Telegram Web Link
የሁለት ሰዓቱ ጦርነት!
((Maggie)) #3

መክሰስ ሰዓት ላይ አንዳንዳችን በሰዓቱ አንዳን ዳችን አርፍደን ተገኘን.

ኩሽናችን በር ላይ ... ግማሹ ድንጋይ ላይ ሌላው በርጩማ ላይ ... የተረፈው ያለቀ መክተፊያ ላይ ...... ተቀምጠን (አባ ብቻ ነበር መደገፊያ ያለው ወንበር ላይ የተቀመጠው እና አያቴ ዊልቼራቸው ላይ) ...አቡሻን እኔ አቅፌው ተኮልኩለን ከተቀመጥን ቦሀላ

"እእእ! የሁለት ሰዓቱን የጭቅጭቅ መንስኤ ፈትተን መፍትሄ እንድናቀርብ ነው የሰበሰብኳቹ?" አለ አባ!

እማ አፏን በሽሙጥ አጣመመች!
..
የሚወጣውን ወጣ የሚወርደው ወረደ የሚጨቀጨቀው ተጨቀጨቀ የሚያርረው አረረ... የሚፈተፈተውን ተፈተፈተ እና....... ይህ ውሳኔ ተወሰነ


ማታ ከ2:00 - 3:00 ሰዓት የዜና ሰዓት!
ከ3:00 እስከ ፈለግንበት ሰዓት የጎረምሶቹ! በተጨማሪ (የማታውን የሰዓት ቅነሳ መሰረት በማድረግ ) ቀን ከ7:00 - 8:00 ስዓት የዜና ሰዓት! እንዲሆን

አባዬ ከወንበሩ ተነስቶ ያቡሻን እጅ እየሳመ.... "አቡሻዬ እንዳንተ አይነት እውነተኛ ታዛቢኮ ያስፈልገናል... አመሰግናለው ልጄ!" ብሎት ወደ ቤት ገባ.

.........................................

ብዙ አቡሻዎች አያስፈልጉንም ትላላቹ??

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Maggi
ባሌ እንዳመነዘረብኝ ባወቅኩ ጊዜ እጅጉን ደስ አለኝ (የመጨረሻ ክፍል ሊሆን የሚችል)

"እናውራ? ማውራት አለብን!" አለኝ አምስት ለሊቶች ሳይነካካኝ አቅፎኝ ካደረ በኋላ። አምስት ጠዋቶች ከንፈሬን ሳይስመኝ ደህና ዋዪ ካለኝ በኋላ:: አምስት አመሻሾች ደረቱ ላይ አቅፎ ግንባሬን ሳይስመኝ እንዴት ዋልሽ ካለኝ በኋላ....

"Finally" አልኩኝ ይህን እንዲለኝ ስጠብቅ እንደነበር በደንብ እያሳበቅኩ

"እንዴ? እንድናወራ እየጠበቅሽ ነበር? ማውራት ፈልገሽ ከነበር ለምን እናውራ አላልሽኝም?" ዝም አልኩ። እንዲህ ነኝ! ራሴን እንዴት መግለፅ እንዳለብኝ የማውቀው ከእናቴ ጋር ስሆን ብቻ ነው። እንዲህ ሲለኝ እንዲህ ብዬው በነበር የምለው ካለፈ በኋላ ነው። እንዲህ ማለት ነበረብኝ የምለው አለማለቴ መዘዝ ከመዘዘ በኋላ ነው። በተለይ ስናደድና ስከፋ ሰዎች የልባቸውን ብለውኝ ከሄዱ በኃላ ነው .... በራሴ ብስጭት እያልኩ 'እንዲህ ባልኩ ኖሮ' የምለው..

"ይሄ እኮ ነው ችግርሽ ምንም ሳታወሪ እንዳዳምጥሽ ትፈልጊያለሽ። ምንም ሳትጠይቂኝ መልስ ትጠብቂያለሽ። ለግምት እንኳን የራቀ ስሜት እያሳየሽኝ በልብሽ ያመቅሽውን ስሜት እንድረዳሽ ትጠብቂያለሽ::" እንዲህ ድምፁን ጮክ አድርጎ አውርቶ አያውቅም። መናደድ ይችላል ለካ! አሁንም ዝም አልኩ። በረዥሙ ተነፈሰ እና ደግሞ በራሱ ድምፅ ማውራት ጀመረ።

"እ የምነግርሽ ነገር አለ ......" እያለ እንዴት እንደሚነግረኝ ይታሽ ጀመር።

'አውቃለሁ' ልለው አስባለሁ ግን አፌ አያወጣውም። ሊነግረኝ ሲጨነቅ አየዋለሁ። እንደማውቅ ልነግረው እጨነቃለሁ። በመጨረሻ ከአፉ የወጣው ሊናገር የፈለገው እንዳልሆነ በሚያስታውቅ ሁኔታ 'ቆይ ሌላው ይቆይና ...' የሚል ለዛ ባለው ድምፅ

"ወደሽኝ ታውቂያለሽ ግን? በፍቅር? " አለኝ።

ደነገጥኩ። ምንድነው ያስደነገጠኝ? እንለያይ ወይም ከሌላ ሴትጋ ግንኙነት አለኝ እንዲለኝ ስጠብቅ ወድጄው እንደነበር ስለጠየቀኝ? ዝም አልኩ። አሁን ግን ያለመናገር አባዜዬ ሳይሆን መልሱን ስለማላውቀው ነው። ወድጄው የማውቅበትን ጊዜ ለማስታወስ ወደኋላ ተጓዝኩ። እሩቅቅቅቅቅቅ ነው።

"ይመስለኛል!" የሚል ቃል ነው ከአፌ የወጣው።

አንገቱን ደፍቶ ዝም አለ። መሬት መሬቱን እያየሁ እንባው መሬቱ ላይ ጠብ ሲል አየሁት። ለማረጋገጥ ቀና አልኩ። በአስር አመት ውስጥ እህቱ የሞተች ጊዜ ካልሆነ ሲያለቅስ አይቼው አላውቅም። ዘልዬ ላቅፈው ፈልግያለሁ። እንባው መሬቱ ላይ ከመድረሱ በፊት በጣቶቼ ከጉንጩ ላይ ልጠርግለት። አታልቅስ ብዬ ልለምነውም እፈልጋለሁ። ከአፌ አይወጣልኝም። አስለቃሽዋ ራሴ ሆኜ ማባበል ትርጉም የሚሰጥ ነገርም አልመስል አለኝ። ለሰራሁትም ላልሰራሁትም ሀጢያት ይቅርታ ጠይቄው ለቅሶውን ላስቆመው እመኛለሁ። ውስጤ ሲታመስብኝ ይታወቀኛል።

"ስራ አልቆ መጥተህ እስክትወስደኝ በናፍቆት የምታመም የሚመስለኝ ጊዜ ነበር፣ ስትስመኝ ከመሳሳቴ መቼም የማልጠግብህ የሚመስለኝ ጊዜ ነበረ ፣ልታገባኝ ሽማግሌ የላክህ ቀን በዓለም ላይ የደስታ መጨረሻው ያ መስሎኝ ነበር ፣ መጀመሪያ ቢሮዬ መጥተህ ያየሁህ ቀን ልቤ በአፌ የምትወጣ መስሎኝ ነበር ፣ እራት ልጋብዝሽ ያልከኝ ቀን ምን ብለብስ ልትወደኝ እንደምትችል ስለብስ ሳወልቅ....... ተቀብቼ የማላውቀውን ሊፒስቲክና ኩል ስቀባ አንድ ሰአት ነበር የፈጀብኝ ፣ የሰርጋችን ቀን ማታ መቼም ከእቅፍህ እራሴን እንደማላርቅ ለራሴ ቃል ገብቼ ነበር ፣ ከልክ በላይ ስታቀብጠኝ በምድር እንደእኔ እድለኛ ሴት እንዳልተፈጠረች ያሰብኩባቸው ጊዜያት ብዙ ነበሩ ፣ ይሄ ሁሉ ፍቅር ከነበረ አዎ አፍቅሬህ አውቅ ነበር። ግን እውነተኛ ፍቅር ቢሆን ያልቅብኝ ነበር? ፍቅር ያልቃል?"

ራሴን ሳብራራ አገኘሁት። አውርቼ ስጨርስ ፈገግ እያለ እንደሆነ አየሁት። ከተናገርኩት ምኑ ነው ደስ የሚያሰኘው? ድንገት ተስፈንጥሮ አቀፈኝ። ግንባሬን ፀጉሬን አንገቴን እየሳመ

"ፍቅር አያልቅም! በጥላቻ ወይ በቂም ግን ይሸፈናል። " እያለኝ ደስ መሰኘቱን ቀጠለ።

ግራ ገባኝ። ምንድነው እየሆነ ያለው? አትሳቅ ተብሎ ሳቁን ለመቆጣጠር እንደሚታገል ሰው ያላለቀ ፈገግታ ፈገግ እያለ ተነስቶ መንጎራደድ ጀመረ። ዓይኖቼን አብሬ ከማንቀዥቀዥ ያለፈ ማድረግ የቻልኩት የለም።

"ጠይቂኝ እስኪ? ምንድነው እንዲህ የሚያስፈጥዝህ በይኝ? ለዛሬ እንኳን ደስታዬን ሙሉ አድርጊው! ለሚሰማኝ ስሜት ግድ አላት ልበል?" አለኝ

እያለ ያለው እንደገባኝ እርግጠኛ አይደለሁም። የቅድሙ እንባውን ከማይ ደስታውን ሙሉ የሚያደርገው የኔ መጠየቅ ከሆነ ሺህ ጊዜ ብጠይቀው ግድ አልነበረኝም።

"ምንድነው ደስ ያሰኘህ?"

"እነዚህን ቃላት ካንቺ አፍ ለመስማት ስንት ቀናት መናፈቄን ታውቂያለሽ? ፈጣሪዬን ለምኜው እንደማውቅ ታውቂያለሽ? ካንቺ አፍ የተሰማሽን ስሜት የሚገልፅ ቃል ፈልቅቆ ከማውጣት ....... "
አልጨረሰውም ቃል ጠፋው::

"ለምን አትጠይቀኝም ነበር? ዛሬ እንደጠየቅከኝ?ለምን ..."

"ለመልሱ ዝግጁ አልነበርኩም ነበር።" አለ ችኩል ብሎ!! ቀጥሎ

"ሁሌም እወድሻለሁ ስልሽ 'እኔም' ነበር መልስሽ። የዛሬ አራት ዓመት ህዳር 7 ጠዋት እወድሻለሁ ስልሽ 'እኔም' ማለቱ ሲያስምጥሽ አየሁ:: እያስጨነቅኩሽ እንደሆነ ስለገባኝ እወድሻለሁ ማለቱንም ተውኩት::"

ምን ልበለው ዝም አልኩ። ተቀምጦ ዝም አለ። እናቱ የሚወደውን ነገር ልትገዛለት ወጥታ መመለሷ እርቆበት በደስታና በጉጉት እንደሚቅበጠበጥ ህፃን እያደረገው ተቀመጠ።

"እኔኮ ግን ባትነግረኝም እንደምትወደኝ አውቃለሁ::" ብዬ ያሰብኩት ነው ያመለጠኝና ቃል ሆኖ የተናገርኩት

"(ፈገግ እንደማለት ብሎ) ቃሌን የሚተካልሽ ነገር አጊንተሽ አይደለም? መቼ ነው ለመጨረሻ ጊዜ ስጦታ የገዛሽልኝ? የዛሬ ሰባት ዓመት የልደቴ ቀን...."

(ሰባት ዓመት ሙሉ ሲዘንጥ የሚያደርገውን ሰዓት እያሳየኝ:: እሱ ባለፈው ወር ጫማ ገዝቶልኝ ነበር::)

"መቼ ነው ለመጨረሻ ጊዜ ፈልገሽ የሳምሽኝ? መቼ ነው ለመጨረሻ ጊዜ ባንቺ ተነሳሽነት ፍቅር የሰራ....." ቃሉን ሁላ ሳይጨርስ ተቀበልኩት

"ያስጠላኛል::" ዛሬ ምን ሆኜ ነው የማስበው የሚያመልጠኝ?

መጀመሪያ ደነገጠ:: ከዛ ከት ብሎ ሳቀ:: ከሶፋው ተነስቶ እግሬ ስር ቁጢጥ ብሎ .... እጆቹን እግሬ ላይ አድርጎ ወደ ላይ እያየኝ እየተንፈቀፈቀ ሳቀ.... ቡፍ ይላል እያረፈ....

"ምንም የሚያስቅ ነገርኮ አልተናገርኩም::"

"(ጭራሽ ከት ብሎ እየሳቀ) እንደሱ አድርገኝ ..... አዎ እሱጋ በለው ..... ብለሽኝ የነበረበት ዘመን እንደነበረ ትዝ ብሎኝ ነው::" ብሎኝ መንፈቅፈቁን ቀጠለ

"የቱጋ መቼ እንዳስጠላኝ አላውቅም::" አልኩት እንደማፈር እያደረገኝ

"ለኔ ያለሽ ስሜት የቀነሰብሽ ቀን" አለኝ ኮስተር ብሎ ቀጠል አድርጎ "ለምን በግልፅ አልነገርሽኝም? እያስጠላኝ ነው ማድረግ አልፈልግም ለምን አላልሽኝም?"

"ባሌ አይደለህ? ሴክስ ማድረግ አልፈልግም ይባላል?"

"ባልሽ መሆኔኮ አንቺን የማስደሰት ሀላፊነትም አብሮ ይሰጠኛል:: abuse እያደረግኩሽ እንድደሰት መብት አይሰጠኝም::" አለኝ:: ምንጣፉ ላይ በቂጡ ተቀመጠና እንደመተከዝ እያለ....

"ልነግርሽ የሚገባ ነገር አለ!" አለኝ

"አውቃለሁ!" አልኩት። ግራ ገባው። እንዴት እንዳወቅኩ ከመጀመሪያው ቀን ጀምሬ ነገርኩት።

"እንዴት አልጠየቅሽኝም? እንዴት አስቻለሽ?"

"አንተ ስንት ዘመን ሁሉ አስችሎህ ዝም ብለኸኝ የለ?"

"እንደዛ ነው የምታስቢው? ምናለ በይሆናል ራስሽን ከምትቀጪ ብትጠይቂኝ
ና የሚሰማኝን ብታውቂው? እኔኮ በዓይኔ ነው ያየሁሽ። የምጠይቅሽ ጥያቄ አልነበረኝም። ራስሽን ይቅር ያላልሽው አንቺ ነሽ። እኔ ገና ድሮ ይቅር ብዬሽ አልፌዋለሁ።"

"ምን ያህል ጊዜያችሁ ነው?"

"ካወቅኳት?" በጭንቅላቴ ንቅናቄ 'አዎ' አልኩት

"ከተዋወቅን ስድስት ወር ገደማ። .......ስለፍቅር ማውራት ከጀመርን አንድ ወር .......ከሳምኳት ሁለት ሳምንት ......." ከዛስ የሚለውን አይኔን አፍጥጬ እጠብቀዋለሁ።

"አድርገን አናውቅም። ታምኚኛለሽ?"
'አዎን' አልኩት በጭንቅላቴ ንቅናቄ:: ..... ዝም ተባባልን!! ..... ወርጄ አጠገቡ ተቀመጥኩ:: .... ምን እያሰበ እንደሆነ ልጠይቀው እፈልጋለሁ:: ግን ከአፌ አይወጣልኝም:: አቅፎ ትከሻው ላይ አስደገፈኝ:: ዝም ተባብለን ብዙ ከቆየን በኃላ ... .... አቅጣጫውን ቀይሮ ከፊቴ ተቀመጠ:: በጣቶቹ አገጬን ደግፎ ቀና አድርጎኝ አይኖቹን አይኖቼ ውስጥ ዘፍዝፎ

"ፍቅሬ እኔ ስላበድኩልሽ ያላንቺ ፍላጎት የራሴ አድርጌ ላቆይሽ እንደማልችል አውቃለሁ:: ምንድነው የምትፈልጊው? መለያየት ከሆነ የምትፈልጊው am ready now. ቢከብደኝም ልለቅሽ ዝግጁ ነኝ!! ምንድነው የምትፈልጊው? እንደገና መሞከር ነው የምትፈልጊው? Am ready ... አሁን ግን እኔን ወይም ቤተሰብሽን ሳይሆን ራስሽን ሰምተሽ ራስሽ ወስኚ .. .... የፈለግሽውን ጊዜ ያህል ውሰጂ የሚያስቸኩለኝ ጉዳይ የለብኝም::" አለኝ

"እሷስ?" (ኤጭ ዛሬ ምንድነው ችግሬ የማስበውን የማወራው?)

"(ሳቅ አለ) እሷ ስላንቺ ታውቃለች ጣጣዬን እስክጨርስ ላለመገናኘት ተስማምተናል::"

"ለመወሰን ብዙ ጊዜ ቢፈጅብኝስ?"

"10 ዓመት ጠብቄሽ የለ? እጠብቅሻለሁ::" አለኝ:: ከጀርባዬ መጥቶ እግሮቹ መሃከል አድርጎኝ ካቀፈኝ በኃላ "ያ የሚያስጠላሽንም ነገር አናደርግም (ድክም ብሎ እየሳቀ) ሆ ሰው ፍሰሃ ያስጠላዋል? (ቡፍ ካለ በኃላ) ራስሽ ፈልገሽ ያውም 'እባክህ ፍቅሬ' ካላልሽኝ አናደርግም" ብሎኝ እጁን በቱታዬ ስር ሰዶ ወገቤን አቀፈኝ::

ይሄ ሰውዬ ዛሬውኑ እባክህ ሊያስብለኝ ነው እንዴ?

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህንና ጥበብ
ጥበብ ይናፍቀኛል፤ ተቻችሎ የሚኖር ህዝብ ያስቀናኛል፤ ድንቁርና ያስፈራኛል።
©ሎሬት ፀጋዬ ገብረመድህን

👇JOIN (ተቀላቀሉን)
https://www.tg-me.com/tsegaye_gebremedihen
ባሌ እንዳመነዘረብኝ .... (ርዕሱን ቀይሩት ስትፈልጉ ግን የቀጠለ ነው) .... #6

"እስክትወስን እጠብቃታለሁ::" ይለኛል። ሁሌም የምንገናኝበት ቦታችን 'የምናውራው አለ' ብሎኝ ተገናኝተኝ የጀበና ቡናችንን እየጠጣን።

"እኔስ? በፍቅርህ የነሆለለ ጅል ልቤስ? ምን ላድርገው? እስከመቼ ጠብቅ ልበለው? ከሚስቱ እስኪታረቅ ልበለው እስኪለያይ? ንገረኝ የቱን ነው የምጠብቀው?" እንባዬ የአይኔን ድንበር አልፎ ተንዠቀዠቀ። ይሄን ያልኩት ብዙ ስለሷ እና ስላወሩት ከነገረኝ በኋላ ነው።

ሚስት ያለው ሰው ወድጄ ለምን ታረቁ የማለት መብት አለኝ? እሱስ የጠላችው ሲመስለው እኔጋ የወደደችው ሲመስለው እሷጋ እየሄደ በልቤ የመቀለድ መብት አለው? ማናችን ነን ልክ? ወይስ ማናችን ነን ትንሽ የተሳሳትን?

የሆነ ቀን እዝችው ቤት ቁጭ ብለን የተሰነጣጠቀ ስኒ ረከቦቱ ላይ አይቼ ተነስቼ አመጣሁት። አሳየሁት።

"ይሄን ስኒ አየኸው ውዴ ብዙ ተሰነጣጥቋል። ግን አልፈረሰም። አንዴ ብቻ ቢወድቅ ግን ይፈረካከሳል።" ብዬው ስኒውን ለቀቅኩት እንክትክቱ ወጣ። "የኔ ልብ ይሄ ስኒ እንደነበረው ነው። የምታነካክተው ከሆነ ከነስብራቱ ይቆይ ተወው።" ብዬው ነበር። የዛን ቀን ነው ለመጀመሪያ ጊዜ የሳመኝ። አልሰብረውም እጠብቀዋለሁ እንደማለት ያለ መሳም።

ከቀናት በፊት

"ለሚስቴ ካንቺጋር ያለኝን ነገር ልነግራት ወስኛለሁ። ከርሷ ጋር ያለኝኝ ነገር ጨርሼ ልምጣልሽ። እያደረግነው ያለነው ነገር ልክ አይደለም። ካንቺ ጋር ቆይቼ እቤት ስገባ ልፈነዳ ነው የምደርሰው።" አለኝ።

ዛሬ መጥቶ

"እስክትወስን እጠብቃታለሁ::" ይለኛል። ከቃሉ ይልቅ ውሳኔዋ መመለስ(አብሮ መኖር) እንዲሆን ተስፋ ማድረጉ። ለማሰብ መዘጋጀቷ እንዴት እንዳስቦረቀው ሳየው ልቤ ደረቴ ስር እንደዛ ስኒ እንክት ስትል ታወቀኝ። ተነስቼ ሮጥኩ። እየጠራኝ ተከተለኝ። ሮጥኩ ታክሲ እስካገኝ ሮጥኩ።

"አየህልኝ? ካልጠፋ ሰው ....ካልጠፋ ወንድ ባለትዳር? 'አላገባም! ካሁን በኋላ መውደድ አልችልም' ስልህ .......'ጊዜ ሀዘንሽን ያደበዝዘዋል። ... የሆነ ቀን የሆነ ሰው ወደ ህይወትሽ ይመጣል። ... ልብሽ ተሰብሮ እንደነበር ያስረሳሻል። .... ትወጃለሽ። ልብሽ እንደገና ሙሉ ይሆናል። ..' ያልከኝ። "

ሆስፒታል አልጋ ላይ ከተኛ ወራት ላለፉት ይስማኝ አይስማኝ እርግጠኛ ላልሆንኩት አባቴ ነው የምለፈልፈው።

"መጣ! ... ያ ሰው ወደ ህይወቴ መጣ ... ወደድኩት። .... ባለትዳር ነው አባ! ... ይሄን ዘመን ሁሉ ቆይቼ ካልጠፋ ሰው ልቤን የሰጠሁት የሚወዳት ሚስት ላለችው ሰው ነው:: ... አንተ እንዳልከኝ ልቤን ሙሉ አላደረገውም። አነከተው።" ተንፈቀፈቅኩ።

በራሴ ተናደድኩ። በፈጣሪ ተናደድኩ። በዓለም ተናደድኩ። በማላውቃት ሚስቱ ተበሳጨሁ። በሱ በራሱ ተናደድኩ። በአባዬም ስለማይሰማኝ ስለማያባብለኝ ተናደድኩ። ለሁሉም መልሴ እናባ ነው። ከአንጀቴ እየተሳበ የሚያንፈቀፍቀኝ እንባ።

"ለምን እንድወደው አደረገኝ? ሳለቅስኮ ነው ያገኘኝ? እንባዬን ጠርጎ አባብሎኝኮ ነው የተዋወቀኝ ...... አላሳዝነውም? .... እዛው እንባዬ ላይ መልሶኝ ይሄዳል?"

የህፃናት ማጫወቻ ቦታ ልጄን እያጫወትኩ ነበር።

"እማ እዛኛው ላይ መጫወት እፈልጋለሁ?" አለኝ ልጄ መጥቶ

"ባባዬ እኔኮ ከፍታ ያመኛል::" አልኩት የከፍታ ፍርሃቴን ለ6 ዓመት ልጄ ማስረዳት እየቸገረኝ። ቀና ብዬ መጫወቻው ላይ ልጆቹን አየኋቸው። አብዛኛዎቹ ከአባታቸው ጋር ነው መጫወቻ ላይ የወጡት ። ጉድለቴን ሊነግሩኝ ...... የልጄ አባት ምን ያህል እንዳጎደለኝ ሹክ ሲሉኝ ..... እንባዬ አይኔን ሞልቶ ደፈራረሰ።

"ይቅር በቃ ሌላ ጨዋታ እጫወታለሁ::" አለኝ የኔ የልጅ አዋቂ ጭንቀቴ ገብቶት።

"እኔ ይዤልሽ ልውጣ?" አለኝ የሚያባብል ድምፅ ከጀርባዬ ........ እሱ ነበር። ምንድነው የሆንኩት? የተሰማኝን ያወቀልኝ መሰለኝ። ውስጤ ያለውን የሰማኝ:: አዎ ማለት አቃተኝ። በጭንቅላቴ ንቅናቄ እየነገርኩት እንባዬ ተከታተለ። ልጄ እንዳያየኝ እያቻኮለ ብድግ አድርጎ ትከሻው ላይ ሰቅሎት ይዞት ሄደ። ተንፈቀፈቅኩ።

"ከሞተ አራት ዓመቱ ነው።" አልኩት ሳይጠይቀኝ። "እንዴት ነው የማይመለስን ሰው መጠበቅ ማቆም የሚቻለው? እንዴት አድርጌ ነው መናፈቅ ማቆም የምችለው:: እንዴት ነው ከርሱ ውጪ ህይወቴን መቀጠል የምለምደው? " እያልኩት እነፋረቅ ጀመር። አባበለኝ። እንደህፃን አባበለኝ። ... ብዙ ጊዜ እንደሚያውቀኝ:: .... ... አልቃሻ ብሆንም ለማላውቀው ሰው አላለቅስም ነበር:: እሱ ግን ባልገባኝ ምክንያት ቀለለኝ::

"የታል ያንተ ልጅ?" አልኩት

"ብቻዬን ነው የመጣሁት። ልጅ የለኝም ከነጭራሹ ..... ህም .... መውለድም አልችልም::" አለኝ መተንፈስ የፈለገ ይመስል ነበር። ልጄ እየተጫወተ እኔና እሱ ብዙ አወራን።

"ሚስቴ ትጠላኛለች። ልጅ ልሰጣት ስለማልችል ትጠላኛለች። .....ልጅ መውለድ እንደማልችል ሳልነግራት ስላገባኋት ትጠላኛለች። ....ለምን እዚህ እንደምመጣም አላውቅም። .....ልጆች ሲጫወቱ አይቼ እመለሳሉሁ። " እያለ ዝብርቅ ያለ ወሬ አወራኝ።

እዚህ ቀን ላይ ነው የመለሰኝ። ለቅሶዬ ላይ። እሱን ካወቅኩት በኃላ አላለቀስኩም ነበራ። ...

"እዚህ ነሽ እንዴ?" እያለች ታላቅ እህቴ ወደአባዬ ክፍል ስትገባ እየተነፋረቅኩ እንደሆነ አየችኝ።
በሩን ዘግታ የአባዬ አልጋ ጠርዝ ላይ እየተቀመጠች። ያለኝን ነገርኳት።

"ያንቺ ካለውኮ ተመልሶ ይመጣል::" አለችኝ።

የምትለው ግራ ገብቷት እንጂ ያለችው ምን ማለት እንደሆነ አልመነዘረችውም።

ለኔ ካለው? ለኔ ካለው አማራጩ እሆናለሁ። የመጀመሪያ ምርጫው እሷ ናት። እሷን ካጣ እኔጋ ይመለሳል? ለኔ ካለው ትርጉሙ ይሄ አይደል? ለኔ እንዲለው እሷ እንድትጠላው ቁጭ ብሎ መመኘት? ለኔ ካለው እንዲፋቱ መፀለይ? ትርጉሙ ይሄ አይደል? ቢለያዩና በቃ ጨርሻለሁ ብሎኝ ቢመጣ ስለወደደኝ ነው ወይስ አማራጭ ስላጣ ብዬ የምቀበለው?..... ለኔ ካለው የሚባል ነገር ምንድነው? እጣዬ ከሆነ ማለት ነው?

ከወራት በፊት የህፃናት መጫወቻው ቦታ ስንለያይ ስልክ ሳንለዋወጥ ... ስማችንን እንኳን ሳንተዋወቅ ቻው የተባባልን ሰዎች ከሱቄ ባሻግር ያለ የጀበና ቡና መጠጫ ቤት ቁጭ ብዬ ቡና ስጠጣ ሲገባ ሳየው ... እንደዛ አስቤ ነበር:: ምናልባት እጣ ፈንታ ነው:: ተዋወቅን ... አወራን .. በተደጋጋሚ ቡና ጠጣን.... የሆነ ቀን እኔም ስለባሌ እሱም ስለሚስቱ ማውራት ትተን ስለራሳችን ስናወራ ራሳችንን አገኘነው:: ....

ምኑጋ ነው የወደድኩት? ምኑጋ ነው ልቤን የከፈትኩት? ልክ እንዳይደለ አውቅ አልነበር? እያወቅኩ የቱጋ ነው የተረታሁት?

......... ...... እንክትክት ያለ ነሆለል ልቤን ከየት ወዴት ልሰብስበው? ሚስቱን ፈቶ እስኪመጣ ጠብቅ ልበለው?

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
መቻቻል የጥንት ባህላችን ነው!
((Maggie))


እሁድ 'ለት ነው.....
ሳይሰስት ያደለው የፍቅረኛውን አንገት አቅፎ ቤተስኪያን ይስማል (ያየውትን ነው እንግዲ! እግር ጥሎኝ ቤተስኪያን ልሳለም ስወጣ አዝመራ ላይ እንደተሰማሩ ጥማድ በሬዎች ተጣምሮ ነው ማየው) .... ተኩል ያደለው ብቻውን ሄዶ ይስማል......ያላደለው እንደኔ እዚ አልጋው ቮካል እየሰራበት እንቅልፉን ይለጥጣል. ....... ስለአልጋዬ ካነሳው አይቀር...... አልጋዬ ቴዲአፍሮን የሚያስንቅ ሙዚቀኛ ነው. ላይቭ ነው ሁሌ ሚያዜምልኝ.....ደግሞ ባንዶቹ! ..አይጦቹ በላይ በኮርኒሱ ሆነው ያጅቡታል.... እሱ ደግሞ በተገላበጥኩ ቁጥር ያንቋርራል. እኔ ሚያሳስበኝ እንቅልፍ መንሳቱ እንዳይመስላቹ.... እንቃፌን ቀላል እለጥጠዋለው! የፖለቲካ ምህዳራችን እንኳ እንደኔ እንቅልፍ አይለጠጥም!..............እንደው እድል ቀንቶኝ ሚስት ያገባው እለት እንዴት እንደምሆን ብቻ ነው....አስቡትማ.... 'የኔ ማር የኔ ውድ እኔኮ እንዴት እንደማፈቅርሽ'..... ብዬ ሳልጨርሥ .......እእእውውውይ! ቃቃቃቃቃቅ!..... ድድድድድድድድ ሲጢጢጢጢጥ.... ሲል!
..............
.....ታድያ እሁድ ለት በኦርኬስትራ ና ቮካል የታጀበ የአልጋዬን 'መልካም ጠዋት(good morning!)' ተቀብዬ ማመራው ወደ ፍሪጄ ነው! በሩን ስከፍት የበረሮዎች ሬስቶራንት የሞቀ የራት ግብዣ ላይ ደርሳለው! (አሁን በነሱ ቤት 'ጣይ ጠልቃለች አሉ! ሁሁሁ) ...........እንደውም አንዱ በርሮ "ፍሬንድ! እስቲ በሩን ዘጋ አድርጊው ...ላይቱን ደብዘዝ አድርጌ ከሚስቴ ጋ ሮማንስ ልሰራ ነበር" ሚል መልክት ሚያስትላልፍ ይመስላል... በዛ ደቂቃ ሁለት ነገር አስገረመኝ......... 1ኛ.በረሮው ቅዝቃዜውን የሚችል አንጀት ከየት አምጥቶ ነው? 2ኛ.በረሮው ወንድ መሆኑን እንዴት አውቄ ነው??? (ምናልባት ተለቅ ስላለ??ምናልባት ተጎኑ ያለችው እየተሽኮረመመች ስለሆነ.....) እያልኩ እየተፈላስፍኩ........

ትላንት ያስተረፍኩትን ሙቅ(አጥሚት) አውጥቼ ማሞቅያው ላይ ጥጄው... ፊቴን ልታጠብ ሄድኩ.....ስመለስ እላዩ ላይ ደርቆ አገኘውት! ሙቀቱ ያለሰልሰዋል ስል ለካ ፍሪጁ አድርቆት ኖሯል .......ለኔ አጥሚት ሲሆን ብቻ ነው እንዴ የሚሰራው ብዬ ፍሪጄን ላኮርፈው ስል................ የጨረስኩት የወተት ጣሳ ውስጥ ባለፈው ያስቀመጥኩት ሩዝ ትዝ አለኝ......... ልቀቅል ስከፍተው የቅድሙ በረሮ ይሁን ሌላ እንጃ..... በቅድሙ አስተያይት አየኝ... ዝም ብዬ ሳስብ " ጀለስካ! ምነው በበረኪና ካልሆነ አልለቅም አልሽኝ! ....ጫጉላዬን መጥፎ ትዝታ ልታደርጊብኝ አሥስበሽ ነው እንዴ??" ሳይለኝ አቀርም.

ሼፍ እንትና እንዳለው ሁለት ኩባያ ሩዝ ባራት ኩባያ ወሀ ቀቅዬ እየበላው... አንድ እንትን መጣ.... ምን አትሉም????? ጉንዳን ነዋ! ጠረቤዛው ላይ ከተበተነው ስኳር መሀል ተለቅ ያለውን መርጦ ተሸክሞ ሊሄድ! አይ ጉንዳን! በላባደሮች ቀን እውቅና ሊሰጠው ሚገባ ፍጥረት! (ሙድ ስንይዝ ኮ ነው! የላባደሮች ቀን ብለን ምናከብረው... ማርያምን!) የጉንዳን ተወካዮች ምክርቤት በዚ ትልቅ ቀልዳችን ሆዳቸውን ይዘው ሳይስቁ አይቀሩም!

ደግሞ አለች የቤቱ እመቤት! ተኝታ ነው ምትወለው! ምን ቸገራት እሷ. ይኸው እነንትና ባንድ እስኪከፍቱ ድረስ ዝምምም! ድመቴ! ባጠገቧ ፋሽንሾው የምታሳይን አይጥ "ወይ ስታምሪ ፣ እንቺኛዋ ትንሽ ወፈር ብለሻል..ዳይት ጀምሪ፣ አንቺ ትንሽ ጅራትሽን አሳጥሪው ፣አንቺ ደግሞ ትንሽ ጥርስሽን ሞረጂው " እያለች አስተያየት ምትሰጥ!! .........እሷ የምታውቀው ስመገብ ፊቴ ቁጭ ብሎ ሚስኪን አይን እያሳዩ እና እግር እየላሱ ፍርፋሪ መለመን! ከሩዙ ሁለት ማንኪያ ብሰጣት.. አሽትታው ሄደች!... "ስጋ ና ወተት ስጠብቅ ጭራሽ ሩዝ! ስግብግብ!" በሚል አይነት አረማመድ! (ቦዘኔ ድመት! እእህ!)

ጓደኛዬ ባለፈው ሊጎበኘኝ መጥቶ " ቆይ አንተ አሁን ብቸኛ ነኝ ብትል ማን ያምንሀል???" አለኝ
"እንዴት?"
"እነዚን ሁሉ ጉድ በነፃ አስጠግተህ እየኖርክ "
"አሁንማ ኮ አስጠግቼ አይደለም....... አስጠግተውኝ ነው!"

ከቤቱም ከዱሩም እንስሳጋ ተቻችለን ስንት ዘመን ኖረንን ምነው አሁን እኛ ለኛ ሲሆንን እርስበርሳችን መቻቻል አቃተንሳ!!!???

ኧረ መቻቻልኮ የጥንት ባህላችን ነው!

@wegoch
@wegoch
@paappii
ባሌ እንዳመነዘረብኝ ባወቅኩ ጊዜ እጅጉን ደስ አለኝ (የመጨረሻ ክፍል!! )

(አልጨረስንም እኮ ብትሉም ጨርሰናል። ጨርሰናል ብትሉም ጨርሰናል)

"አልቻልኩም:: .... አልቻልኩም!" ሁለት እጆችዋን ጨብጣ ደረቴን እየደበደበች ታለቅሳለች:: ጉንጮቿ እና ከንፈርዋ ይንቀጠቀጣሉ። አንጀት የራቀው ሆድዋ ይርበተበታል።

እየደጋገምኩ "እሺ" ከማለት ውጪ የምለው አጣሁ። ድብደባዋን ስታበቃ ንፁህ ያልሆነው መሬት ላይ በነጭ ሱሪዋ ተቀመጠች።

"ላናግርህ እፈልጋለሁ" ብላ ሱቋ ጠርታኝ ነው ሱቁን ዘግታ በእንባዋ እየቀጣችኝ ያለችው።

ከመምጣቴ በፊት ወይም ከጠዋት ጀምሮ አልያም ያለፈውን ቀናት በሙሉ እያለቀሰች እንደነበር አብጦ ለመከፈት የቸገረው አይኗ ያሳብቅባታል። ቅጣት ነው!! ፈጣሪስ ቢቀጣኝ ከዚህ በላይ በምን ቢቀጣኝ ነው ከዚህ የባሰ ህመም የሚያመኝ?

"እመነኝ እየወቅስኩህ አይደለም:: እረዳሃለሁኮ .... መደበቂያ ስትፈልግ .... የምትተነፍስበት ባጣህ ጊዜ አገኘኸኝ ....ጉድለቴን ስታውቀው ስላሳዘንኩህ ያፅናናኸኝ መስሎህ ፍቅርህ ውስጥ ደበቅከኝ። በትዳርህ ተስፋ ስትቆርጥ ልብህን የምታዘው መስሎህ ነው እወድሻለሁ ያልከኝ። ....እኔ ነኝ እንጂ ከንቱዋ እሷን እንደምታፈቅራት እያወራኸኝ ለሷ ባለህ ፍቅር ውስጥ ዘፍቄ የተዘፈዘፍኩ::" አለችኝ በየመሃሉ ሳግ እያቋረጣት

ይሄ ነገሯ ነው እሷ ውስጥ እንድጠለል ያደረገኝ። ራሴን እንዳልወቅስ የምታደርገኝ ነገርዋ ...... ራሴን ይቅር እንድለው የምታደርገኝ ...... ነገርዋ ራሴን እንድወደው የምታደርገኝ ነገሯ ....... ሰብሬያት እንኳን እኔ መጥፎ ስሜት እንዲሰማኝ ከማድረግ ራሷን ትኮንናለች ከዚህ በላይ ቅጣት ካለ ንገሩኝ?

አንዳንድ ሰዎች አንድ ሺህ ነገር አውርተሃቸው አንድ ሺውንም ይሰሙሃል። የቱንም ግን ላይረዱህ ይችላሉ። እሷ ሁለት ቃል አውርቼ ያላወራሁትንም 200 ቃል ደምራ ትረዳኛለች። ያ ነው እሷጋ ያስከንፈኝ የነበረው። የሆንኩትን ልነግራት ስጀምር እንዴት እንደሆነ በማይገባኝ ሁኔታ እኔ እንደተሰማኝ ...እንደዛው አድርጋ .... ትጨርስልኛለች:: እሷም እዛው ስቃይ ላይ እንደነበረች ........ የታመምኩትን እንደታመመች ... የተናደድኩትን ተናዳው እንደነበር ........ ልክ እንደዛው ........ ጥፋቴን እንኳን አጥፍታው የነበር እስኪመስለኝ እኔ እንደሚሰማኝ አድርጋ ትገልጽልኛለች።

ለምን ለሚስቴ መውለድ እንደማልችል እንደደበቅኳት ስትጠይቀኝ። ሌላ ሰው ሲሰማው ውሃ የማያነሳ ራስ ወዳድ ምክንያቴን ሳስረዳት

"አንዳንዴ የምትወደውን የማጣት ፍርሃት ምክንያታዊ እንዳትሆን ያደርግሃል። አሁንህን ለማዳን ነገህን ታበላሻለህ!" ነበር ያለችኝ።

"እረዳሃለሁ እሺ ... ትወዳታለህ!! ...እኔንም ትወደኛለህ። ....እሷ ሳትወድህም ትወዳታለህ! የተናደድክባት ጊዜም ትወዳታለህ። የበቃህ የመሰለህ ጊዜም ትወዳታለህ። ..... እኔ እንድጎዳብህ እንደማትፈልግም አውቃለሁኮ" ደግሞ አቁማ ድምፅ አውጥታ ታለቅሳለች።

"እኔስ ባሌንም ዛሬም ድረስ እወደው የለ ከዛ ደግሞ አንተንም ወደድኩህ አይደለ? አልፈርድብህም እሺ! ልብህ እሷጋ ነው:: አንተ አታዝበትም።"

ይኸው ከራሴ ጋር እንኳን እንዴት ነው ሁለት ሰው መውደድ የቻልኩት እያልኩ የምጣላበትን ሀቅ እኔን ሆና ታብራራልኛለች።

"እኔ ግን መጠበቅ አልችልም! አንተ እሷን ጠብቃት። የጥበቃህ መጨረሻ ምንም ቢሆን እባክህ ስወድህ ተመልሰህ እኔጋ አትምጣ! እኔ አሁን የሚሰማኝ ህመም እንዲያምህ አልመኝልህም ስለዚህ ትዳርህ ይስመርልህ። ባይሆንም ግን አትምጣ።"

መሬቱ ላይ ከነሱፌ አጠገቧ ተዘፈዘፍኩ። ላቅፋት እጄን ስዘረጋ ጥቅልል ብላ ውስጤ ተሸጎጠች። እናቱ ከገረፈችው በኋላ መልሳ ስታባብለው እንደሚብስበት ህፃን ህቅ ብላ አለቀሰች። ቁጥሩን ለማላውቀው ያህል ጊዜ ደጋግሜ ይቅርታ አልኳት። ይቅርታ ባልኳት ቁጥር ህቅታዋ ከአንጀቷ ድረስ እየተሳበ ህቅ እያለች ታለቅሳለች።

"አታስብ እሺ ምንም አልሆንም:: አሁን አባዬ ነቅቶ የለ? ህይወት ሁሉንም አትሰጥም አይደል? .... አልረሳህም ግን እተውሃለሁ።"

እንዴት ነው እንባዋ ሸሚዜን እያጠበው ፈገግ የምትለው? እያለቀሰች የምትስቀው? እየታመመች ደህና እንደሆነች የምትሆነው?

"ሂድ በቃ!" አለችኝ ከእቅፌ ወጥታ .... ልነሳ ስል ደግሞ ያዝ አድርጋኝ ...

"ቆይ ትንሽ ደቂቃ ልይህ.. " ጉንጬን አገጬን አንገቴን ፀጉሬን ስትነካካኝ ቆይታ

"እሺ በቃ ሂድ ...." አለችኝ ድክም ባለ ድምፅ

እየተንፏቀቅኩ ተነስቼ በሩጋ ከደረስኩ በኋላ ዞሬ አየኋት መሬቱ ላይ ኩርምት ብላ ጉልበቶቿን አቅፉ ሳያት ራሴን ጠላሁት። ምንድነው ያደረግኩት? ምንድነው ያደረግኩት? እንዴት ክፉ ነኝ?

እቤት ደርሼ መኪናውን ካቆምኩ ቆየሁ ግን አልወረድኩም። የሆነ ቦታ መጥፋት አሰኘኝ። ብቻዬን የምሆንበት ቦታ!! ባዶ ሆንኩ .....ባዶ .... ፀፀት ብቻ የሞላበት ባዶ ጭንቅላት ..... ህመም የበዛበት ባዶ ልብ !

ወደኃላ ተመልሼ ህይወቴን ማረም ብችል ከየት ነው የምጀምረው? ስህተቱ ይበዛል .... ባለትዳር ሆኜ ሌላ ሴት ስቀርብ? አይደለም ከዛ በፊት ሚስቴ እንድትጠላኝ ያደረጋት ውሸቴን .... እሱም አይደለም:: ለውሸቴ ሰበብ የሆነችኝ እውነቱን ስነግራት የተወችኝ የድሮ ፍቅረኛዬን? .... እሷም ጋር አይደለም .... ለመካንነት ሰበብ የሆነኝ የሞተር ሳይክል አደጋ.... ይሄን ሁላ ባጠፋው ... እኔ አልሆንማ!! ....

ስቆይባት በሩን ከፍታ ብቅ ስትል አየኋት:: እግሬን እየጎተትኩ ወርጄ ወደቤት ገባሁ::

"ምነው ደህና አይደለህም?"

"ደህና ነኝ" ካልኳት በኋላ መልሼ "ደህና አይደለሁም!" አልኳት እየተቆጣሁ እንደሆነ እየታወቀኝ።

"ምን ድረስ ነው ግን የምወድሽ? እንዴት አድርጌ ወድጄሽ ነው በህይወቴ ውስጥ አንቺ እስካለሽበት የሌላ ንፁህ ሰው ህይወት ማመሳቀል እንኳን ቢሆን ሁለቴ ሳላስብ የማደርገው?"

ያልኳት አልገባትም ዝም አለችኝ። አልፋኝ ሄዳ ተቀመጠች። እሷን ምን አድርጊኝ ብዬ ነው የምቆጣት? ዝም ተባብለን ደቂቃዎች ካለፉ በኋላ

መቼም እለዋለሁ ብዬ የማላስበው ነገር የአፌን በር ለቆ ሲወጣ ራሴን ሰማሁት::

"ለተወሰነ ጊዜ ብቻዬን መሆን እፈልጋለሁ!" የተገረመች መሰለች::

"ሁለታችንም ብቻችንን ጊዜ ያስፈልገናል::"

ጨርሰናል!!

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
((Maggie))

(ቆንጅዬ ምስቅልቅል)


አው ዝምተኛ ነኝ! ማውራት አልወድም ጋግርት የሚባል በሽታ ምናልባት አጥቅቶኝ ይሆናል......ግን አስተውላለው! የራሴን ነጥብ ይዛለው! እመዝናለው ....እገረማለው የራሴ ምለውን ልምድም ቀስማለው.... ከሞራል እና ከሀይማኖት አንፃር እያስተያየው እገመግማለው.... ቅሉ ግን .....አልናገርም!
መናገር አንድ ውድ ነገር አሳጥቶኛልና!


ብናገርስ ..ምን ዋጋ አለው!....ሸክላ አፈር ላይ እንደተርከፈከፈ እድለቢስ ውሀ ...ወደ ውስጥ ሳይሰርግ ይቀራላ! ወይ ደግሞ ጭስ በሚወጣባት የቆርቆሮ ቀዳዳ በምታክል ቅንጣት ሽንቁር .......... (ሁሉን በፍቅር ወደሚመረምረው) ልብ ሳይሆን.......... (በስሌት ና ብዜት ወደ ሚመረምረው አዕምሮ) ዘልቆ ገብቶ የተናገርኩትን ሰው ...........ካልኩት ነገር ላይ ሸካራና ሚዋጋ ነገር እየፈለገ መልሶ በንግግሬ ያስገዘግዘኛል....ከዛ ልምከር ልዝከር ባልኩት አፌ መልሶ 'ምነው አፌን በቆረጠው!' ያስብለኛል.

ከተወሰነ ግዜ ወዲህ(በተለይ አንተን ካጣው ወዲህ).........ተናግሬ ካተረፍኩት እፍኝ ነገር ይልቅ ዝምታዬን ተከናንቤ ያተፍኩት ጋን ሙሉ ነገር በልጦ አጊንቼዋለው. መሆን ግን የለበትም ነበር ....

አምላክ ለሁላችንም አንድአንድ አዕምሮና አፍ ያደለን ለብቻችን አስበን ከዛ በአፋችን ተነጋግረን ደግሞ በጋራ እንድናስብ ነበር. ዳሩ ግን ምን ዋጋ አለው........ ምንጣፉን ለአቧራው ብለህ ብትመታው .... ነገሩን ጠምዝዞ ባለ10 አቋም መጥፎ ነገር እየደረደረ ሲወቅስህ ታገኘዋለህ!

በርግጥ ሰው ከሰው ጋር ብቻ አያወራም! ከራሱ ጋር ..ከመፃህፍት ገፀባህርያት ጋር...ከተፈጥሮ ጋር... ከአምላክ ጋር... ከጥበብ ጋር ....ካሀሳቡ ጋ...ከብዙ ነገር ጋር ያወራል... ግን ደግሞ ይህ ነገር ሲበዛ ከተፈጥሮ ህግ ውጭ የመሆን እድሉ ይሰፋል.....
...
...
ለምትወደው ሰው ስህተቱን እንደመሸፈን ያለ መጥፎ ስጦታ የለም. እውነቱን ስትነግረው ትገነባዋለህ.... ታንፀዋለህ... ተመልሶ እንዳይደፈርስ ታጠራዋለህ.... ከእብቅ ማንነቱ ትለየዋለህ.. ... እንደተሳሳተ እያወክ ዝም ያልክ እንደሆነ ግን እየቀበርከው ነው...

ሰው አድጎና ተምሮ አላለቀም....እስኪሞት ድረስ ያድጋልም ይማራልም!.......

ከስተትህ ጋር ስላልተባበርኩ ብትጠላኝ ግድ የለኝም! ለምን እንደሆነ ታውቃለህ?? ከህሊናዬ ጋር ሰላም ፈጥሬያለውና. ብየንስ እዳ የለብኝም....... ሞራህ ተገፍፎልህ....." ልክ አልነበርኩምኮ!" ብለህ ስትፀፀት ያኔ እኔን አትወቅስም........ ድርሻዬን ተወጥቻለዋ!

ፍቅር እውነትን ትከተላለች
............................

እራስህን አጥርተህ ብስብስ ቦታ ብትቆም መልሰህ መበስበስህ አይቀርም........... እኔም ስህተትህን ባልነግርህ ኖሮ ትክክል ነኝ በሚል ትምክህት ዛሬንም ትቀጥል ነበር... እና ብዙ ነፍሶችን ትቀጣና ትበድል ነበር........

በዚ ምክንያት መቼም የማልረሳውን ነገር ተናግረህ ይኸው ዝምታን እንድማርጥ አድርፈኸኛል.....

"መቼም አፍቅረሺኝ አታውቂም!"

የእስከዛሬ መሰበሮቼ ቢሰሉ ይህንን አያክሉም!........ምላስ በሁለቱም በኩል እንደተሳለች ሰይፍ ነች! ትሰብራለችም ትጠግናለችም! .... እኔንም ሰብራኛለች.. .....
ለዛውም ካንተ ከማፈቅርህ ሰው አፍ የወጣ ሲሆን ደግሞ ስብራቱ ባስር ይባዛል...........

ነገር ግን ለምላስህ መርዝ ማርከሻ ልቤ ውስጥ ዘመን ማይሽረው ፍቅር ትተህ ሄደሀል....

አየህ እንዲ ፍቅርህ እያመመኝ እንኳ....... ከቃላት በላይ የሆነው ፍቅር ከልቤ እንዳይነቀል እየፀለይኩ ነው.

ከዚ ሁሉ ነገር ግን
አንድ ነገር አስተምረኸኛል....
ዝምታን!....

ሲያርር ሲከስል ሲጨማለቅ እውነት ከግርጌ ውሸት ከራስጌ ስትሆን... ውጥንቅጡ ሲወጣ.... ዝምምምምምምን ማለትን!

የዘመመውን ለማቃናት አፌን ልከፍት ስል...... ልቤ ውስጥ እንዳይጠፋ የምሳሳለት ፍቅርህ ይይዘኛል.

እናም......... ዝምተኛ ነኝ ... ጋግርታም!.....ባንተ ምክንያት ዝምምምምምምም እላለው! ..........

የዝምታን ትልቅነት ህይወት ምትባል ቅጧ የጠፋት መምህርት አንተን ሰጥታ በመንሳት በደንብ አስተምርኛለች!

እናም አዎ ዝምተኛ ነኝ!

@wegoch
@wegoch
@paappii
ከዕለታት በአንዱ ናፍቆትህ በፀናብኝ ቀን እንዲህ ሳስብ ዋልኩኝ። ፀሐዬ ዮሐንስ "ጊዜው ይርዘም እንጂ ማየት አይሻለሁ ሞት ካለየኝ በቀር በህይዎት እያለሁ" እያለ ያዜማል ሙዚቃውን ለምን ያህል ጊዜ እንደሆነ ባላውቅም፡ ቀኑን ሙሉ ስሰማው ዋልኩኝ። ከእኔ ባልሆነ እና በማልቆጣጠረው ስሜት እየደጋገምኩት። እንዲህ ባለ ፍቅር ውስጥ መኖር የምርም መታደል ነው። ሁሉም ይሄን ስሜት አጣጥሞ ኖሮት ለማውራት ላይበቃ ይችላል። ከልብ የመነጨ ፡ ጊዜ እና ርቀት የማይገድበውን ዕውነተኛ እና ሲወራ አፍ ላይ የሚጣፍጠውን ልብ የሚያሞቀውን ፍቅር! እደለኛነት ተስምቶኛል። በመሀል እንዲህ ሲል ደግሞ "ቀኑም አይመሽ አንቺን ሳላዎሳ በፍቅርሽ ታስሬ ቆጠርኩኝ አበሳ" በንዴት መሀል ፣ በኩርፊያ እንኳን ፣ በብስጭት ውስጥም ሆነን እናወራቸው የነበሩትን ነገሮች ፡ በቀን ውስጥ ለምናምነኛ ጊዜ በትውስታዬ ውልብ እያሉ ፈገግ ያደርጉኛል አንዳንዴም እያስገረሙኝ ፡ ብቻ አንተን ሳላስብ ፡ አንተን ሳላነሳህ አልውልም። ልቤን በሚያሞቀኝ በራሴ ፈገግታ ፈገግ እያልኩኝ ስምህን በለሆሳስ እያንቆለጳጵስኩ እጠራሃለሁ። ዓይኔ ላይ ስምህና ምስልህ የለተጠፈ ይመስል አንድም ቦታ አላጣህም እኮ ደሞ እንዲህ ብሎ ሲያዜም "ካንቺ ተለይቼ ደስ ብሎኝ አልኖርም ዓለም ካንቺ ጋር ናት አለዚያም አታምርም" በኩርፊያ እና በፀባችን ወቅት ከተማ ውስጥ አንድም ሰው ሊወደኝ የሚችል እንደሌለ እስኪሰማኝ ድረስ ይከፋኛል። ስናወራ ፣ ስንስቅ ፣ ነገኣችንን ስናወራ ትላንት የነበሩትን እያነሳን ስንስቅ እንደምትወደኝ በጆሮዬ ስሰማ ፣ እንደምወድህ ስነግርህ ፣ አይን ለአይን እየተያየን በደስታ ያወራንባቸውን ጥቂት ቀናት ሳስብ ደሞ ዓለም ላይ ደስተኛ እና ዕድለኛ ፍጡር ያለ እኔ ያለ አይመስለኝም! ልባዊ ፍቅር ፣ ከነፍስ የሆነ ፍቅር ሙዚቃው ቀጥሏል "በዓይኔም አያሳየኝ ያንቺን ክፉ ለኔ ቀድሜሽ መሞት እመርጣለሁ እኔ ምነው ተለያይተን እኔ ምጨነቀው እባክሽ ነይና መኖሬን ልወቀው " በመራራቅ ውስጥ ያለ ሀያል ፍቅር ፣ በየቀኑ መተያየት ፣ በየሳምንቱ መገናኘት በሌለበት ፡ ተስፋ የተሞላ ልባዊ ፍቅር ውስጥ ሆኜ ክፉህን እንዳያሰማኝ የምፀልይባቸው ቀናት ብዛታቸው ብታይ። ዛሬም ልክ ትላንት በነበረው መውደድ እወድሃለሁ!

መልካም ምሽት

@wegoch
@wegoch
@paappii

#ጠርሲዳ ከበደ
ልብ እና ብል

((Maggie))

አያውቅሽም አታውቂውም... አጋጣሚ አስተያያቹ እንበል..... ወደደሽ ተመሰጠብሽ..... በህሊናው,,,,,,,,,ፍቅረኛው ሆነሽ...ፈልም ላይ ሚሆኑትን ሁሉ ሆናቹ... አግብቶሽ... አሁንም ፊልም ላይ ሚሆኑትን ሁሉ ሆናቹ... ወልደሽለት... በሰላም ስትኖሩ እስክንጃጅ! ሚለውን የወንዲ ማክን ዘፈን ራሱ ለራሱ ጋብዞ የሌለ ምስጥ ብሎብሽ ,,,,,,, ራሱን ሳለው.... ፈገግታውን እንደንጀራ ፊቱ ላይ አስፍቶ ቀረበሽ..... ተለሳልሶ አንጀትሽን ለመብላት ሲሞክር... ተኮሳተርሽ.... አመናጨቅሽው... ተስፋ ሳይቆርጥ ሞከረ ደገመ ደጋገመ..... እውነት መስሎሽ... ጥርስሽን ከፈትሽለት.... ጭንሽን አንደምትከቺ ተስፋ በማድረግ ጥረቱን ቀጠለ.... ገፋበት... የሌለ ሰመጥሽ.... የሌለ ሰመጠ..... ውዴ ማሬ ካንተ ሌላ ካንቺ ሌላ ተባባላቹ.... እቅዱን ነገረሽ...አመንሺው..... ...እንደሱ አይነት ወንድ ስለሰጠሽ ቤተስኪያን ሄደሽ ሻማ አበራሽ.... ለጓደኞችሽ እንደምትወጂው ልታገቢው እንደምትፈልጊ ተናገሽ.... ተቃቅፋቹ ተሳስማቹ እየሳቃቹ የተነሳቹ ፎቶዎች ታግ እያደረግሽ ፌስቡክሽ ላይ ለጠፍሽ... አይለያቹ..ያዝልቃቹ... ስታምሩ.. ኮመንት ጎረፈ.... ወራት ነጎዱ..... በሰርፕራይዝ እና "አታምኚኝም? አትወጂኝም?" ሰበብ ከአንጀትሽ በታች ያለውን አስበላሽ... .. በጣም ስለምትወጂው ትመክሪዋለሽ መውጫ መግቢያውን ትቆጣጠርያለሽ.. ስልክሽን ሳያነሳ ሲቀር ትጨነቂያለሽ... ቴክስት ሳይመልስ ሲቀር ልትሞቺ ትደሻለሽ.... መላ አንቺነትሽን ሰጥተሽዋል... ከሀሳብሽም አይወጣም..... ትጋባላቹ... ምርጥ ግዜ ታሳልፋላቹ... ... ጫጩት ያስፈለፍልሻል.... ለቤትሽ እና ለጫጩቶችስ ራስሽን አሳልፈሽ ት አጭያለሽ......በዚ መሀል
...ሰውዬሽ ሌላ ታሪክ ውስጥ ገብቷል... ኦቨር ቁጥጥርሽ ተጨናቂነትሽ ለልጅና ቤትሽ ብለሽ አፈር መምሰልሽ... እንደድሮው አለመኳኳልሽ የወተት... የት/ት ቤት....የሽንኩርት.. አምጣ ማለትሽ ይሰለቸውና... ፈታ ያለች ፍለጋ ይመርሻል..... የድሮው ባህሪው ለምን ተለወጠ ብለሽ ትብሰከሰኪያለሽ... .. ልትጠይቂው ስትይ በንዴት ይመልስልሻል..... ግራ ይገባሻል ትናደጃለሽም ግን ምንም አታደርጊም....ጫጩት አለሻ!...... ቀስ ብለሽ የልጃገረድ ሽቶ ልብሱ ላይ ማሽተት ትጀምሪያለሽ.... ገንፍለሽ ስትጠይቂ....ትናቂያለሽ... ..... በፍቅር የሞቀው ልብሽ ወደ ብልነት ይቀየራል.... የቀረሽ ብቸኛ ፍቅር የልጅሽ ብቻ ነው......

የ"ልብ" ሆሄያት ቦታ ይለዋወጡብሽና ከግዜያት ቦሀላ

ፍቺ ፈልጋለው ትያለሽ ከሰውዬሽም ከራሱ ፍቅር ጋርም!

@wegoch
@wegoch
@paappii
ወንድ ብሆን ኖሮ!
((Maggie))

ወንድ ብሆን ኖሮ..ምን እንደማደርግ ታውቃላቹ??? የወንደላጤነትን ኑሮ በነፃነት መኮምኮም!..

ሌላሌላውን ተውትና(መረር ምትለዋን ማለቴ ነው) ያለተገደበ ነፃነት ውስጥ መዘፈቅ ነው ምፈልገው!

ለምን አላቹ? ...ጥሩ.... አንደኛ ነጠላ ነኝ..... ሁለተኛው እስካሁን ያልተነቀለልኝ መንፈስ...i am toooo lazy!
...ሰነፍ ነኝ.. እርቦኝ ለመብላት ም ሰንፍ.....
ለስካሁኑ ነጠላነቴ ይህ ስንፍናዬ ትልቅ ቦታ አለው...... .....ስልክ ተቀብሎኝ አንድ ዛግ ብሎ የፈረደበት ተባዕት... .. እናላቹ...ደወለ.... ለማንሳት ሰንፌ ይኸው የማታ እንጀራዬ ተዘጋ....ለነገሩ እንኳንም ቀረውበት..... ጨጓራው ይከዳው ነበር( ፀጉሩ ከከዳው ቦሀላ!)

ስንፍና ሚባል ዛር ከነዘመዶቹ የሰፈረባት ሴት በዛ ላይ ቦሰሮ( ሙያ የሌላት)በነፃነት መኖር ምትችልበት መንገድ ይኖር ይሆን......ብዬ
ከእንቅልፍ በተረፈኝ ግዜ ሳስብ..... የሰነፍ ነገር..... ምኞትን! ማይሆን ምኞትን! አስቤ ቁጭ...... ወንድ ብሆን ኖሮ!

ጎረቤት ቤቴ በመጣ ቁጥር የተበታተነውን የማስቲካ ልጣጭ...... የተበላበት ሰሀን.... ሶፋላይ ድብርድልብስ......ሶፍት..... ማበጠርያ..... ካልሲ.... ጡት ማስያዣ... ዶክመንት...ምናምን.... አይቶ ...ፊቱን ቁጥር አድርጎ "ምነው ምነው ምነው! ሴት አይደለሽም እንዴ??? ፀዳ ፀዳ አታደርጊውም" ከሚል አስተያየት 100ጫማ ከ2ካልሲ መራቅ!

ጠዋት ረፋዱ ላይ ከቁርባን የተረፈ መክፈልት ለበረከት ብለው ሊሰጡኝ በሬን ከሚቆረቁሩት አከራዬ ወይዘሮ ሀረጓ ... "ወይ! እንደው ምን ይሻልሻል ይይይይይይ? እንደ ሴቶቹ በጠዋት ተነስተሽ..ጉድ ጉድ አትይም!" ከሚለው ሽሙጥ ጣል ያለበት አስተያየት መዳንን ነበር ምፈልገው

በተለይ ክንዴን ሳየው!..... ወንድ የመሆን ምኞቴ ቅናትን አስከትሎ አናቴ ላይ ይወጣል.........ወንድ ስለሆነ ብቻ አብዛኛው ሰው...ሁኔታውን አይቶ "አግባ! ብታገባኮ ልክ ትገባላህ" የሚል አስተያየት ይሰነዝርለታል... እኔጋስ??????? እኔጋማ " ቆይ ስታገቢ እንዴት ልቶኚ ነው??? ሸክም?? የሴት ሰነፍስ አይጣል!! ባልሽ ግን ውይይይይ!!" ይባላል.

ቆይ ነጠላ ወንዶች ብቻ ናቸው... አልጋቸውን ለመኝታነትም ለቁም ሣጥንነትም መጠቀም ሚችሉት?.... ማነው ይህንን ህግ ያረቀቀው? እእ?....... እነሱ ብቻ ናቸው... መኮረኒ አጥበው አስጥተው አድቀው ሚቀቅሉት?? .. ... እራት በበሉበት ሰሀን ሳያጥቡ ደግመው ቁርስ መብላት ሚችሉት እነሱ ብቻ ናቸው????? ..
በላብ ብክትትት ያለን ሸሚዝ በሳምንት 7ቀን ከ5 ቀን ሚለብሱት??? ወይስ ካልሲያቸው ደርቆ ሰው እስኪፈነክት ድረስ መል በስ ሚችሉት??

ባሁኑ ዘመን affermative action ያልተወሰደበት ጉዳይ ቢኖር የነጠላ( single) ሴቶች ጉዳይ ነው. "እንደፈለጉ መኖር ይችላሉ!..... አስተያየት ሰጪዎች በሴተ ላጤዎች ኑሮ ላይ አስተያየት ስትሰጡ የአፈርማቲቭ አክሽንን ህግ ተግባራዊ ያድርጉ" ብሎ አቢቹ ማስታወቂያ መልቀቅ አለበት.

ኧረ ጎበዝ እህመነው!... መኖር አልቻልንም!...... መረረን!

በላጤ ወንዶች ስም የተከፈተ fb እድር ውስጥ (ያው በኦንላይን ማስተዛዘን ነው ብዬ ነው ኮ ግሩፕ ያላልኩት) ብገባ ይባስ እያስቀናኑ ሆዴም አባቡት... ... በሴቶች ስም ልግባ ብል.....ምናልባት አንዷ የምታቀኝ የ5 አመት ቂሟን ብትወጣብኝ ስ.... በሰው ፊት ጉድ ሆንኩ አይደል!........ ወይ እንደ አሁንስ ወንድ በሆንኩ! ኤጭ!

@wegoch
@wegoch
@paappii
የዶክተር አብይ መግለጫ!
((Maggie))

አብቹ! ተወዳጁ መሪያችን (የናንተን አላውቅም እኔ ግን ሌላው ቢቀር ጎልማሳነቱን ቀና ብሎ መራመዱንና ቀና ማሰቡን ውድድ አደረግለታለው፣፣ ያው ያለፈው ታሪካችን እንደሚሳብቅብን.. ቀና ብሎ መራመድና ቀና ማሰብ ትንሽ ሚያዳግታቸው ሙሴዎችን ነው ያሳለፍነው)

እናላቹ አቢቹ በfb እድር (የዲጂታል ወሬ ፍትፈታ ጣብያ! ማስተዛዘንንም ይጨምራል..... ማርክ ዙከምበርግ እና ጭፍሮቹ ማያመጡብን ጉድኮ የለም!.............
የርጎ ዝንብ በሆነ ዜና..........
.... የሆነ ሰሞን... የአያቴን ህልፈተ ህይወት አስመልክቶ እዝን ውስጥ ገብቼ ነበር.... ድንኳን ጥለው ...ንፍሮ ቀቅለው.. ቡና አፍልተው ጥብስን የሚያስንቁ ወሬዎች እያወሩ ያስተዛዝኑኛል ብዬ ስጠብቅ.... 'ፍቅር ፈላጊ ኳታኞችና አጋሮቻቸው' በሚለው የfb እድር( ግሩፕ!) የሀዘን መግለጫቸውን አዥጎደጎዱልኝ! ምን እላለው ታድያ ማርክን .....እእእ....ማነው ይሄ ደግሞ.. ስቲቭን ረግሜ ዝም!)

የት ነበር ያቆምኩት........

አዎ....እናላቹ አብቹ በfb እድር ስለ ሰውነቱ ማማር፣ ስለፊቱ መስታወት መምሰል ፤፤በተለይ በተለይ ስለከንፈሩ ሮዝነት ሲወራ ይሰማል. ...... ............ በተለይ አታክልት ወሀ እያጠጣ እያለ፣ አርቴፊሻል እግር ሚሰራበትን የጎበኘ ግዜ፣ መግለጫ ምናምን እየሰጠ እያለ የሚፖሰተው ፎቶ ላይ ........

"በርታ! ፣ታታሪው መሪያችን!፣
ያይናችን ብሌን ነህ!፣ ትንቢት የተነገረልህ መሪ መሆንህን እያረጋገጥን ነው!፣ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ!" የሚል ኮመንት ሲጠብቅ.......

" pmዬ የዛሬው ሜካፕህ አንጀሊናን ያስንቃል! ፣ ፓ! የዛሬው አለባበስ ደግሞ እንትናን ነው ያስታወሰኝ!!፣ ምነው ማዲያትህ ፈጠጠ ?? ፓውደር አለቀብህ እንዴ!?? በዚ አድራሻ ኢሜል አርግልኝ ኦርጅናል ፓውደር ሸጥልሀለው ፣.. ዶክተርዬ የለበሻትን ቱታ የት እንደማገኛት ትጠቁሙኝ?? ......" የሚሉ ኮመንቶች ሲዥጎደጎዱ

ብልጡ መሪ ...ለምን መግለጫ አልሰጥም! በዛውም ለምርጫ ቅስቀሳ የጃጀ ወሬ ከማወራ .... የውበቴን ምስጢር ብናገር ወጣቱ ትውልድ ስለሚበዛ አሪፍ ይሆናል!" ይልና... ... ተዝኽ ለጥቆ ያለውን መግለጫው ይሰጣል


"ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! ዛሬ የምሰጠው መግለጫ ስለሚስጥራዊው ውበቴ ይሆናል...... ከፍትፍቱ ፊቱ ነውና...በጠዋት ተነስቼ ነጭዱቄት በጥብጬ ፊቴን በስ ሱ ቀብቼ ለ15 ደቂቃ በእንፋሎት አጥነዋለው.. ከዛ እታጠበዋለው ቀጥሎ ባለቀው የልጄ ሹራብ አደርቀዋለው... .... .... ሚስቴ ካጠፋችው የእሳት ጥፍያ መሀል ተለቅ ያለው ክሰል መርጥና ጥርሴን ቦርሸዋለው ከዛ ቅድም ባሞቅኩት ውሀ እጉመጠሞጣለው! ንጣቱን ሰፊው ያሀገሬ ህዝብ ይገልጠው ዘንድ ትቸዋለው!

ከኩሽና ወደ ሳሎን ከሳሎን ወደ ምኝታ ቤት በመንጎራደድ ካሎሪዬን እቀንሳለው! ምድረ ዝፍዝፍ አንዳድን የሀገር ልጅ ብልሀቷ ይችው ነች ተጠቀምባት!....... በቀጣይ "አገር መሪ ስትሆን ትለብሰዋለህ" ብላ እናቴ ያስቀመጠችልኝን ልብስ አማርጬ ለብሳለው... እዚ ጋ ባለፈው የለበስኩት ቱታ የምሽቴ ስጦታ ነው!... በተረፈ ያነጋጋሪው የከንፈሬ ጉዳይ እንደሆነ ብዙሀኑ ነግሮኛል...... ይገርማችዋል.. .. በትርፍ ግዜዬ የምንከባከበው የጓሮ አትክልት አለኝ.... የሱን ውለታ በምን ቃላት መግለፅ እንደምችል አላውቀውም.... ለዚ ዝና እንድበቃ ቀይስሬ ትልቅ ሚና ተጫውቷል( ስሜታዊ ሆነው ነበር እዚጋ!) እንባቸውን ጠራርገው..... እእእ! ወደ አዘገጃጀቱ ስንገባ.... ግማሽ ቀይስር ይከተፋል በአንድ ብርጭቆ ውሀ ይቀቀላል ከቀይነት ወደ ሮዝነት እንዲያደላ ግማሽ ኩባያ ውሀ ይጨመራል.... ጣዕም እንዲያመጣ ስኳር ይጨመራል መዐዛው እንዲጣፍጥ የሚስቴን ሽቶ( ኤቭሪባዲ .....ባለህ ነው! ሉባንጃ ወይ ሰንደል አልያም ደግሞ በረሮ ማጥፊያ ፊሊትም ሊሆን ይችላል) ነስነስ አደርግበታለው...... ከዛ በቃ መቀባት........
ሰፊው የሀገሬ ህዝብ ሆይ ይህን ብልሀት ተጠቅመህ አለምን በውበትህ እንደምታስደምመው ጥርጥር የለኝም... በተጨማሪ ክሬዲቴን ምርጫ ላይ ድምጥ በመስጠት እንድትከፍለኝ በውበቴ ስም ጠይቃለው.... አበቃው!"
...

@wegoch
@wegoch
@wegoch
ሁሉንም መፅሀፎቹን አንብባለች፣ ከጥግ እስከጥግ. . .እያሰላሰለች፣ እየመረመረች. . . ከቃላቶቹ ብቻ በደንብ እንደምታውቀው ይሰማታል። እንደምታውቀው፣ እንደምታደንቀው፣ ስለግጥሞቹ ለቀናት እና ለወራት ልታወራውና ልትጠይቀው እንደምትችል አስባለች፣ ደጋግማ። የአድናቆቷን ልክ
የተረዳ ጓደኛዋ የሚያውቀውን ሰው ፈልጎ ስልኩን ሲቀበልላት ፣ የተሰማት ደስታ ልክ አልነበረውም። ስለምትቃረናቸው እይታዎቹ፣ ስለምትደግፈው እሳቤው፣ ስላስደነቃት ምልከታው ሲያወሩ ፣ ሲከራከሩ በምናቧ ትስላለች። ለመጀመሪያ ጊዜ ለመገናኘት ሲቀጣጠሩ ብቻዋን እንዳትሆን፣ አየሩም እንዲቀል ሌላ ጓደኛዋን አብራት እንድትመጣ ትጋብዛታለች። ካፌው ሲደርሱ ተቀምጦ አገኙት፣ ሰላምታ ተለዋወጡ፣ ተቀመጡ። አይኑ ወዲያውኑ ጓደኛዋ ላይ ሄደ። ለሚቀጥለው አንድ ሰአት አይኑ ተሳስቶ እንኳን እሷ ጋር አልተመለሰም። በህይወቷ ለመጀመሪያ ጊዜ የማትታይ የማትዳሰስ የሌለች አካል እንደሆነች ተሰማት። አየሩን በእሱ ድምፅ
ሞላው፣ አንዳንዴ አይኑን ከጓደኛዋ ሳይነቅል “እናንተስ?” የሚል ጥያቄ ይወረውራል፣ ምናልባት የጓደኛዋን እንጂ የእሷን መልስ ለመስማት ፍላጎት እንዳልነበረው ለማወቅ ግን የጠፈር ተመራማሪ መሆን አልነበረባትም። ትንሽነት ተሰማት። ወንዶች እሷን አልፈው ሌላ ሴትን ሲያዩ የመጀመሪያዋ አይደለም። ለምን የእሱ እንደዚህ ጎልቶ ታያት? በሀሳቧ ትልቅ አድርጋ ስለሳለችው ነው? ያደነቀችው ስለስራው ነው እንጂ ስለወንድነቱ አይደለም። ፍራንዝ ፋኖን ስለ “gaze of desire” እና ራሳችንን እንዴት በሌሎች የመፈለግ ምልከታ ውስጥ እንደምንመዝን የፃፈውን አስታወሰች። እንዲያ የጓጓችለት ቀጠሮ ረዘመባት፣ ቶሎ እንዲያልቅ ተመኘች። ጨርሰው ለመሄድ ሲነሱ እንዲፈርምላት ይዛ የመጣችውን መፅሀፍ መልሳ ቦርሳዋ ውስጥ ከተተችው። የምትወዳቸውን ፅሁፎቹን እንደድሮው በንፁህ እና ክፍት ልብ አነባቸው ይሆን? ብላ አሰበች። ባታገኘውስ ኖሮ? አሁንም የሌሎች “gaze of desire” እሷን አልፎ ሲሄድ ታያለች፣ ታጠናለች።

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Hewan Hulet Shi🖤
ቢራ ቢሮ
ደብዳቤ
.
.
.
ሁሉም ነገር ያለዉ ጭንቅላቴ ዉስጥ መሆኑን እያሰብኩ ዳግም ከራሴ ጋር እቃረናለሁ፤ ትዉስታዬ ቢሰወር እይታየ ቢደበዝዝ መገለጥህን እናፍቃለሁ። አጠገቤ ስትቆም የልቤ ምት ከገላዬ አልፎ እንዲሰማ በዜማህም እንደ ቅጠል መወዛወዜን አዉቃለሁና። ጠረንህ ማህሌት ቆሞ እንዳደረ ካህን ያዉደኛል፤ ይሄ ከብሩህነት የረቀቀ ስሜት እንደምን ያለ ተኣብ ነዉ? ነፍሴ አንተን ትሻለች፦
ባታምንም እንኳ እንዲያ አስባለሁ፣ ምንምን መዉደድ የሚቻለዉ ከነፍስ ወዲያ ምን አለ? ባዶነትህ ጥላ ያለዉ እኔም ላይ ታጠላብኝ ዘንድ የወደድሁ፣ በነፍሴና በአእምሮዬ መካከል የተፈጠረዉ ተቃርኖ ያላጠፋኝ፣ ይልቁን መፃረርን ሸሽተዉ ተደጋግፈዉ ያቆሙኝ ያህል ይሰማኛል። ምንምነትህን ወድጄ ስዉር የእግሮችህን ዳና ተከትዬ ይሄም ረቆብኝ በአንተ ዘልቄ ጥላህን መንካት ሲቻለኝ፤ ይህን የጠረን ዳና ከወዴት ነዉ የማዉቀዉ? አልኩኝ፤ የደራ ቀዬ መሀል ቆሜ ከግርግሩ እንኳ ፈቀቅ አላልኹ፤ ታዲያ በሞሳነቴ የማዉቀዉ የደብር እጣን ከወዴት አወደኝ? ይሄስ እንዴት አያስተኣጅብም? ለብዙ ቀናት ባለሁበት ቆሜያለሁ፥ ከቆምኩበት ሳልዘንፍ ክረምት አልፎ ሄዷል፣ እልፍ ተሲያቶች አዝግመዋል፣ በመንገዱ ላይ የተሻገርኩ
ሳይሆን ጊዜም ጎዳናዉም ባለሁበት አልፈዉኝ የተሻገሩ እስኪመስለኝ።
.
.
.
አይኖቼን ስገልጥ ፀሊም ነፋሴ ሆይ ብዬ ጠራዉህ። ወደ አላወቅሁት አለም ወስደህኛልና መገለጥን አስተምረኸኛልና ይህ እንዴት ድንቅ ነዉ ብያለሁ። ለዚህም የኔታዬ ነህ ኦ ረቢ!
.
.
ከሄድኩበት አለም ስመለስ አጠገቤ የነበሩት አበቦች አንገታቸዉን ደፍተዋል ቀለማቸዉም ደብዝዟል። በከናፍሮቼ እንዳልነካኋቸዉ በጣቶቼ መዳበስን
ነፈግኋቸዉ፣ አፋፍ ላይ ወጥቼ የፀሀይዋን መዉጣት እንዳልጠበቅሁ ሰባራ ጉቶ ላይ ተቀምጨ ግባቷን እንዳልቃኘሁ ከዉበቷ ይልቅ ደም የለበሰ አስፈሪነቷ አስበረገገኝ። እኩለ ሌ'ት መስኮቴን ከፍቼ የጨረቃዋ ፀዳል ባህሩ ላይ ሲያርፍ ባህሩም በጨረቃ መሳምን ናፍቆ ማዕበሉን ፀጥ ሲያደርግ እንዳላየሁ፦ ይህ እንዴት ያለ መፍዘዝ እንዴት ያለ ድኩም ብርሃን ነዉ ብዬ ተሳለቅሁ። ከወጣሁበት ተራራ ስወርድ ምቾቴን ሸምቼ በእጆቼ የጨበጥኩትን ረገጥኩ።
.
.
ህልም አለምኩ ጥቁር ህልም ከህልሜ ስነቃም እሸሸግህ ዘንድ ሮጥኩ፡ ነፋስን
ማምለጥ እችል ይመስል፤ ቁልቁል ነፍሰህ በላዬ ስትረብ በዝምታዬ ዉስጥ
እንዲህ አንሾካሾኩ፦ ነፋስን መከተል አለመስከን፣ አለመርጋት የያዙትን መልቀቅ፣ ከደርዙ ለመቆም ትላንትን መርሳት። እናም ነፋሴ ሆይ እንዳሻህ ተመላለስ፤ ነፍሴ በመቅደስህ ሽቶ መዓዛ ትታወድ። ትርምስህም ዉስጥ ልጥፋ ሁለመናህን እንዳይ ደግሞም ምንም አልወቅህ፣ ገላዬ እንዲቀልጥ፥ ጠፍቼም እንዳልቀር ህያዉ እንድሆንም። ከእኔ ርቀህም ሂድ ወደ ጥልቁ፤ እንድታመም ባንተ መሻርን እንድናፍቅ። አይኖቼም ዙሪያየን ይቃኙ በአበቦቹም ፍካት ደስ ልሰኝ፣ ጨረቃም በእኩለ ሌ'ት የባህሩን ከንፈሮች ትዳብስ፤ ማዕበሉም ፀጥ ይበል፣ እኔም ፍቅርን ላቃስት፣ በመሄድህም አልጉደል በመምጣትህም አልሙላ ረቢ ሆይ።
*//*******
~ያንተዉ ቢራቢሮ
ታህሳስ 18 /2013
አዲስ አበባ

@wegoch
@wegoch
@paappii
Meri is back!!

★★ ስንቴ ገረዝኩት? ★★
(ሜሪ ፈለቀ)


"አንቺማ አትገርዢኝም። በስመአብ! " አለ እያማተበ ለመቀመጥም ለመነሳትም በቀረበ አኳኋን አየሩ ላይ ተንጠልጥሎ።

"አየር ላይ ነህ፣ አረፍ ትል?" አልኩት አኳኋኑ ሳቄን እያመጣው

"የታለ ዶክተሩ ከምር? " አለኝ ወንበሩ ላይ ተስተካክሎ እየተቀመጠ

"እኔ ነኝ!!" አልኩት ምን እንደሚያስብ ለመገመት እየሞከርኩ

ካርዱ ላይ የተፃፈው እድሜ 33 ይላል። ወጣት ነው፣ ማንም ሴት አይታው የምትደነግጥለት ዓይነት ቁመናና መልክ፤ በራሱ የሚተማመን የሚመስል ገፅታ ፤

"አንቺማ አትገርዢኝም። ይዤው አረጃታለሁ እንጂ………" አለኝ ለኔ ሳይሆን ለራሱ የሚያወራ በሚመስል ድምፅ

"ለምን? ሴት ስለሆንኩ?"

"አወና ፣ ሴት ብቻ አይደለሽም። ህልም የመሰልሽ ቆንጆ ሴት ነሽ። ሆ!!"

"እሱ ከስራዬ ጋር ምን አገናኘው?"

"ላንቺ ነዋ ስራ…………" ቀጥሎ ያልሰማሁትን ነገር አጉተመተመ

"ይቅርታ አቶ ሲሳይ ብዙ አገልግሎት ፈላጊዎች ውጪ ተሰልፈዋል። ስራችንን እንቀጥል?"

"እህ ስለተቆጣሽ ይሰማሽ መሰለሽ እንዴ?" አለ ወደሱሪው ዚፕ አይኑን እየላከ። መሳቅ አምሮኛል ግን መሳቅ የለብኝም።

"እንዴት ሳትገረዝ ……….?" ጥያቄዬን የምጨርስበት ቃል ስፈልግ

"አረጀህ? አይባልም ግን እሺ! ……….. ባክሽ አንጀት ነው ታሪኩ። ………… ተረት ነገር ነው የሚመስለው።"

"እየሰራሁ ታወራኛለሃ!!"

ብድግ ብሎ ገላውን አራቆተው።
"እንዴ እዚህ አይደለም የምሰራው።።።" አልኩት

"ቆይ ግን ትልቅ ወንድ ገርዘሽ ታውቂያለሽ?" አለኝ ምንም የተጋለጠ ሳይመስለው ተረጋግቶ ልብሱን ወደሰውነቱ እየመለሰ።

" አዎ። አውቃለሁ። "

"እኔን የሚያህል?"

" ካንተም የሚበልጡ"

"ይሄን ነገር መቼም እንዲህ እንደቆመ አትገዘግዢውም አይደል?" እፍረት አይታይበትም። ስለቆመው አክሱም እንጂ ስለቆመው ንብረቱ ያወራ አይመስልም። በድጋሚ መሳቅ አምሮኛል። ፊቴን አዙሬ ፈገግታዬን ደበቅኩበት። ጭንቅላቴ ውስጥ ብቅ ያለው ሀሳብ ግን ቆሞ ነበር እንዴ? የሚለው ነበር። በየሱስ ስም!

"ማደንዘዣ እሰጥሃለሁ።"

"እህ! አይደለም ማደንዘዣ ፀሀይ የመሰልሽ ሴት ነክተሽው ሞቼ እንኳን ቢሆን አይቆምም?"

አሁን አለመሳቅ አልችልም ነበር። መጥሪያዬን ተጭኜ እጄን ከማንሳቴ ሲስተር ገባች።

“ኸረ ፍጥነት? በሩ ላይ ነበረች እንዴ? ” በማያገባው የሚገባ ሰው በቸልታ ማለፍ አልችልም እኮ ግን እንዳልሰማ ወደ ሲስተር ዞርኩ

”OR 2 ይዘጋጅልኝ። ማረፊያውን ታሳይሃለች እዛ ቆየኝ።” ካርዱን ለሲስተር አቀበልኳት። እሷ ያልኳትን ሰምታ ወጥታለች። እሱ እንደተቀመጠ በትዝብት ያየኛል።

“ምንድነው?”

“ይሄን ፊትሽን ግን ስሞትልሽ ፀብ ሲኖረኝ ሲኖረኝ እዋስሻለሁ። እንቢ እንዳትዪኝ! ኸረ በኪዳነምህረት!! “

“አቶ ሲሳይ የሚመለከተን ነገር ላይ ትኩረት እናድርግ?“

“you see እያናደድኩሽ እንኳን ፈገግ ብለሽ ነው የምትቆጪኝ። ምክንያቱም ደሞዝሽን የምከፍልሽ እኔ ነኛ! ባትመቺኝ ሌላ አማራጭ እንደምጠቀም ታውቂያለሽ። ስለዚህ ምን ያህል ስድ የሆነ costumer እንኳን ቢገጥምሽ በትህትና ታስተናግጃለሽ። ረዳቶችሽ ወደውሽ እንጂ ደመወዝ ስለምትከፍያቸው ፈርተውሽ እንዲታዘዙሽ አታድርጊ! እንደዛ ሲሆን አብረውሽ ያሉት ምርጫ እስካጡ ድረስ ብቻ ነው ማለት ነው።”

ልለው ያሰብኩት ብዙ ነበረ። ዋጋ ያለው ስላልመሰለኝ ተውኩትና እንዲወጣልኝ ብቻ በሩን አሳየሁት። ተነስቶ እየወጣ በሩን ተደግፎ ቆም አለና

«ያንቺን ስራ ደመወዝ ከፍለሽ እንደምታሰሪያቸው ሳይሆን እነርሱም የስራው አካል እንደሆኑ እንዲሰማቸው አድርጊ ያኔ ላንቺ ወይ ለደሞዝ ብለው ሳይሆን የራሳቸው ስራ መሆኑን ስለሚያስቡ ማንም ስራው እንዲበላሽበት አይፈልግም።»

«አቶ ሲሳይ ስድስት አመት ይሄን ሆስፒታል ቀጥ አድርጌ አስተዳርያለሁ። ሰራተኞቼን እንዴት መያዝ እንዳለብኝ አንተ አትነግረኝም!!» እንዴት ያለው ነው? እያናደደኝኮ ነው። ፈገግ ብሎ ከወጣ በኋላ መለስ ብሎ

«አይባልም ግን እሺ! ቤት ውስጥ የተቀጠረ ሰው እንኳን አሁን ቀርቷል ሰራተኛ አይባልም። ሆስተስ፣ አቀናባሪ ምናምን ነው የሚባለው። በሙያቸው የሚረዱሽን ሰዎች ሰራተኞቼ? ኸረ አይባልም!» ብሎኝ በሩን ዘጋው!! ኡፍፍፍፍፍፍፍፍ ምን አይነቱን ነው ዛሬ ደግሞ የጣለብኝ?

★ ★ ★

በሶስት ቀናት ውስጥ የተኛሁባቸው ሰዓታት 7 መሙላታቸውን እንጃ። እቤቴ ሄጄ አላውቅም። ተረኛ ታካሚ እስኪገባ ስጠብቅ እያወራ ወደ ውስጥ ዘለቀ።

"ስንቴ ነው የምትገርዢኝ?"

"ማለት?"

"ቁስሉ ተቦትርፎልሻል። ጨርሺኝ ብዬ ነው አንቺውጋ የመጣሁት።"

"አልገባኝም። እስኪ እዛጋ ሁንልኝ። ምን ሆኖ ነው?" አልኩት

"እኔ አንቺን ማሰብ ማቆም አቃተኝ። እሱም አለመቆም አቃተው። ተነፋፋሁ ሲል ቁስሉ ጣጣጣ…………" የሚያሾፍ ይመስላል። ቁስሉ ግን እንዳለው ቆስሎ ነበር።

"ስነስርዓት ባለው መንገድ እንደአዋቂዎች እናውራ?" አልኩት።ማንም ደንበኛ በዚህ መጠን ነፃነት እንዳወራኝ አላስታውስም።

"እኔ የምለው ማሂ?" አለ ኮስተር እንዳለ

" ዶክተር ማህደር" መለስኩለት

"ኡፍ! ከክብርና ከፍቅር የቱ ይበልጥ ይመስልሻል?"

"ሁለቱም ዋጋ ያላቸው የማይነፃፀሩ ነገሮች ናቸው።"

" ዶክተር ብልሽ ያከበርኩሽ ሊመስል ይችላል። ማሂ ስልሽ ግን ውዴታዬን እየነገርኩሽ ነው። ከክብር ሁሌም ፍቅር ይበልጣል። በክብር ውስጥ ፍቅር ላይኖር ይችላል። በፍቅር ውስጥ ግን ሁሌም ክብር አለ" የሆነ ነገሬን ያወቀ ስለመሰለኝ ተናደድኩ። ለተናገረው ትኩረት የሰጠሁ ባለመምሰል

"ጨርሻለሁ። ተጨማሪ አንድ መድሀኒት አዝልሃለሁ። በትክክል መድሀኒቱን ከወሰድክ በድጋሚ እዚህ መመላለስ አያስፈልግህም።" አልኩት

" OK አልጋ ልትሰጪኝ ማለት ነው? እሱ ጥሩ ሀሳብ ነው። "

"አቶ ሲሳይ ለጨዋታ ጊዜ የለኝም።"

" ሊኖርሽ ግን ይገባል ማሂ!። " መልስ ሳይጠብቅ የፃፍኩለትን ወረቀት ተቀብሎኝ ወጣ።

…………አልጨረስንም…………………

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
★★ ስንቴ ገረዝኩት #2 ★★
(ሜሪ ፈለቀ)

"ዶክተር? ያው ሰውዬ ነው የላከልሽ………" ሲስተር ቀለም በፈገግታ በደመቀ ፊት ጠረጴዛዬ ላይ በፎይል የተጠቀለለውን ምሳ አስቀምጣው ወደ በሩ ተመለሰች

"ሲስተር ከዛሬ በኋላ የሚያመጣውን ምሳ እንዳትቀበሉት።" አልኳት

ለሁለተኛ ጊዜ ታክሞ ከሄደ ጀምሮ ሶስት ቀኑ ነው። የምሳ ሰዓት እየጠበቀ ምሳ ይልካል። ጠዋት ፅዳቶቹ አፅድተው ሲጨርሱ አበባ ይልካል።

"አበባውንም ነው ዶክተር?"

"አዎን። ምንም ነገር!!"

"እሺ!!" ብላኝ ወጣች

ሲስተር ለምንድነው የምትሽቆጠቆጥልኝ? ስለምታከብረኝ? ደሞዝዋን ስለምከፍላት? አለቃዋ ስለሆንኩ? እንጂ አትወደኝም…………… ትጠላኝም ይሆናል። ይሄ የተረገመ ሰው ምን እንዳስብ እያደረገኝ ነው?


★ ★ ★

ሆዴ ምግብ አስፈልጎታል። ሆስፒታሉ አቅራቢያ ያለ ሬስቶራንት እራቴን ለመብላት አዝዤ ተቀምጫለሁ። ከየት መጣ ሳልል ከፊቴ ያለውን ወንበር ስቦ ተቀመጠ።

"ማሂ……ዬ……… ?" አለ በተሟዘዘ አጠራር

"አንተ ሰው ለምን አትተወኝም?"

"አቶ ሲሳይ ታፈሰ። ማዕረግ ያለኝ ሰው ነኝ እሺ።"

"Whatever አቶ ሲሳይ ምን እያሰብክ እንደሆነ አልገባኝም። እኔና አንተ ግን ምንም መሆን የምንችል ሰዎች አይደለንም።"

"ምክንያት? በእድሜ ስለምትበልጪኝ?"

"አቤት? "

"በ18 ዓመትሽ ዩንቨርስቲ ብትገቢ፣ 7 ዓመት ዶክተር ለመባል ብትማሪ……"

"ዶክተር ለመሆን " አቋረጥኩት

"ስፔሻሊስት ለመባል የሆነ ዓመት… …… ይሄን ሆስፒታል ከከፈትሽ 6 ዓመት… …… በስሱ 37 የግልሽ ነው። "

እንዲያውቅብኝ ባልፈልግም ተናድጃለሁ። ለምን ተናደድኩ? ትክክለኛ እድሜዬን ስለነገረኝ። እና ምን አናደደኝ? ምክንያት እንኳን የለኝም።

"ቁስልህ ዳነልህ?" ወሬውን መቀየር ነው ፍላጎቴ

"እየደረቀ ነው። ላሳይሽ?" ከመቀመጫው ብድግ አለ

"ኸረ አንተ ሰው?" ለመቀመጥም ለመነሳትም በቀረበ አኳኋን አየሩ ላይ ተንሳፈፍኩ

"አየር ላይ ነሽ! አረፍ ትዪ……" ብሎኝ ተመልሶ ተቀመጠ

ያዘዝኩት ምግብ መጣ። ተነስቶ እጁን ታጥቦ እስኪመጣ ጠብቂኝ ባይለኝም ጠበቅኩት። የጠቀለለውን ሊያጎርሰኝ ዘረጋ
"ጉርሻ አልወድም።" አልኩት

"እንዴ? በሞቴ? በፍቅራችን?" ሆነ ብሎ ሬስቶራንት ውስጥ ያለው ሰው እንዲሰማ ጮክ ብሎ ነው የሚናገረው። ሰዎች እየዞሩ ያዩናል። ግማሾቹም ፈገግ እንደማለት ይላሉ። ጎረስኩለት።

"ማሂዬ ለክብርሽ ይሄን ያህል አትጨነቂ። ……" አለ የተናገረው ተራ ነገር እንደሆነ ሁሉ ለሌላ ጉርሻ እየተሰናዳ። ተበሳጭቻለሁ። ይበልጥ ያበሳጨኝ ደግሞ ያለው እውነት መሆኑ ነው።

"ክብር አንጃ ግራንጃህን ተወኝ። ባለትዳር ነኝ ለባለቤቴ …………"

ሳቁ አቋረጠኝ። አስቂኝ ተረት እንደነገሩት ህፃን ተንፈቀፈቀ::

"ምን ያስቅሃል?"

"ባለቤትሽ ነዋ ያሳቀኝ ሃሃሃሃ "

"ምን ለማለት ፈልገህ ነው?"

" እንዳንቺ አይነት ሴቶች ወይ አላገቡም፣ ወይ አግብተው ፈተዋል፣ ወይ ከባላቸው ጋር ሰላም አይደሉም።"

"እኔ ምን ዓይነት ሴት ነኝ?"

"ካልኳቸው ምድብ ውስጥ ከሌለሽ ልቀጣ? እ?" መልሴን ጠበቀ

መልስ አልነበረኝም። ተነስቼ ጥዬው መሄድ ነበር ፍላጎቴ እግሮቼን ማዘዝ አቃተኝ። ሽንፈቴን መቀበልም መሰለኝ። ልከራከረውም አቅሙ አልነበረኝም።

"እኔ ምን አይነት ሴት ነኝ? " ድምፄ የቅድሙ ጥንካሬ የለው

"እውቀትና ደረጃዋን ድክመትና ሽንፈቷን ለመሸፈን የምትጠቀም ዓይነት ሴት"

ከዚህ በላይ መስማት የሚያሳምመኝ መሰለኝ። ተነስቼ ስወጣ ድምፁ ተከትሎኛል።

"አየሽ አንቺ ይህቺ ነሽ። ትፈረጥጫለሽ።"

እኔ ምን አይነት ሴት ነኝ? የትኛውን ሽንፈቴን ነው በደረጃዬ የሸፈንኩት?
★ ★ ★

ወትሮም ለእንቅልፍ እምብዛም የሆነው ዓይኔ ጭራሽ አልከደን አለ። እቤቴን ጠላሁት። ልብሴን ለመቀየር ካልሆነ በቀር አዳሬም ሆስፒታል ከሆነ ሰነባበትኩ። ምግቤንም የምመገበው እዛው እያስመጣሁ ሆነ። ከዛ ቀን በኋላ ሲሳይን አላገኘሁትም። ከዛ ቀን በኋላ ግን ስላወራናቸው ነገሮች አለማሰብ አቃተኝ። ሁኔታዬን ይብስ ያባባሰው ደግሞ ከቀናት በፊት የገጠመኝ ነገር ነው። ዶክተር ሰይፈ!!! በግምት የ12 አመት ልጅ የምትሆን ህፃን በዊልቸር እየገፋ ሲያልፍ ነበር ያየሁት። ደሜ ሰውነቴ ውስጥ ሲቀዘቅዝ ታውቆኝ ነበር።

«ሲስተር? ዶክተር ሰይፈ ልጅ አለው እንዴ? » ቢሮ እንደገባሁ ጠየቅኳት። ጥያቄዬ ይሁን ሰይፈ የትኛው መሆኑ ግራ ያጋባት አልገባኝም። « ዶክተር ሰይፈ የህፃናት...............»

«እኮ ገብቶኛል። መጠየቅሽ ገርሞኝ ነው። አዎን ሁለት ሴት ልጆች አሉት። አንዷ ልጁ የመኪና አደጋ ደርሶባት she is totally paralyzed እሱ ነው የሚንከባከባት። አይኗም የማየት አቅሙ እየተዳከመ ነው።» አነጋገሯ ውስጥ ያለው ድምፀት ያሳምማል። አንቺ ምን ግድ አለሽ አይነት ነው።

« ሚስቱስ?»

«ህምምም....... ሚስቱ እኮ ሞታለች ዶክተር!»

« ለምን አልነገራችሁኝም? እንዴት አንድ ሰው አይነግረኝም?» ፀፀቴን ማራገፊያ አጥቼ እንጂ እሷ ላይ የምጮህበት ምክንያትም መብትም የለኝም።

« ምን ብለን? ዶክተር አንቺ ልብ ስለማትዪ እንጂ እኮ ለህክምና እዚህ ትመላለሳለች።» ብላኝ በመገረም እያየችኝ ወጣች።

ኡፍፍፍፍፍፍፍ በየሱስ ስም ምንድነው የሰራሁት? ዶክተር ሰይፈ በሙያው ማንም እንከን የማያወጣለት ጎበዝ ነው። በተደጋጋሚ እያረፈደ እና እየቀረ ስላስቸገረ ቦርዱን ሰብስቤ ከስራው እንዲባረር ያደረግኩት ቀን ያሳየኝን ፊት ትርጉም የምረዳው አሁን ነው። ምክንያቱን እንኳን ሊነግረኝ የደከመው ነበር የሚመስለው። እሺ ብቻ ነበር ያለኝ። ከቦርድ አባላቱ አንዱ ምክንያቱን እንድሰማው ጠይቆኝ ነበር።

«ተውት ምክንያቴን ለእናንተ እያስረዳሁ ህመሜን አላበዛም። ለእስከዛሬው ቆይታችን አመሰግናለሁ!» ያለው በሰአቱ ምን ያለ መስሎኝ ነው ከምንም ያልቆጠርኩት? እንዴት ግን አንዳቸው እንኳን ልጁን እያስታመመ ነው አይሉኝም? ይሄን ያህል ድንጋይ ልብ ያለኝ ነው የምመስላቸው? ይጠሉኛል ማለት ነው አይደል?

ማሰብ ይደክማል እንዴ? ማሰብ ደከመኝ:: ስልኬ መልዕክት መቀበሉን ነገረኝ። ከፈትኩት። የማላውቀው ቁጥር ነው።
"ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ አይነኬ የህይወት ክፍል አለው። ያን ሽሽት የሆነ ነገር ውስጥ ይደበቃል። ሌት ተቀን ህሙማንን ማገልገልሽ ለብዙዎች ታታሪነትሽን ይነግራቸዋል። ስራሽ መደበቂያሽ መሆኑን ግን አሳምረሽ ታውቂዋለሽ።"
ከሱ ውጪ ማንም አይሆንም። ቁጥሩን ደወልኩበት። ይሄ ደግሞ ሊያሳብደኝ ነው እንዴ ሀሳቡ?
"ምንድነው ከኔ የምትፈልገው? ምንድነው ግን ችግርህ?"

"ደህና እግዜአብሄር ይመስገን!! ምሳ እንኳን አይመቸኝም። እራት ቢሆንልኝ እመርጣለሁ።" አለኝ ዘና ብሎ።

ምን ልለው ነበር የደወልኩት? ቁጣዬን ምላሴ ላይ ምን ያልከሰክሰዋል?
"እራት ልጋብዝሽ?" አለኝ ዝምታዬን ተከትሎ። ምን እንደምመልስለት ግራ ገባኝ።

"ማሂ ፕሊስ?……… እኔ ደስ ብቻ ነው የሚለኝ። ዶክተር ማህደር እራት ተጋበዘችልኝ ብዬ ቀላል ሴት የሆንሽ አይመስለኝም።" የማስበውን እኔ ከስቤ ሳልጨርሰው ከሱ አፍ እሰማዋለሁ።
"የባለፈው ሬስቶራንት 12 ሰዓት ላይ ላግኝሽ! ውብ ቀን ዋዩ!!" ብሎኝ እንቢም እሺም ሳልለው ስልኩን ዘጋው።

## አሁንም አልጨረስንም##

@wegoch
@wegoch
@paappii
ዝምምምም.........


"ህመሙን የሸሸገ መዳህኒት አይገኝለትም" ትለኛለች አንድ እንደኔ ያልደረሰባትና ያልታመመች እህቴ። አንዳንዴ ይገርመኛል እንዴት ነው በሽታውን ላሸከመኝ ሰው በሽታዬን የምነግረው። በእርግጥ መዳኒቱን ከሷ ውጪ አላገኘው ይሆናል ነገር ግን ይሁን ብዬ ብናገር ደግማ ሌላ በሽታ እንደማትጨምርብኝ ምን ማረጋገጫ አለኝ። እንደው ይህን ሁሉ ትቼ አንኳ ልንገራት ብል ድፍረት ከየት አባቱ ሊመጣ ነው።
ነገር ግን ደሞ ሌላ አማራጭ ያለኝ አይመስለኝም። እውነቱን ተናግሮ የመሸበት ማደር አይደል ሚባለው እኔ ግን እውነቱን ተናግሬ መልሱ ጥሩ ካልሆነ ቀድሞውኑም አይመሽም ከመሸም የማድርበት ያለኝ አይመስለኝም ፤ ልቤ ግን ለመናገር ወስኗል።
ችግሩ እንዴት ተብሎ በየትስ ተሂዶ እንደምነግራት ነው የጨነቀኝ። ሀሳብ ሀሳቤን እያሸነፈ አንድ መሬት የማዮድቅ ሀሳብ መጣልኝ።

"ደብዳቤ"
ደስ አለኝ ምክንያቱም ፊቷ ፊቴን አይገርፈውም፤ ፊት ለፊቴ ጥላኝ ስትሄድም አላይም፤ ሌላው ቢቀር መስማት የማልፈልገውን ምላሽ አጠገቧ ሆኜ እንደማልሰማ ሳስብ ልቤ እርፍ ይላል። ወዲያው ግን ምላሿ ምን ይሆን በሚል አስቀያሚ ጥዬቄ እጨናነቃለው።

ደብዳቤውን ለመፃፍ ስጀምር አጠገቤ ሆና አብራኝ ትፅፍ ይመስል የምፅፈው ይጠፋብኛል። ነገር ግን እንደምንም ሀሳቤን ሰብስቤ መፃፍ ስለነበረብኝ የሞት ሞቴን ጀመርኩት።ለአንድ ደብዳቤ አንድ ሰአት ፈጀብኝ። የፃፍኩት ግን ሦስት ቃል ብቻ ነበር።

"የውብዳር ከልቤ አፈቅርሻለው"

በቃ ጨረስኩ ፤ እጄን ወደ ግንባሬ ስደድሁ፤ ላብ ጠምቆኛል። የላቤ ብዛት ሦስት ቃል ሳይሆን ሦስት መፃፍ የፃፍኩ ነበር የሚመስለው።
ወዲያው ደብዳቤዬን ፖስታ ውስጥ ከትቼ ከቤት ወጣሁ።
ማንም ሰው እንዲያገኘኝ ስላልፈለኩ እርምጃዬ አፈጠንኩት። አንድ የሰፈር ሰው ቢያየኝ ለ'ናቴ ሄዶ "እኔምልሽ ምነው ልጅሽ ሶምሶማ ውድድር መጀመሩን ብትነግሪኝ " ብለው ማውራታቸው አይቀርም ነበር።ነገር ግን ተመስገን ማንም ሳያየኝ ኪዳነምህረት በር ላይ ደረስኩ። ሦስቴ ተሳልሜ ከገባሁ ቡኃላ እሷም እኔም ወደምናውቃት ቦታ ገሰገስኩ። ቦታው ላይ ስደርስ እሷ እንዳለች ያህል ይሰማኝ ጀመር። ቁጭ ብዬ ግራ ቀኜን እማትር ጀመር። ቤ/ክኑ ጭር ብሏል ነገር ግን አንድ ቦታ ተደብቃ ምታየኝ እየመሰለኝ እጄ ድመት እንደገደለ ይንቀጠቀጥብኛል። ፊት ለፊቴ ያለውን ድንጋይ አነሳውና ደብዳቤውን ላስቀምጠው እጄን ወደኪሴ ስልክ ነገር አለሙ ጨለመብኝ።

ከሰአታት ቡኃላ ስነቃ በዘመድ ተከብቤ እራሴን ሆስፒታል አገኘውት። "የደብዳቤ ያለህ ኡኡኡኡኡ" ብዬ መጮህ አማረኝ ነገር ግን በዘመድ ፊት ፍቅር ይዞት ነው የወደቀው መባልን ፈራው።

ዝምምምም......አልሁ

የጌትነት ልጅ ፃፈ

@wegoch
@wegoch
@paappii
★★ ስንቴ ገረዝኩት #3 ★★
(ሜሪ ፈለቀ)

"እኔ ምን አይነት ሴት ነኝ? " ድምፄ የቅድሙ ጥንካሬ የለውም "እውቀትና ደረጃዋን ድክመትና ሽንፈቷን ለመሸፈን የምትጠቀም ዓይነት ሴት" ከዚህ በላይ መስማት የሚያሳምመኝ መሰለኝ። ተነስቼ ስወጣ ድምፁ ተከትሎኛል። "አየሽ አንቺ ይህቺ ነሽ። ትፈረጥጫለሽ።"

★ ★ ★
ወትሮም ለእንቅልፍ እምብዛም የሆነው ዓይኔ ጭራሽ አልከደን አለ። እቤቴን ጠላሁት። ልብሴን ለመቀየር ካልሆነ በቀር አዳሬም ሆስፒታል ከሆነ ሰነባበትኩ። ምግቤንም የምመገበው እዛው እያስመጣሁ ሆነ። ከዛ ቀን በኋላ ሲሳይን አላገኘሁትም። ከዛ ቀን በኋላ ግን ስላወራናቸው ነገሮች አለማሰብ አቃተኝ። "እኔ ምን አይነት ሴት ነኝ?"
"የትኛውን ሽንፈቴን ነው በደረጃዬ የሸፈንኩት?" ማሰብ ይደክማል እንዴ? ማሰብ ደከመኝ:: ስልኬ መልዕክት መቀበሉን ነገረኝ። ከፈትኩት። የማላውቀው ቁጥር ነው። "ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ አይነኬ የህይወት ክፍል አለው። ያን ሽሽት የሆነ ነገር ውስጥ ይደበቃል። ሌት ተቀን ህሙማንን ማገልገልሽ ለብዙዎች ታታሪነትሽን ይነግራቸዋል። ስራሽ መደበቂያሽ መሆኑን ግን አሳምረሽ ታውቂዋለሽ።"
ከሱ ውጪ ማንም አይሆንም። ቁጥሩን ደወልኩበት። "ምንድነው ከኔ የምትፈልገው?" "ደህና እግዜአብሄር ይመስገን!! ምሳ እንኳን አይመቸኝም። እራት ቢሆንልኝ እመርጣለሁ።" አለኝ ዘና ብሎ። ምን ልለው ነበር የደወልኩት?
"እራት ልጋብዝሽ?" አለኝ ዝምታዬን ተከትሎ። ምን እንደምመልስለት ግራ ገባኝ። "ማሂ ፕሊስ?……… እኔ ደስ ብቻ ነው የሚለኝ። ዶክተር ማህደር እራት ተጋበዘችልኝ ብዬ ቀላል ሴት የሆንሽ አይመስለኝም።" የማስበውን እኔ ከስቤ ሳልጨርሰው ከሱ አፍ እሰማዋለሁ። "የባለፈው ሬስቶራንት 12 ሰዓት ላይ ላግኝሽ! ውብ ቀን ዋዩ!!" ብሎኝ እንቢም እሺም ሳልለው ስልኩን ዘጋው።

★ ★ ★
እግሬና ሀሳቤ ሳይስማሙ እግሬ ቀድሞ ሬስቶራንቱ ውስጥ ተገኘ። ሲሳይ ቀድሞኝ ተገኝቷል። ልጨብጠው የዘረጋሁትን እጄን ሳብ አድርጎ አቀፈኝ። ፀጉሬን እንደመሳም አደረገና የምቀመጥበትን ወንበር ሳበልኝ። እራትና ወይን አዘዝን።
አፉ ከማውራት እጁ ከማጉረስ ሳይቦዝን እራት ተመግበን አለቀ። "እኔ ከዚህ በላይ አልጠጣም። ስራ መመለስ አለብኝ።" ያልኩትን የሰማ አይመስልም። ቀዳልኝ። በአትኩሮት ሲመለከተኝ ከቆየ በኋላ "ሴክስ ካደረግሽ ስንት ጊዜሽ ነው? ወራት? አመታት?" አለ ቀለል አድርጎ
"አንተ? ያምሃል እንዴ? " አልኩት ደንግጬ ይሁን አፍሬ ሳይገባኝ "ምነው? አንቺ? ጭራሽ… …… እ? ነው እንዴ?" በማብሸቅ ለዛ ነው ያወራው። ደሞ አብሽቆኛልም። "አንተ እኔን ለማንጓጠጥ የሚያስችለህ ቦታ ላይ እንዳለህ ነው የሚሰማህ?" ሳልጨርስ መንፈቅፈቁን ያዘው " ማሂ ከእኔ ጋር ስታወሪ ጨዋ ቃል አትፈልጊ…… ሃሃሃሃ ‘ትናንት እጄ ላይ ሸለፈትህን ተገርዘህ፣ ልጅህን በማስገረዣ እድሜህ አንዠርግገኸው………‘
በይው " "እንደሱ ለማለት እንኳን አልነበረም።" መለስኩለት "በጨዋኛ ስለሴክስ ምን ታውቅና? እንደማለት አይደል?" "አዎን!" አልኩት "ያልተገረዘ ሴክስ አያደርግም ያለሽ ማነው?" አባባሉ ቀዝቃዛ ስሜት ስለነበረው ስሜቱን የጎዳሁት ስለመሰለኝ ወንዶች ስለማይገረዙባቸው ሀገራት፣ ገጥመውኝ ስለሚያውቁ አጋጣሚዎች ነገርኩት። "ኮንዶም የለ፣ ምን የለ… … ሸብ አድርጎ መሰማራት ነው። ሃሃሃ" ብልግና ያወራ፣ በራሱ ያላገጠ አይመስልም። ደንግጬ ፈጥጬ አየዋለሁ። "ኸረ ስቀልድሽ ነው አንቺ!!" አለ መሳቁን ሳያቆም። በህይወቱ ውስጥ የሚያስከፋው፣ የሚያፍርበት፣ ሊያወራው የማይፈልገው ነገሩ ምን ይሆን? ብዬ አሰብኩ። ሲያወራ ፍፁም ጨዋ፣ ደግሞ ፍፁም ባለጌ፣ ደግሞ ፍፁም አዋቂ፣ ደግሞ ፍፁም ህፃን………ሁሉንም ይሆናል። ሲሳይን ማወቅ ከበደኝ። ያልተገረዘው ቤተሰባቸው ወንድ ልጅ እየሞተ ሲያስቸግራቸው የሄዱበት
ጠንቋይ እንዳይገረዝ ስለነገራቸው መሆኑን እንደለመደው በራሱና በቤተሰቡ
እየቀለደ ነገረኝ። "እያደግኩ ከመጣሁ በኋላ መገረዙ አሳፈረኝ እና አረጀሁ። ""ያፈርክበት ግን አትመስልም ነበር።"
"አንቺጋ ስመጣማ ከማፈር አልፎ አስጠልቶኝ ነበር።" ሲያወራ በራስ መተማመኑ ለሰከንድ አይለየውም። ደጋግሞ ከሚያወራቸው ነገሮች በወላጆቹና በ6 እህቶቹ የተለየ ፍቅር ተሰጥቶት እንደኖረ ገባኝ። ከብዙ
ሰው ጋር መግባባቱ፣ ብዙ ጓደኞች ማፍራቱ ምናልባትም ከተማረው የሳይኮሎጂ ትምህርቱጋ ግንኙነት ይኖረው ይሆናል ስል አሰብኩ።
"ጓደኞች የሉሽም? የሆነ አብረሻቸው አንዳንዴ ዘና የምትዪበት ምናምን?"
"የሉኝም!!" "እሺ ሲደብርሽ፣ ሲከፋሽ፣ ደስ ሲልሽ ወይ የተለየ ነገር ሲገጥምሽ ለማን
ታወሪያለሽ?" አለኝ አይኖቹ የሚያነቡኝ ስለሚመስሉኝ እሸሻቸዋለሁ "ለራሴ አወራዋለሁ።" አልኩት አይኑን ሳይሰብር አየኝ። "አንተስ?" አልኩት "ያ ስሜት በተሰማኝ ሰዓት አጠገቤ ላገኘሁት ሰው። ለምሳሌ በኋላ ሸኝቼሽ ስመለስ ለሆስፒታላችሁ ዘበኛ ደስ እንዳለኝ ልነግረው እችላለሁ።" ቀለል አድርጎ
ነው የሚያወራው "እየቀለድክ ነው?"
"የምሬን ነው። ምነው?" "የምልህ ከእኩዮችህ፣ ቢያንስ ከቤተሰብህ……… ባንተ ደረጃ ካሉ ሰዎች ጋር……… " አላስጨረሰኝም።

"ደረጃ ምንድነው? ደረጃ መዳቢውስ ማነው? እኔን ከኒኛ ዘበኛ ወይ ከዚህ አስተናጋጅ በላይ ወይ በታች ደረጃ የሰጠን ማን ነው? የኔ መማር እና ቢሮ
መቀመጥ? የሳቸው የእኔን እድል አለማግኘትና ዘበኛ መሆን? ንገሪኝ እስኪ
እሳቸው የሚያውቁትን ወይ የሚችሉትን ደረጃ ብለን ባወጣንላቸው ዘበኝነት እንዴት እንመዝነዋለን?" አይቼበት የማላውቅበትን ፈገግታ ፈገግ ብሎ ቀጠለ "አፈር ምን ደረጃ አለው? ነፍስስ ብትሆን ያው ነፍስ አይደለች? በምትሰራው ስራ ካልዳኘናት በቀር? የሰው ደረጃው ‘ሰውነቱ‘ ነው።" አለኝ። ዝም አልኩት። ምንስ ልለው እችል ነበር?
"ቤተሰቦችሽ? የት ናቸው?" አለኝ ወዲያው ከዛኛው ስሜት ወጥቶ "ቤተሰቦቼ………?…… "
"ምነው? ሞተዋል? ተጣልታችኋል? ወይስ…… እንደ እህል ዘርተውሽ ነው
የበቀቀልሽው?…" ተናድጄ አቋረጥኩት ቁስሌን እያወራ እንደሆነ አልገባውም።
"ምንም ስነስርዓት አታውቅም። ባለጌ ነህ እሺ!!" አልኩት "እሺ!" አለኝ ቁጣዬን ከምንም ሳይቆጥረው እጄን እየዳበሰ።
"እሺ ግን ንገሪኝ። ማወቅ እፈልጋለሁ።
ምኑን ልንገረው? አባቴ ከእህቱ ልጅ እንደወለደኝ እና ወንድ አያቴ እንዳሳደጉኝ? ቤተሰቡ ውስጥ እንደ አንዳች መዓት ሲፀየፉኝ እንደኖርኩ? አያቴ ሲሞት ያየሁትን አስቀያሚ የህይወት ገፅታ? የቱን ልንገረው? ለማንም አውርቼው አላውቅም። እንባዬ መጣ። እያየኝ ማልቀስ አልፈለግኩም። ፈርጣጭ ይበለኝ። ተነስቼ መውጣት እንደጀመርኩ እንባዬን ማስቆም አቃተኝ።
ሬስቶራንቱን መግቢያ እንዳለፍኩ እሮጦ ደረሰብኝ። አቀፈኝ። እንደህፃን ደረቱ ላይ
አጥብቆ አቀፈኝ። አለቀስኩ። አላባበለኝም። ፀጉሬን እየደባበሰና እየሳመ ለቅሶዬን እስክተው ጠበቀኝ። ያስለቀሰኝ ምን እንደነበረም አልጠየቀኝም። እያሳቀኝ የሆስፒታሉ መግቢያ ድረስ ሸኘኝ። ሲሰናበተኝ መልሶ አቀፈኝ። እቅፉ ውስጥ ብዙ መኖር ፈለግኩ። ከሆነ ነገር የሸሸገኝ መሰለኝ። ሰላም ያለበት ዓይነት። እሱም የገባው ይመስል አቅፎኝ ለደቂቃዎች ቆየ። ግንባሬን ሳመኝ።

★ ★ ★
ፈገግ እያልኩ መሆኔ ለራሴ ይታወቀኛል። ታካሚዎቼን እየፈገግኩ እንደማዋራቸው ገብቶኛል። ማታ ከሲሳይ ጋር ከተለያየን ጀምሮ እንደዚያ እየሆንኩ ነው። ሲስተር ቀለም በተረኛ ታካሚ ፈንታ ገባች "ዶክተር ሰው ይፈልግሻል?" "ሲሳይ ነው? ትንሽ ታገሰኝ በይውና ተረኛ ታካሚ አስገቢልኝ።" "ዶክተር ……… ባለቤትሽ ነው።
" "ባለቤትሽ? ኢሳያስ?…………"

አሁንም በድጋሚ አልጨረስንም

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
((Maggie))

"ሁሌ ማስበው ስላንተ ነው.... ስላንተ ብቻ! ልክ ትኩስ አፍቃሪ ፍቅረኛውን በየሰከንዱ ስንጥርጣሪ እንደሚያስብ.... ነፍሰጡር ሴት ስለልጇ ቀኑን እያሰበች፤ ለሊቱንም እያለመች እንደምታነጋ...

ለ ሰከንድ ፍልጥላጭ ሳላስብህ ባሳልፍ " ለምን አላሰብሽውም? በሱ ዙሪያ የፀለይሽውን ፀሎት ውድቅ እንዳደርገው ይፈልጊያለሽ?" ፈጣሪ የሚለኝ እስኪመስለኝ ድረስ አንተን በሙሉ ግዜዬ ሳላሳል ስ ሳላስልፍ አስብሀለው

አይኔን ስከድን ምስልህ በድብዛዛ ቀለም ይከሰትልኛል... አይኔን ስገልጥ ያ ምስል ድምቅ ብሎ በብራው ሰማይ ላይ ይታተምብኛል.....
ከጭንቅላቴ ለሰከንድ ወጥተህ አታውቅም.... የብቻህ ግዛት አድርገኸዋል ...

አንተን ማሰቤ ሀሴት ሲፈጥርልኝ ፊቴ በጥርሴ ፀሀይ እንደጠዋት ጀምበር ሰማይላይ በ ስሱ እንደተቀባ የእግዜር ጥበብ በፈገግታ ብሩሽ በደማቁ ይቀባል... እንደገና አንተን ስለማሰቤ ሳስብ ደግሞ ሌላ ፍስሐ ይመጣና " አንች የፈገግታ ቅብ ሆይ! ይችን ጨምሪበትና ይባስ ድምቅምቅ በይበት" ብሎሻ እግዜር ብሎ የደስታ ቀለም ፊቴ ላይ ይርከፈከፋል..

ግንኮ አልነካውህም አላሸተትኩህም... በ ስ ልኬ መስታወት በኩል ብቻ ነው ምስልህን ያየውት! .. በመስታወቱ ውስጥ እንደሚጎበኝ ውድ እና ድንቅ የሙዝየም እቃ!

ከመስታወቱ ውስጥ በምትሀት ተጎትተህ ወጥተህ አጠገቤ ብትከሰት ብዬ አስባለው......... አጠገቤ ተቀምጠህ በእጄ ሳልነካህ (ቅር ሴ አይደለህ!) ብቻ ቁልጭ ቁልጭ እያልኩ ባየውህ ብዬ አልማለው...... በስልክ የሰማውት ድምፅህን በሉባንጃ ጢስ ታጅቦ ወፍራም አቦል ቡና በጀበናዋ ጉረሮ እንደሚንቆረቆረው በለስላሳ አየር ታጅቦ ያጎርናና ድምፅህ በጉረሮህ ኮለል እያለ በጆሮዬ ቢንቆረቆር ብዬ ብዙ ግዜ እግዜርን "በማርያም!" እያልኩ ለምኜዋለው...
መፅሀፍ ሳነብብ...... አፍቃሪው፣ ሸበላው ና እንዳንተ ድምፀጎርናና ገፀባህሪውን እንደ "አንተ" አመናጫቂዋ ፣ማጋጭዋ ፣እንዳንዴ እንደኔቢጤ ሳንቲም ወርወር የምትደረግ ፍቅር ብቻ የምታሳየው ገፀባህሪን ...ሰርዤ ....እኔን በቦታዋ ተካና በዛች የኔቢጤ ሳንቲም በምታክል የፍቅር ግዜያቸው ውስጥ የትዬለሌ ግዜ ዘረጋና በሰመመን የኔና ያንተን የፍቅር ገመድ ገምዳለው.....

እንዲ ባላደርግ ግን እንዴት ቀጥል ነበር? እግዜር ግን ጥበበኛ ነው! ለእንደኔ አይነት አፍቃሪዎች ይህንን ሀሳብ ህልም ምኞት ምናምንየተባሉትን ባይፈጥር ኖሮ እንዴት እንደምንሆን እንጃ!.."

@wegoch
@wegoch
@paappii
2024/09/23 21:27:17
Back to Top
HTML Embed Code: