Telegram Web Link
የቤተክርስቲያን አባቶች እንዲህ ይላሉ
“ኢትዮጵያ ሥጋችን ቤተ ክርስቲያን ነፍሳችን ናት፤ ነፍስ እና ሥጋ ደግሞ አንድ ነው፡፡ አገር ያለሃይማኖት፣ ሃይማኖት ያለአገር የለም፤ ኢትዮጵያን ያህል አገር ማጣት እግዚአብሔርን ከሚያህል ጌታ መለየት ሞት ነው፡፡ ሃይማኖትን እና ነጻነትን ማጣት ሽንፈት ነው፤ ስለ አገር፣ ሃይማኖት እና ነጻነት መሞት ደግሞ ክብር ነው፡፡”

በአባቶቻችን ዘመን የተነገረላት "

ኢትዮጵያ ታበፅ እደዊሁ ሃበ እግዚአብሔር" እንኳንስ የሰው ቀርቶ የእንጨት ጠማማ እንኳ አይገኝብሽም ያልክላት ዘመን መቼ ነው? ለምለም የነበረች ምድር የደም ምድር ሆናለች! እንግዲህ ደግ ሰው አልቋልና አድነን! ለኢትዮጵያም ዘንበል በልላት🙏
አሜን አሜን አሜን

@ortodoxtewahedo
★ ድራማው አልተሳካም ★

★ ሐሰተኛው ነቢይ ኢዩ ጩፋ ሀሰተኛነቱን ማጭበርበሩን ድራማውን በይፋ እያሳየ ነው።★
ከአሰላ ከተማ የመጣው መነኩሴ ነኝ ያለው አጭበርባሪ የውሸት መነኩሴ የለየለት ወመኔ፣የቤተክርስቲያን ጥልቅ ትምህርትና በቂ የአገልግሎት ሙያ የሌለው ወገበ ነጭ ቤተክርስቲያንን ለማሰደብ ቆብና ቀሚስ ከገበያ ገዝቶ ተመሳስሎ የገባ ተኩላ፣ የምንኩስና የቅድስና ሕይወት የሌለው አለሌ መሆኑ ተረጋግጧል።

ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶን ለማስነቀፍና የቅድስት ቤተክርስቲያንን አማኞች ለሐሰተኛ ነቢያት ለመገበር የአጋንንት ማደሪያ ከሆነው ከአጭበርባሪው ኢዩ ጩፋ ጋር ተመሳጥረው ይህንን ቀሽም ድራማ ለመስራት ቢንፈራገጡም የቤተክርስቲያን አምላክ በአጭር ሰዓት ውስጥ ድንቁርናቸውን ለሕዝብ ገልጦባቸዋል።

ኦርቶዶክሳውያን በጣም አስተውሉ፣የጠመጠመ ሁሉ ቄስ፣ቆብ የደፋ ሁሉ መነኩሴ፣የአገልግሎት ቀሚስ የለበሰ ሁሉ ሰባኪ አይደለም ብዙ አስመሳይ፣አጭበርባሪ፣ወንበዴ፣አጽራረ ቤተክርስቲያን አሉና ተጠንቀቁ !!

ከዚህ በፊት በአዲስ አበባ ጦርኃይሎች ሙሉ ወንጌል አዳራሽ ውስጥ ፓስተሮቹ ሕዝብን ለማጨበርበር ጳጳስ ነበርኩ ስሜም አቡነ ያሬድ ይባላል ብሎ አንዱን የእነርሱ ቢጤ የልብ እውር መድረክ ላይ አቁመው ሲዘሉ ቢውሉም እግዚአብሔር በአጭር ቀን ውስጥ ለምዳቸውን ገፎ በኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉ ፊት ውሸታምነታቸውን አጋልጧቸዋል።« የተኩላው ለምድ ሲገፈፍ» በሚለው የመምህር ዘበነ ስብከት ላይ ሙሉ ቪዲዮውን ታገኙታላችሁ። አሁንም ተመሳሳይ ድራማ መስራታቸው አዕምሯቸው የማይነቃ በድንዛዜ መንፈስ የደነቆሩ የአጋንንት ማደሪዎች መሆናቸውን ማሳያ ነው።

ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እውነተኛ መነኮሳት በጾም፣በጸሎት፣በስግደት፣በማይቋረጥ ስብሐተ እግዚአብሔር ሌሊትና ቀን በየገዳማቱና በየአድባራቱ በገድል በትሩፋት ጸንተው የሚታገሉባት እውነተኛ የክርስቶስ መቅደስ ነች።

ለሌሎችም ሼር አድርጉት

@ortodoxtewahedo
ሀሰተኛ ነብያት ያለ ድራማ መኖር አትችሉም ማለት ነው?

ድሮሮሮሮሮ የቀረ ሙድ ምናለ ቢቀርባችሁ? በድራማ የከበረ የሚከብር ጌታ የለምኮ

@ortodoxtewahedo
#ደጉ እና ሩሩህ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ወርሀዊ በዓል እንኳን አደረሳቹ።

"ቅዱስ ሚካኤል ኾይ"

እንደ ፀሐይ ሥነ ጸዳል የሚያንጸባርቁ በሰማይ ላይ ለሚንበለበሉ አክናፎችኽ ሰላም እላለኹ

የእግዚአብሔር ልዩ መልእክተኛ ሚካኤል ኾይ ከላይ ከሰማይ ተመልክተኽ በምትመጣበት ጊዜ ኹሉ በሲዖል የሚኖሩ ግዞተኞች ሚካኤል ኾይ መጣኽልን ደረስክልን እያሉ ደስታቸውን ይገልጻሉ።"

#መልክአ ቅዱስ ሚካኤል

" የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።"

#መዝሙረ ዳዊት 34:7፤)

"በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፤ ሕዝብም ከሆነ ጀምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል፤ በዚያም ዘመን በመጽሐፉ ተጽፎ የተገኘው ሕዝብህ ሁሉ እያንዳንዱ ይድናል። "

#ትንቢተ ዳንኤል 12:1

" የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሀያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ፤ እነሆም፥ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፤ እኔም ከፋርስ ነገሥታት ጋር በዚያ ተውሁት። "

#ትንቢተ ዳንኤል 10:13

" ነገር ግን በእውነት ጽሑፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፤ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር ማንም የሚያጸናኝ የለም።
"
#ትንቢተ ዳንኤል 10:21፤)ዐ

"የመላእክት አለቃ ሚካኤል ግን ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ሥጋ ሲነጋገር። ጌታ ይገሥጽህ አለው እንጂ የስድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረም።"

#የይሁዳ መልእክት 1:9

✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞

@ortodoxtewahedo
አካፋው ሚካኤል (የሰማዕታት ቀን) በስድስት ኪሎ ሰማዕታት ሐውልት የአበባ ጉንጉን በማስቀመጥ ታስቧል ።

ማክሰኞ የካቲት 12 ቀን 2016 ዓ.ም በየካቲት12 ቀን 1929 የፋሺስት ጣልያን ወታደሮች በአዲስ አበባ ያደረሱት አስከፊ ጭፍጨፋ የሚታሰብበት የሰማዕታት ቀን በመታሰቢያ ሀውልቱ ዙሪያ ታስቧል።

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን እንዲሁም የተለያዩ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና የጀግኖች አርበኞች ቤተሰቦች ታድመዋል።

© ዘገባ አዲስ ማለዳ ; ፎቶ ኢፕድ

@ortodoxtewahedo
መፍትሔው ያለው #በቤተ ክህነት እጅ ነው!

የመነኩሴ ልብስ የለበሰው በፎቶው የሚታየው ጎረምሳ ነው።
የተኩላው_ቆዳ_በዐደባባይ_ተገፏል። ቀሪው ጉዳይ የሕግ አገልግሎት መምሪያው የቤት ሥራ ነው።
በዚህ ዘመን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ የተደቀኑ ብዙ ፈተናዎች አሉ።ከእነዚህም ፈተናዎች መካከል አንዱ አልባሳቷን መርካቶ ገዝቶ ማታለል ነው።
በቅርቡ ንዋያተ ቅድሳቱን ከመርካቶ ገዝተው በማጭበርበር የተደራጁ ግለሰቦችን በየሥፍራው እናያለን።
- ይህ አድገኛ አካሄድ በሃይማኖት ላሉትም ኾነ ላልጸኑት የመሰናክል ዓለት ሆኖባቸዋል።በምግባርና በሃይማኖትም ጸንተው ለሚኖሩት ማፈሪያ ሆናል።
የችግሩ፣መፍትሔው ያለው #በቤተ ክህነት እጅ ነው።
እንዴት ይህን ሕገ ወጥ አሠራሪ ሥርዓት የሚያስዝ የጠቅላይ ቤተ ክህነት #መምሪያ ጠፋ?በእርግጥ አውቆ የተኛ በቀሰቅሱት አይሰማማ ነው ። ችግሩ ብዙ ነው ችግሩንም መናገር በቤተ ክህነት ውስጥ ሌላ ችግር ነው ።
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንደ ሃይማኖታዊ ተቋም ርምጃ ብትወስድ በስሟ የሚሰራውን ይህን ሕገ ወጥ ተግባር ለማስቆም ይቻላታል።

@ortodoxtewahedo
አክተሩ
1ኛ ሸሚዝ አልቀየረም
2ኛ ፍሪዝ ነው ጸጉሩ መኖክሴ ፍሪዝ አያረግም
3ኛ የኦርቶዶክስ መምህር አይደለም
4ኛ ፓስተሩ ይህንን ድራማ ሲሰራ ከባድ ስህተት ሰርቶል።

በውሸት የሚነግስ ሴጣን እንጂ ጌታ የለም ።

“ የምናውቀውን እንናገራለን ያየነውንም እንመሰክራለን ።”
 
— ዮሐንስ 3፥11


@ortodoxtewahedo
2024/09/29 19:28:17
Back to Top
HTML Embed Code: