Telegram Web Link
75 " ስሎቬኒያ 1 - 1 ዴንማርክ

ጃንዛ                    ኤሪክሰን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
#EURO2024

በአውሮፓ ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ የዴንማርክ ብሔራዊ ቡድን ከስሎቬኒያ ብሔራዊ ቡድን ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።

የዴንማርክ ብሔራዊ ቡድንን ቀዳሚ ያደረገች ግብ ክርስቲያን ኤሪክሰን ከመረብ ሲያሳርፍ ኤሪክ ጃንዛ ስሎቬኒያን አቻ አድርጓል።

የ 32ዓመቱ ተጨዋች ክርስቲያን ኤሪክሰን በአውሮፓ ዋንጫው ግብ ያስቆጠረ በእድሜ ትልቁ ዴንማርካዊ ተጨዋች መሆን ችሏል።

በምድቡ ሁለተኛ ጨዋታ ቀጣይ ሳምንት ሐሙስ ዴንማርክ ከእንግሊዝ እንዲሁም ስሎቬኒያ ከሰርቢያ ጋር ይገናኛሉ።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የጨዋታ አሰላለፍ !

4:00 እንግሊዝ ከ ሰርቢያ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" የምናስበው ማሸነፍ ብቻ ነው " ዴክላን ራይስ

የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ዴክላን ራይስ ቡድናቸው የምሽቱን ጨዋታ ለማሸነፍ በቂ ዝግጅት ማድረጉን ተናግሯል።

" ለጨዋታው ሙሉ ዝግጅት አድርገናል " የሚለው ዴክላን ራይስ " ወደ ሜዳ የምንገባው ጨዋታውን ለማሸነፍ ብቻ ነው በማለት ተናግሯል።

ዛሬ በአማካይ ስፍራ ስለሚጫወተው አሌክሳንደር አርኖልድ የተናገረው ዴክላን ራይስ " ዛሬ የተለየው አርኖልድ ትመለከታላችሁ " ሲል ተደምጧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ቱሄልን እንዳነጋገሩ ነግረውኛል " ቴንሀግ

የማንችስተር ዩናይትዱ ዋና አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ በምሽቱ የእንግሊዝ እና ሰርቢያ ጨዋታ በአንድ የኔዘርላንድ ሚዲያ ተንታኝ ሆነው ይቀርባሉ።

ከጨዋታው አስቀድሞ አስተያየት እየሰጡ የሚገኙት ኤሪክ ቴንሀግ ስለ ክለቡ አሰልጣኝ ቅጥር ውይይት ሲናገሩም " ዩናይትድ ቱሄልን እንዳነጋገሩ ነግረውኛል በመጨረሻ ግን ምርጡ አሰልጣኝ እንዳላቸው አውቀዋል።"ብለዋል።

ኤሪክ ቴንሀግ አያይዘውም በክለቡ ውላቸውን ለማራዘም የሚያደርጉት ንግግር እስካሁን ከስምምነት አለመድረሱን አረጋግጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
14 ' ሰርቢያ 0 - 1 እንግሊዝ

ቤሊንግሀም

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
30 ' ሰርቢያ 0 - 1 እንግሊዝ

                       ቤሊንግሀም

*በጨዋታዎቹ የሚቆጠሩ ግቦችን በጎል ቻናላችን መመልከት ይችላሉ።

የጎል ቻናላችን 👉 https://www.tg-me.com/+rbdEU4UaEdQxYWFk

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
እረፍት | ሰርቢያ 0 - 1 እንግሊዝ

                       ቤሊንግሀም

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
እንግሊዝ ድል አድርጋለች !

በአውሮፓ ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ከሰርቢያ ብሔራዊ ቡድን ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።

ለእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን የማሸነፊያ ግቧን ጁድ ቤሊንግሀም ከመረብ ማሳረፍ ችሏል።

እንግሊዛዊው ተጨዋች ጁድ ቤሊንግሀም በሶስት ታላላቅ ውድድሮች መሳተፍ የቻለ በእድሜ ትንሹ የአውሮፓ ተጨዋች መሆን ችሏል።

የ 20ዓመቱ ተጨዋች ጁድ ቤሊንግሀም እስካሁን በሁለት የአውሮፓ ዋንጫ እና አንድ አለም ዋንጫ ውድድሮች መሳተፍ ችሏል።

ሀሪ ኬን በአራት ታላላቅ ውድድሮች የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድንን በአምበልነት የመራ የመጀመሪያው እንግሊዛዊ ተጨዋች በመሆን አዲስ ታሪክ ፅፏል።

በምድቡ ሁለተኛ ጨዋታ ቀጣይ ሳምንት ሐሙስ እንግሊዝ ከዴንማርክ እንዲሁም ሰርቢያ ከስሎቬኒያ ጋር ይገናኛሉ።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
መልካም ዕድል!
ከፍ የተደረጉ ኦዶችን አይተዋል ? እንግዲያውስ ተወራረዱባቸው!
Belgium - Slovakia
Austria - France
ለተሻለ ውርርድ ቤቲካን ይጠቀሙ! አሁኑኑ Betika.et ላይ /በቴሌግራም ቦታችን - @BetikaETBot ይወራረዱ!
Play More and Spend less!

•PS4 Slim, 34,999 Birr
•PS4 PRO, 41,999 Birr
•Original Controller 6,499 Birr

Contact Us
0953964175 @heymobile

@heyonlinemarket
" ከሀገሬ ጋር ዋንጫ ማሸነፍ እፈልጋለሁ " ቤሊንግሀም

እንግሊዝ ሰርቢያን ባሸነፈችበት ጨዋታ ብቸኛ የማሸነፊያ ግቧን ያስቆጠረው ጁድ ቤሊንግሀም ከሀገሩ ጋር ዋንጫውን ማሸነፍ እንደሚፈልግ ተናግሯል።

" በሚቀጥሉት ጨዋታዎችም ለቡድኑ ያለኝን ሁሉ ለመስጠት ዝግጁ ነኝ " ያለው ቤሊንግሀም ከሀገሬ ጋር የአውሮፓ ዋንጫውን ማሸነፍ እፈልጋለሁ ብሏል።

ጁድ ቤሊንግሀም በዘንድሮው የውድድር አመት ለክለቡ ሀገሩ ባደረጋቸው ጨዋታዎች አስራ አምስት ጊዜ የጨዋታው ኮከብ ተጨዋች ተብሎ መመረጥ ችሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" በእንግሊዝ መሸነፍ አይገባንም ነበር "

የሰርቢያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ድራጋን ስቶኮቪች ቡድናቸው በምሽቱ ጨዋታ ካሳየው እንቅስቃሴ አንፃር በእንግሊዝ መሸነፍ እንደማይገባው ተናግረዋል።

አሰልጣኙ በንግግራቸውም " ጨዋታው በጣም ጥሩ ነበር እንግሊዝ ጠንካራ ቡድን ነው ፣ እኛ ድፍረት የታከለበት ጨዋታ አድርገናል የፈለግነው እግርኳስ ተጫውተናል።

በምንፈልገው መንገድ ተጫውተን እንግሊዝ እንድትከላከል አድርገናል ባደረግነው ነገር ደስተኛ ነኝ መሸነፍ አይገባንም ነበር በውጤቱ ደስተኛ አይደለሁም።"ሲሉ ተደምጠዋል።

አሰልጣኙ አያይዘውም ዱሳን ታዲችን ተጠባባቂ አድርገው ያስጀመሩት በታክቲካል ውሳኔ መሆኑን ያስረዱ ሲሆን ቀይረው ያስገቡትም ለታክቲክ መሆኑን ገልጸዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
" ቤሊንግሀም ትልቅ ክብር ይገባዋል " ሀሪ ኬን

የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አምበል ሀሪ ኬን ትላንት ምሽት የብሔራዊ ቡድኑን የማሸነፊያ ግብ ያስቆጠረው ጁድ ቤሊንግሀም ትልቅ ክብር እንደሚገባው ተናግሯል።

" እሱ የተለየ ተጨዋች ነው እያገኘ የሚገኘው አድናቆት ሁሉ ይገባዋል " ሲል የተናገረው ሀሪ ኬን እሱ የሚጫወትበት መንገድ ፣ ያለው በራስ መተማመንና በጨዋታ ላይ ያለው ተፅዕኖ አስደናቂ ነው ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
የአልባንያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ክስ ቀርቦበታል !

የአውሮፓ እግርኳስ ማህበር አልባንያ ከጣልያን ጋር ባደረገችው ጨዋታ የተፈጠሩ ክስተቶችን ተከትሎ የአልባንያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ላይ ክስ መክፈቱን አስታውቋል።

ዩኤፋ ክሱን ያቀረበው በጨዋታው የአልባንያ ደጋፊዎች እግርኳስን የማይመጥኑ መልዕክቶች እና የተለያዩ ቡድኖችን የሚደግፉ አርማዎች አሳይተዋል በሚል መሆኑ ተገልጿል።

በተጨማሪም ደጋፊዎቹ በስታዲየሙ ተቀጣጣይ ርችቶች መጠቀማቸው እንዲሁም ቁሳቁሶችን መወርወራቸው ተዘግቧል።

አልባኒያ በቀጣይ ከአውሮፓ እግርኳስ ማህበር ዲሲፕሊን ኮሚቴ ቅጣት ሊጠብቃት እንደሚችል ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ሳዲዮ ማኔ በግብርና ዘርፍ ሊሰማራ ነው !

ሴኔጋላዊው የአል ናስር ተጨዋች ሳዲዮ ማኔ በቀጣይ ሀገሩ በምግብ ራሷን ለመቻል የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ከስፖርቱ በተጨማሪ በግብርናው ዘርፍ ተሰማርቶ ለመስራት ማቀዱን ገልጿል።

የቀድሞ የሊቨርፑል ተጨዋች ሳዲዮ ማኔ በዘርፉ ለመሰማራት የወሰነው ከቀናት በፊት ከሴኔጋል ጠቅላይ ሚኒስቴር ኦስማን ሶንኮ ጋር ከተነጋገረ በኋላ ነው።

የሴኔጋል ጠቅላይ ሚኒስቴር ኦስማን ሶንኮ ሀገሪቱ በምግብ ራሷን እንድትችል እና የምግብ ዋጋ ንረት እንዲቀንስ ከማኔ በተጨማሪ ሌሎች ሴኔጋላዊያን በዘርፉ ከተሰማሩ መንግስታቸው ልዩ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

ሳዲዮ ማኔ ከዚህ በፊት በሀገሩ ሴኔጋል ሆስፒታል ፣ ትምህርት ቤቶች እና ሌሎች መሰረታዊ ነገሮችን ለማህበረሰቡ ሰርቶ ማስረከብ ችሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሰርጅዮ ራሞስ ከሲቪያ ጋር ተለያየ !

ስፔናዊው የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ሰርጅዮ ራሞስ ከላሊጋው ክለብ ሲቪያ ጋር ከአንድ የውድድር ዘመን ቆይታ በኋላ መለያየቱ ይፋ ተደርጓል።

የ 38ዓመቱ የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ሰርጅዮ ራሞስ ባለፈው ክረምት የተጨዋቾች የዝውውር መስኮት በአንድ አመት ውል የቀድሞ ክለቡ ሲቪያን መቀላቀሉ አይዘነጋም።

የቀድሞ የሪያል ማድሪድ ተጨዋች ሰርጅዮ ራሞስ በቀጣይ በነፃ ዝውውር አዲስ ክለብ የሚቀላቀል ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
ሽመልስ በቀለ 1⃣8⃣ ገስት ሀውስ

በውቢቷ ሀዋሳ ቆይታዎ የት ለማረፍ አስበዋል ? ንፁህ እና በደንበኞቻችን ተወዳጅ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን መጥተው የእረፍት ጊዜውን ያሳልፉ።

እንግዶቻችንን ተቀበልን ለእይታ ሳቢ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን ማስተናገድ ከጀመርን አመታትን አስቆጥረናል።

አድራሻችን :- ሀዋሳ አርቴፍሻል ስታዲየም መንገድ ላይ ያገኙናል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለትዕዛዝዎ ይደውሉልን :- 0928684848

#ShemelesBekele18
2024/10/05 17:35:52
Back to Top
HTML Embed Code: