Telegram Web Link
#ሚያዝያ_2
#አንድ_አምላክ_በሆነ_በአብ_በወልድ_በመንፈስ_ቅዱስ_ስም
ሚያዝያ ሁለት በዚህችም ቀን የቃይናን ልጅ #የቅዱስ_መላልኤል የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው፣ ፊቱ እንደ ውሻ የሆነ #ቅዱስ_ክርስትፎሮስ በሰማዕትነት አረፈ፣ የሐሊባ ሃገር ሰው የከበረ አባት #ስምዖን ዕረፍቱ እነረደሆነ ስንክሳር በስም ይጠቅሰዋል።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_መላልኤል

ሚያዝያ ሁለት በዚህችም ቀን የቃይናን ልጅ የመላልኤል የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው፡፡ መላልኤልም መቶ ስልሳ አምስት ዓመት ኖረ ያሬድንም ወለደው።

መላልኤልም ያሬድን ከወለደው በኃላ ሰባት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ። የመላልኤልም መላ ዘመኑ ሁሉ ስምንት መቶ ዘጠና አምስት ዓመት ነው። ቅዱስ መላልኤልም ሚያዝያ ሁለት ቀን በእሑድ ዕለት ሞተ በማከማቻም ውስጥ ቀበሩት።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ክርስቶፎሮስ (ሐዋርያና ሰማዕት)

በዚችም ቀን ፊቱ እንደ ውሻ የሆነ ቅዱስ ክርስትፎሮስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ቅዱስ ሰውን ይበሉ ከነበሩ ሰዎች ሀገር ነው በጦርነትም ማረኩት አባቱም በሐዋርያ ማትያስ እጅ ያመነ ነው። በማረኩትም ጊዜ ቋንቋቸውን አያውቅም ነበር የክብር ባለቤት ወደሆነ እግዚአብሔርም ማለደ ቋንቋቸውንም ገልጦለት እንደርሳቸው ተነሰገረ የክርስቲያን ወገኖችን የሚያሠቃዩአቸውንም ገሠጻቸው የጦር ሠራዊቱንም የሚመራ መኰንን ጽንዕ ግርፋትን ገረፈው። ቅዱስ ክርትፎሮስም መኰንኑን የጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ትእዛዙ ኃይሌን ባትይዘኝና ባታስታግሠኝ አንተና ሠራዊትህ ከእኔ እጅ ባልዳናችሁ ነበር አለው።

መኰንኑም ስለ ርሱ ወደ ንጉሥ ላከ ከእርሱ የሆነውንም ነገረው። ንጉሡም ወደ ርሱ እንዲያመጡት ሁለት መቶ ወታደሮችን ላከለት እርሱም ያለ መፍራት ያለ ማፈግፈግ አብሮአቸው ሔደ። በእጁ በትር ነበረች በላይዋ በጸለየ ጊዜ በቀለችና አበበች። እነዚያ ወታደሮች ተርበው የሚበሉት እንጀራ በአጡ ጊዜ ቅዱስ ክርስትፎሮስ ጸለየ በእነርሱ ዘንድ እንጀራ በዝቶ ተትረፈረፈ እጅግም አድንቀው በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። አባ ጳውሎስ እጅ የክርስትና ጥምቀትን ተጠመቁ።

ወደ ንጉሡም ፊት በደረሱ ጊዜ ንጉስ ዳኬዎስ ሊያስፈራውና ሊሸነግለው ጀመረ ደግሞ እጅግ መልከ መልካም የሆኑ ሁለት አመንዝራ ሴቶችን ወደርሱ ሰደደ እነርሳቸው እንደሚያስቱትና በኀጢአት እንደሚጥሉት አስቧልና። እርሱ ግን ገሠጻቸው አስተማራቸውም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በደማቸው ምስክር ሁኑ። እንዲሁም እነዚያ ሁለት መቶ ወታደሮች በንጉሡ ፊት በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ ራሶቻቸውንም በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማዕትነትንም በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ።

ቅዱስ ክርስትፎሮስም ንጉሡን አንተ የሰይጣንን ሥራ የምትቀበል ማደሪያው የሆንክ ብሎ ዘለፈው ንጉሡም ተቆጥቶ በትልቅ ብረት ምጣድ ውስጥ እንዲጨምሩትና ከበታቹ እሳትን እንዲያነዱ አዘዘ። እንዲሁም አደረጉበት ነገር ግን ከጉዳት እንዳሰቡት ምንም የደረሰበት የለም። ጤነኛ ሆኖ ሰዎችን አስተማራቸው እንጂ።እጅግም አድንቀው በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ። ቅድሱንም ከእርሷ ሊአወጡት ወደዚያች ብረት ምጣድ ቀረቡ ንጉሡም አንገቶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጧቸው አዘዘ የሕይወት አክሊልንም ተቀበሉ። ከዚያም በኃላ ታላቅ ደንጊያ በአንገቱ አንጠልጥለው ከጥልቅ ጉደረጓድ እንዲጨምሩት ንጉሡ አዘዘ በጨመሩትም ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ በጤንነት አወጣው። ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ አንገቱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ ንጉሡ አዘዘ። ቅዱሱም በእግዚአብሔር መንግስት የድል አድራጊነትን አክሊል ተቀዳጀ፡፡

ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡

#ሚያዝያ_1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፣
1, ቅዱስ ክርስቶፎሮስ (ሐዋርያና ሰማዕት)
2, አባ ስምዖን ዘሃገረ ሐሊባ
3, ቅዱስ መላልኤል (የያሬድ አባት - ከአዳም ፭ኛ ትውልድ)
4, እግዚአብሔር ፀሐይን፣ ጨረቃን፣ ከዋክብትን ፈጠረ

#ወርኃዊ_በዓላት
1, ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
2, ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ
3, ቅዱስ ኢዮብ ጻድቅ ተአጋሲ
4, ቅዱስ አቤል ጻድቅ
5, ቅዱስ አባ ጳውሊ ገዳማዊ (ታላቁ)
6, ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ
7, አባ ሕርያቆስ ዘሃገረ ብሕንሳ

ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ። ልባሞች እንደ መሆናችሁ እላለሁ፤ በምለው ነገር እናንተ ፍረዱ። የምንባርከው የበረከት ጽዋ ከክርስቶስ ደም ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን? የምንቆርሰውስ እንጀራ ከክርስቶስ ሥጋ ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን? አንድ እንጀራ ስለ ሆነ፥ እኛ ብዙዎች ስንሆን አንድ ሥጋ ነን፤ ሁላችን ያን አንዱን እንጀራ እንካፈላለንና። 1ኛ ቆሮንቶስ 10÷14—18

ወስብሐት ለእግዚአብሔር✝️
ቅዱስ መላልኤል ያሬድ በስንት ዓመቱ ወለደው?
Anonymous Quiz
48%
በ165 ዓመቱ
16%
በ158 ዓመቱ
16%
በ166 ዓመቱ
20%
በ100 ዓመቱ
በእግዚአብሔር ኃይል ግመልን በመርፌ ቀዳዳ ያሾለከ ሐዋርያ ማን ይባላል?
Anonymous Quiz
16%
ሐዋርያው ማትያስ
29%
ሐዋርያው በርተለሜዎስ
42%
ሐዋርያው ታዴዎስ
13%
ሐዋርያው ፊልጶስ
Audio
"" የመጨረሻዋ ሰዓት "" (፩ዮሐ. ፪:፲፰)

"ነገረ ምጽአት"

(መጋቢት 29 - 2016)

ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
🛑በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

🛑በቴሌግራም👉
https://www.tg-me.com/zikirekdusn
#ሚያዝያ_2_ቀን_የዕለቱን_ወንጌል_እናንብብ📖👇
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ማቴዎስ 15
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²¹ ኢየሱስም ከዚያ ወጥቶ ወደ ጢሮስና ወደ ሲዶና አገር ሄደ።
²² እነሆም፥ ከነናዊት ሴት ከዚያ አገር ወጥታ፦ ጌታ ሆይ፥ የዳዊት ልጅ፥ ማረኝ፤ ልጄን ጋኔን ክፉኛ ይዞአታል ብላ ጮኸች።
²³ እርሱ ግን አንዳች አልመለሰላትም። ደቀ መዛሙርቱም ቀርበው፦ በኋላችን ትጮኻለችና አሰናብታት እያሉ ለመኑት።
²⁴ እርሱም መልሶ፦ ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላክሁም አለ።
²⁵ እርስዋ ግን መጥታ፦ ጌታ ሆይ፥ እርዳኝ እያለች ሰገደችለት።
²⁶ እርሱ ግን መልሶ፦ የልጆችን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባም አለ።
²⁷ እርስዋም፦ አዎን ጌታ ሆይ፤ ቡችሎችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ አለች።
²⁸ በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ፦ አንቺ ሴት፥ እምነትሽ ታላቅ ነው፤ እንደወደድሽ ይሁንልሽ አላት። ልጅዋም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ዳነች።
²⁹ ኢየሱስም ከዚያ አልፎ ወደ ገሊላ ባሕር አጠገብ መጣ፥ ወደ ተራራም ወጥቶ በዚያ ተቀመጠ።
✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️ #ሚያዝያ_2_ቀን #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወዓመቲከኒ ዘኢየኀልቅ። ደቂቀ አግብርቲከ ይነብርዋ። ወዘርዖሙኒ ለዓለም ይጸንዕ"። መዝ 101፥27-28። በቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡት መልዕክታት  ሮሜ 11፥13-25፣ ያዕ 3፥1-13 እና የሐዋ ሥራ 14፥11-19። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 15፥21-29። #የሚቀደሰው_ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው።መልካም የጾም ጊዜና በዓል። በሁላችንም ይሁንልን።
Audio
AudioLab
Converted 11.5 mb
"" የመጨረሻዋ ሰዓት "" (፩ዮሐ. ፪:፲፰)

"ነገረ ምጽአት"

(መጋቢት 29 - 2016)

ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
🛑በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

🛑በቴሌግራም👉
https://www.tg-me.com/zikirekdusn
#ሚያዝያ_3
#አንድ_አምላክ_በሆነ_በአብ_በወልድ_በመንፈስ_ቅዱስ_ስም
ሚያዝያ ሦስት በዚች ቀን የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ የከበረ አባት #አባ_ዮሐንስ አረፈ፣ የከበረ አባት በእስክንድርያ ለተሾሙ አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ አንደኛ የሆነ #አባ_ሚካኤል አረፈ፣ ክርስቲያናዊ ነጋዴ #ቅዱስ_መርቄ አረፈ፣ በተጨመሪም #እግዚአብሔር በእግር የሚራመዱ በክንፍ የሚበሩና በልብ የሚሳቡ በየብስ የሚኖሩ ፍጥረታትን ፈጠረ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_ዮሐንስ

ሚያዝያ ሦስት በዚች ቀን የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ የከበረ አባት አባ ዮሐንስ አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ የኦሪት ምሁራን የሆኑ አዋቂዎች ነበሩ የኦሪትን ሕግ ትምህርቶችንም እያስተማሩት አሳደጉት።

ክርስቲያኖችን በጸና ልቡና የሚከራከራቸውና የሚጣላቸው ነበር መጻሕፍትን አዘውትሮ ከመመርመሩ የተነሣ የ ክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ወደ ዓለም እንደመጣና ሰውም እንደሆነ በሞቱም ዓለምን እንደ አዳነ አመነ። እርሱም የ#ባሕርይ_አምላክ እንደሆነ አምኖ በኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ በአባ ዮስጦስ እጅ ተጠመቀ ዲቁናም ሾመው ከዚያም በኢየሩሳሌም ሀገር ኤጲስቆጶስነት ለመሾም እስቲገባው ድረስ በበጎ ስራና በዕውቀት አደገ።

ኤልያስ የሚባለው እንድርያኖስም በነገሠ ጊዜ ከኢየሩሳሌም ሀገር የፈረሰውን ሕንፃ ሁሉ እንዲያንፁና በስሙ ኤልያስ ተብሎ እንዲጠራ አዘዘ። ከዚህም በአይሁድ ምኲራብ ደጃፍ ላይ ታላቅ ግምብ ሠሩ ከከበረ ድንጊያም ሠሌዳ ሠርቶ በላዩም ስሙን ኤልያስን ጽፎ በመግቢያው አኖረው በዘመኑም ኢየሩሳሌም አሕዛብንና አይሁድን ተመላች ሠለጡኑባትም።

ክርስቲያኖችም ሊጸልዩ ወደ ጎልጎታ ሲመጡ በአዩአቸው ጊዜ አሕዛብ ይከለክሉአቸው ነበር በዚያ ዝሁራ በሚባል ኮከብ ስም መስጊድ ሠርተው ነበርና። ስለዚህም #ክርስቲያኖችን በዚያ እንዳያልፉ ይከለክሏቸው ነበር።
በዚህም አባት ላይ ከአሕዛብ ታላቅ መከራና በምድር ላይም ጐትተውታልና አጐሳቁለውታልና እርሱም ነፍሱን ወደርሱ ይቀበል ዘንድ የክብር ባለቤት #ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስን ለመነው ጌታም ልመናውን ሰምቶ በሰላም አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_ሚካኤል_ዘእስክንድርያ

በዚህችም ቀን ደግሞ የከበረ አባት በእስክንድርያ ለተሾሙ አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ አንደኛ የሆነ አባ ሚካኤል አረፈ። ይህ አባት ከታናሽነቱ ጀምሮ የምንኲስና ልብስ ሊለብስ ወደደ በአስቄጥስ ገዳም በአባ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን መንኲሶ እስከ ሸመገለ ድረስ በዚያ ኖረ።

በብዙ መነኰሳትም ላይ አበ ምኔት ሆኖ ተሾመ በዘመኑ ሁለየ መልካም ተጋድሎ በመጋደል #እግዚአብሔርን ደስ አሰኘው። በወንጌላዊው ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጵጵስና ለመሾም እስቲገባው ድረስ ፍጹም ተጋድሎ በመጋደል ደከመ።

ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ገብርኤል በአረፈ ጊዜ የወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር ያለ ሊቀ ጳጳሳት አራት ወር ኖረ ለዚች ሹመት የሚሻል ሲመረምሩና ሲመርጡ ብዙ ደከሙ። ከብዙ ድካምም በኃላ ሦስት የገዳም ሰዎችን መርጠው ስማቸውን በሦስት ክርታስ ጻፉ የክብር ባለቤት የ#ጌታችንን_ኢየሱስ_ክርስቶስንም ስም በአንዲት ክርታስ ጽፈው እየአንዳንዳቸውን አሽገው በመሠዊያው ውስጥ አኖሩአቸው። ቸር ጠባቂ ይሾምላቸው ዘንድ ኤጲስቆጶሳቱና ካህናቱ እስከ ሦስት ቀን እየጸለዩና እየቀደሱ #እግዚአብሔርን በመማለድ ኖሩ።

ከሦስት ቀኖችም በኃላ አንድ ታናሽ ብላቴና ጠርተው ከእነዚህ ከሦስቱ ስሞች አንዱን አንሥተህ ስጠን አሉት። ያም ብላቴና የዚህን አባት የአባ ሚካኤል ስም ያለበትን ያንን ክርታስ አወጣ። ሁሉም እግዚአብሔር እንደመረጠው አውቀው ይገባዋል ይግባዋል ይገባዋል እያሉ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት እርሱም በሹመቱ ላይሆኖ እንደሚገባ በመልካም አመራር ሥራውን መራ።

የሚጽፍለትም ጸሐፊ መረጡለት ስለ ምእመናን አጠባበቅና ስለማስተማር ወደ ሀገሮች ሁሉና ወደ ኤጲስቆጶሳቱ መልእክትን ይልክ ነበር። እርሱም ከኃጢአታቸው ተመልሰው ንሰሐ እንዲገቡ ሕዝቡን ይመክራቸውና ይገሥጻቸው ነበር እግዚአብሔርን ይፈሩት ዘንድ።

ንጽሐ ነፍስ ንጽሐ ልቡና ያለው ሆነ የዚህን አለም ጣዕም ያለውን ምግብ አይሻም አይመኝም ክብሩንም ቢሆን ወይም ጥሪቱን ድኆችንና ችግረኞችን አስቦ ይመጸውታቸው ነበረ እንጂ፡፡ ከእነርሱ የሚተርፈውንም ለቤተ ክርስቲያን ማሠሪያ ያደረገው ነበር። ይህ አባት ሙሉ ዓመት አልኖረም ከዚያ የሚያንስ ነው እንጂ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_መርቄ_ጻድቅ

በዚህችም ቀን ዳግመኛ ክርስቲያናዊ ነጋዴ መርቄ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከአንጾኪያ ሰዎች ወገን ነው ጉዝፋርም ጣዖት የሚያመልክ ከሀዲ ነው ከሃይማኖት በቀር በምንም በምን አይለያዩም። ከዕለታትም በአንዲቱ መርቄና ጉዝፋር ነበግዱድ ወደሚባል አገር ለንግድ ሒደው ሰው በሌለበት በበረሀ ውስጥ አምስት ቀን ተጓዙ ክርስቲያናዊ መርቄም ባለጸጋ ነው ከእርሱ ጋርም አርባ ልጥረ ወርቅ ነበረ።

በጐዳና በጉዞ ላይም እያሉ ለሞት የሚያደርስ ደዌን መርቄ ታመመ ከዚያም ራሱን አጽናንቶ እንዲህ ብሎ ጻፈ። "ከባሪያህ ልጅ ከባሪያህ መርቄ ለእኔ ያለ በጥቁር በቅሎ የተጫነ አርባ ልጥረ ወርቅ ለአንተ ይሁን #ጌታ_ኢየሱስ_ክርስቶስ የሕያው #እግዚአብሄር_ልጅ የክብር ባለቤት ሆይ ስለ በደሌ ይቅር ብለኸኝ መንግሥተ ሰማያትን ትሰጠኝ ዘንድ ለልጆቼ ለሚስቴም ወይም ለዘመዶቼ አይሁን ብዬአለሁ።"

ይቺን ደብደቤ ጠቅልሎ ወዳጄ ጉዝፋርን ጠራው የሚለውን ሁሉ ያደርግለት ዘንድ አማለው። ከዚያም በምሞትበት ጊዜ አትንካኝ ግን ይህን አርባ ልጥረ ወርቅ እንደተጫነ ከበቅሎው ጋራ ወስደህ የክብር ባለቤት ለሆነ ለሕያው #እግዚአብሔር_ልጅ_ለጌታዬ_ኢየሱስ_ክርስቶስ በእጁ ስጠው። ለልጆቼ እንዳትሰጥ ከእርሱ በቀር ለማንም ቢሆን አትስጥ አለው።

ጉዝፋርም እንዲህ ብሎ መለሰለት አንተ ራስህ ሞቶ ተነስቶ ወደ ሰማይ ወጣ የምትል አይደለምን እኔ ወደ ሰማይ ወጥቼ ልሰጠው እችላለሁን። መርቄም እንዲህ አለው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒድ ራሱ ወደ አንተ ይመጣል እጅ በእጅ ስጠው።

ከዚህ በኃላ መርቄ ለመሞት ሲቃረብ ራቀወ ብሎ በመቀመጥ ጉዝፋር መሞቱን ይጠብቅ ነበር። ወደርሱም መላእክት የብርሃን ልብስ ይዘው ሲወርዱ አየ ከእርሳቸውም ጋራ ጻድቃን ሰማዕታት አሉ ዳዊትም በመስንቆ ያመሰግን ነበር መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በስጋው ላይ ሦስት ጊዜ ዞረ ያንጊዜም የመርቄ ነፍስ ከሥጋዋ ተለይታ ወደ ሰማይ እንዲህ ባለ ሁኔታ ዐረገች። ሁለት አንበሶችም መጡ ምድሩንም ቆፍረው ቀበሩት።

ጉዝፋርም ተነሣ የመርቄንም ወርቅ ጭኖ ስለአየው ሁሉ እያደነቀ ሔደ። አንጾኪያም በደረሰ ጊዜ የቤተ ክርስቲያኑን አስተዳዳሪ ቀሲስ ታዴዎስን አግኝቶ መርቄ እንዳለው ነገረው። ቀሲስ ታዴዎስም ሊረከበው ወደ ጉዝፋር ሔደ። ግን የክብር ባለቤት ከሆነ ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለማንም አልሰጥም ወዳጄ መርቄ እንዳማለኝ እጅ በእጅ እሰጠዋለሁ እንጂ ብሎ ከለከለው።

ከዚያም ሒዶ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ቅጽር ግቢ ገባ።ቀሲስ ታዴዎስም ደጁን ከፈተለት የተጫነውንም ወርቅ አውርዶ በፊቱ አኑሮ በዚያ ቆመ። ከሌሊቱ እኩሌታ ላይ እንደ ነጐድጓድ ድምፅ ያለ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሰማ። ታላቅ ብርሃንም ወጣ #ጌታችንም ከሰማይ ወርዶ በመሠዊያው ላይ ተቀመጠ መላእክትም ከእርሱ ጋር አሉ።
ከመላእክትም አንዱ ከሀዲ ጉዝፋር ከዚህ ለምን ቆምክ አለው። እርሱም ወዳጁ መርቀፀ ለክብር ባለቤት #ለጌታ_ኢየሱስ_ክርስቶስ እንጂ ለሌላ እንዳይሰጥ ብሎ እንዳማለው ነገረው። መልአኩም የክብር ባለቤት የሕያው #እግዚአብሔር_ልጅ_ጌታ_ኢየሱስ_ክርስቶስ ይህ ነውና ና ስገድ አለው።

ጉዝፋርም ሰገደ ደብዳቤውንም ሰጠው።እየተንቀጠቀጠም የክብር ባለቤት #ጌታዬ_ኢየሱስ_ክርስቶስ ሆይ አመንኩብህ አለ። ጌታም ያንን ወርቅ ይመዝኑ ት ዘንድ አዘዘ። አርባ ልጥርም ሆነ ጉዝፋርንም ከቀሲስ ታዴዎስ ዘንድ እንዲጠመቅ አዘዘው። ከቤተሰቡ ሁሉ ጋር ተጠመቀ የተጠመቁትም ሰባ አምስት ነፍስ ሆኑ።

ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይሁን አሜን፡፡

#የዕለተ_ሐሙስ_ፍጥረታት

#ሐሙስ፡- የሚለው የዕለቱ ስም ሀምሰ ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ነው #አምስተኛ ማለት ነው፡፡ አምስተኛነቱም እግዚአብሔር ፍጥረታትን መፍጠር ከጀመረበት ከዕለተ እሑድ ጀምሮ ያለው ቀን ማለት ነው፡፡

  #የሐሙስ_ፍጥረታት
እግዚአብሔር ሐሙስ በቀዳማይ ሰዓት ለሊት “#ውሃ_ሕያው_ነፍስ_ያላቸው_ተንቀሳቃሾች_ታስገኝ” ብሎ በማዘዝ ሦስት አይነት ፍጥረታትን ፈጠረ፡፡ ዘፍ 1፡20 በዕለተ ሐሙስ የተፈጠሩት ሦስት ፍጥረታት ዘመደ እንስሳት የሚባሉት አሣዎች፣ ዘመደ አራዊት የተባሉት ኣዞ፣ጉማሬ፣ አሳነባሪ፣ ዘመደ አዕዋፍ የሚባሉት ደግሞ ዳክዬዎች ናቸው፡፡ 
#በዕለተ_ሐሙስ_የተፈጠሩት_ፍጥረታት_ተፈጥሮአቸው_ከአራቱ_ባሕሪያተ_ስጋ /መሬት፣ ውሃ ፣ነፋስና፣ እሳት/ ነው፡፡ አካላቸው ሥጋና ደም፣ አፅምና ጅማት ሲሆን በደም ነፍስ ይንቀሳቀሳሉ የደመ ነፍስ እውቀት አላቸው ደመነፍስ ማለትም በደም ነፍስነት፣ ኃይልነት የሚንቀሳቀሱ፣ የደም ነፍስ ያላቸው፣ ደማቸው ሲቆም እንቅስቃሴያቸውም የሚቆም ማለት ነው፡፡
   #የሐሙስ_ፍጥረታት_በአካሄዳቸው_በአኗኗራቸው_አንፃር_በሦስት_ይከፈላሉ በአካሄዳቸው በልብ የሚሳቡ፣ በእግር የሚሽከረከሩ፣ /የሚሄዱ/፣ በክንፍ የሚበሩ ይባላሉ፡፡

#በአኗኗራቸውም አንጻር በባህር ውስጥ ተፈጥረው በረው ወደ የብስ፣ ወደ ደረቁ መሬት የወጡ፣ በዚያው በተፈጠሩበት በባህር ውስጥ የቀሩ፣ ወጣ ገባ እያሉ ማለት ከባህር ወደ የብስ፣ ከየብስ ወደ ባሕር ወጣ ገባ እያሉ የሚኖሩ ይባላሉ፡፡ ከእነዚህም ፍጥረታት የሚበሉና የማይበሉ ለሰው የሚገዙና፣ የማይገዙም አሉ፡፡
    
#የሐሙስ_ፍጥረታት_ምሳሌነት

#በባሕር_ውስጥ_የሚኖሩት_ምሌሳነታቸው፡-

በእግዚአብሔር አምነው በስሙ ተጠምቀው በዚያው ፀንተው የሚኖሩ ሰዎች፤
በሕገ እግዚአብሔር ፀንተው በትዳር ተወስነው በሀብት በንብረታቸው መልካም ስራ እየሠሩ ዓሥራት አውጥተው፣ በዓላትን አክብረው የሚኖሩ የሕጋውያ ሰዎች፤
ግብራችንን አንተውም ብለው ሲሰርቁ ሲቀሙ፤ ሲምሉና ሲገዘቱ የሚኖሩ የኃጥአን ምሳሌ ናቸው፡፡

#ወጣ_ገባ_እያሉ_የሚኖሩት_ምሳሌነታቸው
  አንድ ጊዜ ወደ ዓለም አንድ ጊዜ ወደ ገዳም ሲመላለሱ የሚኖሩ መነኮሳት፣
አንድ ጊዜ ወደ ሀይማኖት አንድ ጊዜ ወደ ክህደት የሚወላውሉ ሰዎች፤
#በባሕር_ተፈጥረው_በረው_ወደ_የብስ_የሄዱት
ከዘመድ አዝማድ ተለይተው ርቀው ከበረሃ ወድቀው ደምፀ አራዊቱን ፀብአ አጋንንቱን ግርማ ለሊቱን ታግሰው የሚኖሩ የመናንያን ምሳሌ ናቸው፡፡
አንድም በባህር ተፈጥረው በረው ወደ የብስ የሚኖሩት የከሀዲዎች ምሳሌ ነው በሀይማኖት ኖረው በኋላ ይክዳሉና
           
#አካሄዳቸውም 
#በልብ_የሚሳቡ፡- የመንግስት ምሳሌ ናቸው እነዚህ በልብ (በደረት) ተስበው ስራቸውን ፈቃዳቸውን እንዲፈፅሙ መንግስትም በልቡ ያሰበውን ይሠራል ይፈፅማል፡፡
#በእግር_የሚሽከረከሩ
“ያላችሁን ትታችሁ ተከተሉኝ” ባለው አምላካዊ ቃል መሠረት ሁሉን ትተው ከሴት ከወንድ እርቀው ድንግልናቸውን ጠብቀው ከትሩፋት ወደ ትሩፋት እየተሸጋገሩ የሚኖሩ የመናንያን ምሳሌ፡፡

#በክንፋቸው_የሚበሩት፡- ሥጋችሁን እንጂ ነፍሳችሁን ለመግደል የማይችሉትን አትፍሩ ባለው አምላካዊ ቃል ተመርተው ሳይፈሩ ዓላውያን ነገስታት ካሉበት ገብተው ሃይማኖታቸውን በመመስከር ሰማዕታትነታቸውን የሚፈፅሙ ሰማዕታት ምሳሌ ናቸው፡፡
  #ሰው_የሚባላቸውና_ለሰው_የሚገዙት፡- ለእግዚአብሔርና ለሰው በፍቅር በትሕትና የሚገዙ፣ የእግዚአብሔርን ፍቃድ የሚፈፅሙ የፃድቃን ምሳሌ ናቸው፡፡
#ሰው_የማይበላቸው_ለሰው_የማይገዙት ለእግዚአብሔርም ለሰውም የማይገዙ፣ አንገዛም አንታዘዝም ብለው በትዕቢት በዓመፅ የሚኖሩ የሃጣን ምሳሌ ናቸው፡፡
እግዚአብሔር ከአንድ ባሕር ሦስት ወገን የሆኑ ፍጥረታትን ፈጠረ፡፡ ከአንድ ማየገቦ ሦስት ትውልድ፡- ትውለደ ሴም፣ ትውልደ ያፌት፣ ትውልደ ካም ይጠመቁ ዘንድ መሰጠቱን  ያሳያል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ልጅነት በአብ‹ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ተጠምቀው ለመሰጠቷም ምሳሌ ነው፡፡
  በዕለተ ሐሙስና በዕለተ ዓርብ የተፈጠሩት ፍጥረታት “እንስሳት” በመባል አንድ ቢሆኑም በአኗኗራቸውና በግብራቸው ይለያያሉ፡፡ የሐሙስ ፍጥረታት ከባሕር ተለይው በየብስ /በምድር/ መኖር አይችሉም የፀሐይ ሙቀት ሲነካቸው ይሞታሉ፡፡
  የግብር ፍጥረታትም ከምድር ተለይተው በባህር ውስጥ መኖር አይችሉም የባህር ውርጭ ቅዝቃዜ ይገድላቸዋልና፡፡

#ሚያዝያ_1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት፣
፩, ቅዱስ መርቄ ጻድቅ (ክርስቲያናዊ ነጋዴ)
፪, ቅዱስ ዮሐንስ ዘኢየሩሳሌም
፫, አባ ሚካኤል ዘእስክንድርያ
፬, #እግዚአብሔር በእግር የሚራመዱ በክንፍ የሚበሩና በልብ የሚሳቡ በየብስ የሚኖሩ ፍጥረታትን ፈጠረ

#ወርኃዊ_በዓላት
፩, በዓታ ለእግዝእትነ #ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ
፪, ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
፫, ቅዱሳን ሊቀ ካህናት አበው (ዘካርያስና ስምዖን)
፬, አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ
፭, አቡነ ዜና ማርቆስ
፮, አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዘደብረ በንኮል

እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም። መብራትንም አብርተው ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል። መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።(ማቴ. ፭÷፲፬-፲፮)

        ✝️ወስብሐት ለ#እግዚአብሔር✝️
መጻሕፍትን አዘውትሮ ከመመርመሩ የተነሣ የክብር ባለቤት "ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ" ወደ ዓለም እንደመጣና ሰውም እንደሆነ በሞቱም ዓለምን እንደ አዳነ ያመነው ቅዱስ አባት ማን ይባላል?
Anonymous Quiz
35%
ቅዱስ መርቄ ጻድቅ
24%
አባ ሚካኤል
30%
ቅዱስ ዮሐንስ ዘኢየሩሳሌም
11%
ቅዱስ ዮሐንስ ዘሮም
አባ ሚካኤል በእስክንድርያ ለተሾሙ ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ስንተኛ ናቸው?
Anonymous Quiz
31%
75ኛ
20%
70ኛ
22%
61ኛ
27%
71ኛ
ቅዱስ መርቄ ወርቁን በአደራ መልክ የክብር ባለቤት ለሆነ ለሕያው እግዚአብሔር ልጅ ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ስጥልኝ ያለው ማንን ነው?
Anonymous Quiz
41%
መልአኩን
40%
ጉዝፋርን
9%
ነበግዱን
10%
ቤተሰቦቹን
Channel name was changed to «ቅዱሳን ኅሩያን የዲ°ን ዮርዳኖስ ትምህርቶች»
Audio
AudioLab
"" ሕማማተ ክርስቶስ ""

"በዓለ ስቅለት"

(መጋቢት 27 - 2016)
Converted size

https://www.tg-me.com/zikirekdusn

https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
2024/09/24 09:19:25
Back to Top
HTML Embed Code: