Telegram Web Link
ጥቆማ‼️

እንዳያመልጣቹ ‼️

ምንም ገንዘብ ሳታወጡ ብር ልታገኙባቸው የምችሏቸው የኦንላይን ኤርድሮፖች ባዲሱ ቻናላችን መለቀቅ ተጀምሯል።

አሁንኑ በመቀላቀል
ትርፋማ ይሁኑ👇👇
https://www.tg-me.com/sheger_crypto
https://www.tg-me.com/sheger_crypto
በመዲናዋ የድምጽ ብክለት ጉዳት እያስከተለ ነው ተባለ  

በአዲስ አበባ ከተማ የድምጽ ብክለት በማህበረሰቡ ላይ ጉዳት እያስከተለ መሆኑን የአዲስ አበባ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ።

ባለስልጣኑ ከብዙ ምንጮች የሚነሱ ከቁጥጥር ውጭ የሆኑ ከፍተኛ ድምጾች በህብረተሰቡ ላይ አለመረጋጋት፣ ደስታ ማጣትና እና ሌሎች የጤና እክሎችን እያስከተሉ መሆኑን ለአራዳ ገልጿል።
 
ብክለቱ የመስማት ችግርን፣ አለመግባባትን፣ የደም ግፊት፣ የአዕምሮ ህመም፣ በእርጉዝ ሴቶች ላይ ደግሞ ፅንስ ማስወረድ ችግርና የጤና እክል እያስከተለ እደሚገኝ ጠቁሟል።

ከመገበያያ ስፍራዎች፣ ከሆቴሎች፣ ከሃይማኖት ተቋማት፣ ከስፖርት ሜዳዎች፣ ከሙዚቃ ማጫዎቻና ሌሎች ስፍራዎች የሚወጡ ድምጾች ለድምጽ ብክለት መንስኤ ናቸው ነው የተባለው።

ደካማ የሆነው የመዲናዋ የግንባታ ዲዛይንም ለድምጽ ብክለት ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለውም አንስቷል።

Arada_Fm

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
"ፖሊሱ ተይዞ ምርመራ እየተደረገበት ነው" የአፋር ፖሊስ

በማህበራዊ ሚዲያዎች የከባድ መኪና ሹፌር በማስቆም ሲያስፈራራ እና ሲያንገላታ  የሚታየው የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ውሎ ምርምራ እየተጣራ እንደሚገኝ የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ቢልኤ አህመድ ገልጸዋል።

ይህ አሽከርካሪ ላይ በግድ መንገደኛ የመጫን ተግባር ከፖሊስ ዲሲፕሊን ውጭ የሆነ ተግባር  በመሆኑ  የአፋር ክልል ፖሊስ ጉዳዩን በማጣራት ተመጣጣኝ የሆነ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ማረጋገጣቸውን ፋስት መረጃ ከአፋር ፖሊስ ያገኘው ሰምቷል።

ኮሚሽነር ጄነራሉ ይህ ተግባር የህዝብ ልጅ እና በህዝባዊ  ወገንተኝነቱ የሚታወቀው የአፋር ፖሊስ እንደማይወክል አሰረድተዋል።
fastmereja

@ethio_mereja_news
#Tecno #Camon30Pro5G

Tech – art leather ቴክኖሎጂ በመጠቀም እጅግ ዘመናዊ ዲዛይን የተላበሰው አዲሱ Tecno Camon 30 pro 5G ምርጫዎ ያድረጉ!

#Camon30Et #Camon30pro5GEt #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt
ደሞዝ‼️

የወላይታ ዞን የሠራተኞቹን ደሞዝ ከሚቀጥለው ዓመት ተበድሮ ለመክፈል መገደዱ ተገለፀ!!

የዞኑ የመንግሥት ሠራተኞች ባለፉት ሳምንታት ጀምሮ በአደባባይ የሦስት ወራት ደሞዛቸው እንዲከፈላቸው በሰላማዊ ሰልፍ በመጠየቅ ላይ ይገኛሉ።

ያምሆኖ እስከአሁን ለጥያቄያቸው ከዞንና ከክልል መስተዳድሮች ተግባራዊ ምላሽ እንዳላገኙ ሠራተኞቹ ተናግረው በዚህም የተነሳ አሁን ላይ ከነቤተሰቦቻቸው በችግር ላይ መውደቃቸውን ሠራተኞቹ ተናግረዋል።

የሠራተኞቹን የደሞዝ ይከፈለን ጥያቄ አስመለክቶ ከዶቼ ቬለ ጋር ቃለምልልስ ያደረጉት የዎላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ፎላ ዞኑ ለሠራተኞቹ ደሞዝ መክፈል ያተቸገረው በሁለት ምክንያቶች ነው ይላሉ፦ አንድም የወረዳ መዋቅሮች መሥፋት ሁለትም ሲንከባለል በመጣው የአፈር ማዳበሪያ ዕዳ የተነሳ የበጀት አለመጣጣም በመከሰቱ ነው ብለዋል።

በተለይም በዞኑ አዳዲስ የወረዳ መዋቅሮች መበራከት፣ የሠራተኞች እና ተሾሚዎች ቁጥር መጨመር ለበጀት ጉድለቱ መከሰት ምክንያት መሆኑን የጠቀሱት ዋና አስተዳዳሪው “በተለይም ባለፉት አራት ዓመታት የአገልግሎት ተደራሽነትን ለመፈጠር ተጨማሪ የወረዳ እና የከተማ አስተዳደሮች በመቋቋሙ የሠራተኛውና የተሾሚዎችን ቁጥር እንዲጨምር በማድረግ በ2009 ዓም ላይ 23 ሺህ የነበረው የዞኑ ሠራተኞች ቁጥር አሁን ላይ ከ61 ሺህ በላይ ደርሶ በዕቅድ ላይ ያልተመሠረተ የሠራተኛ ቅጥር በዞኑ ላይ የበጀት ጫና ፈጥሮ ይገኛል“ ብለዋል።

ወላይታ ሶዶ ደሞዝ እንዲከፈላቸው በሰልፍ የሚጠይቁ የመንግሥት ሠራተኞች ዎላይታ ሶዶ ደሞዝ እንዲከፈላቸው በሰልፍ የሚጠይቁ የመንግሥት ሠራተኞች የዎላይታ ዞን በሠራተኞች ቁጥር መጨመር እና በማዳበሪያ ዕዳ ምክንያት ደሞዝ ለመክፈል መቸገሩን አስተዳዳሪው ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት አጣዳፊ የሆነውን የሠራተኞችን ደሞዝ ለመክፈል የዞኑ መስተዳድር ከቀጣዩ የ2017 ዓም በጀት ታሳቢ የሚደረግ ብድር በመውሰድ ችግሩን በጊዚያዊነት ለመፍታት እየጣረ እንደሚገኝ ዋና አስተዳዳሪው ተናግረዋል።

በተቃራኒው የዎላይታ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ ከ 3 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ የተገለፀ ቢሆንም በአከባቢው ልማት ስራዎች ቆሞ በአብዛኛው መዋቅር ደመዝ መክፈል አለመቻሉ ለበርካቶች "ለምን" የሚል ጥያቄ ፈጥሯል።

@ethio_mereja_news
ጓደኛቸውን በመግደል ሲያሽከረክረው የነበረውን መኪና ወስደው ተሰውረዋል የተባሉ ሁለት ግለሰቦች በ24 ሰዓታት ውስጥ በቁጥጥር ስር ዋሉ!

የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው ግንቦት 8 ቀን 2016 ዓ/ም በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሰሜን ማዘጋጃ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡ከአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል እና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ዘርፍ  የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ገ/ሚካኤል ሰይፉ የተባለው ሟች የወንጀል ፈፃሚዎቹ የቅርብ ጓደኛ በመሆኑ በየዕለቱ እየተገናኙ አብረው የሚውሉ፣ የሚዝናኑ እና በእጅጉ የጠነከረ የጓደኝነት ግንኙነት ያላቸው የሱሉልታ ከተማ ነዋሪዎች እንደሆኑ  ተጠርጣሪዎቹ ለፖሊስ በሰጡት ቃል አረጋግጠዋል።

በዕለቱ ሟች በወንጀሉ ከተጠረጠሩት ከሁለቱ ጓደኞቹ ጋር አብሮ ሲዝናና እንዳመሸ ታውቋል።ተጠርጣሪዎቹ  ቴዎድሮስ ታከለ እና  ሲሳይ ጥላሁን ከምሽቱ 5 ስዓት ገደማ የጓደኛቸውን  አንገት በማነቅ ህይወቱ እንዲያልፍ ካደረጉ በኋላ አስክሬኑን መንገድ ላይ በመጣል  ሞባይል ስልኩንና መታወቂያውን ጨምሮ በወቅቱ ሲያሽከረክረው የነበረውን የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 4-15624 ኢት መኪና ወስደው ተሰውረዋል ተብሏል፡፡

ፖሊስ የወንጀሉ ሪፖርት ከደረሰው በኋላ ባደረገው ያልተቋረጠ ክትትል ወንጀሉን ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩትን ግለሰቦች ለይቶ በማወቅ በ24 ሰዓታት ውስጥ በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል፡፡ አንደኛው ተጠርጣሪ ከአየር ጤና አካባቢ የተያዘ ሲሆን ሁለተኛው ተጠርጣሪ  ደግሞ ሱሉልታ ከተማ ውስጥ ሊገኝ ችሏል፡፡

ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ በተከናወነ ምርመራ የማስፋት ስራ የሰረቁትን ተሽከርካሪ በሸገር ከተማ ወለቴ ተብሎ ወደሚጠራው አካባቢ በመውሰድ እንዲሸጥላቸው ለአንድ ግለሰብ እንደሰጡት በማረጋገጥ መኪናው ከቆመበት በምሪት እንዲመለስ ተደርጓል፡፡ተሽከርካሪውን ለመሸጥ ተስማምቶ ከተጠርጣሪዎቹ የተቀበለውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ በህግ ተጠያቂ ለማድረግ የክትትል እና የምርመራ ስራው  የቀጠለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

@ethio_mereja_news
ማስታወቂያ!

የመውጫ ፈተና ድጋሚ ተፈታኞች የምዝገባ ጊዜን ስለማሳወቅ!

በ2016 ዓ.ም ሰኔ ወር ላይ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና በድጋሚ ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ አመልካቾች በሙሉ፤
ምዝገባ የሚከናወነው ከግንቦት 14 – 21/2016 መሆኑን አውቃችሁ የምዝገባ ክፍያ አምስት መቶ (500.00) ብር በመክፈል በ https://exam.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ማሳሰቢያ፤
1. ለመጀመሪያ ጊዜ የመጫ ፈተና የምትፈተኑ እጩ ተመራቂዎች ምዝገባ የሚካሄደው እና የአገልግሎት ክፍያ በተቋማችሁ በኩል መሆኑን እየገለጽን አስፈላጊ የመፈተኛ መረጃዎች በተቋማችሁ የሚደርሳችሁ መሆኑን እናሳውቃል።

2. የድጋሚ ተፈታኞች የአገልግሎት ክፍያ አምስት መቶ ብር (500.00 ብር) በቴሌ ብር ብቻ የሚከናወን ይሆናል።

የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር
#Tecno #Camon30Pro5G

Tecno Camon 30 pro 5G በአስገራሚ ቴክኖሎጂዎች እና በአገልግሎቱ ልቆ የቀረበ የዘመኑ ምርጥ ስልክ!

#Camon30Et #Camon30pro5GEt #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ የቀድሞ የሰላም ሚንስትር ዴኤታ ታዬ ደንድዓ ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ ትላንት ባዋለው ችሎት ውድቅ ማድረጉን የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ ክሱ እንዲሻሻልላቸው ያቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ የክስ መቃወሚያ ውድቅ ያደረገው፣ ክሱን ማሻሻል የሕግ አግባብነት እንደሌለው በመጥቀስ እንደኾነ ዘገባዎቹ አመልክተዋል።

ታዬ ፕሮፓጋንዳ ጽሁፍ እንዳልጻፉና ወንጀል እንዳልፈጸሙ በመግለጽ ለችሎቱ የዕምነት ክህደት ቃላቸውን እንደሰጡ ዘገባዎች አመልክተዋል።

ታዬ፣ ፖሊስ ይዞብኛል ያሉት የመጽሃፍ ረቂቅ እንዲለቀቅላቸው ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው እንደጠየቁና ፍርድ ቤቱም በአቤቱታቸው ላይ ውሳኔ እንደሚሰጥ መግለጡ ተነግሯል።

ፍርድ ቤቱ የዓቃቤ ሕግ ምስክሮችን ለመስማት ለግንቦት 29 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል ተብሏል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ሰበር ፍልስጤም

አየርላንድ እና ስፔንን ጨምሮ ሶስት የአውሮፓ ሀገራት ፍልስጤምን እንደ ሀገር እውቅና ሰጥተዋል።

ኖርዌይ ለፍልስጤም መንግስት በይፋ እውቅና ሰጥታለች፣ ሲሉ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በይፉ ተናግረዋል።

ይህንን ተከትሎ የእስራኤል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀገራቱ ለፍልስጤም ሉዓላዊነት እውቅና የሰጡትን ውሳኔ በመቃወም የአየርላንድ እና የኖርዌይ አምባሳደሮች በአስቸኳይ እንዲጠሩ አዝዟል።

@ethio_mereja_news
ኢትዮጵያ በሶማሊላንድ፣ ሃርጌሳ የሚገኘውን የቆንስላ ጽህፈት ቤቷን ሙሉ አገልግሎት ወደሚሰጥ ኤምባሲ ማሳደጓን የሶማሊላንድ ሚኒስትር ገለጹ‼️

የሶማሊላንድ የመረጃ፣ የባህል እና የብሔራዊ መመሪያ ሚኒስትር አሊ ሐሰን መሐመድ (አሊ ማርሃን) ለቢቢሲ ሶማሊኛ ከቀናት በፊት ራሷን በነጻ አገርነት ያወጀችው የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት ሙሳ ቢሂ አብዲ ቆንስላው ወደ ኤምባሲ ማደጉን አስመልክቶ የተናገሩትን አረጋግጠዋል።

ከአንድ ወር በፊት ሶማሊያ በሶማሊላንድ እና በቱንትላንድ ግዛት የሚገኙ የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅ/ቤቶች እንዲዘጉ ውሳኔ ማሳለፏ የሚታወስ ነው።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ትናንትና ከትናንት ወዲያ ሪያድ ውስጥ ስድስተኛው የኢትዮጵያና ሳዑዲ ዓረቢያ የሚንስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ተካሂዷል።

ኹለቱ ወገኖች በጸጥታ፣ ሰላም፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ እንስሳት፣ ግብርና፣ መሠረተ ልማት፣ ኢነርጂና ማዕድን ዘርፎች የኹለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር እንደተስማሙ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል።

የኢትዮጵያን ልዑካን ቡድን የመሩት፣ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ታዬ አጽቀሥላሴ እንደኾኑና ከአገሪቱ የውሃ፣ አካባቢና ግብርና ሚንስትር ጋር ጭምር እንደተወያዩ ተገልጧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ትናንትና ከትናንት ወዲያ ሪያድ ውስጥ ስድስተኛው የኢትዮጵያና ሳዑዲ ዓረቢያ የሚንስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ ተካሂዷል።

ኹለቱ ወገኖች በጸጥታ፣ ሰላም፣ ንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ እንስሳት፣ ግብርና፣ መሠረተ ልማት፣ ኢነርጂና ማዕድን ዘርፎች የኹለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር እንደተስማሙ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል።

የኢትዮጵያን ልዑካን ቡድን የመሩት፣ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ታዬ አጽቀሥላሴ እንደኾኑና ከአገሪቱ የውሃ፣ አካባቢና ግብርና ሚንስትር ጋር ጭምር እንደተወያዩ ተገልጧል።

@ethio_mereja_news
#Tecno #Camon30Pro5G

ፍጥነት እና ቅልጥፍና መገለጫው የሆነውን MediaTek Dimensity 8200 ፕሮሰሰር አካቶ Tecno Camon 30 pro 5G ቀርቦሎታል

#Camon30Et #Camon30proEt #Camon30 #Camon30Pro #TecnoEt
ለአሸከርካሪዎች ዝግ የተደረጉ መንገዶች‼️

ዛሬ ከ11:00 ጀምሮ ከፖሊስ ስራ ጋር በተያያዘ ሜክሲኮ አካባቢ በሚገኘው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዋና መስሪያ ቤት ፕሮግራም ይካሄዳል፡፡

👉 ከልደታ በላይኛው መንገድ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ

👉 ከአፍሪካ ህብረት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ

👉 ከጠማማ ፎቅ በንግድ ምክር ቤት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ

👉 ከገነት መብራት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ

👉 ከሰንጋ ተራ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ

👉 ከዲአፍሪክ ሆቴል ወደ ሜክሲኮ አደባባይ

👉 ከቡናና ሻይ በላይኛው መንገድ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ

ፕሮግራሙ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሆኑ አሽከርካሪዎች የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥማቸው አማራጭ መንገዶች እንዲጠቀሙ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

@sheger_press
"ዘንድሮ በወረቀት ከሚሰጠው ፈተና ጎን ለጎን ለመጀመሪያ ጊዜ በኦንላይን የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መንግሥት በሚያዘጋጃቸው ኮምፒውተሮች ይከናወናል፡፡" - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

በዚህ ዓመት የ12ኛ ክፍል ፈተና በወረቀት እንዲሁም በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር ውሳኔ ማስተላለፉ ይታወቃል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ በተለይ የግል ትምህርት ቤት ተፈታኞች የራሳቸውን ላፕቶፕ እንዲያዘጋጁ ተወስኗሉ የሚሉ መረጃዎች ሲዘዋወሩ ታይቷል፡፡

"ይህንን በተመለከተ ለትምህርት ቤቶች የተላለፈ መልዕክት አለመኖሩንና ወላጆች ኮምፒውተር እንዲያዘጋጁ መጠየቃቸውም ተገቢ አለመሆኑን" የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለኢቢሲ ተናግረዋል፡፡

"ፈተናው መንግሥት በሚያዘጋጀው የኮምፒውተር አቅርቦት ይከናወናል" ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ "ተማሪዎች አንብበውና በቂ ዝግጅት አድርገው የተመዘገቡበትን መታወቂያ ብቻ ይዘው መምጣት ነው የሚጠበቅባቸው" ብለዋል፡፡ "ሆኖም ትምህርት ቤቶችም ሆኑ ተማሪዎች የግል ኮምፒውተሮቻቸውን ለፈተናው መጠቀም ከፈለጉ እንደማይከለከሉ" ተናግረዋል፡፡

በኦንላይን ፈተና የሚወስዱ ተፈታኞች ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ በልምምድ ላይ እንደሚገኙ ያነሱት ኃላፊው፤ 156 የኮምፒውተር ባለሙያዎች ሰልጥነው በክልሎች ስልጠና እንዲሰጡ መሰማራታቸውን ጠቁመዋል፡፡

በዘንድሮው ፈተና ልምዶችን በመያዝ፤ በሚቀጥሉት ከ3 እስከ 5 ዓመታት ጊዜ ውስጥ የ12ኛ ክፍል ፈተናን ሙሉ በሙሉ በኦንላይን የመስጠት ዕቅድ መኖሩን ገልፀዋል፡፡

የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 3-5/2016 ዓ.ም ለማኅበራዊ ሳይንስ እንዲሁም ከሐምሌ 9-11/2016 ዓ.ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ይሰጣል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ከግንቦት 5-7 ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄዱ የነበሩ እና የሰርግ ስነስርዓትን ታድመው ይመጡ የነበሩትን ጨምሮ አጠቃላይ 40 ሰዎች በፀጥታ ሀይሎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎችንና የተጎጂ ቤተሰቦችን አነጋግሮ አሻም ቲቪ ዘግቧል።

ከዚህ ቀደም ብሎ ግንቦት 4 በፋኖ ሀይሎች እና በመከላከያ ሰራዊት መካከል ውጊያ እንደነበር ተገልጿል።

የአካባቢው ነዋሪዎች በስጋት ምክንያት አካባቢያቸውን ለቀው ወደ ባህርዳር እና ወደ ገጠራማ አካባቢዎች መሰደዳቸውን ዘገባው ጠቅሷል።

የምዕራብ ጎጃም ዞን ኮማንድ ፖስት ም/ሰብሳቢ አቶ እእድሜአለም አንተነህ በበኩላቸው በአካባቢው ውጊያ እንደነበር ገልፀው ነገርግን አንድም ንፁሃን አልሞቱም ሲሉ ለጣቢያው መናገራቸውን ሸገር ተመልክቷል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2024/09/30 09:27:19
Back to Top
HTML Embed Code: