Telegram Web Link
https://youtu.be/lRZDCrTCoIk
ፈጥሮ የማይጥል ወዶ የማይጠላ እግዚአብሔር ብቻ ነው ክርስቲያኖች። ሰው እንደተሰባሪ ብርጭቆ ነው። እግዚአብሔርን የተመረኮዘ አይወድቅም።
https://youtu.be/ADoQmZzrgJw
ሌሎችን መንፈሳዊ እንዲሆኑ ታስተምሩ ነበር እንጂ እናንተ መንፈሳውያን አልነበራችሁም፡፡ እናንተ ድራማ ስትሠሩ ነውኮ የኖራችሁት፡፡ መድረክ ላይ ወጥታችሁ መንፈሳዊ ድራማ ትሠሩ ነበር፡፡ ልብሳችሁ፣ንግግራችሁ፣የእጅ አጣጣላ ችሁ፣ ጸሎታችሁ፣ የተዋናይ ነበርኮ፡፡ የማትሆኑትን ነበር ስታስተምሩ የነበራችሁት፡፡ ለመሆኑ ለሕዝቡ የምታስተምሩትና እናንተ የምትመሩበት የሃይማኖት መጽሐፍ አንድ ነው? ወይስ ይለያያል?
https://youtu.be/s2qBoAHSdhs
በገዳም ያሉ አባቶች እናቶች በፆመ ፍልሰታ በዝግ በማሳለፍ ከራሳቸው እስከ አገራቸው ያለውን፣ የወደፊት ነባራዊ ሁኔታ የሚያውቁበት ከእመቤታችንም ብዙ ፀጋ የሚቀበሉበት ወቅት ነው፡፡ በተለይ የዓመቱ የመጨረሻ የሱባኤ ጊዜ ስለሆነ አዲሱን ዓመት የበረከት እንድታደርግልን በዘንድሮ ያልሆነልንን በዓዲሱ ዓመት እንድታከናውንልንና ብዙ አዳዲስ ነገሮችን የምንጠይቅበት ጊዜ ስለሆነ ልናስብበት ይገባል፡፡
https://youtu.be/jdzUdqhVCPM
ኢትዮጵያ ማለት እኔና እናንተ በምናውቃት ልክ ብቻ ያለች ሀገር አይደለችም። ኢትዮጵያ ከምድር ሀገራት ሁሉ እጅግ ምስጢራዊና ረቂቅ ሀገር ናት። ይሄን ስላችሁ ደግሞ በግምት ወይም በስሜት ተገፍቼ አይደለም።
https://youtu.be/Q1G-aro4Z1Y
ውሆችም ከባህር ይደርቃሉ::ወንዙም ያንሳል ደረቅም ይሆናል:: ወንዞችም ይገማሉ:: የግብፅ መስኖዎችም ያንሳሉ ይደርቃሉም:: ደንገልና ቄጤማ
ይጠወልጋሉ:: በአባይ ወንዝ ዳር ያለው መስክ በአባይም ወንዝ ዳር የተዘራ እርሻ ሁሉ ይደርቃል:ይበተንማል:አይገኝምም:
አሳ አጥማጆች ያዝናሉ::በአባይም ወንዝ መቃጥን የሚጥሉ ሁሉ ያለቅሳሉ::በውሆችም ላይ መረብ የሚጥሉ ይዝላሉ:: ይላል የእግዚአብሔር ቃል...
https://youtu.be/0NQaAfx8Cg0
ማተብ ሃይማኖት ነው ፣ ማተብ እምነት ነው ፣ ማተብ የኢየሱስ ክርስቶስ ግልጽ ምስክርነት ነው ፣ ማተብ በጥምቀት በኩል የአምላክ ልጆች መሆናችንን በመንፈስ ቅዱስ የታተምንበት የልጅነት ምልክታችን ነው ፣ የመስቀል ማተብ በአንገታችን አስረን ኢየሱስ ክርስቶስን በአደባባይ ለዓለም የምንመሰክረው የደም ማህተማችን ነው
የመስቀሉ ማተብ ለኛ ምልክታችን ነው ።
https://youtu.be/UQh-xCx1qA0
የላመ የጣመ ምግብ ይዘን በዓታቸው ድረስ እንሄዳለን፡፡ የዓለሙን ርኩሰትና እርባና ቢስ ወሬዎች እየነገርን የጠራ ሕሊናቸውን እናደፈርሳለን፡፡ ፋታ ሳይሰጥ ለሚፈትናቸው ሰይጣን ጦር አቀባይ እንሆንባቸዋለን፡፡ ብንችል ‹ጸሎት ያደርጉልኛል› በሚል ሰበብ ከበዓታቸው አፍልሰን በከተማ ሰርቢሶቻችን እናስቀምጣቸዋለን፡፡
https://youtu.be/8CwUMMFh9gA
በጾመ ፍልሰታ ባሕታውያን ብቻ ሳይኾኑ ዓለማውያንም በእግዚአብሔር ቸርነት፣ በእመቤታችን አማላጅነት የሰይጣንን ፈተና ድል ለማድረግ እንዲቻላቸው ከቤተሰቦቻቸው ተለይተው በየገዳማቱና በየአብያተ ክርስቲያናቱ በዓት አዘጋጅተው፣ ሱባዔ ገብተው፣ ፈቃደ ሥጋቸውን ለፈቃደ ነፍሳቸው አስገዝተው ይጾማሉ፤ ይጸልያሉ፡፡
https://youtu.be/ccsB8YY9Xr0
በጾመ ፍልሰታ ባሕታውያን ብቻ ሳይኾኑ ዓለማውያንም በእግዚአብሔር ቸርነት፣ በእመቤታችን አማላጅነት የሰይጣንን ፈተና ድል ለማድረግ እንዲቻላቸው ከቤተሰቦቻቸው ተለይተው በየገዳማቱና በየአብያተ ክርስቲያናቱ በዓት አዘጋጅተው፣ ሱባዔ ገብተው፣ ፈቃደ ሥጋቸውን ለፈቃደ ነፍሳቸው አስገዝተው ይጾማሉ፤ ይጸልያሉ፡፡
https://youtu.be/18HPQUJgeWg
ቤተ ክርስቲያንን ያገለግሉ ዘንድ የኃላፊነት መክሊቱን ከተቀበሉት ከፓትርያርክ እስከ ታች ካሉት ጀምሮ በአርባና በሰማንያ ቀን ልጅነትን እስከተቀበልነው ድረስ እግዚአብሔር እንደ አቅማችንና እንደጸጋችን የሰጠን ሥጦታ አለ። ሐይማኖታችን፣ ሥርዓታችን የተሰጡን መክሊቶች ናቸውና በሚገባ ልንይዝና ልንጠብቃቸው ይገባል። ጌታ ዕንቁዎቻችሁን በእርያ ፊት አታስቀምጡ ያለው ለዚህ ነው። ዕንቁ የሆነው መክሊት ሐይማኖታችንና ሥርዓታችን ነው «ማንም አክሊልህን እንዳይወስድብህ ያለህን አጽንተህ ያዝ» ተብሏል ራእ 3፥11።
እኔን እንደገረመኝ እናንተም ትገረሙ ዘንድ ይህን ጋበዝኳችሁ. ሻሎም!!!😊
2025/02/24 16:04:56
Back to Top
HTML Embed Code: