Telegram Web Link
ዩናይትድ ዝውውሮቹን በፍጥነት ማጠናቀቅ ይፈልጋሉ !

በዝውውር መስኮቱ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ የሚገኙት ማንችስተር ዩናይትዶች የማትያስ ዴሊትን እና ጆሽዋ ዚርክዜን ዝውውር በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየሰሩ መሆኑ ተገልጿል።

ማንችስተር ዩናይትድ አሁን ላይ ከባየር ሙኒክ ጋር በማትያስ ዴሊት የዝውውር ሒሳብ ዙሪያ ለስምምነት መቃረባቸው ተነግሯል።

ቀያዮቹ ሴጣኖች በተጨማሪም ጆሽዋ ዚርክዜን ዝውውር ለማጠናቀቅ የተወሰኑ ስራዎች እንደሚቀሯቸው ተነግሯል።

ተጨዋቹ የህክምና ምርመራውን ለማድረግ ወደ ማንችስተር ለመጓዝ በዝግጅት ላይ መሆኑ ሲገለፅ በሚቀጥሉት ቀናት ዝውውሩ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የርገን ክሎፕ ወደ አሜሪካ ያመሩ ይሆን ?

የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን ጀርመናዊውን አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ በቀጣይ የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርገው በሀላፊነት ለመሾም ጥረት ሊያደርጉ መሆኑ ተገልጿል።

አሜሪካ ካዘጋጀችው የዘንድሮው የኮፓ አሜሪካ ምድብ ጨዋታ መሰናበቷን ተከትሎ አሰልጣኝ ግሬግ ቤርሀልተርን ከአሰልጣኝነት ማሰናበቷ ይታወቃል።

አሜሪካ በቀጣይ በጣምራ በምታዘጋጀው የ2026 አለም ዋንጫ ውድድር አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ቡድኑን እንዲመሩ ፍላጎት እንዳላት ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ዩናይትድ ዝውውሮቹን በፍጥነት ማጠናቀቅ ይፈልጋሉ ! በዝውውር መስኮቱ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ የሚገኙት ማንችስተር ዩናይትዶች የማትያስ ዴሊትን እና ጆሽዋ ዚርክዜን ዝውውር በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየሰሩ መሆኑ ተገልጿል። ማንችስተር ዩናይትድ አሁን ላይ ከባየር ሙኒክ ጋር በማትያስ ዴሊት የዝውውር ሒሳብ ዙሪያ ለስምምነት መቃረባቸው ተነግሯል። ቀያዮቹ ሴጣኖች በተጨማሪም ጆሽዋ ዚርክዜን ዝውውር ለማጠናቀቅ…
ጆሽዋ ዚርክዜ ዛሬ ምሽት ወደ እንግሊዝ ያመራል !

ኔዘርላንዳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ጆሽዋ ዚርክዜ ከቦሎኛ ወደ ማንችስተር ዩናይትድ የሚያደርገውን ዝውውር ለማጠናቀቅ ዛሬ ምሽት ወደ እንግሊዝ እንደሚያመራ ተገልጿል።

የ 23ዓመቱ የፊት መስመር ተጨዋች ጆሽዋ ዚርክዜ በነገው ዕለት የህክምና ምርመራውን በማድረግ በይፋ ማንችስተር ዩናይትድን ይቀላቀላል።

ማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋቹን በ 42.5 ሚልዮን ዩሮ በሆነ የዝውውር ሒሳብ በአምስት አመት ኮንትራት እንደሚያስፈርሙት ተገልጿል።

ቀያዮቹ ሴጣኖች በተጨማሪም ሩድ ቫን ኔስትሮይ እና ሬኔ ሀኬን በክለቡ የአሰልጣኞች ቡድን ውስጥ ማካተታቸውን በይፋ አስታውቀዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ዩናይትድ ከቫን ዴ ቢክ ዝውውር ስንት ያገኛል ? የማንችስተር ዩናይትዱ የመሐል ሜዳ ተጨዋች ዶኒ ቫን ዴቢክ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊውን የስፔን ክለብ ጂሮና ለመቀላቀል ከጫፍ መድረሱ ተገልጿል። ቀያዮቹ ሴጣኖች ከተጨዋቹ ዝውውር 500,000 ዩሮ እንደሚቀበሉ ሲገለፅ በውሉ ውስጥ ታይቶ የሚጨምር እስከ አራት ሚልዮን ዩሮ የሚሆን ክፍያ እንደሚካተት ተነግሯል። ኔዘርላንዳዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች…
ዶኒ ቫን ዴ ቢክ በይፋ ጂሮናን ተቀላቀለ !

የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳታፊው የስፔኑ ክለብ ጂሮና ኔዘርላንዳዊውን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ዶኒ ቫን ዴቢክ ከማንችስተር ዩናይትድ ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል።

ጂሮና ለተጨዋቹ ዝውውር 500,000 ዩሮ የዝውውር ሒሳብ ለማንችስተር ዩናይትድ መክፈላቸው ተገልጿል።

ዶኒ ቫን ዴቢክ በጂሮና እስከ 2028 የሚያቆየውን የአራት አመት ኮንትራት መፈረሙ ይፋ ተደርጓል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
የርገን ክሎፕ ወደ አሜሪካ ያመሩ ይሆን ? የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን ጀርመናዊውን አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ በቀጣይ የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርገው በሀላፊነት ለመሾም ጥረት ሊያደርጉ መሆኑ ተገልጿል። አሜሪካ ካዘጋጀችው የዘንድሮው የኮፓ አሜሪካ ምድብ ጨዋታ መሰናበቷን ተከትሎ አሰልጣኝ ግሬግ ቤርሀልተርን ከአሰልጣኝነት ማሰናበቷ ይታወቃል። አሜሪካ በቀጣይ በጣምራ በምታዘጋጀው የ2026 አለም ዋንጫ ውድድር…
ክሎፕ የአሜሪካን ጥያቄ ውድቅ አደረጉ !

በቅርቡ ከሊቨርፑል ጋር የተለያዩት ጀርመናዊው አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ከአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን የቀረበላቸውን የአሰልጣኝነት ጥያቄ ውድቅ ማድረጋቸው ተገልጿል።

የአሜሪካ እግርኳስ ፌዴሬሽን ባለፈው ሳምንት ከአሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ጋር ተነጋግረው የነበረ ቢሆንም ብሔራዊ ቡድኑን የሚቀላቀሉበት እድል አለመኖሩ ተነግሯል።

አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ከዚህ በፊት እንደተናገሩት አሁን ላይ ወደ ሀላፊነት መመለስ እንደማይፈልጉ እና እረፍት ማድረግ እንደሚፈልጉ ማረጋገጣቸው ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
#BiniyamGirmay🇪🇷 ኤርትራዊው ብስክሌተኛ ቢንያም ግርማይ በዓለም ላይ ከፍተኛ የሆነ ስፍራ የሚሰጠውን ቱር ደ ፍራንስ የተሰኘውን የፈረንሳዩን የብስክሌት ውድድር ‘ስቴጅ 3’ በማሸነፍ የመጀመሪያው ጥቁር አፍሪካዊ በመሆን ለኤርትራ እና ለአፍሪካ ታሪክ ሰርቷል። ከውድድሩ መጠናቀቅ በኋላ የውድድሩ ተሳታፊዎች ወደ ቢኒያም በመሄድ " እንኳን ደስ አለህ ! አንተ በጣም ምርጡ ነበርክ ፤ በጣምም ጠንካራ…
ቢኒያም ግርማይ ለሶስተኛ ጊዜ አሸናፊ ሆነ !

ኤርትራዊው ብስክሌተኛ ቢኒያም ግርማይ በታላቁ የቱር ደ ፍራንስ ውድድር በአስራ ሁለተኛው ቀን ውድድር ቀድሞ በመግባት ለሶስተኛ ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ መሆን ችሏል።

በመጨረሻዎቹ መቶ ሜትሮች የነበረውን ከባድ ፉክክር መርታት የቻለው ቢኒያም ግርማይ በቱር ደ ፍራንስ በርካታ ነጥብ በመሰብሰብ አረንጓዴ ማሊያውን ( Green Jersey ) አስጠብቋል።

ቢኒያም 203 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የ12ኛ ቀን ውድድር በ4 ሰዓት ከ17 ደቂቃ ከ15 ሰከንድ በመግባት አጠናቋል።

በዘንድሮው ውድድር በአጠቃላይ ውጤት ታዴ ፖጋቻር የቢጫ ማሊያውን ውድድር እየመራ ሲሆን ፣ ቢኒያም ግርማይ ደግሞ በርካታ ነጥብ በመሰብሰብ የአረንጓዴ ማሊያ መሪ ነው።

ቢኒያም ግርማይ ከድሉ በኋላ በሰጠው አስተያየት " ከአሁን ጀምሬ የአረንጓዴ ማልያውን ለማስቀጠል ትኩረት ማድረጌን እቀጥላለሁ ፣ ይህንን ክብር ካገኘሁ በኋላ ፈጣንነት እየተሰማኝ ነው።"ሲል ተደምጧል።

ቢኒያም ባለፈው ሳምንት ሶስተኛውን መድረክ በማሸነፍ የመጀመሪያው ጥቁር አፍሪካዊ ሆኖ ታሪክ መፃፉ አይዘነጋም።

ኤርትራዊው ብስክሌተኛ ቢኒያም ግርማይ በተለያዩ ጊዜያት ባስመዘገባቸው ስኬቶች “ የአፍሪካ የብስክሌት ንጉሥ “ የሚል ቅፅል ስም ተሰጥቶታል።

Credit - BBC News Amharic

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ሮድሪ ማድሪድ እንዲመጣ እየጠየቅኩት ነው " ካርቫል

ስፔናዊው የሎስ ብላንኮዎቹ የመስመር ተጨዋች ዳኒ ካርቫል የማንችስተር ሲቲው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሮድሪ ሪያል ማድሪድን እንዲቀላቀል እየጠየቀው መሆኑን ገልጿል።

" ሮድሪ ማድሪድ እንዲመጣ በየቀኑ እየነገርኩት ነው ሲቲን እንዲለቅ ጠይቄዋለሁ እሱን እንፈልገዋለን ፣ ኮንትራት እንዳለው ነግሮኛል ነገርግን ለእኛ ቢፈርም ትክክለኛው ተጨዋች ይሆናል።"ሲል ዳኒ ካርቫል ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
አርሰናል ለዎልቭስ ስንት አቅርቦ ነበር ? የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል እንግሊዛዊውን ግብ ጠባቂ ዳንኤል ቤንትሌይ ከዎልቭስ ለማስፈረም የመጀመሪያ የዝውውር ሒሳብ አቅርበው ውድቅ ተደርጎባቸዋል። መድፈኞቹ ዳንኤል ቤንትሌይን ለማስፈረም አቅርበው ውድቅ የሆነባቸው ሒሳብ 50,000 ፓውንድ እንደነበር ለዎልቭስ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ዘግበዋል። በአሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ የሚመሩት አርሰናሎች የ 30ዓመቱን…
አርሰናል ወጣት ግብ ጠባቂ ለማስፈረም ጠየቀ !

አማራጭ ግብ ጠባቂ ለማስፈረም በእንቅስቃሴ ላይ የሚገኘው አርሰናል የአያክሱን እንግሊዛዊ ወጣት ግብ ጠባቂ ቶሚ ሴትፎርድ ለማስፈረም የዝውውር ጥያቄ ማቅረባቸው ተገልጿል።

ባለ ጥሩ ተሰጥኦ ባለቤት መሆኑ የተነገረው የ 18ዓመቱ ግብ ጠባቂ ቶሚ ሴትፎርድ በአያክስ ያለው ውል በ2025 የሚጠናቀቅ ሲሆን መድፈኞቹን መቀላቀል ይፈልጋል ተብሏል።

መድፈኞቹ ከቀናት በፊት እንግሊዛዊውን ግብ ጠባቂ ዳንኤል ቤንትሌይ ከዎልቭስ ለማስፈረም 50,000 ፓውንድ አቅርበው ውድቅ እንደሆነባቸው ይታወሳል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
አርሰናል ተጫዋቹን በውሰት ሊሰጥ ነው !

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የመሐል ሜዳ ተጨዋቹ ሳምቢ ሎኮንጋ በውሰት የላሊጋውን ክለብ ሲቪያ ለመቀላቀል ከጫፍ መድረሱ ተገልጿል።

ሲቪያ የተጫዋቹን ሙሉ ደሞዝ ለመክፈል ከስምምነት መድረሳቸው ሲገለፅ እንዲሁም በሚቀጥለው አመት በ12 ሚልዮን ዩሮ የመግዛት አማራጭ እንደሚካተትላቸው ተነግሯል።

ቤልጂየማዊው ተጨዋች ሎኮንጋ በቀጣይ የህክምና ምርመራውን በማድረግ ሲቪያን እንደሚቀላቀል ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from HEY Online Market
•PlayStation 5, 73,000 Birr
•Playstaion 5 Slim, 78,000 Birr

•PlayStation 4 Slim, 35,000 Birr
•PlayStation 4 Pro, 43,000 Birr

•Playstaion portal, 35,000 Birr
•Meta Quest 2, 55,000 Birr
•Meta Quest 3, 83,000 Birr

Contact
0953964175 @heymobile

@heyonlinemarket
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
Al Ahly - Pyramids
Dundalk - Drogheda
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
የአሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት የእንግሊዝ ቆይታ ?

የእንግሊዝ እግር ኳስ ማህበር አሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት በእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝነታቸው እንዲቀጥሉ እንደሚፈልጉ ተገልጿል።

እንግሊዝ እሁድ ከስፔን በምታደርገው የአውሮፓ ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ውጤት ምንም ቢሆን አሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት እንዲቀጥሉ ይፈልጋሉ።

አሰልጣኝ ጋሪዝ ሳውዝጌት የአውሮፓ ዋንጫው ከመጀመሩ አስቀድሞ ዋንጫውን የማያሸንፉ ከሆነ ብሔራዊ ቡድኑን ሊለቁ እንደሚችሉ ጠቁመው ነበር።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
Photo
የዩራጓይ ተጨዋቾች ቅጣት ሊጣልባቸው ይችላል !

የደቡብ አሜሪካ እግርኳስ ማህበር ትላንት ሌሊት በዩራጓይ ተጨዋቾች እና ኮሎምቢያ ደጋፊዎች መካከል የተፈጠረውን ክስተት እየመረመረ እንደሚገኝ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ አስታውቋል።

በጨዋታው ዳርዊን ኑኔዝን ጨምሮ የዩራጓይ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋቾች ወደ ተመልካች መቀመጫ ወንበር በመግባት ከኮሎምቢያ ደጋፊዎች ጋር ተደባድበው ነበር።

ተጨዋቾቹ ከደጋፊዎች ጋር ፀብ ውስጥ የገቡት የኮሎምቢያ ደጋፊዎች ቤተሰቦቻቸውን ለማጥቃት መሞከራቸውን ተከትሎ እንደሆነ መግለፃቸው ይታወሳል።

የሊቨርፑሉ ተጨዋች ዳርዊን ኑኔዝ እና በተፈጠረው አለመግባባት የተሳተፉ ሌሎች የዩራጓይ ተጨዋቾች ተፈፃሚነቱ እስከ ሊግ የሚደርስ የጨዋታ እገዳ ቅጣት ሊጠብቃቸው እንደሚችል ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ለተሰንበት ግደይ ከኦሎምፒክ ለምን ቀረች ?

የዘንድሮው የአለም አትሌቲክስ የስፖርታዊ ጨዋነት ሽልማት አሸናፊዋ አትሌት ለተሰንበት ግደይ በዘንድሮው የ2024 ፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር ሀገሯን አትወክልም።

አትሌት ለተሰንበት በኦሎምፒክ ውድድር የማትሳተፈው በቅርቡ በፈፀመችው ጋብቻ ምክንያት በቂ የልምምድ ጊዜ ባለማግኘቷ መሆኑን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ረ/ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ከሸገር ኤፍኤም ጋር ባደረገችው ቆይታ ተናግራለች።

" ለተሰንበት ጋብቻ ፈፅማለች እኛም በጣም ደስ ብሎናል " ያለችው ደራርቱ ቱሉ "  በአጋጣሚ ለጋብቻ ስነ ስርዓቱ መሄድ አልቻልንም ለሌሎች አትሌቶች እንደምናደርገው ወይ ከኦሎምፒክ ስንመለስ ያለችበት ሄደን እንኳን ደስ አለሽ እንላታለን " ብላለች።

" ለተሰንበት ግደይ ጨዋ እና በሐይማኖቷ ጠንካራ የሆነች አትሌት ነች እንደ እናት በጣም ደስ ብሎኛል ፣ ለሁሉም አትሌቶች የምመኘው ነው ብትመጣ እና በኦሎምፒክ አብራን ብትሆን ደስ ይለን ነበር።" ደራርቱ ቱሉ

አትሌት ለተሰንበት ግደይ ከወራት በፊት በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ በሐይማኖታዊ ስነ-ስርዓት ጋብቻዋን ፈፅማለች።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
አርሰናል ወጣት ግብ ጠባቂ ለማስፈረም ጠየቀ ! አማራጭ ግብ ጠባቂ ለማስፈረም በእንቅስቃሴ ላይ የሚገኘው አርሰናል የአያክሱን እንግሊዛዊ ወጣት ግብ ጠባቂ ቶሚ ሴትፎርድ ለማስፈረም የዝውውር ጥያቄ ማቅረባቸው ተገልጿል። ባለ ጥሩ ተሰጥኦ ባለቤት መሆኑ የተነገረው የ 18ዓመቱ ግብ ጠባቂ ቶሚ ሴትፎርድ በአያክስ ያለው ውል በ2025 የሚጠናቀቅ ሲሆን መድፈኞቹን መቀላቀል ይፈልጋል ተብሏል። መድፈኞቹ ከቀናት…
አርሰናል ሶስት ግብ ጠባቂ ማስፈረም ይፈልጋል !

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል በዝውውር መስኮቱ መጀመሪያ ሶስት ግብ ጠባቂዎችን ለማስፈረም አቅደው እየተንቀሳቀሱ መሆኑ ተገልጿል።

መድፈኞቹ የቁጥር አንድ ግብ ጠባቂ ቦታውን ስፔናዊውን ዴቪድ ራያ በቋሚነት በማስፈረም መጀመራቸው ተነግሯል።

መድፈኞቹ በቀጣይ ቁጥር ሁለት እና ቁጥር ሶስት ግብ ጠባቂ ለማስፈረም በጥረት ላይ እንደሚገኙ ተዘግቧል።

አሮን ራምስዴል በቀጣይ ክለቡን ከለቀቀ በቁጥር ሁለት ግብ ጠባቂነት ስፔናዊውን የእስፓኞል ግብ ጠባቂ ሁዋን ጋርሽያ የመጀመሪያ ምርጫቸው እንደሚያደርጉ ተገልጿል።

በተጨማሪም ቁጥር ሶስት ግብ ጠባቂ አድርገው የመጀመሪያ ተመራጭ ያደረጉት የዝውውር ጥያቄ ያቀረቡለትን የ 18ዓመቱን የአያክስ ግብ ጠባቂ ቶሚ ሴትፎርድ መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ዩናይትድ ዝውውሮቹን በፍጥነት ማጠናቀቅ ይፈልጋሉ ! በዝውውር መስኮቱ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ የሚገኙት ማንችስተር ዩናይትዶች የማትያስ ዴሊትን እና ጆሽዋ ዚርክዜን ዝውውር በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየሰሩ መሆኑ ተገልጿል። ማንችስተር ዩናይትድ አሁን ላይ ከባየር ሙኒክ ጋር በማትያስ ዴሊት የዝውውር ሒሳብ ዙሪያ ለስምምነት መቃረባቸው ተነግሯል። ቀያዮቹ ሴጣኖች በተጨማሪም ጆሽዋ ዚርክዜን ዝውውር ለማጠናቀቅ…
የሙኒክ ደጋፊዎች ዴሊት እንዳይለቅ ድምጽ አሰባሰቡ !

የጀርመኑ ክለብ ባየር ሙኒክ ደጋፊዎች የተከላካይ ስፍራ ተጨዋቹ ማትያስ ዴሊት ወደ ማንችስተር ዩናይትድ የሚያደርገውን ዝውውር ለማስቆም ድምጽ ማሰባሰባቸው ተገልጿል።

ማትያስ ዴሊት ባየር ሙኒክን እንዳይለቅ በተጀመረው የድምፅ ማሰባሰብ ሂደት ላይ 68,000 የክለቡ ደጋፊዎች መፈረማቸው ተነግሯል።

ማንችስተር ዩናይትድ ተጫዋቹን በ50 ሚልዮን ዩሮ የዝውውር ሒሳብ ለማስፈረም ከባየር ሙኒክ ጋር ለመስማማት መቃረባቸው ይታወቃል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ማድሪድ ለኪሊያን ምባፔ አቀባበል ያደርጋል ! ሪያል ማድሪድ በቅርቡ ወደ ቡድናቸው የቀላቀሉትን ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ ቀጣይ ሳምንት ደማቅ አቀባበል እንደሚያደርጉለት ይፋ አድርገዋል። ሎስ ብላንኮዎቹ ለኪሊያን ምባፔ ቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ ሐምሌ 9/2016 ዓ.ም ይፋዊ አቀባበል በሳንቲያጎ በርናቦ ስታዲየም ማዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። ኪሊያን ምባፔ ከይፋዊ ትውውቁ በኋላ በሳንቲያጎ…
በምባፔ አቀባበል ላይ 80,000 ደጋፊዎች ይጠበቃሉ !

ሪያል ማድሪድ በሳንቲያጎ በርናቦ ፈረንሳዊውን የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ ለማስተዋወቅ ያዘጋጀው የመግቢያ ትኬቶች ተሸጠው መጠናቀቃቸው ተገልጿል።

ይህንንም ተከትሎ በአቀባበል ስነስርዓቱ 80,000 የሪያል ማድሪድ ደጋፊዎች በሳንቲያጎ በርናቦ ስታዲየም ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በአቀባበሉ ዚነዲን ዚዳንን ጨምሮ በርካታ የሪያል ማድሪድ የቀድሞ ታሪካዊ ተጨዋቾች እንዲገኙ ግብዣ እንደቀረበላቸው ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
🇪🇹 WANAW 🤝 ESCFUK 🇬🇧

የኢትዮጵያ ስፖርትና ባህል ፌደሬሽን በዩናይትድ ኪንግደም ከሐምሌ 12-14፣ 2024 የሚያዘጋጀው 12ኛው አመታዊ የስፖርትና የባህል ፌስቲቫል ዛሬ ይጀምራል!

ዋናው ስፖርት የዚህ ደማቅ ፌስቲቫል ይፋዊ ስፖንሰር እና ትጥቅ አቅራቢ በመሆኑ በድጋሚ የተሰማውን ኩራት ይገልፃል።

Instagram | Facebook | TikTok

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
🎉ፏ ፈሽ በአርባምንጭ ከሳፋሪኮም ጋር!🎊

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የ2016 ሳፋሪኮም ታላቁ የአርባምንጭ ሩጫ የክብር ስፖንሰር በመሆኑ ታላቅ ኩራት ይሰማዋል! ለመጀመሪያ ግዜ እየተደረገ ባለው በዚህ የታላቁ ኢትዮጵያ የሩጫ ውድድር በአረንጓዴዋና ውቢቷ አርባምንጭ ተገናኝተን በጋራ ፏ ፈሽ እንበል!

🎽የታላቁን የአርባምንጭ ሩጫን ቲሸርት በM-PESA እየገዛን ከሴቻ (ፌሬንድሽ ካፌ) ወይም ከሲቀላ(ቱሪስት ሆቴል) እንውሰድ!

🌴 ሐምሌ 7 እንገናኝ!

🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናዉርድ:
https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom
#SafaricomEthiopia
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether
#EURO2024

እንግሊዝ ውስጥ በርካታ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቻቸው በመጪው ሰኞ ጠዋት ከተለመደው የመግቢያ ሰዓት ዘግይተው እንዲገቡ ፍቃድ እንደሚሰጡ ተገልጿል።

ትምህርት ቤቶቹ ይህንን የሚያደርጉት ተማሪዎቹ እሁድ ምሽት እንግሊዝ ከስፔን ጋር የምታደርገውን የአውሮፓ ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ አምሽተው እንዲመለከቱ መሆኑ ተነግሯል።

አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ዛሬ ተማሪዎቻቸው የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ማልያን ለብሰው እንዲገቡ መፍቀዳቸው ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/10/01 04:59:05
Back to Top
HTML Embed Code: