Telegram Web Link
የለቡ መርጡለ አርሴማ ወአቡነ አዳም ገዳም
ሕንጻ ቤተመቅደስ በቅዱስ ፓትርያርኩ ተባርኮ
መንፈሳዊ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

የካቲት ፱ ቀን ፳፻፲ወ፮ ዓ/ም አዲስ አበባ

በአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሥር መጋቤ ሀብታት ስማቸው ከበደ እና ወለተሃና የተባሉ በጎ አድራጊ ምእመናን በ ወራት ጊዜ ውስጥ የታነጸውና ውብ በሆነ መንገድ ግንባታው የተጠናቀቀው የለቡ መርጡለ አርሴማ ወአቡነ አዳም ገዳም ሕንጻ ቤተመቅደስ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ጸሎት ተባርኮ መንፈሳዊ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

ለረዥም ዓመታት በአነስተኛ የቆርቆሮ መቅደስ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውን የገዳሙን ሕንጻ በአዲስና ባማረ መልኩ እንዲሠራ መልአከ ጽዮን አባ እስጢፋኖስ ይርጋ የለቡ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት አርሴማ የሁለቱ አጥቢያዎች ዋና አስተዳዳሪ ከላይ የተገለጹትን የመነንፈስ ልጆቻቸውን በማሳሰብ እንዳሳነጹ በዕለቱ በቀረበው ሪፖርት ተገልጿል። በገዳሙ ያለው ጸበል ለበርካታ ምእመናን እና የሌላ ሃይማኖት ተከታዮች የፈውስ ቦታ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።

በቡራኬ ሥርዓቱ ላይ ቅዱስነታቸውን በመከተል ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤ ዋና ሥራ አስኪያጅ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እንጦንስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌና የምሥራቅ ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊና መተከል አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስየዳውሮ-ኮንታ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ሊቀ አእላፍ በላይ መኮንን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች እንዲሁም በርካታ ቁጥር ያላቸው ምእመናን ተገኝተዋል።

@ortodoxtewahedo
አቶ ስማቸው ከበደ ያሰሩት ቤተክርስቲያን እየተመረቀ ነው

አቶ ስማቸው ከበደ ይባላሉ የኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ባለቤት ሲሆኑ ከእዚህ በፊት በተለያዩ በጎ አድራጎት ስራዎች ላይ እና በተለያዩ ሀገራዊ ልማቶች ላይ በመሳተፍ ይታወቃሉ።

አሁን ደግሞ በዛሬው ዕለት የካቲት 9/2016 ዓ/ም ቅዱስ ፓትርያርኩ እና በርካታ ምዕመናን በተገኘበት የለቡ መርጡለ ቅድስት አርሴማ ወአቡነ አዳም ገዳምን ከ 100,000,000 (ከመቶ ሚሊየን ብር ) በላይ በመመደብ ገንብተው አጠናቀው በማስመረቅ ላይ እንደሚገኙ የኔታ ቲዩብ ማረጋገጥ ችሏል።

@ortodoxtewahedo
በአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሥር መጋቤ ሀብታት ስማቸው ከበደ እና ወለተሐና የተባሉ በጎ አድራጊ ምእመናን በወራት ጊዜ ውስጥ የታነጸውና ውብ በሆነ መንገድ ግንባታው የተጠናቀቀው የለቡ መርጡለ አርሴማ ወአቡነ አዳም ገዳም ሕንጻ ቤተመቅደስ ::

@ortodoxtewahedo
Forwarded from LikeBot
#ሰንበተ ክርስትያን

እሑድ ማለት"አሐደ" ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን ትርጉሙ የመጀመሪያ እንደማለት ነው። ይኽች ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ "ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን " በመባል ትታወቃለች።

ዮሐንስም በራዕዩ "የጌታ ቀን" ያላት ናት
(ራዕይ 1፥10)

ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ "ዕለተ እግዚአብሔር" የሚላት ዕለተ እሑድ ናት።

መልካም ዕለተ ሰንበት ይኹንልን

#መልካም ቀን

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
ወእንዘ ትፈትል ወርቀ ወሜላተ
አስተርአያ ገብርኤል ግብተ
(ሐርና ወርቁን ስትፈትል
ገብርኤል በድንገት ተገለጠላት)

ቅዱስ ያሬድ

@ortodoxtewahedo
2024/09/29 17:40:43
Back to Top
HTML Embed Code: