Telegram Web Link
" አቡበከር ናስር የማሜሎዲ ሰንዳውንስ ተጨዋች አይደለም " ሩላኒ ሞክዌና

በደቡብ አፍሪካ ሊግ ለማሜሎዲ ሰንዳውንስ የሚጫወተው ኢትዮጵያዊው የፊት መስመር ተጨዋች አቡበከር ናስር አሁን ላይ የክለቡ ተጨዋች አለመሆኑን አሰልጣኝ ሩላኒ ሞክዌና ተናግረዋል።

የማሜሎዲ ሰንዳውንስ ዋና አሰልጣኝ ሩላኒ ሞክዌና ትላንት ምሽት ከሀገሪቱ መገናኛ ብዙሀን ጋር ባደረጉት ቆይታ ስለ አቡበከር ናስር የክለቡ ሁኔታ ተጠይቀው ነበር።

ለወራት በጉዳት ላይ የነበረው አቡበከር ናስር በዘንድሮው የውድድር አመት በሁለተኛው ዙር ከማሜሎዲ ሰንዳውንስ የቡድን ዝርዝር ውጪ ተደርጎ እንደነበር ይታወሳል።

አሰልጣኝ ሩላኒ ሞክዌና በሰጡት አስተያየትም በቡድን ዝርዝራቸው ውስጥ ስላልተመዘገበ ተጨዋች መናገር እንደማይፈልጉ በመግለፅ " አቡበከር ናስር አሁን ላይ የእኛ ተጨዋች አይደለም "ሲሉ ተደምጠዋል።

አሰልጣኝ ሩላኒ ሞክዌና ይህንን ይበሉ እንጂ ክለቡ ማሜሎዲ ሰንዳውንስ እስካሁን ስለ አቡበከር ናስር ሁኔታ በይፋ ያለው ነገር የለም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ጄሴ ማርሽ አርጀንቲና እንድትቀጣ ጠይቀዋል !

የካናዳ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ጄሴ ማርሽ የትላንት ተጋጣሚያቸው አርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ቅጣት እንዲጣልበት አወዳዳሪውን አካል ጠይቀዋል።

አሰልጣኙ ቅጣቱ እንዲጣል የጠየቁት የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ተጨዋቾች ከእረፍት መልስ ከመልበሻ ቤት ለመውጣት የተወሰኑ ደቂቃዎች መዘግየታቸውን ተከትሎ ነው።

አሰልጣኝ ጄሴ ማርሽ በንግግራቸውም " ከእኛ ጋር እንዴት እንደሚጫወቱ ቪዲዮች እየተመለከቱ ሲተነትኑ እንደነበር አውቃለሁ ዳኞች የሆነ ነገር ማድረግ ነበረባቸው እኛ ብንዘገይ እንቀጣ ነበር አርጀንቲና መቀጣት አለባት።"ብለዋል።

ጨዋታውን የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ከእረፍት በኋላ ባስቆጠራቸው ግቦች 2ለ0 ማሸነፉ አይዘነጋም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" የምድቡ መሪ ሆነን ማለፍ እንፈልጋለን " ከሪም አክቱርኮግሉ

የቱርክ ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጨዋች ከሪም አክቱርኮግሉ የምሽቱን የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ ለማሸነፍ አልመው ወደ ሜዳ እንደሚገቡ ገልጿል።

" ለየትኛውም ጨዋታ የምንዘነጋጀው ለማሸነፍ ብቻ ነው " የሚለው ከሪም አክቱርኮግሉ ፖርቹጋልን ለማሸነፍ በጥሩ ሁኔታ ተዘጋጅተናል አሸንፈን የምድቡ የበላይ ሆነን ማለፍ እንፈልጋለን ብሏል።

የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ከቱርክ ብሔራዊ ቡድን ጋር የአውሮፓ ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታቸውን ዛሬ ምሽት 1:00 ያደርጋሉ።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የኢትዮጵያ  ቡና ይፋዊ አጋር የሆነው ቤቲካ - የኢትዮጵያ ቡናን  23ኛ የጨዋታ ቀን የዲጂታል መፅሄት ይዞ ቀርቧል።
በመፅሄቱ ላይ የዕለቱ ጨዋታን የተመለከቱና ሌሎች የተለያዩ መረጃዎች የሚቀርቡ ይሆናል፡፡

መፅሄቱን ለማግኘት ቀጣዩን ሊንክ ይጫኑ

https://www.tg-me.com/betikaethiopia/5347

የጨዋታ መፅሄት ቁጥር 23
ኢትዮጵያ መድን ከ ኢትዮጵያ ቡና
ዛሬ 9:00

ቤቲካ - የኢትዮጵያ ቡና ይፋዊ አጋር
ቼልሲ ተጨዋች ለማስፈረም ተቃርበዋል !

የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ እንግሊዛዊውን ወጣት የፊት መስመር ተጨዋች ኦማሪ ኬሊማንን ከአስቶን ቪላ ለማስፈረም መቃረባቸው ተገልጿል።

ሰማያዊዎቹ ለ 18ዓመቱን የፊት መስመር ተጨዋች ኦማሪ ኬሊማን ዝውውር 19 ሚልዮን ፓውንድ ወጪ እንደሚያደርጉ ተነግሯል።

ለእንግሊዝ ከ 19ዓመት በታች ቡድን የሚጫወተው ኦማሪ ኬሊማን በቀጣይ የህክምና ምርመራውን አድርጎ በይፋ ቼልሲን እንደሚቀላቀል ይጠበቃል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የጣልያን እና ክሮሽያን ጨዋታ የሚመሩት ዳኛ ማን ናቸው ?

የጣልያን ብሔራዊ ቡድን ከክሮሽያ ብሔራዊ ቡድን ጋር ሰኞ ምሽት የሚያደርጉትን የምድብ የመጨረሻ ተጠባቂ ጨዋታ ኔዘርላንዳዊው ዳኛ ዳኒ ማኬሌ እንደሚመሩት ተገልጿል።

የምድቡን ተጠባቂ ጨዋታ የሚመሩት ኔዘርላንዳዊ ዳኛ ዳኒ ማኬሌ ከዳኝነት ስራቸው በተጨማሪ በትርፍ ጊዜያቸው በሀገራቸው የፖሊስ ኢንስፔክተር መሆናቸው ተነግሯል።

የጣልያን ብሔራዊ ቡድን ከዚህ በፊት በ 41ዓመቱ ዳኛ ዳኒ ማኬሌ እየተመራ ያደረጋቸውን ሶስት ጨዋታዎች አልተሸነፈም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የጨዋታ አሰላለፍ !

10:00 ጆርጂያ ከ ቼክ ሪፐብሊክ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ፒኤስጂ የምባፔን ደሞዝ አለመክፈላቸው ተገለጸ !

የፈረንሳዩ ክለብ ፒኤስጂ በቅርቡ ሪያል ማድሪድን ለተቀላቀለው የቀድሞ ተጨዋቻቸው ኪሊያን ምባፔ የሁለት ወራት ደሞዝ አለመክፈላቸው ተገልጿል።

ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ የቀድሞ ክለቡ ፒኤስጂ ያልከፈለው 100 ሚልዮን ዩሮ የሚጠጋ የደሞዝ እና ጉርሻ ክፍያ መጠየቁ ተነግሯል።

የ 25ዓመቱ የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ በቅርቡ በነፃ ዝውውር ሪያል ማድሪድን በይፋ መቀላቀሉ አይዘነጋም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2 ' ጆርጂያ 0 - 0 ቼክ ሪፐብሊክ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
26 ' ጆርጂያ 0 - 0 ቼክ ሪፐብሊክ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
እረፍት | ጆርጂያ 1 - 0 ቼክ ሪፐብሊክ

ሚካውታድዝ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ቡናማዎቹ ድል አድርገዋል !

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ የሀያ ስምንተኛ ሳምንት መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ቡና ከ ኢትዮጵያ መድን ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የኢትዮጵያ ቡናን የማሸነፊያ ግቦች አንተነህ ተፈራ እና አብዱልከሪም ወርቁ ከመረብ ሲያሳርፉ ያሬድ ዳርዛ ለኢትዮጵያ መድን አስቆጥሯል።

ኢትዮጵያ መድን ከሰባት ተከታታይ ድል በኋላ ሽንፈት አስተናግደዋል።

ኢትዮጵያ ቡና አምስተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

3️⃣ ኢትዮጵያ ቡና :- 50 ነጥብ

1️⃣0️⃣ ኢትዮጵያ መድን :- 37 ነጥብ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
58 ' ጆርጂያ 1 - 1 ቼክ ሪፐብሊክ

ሚካውታድዝ ሺክ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#EURO2024

በአውሮፓ ዋንጫ ውድድር የምድብ ሁለተኛ ጨዋታ የጆርጂያ ብሔራዊ ቡድን ከቼክ ሪፐብሊክ ብሔራዊ ቡድን ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።

የጆርጂያን ግብ ሚካውታድዝ ከመረብ ሲያሳርፍ ፓትሪክ ሺክ ቼክ ሪፐብሊክን አቻ ማድረግ ችሏል።

የምድብ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

1️⃣ ቱርክ :- 3 ነጥብ

2️⃣ ፖርቹጋል :- 3 ነጥብ

3️⃣ ቼክ ሪፐብሊክ :- 1 ነጥብ

4️⃣ ጆርጂያ :- 1 ነጥብ

በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ እሮብ ጆርጂያ ከፖርቹጋል እንዲሁም ቼክ ሪፐብሊክ ከቱርክ ጋር የሚጫወቱ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የጨዋታ አሰላለፍ !

1:00 ቱርክ ከ ፖርቹጋል

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Forwarded from WANAW SPORT
🔥 #በፍፁም እንዳያመልጥዎ!

📌 ለበለጠ መረጃና ትዕዛዝ 📲 09011382830910851535 እና 0913586742 ላይ ይደውሉ።

👉🏾 እንዲሁም በቴሌግራም @Wanawsales ላይ የሽያጭ ሰራተኞቻችንን በቀጥታ በማናገር ይዘዙን።

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear
TIKVAH-SPORT
Photo
አርዳ ጉለር ለምን ከአሰላለፍ ውጪ ሆነ ?

የቱርክ ብሔራዊ ቡድን ወጣቱ የመሐል ሜዳ ተጨዋች አርዳ ጉለር ከደቂቃዎች በኋላ በሚደረገው የፖርቹጋል ጨዋታ ተጠባባቂ ሆኖ ይጀመራል።

አርዳ ጉለር ጨዋታውን በቋሚነት ለመጀመር መቶ በመቶ ብቁ አለመሆኑን የቱርክ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ቪንሴንሶ ሞንቴላ ገልፀው ነበር።

የ 19ዓመቱ የመሐል ሜዳ ተጨዋች አርዳ ጉለር ቱርክ ጆርጂያን ባሸነፈችበት የመጀመሪያ ጨዋታ ድንቅ ግብ ማስቆጠር ሲችል የጨዋታው ኮከብ በመባልም መመረጥ ችሏል።

በጆርጅያ ጨዋታ በጨዋታው መገባደጃ ደቂቃዎች ተቀይሮ የወጣው አርዳ ጉለር ባለፈው ሐሙስ ከቡድኑ ጋር ልምምድ ሳይሰራ ቀርቷል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#EURO2024

የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አምበል ክርስቲያኖ ሮናልዶ በእግርኳስ ህይወቱ የቱርክ ብሔራዊ ቡድን ላይ ግብ አላስቆጠረም።

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከቱርክ ብሔራዊ ቡድን ጋር ሶስት ጊዜ የተጫወተ ሲሆን እ.ኤ.አ 2012 ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ማስቆጠር ሳይችል ቀርቷል።

ሮናልዶ በምሽቱ ጨዋታ ሁለት መቶ ዘጠኝ ኢንተርናሽናል ጨዋታውን ከፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ጋር የሚያደርግ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
2024/10/01 14:34:50
Back to Top
HTML Embed Code: