺኝ እኮ፤ ካፊያ ፈርቼ ብገባ ዶፍ ለቀቅሺብኝ› አላቸው ሁለቱ ጓደኛሞች አፍጥጠው ‹ምነው?!› ብለው ጠየቁት
‹ስታወራ እኮ ሀምሌን ሆነክብኝ! እየተፋህብኝ ነው፡፡› መለሰላቸው ወደአንዱ እየተመለከተ
ጠብ ሊነሳ እንደሆነ ቀልቤ ስለነገረኝ ጠቡ ደግሞ ወደ ብሄር ግጭት ማደጉ ስለማይቀር “ዝናብ በስንት ጣዕሙ” ብዬ ካፌውን ጥዬ ወጣሁ፡፡ ዝናቡም አቁሟል፡፡ ወደ ሰፈር ለመመለስ ታክሲ ለመያዝ ስራመድ አንድ ሸምገል ያሉ ሰውዬ አየሁኝ፡፡ የ8ኛ ክፍል ሂሳብ መምህሬን አስታወሱኝ፤ የ8ኛ ክፍል መምህሬ አሁን አሁን ሳስባቸው በጣም ያስቁኛል፤ ያኔ ግን ያበሳጩኝ ነበር፡፡ ሰፈራችን ባለው በ“መማር ምን ሊበጀኝ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት” እኔ፣ ዱባለ እና ገጀረው አብረን ተምረናል፡፡ ከዱባለጋ አንድ ክፍል የሆንኩት ደግሞ (ዳዊት እንዳይመስልህ ወንድሜ 7ኛ ክፍልን ነው 3 ጊዜ ሀትሪክ የሰራው) ቢሆንም ከገጀራው ጋር ግን አንድ ክፍል የሆነው ዘግየት ብሎ ትምህርት ስለጀመረ ነው፡፡ ገጀራው የሰፈራችን ልጅ ባይሆን ኖሮ “መምህር ነው” ብለው ያስያዙንን ሁለት ልጆች እኔና ዱባለ ደፍረን አስይዘን ባልበላናቸው ነበር፡፡ ገጀራው እድሜው በጣም ትልቅ ነው፤ እኛ ብቻ ሳንሆን አስተማሪዎቹም ይፈሩታል፡፡ እኚ ሂሳብ መምህራችን እንኳን እኔን፣ ዱባለን እና መሰሎቻችንን ውሀ ቀጠነ ብለው ቤተ-እግዚሀር እንደ ገባ ውሻ ሲያንከለክሉን ሳሮንንና ገጀራውን ግን ያከብሯቸው ነበር፡፡(እዚጋ እንዳትሸወዱ ሳሮን የገጀራው እህት ወይም የስጋ ዝምድና ኖሯት አደለም ሂሳብ መምህራችን ሚያከብሯት፤ ይልቁንም የክፍላችን ቆንጆ ስለሆነችና አስተምረው ሲጨርሱ ከሷ ጎን ተቀምጠው ማውራት ስለሚወዱ ነው፡፡) ሂሳብ መምህራችን አንድ ጥያቄ ለተማሪው ይወረውሩና ተሸቀዳድመው እኔ ላይ ያፈጣሉ
‹አጅሬው እስኪ ተነስ! ይሄ ምንድን ነው?› ያፈጡባኛል መቼም ይጠይቁኛል አይባልም በዚ አኳኳን
እኔም ብድግ ብዬ ለመልሱ ሚቀራረብ መልስ ስሰጥ
‹ጨርሰዋ ደደብ!!!› ይሉኝና ወደ ዱባለ ዞር ብለው ‹ተነስ አንተኛው!› ይሉታል
ዱባለም ተነስቶ ፀጉሩን ያፍተለትላል
‹ተናገር እንጂ ምን ይለጉምሀል! አለምዘላለምህን ማትሻሻል 7ኛ ክፍልን ሀትሪክ ሰርተክ 8ኛ ደረስክ ይኸው እዚህም ቁጭ ብለህ ቂጥህን ከመደፍጠጥ የዘለለ ምንም አትሰራም፤ ቁጭበል ዶማ!› ይሉና ከዱባለ ኋላ ገጀራው አለ፤ ወደሱ ገና ማየት ሲጀምሩ.. ሳይጠይቁት ‹አላውቀውም!› ብሎ በልበ ሙሉነት ይመልስላቸዋል፡፡
‹ጎሽ! እንደዚ ነው ሚባለው፡፡ ካላወክ አላውቅም አትልም አንት ደደብ!!!› መልሰው ዱባለ ላይ ያፈጣሉ፡፡ ዱባለ አንገቱን ሰብሮ ፀጉሩን ያፍተለትላል፡፡ ‹እስኪ ሳሮን ሞክሪ› ብለው ወደሷ ይዞራሉ፡፡ (ለወትሮው እንደምታረገው በጣም የከበዳትን በአይኗ ስትነግራቸው እራሳቸው ይመልሳሉ፤ የቀለላትን ግን ተነስታ ትሞክራለች፡፡) ሳሮን በቄንጥ ተነሳችና እኔ የተናገሩኩትን ቃል በቃል ስትናገር (የኮፒ ራይት መብትኮ እዚ ሀገር አይሰራም ብዬክ ነበር አልኩት ለበድሉ ጠጋ ብዬ) ገና ሳትጨርሰው ከአፏ ተቀብለው እራሳቸው አሟሉትና ‹ጎበዝ ልጅ! እዚ ከድንጋይ ጋር ተቀምጠሸ ግንበኛ አስመሰሉሽ› ብለው እሷን ለማሞገስ እኛን ይሰድባሉ፡፡
አይ ሂሳብ መምህሬ ብዙ ታሪክ ሰርተዋል እኮ አልተፃፈላቸውም እንጂ፡፡ የታክሲ የመጨረሻውን ሰልፍ ለማግኘት ስራመድ ተባራሪ ታክሲ አግኝቼ ገባሁ፡፡ ሂሳብ ስሰጠው ለሰልፉ ጫፍ ስጓዝ አንድ ፌርማታ እንደመጣሁና ተጨማሪ ብር ከሀምሳ እንደሚያስከፈለኝ በታላቅ ማመነጫጨቅ ወያላው አበሰረኝ፡፡

@wegoch
@wegoch
ማንም ከኢትዮጵያዊነት ማማ ሊያወርደኝ አይችልም!
(ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ)
ለእኔ ቋንቋዬ የሀሳብ መግለጫ፣ ባህሌ የአኗኗሬ መንገድ ብቻ ነው፡፡
እናቴ ጉራጌ ናት – ክስታኔ፡፡ አባቴና አባቱ ክስታንኛ አቀላጥፈው የሚናገሩትን ያህል ኦሮምኛም ይናገራሉ፡፡ በድሉ – ዋቅጅራ – ደበላ – ወልደጊዮርጊስ – ካሳ እያለ የሚዘልቀው የአባቴ ወገን መጠሪያ ሌሎችን የሚያስጨንቃቸውን፣ ግራ የሚያጋባቸውን ያህል እኔን
አስጨንቆኝ አያውቅም፤ ግራም አያጋባኝም፡፡ የማያስጨንቀኝ እነሱን ስለምጠየፍ አይደለም፡፡ የማያስጨንቀኝ በማኛቸውም ማንነት ማንነቴን መበየን፣ ስለማልፈልግ ነው፡፡
እናቴ ኬርአለም ክስታኔ ናት፤ አባቴና አያቴ የኦሮሞና የጉራጌ ድብልቅ ሊሆኑ ይችላሉ፤ ወልደጊዮርጊስና ካሳ ትግሬ ወይም አማራ ሊሆኑም ላይሆኑም ይችላሉ፡፡ እኔ ውስጥ ያለው ግን ከነዚህ ሰዎች ጎሳ በላይ ነው፡፡ እኔ ውስጥ በደም ከዝርያዎቼ ከተቀበልኩት ይልቅ፣ ካደግኩበት የኦሮሞ ማህበረሰብ ከልጅነት እስከ ጉርምስና የቀሰምኩት ይበልጣል፡፡
በወጣትነቴ ባሌ ለሦስት አመታት፣ ጎንደርና ጎጃም ለአሥር አመታት ስኖር ማንነታቸውን አትመውብኛል፡፡ ባህር ተሻግሬም አውሮፓ ላይ ያን ያህል ኖሬያለሁ፡፡ ታዲያ እንዴት ነው የእኔን ማንነት በእናትና አባቴ ጎሳ (ምንም ይሁን ምን) የሚገለጸው?
አዎ የክስታኝና ቋንቋን አፌን ፈትቼበታለሁ፤ እርግጥ ነው በጉራጌና በኦሮሞ ባህል ከልደት እስከ ጉርምስና ጥሪት ቋጥሬበታለሁ፤ አንድም ቀን ግን እራሴን ጉራጌ ወይም ኦሮሞ ብዬው አላውቅም፡፡
ላለፉት ሃያ አምስት አመታት ማንነትን በጎሳ የመበየን ፖለቲካ ተንሰራፍቶ እንኳን ጎሳዬን የማንነቴ መበየኛ አድርጌው፣ ወይን ሆኖ ተሰምቶኝ አላውቅም፡፡ ለዚህ ነው ጉራጌ ወይም ኦሮሞ መሆን አለመሆኔ የማያስጨንቀኝ፡፡
እኔ ከዚያ የበለጠ ሳልሸራረፍ የሚገልጠኝ ማንነት አለኝ –
# ኢትዮጵያዊነት

@wegoch
@wegoch
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
"መሄድ መምጣቱን ዕብደት በሚመስል መልኩ በጣም ዕወደው ነበር" ትለኛለች ግርምቴ በጣም እንዳደምጣት አድርጎኛል። ዓይኔን ከአይኖቿ መንቀል አልፈልግም።እንድታወራኝ ፣ እንዳላቋርጣት ፣ እያዳመጥኩሽ ነው ፣ታሪክሽን ወድጄዋለሁ እያልኳት እንደሆነ እንዲገባት። "ታውቂያለሽ ይሄ የተለየ ባህሪዬ ሳይሆን አይቀርም። ማንም ሰው እንዲህ እያለ ሲያወራ ሰምቼው አላውቅም። ለነገሩ እኔ ብዙ ሰው አልቀርብም። ሁሌ አብሮኝ ሲሆን ይሰለቸኛል። ደሞ ትንሽ ራቅ ሲለኝ እጅጉን ይናፍቀኛል። ድፍን ሰባት ዓመታትን በዚህ ሁኔታ አሳልፈናል። ሁለት ዓመት ለትምህርት ማሌዢያ ቆይቼ ስመጣ ፡ ቤቱ ምንም አልተቀየረም። ሁሉም ዕቃዎች እንዳሉ ናቸው። ቦታቸው እንኳን አልተለዋወጠም። እንዴት ሴት አትመጣም እዚህ ቤት? እላለሁ በውስጤ።አውቃለኋ ፡ ሴት የሚያመጣ ቢሆን የቤቱን ጠረን መለየት እችላለሁ።" "ስሚኝማ እኔኮ ለሁለት ዓመታት ከሱ ተለይቼ ትምህርት ላይ በነበርኩ ጊዜ ከአንድም ሁለት ወንድ አውቃለሁ። በእርግጥ ኢትዮጵያ እያለሁ ቢሄድም ቢመጣም ምንም ነገር መሀል ላይ አይገባም ። ማንም ወንድ እንዲገባ ዕድል ሰጥቼው አላውቅም። አንዳንዴ...እኔ ከዚህ ልጅ የምፈልገው ምንድነው? ስል ራሴን እጠይቃለሁ። ምላሼ ምን እንደሆነ ተረድቼው ግን ኣላውቅም። ተጋብተን ልጆች እንድንወልድ እንስማማና ድንገት የሚሰለቸኝ ነገር ይኖራል። የሚገርምሽ
...ኣንዳንዴ ዕብደት መሳይ ስሜት ይሰማኛል። እንዲሄድ እመኛለሁ ፡እንዲናፍቀኝ ፣ ሌላ ሴት ይዞ እንድቀና እመኛለሁ። እሱ ግን በጭራሽ አያደርገውም ነበር! " "ከ 3 ዓመት በፊት ምን ሆነ መሰለሽ? ቤት አሟላን ፡ ልንጋባ ፣ ልጆች ልንወልድ ፣ ቤተሰብ ልንመሰርት ሃሃሃ(ረጅም ሳቅ) ከዛ ብድግ ብዬ ስልክ አለማንሳት ፡ እሱን አለማግኘት ምናምን ሆነ ስራዬ ለ 4 ወራት ያህል። አልገርምም? ከዛ በ 4ኛ ወሬ ቀጥ ብዬ አንድ ሰኞ ቀን ማታ ቤቱ ሄድኩኝ። ቁልፍ ስላለኝ ቤት ባይኖርም ከፍቼ ገብቼ ጠብቀዋለሁ ብዬ።ስገባ አልጋ ላይ ጋደም ብሎ መፅሀፍ እያነበበ አገኘሁት። በምን ፍጥነት እንደሆነ አላውቅም ብድግ ብሎ ስንተቃቀፍ። ለረጅም ሰዓት ተቃቅፈን ቆየን፡ አልተቀመጥንም ተያይዘን ወጣን ፡ ራት በላን ፡ ከተማዋን ስናካልላት ሊነጋ ሲል ቤታችን ገብተን ተኛን። እንደዚህ ያሉ ሰዎች ገጥመውሽ ያውቃሉ?" አለችኝና ዓይኔን ተመለከተች። ጭንቅላቴን ብቻ በማወዛወዝ ገጥመውኝ እንደማያውቁ መለስኩላት። በቃላት ቢሆን ምላሼ፡ እንደማቋርጣት ስለተሰማኝ ቃል ማውጣት አልፈለኩም። "እኛ ብቻ የሆን ይመስለኛል የምር። እና እንደዛ ሆነን አድረን በማግስቱ ስራ ቀርተን ቤት ዋልን። ከዛ ለ 3ሳምንታት በጥሩ መዋደድ ከቆየን በኋላ ነበር ሁለተኛ ዲግሪዬን ልሰራ ከሀገር የወጣሁት። ስመለስ ሁሉም ነገር በቦታው ነበር። እዛ እያለሁም በየመሀሉ እንደዋወል ነበር፡ በፅሁፍ መልዕክቶች እናወራ ነበር ምናምን። ትምህርቴን ጨርሼ ከመጣሁ 6 ወራት ገደማ ሆኖኛል። በቀደም ቅዳሜ ዕለት እንደልማዴ ከ 2 ወራት ምናምን የመኮራረፍ ስሜት በኋላ፡እቤቱ ስሄድ ገና ከመግቢያው ጀምሮ አዲስ ነገር አየሁ። በሩ ላይ የእግር መርግጫ ወይም የቆሻሻ ጫማ መጥረጊያ የሚመስል ትንሽዬ ምንጣፍ ነገር ተነጥፏል። አለወትሮው የቤቱ ጠረን ሰው ሰው ይሸታል። ማለቴ እም . . . ብቻ ሰው ያለበት ቤት ይመስላል። አለ አይደል ህይወት ያለው ፣ደስ የሚል ምግብ የሚበስልበት ፣ቡና የሚፈላበት ቤት፣ ጧት ላይ ቆንጆ ቁርስ የሚበላበት፣ እራት ሰዓት በሚያማምሩ ዕቃዎች የተሞላ የምግብ ጠረጴዛ ያለው የሚመስል፡ ሳቅ የሚደምቅበት ፡ክረምት የሚሞቅበት ፣ማታ የምትናፍቂው ዓይነት ጠረን ያለው ቤት መሰለኝ። ልግባ ልመለስ በሚል ማመንታት ውስጥ ሆኜ ፡ ይሄ ቤትማ የሚኩ አይሆንም አልኩ ለአፌ። ልቤ ግን የሆነ ያወቀው ነገር አለ። ልቤን ማመን አልፈለኩም። በር ላይ እንደቆምኩ ሰው ቢያየኝ ምን ይለኛል ብዬ ደንገጥ አልኩና ፡ እግሬ የሆነ ሸክም እየመሰለኝ ዓይነት ነገር ጎ~ተ~ት አድርጌው ተጉዤ በሩን እንደማንኳኳት አደረኩኝ። የምታምር ፣ ከቆንጆ፣ ዘናጭ ከሆነች ሴት፣ የምትወደድ ዓይነት ፣በስራ ቦታ ፣በቤተሰቦቿ ፣ በጓደኞቿ የምትከበር ፣ታድለሽ ምናምን የምትባል
ዓይነት ሴት ድምፅ "ማነው?" ስትል ተሰማኝ። ያን የመሰለ ድምፅ አልጠላሁትም መሰለሽ? ቀጥ ብዬ ገባሁ ቤቱ ተለውጧል። ቀና ስል ግድግዳው ላይ ሚኪን የሚመስል ወንድ ፊት ለፊት ከቆመችው ሴት ጋር በትልቁ ፎቶግራፋቸው አለ። እንግዳ እንዳልሆንኩባት ታስታውቃለች። ፊቷ ጠይም ፡ ሞላ ያለ፡ ዓይኖቿ የሚያምሩ ፡ ሙሉ ፈገግታ የሚታይባት ሴት ነች። ምን ያስቃታል? አልኩኝ በልቤ። የሚኪ የወንድሙ ሚስት መሆን አለባት። አይገርምም ሚኪ እሱን የሚመስል ወንድም አለው ማለት ነው? ቤቱን የቀየረው ብቻዬን ከሆንኩ ይሄ ትልቅ ቤት
ምን ያደርግልኛል እናንተ ኑሩበት ብሏቸው ሰጥቷቸው ሌላ አነሰ ያለ ቤት ተከራይቶ ነው ማለት ነው? እያልኩ ሳስብ "ፀጊ ደህና ነሽ"? አለችኝ በማርያም ምን ሆኜ እንደደነገጥኩ አትጠይቂኝ.." ሚኪ ቤት የለም ለስራ ወደ ክፍለሀገር ወጥቷል።ትላንት ነው የሄደው" አለችኝ።
አፌ የሆነ ነገር ለመናገር ተከፍቶ አንደበቴ ግን ተይዞ እንደነበር አስታውሳለሁ። አዎ አፌን ከፍቼ ነበር። ከትንሽ ዝምታ በኋላ ደፍሬ ጠየኳት። ከ 2 ኣመት በፊት ይሰራበት የነበረ መስሪያ ቤት ውስጥ ፡የስራ ባልደረባው የነበረች ሴት እንደሆነች ፡እኔን በዝና እና በፎቶዬ በጣም ታውቀኝ እንደነበር ዓይነት ነገር ፡ከሚኩ ጋር የፍቅር ግንኙነት በጀመሩ በ3ኛው ሳምንት ምክር ቤት ተፈራርመው ጋብቻ እንደመሰረቱ ፣አሁን የ 1 ወር ከ15 ቀን ነብሰ ጡር እንደሆነች ነገረችኝ"
። ከዛ በዝምታ ለብዙ ደቂቃ እንደተቀመጥኩ የገባኝ በማግስቱ ጧት ላይ ነበር። በምን ዓይነት ሀኔታ ውስጥ ፣ እንዴት ባለ ስሜት እና በምን ትራንስፖርት
እንደሄድኩ እንኳን ሳላውቅ ራሴን ጧት አልጋ ላይ አግኝቼዋለሁ። ከፍቶኝ ይሁን ፣
ባዶነት ስሜት ተሰምቶኝ ፣ፀፅቶኝ ፣ቁጭት ውስጤ ገብቶ በውል እንኳን
አላውቀውም ምን እንደዛ እንዳደረገኝ።
ቀሽም ሴት ነኝ አይደል? ዕቅድ ፣ተስፋ የሌለኝ ፣ህይወት ትርጉሟ የተዛባችብኝ? አለችኝና እጇ ላይ የነበረውን በብርጭቆ የተቀዳውን አልኮል መጠጥ በአንድ ትንፋሽ ጨርሳ ብርጭቆውን እንደያዘችው ቀና አለች። ዓይኖቻችን ሲገጣጠሙ እያዳመጥኳት እንደሆነ ስታውቅ "እና ሚኩ ጥፋተኛ
ነው? እሺ እኔስ አፍ አለኝ? ለምን ብዬ የመጠየቅ? ቤት ውስጥ ያለችውስ ሚስቱ ምን ጥፋት አለባት? ቆይ እንዳገባ ሲያውቅ ለምን ቤቱን አልቀየረም? ይሄንን ሁሉ ጊዜ አብረን ስንሆን በመሀከላችን ሁለታችንንም የሚያውቅ ሰው የለም ማለት ነው? እንዴት አልሰማሁም ማግባቱን?" እያለች ራሷንም እኔንም ትጠይቃለች። አጎነበስኩ ግራ ገብቶኝ ፡ የምላት ፣የምመልስላት ፡መልስ ማገኝ ይመስል ወደ መሬት ዝቅ ብዬ አያለሁ። እንደዚህ ሆና አላውቃትም። ለነገሮች ሁሉ ቸልተኛ እንደሆነች ነበር የማውቀው። የሚሆነው ይሆናል ካልሆነም ይቀራል የምትል ዓይነት ሴት። ከስራ ስወጣ እንደምትፈልገኝ ነግራኝ ነበር የተገናኘነው። ፀፀት ያንገበገበው ስሜት ዓይኗ ውስጥ አይባታለሁ። አይዞሽ ፣በርቺ ፣ጠንከር በይ ፡ያልፋል ፡ ሁሉም ሰው የሚያጋጥመው ነው ምናምን የሚባሉት ማፅናኛዎች ይጠቅሟታል? ያስፈልጋታል? ቦታቸው ናቸው? ራሷን እየቀጣች እንደሆነ ይሰማኛል ምን ግዜ የታክሲ ደንበኛዋን እንደጠራች አላየኋትም ብድግ ብላ በአግባቡ ሳትሰናበተኝ እያየኋት ሄዳ ገባች...ሌላ መተላለፍ!

@getem
@getem
@paappii

#Tersid kebede
#እንድቅትዮን
ዕንቁላል ፋብሪካ በሚገኘው በገነት መናፈሻ
#ማክሰኞ ሚያዚያ 29 2011ዓ.ም.
አመሻሹ 11:30
መግቢያ ዋጋ 50 ብር

@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
ስራ እና የስራ ልምድ
(ቡሩክ ካሳሁን)

በሀገራችን እየተበራከተ ለመጣው የስራ አጥ ቁጥር ማሻቀብ ምንም እንኳን ብዙ ምክንያት ቢኖሩትም ለእኔ ግን በዋናነት የሚታየኝ ስራ በሌለባት ሀገር ውስጥ የስራ ልምድ ማፈላለጉ ይመስለኛል፡፡ አስቡት እስኪ ስራ በሌለባት ሀገር “የስራ ልምድ” እየጠየቁ “ስራ” መከልከል፤ የማያልቅ አዙሪት ውስጥ መግባት ነው፡፡ “ስራ የሌለኝ የስራ ልምድ ስለሌለኝ ነው፡፡ የስራ ልምድ የሌለኝ ስራ ስለሌለኝ ነው፡፡” የሚል አዙሪት ውስጥ መዘፈቅ፡፡ አንድ ግዜ ጓደኛዬ ዱባለ በ“የስራ ልምድ” እና በ“ስራ” ጠኔ ሲመታ ከዚህ ችግር ለማምለጥ የተጠቀመው ስራ አገኝበታለው ብሎ ባሰበው ሙያ ሀሰተኛ “የትምህርት ማስረጃ” እና “የስራ ልምድ” በማጋጀት ወደ ሰርቶ አደር ማህበረሰብ ራሱን መቀላቀል ነበር፡፡ ያም ቢሆን ቀላል አልሆነለትም፡፡ የውበት ባለሙያ እንደሆነና በዛም ልምድ እዳለው አድርጎ ያዘጋጀው ዱባለ ከተማችን ላይ አለ የተባለ የውበት ሳሎን ሊቀጠር ተወዳደረ፡፡ ልምዱና ማስረጃዎቹ ጥሩ ተደርገው ስለተሰሩ በቀዳሚነት ከተወዳዳሪዎቹ ተመርጦ ለተግባር ፈተና ተቀጠረ፡፡ ይህን ጊዜ ታዲያ ዱባለ ‹‹ለካ አዳሜ እንደዚ ነው ስራ የያዘው፡፡ ስራ የማይዙት ልምድ የሌላቸው ሳይሆኑ የዋሆች ናቸው፡፡›› አለ፡፡
በዱባለ እድል ጠማማነት ብተማመንም እንደዚ ይከፋበታል ብዬ ግን አስቤ አላውቅም፡፡ የተወዳደረበት የስራ መደብ የፌሻል (የፊት ውበት) ስራ ረዳት ባለሙያ ለመሆን ነበር፡፡ ነገር ግን የስራ እድሜው ከተግባር ፈተና አልዘለለም፡፡ ለፈተና በሄደ ሰዓት የተከሰተውን እንደሚከተለው አድርጎ አጫወተኝ…
‹‹ ሚገርም እኮ ነው! እኔ ሴቶች ይመጣሉ ብዬ ለዛውም ሀብታሞች ፊታቸው የጠራ፣ የበራ እንዲሁ የውበት ሳሎን ለመግባት እንጂ መሰራት ማያስፈልጋቸው ቆነጃጅት ስጠብቅ ወዳጄ የመጣው መንግስቱ ሀ/ማርያምን የመሰለ ሰውዬ፡፡ በመጀመሪያ ‹ይቅርታ ብርጭቆ ወረቀት ጨርሰናል› ብዬ አግባብቼ ልመልሰው ሞክሬ ነበር፡፡ ጭራሽ ፊቱን አኮሳትሮ የስራዬን ክብደት በአጭሩ አስረዳኝ፡፡ ዋናዋ የፌሻል ስራ ባለሙያዋ መጣችና ሰውየውን ፊቱን ለመስራት የሚደረገውን ቅድመ ዝግጅት እንዳደርግለትና የቆዳውን አይነት (ስኪን ታይፕ) ለይቼ እንድጠብቃት ነግራኝ ሄደች፡፡ ወንበር ላይ አስቀምጬ ፎጣ ካለበስኩት በኋላ ትኩር ብዬ የፊቱን ቆዳ እሷ እስክትመጣ ድረስ ስመለከት ቆየሁ፡፡ ጓንት አድርጋ ስትመጣ እሷም እንደ እኔ የሰውየው ፊት ከብዷት (ቀፏት ከማለት ይሻላል) ጓንት አድርጋ የመጣች መስሎኝ ነበር ለካ ደንብ ነው፡፡ ካጠገቤ ቆማ ቅባቶችን እያወጣች
‹የቆዳውን አይነት ለየኸው?› ብላ ጠየቀችኝ
‹አዎ ለይቼዋለው የሰው ቆዳ አይነት ነው›› መለስኩላት
ሰውየው አፈጠጠብኝ!
‹ምን?!› ብላ መልሳ ጠየቀችኝ፡፡ ባታምነኝ ነው ብዬ ‹አገላብጠሸ እዪው ሲታይ አይመስልም እንጂ የሰው ቆዳ ነው፡፡ ምን አስዋሸኝ ዘመዴ አይደል› አልኳት፡፡
‹ቀስ ብለህ ጋውኑን አውልቅና ከዚህ ውጣ!› አለችኝ አይኗን እያጉረጠረጠች
‹እና አንቺን ለማስደሰት የአዞ ቆዳ ነው ልበልሽ? ገፈሽ አትሸጪው ምን ያረግልሻል አይነቱ? አርፈሽ ሚሰራውን ሰርተሽ ብርሽን አትቀበዪም?›
‹ጥበቃ ሳልጠራ ውጣ!› አንባረቀችብኝ፡፡ እኔም በኋላ ፖሊስጋ ወስዳኝ ከነማስረጃዬ መቀመቅ እንዳልወርድ ላጥ ላጥ ብዬ ወጣሁአ ››
.
.
.
@wegoch
@wegoch
@burukassahunC
ኢትዮጵያ እግር ኳስ¿¡ ወይስ ኳስ ራስ?!
(ቡሩክ ካሳሁን)

ከማልወዳቸውም ከማልጠላቸውም ነገሮች አንዱ እግር ኳስ ነው፡፡ እኔ በህይወቴ በእግር ኳስ ያለ አንድ ቀን ተበሳጭቼም ይሁን አዝኜ አላውቅም፡፡ አንድ ጊዜ ትዝ ይለኛል ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ዋንጫ አልፋ ከማን ጋር ተጋጥማ ይሁን አላውቀውም (ሳስበው ግን ከማድሪድጋ ይመስለኛል) ተጠበጠበች አልኳቹ ተጠበጠበች! (ሀገራችንን ሲጠበጥቡ ኸረ መላ በሉ እያልኳቹ ሰሚ አጥቼ ይኸው ዳኛዎቻችን መጠብጠብ ጀመሩ)፡፡ እና ያው የሀገር ጉዳይ ነበር ጨጓራዬ ሲነድ አደረ ሲነድ፡፡ ( እኔኮ መሸነፉን ይሸነፉ ግዴለም፤ ሰው 50 ብር ሊያሲዝ ይችላል ብለው ገምተው ቢጫወቱ ምናለበት፡፡ ይኸው እስከዛሬ በዛች 50 ብር ምክንያት ጨጓራዬ ይነዳል፤ ደግሞኮ ከእስፖርት ፌዴሬሽንጋ ነበር ያስያዝኩት።)
እግር ኳስን አጥብቄ ባልወድም የሚወዱ ሰዎችን መብት አልጋፋም፡፡(አንዳንዶች ግን ኳስ ከመውደድም አልፈው የሚወልዱ ሁላ ይመስላቸዋል፡፡) ነገር ግን አንድ ሰው ኳስን እንደ ኳስ እንጂ ኳስ ራስ ሆኖ ሲደግፍም ሆነ ሲጫወት ማየት አልወድም፡፡ (አልወድማ ደስ አይለኝም፡፡) እነዚ ኳስ ራሶች ተጫዋች ከሆኑ ልክ ሲናደዱ በዳኛውና በኳሱ መካከል ያለው ልዩነት ይጠፋባቸውና በቃ ዳኛውን እያጣጠፉ ወደ ጎል ይለጉታል፡፡ እዚጋ ግን ዳኛዎቹ ብዙ ጊዜ ያስቸግራሉ፤ ሚሮጡት ነገር አለ፡፡ ምን አለበት እስኪ ኳስ ሆነው ሃላፊነታቸውን ቢወጡ፡፡ ደግሞ አንዳንዱ ተጫዋች ህግ አያከብርም ወስዶ ዳኛውን በቦክስ፣ በጡጫ ያጣድፈዋል ይሄ እኮ ‹ማኖ› እኮ ነው፡፡ ፋራ ነው እንዴ፡፡ ልክ ግን እንደዚ ‹ማኖ› ሲነካ ያው ፌደራሎች እንደዳኛ ያገለግላሉ (ኢትዮጵያም አይደል ያለነው) እየሮጠ አንዱ ፌደራል ይመጣና ዳኛውን በቦክስ ሚነድሉትን ገለል ካደረገ በኋላ ለተቃራኒ ቡድን ቅጣት ምት እንዲመቱ ዳኛውን አመቻችቶላቸው ይሄዳላ፡፡ ዘጠና ደቂቃዋ እስክታልቅ የበረታ ዳኛ እየሮጠም እየተጎተተም ተጫዋቾቹን የማዳከም ስልት ይጠቀማል፡፡ (እዚጋ ደግሞ ለእድለ ቢስ ዳኛ በደከመ ተጫዋች ሌላ ተቀያሪ ገብቶ ያበጥረዋል፤ በጣም እድለቢስ ሲሆን ደግሞ ተቀያሪ ተጫዋች ባይኖር እንኳን የቡድን መሪው ገብቶ ያገላብጠዋል፡፡) እና በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ የጎድን አጥንት ያለው ዳኛ ማግኘት ከባድ ነው፡፡
ደጋፊ ደግሞ ኳስ ራስ ሲሆን የሚከተሉት ምልክቶች ይታይበታል፡፡ ሚደግፈው ቡድን ሲያሸንፍ፤ ተንደርድሮ ድራፍት ቤት ይገባና ሂሳብ በኔ ነው ይላል እዛኮ ልጁ ሂሳብ ደብተር ጨርሶ ግዛልኝ ካለው ወር አልፎታል፡፡ አንዳንዱ ደግሞ ጥግብ ብሎ ይሰክርና አስፋልት መንገድ ዘግቶ አንቡላንስ አሳልፈኝ ሲለው ቀስ በል እስኪ ወተት ጥደሀል ይለዋል (እንደነዚ አይነቶቹ ላይ ፌደራሎቻችን የፈላ ወተት ቢደፉባቸው የወተት መግዣ ቦንድ እገዛለው)፡፡ የኳስ እራሶች ችግር ግን ጎለቶ ሚወጣው የተሸነፉ እለት ነው፡፡ ከሜዳ ውስጥ ይጀምራሉ፡፡ ገና ጨዋታው እየተኪያሄደ እንደሚሸነፉ ቆሌያቸው ሲነግራቸው ‹ዋ.ዋ.ዋ…› ይሉታል ዳኛውን በህብረት፡፡ ያን ጊዜ ዳኛው ስልክ ደውሎ ቤተሰብ ይሰናበታል፤ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አልጋ ያሲዝና ብሞት እንኳን የጀግና ሞት ልሙት ብሎ ጨዋታውን ያስጨርሳል፡፡ መጨረሻ ላይ እነዚ ኳስ ራሶች በመጀመሪያ ዳኛውን ከተጫዋቾች የተረፈ የጎድን አጥንት ካለው ጎኑን እየዳበሱ አረጋግጠው እየረገጡ ይሰብሩለታል (ደግነቱ ሳያረጋግጡ አይረግጡም :-) ) ከዛ በወንበር ከባላጋራቸው ደጋፊጋ ይከሳከሳሉ፡፡ በቸርነቱና በምህረቱ ተርፎ ወደቤቱ የተመለሰ ደጋፊ ደግሞ ‹ነገ ስራ ገቢ ስለሆንኩ ስትራፖ እንዳይዘኝ› ብሎ ሚስቱን የዳኛውን ጽዋ ያቃምሳታል፡፡ ታዲያ እኔ እንዴት አርጌ ኳስ ራሶችን ልውደድ!?፡፡ (እነዚ ኳስ ራሶች ግን ተጫዋችም ሆነ ደጋፊ caseአቸው ይሄ በጫማ ጥፊ ሰይጣን በሚያወጣው ፓስተር ቢታይ ሚበጅ ይመስለኛል። እሾህን በእሾህ ነው ዘመዴ።)
ለዳኞች ለወደፊት ምክር
የትኛውንም አይነት የኢትዮጰያ ጨዋታ ከማጫወታቹ በፊት ‹ለህይወቴ ያሰጋኛል› ብላቹ ፖሊስ ጣቢያ አመልክቱ፡፡ ከፌደራል ፖሊሶች የመስታወት ጋሻ ብትዋሱ 30 ፐርሰንት የመትረፍ እድላችሁን ታሰፋላቹ፡፡ በተለይ ስማቸው ላይ ‹ወ› ያለበት ቡድን ስታጫውቱ ከመወሰናቹ በፊት የቡድን መሪውን አማክሩ (ማምሺያም እድሜ ነው)፡፡ ደግሞ ፀብ ሲነሳ ስትሮጡ ለፍጥነት እንዲረዳቹ ታኬታችሁን አውልቃቹ በእጃቹ ይዛቹ ፈትለክ በሉ (ከፊት ሚመጣም ካለ በታኬታው ድው)፡፡ከዚ ሁላ ጥረት በኋላ ግን ከነዚ ኳስ ራስ እጆች ላይ ከወደቃቹ አጉል ቦታ እንዳይመቷቹ ጥቅልል ብላቹ በፊታቹ ተኙ፡፡ በቃ ምንም ማድረግ አይቻልም ኢትዮጵያም አይደል ያለነው!?!!።

ሚያዚያ 2010 ዓ.ም

ቡሩክ ካሳሁን ቴሌግራም ቻናል @burukassahunC

@wegoch
@wegoch
‹‹ግን.... ባይሆንስ?››
----------------------------------------------

ቴድ ቶክ ማየት በጣም ደስ ይለኝ የለ? ከምሳ ሰአቴ ቀንሼ ነው የማየው…አፌን በምግብ፣ አእምሮዬን ደግሞ በጥሩ የቴድ ቶክ ተናጋሪዎች ታሪክ ስሞላ ፍስሃ
ይሰመኛል፡፡ በሁለት በኩል መመገብ ነዋ ዛሬ ያየሁት የዳያንን ነው፡፡ ዳያን ቮን ፈርነስተንበርግ (ስሟ መርዘሙ፣ ደግሞ
ማስቸገሩ).. ዳያን እጅግ ስመጥር የፋሽን ዲዛይነር ናት፡፡ አለም ላይ አሉ
ከሚባሉት አንዷ፡፡ ዳያን ንግግሯ መጀመሪያ አካባቢ ናዚ ጀርመን አይሁዶችን እያደነ በሚገድልበት
ጊዜ ወጣት ስለነበረችው አይሁዳዊ እናቷ ታወጋናለች፡፡ እንደሌሎቹ አይሁዳዊያን በጀርመኖች ለሞት የታጨችው እናቷ መልካም ነገር ገጥሟት ጀርመንኛ ትንሽ ትንሽ የምትናገር ጠና ያለች ሴት መዋወቋ ሕይወቷን ሊያርፍላት እንደሚችል ተስፋ አደረገችና ተጣበቀችባት፡፡ ከእሷ አልለይ አለች፡፡ በሄደችበት ሁሉ ትከተላት ጀመር፡፡ በመጨረሻም ለማይቀረው ፍርድ እስረኞቹ ሁሉ ተሰበሰቡና አንድ የጀርመን ወታደር በተራ እየተቀበለ ‹‹አንቺ በግራ፣ አንቺ በቀኝ›› እያለ እንዲሰለፉ ሲደረግ፣ ተስፋ ያደረገችባት ሴት ‹‹አንቺ በቀኝ ተሰለፊ›› ተባለች፡፡ ያቺ ጀመርንኛ ታተርፈኛለች ብላ ያመነችው የዳያን እናትም የወታደሩን ትእዛዝ ሳትጠብቅ ከሴቲቱ ላለመለየት ቶሎ ብላ በቀኝ ተሰለፈች፡፡ ወታደሩ ምንም አላላትም፡፡ ተዋት፡፡ ምን ያደርጋል! እስካሁን ድረስ ብዙ እስረኛ በተባለው መስመር ሲሰለፍና ይሄ ሁሉ ሲከናወን ከፍ ባለ ቦታ ላይ ቁጭ ብሎ በዝምታ
የሚቃኘው የወታደሮቹ ሃላፊ ግን ወዲያውኑ የዳያን እናት ጋር መጥቶ በያዘው ጅራፍ ገረፋትና በግራ በኩል እንድትሰለፍ ገፈተራት፡፡ እያንገሸገሻት በስተግራ ተሰለፈች፣ ውስጧ በከፍተኛ ጥላቻ ተሞልቶ ቀና ብላ አየችው፡፡ ‹‹ለምን እንዲህ ያደርጋል? ቢተወኝ ምናለ….?››ብላ እጅግ ተማርራ ቀና ብላ አየችው፡፡ እስከዚያች ቅፅበት በብዙ ስቃይ ብታልፍም ከፈለገችው ሰልፍ አውጥቶ ወደፈራችው ሰልፍ የገፈተራትን ሰው ግን ከማንም በላይ አጥብቃ ጠልታው ቀና ብላ አየችው፡፡
ከዚያ የሆነው ግን ይሄ ነው፡፡ እንዲህ እስክትንገሸገሽ የጠላችው ሰው ነው
ሕይወቷን ያተረፈው፡፡ ለምን? በቀኝ በኩል የተሰለፉት ሰዎች በጋዝ ታፍነው ሊገደሉ የተመረጡና በኋላም ያለቁ ነበሩ፡፡ ዳያን ይሄን ታሪክ ለምን ነገረችን? አልፍ አልፎ ሁላችንም እንደ ዳያን እናት ባይከፋም የመረጥነው መንገድ ስለተዘጋብን ዓለም ክንብል ብላ የተደፋችብን፣ እጅግ ከባድ ነገር የደረሰብን ይመስለናል፡፡…ግን ባይሆንስ? ተገፍትረን የያዝነው መንገድ መርጠነው ካጣነው መንገድ የተሻለ ቢሆንስ?

@wegoch
@wegoch
@paappii


#hiwot emishaw
ስብሰባው
=======+++++=====
አንዱ አብዮታዊ ፈጣሪን ከሰይጣን ጋር ሊያስታርቅ እቅድ አዘጋጅርና ሽማግሌዎችን መርጦ ውይይት እያደረገ ነው። (መግለጫ መስጠቱ ነው)

ሰብሳቢው:- የስብሰባው አጀንዳ ሰይጣንን ከፈጣሪ ጋር እንዴት ማስታረቅ አለበን የሚል ነው። እንደምታውቁት የሰይጣንን ቦታ መላእኩ ከተረከበ በሁዋላ ሰይጣን እንቅልፉን አልተኛም። እንደምታዩት እርስ በእርሳችን ጠብ ጭቅጭቅ ንትርክ ሁኗል ተግባራችን። ስለዚህ እሄን ነገር ሰላም ለማድረግ ሰይጣን ከፈጣሪ ጋር መታረቅ አለበት። በዚህ ጉዳይ ሰፊ ማብራሪያ እንድትሰጡበት እንፈልጋለን '' ሲል ስልኩን መነካካት ጀመረ
*
ሽማግሌ ተመረጠ (ሉካን ቡዱን መሆኑ ነው)
****
ሰይጣን እንቅልፉን ተኝቶ አገኙት
***
ሠው:- ሰይጣን የተመቸህ ትመስላለህ ?
ሰይጣን:- እድሜ ለናንተ ሰላሜን ሰጣችሁኛል ዛሬ ምን እግር ጣላችሁ?
ሠው:- ፈቃድህ ከሆነ አንተን ከእግዚአብሄር ጋር ለማስታረቅ አስበን ነበር
ሰይጣን:- አይሆንም! አትልፉ! ከናንተ ጋር የታረቅኩት ይበቃል። እሱ እኮ ካንዴ ሁለት ጊዜ ከስልጣኔ አስለቅቆኛል። እንደምታዩኝ እንቅልፋም አድርጎኛል። ስሜን ስልጣኔን እና ማንነቴን ቀይሮ አንኮታኩቶኛል። እና እንዴት እታረቀዋለሁ?
ሰው:- ደግሞ ከየትኛው ስራህ ነው ያስለቀቀህ ?ለሚካኤል ከሰጠው ውጭ
ሰይጣን:-አዎ! ለዘመናት ብቻየን ስፈነጥዝበት የነበረውን ዝሙትና ተንኮል ንትርክና ጭቅጭቅ ውሸትንና ክህደት አብዝቶ ለሚሰራው ሰው ለተባለው ፍጡር አሳልፎ ሰጠብኝ። ሰዎች በኔ ስም እየተጠሩ እርስ በእርሳቸው ይናከሳሉ። እኔ ለመስራት የሚከብደኝን ሀጢያት እናንተ እንደጽድቅ ትቆጥሩታላችሁ። እኔ እስካሁን ሰው አልገደልኩም። እናንተ ግን ሰውን አርዳችሁ ትበሉ ጀመር: እኔ እስካሁን ከሴት ጋር አልተኛሁም ለናንተ ግን ዝሙት ስራችሁ ነው ሰዎች ሰይጣን አሳሳተኝ ትሉኛላችሁ እኔ ግን እንኳን ላሳስታቸው በስራችሁ ታስቀኑኛላችሁ:: እግዚያብሔር እኔን የሚያሸንፈኝ በቃሉ ነው: ሀይሉ ያንበረክከኛል: እኔ የእግዚብሄርን ወንበር የደፈርኩት በወቅቱ ከኔ በላይ ስላልነበር ነው: እናንተ ግን ካለቃችሁ በላይ አለቃ መሆን ያምራቹሃል: ከባሏ በላይ የቤቱ አባወራ ትሆናላችሁ: ከሻጩ በላይ ትርፋማ ትሆናላችሁ: ካረ'ባው ይልቅ ወተት ትጠግባላችሁ: ጠዋት ማታ ስርቆት: ሌት ተቀን ዝሙት: ሰርክ ጭቅጭቅ: ነጋ ጠባ ጦርነትና ሀሜት!! ያንተ ያለህ እኔ የማላውቀውን ሀጢያት ሁሉ አሳያችሁኝ እኮ
ሠው:-እና አንተ እያሳሳትክን እኮ ነው
ሰይጣን:- በቀር ለሀሜትማ ምን ተይዞላቹሀል: እኔ አመንዝሩ ስረቁ ቀሙ ተጋደሉ ተጣሉ ብዬ አማልኳቹህ? ካለአመነዘራችሁ ብልታቹሁን እቆርጣለሁ: ካልሰረቃችሁ እጃችሁን እሰብራለሁ አልኳቹሁ? ካላማቹህና ካልገደላችሁ ዘራችሁን አጠፈዋለሁ አልኳቹሁ? በነጻ የሚጠጣውን ጸበል ንቃችሁ በብር የሚገዛውን አልኮል የምትጋቱ እናንተ! ሚስታችሁን ህጻን እያስታቀፋቹህ የምትሴስኑ እናንተ! የሠራን የምትቀሙ የሠረቀን የምትሸልሙ: የቀማን ጀግና የገደለን ታጋይ እያላችሁ ስላንድነት የታገለውን በፍላጻ የምትቆራርጡ እናንተ! ከከቅቤ ላይ ሙዝ ከእንጀራ ላይ ሳጋቱራ ጨምራቹሁ የምትሸጡ እናንተ! ከወደቀ እንጨት ላይ ምሳር ይበዛበታል ሁኖ ነገሩ ጥፋታችሁን ሁሉ በኔ ስታላኩ የማይሰቀጥጣቹሁ እናንተ! ደግሞ እኔሳ ስልጣኔን ተቀምቼ አርፌ በተኛሁ ምን አረኩ?
ሰው:- እሹ አሁን ወቄስታውን ተወውና የመጣነው ከእግዚአብሄር ጋር ልናስታርቅህ ነው
ሰይጣን:- (ከትከት ብሎ ስቆ) 'ልናስታርቅህ ነው' ነው ያላችሁ? ትገርማላቹሁ እኮ! መታረቅን እንጂ ማስታረቅንማ ትወዱት የለ! አስታራቂማ እንደምድር አሽዋ በዝቶ የለ! የጠፋው እኮ የሚታረቀው ነው! ከሲኦል ይልቅ የሚያስፈራችሁ እኮ ይቅርታ ነው! ይቅርታ የሚባለው ነገር አይደለም ተግባሩ ስሙ በራሱ ያንቀጠቅጣቹሃል! እናንተ እርስ በእርሳቹሁ ሳትታረቁ ሰው ለማስታረቅ ጉባዬ ትጠራላችሁ! በስድብና በቂም ልባቹህ ተሞልቶ ጸጉራቹህ ስለሸበተ ብቻ እናስታርቅ ትላላችሁ! ለመሆኑ እስካሁን ከወጡት ሙዚቃ ስለእርቅ የተዘፈነ አለ? ''እያየህ በለው: ገዳይ ና ገዳይ ና: ነይ ማታ ማታ: ልቡን ልበለው: አምጡት ምንሽሬን' የሚለውን ከመሥማት ውጭ ስለእርቅ አድምጠን እናውቃለን? ሰው ከገዛ ህሊናው ጋር ተጣልቶ ያስታራቂ ያለህ እያለ እየጮህ እናንተ ከዚህ እኔን ትረብሻላቹሁ' ሲል ትቷቸው ሄደ
=====
ሰብሳቢው:- ሰይጣንን አገኛችኛችሁት?
ሽማግሎች:- አግኝተነው ነበር ነገር ግን ሰድቦ ሰደደን
ሰብሳቢው:- ባይሆን አስማት አላስተማራችሁም?
''እየተከዘ''

Mezin worku

@wegoch
@wegoch
2024/09/28 09:36:33
Back to Top
HTML Embed Code: