ለሀዋሳ ከተማ እግር ኳስ ክለብ አሸኛኘት ተደረገለት
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 ውድድሩን ለማከናወን ዝግጅቱን ሲሰራ የነበረው ሀዋሳ ከተማ በሲዳማ ጎፈሬ ዋንጫ ላይ እና በተለያዩ የወዳጅነት ጨዋታዎች አዳዲስ ፣ ነባር እንዲሁም ታዳጊ ተጫዋቾችን በመያዝ ልምምዱን ሲሰራ እና ሲወዳደር ቆይቶ ለዋናው የፕሪሚየር ሊግ ውድድር ራሱን አዘጋጅቶ ወደ አዳማ ከማምራቱ በፊት ዛሬ ምሽት በሴንትራል ሀዋሳ ሆቴል አሸኛኘት ተደርጎለታል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እና የክለቡ የበላይ ጠባቂ አቶ መኩሪያ መርሻዬ ፣ የክለቡ ከፍተኛ የቦርድ አመራሮች ፣ ከፍተኛ የከተማ አስተዳደሩ የመምሪያ ሀላፊዎች ፣ የክለቡ አመራር ፣ የደጋፊ ማህበሩ ተወካዮች ፣ አሰልጣኞች እና ተጫዋቾች በተገኙበት ነው በሴንትራል ሀዋሳ ሆቴል ሽኝቱ የተደረገው።
የከተማው ከንቲባ እና የክለቡ የበላይ ጠባቂ አቶ መኩሪያ በንግግራቸው የስራ መመሪያ ለክለቡ አባላት ያቀረቡ ሲሆን የዘንድሮው አመት የተሻለ ውጤት እንዲመጣ ከተማ አስተዳደሩም ሆነ እርሳቸው በልዩ ትኩረት ሰጥተው እንደሚከታተሉ ገልፀዋል። በመቀጠል የክለቡ አሰልጣኝ ዘርአይ ሙሉ እና አምበሉ ሙጂብ ቃሲም ክለቡ ያደረገላቸው ትኩረት እንዳስደሰታቸው ጠቁመው። ከክለቡ የተላለፈውን መመሪያ ተግባራዊ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆናቸውን አሳስበዋል። በመጨረሻም የኬክ መቁረስ እና የእራት ግብዣ ተከናውኖ ፕሮግራሙ ተጠናቋል።
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 ውድድሩን ለማከናወን ዝግጅቱን ሲሰራ የነበረው ሀዋሳ ከተማ በሲዳማ ጎፈሬ ዋንጫ ላይ እና በተለያዩ የወዳጅነት ጨዋታዎች አዳዲስ ፣ ነባር እንዲሁም ታዳጊ ተጫዋቾችን በመያዝ ልምምዱን ሲሰራ እና ሲወዳደር ቆይቶ ለዋናው የፕሪሚየር ሊግ ውድድር ራሱን አዘጋጅቶ ወደ አዳማ ከማምራቱ በፊት ዛሬ ምሽት በሴንትራል ሀዋሳ ሆቴል አሸኛኘት ተደርጎለታል። የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እና የክለቡ የበላይ ጠባቂ አቶ መኩሪያ መርሻዬ ፣ የክለቡ ከፍተኛ የቦርድ አመራሮች ፣ ከፍተኛ የከተማ አስተዳደሩ የመምሪያ ሀላፊዎች ፣ የክለቡ አመራር ፣ የደጋፊ ማህበሩ ተወካዮች ፣ አሰልጣኞች እና ተጫዋቾች በተገኙበት ነው በሴንትራል ሀዋሳ ሆቴል ሽኝቱ የተደረገው።
የከተማው ከንቲባ እና የክለቡ የበላይ ጠባቂ አቶ መኩሪያ በንግግራቸው የስራ መመሪያ ለክለቡ አባላት ያቀረቡ ሲሆን የዘንድሮው አመት የተሻለ ውጤት እንዲመጣ ከተማ አስተዳደሩም ሆነ እርሳቸው በልዩ ትኩረት ሰጥተው እንደሚከታተሉ ገልፀዋል። በመቀጠል የክለቡ አሰልጣኝ ዘርአይ ሙሉ እና አምበሉ ሙጂብ ቃሲም ክለቡ ያደረገላቸው ትኩረት እንዳስደሰታቸው ጠቁመው። ከክለቡ የተላለፈውን መመሪያ ተግባራዊ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆናቸውን አሳስበዋል። በመጨረሻም የኬክ መቁረስ እና የእራት ግብዣ ተከናውኖ ፕሮግራሙ ተጠናቋል።
የ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ጨዋታውን ከፋሲል ከነማ ጋር በጥሩ እንቅስቃሴ 3ለ3 አጠናቆ የነበረው ክለባቸን ሀዋሳ ከተማ በዛሬው ዕለት በ2ኛ ሳምንት ጨዋታው ከጥሩ እንቅስቃሴ ጋር ሻሸመኔ ከተማን በእዮብ አለማየሁ ጎል 1ለ0 አሸንፎ ወጥቷል።
እንኳን ደስ አላችሁ 🙏
እንኳን ደስ አላችሁ 🙏