Telegram Web Link
🥁 እነሆ አሸናፊ 🥁🥁

🌟 የዴሊ ጃክፖት የ 100,000ብር አሸናፊ::

🌟 ቤቲካ ዛሬም ውድ ደንበኞቹን ማንበሽበሹን ቀጥሏል!

🔥 እርስዎስ ምን ይጠብቃሉ?ቀንዎን ዳጎስ ባለ አሸናፊነት ከመጀመር የተሻለ ምን አለ?

👉🏾 አሁኑኑ የነገውን ያሸንፉ Betika.et !

ቤቲካ የአሸናፊዎች ቤት!
Forwarded from HEY Online Market
iPhone 16 Promax
iPhone 16 Pro
iPhone 16 Plus
iPhone 16
Available Now!

0925927457 @eBRO4
0953964175 @heymobile
@heyonlinemarket
#PremierLeague

የአምስተኛ ሳምንት የ እንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሐ ግብሮች ሲገባደዱ ማንችስተር ሲቲ የሊጉን መሪነት ተረክበዋል።

በውድድር አመቱ አራት ቡድኖች በሊጉ ያልተሸነፉ ሲሆን :-

- ማንችስተር ሲቲ
- አርሰናል
- ብራይተን እና
- ኖቲንግሀም ፎረስት በሊጉ ያልተሸነፉ ብቸኞቹ ክለቦች ናቸው።

በተቃራኒው :-

- ሌስተር ሲቲ
- ክሪስታል ፓላስ
- ኢፕስዊች ታውን
- ሳውዝሀምፕተን
- ኤቨርተን እና
- ዎልቭስ በሊጉ የአምስት ሳምንታት ጎዞ ሶስት ነጥብ ማግኘት ያልቻሉ ክለቦች ሆነዋል።

በወራጅ ቀጠናው ሳውዝሀምፕተን ፣ ኤቨርተን እና ዎልቭስ ይገኛሉ።

በቀጣይ የስድስተኛ ሳምንት መርሐ ግብርም :-

- ኒውካስትል ዩናይትድ ከ ማንችስተር ሲቲ

- ቼልሲ ከ ብራይተን እና

- ማንችስተር ዩናይትድ ከ ቶተንሀም የሚያደርጉት ጨዋታ ከተጠባቂ መርሐ ግብሮች መካከል ይገኙበታል።

@tikvahethsport @kidusyoftahe
አሸናፊዎች ተለይተዋል።

ትክክለኛ ምላሽ ቀድመው የሰጡት ከስር የተገለፁት የቤተሰባችን አባላት ናቸው።

ትክክለኛ ምላሽ የሰጡትን በመፈለጉ ሂደት የተዘለለ እና ያልታየ ካለ ማሳወቅ ይቻላል። Edit የተደረገ መልስ ተቀባይነት አይኖረውም።

ስጦታ የሚበረከትላቸው ቀድመው የመለሱ ሶስት አሸናፊዎች ብቻ ናቸው።

የማንችስተር ሲቲ እና አርሰናል ጨዋታ :-

1️⃣@The_endxyz
2️⃣ኛ Yonathan
3️⃣@LEAVETOALLAH

የባርሴሎና እና ቪያሪያል ጨዋታ :-

1️⃣@Gunne_rs
2️⃣ኛ Habtamu
3️⃣@Nalosmigad

የኢንተር ሚላን እና ኤሲ ሚላን ጨዋታ :-

1️⃣@Gd20ya
2️⃣ኛ Freedom Tesema
3️⃣@Abiiti

@tikvahethsport
“ በሜዳችን በደንብ እንጠብቃቸዋለን “ ጋብሬል

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የኋላ መስመር ተጨዋች ጋብሬል ማግሀሌስ ቡድናቸው ማንችስተር ሲቲን በሜዳው ሲገጥም ለማሸነፍ እንደሚጠብቅ ገልጿል።

በመጨረሻ ደቂቃ በተቆጠረ ግብ ነጥብ ከጣሉበት ከምሽት ጨዋታ በኋላ አስተያየቱን የሰጠው ጋብሬል ማግሀሌስ “ አሁን እነሱን በሜዳችን በጥሩ ሁኔታ እንጠብቃቸዋለን “ ሲል ተናግሯል።

ጋብሬል ማግሀሌስ አርሰናል ከተቀላቀለ ወዲህ ከየትኛውም የፕርሚየር ሊግ ተከላካይ በበለጠ 16 የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ግቦችን አስቆጥሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ የሊቨርፑል አምበል መሆን እፈልጋለሁ “ አርኖልድ

እንግሊዛዊው የመስመር ተጨዋች አሌክሳንደር አርኖልድ በቀጣይ የሊቨርፑል አምበል የመሆን ህልም እንዳለው በሰጠው አስተያየት ገልጿል።

“ የሊቨርፑል አምበል መሆን እፈልጋለሁ የሁልጊዜም ህልሜ ይህ ነው ሊሳካም ላይሳካም ይችላል የእኔ ውሳኔ አይደለም የሚሆነው “ ሲል አሌክሳንደር አርኖልድ ተናግሯል።

“ አሁን ሙሉ ትኩረት የማደርገው የውድድር አመቱ ላይ እና ቡድኑ ሊጉን እንዲያሸንፍ ማገዝ ነው ፣ አውሮፓ ላይ ማንም ሊቀርበው የማይፈልገው ተከላካይ መሆን እፈልጋለሁ።"አርኖልድ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የኒውካስል ካራባኦ ካፕ ጨዋታ ተራዘመ !

ኒውካስል ዩናይትድ ነገ ከዌምብለደን ጋር ሊያደርገው የነበረው የካራባኦ ካፕ ሶስተኛ ዙር ጨዋታ ለሌላ ጊዜ መራዘሙ ይፋ ተደርጓል።

ጨዋታው የተራዘመው በዌምብለደን ቼሪ ሬድ ሪኮርድስ ስታዲየም በገጠመ የጎርፍ አደጋ ምክንያት ስታዲየሙ ጉዳት ስለደረሰበት መሆኑ ተገልጿል።

አሰልጣኝ ኤዲ ሀው ጨዋታውን አስመልክቶ ዛሬ ጠዋት ሊሰጡ የነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ መሰረዙ ተጠቁሟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ ባርሴሎና ተጨማሪ ተጨዋች ባለማስፈረሙ አመሰገንኩ “ ዣቪየር ቴባስ

የስፔን ላሊጋው ፕሬዝዳንት ዣቪየር ቴባስ ባርሴሎና በአሁን ሰዓት ትልቅ ዋንጫዎችን ማሸነፍ እንደሚችል ገልጸዋል።

“ ባርሴሎና ተጨማሪ ተጨዋች ባለማስፈረሙ ፈጣሪን አመሰገንኩ “ ያሉት ፕሬዝዳን ዣቪየር ቴባስ ባይሆን ጨዋታዎችን 10ለ0 ነበር የሚያሸንፉት “ ብለዋል።

ፕሬዚዳንቱ አያይዘውም ባርሴሎና የስፔን ላሊጋ እና ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫዎችን ማሸነፍ እንደሚችል ተናግረዋል።

“ እንደ ላሚን ያማል እና ቪንሰስ ጁኒየር ያሉ ተጨዋቾችን ልንከባከባቸው ይገባል።“ ዣቪየር ቴባስ

ባርሴሎና የግብ ጠባቂው ቴር ስቴገንን መጎዳት ተከትሎ ጉዳቱ የረጅም ጊዜ ከሆነ በቀጣይ ግብ ጠባቂ ማስፈረም እንደሚችል ፕሬዝዳንቱ አያይዘው ገልጸዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
🌼 እስከ ጥቅምት 15 #ከዋናው ይዘዙ! 🌼

📌 ለበለጠ መረጃና ትዕዛዝ 📲 09011382830910851535 እና 0913586742 ላይ ይደውሉ።

👉🏾 እንዲሁም በቴሌግራም @Wanawsales ላይ የሽያጭ ሰራተኞቻችንን በቀጥታ በማናገር ወይም በቴሌግራም ቦት @WanawSportBot ይዘዙን።

Instagram | Facebook | TikTok

🏅ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
ቴር ስቴገን ለረጅም ጊዜ ከሜዳ ይርቃል !

ጀርመናዊው የባርሴሎና ግብ ጠባቂ ቴር ስቴገን ትላንት ምሽት ክለቡ ቪያሪያልን ባሸነፈበት ጨዋታ ከባድ ጉዳት አስተናግዶ ተቀይሮ ለመውጣት ተገዷል።

ግብ ጠባቂው በቀኝ ጉልበቱ ላይ የመሰበር አደጋ እንዳጋጠመው ባርሴሎና ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።

ቴር ስቴገን ዛሬ ከሰዓት በኋላ የቀዶ ጥገና ህክምና እንደሚያደርግ ባርሴሎና አያይዞ ይፋ አድርጓል።

ይህንንም ተከትሎ ቴር ስቴገን በጉዳቱ ምክንያት እስከ ስምንት ወራት ጊዜ ከሜዳ ሊርቅ እንደሚችል ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ማድሪድ የተጫዋቹን ውል ሊያራዝም ነው ! ሪያል ማድሪድ የፈረንሳዊውን የግራ መስመር ተጨዋች ፌርላንድ ሜንዲ ኮንትራት ለማራዘም ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል። ተጨዋቹ በሪያል ማድሪድ ቤት ለአንድ ተጨማሪ አመት የማራዘም አማራጭ ያካተተ አዲስ የሶስት አመት ውል ለመፈረም መስማማቱ ተነግሯል። ሎስ ብላንኮዎቹ ካናዳዊውን የባየር ሙኒክ የመስመር ተጨዋች አልፎንሶ ዴቪስ የሚያስፈርሙ ከሆነ ፌርላንድ ሜንዲ…
ማድሪድ የተጫዋቹን ውል አራዝሟል !

ሪያል ማድሪድ የፈረንሳዊውን የግራ መስመር ተጨዋች ፌርላንድ ሜንዲ ኮንትራት ማራዘሙን አሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቲ በይፋ አረጋግጠዋል።

ተጨዋቹ በሪያል ማድሪድ ቤት ለአንድ ተጨማሪ አመት የማራዘም አማራጭ ያካተተ አዲስ የሶስት አመት ውል መፈረሙ ተነግሯል።

“ ፌርላንድ ሜንዲ አዲስ ውል ፈርሟል በእሱ በጣም ደስተኞች ነን “ ሲሉ አሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቲ ተናግረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ አርሰናል ምንም ቢያደርግ መጨረሻ ላይ ዋንጫው የኛ ነው “ አካንጂ

የማንችስተር ሲቲው ተጨዋች ማኑኤል አካንጂ ሁልጊዜም ከአርሰናል ጋር ስንጫወት ድራማ መስራት ነው የሚፈልጉት በማለት ተናግሯል።

“ በምሽቱ ጨዋታ እንዳደረጉት ከእነሱ የተሻለ ይኖራል ብዬ አላስብም “ ያለው ማኑኤል አካንጂ ነገርግን በዚህ አመትም የተለየ አይሆንም በመጨረሻ ዋንጫው የኛ ነው ሊጉን በድጋሜ እናሸንፋለን “ ብሏል።

“ እነሱ ሁልጊዜ የሚፈልጉት ድራማ ነው ፣ በአንድ ነጥብ ከተደሰቱ ለእነሱ ሰርቷል እኛ ግን ደስተኛ አይደለንም ቢሆንም አሁንም የሊጉ መሪ ነን “ ሲል ማኑኤል አካንጂ ተናግሯል።

“ ለማሸነፍ ሞክረን ነበር በተለይ የአንድ ተጨዋች ብልጫ በወሰድንበት ከእረፍት በኋላ ነገርግን በአስር ተጨዋች በፍፁም ቅጣት ምት ክልላቸው ውስጥ ሲከላከሉ ነበር ከባድ ነበር “ ማኑኤል አካንጂ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ኤቨርተን አዲስ ባለቤት ማግኘቱ ይፋ ሆነ !

የመርሲሳይዱ ክለብ ኤቨርተን ባለቤት ፋርሀድ ሞሽሪ በክለቡ ያላቸውን ድርሻ ለፍሬድኪን ግሩፕ ለመሸጥ ከስምምነት መድረሳቸውን ይፋ አድርገዋል።

ይህንንም ተከትሎ ፍሬድኪን ግሩፕ ፋርሀድ ሞሽሪ በመርሲሳይዱ ክለብ ኤቨርተን የነበራቸውን 94.1% ድርሻ በመግዛት ክለቡን በበላይነት እንደሚቆጣጠረው ተነግሯል።

ፍሬድኪን ግሩፕ የክለቡን ድርሻ በመቆጣጠር የተወሰነውን እዳም ለመክፈል ከስምምነት መደረሱ ተዘግቧል።

አሜሪካዊው ፍሬድኪን በተጨማሪ የጣልያኑ ክለብ ሮማ ባለቤት እና ፕሬዝዳንት መሆናቸው ይታወቃል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
“ አርሰናል ባለፉት ሁለት አመታት ትልቁ ተፎካካሪያችን ነው “ ጋርዲዮላ

የማንችስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ባለፉት ሁለት አመታት አርሰናልን በዋንጫ ፉክክሩ በመርታታቸው “ እድለኛ ነበርኩ “ ብለዋል።

“ አርሰናል ባለፉት ሁለት አመታት ትልቁ ተፎካካሪያችን ነው ፤ እነሱን በመርታታችን እድለኞች ነን ነገርግን ፍልሚያውን እናውቀዋለን ፈተናውን መቀበል አለብን “ ሲሉ ጋርዲዮላ ተናግረዋል።

ኬቨን ዴብሮይን ያጋጠመው ጉዳት ለረጅም ጊዜ ከሜዳ ያርቀዋል የሚል እምነት እንደሌላቸው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ አያይዘው ገልጸዋል።

አሰልጣኙ ቀጥለውም ዴብሮይን ቡድናቸው በቀጣይ ከዋትፎርድ እና ኒውካስል ዩናይትድ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ መድረሱን እርግጠኛ እንዳልሆኑ ተናግረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ስሑል ሽረ አመቱን በድል ጀምረዋል !

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የ 2017 የውድድር ዘመን ስሑል ሽረ ከአዳማ ከተማ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 3ለ2 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የስሑል ሽረን የማሸነፊያ ግቦች አሌክስ ኪታታ ፣ አላዛር አድማሱ እና አሊያስ አህመድ በፍፁም ቅጣት ምት አስቆጥረዋል።

አዳማ ከተማን ከሽንፈት ያልታደጉ ግቦች ነቢል ኑሪ እና ቢኒያም አይተን በፍፁም ቅጣት ምት ከመረብ አሳርፈዋል።

ቀጣይ መርሐ ግብራቸው ምን ይመስላል ?

አርብ ⏩️  ሀዋሳ ከተማ ከ ስሑል ሽረ

አርብ ⏩️ ባሕር ዳር ከተማ ከ አዳማ ከተማ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ኬይለር ናቫስ ወደ ባርሴሎና ?

ኮስታሪካዊው ግብ ጠባቂ ኬይለር ናቫስ የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ሊያስፈርመው የሚፈልግ ከሆነ ቡድኑን ለመቀላቀል ፍላጎት እንዳለው ተዘግቧል።

የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂው ቴር ስቴገን ለረጅም ጊዜ መጎዳቱን ተከትሎ አዲስ ግብ ጠባቂ ያስፈርማል ተብሎ ይጠበቃል።

የቀድሞ የሪያል ማድሪድ ግብ ጠባቂ ኬይለር ናቫስ በቅርቡ ከፒኤስጂ ጋር ከተለያየ በኋላ ያለ ክለብ ይገኛል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የሮድሪ ጉዳት ሁኔታ ምን ይመስላል ?

የማንችስተር ሲቲው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሮድሪ በትላንቱ የአርሰናል ጨዋታ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ መውጣቱ ይታወሳል።

ስፔናዊው አማካይ ሮድሪ በቀኝ ጉልበቱ ላይ ያጋጠመው ጉዳት የ " ACL " ጉዳት ሳይሆን እንዳልቀረ በመዘገብ ላይ ይገኛል።

ይህ ከሆነ ሮድሪ ከጉዳቱ አገግሞ ወደ ሜዳ ለመመለስ በርካታ ወራት እንደሚያስፈልገው እና ምናልባትም በዚህ የውድድር አመት ላንመለከተው እንደምንችል ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
የሮድሪ ጉዳት ሁኔታ ምን ይመስላል ? የማንችስተር ሲቲው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሮድሪ በትላንቱ የአርሰናል ጨዋታ ጉዳት አጋጥሞት ተቀይሮ መውጣቱ ይታወሳል። ስፔናዊው አማካይ ሮድሪ በቀኝ ጉልበቱ ላይ ያጋጠመው ጉዳት የ " ACL " ጉዳት ሳይሆን እንዳልቀረ በመዘገብ ላይ ይገኛል። ይህ ከሆነ ሮድሪ ከጉዳቱ አገግሞ ወደ ሜዳ ለመመለስ በርካታ ወራት እንደሚያስፈልገው እና ምናልባትም በዚህ የውድድር አመት…
ሮድሪ ከውድድር አመቱ ውጪ ሊሆን ይችላል !

ስፔናዊው የማንችስተር ሲቲ አማካይ ሮድሪ በትላንቱ የአርሰናል ጨዋታ ያጋጠመው ጉዳት ከባድ መሆኑን ዘ አትሌቲክ አረጋግጧል።

ይህንንም ተከትሎ የማንችስተር ሲቲው ተጨዋች ሮድሪ በጉዳቱ ምክንያት ለረጅም ጊዜ ከሜዳ ይርቃል ተብሎ ይጠበቃል ።

ማንችስተር ሲቲዎች ተጨዋቹ በጉዳት ከውድድር አመቱ ውጪ ይሆናል የሚል ፍራቻ እንዳላቸው ተነግሯል።

ሮድሪ በእግርኳስ ህይወቱ ከዚህ በፊት በጉዳት ምክንያት ለሀገሩ እና ክለቡ ያመለጡት ጨዋታዎች ስምንት ብቻ መሆናቸው ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/09/28 15:25:02
Back to Top
HTML Embed Code: