Telegram Web Link
“ I WILL NEVER WALK ALONE “ የርገን ክሎፕ

በሊቨርፑል ቤት የመጨረሻ ጨዋታቸውን የመሩት አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ የመጨረሻ መልዕክታቸውን ለደጋፊዎች አስተላልፈዋል።

“ እኔ የእናንተ ነኝ “ በማለት ለክለቡ ያላቸውን ፍቅር የገለፁት ክሎፕ ደጋፊዎቹን “ የአለም ሁሉ ምርጦች ናችሁ “ ሲሉ አሞካሽተዋል።

“ ከክለቡ ጋር የመጨረሻዬ እንደሆነ አይሰማኝም “ ሲሉ “ I WILL NEVER WALK ALONE “ በማለት ለደጋፉዎች መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ በእንግሊዝ እግርኳስ ታሪክ ፅፈናል “

የማንችስተር ሲቲ የመሐል ሜዳ ተጫዋች ሮድሪ ስኬታቸውን “ ታሪክ ሰርተናል “ ሲል ገልፆታል።

“ ታሪክ ከመስራት ባለፈ አዲስ ምዕራፍ ፅፈናል “ ያለው ሮድሪ “ ለተከታታይ አራት ዓመታት የሊጉን ዋንጫ ማሸነፍ ቀላል አይደለም “ ብሏል።

ሮድሪ በመጨረሻም “ ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መጥቼ ብዙ ነገሮችን አሳክቻለው “ ሲል ከታሪካዊው ድል በኋላ ተደምጧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" አሁን ቀጣዩን ዋንጫ ማሸነፍ እንፈልጋለን " ሀላንድ

የፕርሚየር ሊጉን የወርቅ ጫማ ለሁለተኛ ተከታታይ አመት ማሸነፍ የቻለው ኤርሊንግ ሀላንድ በቡድኑ መኩራቱን ገልጿል።

" በክለቡ ኮርቻለሁ አስደሳች ድል ነበር ሁሉም ተጨዋቾች ክብር ይገባቸዋል የዘንድሮው ዋንጫ ለአራተኛ ተከታታይ አመት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል " ሲል ኤርሊንግ ሀላንድ ተናግሯል።

ኤርሊንግ ሀላንድ ቀጥሎም አሁን ቡድናቸው ቀጣዩን የውድድር አመት ዋንጫ ማሸነፍ እንደሚፈልግ ገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#laliga 🇪🇸

በስፔን ላሊጋ የሰላሳ ሰባተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ባርሴሎና ራዮ ቫዬካኖን 3ለ0 ሲያሸንፍ ሪያል ማድሪድ ከቪያሪያል 4ለ4 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል።

የባርሴሎናን የማሸነፊያ ግቦች ፔድሪ 2x እና ሮበርት ሊዋንዶውስኪ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።

ለሪያል ማድሪድ ግቦችን አርዳ ጉለር 2x ፣ ሆሴሉ እና ሉካስ ቫስኩዌስ አስቆጥረዋል።

የቪያሪያልን አራት የአቻነት ግቦች አሌክሳንደር ሶርሎት 4x ከመረብ ማሳረፍ ችሏሰ።

በሌላ ጨዋታ አትሌቲኮ ማድሪድ በኦሳሱና 4ለ1 በሆነ ውጤት ተሸንፈዋል።

ባርሴሎና ማሸነፉን ተከትሎ በሊጉ ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁን አረጋግጧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ፔፕ ጋርዲዮላ በሲቲ እንደሚቀጥሉ ገለጹ ! ስፔናዊው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በሚቀጥለው የውድድር ዘመን በማንችስተር ሲቲ አሰልጣኝነታቸው እንደሚቀጥሉ በሰጡት አስተያየት ገልፀዋል። በማንችስተር ሲቲ ቤት እስከ 2025 የሚያቆይ ኮንትራት ያላቸው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ " ውሌ እስከሚጠናቀቅ እዚህ አለሁ " ብለዋል። እኔ እዚህ እስካለሁ ሌሎች ክለቦች ሊጉን ለማሸነፍ ይቸገራሉ የሚል እምነት የለኝም ያሉት…
ፔፕ ጋርዲዮላ ሲቲን ሊለቁ እንደሚችሉ ገለጹ !

ስፔናዊው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በሚቀጥለው የውድድር አመት መጨረሻ ከማንችስተር ሲቲ ጋር ሊለያዩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።

" ማንችስተር ሲቲን ለመልቀቅ ተቃርቢያለሁ " ያሉት አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በሚቀጥለው አመት እዚሁ ለመቆየት አስቢያለሁ ከዛ በኋላ ለመልቀቅ የምቃረብ ይሆናል በማለት ተናግረዋል።

በሚቀጥለው የውድድር አመት መጨረሻ ውላቸው የሚጠናቀቀው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ከክለቡ ጋር በቀጣይ ለመነጋገር ማሰባቸውንም ጠቁመዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from HEY Online Market
•MacBook Air, M1
•MacBook Pro, M1

•MacBook Air, M2
•MacBook Pro, M2

•MacBook, M1 Pro
•MacBook, M2 Pro

•MacBook, M1 Max
•MacBook, M2 Max

Contact Us
0953964175 @heymobile
@heyonlinemarket
ሽመልስ በቀለ 1⃣8⃣ ገስት ሀውስ

በውቢቷ ሀዋሳ ቆይታዎ የት ለማረፍ አስበዋል ? ንፁህ እና በደንበኞቻችን ተወዳጅ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን መጥተው የእረፍት ጊዜውን ያሳልፉ።

እንግዶቻችንን ተቀበልን ለእይታ ሳቢ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን ማስተናገድ ከጀመርን አመታትን አስቆጥረናል።

አድራሻችን :- ሀዋሳ አርቴፍሻል ስታዲየም መንገድ ላይ ያገኙናል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለትዕዛዝዎ ይደውሉልን :- 0928684848

#ShemelesBekele18
የርገን ክሎፕ ይናፍቀኛል “ ፔፕ ጋርዲዮላ

የማንችስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ የመጨረሻ ጨዋታቸውን በሊጉ ለመሩት የርገን ክሎፕ ልዩ ቦታ እንዳላቸው ተናግረዋል።

“ የርገን ክሎፕ በጣም ይናፍቀኛል “ ያሉት ፔፕ ጋርዲዮላ “ በህይወቴ ውስጥ አስፈላጊው ሰው ነበር የመጨረሻ ጨዋታው ልዩ እንደነበረ ተስፋ አደርጋለሁ “ ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethsport @kidusyoftahe
የፈረንሳይ ሊግ ፍፃሜውን አገኘ !

የዘንድሮው የ2023/24 የውድድር አመት የፈረንሳይ ሊግ ትላንት ከተደረጉ የመጨረሻ ሳምንት መርሐ ግብሮች በኋላ ፍፃሜውን አግኝቷል።

ፒኤስጂ ለሶስት ተከታታይ አመታት ሊጉን በማሳካት ቀደም ብሎ ሊጉን በበላይነት ማጠናቀቁን ማረጋገጡ ይታወሳል።

ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ በሀያ ሰባት ግቦች የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ተጨዋች በመሆን አጠናቋል።

ኪሊያን ምባፔ ለስድስት ተከታታይ አመታት የፈረንሳይ ሊግ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ተጨዋች በመሆን ማጠናቀቅ ችሏል።

በሚቀጥለው የውድድር አመት ፒኤስጂ ፣ ሞናኮ ፣ ብረስት እና ሊል በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ውድድር ተሳታፊ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

እንዲሁም ኒስ በዩሮፓ ሊግ ኦሎምፒክ ሊዮን ደግሞ በኮንፈረንስ ሊግ ከፈረንሳይ ሊግ የሚሳተፉ ይሆናል።

ሎርየንት እና ክሌርመንት ፉት ከሊጉ በቀጥታ መውረዳቸው ሲረጋገጥ ሜትዝ በሊጉ ለመቆየት የማጣሪያ ጨዋታ ያደርጋል።

የሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ ከላይ በምስሉ ላይ ተያይዟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ቶተንሀም ወደ ደቡብ ኮርያ ያመራል !

የፕርሚየር ሊጉ ክለብ ቶተንሀም ለሚቀጥለው የ2024/25 የውድድር አመት ቅድመ ዝግጅት ለማድረግ ወደ ደቡብ ኮርያ እንደሚያመራ ይፋ ተደርጓል።

ቶተንሀም በደቡብ ኮርያ የቅድመ ውድድር ቆይታው ከጀርመኑ ክለብ ባየር ሙኒክ እንዲሁም ሌሎች ክለቦች ጋር የወዳጅነት ጨዋታዎች እንደሚያደርግ ተገልጿል።

በቀጣይ በዩሮፓ ሊግ የሚሳተፈው ቶተንሀም ከደቡብ ኮርያ በተጨማሪም ወደ ጃፓን በማምራት የቅድመ ውድድር ዝግጅቱን እንደሚያደርግ ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አስቶን ቪላ ከአዲዳስ ጋር ስምምነት ፈፀመ !

የፕርሚየር ሊጉ ክለብ አስቶን ቪላ ከሚቀጥለው የውድድር አመት ጀምሮ አዲዳስ ይፋዊ የክለቡ ትጥቅ አቅራቢ ተቋም በመሆን ከስምምነት መድረሳቸውን አስታውቀዋል።

የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ቦታን በማግኘት ድንቅ የውድድር አመት ያሳለፈው አስቶን ቪላ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የአዲዳስን የመጫወቻ እና ልምምድ ማልያ እንደሚለብስ ተገልጿል።

ክለቡ ከእውቁ የስፖርት ትጥቅ አቅራቢ ብራንድ አዲዳስ ጋር ለበርካታ አመታት የሚቆይ የውል ስምምነት መፈፀሙን አሳውቋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" የምንሄደው ኤፌ ካፑን ለማሸነፍ ነው " ኦናና

የማንችስተር ዩናይትዱ ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናና ቡድናቸው ቀጣይ ሳምንት ከማንችስተር ሲቲ ጋር የሚያደርገውን የኤፌ ካፕ ፍፃሜ ጨዋታ ለማሸነፍ ወደ ሜዳ እንደሚገባ ገልጿል።

የኤፌ ካፕ ዋንጫው ጥሩ አመት ላላሳለፉት ቀያዮቹ ሴጣኖች አስፈላጊ መሆኑን ያነሳው አንድሬ ኦናና " እኛ ማንችስተር ዩናይትዶች ነን ወደ ፍፃሜው የምናመራው ለማሸነፍ ነው " ሲል ተደምጧል።

የእንግሊዝ ኤፌ ካፕ ፍፃሜ ጨዋታ የፊታችን ቅዳሜ 11:00 ሰዓት በዌምብሌይ ስታዲየም በማንችስተር ዩናይትድ እና ማንችስተር ሲቲ መካከል ይደረጋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
Bologna - Juventus
Salernitana - Verona
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
#Tecno #Camon30Pro5G

ቪድዮዎች  እና ምስሎችን በከፍተኛ ጥራት ማንሳት እንዲያስችል Sony Imx890 የካሜራ ሴንሰርን የተገጠመለት አዲሱ Tecno Camon Pro 5G ምርጫዎ ያድርጉ

#Camon30Et #Camon30pro5GEt  #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt
ክሮሽያ ስብስቧን አሳውቃለች !

የክሮሽያ ብሔራዊ ቡድን በቀጣይ ጀርመን በምታዘጋጀው የ2024 አውሮፓ ዋንጫ ውድድር የሚጠቀመውን ስብስብ ይፋ አድርጓል።

የ 38ዓመቱ የሪያል ማድሪድ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሉካ ሞድሪች ለብሔራዊ ቡድኑ ጥሪ ቀርቦለታል።

ሉካ ሞድሪች በእግርኳስ ህይወቱ አምስተኛ የአውሮፓ ዋንጫ ውድድሩን የሚያደርግ ይሆናል።

ሙሉ ስብስቡ ከላይ በምስሉ ላይ ተያይዟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ኮማን ጉዳት እንዳጋጠመው ተገለጸ !

ፈረንሳዊው የባየር ሙኒክ የፊት መስመር ተጨዋች ኪንግስሌይ ኮማን በድጋሜ ጉዳት እንዳጋጠመው ተገልጿል።

ተጨዋቹ በልምምድ ወቅት የጉልበት ጉዳት እንዳጋጠመው ሲገለፅ የጉዳት መጠኑ ምን ያህል እንደሆነ በይፋ የታወቀ ነገር የለም።

ኪንግስሌይ ኮማን ለቀጣዩ የአውሮፓ ዋንጫ ውድድር በፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ጥሪ ከቀረበላቸው የፊት መስመር ተጨዋቾች አንዱ መሆኑ ይታወቃል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ፖቼቲኖ እንደማይቀጥሉ ሰምቻለሁ " ፈርዲናንድ

የቀድሞ እንግሊዛዊ የማንችስተር ዩናይትድ የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ሪዮ ፈርዲናንድ አርጀንቲናዊው አሰልጣኝ ማውሪስዮ ፖቼቲኖ ከቼልሲ ጋር እንዳማይቀጥሉ መስማቱን ገልጿል።

ሪዮ ፈርዲናንድ ከውስጥ ሰምቼዋለሁ እንዳለው መረጃ ከሆነ አርጀንቲናዊው አሰልጣኝ ማውሪስዮ ፖቼቲኖ በሚቀጥለው አመት " በምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ቤት አይቀጥሉም " ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ባምላክ ተሰማ የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ይመራሉ !

ኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማ ከሀያ አንድ ቀናት በኋላ የሚደረግ የአፍሪካ አህጉር የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ጨዋታ እንዲመሩ በፊፋ ተመርጠዋል።

ባምላክ ተሰማ በምድብ ሶስት የሚገኙት የቤኒን እና ናይጄሪያ ብሔራዊ ቡድኖች የሚያደርጉትን የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ አራተኛ ጨዋታ በመሐል ዳኝነት እንደሚመሩ ታውቋል።

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ አራተኛ ጨዋታ ሰኞ ሰኔ 3/2016 ዓ.ም የሚደረግ ይሆናል።

በተጨማሪም አልጄሪያ ከጊኒ ጋር የምታደርገውን የአለም ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ሰስተኛ ጨዋታ ኢትዮጵያዊው ዳኛ ባምላክ ተሰማ ሊመሩ እንደሚችሉ እየተገለፀ ይገኛል።

አልጄሪያ ለጨዋታው የተመረጡ የጋቦን ዳኛ እንዲቀየሩ ፊፋን መጠየቋ ሲገለፅ ጨዋታውን ባምላክ ተሰማ በዋና ዳኝነት እንዲሁም ቴዎድሮስ ምትኩ በአራተኛ ዳኝነት እንደሚመሩ ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/10/05 13:13:43
Back to Top
HTML Embed Code: