Telegram Web Link
#Tecno #Camon30Pro5G

ቴክኖ ሞባይል በአይነቱ የተራቀቀውን አዲሱን Tecno Camon 30 pro 5G ምርጫዎ ያድርጉ ሲል ይጋብዛል!

#Camon30Et #Camon30pro5GEt #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt
በአዲስ አበባ የመንደር ንግድ ቁጥጥር የአሰራር ስርዓት መመሪያ ሊተገበር ነው ተባለ 🥹

የንግድ ስርዓቱን ፍትሃዊና ቀልጣፋ ለማድረግ የሚያግዝ የመንደር ንግድ ቁጥጥር የአሰራር ስርዓት መመሪያን ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት ማጠናቀቁን የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ አስታወቀ።

መመሪያውን አስመልክቶ ቢሮው በሰጠው መግለጫ እንዳመለከተው መመሪያ ቁጥር 159 /2016 ተግባር ላይ ሲውል የንግድ ስርዓቱን ፍትሃዊና ቀልጣፋ ለማድረግ እገዛ ያደርጋል ብሏል።

መመሪያው በወረዳ ደረጃ ያሉ የንግድ ተቆጣጣሪዎች ቁጥጥር የሚያደርጉበትን ስርዓት ያመላከተ ነው ተብሏል።

እንዲሁም የንግድ ፍቃድ ሳይኖራቸው የሚሰሩትን ከአስተዳደራዊ እስከ ህጋዊ እርምጃ የሚወሰድበት አግባብ ላይ አፅንኦት የሰጠ መሆኑም ተገልጿል።

መመሪያው ህግና ስርአትን የተከተለና ወጥነት ያለው አሰራር በሁሉም ወረዳዎችና ክፍለ ከተሞች ለመዘርጋትም እድል ይፈጥራል ተብሏል።(Arada_Fm)

@ethio_mereja_news
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን ከሚገኘው ኦላላ መጠለያ ጣቢያ ከኹለት ሺህ በላይ የሱዳን ስደተኞች ከሐሙስ ጀምሮ የርሃብ አድማ ማድረጋቸውን የሱዳን ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ስደተኞቹ የርሃብ አድማ ያደረጉት፣ በመጠለያ ጣቢያው የደኅናነት ስጋት በመባባሱና የአገልግሎቶች አቅርቦት በማሽቆልቆሉ እንደኾነ ዘገባዎቹ አመልክተዋል።

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኩርሙክ የስደተኞች መጠለያም፣ ሱዳናዊያን ስደተኞች በተመሳሳይ ምክንያት የርሃብ አድማ ማድረጋቸው ተነግሯል።

በኹለቱ ክልሎች ከ47 ሺህ በላይ የሱዳን ስደተኞች እንደሚገኙ የተመድ ስደተኞች ኮሚሽን መረጃ ያመለክታል።

@ethio_mereja_news
#Tecno #Camon30Pro5G

Tecno Camon 30 pro 5G እያንዳንዱ ፎቶ እና ቪድዮ ከፍተኛ ጥራት እንዲላበሱ የSony IMX890 ካሜራ ሴንሰር ገጥሞ ቀርቧል!

#Camon30Et #Camon30Pro5GEt #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር፣ ከአላማጣ አካባቢ ገርጃለ እና በቅሎ ማንቂያ ከተባሉ ቦታዎች "የተወሰኑ" የትግራይ ተዋጊዎች እንዲወጡ ማድረጉን የክልሉ ቴሌቪዥን ትናንት ምሽት ዘግቧል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ተዋጊዎች ከተጠቀሱት አካባቢዎች እንዲወጡ ያደረገው፣ በፕሪቶሪያው የግጭት ማቆም ስምምነት የትግበራ እቅድ መሠረት ወደ ቀያቸው ለሚመለሱ ተፈናቃዮች ደኅንነት ሲል እንደኾነ ዘገባው አመልክቷል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ከኹለቱ አካባቢዎች ምን ያህል ተወጊዎች እንዳስወጣ ግን ዘገባው አልጠቀሰም።

የትግራይ ኃይሎች እና የአማራ ክልል ታጣቂዎች ከሳምንታት በፊት በተጠቀሱት አካባቢዎች መጋጨታቸውና የትግራይ ኃይሎችም አካባቢዎቹን መቆጣጠራቸው እንደተዘገበ አይዘነጋም።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን ከሚገኘው ኦላላ መጠለያ ጣቢያ ከኹለት ሺህ በላይ የሱዳን ስደተኞች ከሐሙስ ጀምሮ የርሃብ አድማ ማድረጋቸውን የሱዳን ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ስደተኞቹ የርሃብ አድማ ያደረጉት፣ በመጠለያ ጣቢያው የደኅናነት ስጋት በመባባሱና የአገልግሎቶች አቅርቦት በማሽቆልቆሉ እንደኾነ ዘገባዎቹ አመልክተዋል።

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኩርሙክ የስደተኞች መጠለያም፣ ሱዳናዊያን ስደተኞች በተመሳሳይ ምክንያት የርሃብ አድማ ማድረጋቸው ተነግሯል።

በኹለቱ ክልሎች ከ47 ሺህ በላይ የሱዳን ስደተኞች እንደሚገኙ የተመድ ስደተኞች ኮሚሽን መረጃ ያመለክታል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ኩዌይት የገጠማትን የቤት ሠራተኞች እጥረት ለመቅረፍ፣ ሰሞኑን አንድ ልዑካን ቡድን ወደ ኢትዮጵያ እንደምትልክ የአገሪቱ ጋዜጣ ኩዌይት ታይምስ አስነብቧል።

ከኢትዮጵያ ሠራተኞችን መቅጠር በሚችልበት ኹኔታ ዙሪያ ለመምከር በመጪው ሳምንት ሰኞ ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዘው ልዑካን ቡድን፣ የመንግሥት ባለሥልጣናትንና የሠራተኛ ቅጥር ቢሮዎችን ሃላፊዎች ያካተተ እንደኾነ ዘገባው አመልክቷል።

ኩዌይት የቤት ሠራተኞች እጥረት የገጠማት፣ የፊሊፒንስ መንግሥት በኹለቱ አገራት መካከል የተፈረመውን የሠራተኛ ቅጥር ስምምነት አላከበረም በማለት ካለፈው ዓመት ግንቦት ጀምሮ ከፊሊፒንስ ሠራተኞችን መቅጠር በማቆሟ እንደሆነ ተገልጧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሰኔ 10 ጀምሮ ወደ ኦሮሚያ ክልል ነቀምቴ ከተማ አቋርጦት የነበረውን በረራ እንደገና እንደሚጀምር ማስታወቁን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘግቧል።

አየር መንገዱ ወደ ነቀምቴ በድጋሚ በረራ የሚጀምረው፣ በሳምንት አራት ጊዜ እንደኾነ መናገሩን ዘገባው አመልክቷል።

አየር መንገዱ የበረራ ብዛቱን ለማሳደግ የአውሮፕላን ማረፊያውን የቀድሞ የመንገደኞች ተርሚናል የማደስ ሥራ በቅርቡ ይጀምራል መባሉንም ዘገባው ጨምሮ ጠቅሷል።

አየር መንገዱ ከጥቂት ሳምንታት በፊት፣ ለዓመታት አቋርጦት የቆየውን የደምቢዶሎ በረራ በድጋሚ መጀመሩ አይዘነጋም።

@ethio_mereja_news
ኢትዮጵያ፣ በአውሮፓ ኅብረት አዲስ የደን ጥበቃ ሕግ መሠረት የቡና ምርቷን ሰንሰለት ወደምታስተካክልበት ደረጃ ለመሸጋገር ፍላጎት ካሳየች ኅብረቱ የገንዘብ ድጋፍ ሊያደርግ እንደሚችል ከኅብረቱ ምንጮች መስማቱን ጠቅሶ ሊ ሞንድ ጋዜጣ ዘግቧል።

በቀጣዩ የፈረንጆች ዓመት ተግባራዊ የሚኾነው የኅብረቱ አዲስ ሕግ፣ አባል አገራት ደኖችን በመጨፍጨፍ የተመረተ ቡና ከውጭ አገራት ገዝተው እንዳያስገቡ የሚያግድ ነው።

ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ ከሌሎች ቡና አምራችና ላኪ የአፍሪካ አገራት ወደኋላ እንደቀረች የኅብረቱ ምንጮች መጠቆማቸውንም ዘገባው አመልክቷል።

አንዳንድ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ኢትዮጵያ የቡና ምርቷን ሰንሰለት ከኅብረቱ አዲስ ሕግ ጋር ለማጣጣም በትንሹ አምስት ዓመት ያስፈልጋታል ብለዋል ያለው ዘገባው፣ አንድ የሆላንድ ኩባንያ በደን ጭፍጨፋ የተመረተ የኢትዮጵያ ቡና ካለ በሳተላይት የመለየት ሥራ መጀመሩ አገሪቱን ከችግር ሊታደጋት ይችል ይኾናል ብሏል።

@ethio_mereja_news
የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ከመጽደቁ ከኹለት ወራት በፊት ያቀረብኳቸው አብዛኞቹ ምክረ ሃሳቦች ወደ ጎን ተገፍተዋል በማለት ለፍትህ ሚንስቴር ቅሬታ ማቅረቡን ከኮሚሽኑ ሚስጢራዊ ሰነድ መመልከቱን ጠቅሶ ሪፖርተር ዘግቧል።

በሽግግር ፖሊሲው ውስጥ ሳይካተት ከቀረው የኮሚሽኑ ምክረ ሃሳብ አንዱ፣ ፖሊሲው "ለሰብዓዊ መብት ጥሰት ተጎጂዎች" የሰጠው ትርጉም አብዛኛውን የኅብረተሰብ ክፍል አግልሏል የሚል እንደኾነ ዘገባው አመልክቷል።

የባለሥልጣናት የሕግ ከለላ፣ ከመብት ጥሰት ተጠያቂነት እንደማያድናቸው በፖሊሲው ውስጥ በግልጽ እንዲጠቀስና ፖሊሲው ግልጽና ተዓማኒ እንዲኾን የዓለማቀፍ ፍርድ ቤቶች ትብብር እንደሚያስፈልግ እንዲያካትት ኮሚሽኑ ያቀረባቸው ምክረ ሃሳቦችም በተመሳሳይ አልተካተቱም ተብሏል።

ኮሚሽኑ፣ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲው ለኹሉም ጥሰቶች "ኹሉን ዓቀፍ የሕግ መሠረት" ሊኾን እንደማይችል የሚገልጽ ሌላ ሕግ እንዲወጣ መጠየቁንም ዘገባው ጠቅሷል።

@ethio_mereja_news
#Tecno #Camon30Pro5G

ልዩ ዲዛይን እና ቴክኖሎጂ አጣምሮ የቀረበዉ Tecno Camon30 Pro 5G ምርጫዎ ያድርጉ!

#Camon30Et #Camon30Pro5GEt #Camon30 #Camon30Pro5G #TecnoEt
በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሺ በቀለ ያቀረቡት መልቀቂያ ተቀባይነት ማግኘቱ ተሰማ

በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው እያገለገሉ የሚገኙት የቀድሞው የውኃ ሀብት ሚኒስትር ስለሺ በቀለ (ዶ/ር) ከተሾሙበት የመንግሥት የሥራ ኃላፊነት ለመልቀቅ ያቀረቡት ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ምንጮች ገለጹ።

ስለሺ በቀለ (ዶ/ር) በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደርነት ሹመታቸው ብቻ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ ከመንግሥት መዋቅር በመልቀቅ በግል ተቀጥረው በሙያቸው ለማገልገል ማቀዳቸውንም ምንጮቹ ገልጸዋል።

ስለሺ (ዶ/ር) በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የሥልጣን ዘመን ወቅት የፓርቲ አባል ሳይሆኑ የመንግሥት መዋቅርን መቀላቀላቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ከዚያ አስቀድመው በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በውኃ ምኅንድስና ሙያቸው በግል ተቀጥረው ሲያገለግሉ ነበር።

ስለሺ በቀለ (ዶ/ር) ከአሜሪካ አምባሳደርነታቸው በመልቀቅ ወደ ቀደመ የግል ሥራቸው ለመመለስ መፈለጋቸውን የጠቀሱት የሪፖርተር ምንጮች፣ ጥያቄያቸውንም ለመንግሥት አቅርበው ተቀባይነት ማገኘቱን ገልጸዋል።

አምባሳደር ስለሺ በቀለ መልቂቂያ ስለማቅረባቸውና መልቀቂያውም ተቀባይነት ማግኘቱን በመጥቀስ መረጃውን እንዲያረጋግጡ የጠየቅናቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ነብዩ ተድላ (አምባሳደር)፣ ስለዚህ ጉዳይ የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ገልጸዋል ሲል የዘገበው ሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

@ethio_mereja_news
ኦሮሚያ ባንክ ለብድር ካቀረበው 43.5 ቢሊዮን ብር 26 በመቶ የሚሆነውን ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በብድር ማቅረብን አስታወቀ!

ከተመሰረተ 15 ዓመታት ያስቆጠረው ኦሮሚያ ባንክ 54 ቢሊዮን ብር በቁጠባ መልክ ማሰባሰቡን፤ ከዚህ ውስጥም ለብድር ካቀረበዉ 43.5 ቢሊዮን ብር ዉስጥ በነፍስ ወከፍ ሲሰላ በአማካይ አንድ ተበዳሪ 1.5 ሚሊዮን ብር ከባንኩ ማግኘቱ ተገልጿል።ይህም የብድር ስርጭቱ ከባንኩ ደንበኞች ምጣኔ አኳያ 92 በመቶ ይይዛል እንዲሁም ከተበደሩት ብድር አንፃር ደግሞ 26 በመቶ ይሸፍናሉ ተብሏል።

ቀሪው የብድር አቅርቦት ለከፍተኛ ተበዳሪዎች ማቅረብን የገለፀዉ የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተፈሪ መኮንን ይህም የብድር አቅርቦት በአማካይ አንድ ተበዳሪ 5 ሚሊዮን ብድር መውሰዱ ተናግረዋል።የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተፈሪ መኮንን ጨምረዉ እንደተናገሩት የባንኩ የተበላሸ የብድር መጠኑ ከ1.6 በመቶ እስከ 2 በመቶ የሚደርስ እንደሆነ ገልፀዋል።

በብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት የተበላሸ ብድር መጠን ጣሪያ 5 በመቶ መሆኑን የጠቀሱት ፕሬዝዳንቱ አሁን ላይ በዘርፉ ያለው አማካይ የተበላሸ የብድር መጠን 3.6 በመቶ መሆኑን አብራርተዋል።አሁን ላይ ቅርንጫፎችን ከመክፈት ወደ ዲጂታል የባንክ አገልግሎት ፊቱን ያዞረዉ ባንኩ "ኦሮ ዲጂታል" በተሰኘው አገልግሎት ቴሌግራምን ጨምሮ በ7 አማራጮች አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።

Via Capital
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
መንግስት  እየፈጸመብኝ  ያለው ከፍተኛ ጥቃትና ጫና አስጊ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ኢሰመጉ ገለፀ።

ኢሰመጉ ይህን ያለው አሁን አመሻሽ ላይ ባወጣው መግለጫው ላይ ነው።

በመግለጫውም እንዳሰፈረው ኢሰመጉ፣ በስራ ኃላፊዎች፣ ሰራተኞችና አባላት ላይ በፌደራልና በክልል መንግስታት እንዲሁም በከተማ አስተዳደሮችና በሌሎች የመንግስት አካላት እየደረሱ ያሉ ጥቃቶች አስጊ ደረጃ ላይ ደርሷል ብሏል።

እየደረሱ ካሉት መካከል ግድያዎች፣ ህገ ወጥ እስሮችን፣ ጥቃቶችን፣ ከፍተኛ ጫናዎች፣ማስፈራሪያዎች፣ ዛቻዎች፣ ማሸማቀቆች፣ እንግልቶች፣ ስልታዊ የስራ ገደቦች፣ የምርመራ ፈቃድና የመረጃ ክልከላዎች፣ ህገ ወጥ ከትትሎች፣ ቢሮ ሰበራዎች፣ የንብረት ነጠቃ እና መውሰድ፣ ስም ማጥፋትና ውንጀላና እየደረሰብኝ ነው ሲል ገልጿል ።

የተገለጹት ጫናዎች  በሌሎች መሰል የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች እንዲሁም ተቋማት ላይ እየተፈጸሙ ያሉ ጫናዎች ሲሆኑ በአገሪቱ ያለው የሲቪል ምህዳር ምን ያክል አሳሳቢ ሁኔታ ላይ መድረሱን የሚያሳይ ነው ሲልም ተችሏል ።

በመሆኑ መንግስት ለሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች የሚያደርገውን ጥበቃ ምቹና አስቻይ የሆኑ የህግና የፖሊሲ ማዕቀፎችን በመዘርጋትና በመተግበር በአገሪቱ ያሉ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች እንዲሁም ተቋማቶቻቸው በነጸነት ተንቀሳቅሰው ደኅንነታቸው ተጠብቆ የሰብዓዊ መብቶች የማስከበር ስራዎችን የሚሰሩበት ሁኔታ እንዲፈጥር ጠይቁል።


በዓለም አቀፍ፣ በአህጉር አቀፍና በአገር አቀፍ ደረጃ ሰብዓዊ መብቶች ላይ የሚሰሩ ተቋማትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በኢሰመጉ ላይ በመንግስት አማካኝነት እየደረሱ ያሉ አስጊ ደረጃ ላይ የደረሱ ጥቃቶችና ከፍተኛ ጫናዎችን በመገንዘብ እነዚህ ጥቃቶችና ከፍተኛ ጫናዎች እንዲቆሙና ተጠያቂነት እንዲሰፍን እንዲያደርጉ እንዲሁም ከለላን በማቅረብ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ሲል አሳስበዋል ።

ኢሰመጉ ከምስረታው ጊዜ አንስቶ በርካታ የሰብዓዊ መብቶችን የማስከበር ስራዎችን ሲሰራ የቆየ መንግስታዊ ያልሆነ ተቋም ነውም ተብሏል።

Ethio FM
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የሕገመንግሥት አጣሪ ጉባዔ፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከኅዳር 26 ቀን ጀምሮ ተግባራዊ ባደረገው አዲስ ደንብ ዙሪያ ምላሽ እንዲሰጥ መጠየቁን ሪፖርተር ዘግቧል።

ደንቡ እንዲሻር ለጉባዔው የሕገመንግሥት ትርጉም ጥያቄ ያቀረበው "ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች" የተባለ ሲቪክ ድርጅት ነበር።

አቤቱታው፣ ደንቡ በሕግ የፈረሰው የክልሉ ምክር ቤት ያወጣቸው ሕጎች ተፈጻሚነታቸው እንዲቀጥል አድርጓል የሚል ነው።

ደንቡ ካስቀጠላቸው አዋጆች መካከል፣ የክልሉን ፖሊስ ኮሚሽን አፍርሶ ሌላ ኮሚሽን ያቋቋመውና በጦርነቱ አንሳተፍም ያሉ በርካታ ፖሊሶች የተባረሩበትና የጡረታ መብታቸው የታገደበበት አዋጅ እንደሚገኝበት ዘገባው አመልክቷል።

ከጥቅምት 24 ቀን 2013 እስከ ኅዳር 30 ቀን 2015 ዓ፣ም ሠራተኞች በውዝፍ ደመወዝ ዙሪያ የሚያቀርቡት አዲስ ክስ ታግዶ እንዲቆይ መደረጉም ሌላኛው አቤቱታ ነው ተብሏል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የሶማሌላንድ ራስ ገዝ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ፣ ሶማሊላንድ ከኢትዮጵያ ጋር የተፈራረመችው የባሕር በር የመግባቢያ ስምምነት የዓለማቀፍ የንግድ መርከቦችን እንቅስቃሴ ደኅንነት አስተማማኝ ለማድረግ ያስችላል ማለታቸውን ፋይናንሻል ታይምስ ጋዜጣ አስነብቧል።

በስምምነቱ መሠረት፣ ኢትዮጵያ ሶማሊላንድ ውስጥ የባሕር ኃይል ጣቢያ ከመገንባት በተጨማሪ የንግድ መርከቦች እንደሚኖሯትና ሶማሊላንድም ከኢትዮጵያ የአገርነት እውቅና እንደምታገኝ ቢሂ መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል።

ቢሂ፣ ስምምነቱ ተግባራዊ ከኾነ፣ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል በባሕር በር ሳቢያ ግጭት እንዳይቀሰቀስ ያደርጋል ማለታቸውም ተገልጧል።

በመግባቢያ ስምምነት ውስጥ ተሳታፊ የኾኑ አንድ የኢትዮጵያ ባለሥልጣንም፣ ስምምነቱ ተግባራዊ ይኾናል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል ተብሏል።

@ethio_mereja_news
በነፃ ዱባይ ሄደው መዝናናት ይፈልጋሉ? 😎

ቀላል ነው! ከግንቦት 7- ሰኔ 7 የYangoን መተግበሪያ ከAppstroe ወይም Playstore አውርደው፣ የመጀመሪያ ጉዞዎን ያድርጉ። 🚗

አሸናፊው በዕጣ ይመረጣል፤ ውድድሩ እንደተጠናቀቀ አሸናፊውን እናሳውቃለን። መልካም ዕድል!
ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በዓለም አቀፍ የአይሲቲ ፍጻሜ ውድድር አሸነፉ

ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በቻይና በተካሄደው የሁዋዌ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ፍጻሜ ውድድር ሦስተኛውን ሽልማት አሸነፉ።በቻይና ሼንዘን ከተማ በኮምፒውቲንግ ትራክ የተሳተፉት ሦስት ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ሦስተኛውን ሽልማት ከማሌዢያ፣ ሜክሲኮ እና ኬንያ ቡድኖች ጋር ተጋርተዋል።

ውድድሩ ከግንቦት 14 እስከ 18 ቀን 2016 ዓ.ም ከመላው ዓለም የተውጣጡ ተማሪዎች በተሳትፉበት በሦስት የውድድር ትራኮች ተከፋፍሎ የተካሄደ መሆኑ ተገልጿል፡፡በውድድሩ ከአርባ ምንጭና ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች በተገኙ ተማሪዎች የተወከለው የኢትዮጵያ ቡድን በኮምፒውቲንግ ትራክ ውድድር ሽልማት አሸንፎ ዛሬ ወደ ሀገሩ መመለሱን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።

ሚኒስቴሩ የተማሪዎችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት እድል የሚፈጥሩ ውድድሮች ላይ ተሳትፎውን በማሳደግ ከዓለም ዓቀፍ ድርጅቶች ጋር መስራቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጾ÷ ውድድሩን ላሸነፉ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል።

@ethio_mereja_news
Public Holidays draft law.pdf
420.3 KB
ግንቦት 20 ስራ ዝግ ይሆናል⁉️

ግንቦት 20 ለአመታት በህዝባዊ በዓላት ዝርዝር ዉስጥ ተካትቶ በህግ ሳይጸድቅ ሲከበር ቆይቷል። ግንቦት 20 የያኔዉ ኢህአዴግ የደርግ መንግስትን ገልብጦ ስልጣን የያዘበት ወይንም ማዕከላዊ መንግስትን የተቆጣጠረበት እለት ሆኖ በየአመቱ ስራ እና ትምህርት ዝግ ሆኖ ሲከበር ቆይቷል።

የህግ ባለሙያዎች ግንቦት 20 ለአመታት ሲከበር የቆየበት መንገድ ህጋዊ መሰረት የሌለዉ መሆኑን ሲናገሩ ይደመጣል። በአሉ በልማድ በህዝብ በዓላት ዝርዝር ዉስጥ ቢገባም በም/ቤት ጸድቆ እንዲከበር ግን አልተወሰነም ይላሉ። የሆነዉ ሆኖ ግንቦት 20 በተለይም ላለፉት 29 አመታት በድምቀት ሲከበር ቆይቷል። ከኢትዮጵያ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ባሉባቸዉ ሀገራትም ቀኑ ታስቦ ይዉል ነበር።

ኢህአዴግ ከመፍረሱ ጥቂት አመታት በፊትም ሆነ ከፈረሰ በኋላ ቀኑ በተቀዛቀዘ መልኩ ሲከበር እና ኋላ ላይም ሲቀር ተመልክተናል። እለቱ ትምህርት እና ስራ ዝግ ሆኖ ይከበር በመሆኑ ኢህአዴግ ስልጣኑን ካጣ በኋላ የቀኑ መከበር እና አለመከበር ፤ ስራና ትምህርት ዝግ መሆን እና አለመሆኑ በየአመቱ ለሰዎች አዲስ ሆኖ ጥያቄ ይፈጥራል። ከዚህ ቀደም በአሉ ሲከበርበት የቆየበት መንገድ ህጋዊ መሰረት የሌለዉ መሆኑን ያነጋገርናቸው የህግ ባለሙያዎች ነግረዉናል። በተጨማሪም በቅርቡ በቀረበዉ ረቂቅ አዋጅ ላይም በአሉ አለመካተቱን ነግረዉናል። ይህንንም ጥያቄ ለመመለስ በቅርቡ በሚኒስሮች ም/ቤት እና በፍትሕ ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የተመራዉን የሕዝብ በዓላትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ዳጉ ጆርናል ለመመልከት ሞክሯል።

በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ይጸድቃል የሚባለዉ ረቂቅ አዋጅ ላይ ታድያ ግንቦት 20 ከህዝባዊ በዓላት ዝርዝር ዉስጥ አልተካተተም። በዚህም መሰረት አዋጁ ሲጸድቅ ግንቦት 20 በህዝባዊ በአልነት የማይከበር እና ስራም ሆነ ትምህርት ዝግ የማይደረግበት ቀን ነዉ ለማለት ያስችላል።

አሁን ላይ አዋጁ ባይጸድቅም ቀድሞዉንም ሆኖ በአሉ የሚከበርበት መንገድ ህጋዊ መሰረት የሌለዉ በመሆኑ በእለቱ ስራም ሆነ ትምህርት እንዲዘጋ የሚያስገድድ አግባብ የለም።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
2024/09/30 11:27:52
Back to Top
HTML Embed Code: