Telegram Web Link
የዘንድሮ ኢሬቻ መስከረም 25 እና 26 እንደሚከበር የአባገዳዎች ህብረት አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢሬቻ 2017 መስከረም 25 እና 26 እንደሚከበር የአባገዳዎች ህብረት አስታውቋል፡፡ አከባበሩን አስመልክቶ መግለጫ የሰጠው ህብረቱ÷ መስከረም 25 ኢሬቻ ሆረ ፊንፊኔ በማግስቱ መስከረም 26 ቀን 2017 ዓ.ም ደግሞ ኢሬቻ ሆረ አርሰዴ በድምቀት እንደሚከበር ገልጿል። ህብረቱ በሆረ ፊንፊኔ እና በሆረ አርሰዴ ለሚከበረው በዓል ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁንም አስታውቋል፡፡…

https://www.fanabc.com/archives/263629
5 ሚሊየን ቋሚ በጎ ፈቃደኞችን ለማፍራት መታቀዱ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በተያዘው በጀት ዓመት 5 ሚሊየን ቋሚ በጎ ፈቃደኞችን ለማፍራት ዕቅድ መያዙን የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ። ሚኒስትሯ ከለውጡ ወዲህ የበጎ ፈቃድ ስራዎች ባህል እንዲሆኑ ሰፋፊ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል፡፡ በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም በክረምት በጎ ፈቃድ ስራዎች ከ 24 ሚሊየን በላይ ወጣቶች በ13…

https://www.fanabc.com/archives/263632
አቶ ሽመልስ አብዲሳ በምስራቅ ሸዋ ዞን አዲሱ የቀበሌ መዋቅር የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሽመልስ አብዲሳ በምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ አዲሱ የቀበሌ መዋቅር የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ። በጉብኝቱ ላይ የብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ከፍያለው ተፈራ ጨምሮ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

https://www.fanabc.com/archives/263626
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
መስቀል በጉራጌ (በሶዶ ክስታኔ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስተላለፉት መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል:-

የመስቀል በዓል የሕልም ጉልበት የታየበት በዓል ነው፡፡

ንግሥት ዕሌኒ መስቀሉን ለማውጣት ያለመችው ምንም አመቺ ነገር ባልነበረበት ጊዜ ነው፡፡ ዙሪያዋ ጨለማ ነበር፡፡ መንገዶች ሁሉ ዝግ ነበሩ፡፡ ነገሮች ሁሉ አስቸጋሪ ነበሩ፡፡ ማንም በማያስበው ጊዜ፤ አይቻልም አይሞከርም በሚባልበት ወቅት፤ አንድ ቀን፤ ፈጣሪዋ ሲፈቅድ፤ መስቀሉን ከተቀበረበት ሥፍራ ለማውጣት ሕልም ነበራት፡፡

ሕልሟ እንዲሳካ ሠራች፤ ታገለች፡፡ ጨለማውን እየገፈፈች፤ አስቸጋሪውን ጎዳና እየጠረገች፤ ከውስብስብ ችግሮች ጋር እየተጋፈጠች ወደ ፊት ተጓዘች፡፡ በመጨረሻም ኢየሩሳሌም ተሻግራ፣ መስቀሉን ከተቀበረበት ሥፍራ ለማውጣት በቃች፡፡ ሕልሟ እውን ሆነ፡፡ ታሪክን ቀየረች፡፡ ልዕልናን ዐወጀች፡፡ ደመራ ለሚታገል፤ ተስፋ ለማይቆርጥና እስከ መጨረሻው ለሚጸና ሰው ሕልሙ አንድ ቀን እውን እንደሚሆን የሚያሳይ ትእምርት ነው፡፡

እዮሃ፤ ማለት “ይሄዋ” ማለት ነው ይባላል፡፡

ይሄው ተገኘ፤ ይሄው ተሳካ፤ ይሄው እውን ሆነ ማለት ነው፡፡ ከበረቱ፤ ከታገሉና ከጸኑ የማይሳካ ምን ነገር አለ? ሕልሙን ለሚያውቅ፤ ሕልሙ እንዲሳካ በነገሮች ተስፋ ሳይቆርጥ ለሚለፋ፤ እንደ ንግሥት እሌኒ ሕልሙ እውን ሆኖ አንድ ቀን ማየቱ አይቀርም፡፡ የሕልሙን ደመራ መደመሩ አይቀርም፡፡ “እዮሃ”፤ “ይሄዋ!” ማለቱ አይቀርም፡፡

መስቀል ኅብረ ብሔራዊ…

https://www.fanabc.com/archives/263640
እንደ ደመራው ተደምረን ልዩነቶችን በማስወገድ ለአንዲት ኢትዮጵያ መቆም ይገባናል – ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር)

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) እንደ ደመራው ተደምረን ልዩነቶችን በማስወገድ ለአንዲት ኢትዮጵያ መቆም ይገባናል ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ የመስቀል በዓልን ምክንያት በማድረግ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፤ የመስቀል በዓል አንድነት፣ አብሮነትና መደመር የሃያልነት፣ የመድመቅና የመጉላት መሰረት…

https://www.fanabc.com/archives/263645
የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል የሆነው የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት በአማራ ክልል የሚገኝ ነው፡፡ የጎርጎራ ፕሮጀክት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ገበታ ለሀገር” በሚል ይፋ ካደረጓቸው ሶስት ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ መሆኑ ይታወቃል። የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶች የመጀመሪያው ዙር ከአዲስ አበባ ውጪ ሶስት ቦታዎችን ከአማራ ክልል ጎርጎራ፣ ከኦሮሚያ ክልል…

https://www.fanabc.com/archives/263649
የመስቀል ደመራ በዓል ሲከበር ሰላምን በማጽናትና አብሮነትን በማጠናከር ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስቀል ደመራ በዓልን ስናከብር ከምንም በላይ ሠላማችንን በማጽናትና አብሮነታችንን በማጠናከር ሊሆን ይገባል ሲል የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ገለጸ፡፡ የክልሉ መንግስት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ2017 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በሠላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቱን ገልጿል፡፡ የክልሉ መንግስት የመስቀል ደመራ በዓልን ስናከብር ከምንም በላይ ሠላማችንን በማጽናት፣…

https://www.fanabc.com/archives/263652
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የጥንቃቄ መልዕክት

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰሞኑን የተለያዩ የዲጂታል ሚዲያዎችን በመጠቀም ሽልማቶችን ለመሸለም በሚመስል መልኩ የኢትዮ-ቴሌኮም ነጻ የዳታ ሽልማት ለሁሉም አሮጌ ሲም ካርድ ተጠቃሚዎች በሚል መልዕክቶች ወደ ተለያዩ ግለሰቦች እየተላኩ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አረጋግጧል። ይህ መልዕክትም የግለሰቦችን ሚስጥራዊ መረጃዎች የማጥመድ ጥቃት (Phishing Attack) መሆኑን ማረጋገጥ ችሏል። በጥቃት አድራሾቹ ለተጠቃሚዎች…

https://www.fanabc.com/archives/263655
መስቀል በአስቸጋሪ፣ በፈታኝና በድንግዝግዝ ውስጥ ሆኖ ነገን የማየት ተምሳሌት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) መስቀል በአስቸጋሪ፣ በፈታኝና በድንግዝግዝ ውስጥ ሆኖ ነገን የማየት ተምሳሌት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለመስቀል በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት÷ የመስቀል በዓል ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ በኢትዮጵያውያን የሚከበር በዓል ነው ብለዋል። አከባበሩ ኅብራዊ ነው፣ የየአካባቢው ቀለም ይጨመርበታል፣…

https://www.fanabc.com/archives/263658
የመስቀል በዓል የአብሮነትና የመተሳሰብ እሴቶች እንዲጠናከሩ እያገዘ ነው – አቶ እንዳሻው ጣሰው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስቀል በዓል የአብሮነትና የመተሳሰብ እሴቶች እንዲጠናከሩ በማገዝ የበኩሉን ሚና እየተወጣ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር እንዳሻው ጣሰው ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ የ2017 ዓ.ም የመስቀልን በዓልን አስመልክቶ ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፤ በዓሉ ሃይማኖታዊና ባህላዊ ገፅታ እንዳለው ገልጸዋል። ተራርቀዉ የሠነበቱ ቤተሰቦች የሚገናኙበት፣ ቤተሰባዊና ማህበረሰባዊ ትስስሮች የሚታደሱበት መሆኑንም…

https://www.fanabc.com/archives/263665
የተለያዩ ሀገራት ኤምባሲዎችና ዓለም አቀፍ ተቋማት ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የተለያዩ ሀገራት ኤምባሲዎችና ዓለም አቀፍ ተቋማት ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልካም ምኞት መግለጫ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የአውሮፓ ህብረት በማህበራዊ ትስስር ገጹ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ ሲል መልዕክቱን አጋርቷል፡፡ በኢትዮጵያ የእስራኤል ኤምባሲ በበኩሉ፥ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለመስቀል (የደመራ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ ብሏል፡፡ በዓሉም…

https://www.fanabc.com/archives/263668
Live stream finished (35 minutes)
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የመስቀል በዓልን አስመልክቶ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ በመልእክታቸው÷ በዓሉን ስናከብር በመስቀሉ የተገለጠውን የክርስቶስ ቤዛነት፣ ፍቅር እና እውነትነት ዓርዓያ በመከተል እርስ በርሳችን በመዋደድ ልዩነትን፣ መራራቅን እና አለመግባባትን በማስወገድ ህብረ ብሄራዊ አንድነነትን ለማጠናከር ቃል…

https://www.fanabc.com/archives/263671
የሐረሪ ክልል መንግስት ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልላዊ መንግስት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፏል፡፡ የክልሉ መንግስት በመልእክቱ÷ ህዝበ ክርስቲያኑ የመስቀል ደመራ በዓል እሴቱን ጠብቆ እንዲከበር በማድረግ የተቸገሩ ወገኖችን በማብላትና የተጠሙትን በማጠጣት እንዲሁም የተለመደ የመተዛዘንና የመረዳዳት ባህሉን እንዲተገብር ጥሪ አቅርቧል። ህዝበ ክርስትያኑን ጨምሮ መላው የክልሉ ነዋሪ ሰላምን፣…

https://www.fanabc.com/archives/263674
የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በድምቀት ይከበራል

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2017 ዓ.ም መስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በድምቀት ይከበራል። በበዓሉ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ሚኒስትሮችና የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች፣ አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶችን ጨምሮ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ቱሪስቶች በበዓሉ ላይ ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል። በአሁኑ ሰዓትም…

https://www.fanabc.com/archives/263677
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለመስቀል በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ በመልዕክታቸውም÷ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ፣ ደሙን አፍስሶ፣ ለሰዉ ልጆች ሁሉ ፍቅሩን ገልጿል ብለዋል፡፡ ይህ ሁሉ ዋጋ የተከፈለበት መስቀል ምሳሌነት በዚህች ምድር ስንኖር እርሰበርሳችን ያለ ምንም ልዩነት በፍቅር፣ በምህረት እና በመተሳሰብ…

https://www.fanabc.com/archives/263681
የመስቀል በዓል እሴቱን ጠብቆ የሀገር ሃብት ሆኖ እንዲቀጥል ሁሉም ኃላፊነቱን መወጣት አለበት- የኮሙኒኬሽን አገልግሎት

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስቀል በዓል እሴቱን ጠብቆ የሀገር ሃብት ሆኖ እንዲቀጥል ሁሉም ኃላፊነቱን መወጣት አለበት ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስገነዘቡ። አገልግሎቱ የመስቀል ደመራ በዓልን አስመልክቶ ባስተላለፈው የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት፤ በመላዉ ኢትዮጵያ የደመራ እና የመስቀል በዓል ጥንታዊነቱን ይዞ የቀጠለ የዐደባባይ በዓል ነው። ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣…

https://www.fanabc.com/archives/263684
ማስታወቂያ!

#የቴክኖ የአዲስ ዓመት ልዩ የበዓል ስጦታ!

የአዲስ አመት ልዪ ስጦታ ከቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ፣ ከየትኛውም የቴክኖ ሱቅ የቴክኖ ስማርት ስልክን ሲገዙ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር ፎቶ በመነሳት የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ እና ብዙ ላይክ በማግኘት የዱባይ ደርሶ መልስ የቢዝነስ ክላስ የአውሮፕላን ትኬት፣ ላፕቶፖች፣ የቴክኖ ስማርት ስልኮችን እና ገደብ አልባ የኢንተርኔት ፓኬጆችን ይሸለሙ፡፡

የውድድሩ መመሪያ

1. የቴክኖ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የቴክኖ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡ ብዙ ላይክ እና ኢንጌጅመንት ያገኘው ተሸላሚ ይሆናል፡፡
- Tag ሲያደርጉን ለ Facebook @TecnoEt ፣ ለ Instagram @TecnoMobileEthiopia እና ለ TikTok @TecnoEt ን  ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።)
- በተጨማሪም #TecnoEt2017 ን keyword መጠቀም እንዳይረሱ)
2024/09/28 06:15:44
Back to Top
HTML Embed Code: