Telegram Web Link
ለውብ ቀን
💚
ነፃነትህም የተፈጥሮ ለመሆኑ ተንታኝ እስኪነግርህ አትጠብቅ፡፡
መመሪያህ ፍቅር እንጂ ጥላቻ አይሁን፤ ፍቅር ከጥላቻ ጋር ህብረት የለውም፤ ባለሰይፍን
በሰይፍ መቀየሩም፣ ጉልቻ ቢለዋወጥ… ነውና
መንገድህ ሁሉ ፍፁም ሰላማዊ ይሁን!
እውነት እውነት እልሀለሁ፡- ነፃነትን የሰወረ መቃብር የሚፈነቀለው በፍቅር ብቻ ነው፤ ዘላቂ
ለውጥም ከምህረት እንጂ ከበቀል አይሰርፅም።


ሸጋ ቀን !!!💚💛

@wegoch
@wegoch
@balmbaras
የምንችለውን ወይስ የሚገባንን?
(ዲ.ዳንኤል ክብረት)

ይነበብ
፨፨፨

የሚቻለውን መሥራት የዐቅም ጉዳይ ነው፡፡ የሚገባውን መሥራት ግን የሕግና የሞራል ጉዳይ ነው፡፡ ኃይልን ለመጠቀም የሚያስችል ትምህርት ለሚማሩ ሰዎች በጥብቅ የሚነገራቸው ነገር ቢኖር የተገቢነት ጉዳይ ነው፡፡ ካራቴ፣ ጂዶ፣ ቦክስ፣ ውትድርና፣ ፖሊስነት የተማሩ ሰዎች ኃይልን ለመጠቀም ቅርብ ናቸው፡፡ በእጃቸው ማጠናፈር፣ በእግራቸው መዘረር፣ በጉልበታቸው ማርገፍ፣ በመሣሪያቸው ማንጠፍ፣ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን በባረቀባቸው፣ በፈላባቸውና በነደዳቸው ቁጥር ኃይል እንዳይጠቀሙ የተገቢነትን ጉዳይ እንዲያስቡበት ይመከራሉ፤ ይሠለጥናሉ፡፡ ይቻላል ሳይሆን ይገባል ወይ? ብለው እንዲጠይቁ፡፡

አሁን ባለቺው ኢትዮጵያ ‹ይቻላል› እንጂ ‹ይገባል› ተገቢውን ቦታ አላገኘም፡፡ ሁሉም የሚችለውን ለማድረግ ነው የተነሣው፡፡ ‹ይህንን ማድረግኮ ይቻላል፤ እነ እንትናን መቀስቀስኮ ይቻላል፤ እንዲህ አድርገን ልናሳያቸውኮ እንችላለን፤ እንዲህ ብሎ መከራከርኮ ይቻላል፤ እንዲህ አድርጎ ምላሽ መስጠት ይቻላል፤ እንዲህ ሠርቶ መበሻሸቅ ይቻላል› የሚሉ ነገሮችን ነው የምንሰማው፡፡ ባለ ሥልጣኑም፣ ፖለቲከኛውም፣ አክቲቪስቱም፣ ጸሐፊውም፣ ጋዜጠኛውም ምን ማድረግ እንደሚችል እየነገረን ነው፡፡ ሁሉም የጉልበቱን ልክ እያሳየን ነው፡፡ ‹ይህንን ማድረግ ተገቢ ነው?› ብሎ የሚጠይቅ ግን ብዙም የለም፡፡



ሁላችንም የምንችለውን ብቻ ካደረግን የሚተርፍ አይኖርም፡፡ የሚያኗኑረን ተገቢውን ብቻ ለማድረግ ያለን የአእምሮ መለኪያ ነው፡፡ ኃይልንና ጉልበትን ከማን አለብኝነት የማቀቢያው መንገድ ‹ተገቢነት› ነው፡፡ ይህ ደግሞ ከሕግና ከሞራል አንፃር የሚታይ ነው፡፡ ለጊዜው ዐቅም ወይም ሥልጣን ወይም ዕድል የላቸውም ብለን በምናስባቸው ወገኖች ላይ ‹እንችላለን› በሚል ስሜት ብቻ የምናከናውነው ተግባር ሌላ ‹እችላለሁ ባይ› ይፈጥራል፡፡ የማሸነፊያው ኃይል ሐሳብ መሆኑ ይቀርና ጉልበት ይሆናል፡፡ ጉልበት ማጠራቀም ደግሞ ሐሳብን ከማጠራቀም ይልቅ ቀላል ነው፡፡ ሂደታችንም ያረጀን ጉልበታም በአፍለኛ ጉልበታም የመተካት ሂደት ይሆናል፡፡ የሰው ልጅ ዛሬ ዛሬ ዛፎችን የማይቆርጠው፣ እንስሳትን የማያድነው፣ በካይ ጋዝ ወደ አየር የማይለቀው ዐቅም አንሶት አይደለም፡፡ ይህን ሁሉ ማድረግ ይችላል፡፡ ግን አይገባውም፡፡

ማኅበረሰብን በሰላምና በጤና የሚያኑዋኑረው ‹ተገቢነት› ነው፡፡ ይህን ነገር መናገር፣ መጻፍ፣ ማሠር፣ መግደል፣ መከልከል፣ መውሰድ፣ መስጠት፣ ተገቢ ነው ወይ? የሚያስገኘው ጥቅም ምንድን ነው? ያኗኑራል ወይ? በዜጎች ላይ የሚያስከትለው ተጽዕኖ ምንድን ነው? የሚሉት ጉዳዮች መታየት አለባቸው፡፡ ማድረግ የምችለውን ሁሉ ማድረግ፣ መናገር የምንችለውን ሁሉ መናገር፣ መጻፍ የምንችለውን ሁሉ መጻፍ፣ ማባረር የምንለውን ሁሉ ማባረር፣ ማፍረስ የምንችለውን ሁሉ ማፍረስ፣ መገንባት የምንችለውን ሁሉ መገንባት አለብን? ተገቢ ነው?



የሰው ልጅ አካላት በሦስት መልክ ይገለጣሉ፡፡ በአንድ በኩል ለሕዝብ ሁሉ የሚገለጡ የአካል ክፍሎች አሉ፡፡ በሌላ በኩል ለተወሰኑ ሰዎች ብቻ የሚገለጡ የአካል ክፍሎች አሉ፡፡ ሦስተኛዎቹ ደግሞ ለማንም የማይገለጡ የአካል ክፍሎች ናቸው፡፡ በፎቶ ግራፎቻችን ላይ በብዛት የምናገኛቸው ለሕዝብ ሁሉ የሚገለጡትን የአካል ክፍሎቻችንን ነው፡፡ እነዚህ የአካል ክፍሎች ብዙ ጊዜ ልብስ አይለብሱም፡፡ ቢለብሱም በአደባባይ ልብሳቸው ሊወልቅ የሚችል ነው፡፡ ለቅርብ ሰዎቻችን ብቻ የምናሳያቸው የአካል ክፍሎችም አሉን፡፡ እነዚህ ብዙ ጊዜ በልብስ ተሸፍነው የሚውሉ ናቸው፡፡ እነዚህን ለሰው ሁሉ መግለጥ የጤናም፣ የሞራልም፣ የባሕልም፣ የሥነ ምግባርም ቀውስ ያመጣል፡፡ ሦስተኛዎቹ በቆዳችን ተሸፍነው የሚኖሩ የሰውነት ክፍሎች ናቸው፡፡ እነዚህን ለማየት የውስጥ አካልን የሚያሳዩ መሣሪያዎች ያስፈልጋሉ፡፡ በቀዶ ጥገና ለማየትም የተለየ ሞያና ሥነ ምግባር ይጠይቃሉ፡፡ እነዚህ በቆዳ ተሸፍነው የሚኖሩ የሰውነት ክፍሎቻችንን ከፍተን ብንተዋቸው በሰውዬው ላይ አደጋ ይከሠታል፡፡ መጨረሻውም ሞት ነው፡፡

የሰው ልጅ ጉዳዮችም እንዲሁ ናቸው፡፡ ለሁሉም የሚገለጡ አሉ፡፡ ለተመረጡ ብቻ የሚገለጡ አሉ፡፡ ለማንም የማይገለጡም አሉ፡፡ አሁን በሀገራችን እያየን ያለነው ግን ከዚህ በተለየ ነው፡፡ ሁሉንም በአደባባይ የመዘርገፍ አባዜ ውስጥ ወድቀናል፡፡ ይህንን የምናደርገው ደግሞ ‹ማድረግ እንችላለን› በሚል ጉልበተኛ ስሜት ነው፡፡ ‹ማድረግ ተገቢ ነውን?› በሚል የጠቢብነት መንፈስ አይደለም፡፡ ከሕዝብ ሁሉ ጋር የምናደርጋቸው ነገሮች አሉ፤ ከተመረጡ ወገኖች ጋር መነጋገር፣ መከራከር መወያት ያለብን ነገሮችም አሉ፡፡ አንዳንድ ነገሮች ግን ስሜታችንን ቢገፋፉትም፣ ውስጣችንን በል በል ቢለንም፣ ጉልበታችን ቢሞግተንም፣ እንኳን ይዘን መኖር ያሉብንም ነገሮች አሉ፡፡ ይገለጡ ቢባሉ እንኳን በተገቢው መንገድ ለመያዝ የሚችሉ ሰዎች ያስፈልጉናል፡፡ ተገቢነት ይህን ይጠይቃልና፡፡
እስኪ የሀገራችን ኃያላን - የምትችሉትን ሁሉ ማድረግ ተውና የሚገባችሁን ብቻ አድርጉ፡፡

ምንጭ ፦ የዳንኤል ክብረት የጡመራ ገጽ / Daniel Kibret Blog /

#ንባብ_ለሕይወት

@Wegoch
@wegoch
ጣታቸው ከሙስበሃው ተፋትቶ፣ ዚክርን ትቶ በእንቅልፍ ብዛት ደልቦ ከመሞት በላይ
አፈሙዝ አያስፈራቸውም።
------
እነዚህን ልቦች የቱንም ያክል ብትታጠቅ አታሸብራቸውም፣ መዝከሪያ ሙስበሃቸውን
አታስጥላቸውም!!

መልካም ጁምኣ!!💚💛❤️

@balmbaras
@wegoch
@wegoch
ከቀናቶች በአንዱ
(ቡሩክ ካሳሁን)

‹አንዳንዴ በመናገርና ባለመናገር መካከል ያለው ልዩነት አስገራሚ ነው› ዱባለ ነው፡፡
‹እንዴት› አልኩት
‹ስለ አንድ ነገር ወይም ስለ አንድ ሰው፤ ስለተደረገ ነገር እራስ ላይም ሊሆን ይችላል፤ ሲደረግ እያየክ እንዳላየ ሆነክ ዝም ስትል፤ አንድ የራሽያዎች ተረት አለ፤ እዛጋ የተሰቀለው የበሬ ፎቶ ይታይሀል?› አለኝ የስጋ ቤት ታፔላ ላይ ወደተሰቀለው እያሳየኝ፡፡
‹አዎን› ብዬ መለስኩለት
‹እንግዲያውስ እያየክ ዝም ካልክ ከሱ አትሻልም ምክንያቱም ይሄ በሬ በጣም ብዙ በሬ ወገኖቹ እዚ እየገቡ ስጋቸው ሲቆረጥ አጥንታቸው ሲፈለጥ አይቷል ነገር ግን ምንም አይናገርም፡፡ አንተም ዝም ካልክ ከሱ አትሻልም ማለት ነው፡፡› አለኝ
.
ወዲያው ሁለት ጠብደል ሌቦች አንዲት ልጅን ሀብል ነጥቀዋት ሲሮጡ ባቅራቢያዋ የነበረ ‹ፋኖ› ማለት ይቀለኛል (ወዶ ሟች ማለቴ ዘማች ለማለት ነው) ሁለቱን ሌቦች ሊያሯሩጥ ሲከተላቸው አንዴ ቆሙና ፍሬውን ከገለባው ለዩት (መቼም ደበደቡት ብዬ ስራቸውን አላጣጥልባቸውም)፡፡ እንደዛ ሲመክረኝ የነበረው ዱባለን ዞር ብዬ ‹ኸረ ሊገሉት ነው ሄደን እንገላግል› ስለው ‹ለዛሬ የበሬውን ፎቶ ነኝ፡፡ ይልቅ ለምስክርነት ምናምን ብለው አፋፍሰው ሳይወስዱን ቶሎ ስልታዊ ማፈግፈግ እናድርግ አለበለዚያ እስኪጣራ ብለው አስገብተው መንግስት ካልተገለበጠ አያስወጡንም፤ ቴክኒካሊ ስፒኪንግ መቼም ማለት ነው› ብሎኝ አረፈው፡፡
ጥቂት ሶምሶማ ከሮጥን በኋላ መራቃችንን ስናረጋግጥ ረጋ ብለን መሄድ ጀመርን፡፡ የት እንዳለን ጠየቅኩት፡፡ ‹ምን አውቃለው እኔ ጂ.ፒ.ኤስ እንጠቀማ› አለኝና ዞር ዞር ብሎ ንግድ ባንክ ከፈለገ በኋላ ‹ይኸው ቄራ ደርሰናል › አለኝ፡፡ ተአምር ነው ፒያሳ ለተነሳ ጠብ በሶምሶማ ቄራ ከደረስን ብንሮጥ ኖሮ ከኦሮሞና ከሱማሌ ወገኖቻችን ጋር ሶስተኛ ቦታ ተካፋይ ሆነን ጦር መማዘዛችን አይቀሬ ነበር፡፡ ዱባለ የነፍስ አባቱን ስላገኘ ሁለታችንም ከተሳለምን በኋላ በግራ እጃቸው እሱን ያዝ አድርገው አስቀሩት ጎንበስ ብሎ አሜን አሜን ሲል ይታየኛል፡፡ ተመልሶ ሲመጣ ምነው ምን ብለውህ ነው እንዲ ‹አሜን አሜን ስትል የነበረው?› ብዬ ጠየቅሁት፡፡
እርሱም ‹አይ ጥቂት አወሩኝና ሊሄዱ ሲሉ መስቀል ተሳልሜ ይፍቱኝ አባቴ ብላቸው ‹ሀጢያትህን እንደ ቴዲ አፍሮ ኮንሰርት አሁንም አሁንም ይሰርዘው፤ ምቀኞችህን መተንፈሻ ፍቃድ ይከልክልልህ› አይሉኝም መሰለህ› አለኝ፡፡
‹ዉዉዉ በቃ በዚ አቋማቸው ለመጨረሻ ጊዜ ነዋ ዛሬ የተሳለምናቸው› አልኩት ፡፡
‹እቺ ሌባ› አለ ዱባለ ቀና ብዬ ሳይ የቀበሌያችን ሊቀመንበር የነበረችዋ ሴትዮ ናት፡፡
‹ምነው ምን አደረገችህ› ጠየቅሁት
‹ምን ማታረገው ነገር አለ እቺ፤ ባለፈው 1 ማህተም ለማስመታት እሷ ምድር ላይ ተንቀባራ ‹‹ወረቀቱን ከ4ኛ ፎቅ አምጣ›› አለቺኝ እሺ ብዬ አመጣሁ፤ 3ኛ ፎቅ ውሰደውና አስፈርም አለችኝ ሄጄ አስፈረምኩ፤ ያን ሁሉ ደረጃ እንደ ኮትኳች አጎንብሼ ወጥቼ ወርጄ ሳበቃ ‹‹የማህተም መምቻ ቀለም አልቋል ሰሞኑን ና›› አትለኝም መሰለህ፤ ድሮም ኢትዮጵያና ቢሮክራሲ› አለኝ እልህ በያዘው ድምፅ
‹ቅጠል ጨፍጭፈህ ለቀለምነት አምጣ ካልተባልክም ከፍታ ነው › አልኩት እየሳኩኝ
በመራመድ ላይ እያለን ገጀራው የሰፈራችን ግዙፉ ከፊታችን ድቅን አለ፡፡ ‹እንዴ ደሞ እዚ ምን ትሰራለህ? ሰፈር ደረስን እንዴ?› አለ ዱባለ ድንግጥ ብሎ
ገጀራውም ‹ አሁን ምንም ወሬ አልፈልግም ባለፈው ያበደርኩህን 5 ብሬን አምጣ› ብሎ ሳይጨርስ ዱባለ ሩጫ ሲጀምር ገጀራው ለ5 ብር ብሎ 5ሺ ገደማ የገዛውን ስልክ ወርውሮ ዱባለ አናት ላይ እንደ እንቁጣጣሽ ርችት በተነው፡፡ ዱባለ ጭንቅላቱን እንኳን አላሻሸም ቦልትን በሚያስንቅ ሁኔታ ገሰገሰ፤ ገጀራው ስልኩ መበተኑን ሲያይ ‹ወይኔ ስልኬን› ብሎ ከበፊቱ የበለጠ ንዴቱ ጨምሮ ተከትሎት መሮጥ ጀመረ፡፡ ገጀራው ዛፍ በመቁረጥ ሚተዳደር ፀረ ልማት ወጣት ነው፡፡ መጥረቢያ ይዞ ቢሆን ኖሮ ብዬ አሰብኩትና ስለዘገነነኝ ቶሎ ቶሎ ወደቤት አቀናሁ፡፡
2010 ዓ.ም

@burukassahunc

@wegoch
@wegoch
@wegoch
Forwarded from SPACE COMPUTER
🇪🇹🇪🇹🇪🇹አምስተኛው የብርሃን ዕለት የመጀመሪያው ማክሠኞ ነው። ይምጡና አብዝተው ያትርፉ እንድቅትዮን ዕንቁላል ፋብሪካ በሚገኘው #ገነት_መናፈሻ ሠኔ 4/2011

እማይቀርበት!


@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
ለቅዳሜያችን
💚
ሲታሰብ ከባድ ቢመስልም በአንድ ወቅት ውስጥህን ያቆሰሉትን ያቆሸሹትን የጎዱህን
የጣሉህን ሁሉ ተዋቸው።
አንተ ደስታህን ሊሰጥህ ስለሚችል ነገር ብቻ ላይ ትኩረትህን አድርግ።
ባሳዘኑህ ነገሮች ላይ ባተኮርክ ቁጥር አሁን ያለህን የደስታህን ጊዜ ታጣዋለህ። በቻልከው
መጠን አስተሳሰብህን ቋጥሮ ከያዘክ የሀሳብ እስር ቤት ራስህን በራስህ አውጣ።
ስለ ህመምህ ብቻ ካሰብክ ከፊትለፊትህ ያለውንንና እንዳትንቀሳቀስ ያደረገህን ግርግዳ
ራስህ በራስህ ታጠነክረዋለህ።
ከፊትህ ያለውን ግርግዳ ናቀውና እለፈው ትልቅነቱን ሳይሆን
የአንተን የአሁን የደስታህን ትልቅነት ብቻ አስብ።
ስላለፈው ሳይሆን ስለአሁኑ ስለቀረው ሳይሆን ስለመጪው የምታስብ ሁንና ደስታህን
በእጅህ አድርግ።

ፍልቅልቅ ያለች ፣ ድምቅምቅ፣ሽብርቅርቅ ያለች ቅዳሜ ትሁንልን!!💚💛

@wegoch
@wegoch
@balmbaras
እንደምን አመሻችሁ ወዳጆቸ፡፡

ሁሌም የሚቆጨኝ በጣምም የሚያሸማቅቀኝ የዚህ ትዉልድ አካል መሆኔ ነዉ::
ምናለ በዛን በደጋግ አባቶቸ ዘመን ፈጥረህኝ ላይሆን ያስብለኛል፤ከእወቀትም ባዶ ከጥበብም አላዋቂ ከሀይማኖት ና ምግባረም ዜሮ ከሆነ የትዉልድ አካል አንዱ መሆኔ እናቴ ማርያምን ይቆጨኛል፡፡
በተለይ በተለይ የዘመናት የአበዉ የትንቢት መፈፀሚያ የሰቆቃዉ ዘመን በደረሰበት በዚህ የሺወች አመታት መቋጫዉ እረጉም ዘመን መፈጠሬ ያሳፈረኛል፡፡
የትንቢቱ ቃል ሲፈፀም በአይን ማየት በጀሮስ መስማቱ ምን ያክል ያስፈራል በእዉነት ሳስበዉ ልቦናየ እራደብኝ፡፡
ይህ የተንኮላዉያን ዘመን ዘመናችን ሊያሳጣን ነዉ ይህ የእርኩሳን ዘመን ሊያራክስን ነዉ፡፡
ሰሞኑን የሚሰማዉ ጉድ ደግሞ ያስፈራል እኒህ የኢሉሚናቲ ቡድን የሰይጣን ጋሻጃግሬ የረከሱ ርኩሳን ግብረሰዶማውያን የቅድስት ሀገራችንን ቅድስና ሊያሳጡ ሊመጡ ነዉ አሉን፡፡
ወገኖቸ የሚገርምዉ እኮ የሚመጡት የኛቱን የኦረቶዶክስን ቤተክረስቲያን ሊጎበኙ ነዉ፡፡ ያዉም ፃድቅም ነጉስም ካህንም የሆነዉን የላሊበላን ቤተ መቅደሶች ሊጓበኙ፡፡ ይህ አያስለቅስም? ይህ አያስቆጫችሁም? የአባቶቻችንን አደራ እንብላ? ዝም እነበላቸዉ?
አላማዉ ግልፅ ነዉ፡፡ ለምን ይመጣሉ?
ብዙ ጊዜ በዚሁ ፔጅ ላይ በተደጋጋሚ ገለጨዋለሁ የአለሙ የፖለቲካ አላም የምእራባዉያን ክፋት ዋናዉ አላማቸዉ የመጀመሪያዉ እቅዳቸዉ ኦረቶዶክስን ከአለም የእምነት ተቋማት ዝርዝር ዉስጥ ማዉጣት ነዉ፡፡ ኦረቶዶክስ የሚባል ሀይማኖትን ከምድረ ገፅ ላይ ማጥፋት ነዉ፡፡ ለምን? የአንድ ጻድቅ ፀሎት ብቻ የሉስፈር ድልዳል መቀመጫዉን ያሳጣዋል፡፡ እንደ ጦረም ይወጋዋል የጻድቅ ሰዉ ጸሎት ሀይል አላት ና! ስለዚህ የአለሙን አስተሳሰብ ግሎባላይዜሽን በተባለ ቁማር ጠፍንጎ በአንድ መንደር አስተሳሰብ ዉስጥ በማስገባት የሉሲፈር ወንበረ በማይነቅንቅ በሰወች የልብ ዙፋን ዉስጥ ፀንቶ እንዲኖር ማድረግ ነዉ፡፡ ይህንን ለማድረግ ደግሞ የኢትዮጵያ ሰወች የቃልኪዳን ንፃህናቸዉን ማሳጣት ና ማጉደፍ ነዉ፡፡
እኔ እኮ የሚገረመኝ እንዴት ማስተዋል አቃተን፡፡
ለምንስ አላማ ለምንስ ጉዳይ እንደሚመጡ ነገሪ እኮ አያስፈልግም ለምን ቢሉ፡፡
ለመዘናናት እማ ፖሪስ አትመረጥም? የዉብ ህንፃወች ባለቤት ዱባይስ ከኢትዮጵያ ድንኮነች እጅጉንስ አትስብም? የቱርክ አረቲፊሻል ተፈጥሮስ ከኢትዮጵያዉያን ኮረብታወች ለመዝናናት አትመረጥም፡፡
ወዳጀ ወዲህ ነዉ አላማዉ ....
ይህንን የረከሰ የእረኩሳን ማህበር ሀገራችን እኒዲረግጣት አንፈቅድለትም፡፡
ስለዚህስ ብንሞትም አይቆጨን ከሀጣን ጋ ተባብረን በሂወት ከምንኖር ይልቅ ሙተን ከፃድቃን ጋ ህያዉ ብንሆን ይሻለናል፡፡
ሁሉም ሰዉ ይህንን መልክት ለሚችለዉ ሰዉ ሸር ያድረግ ማንም ግብረሰዶም ሀገራችን እንዳይገባ በእያለንበት ሀሳቡን ለማህበረሰባችን እናሳወቀዉ ከ መንግስትም ሆነ ከሚመለከታቸዉ አካላት ደረሶ ቶሎ እልባት እንዲያገኝ፡፡
ሁላችንም ና ቡ ቴ እንበል የአባቶቻችን እርስት አሳልፈን አንሰጥም!
ይህ ፈለገ ጥበባት ነዉ ፡፡

ሀሳብ አስተያየት @paulos3 ላይ አድረሱኝ
26/9/7511

@wegoch
@wegoch
ባቲ!!
----------
ለባቲ የተዘፈነው ሁሉ ደሳሳ ጎጆዎቿ በሆዳቸው አቅፈው ከያዙት ፍቅርና ውበት፡ አንድነትና
ደግነት ሊስተካከል ከቶ አይችልም!! ባቲ ገለል ያለች፣ መንግስትም ሰይጣንም "እጃቸውን"
ብዙም ያላስገቡባት፣ በነበረ ልማዷና ወጓ ያለች የወሎ ሆድ፡ የወሎ ኗሪ ምስክር ነች!!
ባቲ እንደ ቦሌ የሰውን ደም ድንገት አፍልታ ድንገት የምታቀዘቅዝ
ብርቅርቅ፣ሽብርቅርቅ፣ስሜትና ጥድፊያ ከቶ አይደለችም። ባቲ ቀስ ብላ የምትገባህ፣ እንደ
ውሃ እያሳሳቀች የምትወስድህ፣ የረጋች፣ ለብ ያለች፣ ያልተንቀለቀለች አርምሞዋ የበዛ
"አስማጭ" ከተማ ናት!! ይሄ ሁሉ እንዲገባህ ወደ ውስጥ ግባ!!

መልካም አዳር !!!!

@wegoch
@wegoch
@balmbaras
ለሰንበቲታችን
💚
ዘርአ ያዕቆብ ለኔ ኢትዮጵያዊ ነውና ሲመክረኝ እንዲህ ይላል፦
ልጄ ሆይ በምር እንዳትፀፀትና በቁጣህም ላይ ፀሐይ እንዳትጠልቅብህ ከቶ ቁጡ አትሁን።
ባልንጀራህን ብታሳዝነውም ለእሱ ያደረግህበትን ተሎ ተነስተህ ስለክፉ መልካም መልስለት
እንጂ አትዘግይ።
ከስህተትም ለመመለስ ትጋ። አምላክ እንዲባርክህና ሰላም እንዲሆንላችሁ ከእርሱ
ከባለእንጀራህ ጋር ሰላማዊ ሰው ሁን
ከችግረኞችና ከሃዘንተኞች ጋር አፅናኝና ርሕሩሕ ሁን። እግዚአብሔር ዋጋህን ይከፍልሀልና
ምፅዋት ማድረግን አትርሳ
እግዚአብሔር በመልካም ነገር ሁሉ እንዲያጠግብህ እንጀራ ቢኖርህ ከተራቡት
ወንድሞችህ ጋር ተካፈለው።
ያስጥልሃል እንጂ እግዚአብሔር የሓጥአንን በትር ባንተ ላይ አያሳርፈውምና ኅይል ቢኖርህ
የእሚባረሩ ወንድሞችህን አስጥላቸው።
እግዚአብሔር የተሰወረውን ምስጢር እንዲያሳይህና እንዲያስታውቅህ ጥበብ ካለህ
ዕውቀት ለሌላቸው አስተምራቸው ።

መልካም የረፍት ቀን!!💚💛

@wegoch
@wegoch
@balmbaras
ለውብ ቀን
💚
ውጤቱ ምንም ይሁን እውነት ለመናገር አትፍራ ብቻህንም ብትሆን ሁልጊዜም ለራስህ
እውነተኛ ሁን ።
ሰዎች ካንተ የሚጠብቁትን ሳይሆን ልብህ የሚያቀውን እውነት ተከተል
ምናልባት የእውነት መጀመሪያ መሪር ሊሆን ይችላል
ነገር ግን በመጨረሻ እውነት ነጻ ያወጣሃል
መፅሀፉም እንደሚለው "ቃልህ እውነት ነው፤ በእውነትህ ቀድሳቸው”
አበው አባባል ደግሞ " ሁሉም ያልፋል እውነት ብቻ ይተርፋል"


ሸጋ ቀን ይሁንልን!!!💚💛

@wegoch
@wegoch
@balmbaras
ፍቺ
(ቡሩክ ካሳሁን)

ወደ ቢሮዬ በሩን ከፍቼ ልገባ ቁልፌን አውጥቼ ብሞክር በሩ ክፍት ነው፡፡ ሌባ ነው መቼስ በዚ ጠዋት እያልኩ ቀስ ብዬ ስገባ ፀሐፊዬ ያለወትሮዋ በጠዋት ገብታ አገኘዋት፤‹ምነው ያስቀየምኩሽ ነገር አለ እንዴ? በጠዋት መጣሽ› አልኳት፤ እርሷ ግን በደማቅ ፈገግታ ተቀበለችኝ፡፡ ኦኬ ዛሬ ቀኑ ሰላሳ መሆኑን አወኩኝ፡፡ ‹ሰላም የባለጉዳይ ወረቀቶችን እንደ ቅደም ተከተላቸው አምጪልኝ› ብያት ገባሁ፡፡ የወረቀት ናዳ ፊቴ አምጥታ ቆለለችው፡፡ ከላይ ያለውን አነሳው ጉዳዩ የሚከተለውን ይመስላል፡፡ ደንበኛዬ ከባለቤቷ መፋታት ትፈልጋለች ባልየው ግን የሙጥኝ ብሏል እኔም እንደጠበቃ ብችል ባልየውን ካልቻልኩ ዳኛውን አግባብቼ ላፋታቸው ቆርጬ ተነሳው፡፡ በቅድሚያ ባለቤትየውን አናገርኩት፤ ባልየው መፋታት አይፈልግም ችክ ያለ ሰውዬ ነው እንደውም ችክ ከማለቱ የተነሳ አንዴ ተሳስቶ የተናገረውን ቃል እራሱ እንደ እዝጌር ቃል ሰማይና ምድር ይለፉ እንጂ አልቀይርም የሚል አይነት ሰው ነው፡፡ ደውዬ የሚስቱ ጠበቃ እንደሆንኩና ስለፍቺው ጉዳይ ላነጋግረው እንደምፈልግ ነገርኩት ‹ስለምን ፊቺ ነው ምታወራው?› በስልኩ አንባረቀብኝ፤ እሱን ተገናኝተን ብናወራ አይሻልም ብዬ አንድ ካፌ ቀጠርኩትና ተገናኘን፡፡
‹ሰላም አቶ ኩራባቸው?›
‹ነኝ›
አስተናጋጇ መጣች ‹ምን ልታዘዝ› ብላ ወደኛ አቀረቀረች
‹ለኔ ግማሽ ሊትር ውሀ አምቺልኝ› አልኳት
ኩራባቸውም ‹ለኔ ወተት በሻይ አምቺልኝ› አለ ካነጋገሩ ወተት በቡና ለማለት እንደፈለገ ያስታውቃል ብቻ ደረቅ ነው አላልኳችሁም በቃ ደረቀ፡፡ አስተናጋጇ ተገርማ ደግማ ብትጠይቀውም ጋሽ ኩሬ ‹ባንገቴ ቢላዋ ወተት በሻይ› አለ እኔም መጥቶለት ሲጠጣው ለማየት ቴዲ አፍሮ አልበም ሊያወጣ ነው እንደተባለ ሰው በጉጉት መጠባበቅ ጀመርኩ፡፡
‹እሺ ወደጉዳያችን ስንገባ ጠበቃ ምንተስኖት እባላለው የወ/ሮ ሰብለ ጠበቃ ነኝ እና ወ/ሮ ሰብለ ፍቺ መፈፀም ትፈልጋለች› አላስጨረሰኝም
‹እኔ አልፈልግማ›
‹ጥሩ ነው ግን የሷ ፍላጎትን መጠበቅ ነው የኔ ስራ እና በሰላማዊ መንገድ እንዲፈፀም በማለት ቀድሜ ላናግርህ ፈለኩ›
እስተናጋጇ ለኔ ውሀዬን ለሱ ደሞ ሻይና ወተት አምጥታለት ወተት በሻይ ያወራርድ ጀመር (ጉጉቴ ወጣልኝ)
አስተናጋጇ ዞር እልዳለች
‹ፍቺ ብሎ የምን ሰላማዊ ነው ምታወራው እኔኮ ሰብሊን ልፈታት አልፈልግም ያለ እሷ መኖር አልችልም›
‹ተው እንደሱ አይባልም አንተ ከሷ ውጪ አደል እንዴ የተወለድከው ስለዚህ ከሷ ውጪ ትኖራለህ ማለት ነው፡፡ ደሞ ጥሩ መልክና ቁመና አለህ ወላድ በድባብ ትሂድ ይሄ ቀረሽ ማትባል ሴት ታገባለህ ለምን ችክ ትላለህ፡፡ (በሆዴ አቤት መቼም ነፍሴ አይማርም ይሄን የመሰለ ሰው ለእንጀራዬ ብዬ መልከህ ቁመናህ እላለው ይሄ ዝንጀሮ አልኩኝ)
‹አንተ ማታውቀው ብዙ ነገር አለ እሷ ማለት ለኔ የህይወቴ መነሻ እና መድረሻ ናት እኔና እሷን ማንም አይለየንም ከሷ ከምለይ ሀገር አቃጥላለው›
ይህን ጊዜ ብልጭ አለብኝ ‹ሀገር አቃጥላለው ላልከው አታስብ በውሀ ጥም ተቃጥሎ የሰለጠነ በቂ ፌደራል ያላት ሀገር ውስጥ ስለምትኖር ሞክረውና በአግባቡ ራሱ ክብሪት መጫር እንዳትችል ነው ሚያረጉህ፤ ማንም አይለየንም ላልከው ደግሞ ፍርድ ቤት ሚባል የህግ አካል አለ ጥሩ አድርጎ የተቀላጠፈ አገልግሎት የሚሰጥህ በሀሳቤ ማትስማማ ከሆነ የህግ አካላትን በመዘንጋት ብዬ ራሱ ዘብጥያ ላወርድህ እችላለሁ›
‹ጭራሽ ልታስፈራራኝ ነው እንዴ የመጣኸው በቃ እንደውም አ.ል.ፈ.ታ.ት.ም!!! ከሰብልዬ ጋ አልፋታም አራት ነጥብ›
‹ተው አንተ እንደዚ ችክ ብለህ ሰብልዬ ሰብልዬ አትበልብኝ በዛብህም መጨረሻው ያላማረው እንደዚ ችክ ብሎ ሰብልዬ ሰብልዬ ሲል ነው አንተ እንቢ ብትልምኮ ፍቺው አይቀርም ልፋ ቢልህ ነው እንጂ›
‹ነው እና ለምን መጣህ ዳግመኛ እንዳታገኘኝ›
ብሎኝ ተነስቶ ሊፈረጥጥ ሲል ቀኝ እጁን ግጥም አርጌ ‹እና ባለ ካፌዎቹን እግዜር ይስጥልኝ ብለካቸው ልትወጣ ነው?! እዚ ካፌ ያስከፍላሉ ሂሳቧን› አልኩት፡፡ እጄን ከእጁ ላይ መንጭቆ ካስለቀቀ በኋላ የነተበች 100 ብር ጠረጴዛው ላይ ወርውሮ ሄደ፡፡ ‹ኸረ የበረረ መኪና ይብላክ› አለኩኝ በሽቄ፡፡
ይሄ ሰውዬ 50 ብር ለማይሞላ አገልግሎት 100 ብር መክፈሉ ንብረት ክፍፍሉን አስቀድሞ ሀብት ማውደም ላይ እንዳለ ተረዳሁ፡፡ ተነስቼ ልወጣ አልኩና ጡር ፈርቼ ካስተናጋጇ መልስ ተቀብየ ወጣሁ፡፡
አይደርስ ነገር የለም የቀጠሮ ቀን ደረሰ እና ፍርድ ቤት ቆምን፡፡ እሰጥ አገባውም ባጭሩ ይሄንን ይመስላል

ዳኛ ‹በቀረበው የፍቺ ሃሳብ ባለቤት ትስማማለህ›
ኩራባቸው ‹በፍፁም አልስማማም ክቡር ፍርድ ቤት እኔ ከሰብለጋ እስከ…› እያለ ፉፋውን ሊነፋ ሲል ዳኛው መች አስጨርሰውት
‹ይበቃል የአመልካች ጠበቃ የምትለው ነገር አለ› አሉ ዳኛው
‹አንጀቴን ነው ያራሱት ክቡር ዳኛ› ልል ካሰብኩ በኋላ ፍርድ ቤት መሆኑ ሲታወሰኝ እንደመባነን ብዬ ‹እኔ ክቡር ፍርድ ቤት በመጀመሪያ ባለቤትየው በዚህ ሃሳብ ቢስማማ ነበር የሚገርመው ሲጀመር እነዚህ ሁለት ሰዎች በአንድ ነገር ላይ መስማማት ቢችሉ ቀድሞዎኑ ፍቺ ለምን አስፈለገ? አንዳቸው ለአንዳቸው ግልብጥ ናቸው፡፡ ተቃርኖ ይቀናቸዋል፤ ይገርሞታል የቤት ሰራተኛቸው የነሱን ዘውድና ጎፈርነት ለማቻቻል ወጥ በስኳርና ወጥ በጨው መስራት ነው የቀራት፡፡ በስተቀኝ ያሉት ጎረቤታቸው እትየ አስካል በነሱ እረፍት የለሽ ጭቅጭቅ የተነሳ የእድሜ ልክ የጆሮ በሽተኛ ሆነዋል፤ በስተ ግራ ያሉት ጋሽ ዱለቻ ነጋ ጠባ ሲጨቃጨቁ ‹ምነው የአስካልን ጆሮ በሰጠኝ› እያሉ ፈጣሪን መለመን ጀምረዋል፡፡ ለነዚህ ሰዎች ፍቺ ማለት ሰርግ እንደማለት ነው፡፡ እንደውም አልፋታም ብሎ ከመቃወም ደግሰው ነበር መፋታት የነበረባቸው፡፡ አመሰግናለሁ ክቡር ፍርድ ቤት፡፡
ኩራባቸው ‹የምናገረው አለኝ ክቡር ፍርድ ቤት›
ዳኛ ‹ቀጥል›
ኩራባቸው ‹እኔ ሚስቴን በጣም ነው የምወዳት ከመንከባከብ ያለፈ አንዳች ነገር አጉድዬባት አላውቅም…›
‹ሌላ ሚስት ካለህ ነው እንጂ…› ሰብልዬ አላስጨረሰችውም አቋርጣው ገባች ‹ሌላ ሚስት ካለህ ነው እንጂ አሁን ያልከው በሙሉ ከኔጋ እንዳልሆነ መቼም ይሄ ድንጋይ ልብክ ያውቀዋል…›
ባልና ሚስቱ ጭቅጭቃቸውን ጀመሩ፡፡ ፍርድ ቤቱ ገበያ ሆነ፡፡ ዳኛው በመዶሻቸው ጠረጴዛውን ነድለው ነድለው እንዳልነበር አደረጉት፤ ዳሩ ማን ሰምቷቸው ያ ደረቅ ሰውዬ ድርቅ ብሎ ይጨቃጨቃል፡፡ ተዉ ቢባሉ ቢሰሩ አቃቱ ያን ግዜ ዳኛው ‹ምነው የእትየ አስካልን ጆሮ በሰጠኝ› ብለው አረፉት፡፡


ሰኔ 2009 ዓ.ም
@wegoch
@wegoch
@burukassahunc
ለውብ ቀን
💚
ድርጊት ከቃላት የበለጠ ይናገራል!
ዴል ካርኒጌ
ፈገግታችን የስሜታችን ነፀብራቅ ነው፡፡ በሰዎች ላይ የሚያሳድረውን ተፅዕኖም አንዘንጋ፡፡
ብሩህ ፈገግታ፣ እወድሃለሁ፣ ስላየሁህ ደስ ብሎኛል የሚሉትን ቃላት ይወክላል፡፡
እያሻሸነው ፍቅራችንን የምናሳየው ውሻችን ሳይቀር ከሩቅ ሲመለከተን ጭራውን እያወዛወዘ
የሚሆነውን የሚያሳጣው ለምን ይመስላችኋል?
የህፃን ፈገግታም ከልብ የመነጨ ስለሆን መሰል ተፅዕኖ አለው።
አዎ! በካርኒጌ ሀሳብ እኔም እስማማለሁ ድርጊት ከቃላት የበለጠ ይናገራል።
---------------------------------------------

ሳቅና ፈገግታ ሰደቃ ነው ብለው
ነግረውኝ ሼሆቼ ስንቱን ቀን ሰደኩት
በውብ ሳቅ ሸኝቼ!!!

ሸጋ ጁምኣ!!!💚💛

@wegoch
@wegoch
@balmbaras
ለቅዳሚታችን
💚
ለውብ ቀን
ከሁሉም በላይ ራሳችሁን አትዋሹ ራሱን የሚያዋሽና ውሸቱን የሚያደምጥ ሰው
በዙሪያውና በውስጡ ያለውን..እውነት እንኩዋን ማክበር አይችልም::
በዚህም ለራሱም ሆነ ለሌሎች ያለውን አክብሮትያጣልእናም
ክብር-የለሽ ከሆነ ማፍቀርም ያቆማል።
ዶስቶቭስኪ

ሸጋ ሸጊቱ ቅዳሜ!!💚💛

@wegoch
@wegoch
@balmbaras
2024/09/28 09:32:05
Back to Top
HTML Embed Code: