Telegram Web Link
ፆመ ነነዌ  ከሰኞ - ዕሮብ (ከየካቲት 18 -20 )

የነነዌን ህዝብ ጸሎት የሰማ አምላክ የኢትዮጵያንም ህዝብ ልመና ለቅሶ ችግር ይሰማ ዘንድ ቅዱስ ፍቃዱ ይሁን አሜን፡፡

           ፆመ ነነዌ

ዮናስ ማለት 'ርግብ: የዋህ' ማለት ሲሆን ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ነው::በሰራፕታ ተወልዶ ያደገው ነቢዩ በልጅነቱ ታሞ ሙቶ ነበር:: ታላቁ ነቢይ ኤልያስ ግን 7 ጊዜ ጸሎት አድርጐ ከሞት አስነስቶታል::እናቱ የሰራፕታዋ መበለትም ደግ ሴት ነበረች::
    ቅዱስ ዮናስ በእድሜው ከፍ ሲል የቅዱስ ኤልያስ ደቀ መዝሙር ሆነ:: የነ ኤልሳዕና አብድዩም ባልንጀራ ነበረ:: ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስ ካረገ በሁዋላ: ቅ.ል.ክርስቶስ በ፰፻ ዓመት አካባቢ የነነዌ ሰዎች ኃጢአት ከመሥፈርቱ በማለፉ የእግዚአብሔር ቃል ወደ አማቴ ልጅ ወደ ዮናስ መጣ::

  ሒድና ለነነዌ ሰዎች ንስሃን ስበክላቸው" አለው:: ከነቢያት ወገን ከሙሴና ከዳዊት ቀጥሎ የዮናስን ያህል የዋህ ገራገር የለምና እንቢ አለ ሰምቶ ዝም አለ:: እግዚአብሔር እየደጋገመ ሲናገረው ግን "እንዲህ የሚዘበዝበኝ ከፊቱ ብቀመጥ አይደል!" ብሎ ወደ ተርሴስ ኮበለለ።
     ወገኖቼ አንድ ነገርን ልብ እንበል:: እንኩዋን ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዮናስ እኛ ክፉዎችም ከጌታ ፊት መሸሽ እንደማይቻል ጠንቅቀን እናውቃለን:: ታዲያ ለምን ሸሸ ቢሉ:- ጥበበ እግዚአብሔር በውስጡ ስለ ነበረበት ነው::

   ምክንያቱም ዮናስ በአሣ አንበሪ ሆድ 3 ቀን ሌሊት ኖሮ: ሙስና ጥፋት ሳያገኘው መውጣቱ ለጌታ ትንሳኤ ጥላ ምሳሌ ነው:: ለዚህም ምስክሩ ራሱ ጌታችን ነው:: "ወበከመ ነበረ ዮናስ ውስተ ከርሠ አንበሪ ሠሉሰ ዕለተ ወሠሉሰ ለያልየ: ከማሁ ይነብር ወልደ እጉዋለ እመ ሕያው ውስተ ልበ ምድር ሠሉሰ ዕለተ: ወሠሉሰ ለያልየ" እንዲል:: ማቴ. 12:39

   ቅዱስ ዮናስ በገንዘቡ ዋጅቶ ወደ መርከብ በገባ ጊዜ ታላቅ ማዕበል ሆነ:: የእምነት ሰው ነውና እንዲያ እየተናወጡ እርሱ በእርጋታ ተኝቷል:: እነርሱ ግን ቀስቅሰው ቢጠይቁት እጣ ወድቆበታልና የእኔ ጥፋት ስለ ሆነ ወደ ማዕበሉ ጣሉኝ" አላቸው::
     እያዘኑ ቢጥሉት ታላቅ ጸጥታ ሆነ:: እነዚያ አሕዛብም እግዚአብሔርን በመስዋዕትና በስዕለት አከበሩ:: ዮናስ ግን በማዕበልና በአሣ አንበሪ ሆድ ውስጥ ለ3 ቀናት ጸለየ:: አሣ አንበሪው በ3ኛው ቀን ወደ ነነዌ ተፋው::ቅዱሱም "እስከ ሠሉስ ዕለት ትትገፈታእ ነነዌ ዐባይ ሃገር" እያለ ንስሃን ሰበከ::

የነነዌ ሰዎች ኃጢአታቸውን አምነው ቢጸጸቱ ከሰማይ ወርዶ ከደመና ደርሶ የነበረው የእሳት ማዕበል ተመልሶላቸዋል::
    የነቢዩ ትንቢት ግን አልቀረምና ታላቁዋ ነነዌ ከ፫፻ ዓመታት በኃላ ጠፍታለች:: ቅዱስ ዮናስ ግን በቀሪ ዘመኑ ፈጣሪውን እያገለገለ ኑሯል:: ጠቅላላ እድሜውም 170 ዓመት ነው::

አምላከ ቅዱስ ዮናስ እድሜ ለንስሃ: ዘመን ለፍስሃ አይንሳን:: ከበረከቱም ይክፈለን::
በጾመ ነነዌ ስለ ሃገርና ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላምና አንድነት መጸለይ ይገባል::
  ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል:: ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም:: ዮናስ በአሣ አንበሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ: እንዲሁ የሰው ልጅ(ጌታችንን) በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል:: የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነስተው ይፈርዱበታል:: በዮናስ ስብከት ንስሃ ገብተዋልና:: እነሆም ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ::
                    ማቴ. 12:39
ለሀገራችን ሰላም ለምድራችንም በረከትን ያድልልን!!
       ወስብሐት ለእግዚአብሔር
        ወለ ወላዲቱ ድንግል
         ወለመስቀሉ ክብር

@ortodoxtewahedo
አራት የገዳም አባቶች ተገደሉ

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሚገኘው ጥታዊው የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም እራሱን ኦነግ ሸኔ ብሎ በሚጠራው ቡድን የገዳሙን መጋቢ ጨምሮ አራት አባቶችን መግደሉን ገዳሙ አስታውቋል፡፡
ሰኞ የካቲት 11 ቀን 2016 ዓመተ ምሕረት ታጣቂዎቹ ሦስት አባቶችን አግተው ወደ በረሃ ከወሰዱ በኋላ የታገቱትን ለማስለቀቅ ገዳሙ ጥረት በሚያርግበት ወቅት የካቲት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ተጨማሪ አባቶችን በመያዝ
1. የገዳሙ መጋቢ አባተክለማርያም ዐሥራት
2. የገዳሙ ጸሐፊ አባ ኪዳነ ማርያም ጥላሁን
3. የገዳሙ የመጽሐፍ መምህርና ቀዳሽ አባ ገ/ማርያም አበበ
4. በአመክሮ የሚኖሩ መናኝ ኃይለማርያም የተባሉት የገዳሙ የሥራ ኃላፊዎች እንደተገደሉና አብረው ከነበሩት አንድ አባት ብቻ ማምለጥ መቻላቸውን እንደተረዱ የገዳሙ ኃላፊዎች ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) ገልጸዋል፡፡
የገዳሙ የሥራ ኃላፊዎች ቡድኑ ከዚህ ቀደም ገዳሙን በመዝረፍ ለከፋ ችግር አጋልጦት መቆየቱን አስታውሰው ገዳሜ ጸጥታውን የሚያስከብረበት መሣሪያች በቡድኑ በመወረሳቸው ለከፋ የጸጥታ ችግር መጋለጡን ገልጸዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት ገዳማውያ በስጋት ላይ መሆናቸውንና የመንግሥት የጸጥታ አካላትን እገዛ እንደሚሹ አስታውቀው መረጃውንም በየደረጃው ለሚገኙ የሀገረ ስብከቱና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ማሳወቃቸውን ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያና የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት EOTC TV በክሰተቱ ሕይወታቸው ላጡ ሰማዕታት አባቶች የተሰማውን ኃዘን ይገልጻል፡፡ ጉዳዩ አስመልክቶ ዝርዝር መረጃ እየተከታተለ የሚያቀርብ መሆኑን ያስታውቃል፡፡
EOTC TV

@ortodoxtewahedo
“…ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፥ እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው።”

ሮሜ 8፥36


@ortodoxtewahedo
ሰሞኑን በማኅበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ ስለሚገኘው "መነኩሴ "ነኝ ባይ ግለስብ በሀገረ ስብከቱ የማይታወቅ መሆኑን ሀገረ ስብገቱ ገለጸ።
የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰሞኑን በማኅበራዊ ድረ ገጾች ራሱን "መነኩሴ"በማስመሰልና በአርሲ ሀገረ ስብከት አገልጋይ እንደሆነ በመግለጽ የሚንቀሳቀሰውን ግለሰብ የማያውቀውና ሐሰተኛ "መነኩሴ" መሆኑን ለጠቅላይ ቤተክህነት በጻፈው ደብዳቤ አስታወቀ።
ከየካቲት 12 ቀን 20916 ዓ.ም ጀምሮ በማኀበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ የሚገኘው ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ተችቶ የማስተቸት ድራማዊ ትዕይንት ላይ የቀረበው አስመሳይ " መነኩሴ "ግለሰብ በሀገረ ስብከታችን በተለይ በአሰላ ከተማ በቅዳሴ መምህርነት በስብከተ ወንጌል እንዳገለ በማስመሰል በሰጠው የሀሰት ምስክርነትን በተመለከተ እውነተኛ ምላሽ መስጠት ማስፈለጉን የጠቀሰው ሀገረ ስብከቱ"መንኩሴ "መሳዩ ግለሱብ በሀገረ ስብከቱ በየተኛውም የከተማና የገጠር ገዳማትና አድባራት የማይታወቅና ምንም ዓይነት አገልግሎት ሲሰጥ ያልነበረ መሆኑን ገልጿል።
በተጨማሪ በሀገረ ስብከቱ የሚገኙት ሁሉንም አገልጋዮች የሚታወቁና የተመዘገቡ መሆኑን የጠቀሰው ሀገረ ስብከቱ ግለሰቡ በሀገረ ስብከቱ ካሉት አገልጋች መካከል የማይታወቅና ያልተመዘገበ ከመሆኑም በላይ ሀገረ ስብከቱ በፍጹም የማያውቀው ቀሳጢ ነው በማለት ሐሰተኛ ማንነትን በመላበስ የቤተክርስቲያንን ስም ለማጠልሸተ የተሰማራ መሆኑን ገልጿል።
ስለሆነም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ግለሰቡ የቤተ ክርስቲያናችንን ዓርማ ወይም አልባሳት በመልበስና የሀገረ ስብከታችንን መልካም ገጽታ በማጉደፉ ግለሰቡንና እዩ ጩፋ የተባለውን አጽራረ ቤተ ክርስቲያን በህግ እንዲጠይቅን ስንል በታላቅ አክብሮት እናሳስባለን፤በማለት ለጠቅላይ ጽሕፈት ቤቱ በጻፈው ደብዳቤ ጨምሮ ገልጿል።

ምንጭ: የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

@ortodoxtewahedo
ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪ አቀረበ!

ጥቁር ልብስ!!!

ጾመ ነነዌን ምክንያት በማድረግ ጥቁር ልብስ ብቻ በመልበስ በጾምና በጸሎት ምሕላ በመያዝ ከቤተ ክርስቲያን ዓውደ ምህረት በመገኘት ወደ እግዚአብሔር ጾም፣ ጸሎትና ምሕላ እንድታቀርቡ ሲል ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪ አስተላለፈ።

@ortodoxtewahedo
የውሸት ክህነቱን በአንደበቱ ያረጋገጠው ዱርዬ
***

ይህን ምስኪን የጩፋ ዘመዶች ለማሳመን ብሎ ዱርየው ባለቀሚስ ሲናገር አንድ ያላስተዋለው ነገር ከአፉ አምልጦታል።

ክህነት/ቅስናውን ከዬት እንዳገኘ ለማስረዳት ሲመልስ
ከባህር ዳር ሀገረስብከት ከነበሩት ከብጽኡ አቡነ ጴጥሮስ ከሚባሉ ሊቀ ጳጳስ ቅስና ተቀብያለው ይላል።

....ከእዛን ቀጠል አድርጎ ከአቡነ ጴጥሮስ የተቀበልኩት የቅስና ካርድ ስለጠፋ አዲስ አበባ ሀገረስብከት ሄጄ አቡነ ሳሙኤል ከሚባሉ ሊቀ ጳጳስ ይህን ካርድ(ቪዲዮው ላይ የሚያሳየውን ካርድ) ወስጃለው ብሎ ይተርካል።

ይህ ዱርዩ የዘነጋው አንድ ሃቅ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርዓት መሰረት ክህነት ያለው አንድ አካል የክህነት ካርዱ ቢጠፋበት ቀድሞ ክህነት ወደወሰደው ሀገረስብከት በመሄድ ቀድሞ ክህነት ከመውሰዱ በፊት ያመጣቸው ፋይሎች ተጣርተው ማስረጃ ወይም ድጋሚ የክህነት መታወቂያ ካርድ ይሰጠዋል እንጅ ክህነት ካልወሰደበት ሀገረስብከት አይወስድም።

ምክንያቱም ክህነት ያልሰጠው ሀገረስብከት ስለሰውዬው የክህነት ማረጋገጫነት አንዳች ፋይል የለውም።

ቀድሞ ክህነት ያልወሰደበት ሀገረስብከት ይህ ሰው ካህን ይሁን ቦዘኔ የትኛውን ፋይሉን አጣርቶ ነው ድጋሚ የክህነት ካርድ የሚሰጠው ?

በአጭር አማረኛ በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ የተመረቀ መሃንዲስ ዲግሪው ስለጠፋ አርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ አመልክቶ የትምህርት ማስረጃውን ወሰደ እንደማለት ነው።

ቀሽም ተውኔት።

ለማንኛውም መኖክሴ ከቅድስት ቤተክርስቲያን ሲመ*Fiq አዲስ አይደለም። ነገር ግን በውሸት ቄስ ነኝ መኖክሴ ነኝ ብሎ መጋጋጥ ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው?

የመነfeq ሰው ምዕመን ይሁን ፓትርያሪክ በየትኛውም መመዘኛ ውሃ አያነሳም። የሁለቱም መጥፋት ስያሜው ክህደት ይባላል።

ይህ ሰው ክህነት አልባ የሆነ ሞላጫ ዱርዬ መሆኑ የምታረጋግጥበት "ከማርያም ጋር እኔን እኩል ነኝ ፣መላእክት ምንም አያውቁም፣" ማርያም እንዴት የህይወት መብልን ያገኘንባት ትባላለች?" ገለመሌ እያለ እንኳን ለኦርቶዶክስ ለቃለህይወት እና መካነኢየሱስ አማኝ እራሱ የሚሰቀጥጥ ንግግር ሲያበዛ ነበር።

እንግዲህ ጩፊዝም እንዲለመልም ውሸት ማደባሪያ ናት

Kune Demelash kassaye -Arba Minch

@ortodoxtewahedo
በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።
ከሄድሁ በኋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ፥ ደቀ መዛሙርትንም ወደ ኋላቸው ይስቡ ዘንድ ጠማማ ነገርን የሚናገሩ ሰዎች በመካከላችሁ እንዲነሡ እኔ አውቃለሁ።

ሐዋርያት 20 : 28-30
✞ኪዳነምህረት እመቤት✞
♡የመዝሙር ግጥሞች♡
✞ኪዳነምህረት እመቤት✞

ኪዳነ ምህረት እመቤት እመቤት(፪)
ነይልን ነይልን ካለንበት (፪)

ከሰማያት በላይ /ካለው ከማደሪያሽ/(፪)
ዝማሬ ከሞላው ከዘላለም ቤትሽ
የምድር ፍጥረታት /ማርያም ማርያም ሲሉሽ/(፪)
የቃል እናት እመቤቴ /ነይ በሰረገላሽ/(፪)
       አዝ= = = = =
ከጸጥታ ወደብ /ከፍቅር አውድማ/(፪)
ከሰላሙ መንደር ከእውነት ከተማ
ሰዐሊ ለነ ቅድስት /ውዳሴሽ ሲሰማ/(፪)
ከሚካኤል ከገብርኤል ጋር /ነይልን ከራማ/(፪)
       አዝ= = = = =
ዘርፋፋው ቀሚስሽ /ይውረድ ከሰማያት/(፪)
እንባችን ይታበስ ባንቺ አማላጅነት
የጽዮን ዝማሬ /ተሞላች ነፍሳቸን/(፪)
ንዒ ንዒ ንዒ እንበል /እንደ አባቶቻችን/(፪)
       አዝ= = = = =
ፍጥረታት ሊድኑ /በአማላጅነትሽ/(፪)
የዘላለም ኪዳን አማኑኤል ሰጠሽ
ትውልድ ይህን አምኖ /ብፅይት ይልሻል/(፪)
እናቴ መመኪያዬ /ምርኩዜ ሆነሻል/(፪)
       አዝ= = = = =
የልብን ሲያዋዩሽ /ሰምተሽ ዝም አትይም/(፪)
ችግረኛን አይቶ ልብሽ አይጨክንም
ከአይን ጥቅሻ /ፈጥነሽ ትደርሽለታለሽ/(፪)
ከሐዘን ከመከራ /ታሳርፊዋለሽ/(፪)

            መዝሙር
          ለምለም ከበደ

"ከመረጥሁት ጋር ቃል ኪዳኔን አደረግሁ"
                  መዝ፹፱፥፫

@ortodoxtewahedo
#እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የምህረት ቃል ኪዳን የተቀበለችበት አመታዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ ።

#እንጦጦ ሀመረ ኖህ ኪዳነ ምህረት ገዳም

በአዲስ አበባ ከተማ በስተሰሜን ምሥራቅ በጉለሌ ክፍለ ከተማ የምትገኝ ስመጥርና ታሪካዊ ገዳም ስትሆን በተራራ፣በሸለቆና በወንዞች የተከበበች በመሆኑዋ በተፈጥሮ አቀማመጧ አረንጓዴ የተላበሰች ናት፡፡ ይህም ለቤተክርስቲያኗ ውበትና ግርማ ሞገስ ከመስጠት አልፎ በሚያስደስት ፀጥታ የአዕዋፍ ዝማሬ ተሞልታ ጸጋን እንድትላበስ አድርጓታል፡፡
ይህች ቦታ የተቆረቆረችው በ484 ዓ/ም ሲሆን በ500 ዓ.ም በአባ ሊባኖስ የአንድነት ገዳም ሆና ተቋቋመች፡፡ አባ ሊባኖስ ወደ ሌላ መንፈሳዊ ተልእኮ ለመሄድ መነኮሳቱን ሲሰናበቱ እንዲህ የሚል ትንቢት ተናግረው ነበር ‹‹ልጆቼ ሆይ በሉ ይህችን ቅድስት ቦታ አደራ ሰጥቻችኋለሁ በኋላ ዘመን ታላቅ ቦታ ትሆናለች' አጋንንት ይወገዱባታል' የብዙ ቅዱሳን አፅም ያርፍባታል' ነገስታት ጳጳሳት ይሰግዱባታል' ብዙ መናንያን መጠጊያ ያደርጋታል ቤተ መቅደሷም በወርቅ በብር ተጊጣ ትታነጻለች የአንድነቱም ገዳም ተሻሽሎ ይቋቋምባታል››፡፡ በ9ኛ መቶ ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት የአክሱም ጽዮንን ቤተ መቅደስ ለማቃጠል ስትነሳ ንጉሡ አንበሣ ውድም ታቦተጽዮንን በምሥጢር በማስያዝ ወደ ሸዋ መጥተው በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነምሕረት ገዳም ታቦተ ጽዮንን አሳድረው ወደ ዝዋይ ደሴት ሲሄዱ ለገዳሟ ንዋየ ቅድሰት ስጦታ አበርክተዋል ጸበሏን ተጠምቀው ቦታውን መርቀው ሄደዋል፡፡
በ12ኛው መቶ ክ/ዘመን ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከንጉሥ ላሊበላ ጋር ወደ ዝቋላ አምባ ሲመጡ በዚህች ገዳም በእንግድነት አድረው በጸበሏ ተጠምቀው ቦታውን ባርከዋል፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስም ለመነኮሳቱ እንዲህ ብለው ነበር ‹‹ይህች ገዳም ታላቅ ስመጥር ገዳም ትሆናለች ከእርሷ በታች የሚታየው ጫካና ዱር መናገሻ ከተማ ይሆናል፡፡››
አፄ ዘርዓ ያዕቆብም ወደዚህች ገዳም መጥተው አቀማመጧንና የጸበሏን ፈዋሽነት ተመልክተዋል ‹‹ዳሯ እሳት መሐሏ ገነት ይሁን›› ብለው ብዙ ስጦታ አበርክተዋል፡፡ አፄ ልብነ ድንግልም ወደ ገዳሟ መጥተው ተማህጽኖ አድርገው በጸበሏ ተጠምቀው ታቦተ ልደታንና ብዙ ንዋየቅድሳት ሰጥተው ሄደዋል፡፡ በንግስት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት ይህች ገዳም ሐመረ ኖኅ ኪዳነምህረት ገዳም ተብላ ተሰይማለች፡፡
ይህች ቦታ እንደተነገረላት ትንቢት ብዙ ቅዱሳንና ነገሥታት መጥተው የሰገዱባት የባረኳት' ጸበሏ የአጋንንት ድል መንሻ' የብዙ መነኮሳት መጠጊያ 'የህሙማን መፈወሻ' የእመቤታችንን ቃል ኪዳን ለማግኘት ብዙን ጊዜ ለሱባኤ ከሚመረጡ ቦታዎች አንዷ ናት፡፡ ይህች ደብር በ1957 ዓ/ም የተመሠረተ ሰንበት ት/ቤት ሲኖራት በ1984 ዓ/ም በብፁዓን ጳጳሳት ‹‹መርሶ ሕይወት›› /የሕይወት ወደብ/ የሚለውን ስያሜ አግኝቷል፡፡ የገዳሟ ስያሜ ሐመረ ኖኅ ( የኖኅ መርከብ ) እንደሆነ ሁሉ መርሶ ሕይወት ( የሕይወት ወደብ ) በመባሉ ሁለቱ ተዛማችነት አላቸው ፡፡ ይህ ሰንበት ት/ቤት ለየት የሚያደርገው በግል መኖሪያ ቤት በጋሞኛ ቋንቋ ይሰጥ የነበረውን ትምህርት ከ1986 ጀምሮ በሰ/ት/ቤቱ ስር በማቀፍ የወንጌል ትምህርቱን ከመማር ባሻገር ለጋሞ ሕዝብ መንፈሳዊ እንቅስቃሴን በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
አዘጋጅ፡- እህተ ማርያም (በሰ/ት/ቤታችን ሰሌዳ መጽሔት ቀርቦ የነበረ)

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለዘለአለም ትኑር!!!

ሰው ሁሉ ለመናገር የዘገየ ለመስማት የፈጠነ ይሁን !
(ያዕቆብ 1፥19)

< ወስብሐት ለእግዚአብሔር

@ortodoxtewahedo
2024/09/29 21:30:58
Back to Top
HTML Embed Code: