Telegram Web Link
የመውጫ ፈተና‼️

ትምህርት ሚኒስቴር ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ፤ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 14 እስከ 21/2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ አሳውቋል።(tikvah)

@sheger_press
ሹመት‼️

የቀድሞ የመከላከያ ሚንስትር ቀንዓ ያደታ የጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ ምክትል የደህንነት አማካሪ ሆነው ተሾሙ።

ዋዜማ በደረሳት መረጃ መሰረት ቀንዓ ያደታ በሚንስትር ዴዔታ ማዕረግ ከመሾማቸው አስቀድሞ በተለያዩ የፌደራልና የክልል የፀጥታ ተቋማት ውስጥ አገልግለዋል።

በኦሮሚያ የፀጥታ ዘርፍ ኀላፊ እንዲሁም የፌደራሉ ፖሊስ ምክትል ኮምሽነር ሆነው ሰርተዋል። በትግራዩ ጦርነት ሲጀመር የመከላከያ ሚንስትር የነበሩት ቀንዓ በመሀል በአብርሃ በላይ መተካታቸው ይታወሳል።

የጠቅላይ ሚንስትሩ የደህንነት አማካሪ ሚንስትር በነበሩት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ተይዞ የነበረው የዋና አማካሪነት ቦታ እስካሁን አልተተካም።

[ዋዜማ]

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
እንድታውቁት‼️

ዛሬ መንገድ ይዘጋል።

ዛረረ ሚያዚያ 13 ቀን 2016 ዓ/ም በአዲስ አበባ መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገ ሩጫ ይካሄዳል።

ሩጫው የ2016 " የኢትዮጵያ ታምርት " የጎዳና ላይ የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ነው።

የአዲስ አበባን ዋና ዋና መንገዶችን የሚያካልል እንደሆነም ታውቋል።

መነሻው መስቀል አደባባይ ከዛም በለገሃር ፣ ሜክሲኮ አደባባይ ፣ ቡልጋሪያ ማዞሪያ ፣ ቄራ ፣ ጎተራ ማሳለጫ ፣ አጎና ሲኒማ ፣ ጥላሁን አደባባይ አድርጎ መዳረሻውን መስቀል አደባባይ ያደርጋል።

ይህን ተከትሎ ሩጫው ተጀምሮ እስኪያልቅ የሚዘጉ መንገዶች እንዳሉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

በዚህ መሰረት ፦

- ከመገናኛ ወደ መስቀል የሚወስደው መንገድ ኡራኤል አደባባይ
- ⁠ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል
- ከመስቀል ፍላዎር አደባባይ ወደ አጎና መስቀለኛ
- ከጎርጎሪዎስ አደባባይ ወደ ጎተራ
- ከጎተራ ሼል ወደ ጎተራ
- ከማሞ ማቋረጫ ወደ ጎተራ
- ከጎፋ ገብርኤል ወደ ጎፋ ማዞሪያ
- ከአልማዝዬ ሜዳ ወደ ቄራ በረት
- ከመካኒሳ አቦ አደባባይ ወደ ሳር ቤት አደባባይ
- ከካርል አደባባይ ወደ ሳር ቤት አደባባይ
- ከልደታ ፀበል ወደ ኤዩ መብራት
- ከቡልጋሪያ ማዞሪያ ወደኤዩ መብራት
- ከኦርቢስ መታጠፊያ/ጮራጋዝ/ መስቀለኛ ወደ ሲጋራ ፋብርካ
- ከጠማማ ፎቅ ወደ ጥይት ፋብርካ
- ከላንድ ማርክ ሆስፒታል ወደ ገነት መብራት
- ከከፍተኛ ፍ/ቤት /ባልቻ ሆስፒታል/ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከአረቄ ፋብርካ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
- ከሠንጋ ተራ 40/60 መስቀለኛ ወደ ሠንጋ ተራ መብራት
- ከበድሉ ህንፃ ወደ ቴሌ ባር
- ከብሔራዊ ቲያትር መብራት ወደ ለገሃር መብራት
- ከሀራምቤ መብራት ወደ ሳንጆሴፍ መብራት
- ⁠ከብ/ቤተመንግስት ወደ መስቀል አደባባይ
- ⁠ከኢንተርኮንትኔታል ሆቴል ወደ ባምቢስ የሚወስዱ መንገዶች ከማለዳው 11:00 ሰዓት ጀምሮ ሩጫው እስኪጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።

#AddisAbabaPolice
በፀጥታ ችግር ምክንያት የንግድ ፍቃዳቸውን ማድስ አልቻሉም ለተባሉ በአማራ ክልል ለሚገኙ ነጋዴዎች የንግድ ፍቃዳቸውን በድጋሚ ማደስ እንደሚችሉ ሚኒስትሩ ገልጿል።

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር በአማራ ክልል ያሉ ነጋዴዎች የንግድ ፍቃድ ማደሻ ጊዜን ለተጨማሪ ሶስት ወራት እንዲራዘም ማድረጉን አስታዉቋል።

በክልሉ ያሉ ነጋዴዎች የኦላይን የንግድና ምዝገባ ፍቃድ አገልግሎት ያለ ቅጣት ማደሻ ጊዜ መጠናቀቁን ተከትሎ እንዲራዘም የተደረገዉ በጥር ወር ላይ ቢሆንም አሁን ደግሞ ለሁለተኛ ጊዜ በፀጥታ ችግር ምክንያት የንግድ ፍቃዳቸውን ማደስ ላልቻሉ ነጋዴዎች እስከ ሰኔ 30፤2016 ዓ.ም. ማደስ ይችላሉ መባሉን ካፒታል ዘግቧል።
ቀሲስ በላይ መኮንን ከሰሞኑ "ተሳትፈዉበታል" በተባለው የማጭበርበር ድርጊት የተነሳ የአፍሪካ ህብረት የዉጪ ምንዛሬ የሚያስቀምጥበትን የባንክ ሂሳብ ከኢትዮጵያ ዉጪ ለማድረግ እንዳሰበ ተሰማ

👉🏼 ህብረቱ ለሶስተኛ ጊዜ በሀሰተኛ ሰነድ ልጭበረበር ነበር ያለ ሲሆን "ታማኝ" በተባሉ ሰዎች የተፈጸመው ሙከራ ወደፊት "በባለስልጣናት ላለመሞከሩ ማረጋገጫ ስለሌለኝ ነዉም" ብሏል

ከሰሞኑ ቀሲስ በላይ መኮንን በሀተኛ ሰነድ 6 ሚሊዮን 50 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ገንዘብ ለማዘዋወር ሞክረዋል መባላቸውን ዳጉ ጆርናል ተከታታይ መረጃዎችን አድርሷል። ይህንኑ ተከትሎ ቀሲስ በላይ የተጠረጠሩበት ድርጊት መነጋገሪያ ሆኖ የቆየ ሲሆን ዘ ሪፖርተር ደግሞ አዲስ መረጃ አጋርቷል።

ቀሲስ በላይ በአፍሪካ ህብረት ቅጥር ጊቢ ዉስጥ በሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በመገኘት ሀሰተኛ ሰነድ በመጠቀም ከህብረቱ የሂሳብ ቁጥር ለግንባታ እና ሌሎች ስራዎች ክፍያ በሚል 6 ሚሊዮን 50 ሺህ ዶላር ለማዘዋወር ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ዉለዋል።

ስማቸዉ ያልተጠቀሰ የዘ ሪፖርተር ምንጭ ታድያ ይህንን ድርጊት ተከትሎ የአፍሪካ ህብረት የዉጪ ምንዛሬ የሚያስቀምጥበትን የባንክ ሂሳብ ከኢትዮጵያ ዉጪ ለማድረግ እንዳሰበ ተናግረዋል። ህብረቱ ለሶስተኛ ጊዜ በተጭበረበረ ሰነድ ከባንክ ሂሳቡ ሊወጣ የነበረ ገንዘብን በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን ያስታወቀ ቢሆንም "እምነትና እዉቅና" ባላቸዉ ሰዎች የተፈጸመዉ ተግባር ወደፊት በባለስልጣናት ለላመሞከሩ መተማመኛ የለኝም በማለቱ መሆኑን ዘገባው አመላክቷል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በአፍሪካ ህብረት ቅጥር ጊቢ ዉስጥ ያለዉ ቅርንጫፉ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት የተከፈተ ሲሆን በዋነኛነት የአፍሪካ ሒሳቦችን በተለይ ለማስተዳደር ነው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮም የአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ ማዕከልን ጨምሮ የተቋሙ ከፍተኛ የዉጭ ምንዛሪ ክምችት ያላቸዉ አካውንቶችን በማካተት ቁጥጥር ያደርጋል።

ቀሲስ በላይ በወቅቱ ሀሰተኛ የህብረቱ ማህተም ያረፈባቸዉን ወረቀቶች በመያዝ ለግባታ እና የማሽነሪዎች አቅርቦት በሚል ክፍያዉን መጠየቃቸውን ዳጉ ጆርናል ከዘገባው ተመልክቷል። ክፍያዉ ከመፈጸሙ በፊት ወደ ህብረቱ የስልክ ጥሪ ያደረጉት የባንኩ ሰራኞች የክፍያዉን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ሲሞክሩ የህብረቱ የፋይናንስ ክፍል የማያዉቀዉ መሆኑን እና ክፍያዉ እንዲታገድ ህብረቱ መጠየቁ መረጃዉ ይደርሳቸዋል።

ህብረቱ ይህንን ተከትሎም ግለሰቡ እንዲያዙለት ጠይቆ ቀሲስ በላይ በህብረቱ ጠባቂዎች በቁጥጥር ስር ዉለዉ በፌዴራል ፖሊስ ተላልፈዉ መሰጠታቸዉን ዳጉ ጆርናል መዘገቡ ይታወሳል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የፋይናንሺያል አስተዳደር ዲቪዥን ኃላፊ ማዳሊስቶ ሙኡሶ ሎሌም ወዲያውኑ ለፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል እና የትራፊክ አደጋ ምርመራ ክፍል ደብዳቤ ጽፈዋል ብሏል ዘገባዉ። ኃላፊዉ የተለያየ መጠን ያለው ገንዘብ ከአፍሪካ ህብረት ሒሳብ ወደ አራት ግለሰቦች ሒሳብ እንዲዘዋወር የጠየቁ ሰነዶች ሁሉም ፎርጂድ ናቸው ብለዋል በጻፉት ደብዳቤ።

ከዚህ ክስተት በኋላ የህብረቱ እና የባንኩ  ሰራተኞች ለፖሊስ ቃላቸዉን መስጠታቸው በዘገባዉ ተጠቅሷል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ ለዜና ምንጩ ከሰጡት ቃል ዳጉ ጆርናል እንደተመለከተው "በመሠረቱ ጥሬ ገንዘብ በውጭ ምንዛሪ ብቻ ሊሰጥ አይችልም ። ለማጭበርበር የሞከረዉም ግለሰብ መጥቶ መጠኑን በጥሬ ገንዘብ ሲጠይቅ ይህን እንኳን አያውቅም ነበር ማለታቸዉን ነዉ።

አክለዉም " ግለሰቡ እዚህ አገር የዶላር አካውንት ከሌለው ገንዘቡ ቢተላለፍም እንኳ የትም ሊደርስ አይችልም።  አጭበርባሪዎች በየቀኑ ወደ ባንካችን ይመጣሉ።  ባንክ ስለምንሰራ የተለመደ ነው።  እኛ ግን ሁልጊዜ ከመሳካታቸው በፊት እናጣራለን።  ለፍርድም እየወሰድናቸው ነው። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የደንበኞቹን ሒሳቦች የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት።  ያንንን እያደረግን ነው።  የአፍሪካ ህብረትም እስካሁን ድረስ ቀጥተኛ ቅሬታ አላቀረበብንም" ሲሉ አቶ አቤ መናገራቸውን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል።

"ማጭበርበር ሲያጋጥም ይህ ለሶስተኛ ጊዜ ነው" ያሉት ስማቸው ያልተጠቀሱት የዜና ወኪሉ የአፍሪካ ህብረት ምንጭ" አሁን ማጭበርበሩ በተከበሩ ሰዎች እየተሞከረ ስለሆነ ተጨንቀናል" ብለዋል። ይህ ድርጊት  "ባለስልጣናት አንድ ቀን ተመሳሳይ ነገር ላለማድረጋቸዉ ምንም አይነት ዋስትና የለንም" ያሉም ሲሆን  "እምነት እያጣን ነው" ብለዋል።

ባለስልጣኑ አክለዉም በዚህ የተነሳ "ኢትዮጵያ ውስጥ ለደሞዝ አነስተኛ መጠን ያለው ፎሬክስ(የዉጪ ምንዛሪ ) ለመያዝ ወስነናል ፤ የድርጅቱን ገንዘብ ከኢትዮጵያ ውጭ ማቆየት እንድናስብ ያስገድደናል" ሲሉ ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የአፍሪካ ህብረት ባለስልጣን መናገራቸውን ዳጉ ጆርና ከዘገባው ተመልክቷል።

Via The Reporter

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ይኼ ከወላይታ ዩኒቨርስቲ የተማሪ መመገቢያ አዳራሾች አንዱ ላይ የተለጠፈ ማስታወቂያ ነው።

"ዩኒቨርስቲው በጀት ስለጨረሰ የተሰጣችሁን ብሉ" ነው አንድምታው። ወላጅ/አሳዳጊ ልጁን ወደ ዩኒቨርስቲ ሲልክ መንግስትን አምኖ ነው። "ልጄ ቀለም ይቆጥርልኛል" ከሚለው ባሻገር "ቤት እንዳለውም ባይሆን ቢያንስ ልጄ አይራብም፣ ደህንነቱ ይጠበቃል" የሚል ያልተፃፈ የጋራ ውሉን ተማምኖ የአብራኩን ክፋይ ስስቱን ወደ ትምህርት ተቋማት ይሰዳል።

መንግስት ለነዚህ የትምህርት ተቋማት በጀት መድቦ አደራውን ለመወጣት እንደሚሞክር ቢጠበቅም፤ ለምግብ የተሰጠኝ ገንዘብ ከወራት በፊት አልቋል የሚል ዜና ያውም ለተማሪዎቹ ምጣኔ እና ኃብት አስተዳደርን ከሚያስተምር ተቋም ሲነገር ያስደነግጣል... ያሳፍራል... አይደለም ወላጅን ማንኛውንም ሰው ጭንቀት ላይ ይጥላል።


እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ እንጠይቃለን:

1. ለአመት የተበጀተ በጀት በምግብ ዋጋ ንረት ግማሽ ላይ የሚያልቀው ምግቡን የሚገዙት ከዚምባቡዌ እና ቬንዙዌላ ነው ወይ? በጀቱ ሲበጀት ይህን የገበያ ለውጥ ታሳቢ ማድረግ ለምን አልተቻለም?

2. ትምህርት እንዳይቋረጥ ባለው ጥሬ ዕቃ አገልግሎት እየሰጠሁ ነው ያለው ዩኒቨርስቲው የጠቀሳቸው ጥሬ ዕቃዎች መቼ የገቡ፣ በምን አይነት የንፅህና ይዞታ ላይ ያሉ፣ ምን ያህል ጊዜ የሚያቆዩ ናቸው?

3. በህክምና ምክንያት የተለየ ምግብ መብላት ያለባቸውን ተማሪዎችስ እንዴት ለማስተናገድ ታስቧል?

3. ወትሮም ሆድ ጠብ የማይለው ምግብ መጠን እና ጥራቱ ሲያንስ የተማሪዎች ጤና እና ንቃት የሚያሳርፈውን ጉዳት እንዴት ሊያካክሱት አሰቡ? የልጆቹ የትምህርት አቀባበል ላይ ተፅዕኖ አይኖረውም?

Via: Surafel Dereje(Dagu)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ትጥቅ አንግበው የሚታገሉ አካላት ወደ ሀገራዊ ምክክር መድረክ እንዲመጡ ጥሪ ቀረበ

ትጥቅ አንግበው የሚታገሉ አካላት ወደ ሀገራዊ ምክክሩ መድረኮች እንዲመጡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ፡፡

ግጭት ሕይወትና ንብረትን ያጠፋል እንጂ ችግርን እንደማይፈታ የገለጹት የኮሚሽኑ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገ/ሥላሴ÷ ታሪካዊ አጋጣሚ በሆነው ሀገራዊ ምክክር በመሳተፍ ሐሳብን በማቅረብ መግባባት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

በዚህም ትጥቅ አንግበው እየታገሉ ያሉ አካላት ወደ ምክክሩ እንዲመጡ ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ መቆየቱን አስታውሰው÷ አሁንም ወደ ምክክሩ እንዲመጡ በመጠየቅ ሲመጡም ጥበቃ እንደሚደረግላቸው አረጋግጠዋል፡፡

ኮሚሽኑ የሚያመቻቻቸው መድረኮችም ማንኛውም ሰው በነጻነት የሚሳተፍባቸው መሆናቸውን አስረድተው÷ ትጥቅ አንግበው የሚታገሉ አካላት ወደ ሀገራዊ ምክክር መድረኩ እንዲመጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡(ኤፍ ቢ ሲ)

@ethio_mereja_news
የአማራ ክልል መንግሥት ለሕዝቡ ጥሪ አቀረበ‼️
የሕወሓት ታጣቂ ቡድን የሰላም አማራጮችን ወደ ጎን በመተው የማንነት ጥያቄ ያለባቸውን የራያ አላማጣ፣ የራያ ባላ፣ ኦፍላ፣ ኮረም እና ዛታ አካባቢዎችን በወረራ ይዟል::

ይህንን ተከትሎ የአማራ ብሔራዊ ክልል መንግሥት ከሰሞኑ ባወጣው መግለጫ የአማራ ሕዝብ ዛሬም እንደትላንቱ ከሀሰት ፕሮፓጋንዳ እና ከሰርጎ ገቦች ራሱን እና አካባቢውን እንዲጠብቅ ጥሪ አስተላልፏል::

ሕዝቡ ከክልሉ መንግሥት እና በየአካባቢው ከሚገኙ አስተዳደሮች ጋር የጠበቀ ቁርኝት በመፍጠር ጠላቶቹ የከፈቱበትን ጥቃት ለመመከት በሚደረገው ጥረት የድርሻውን እንዲወጣ ነው ጥሪ ያደረገው::

የክልሉ መንግሥት ከአማራ ሕዝብ በተጨማሪ ለፌደራል መንግሥት እና ለዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ  ጥሪ አቅርቧል፤ ለፌደራል መንግሥት ባስተላለፈው ጥሪ የሕወሓት ታጣቂ ቡድን በወረራ ከያዛቸው ቦታዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ለቆ እንዲወጣ እና ሕዝቡን ከጥፋት መታደግ እና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት መታደግ እንደሚገባ ጠቁሟል::

ለዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ደግሞ ሕወሓት በክልሉ ሕዝብ ላይ የፈጸመውን ወረራ በጥብቅ እንዲያወግዝ እና ከክልሉ ሕዝብ ጎን እንዲቆም ጥሪ አቅርቧል::
ሚያዝያ 14 ቀን 2016 ዓ.ም
(አሚኮ )

@sheger_press
@sheger_press
አማጺው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ወረ ጃርሶ ወረዳ ከአማራ ክልል በተነሱ ተሽከርካሪዎች ላይ ባለፈው ሳምንት ዓርብ በርካታ ሰዎችን አፍኖ መውሰዱን ዋዜማ በስፍራው ካሉ ምንጮቿ ሰምታለች።

አማጺው ቡድን እገታውን የፈጸመው፣ በጎሃጽዮን እና ቱሉ ሚልኪ ከተሞች መሃል ባለች ቢቱ ወንዝ ተብላ በምትጠራ ሥፍራ እንደሆነ ምንጮች ተናግረዋል።

እገታው የተፈጸመው፣ መነሻውን ከምሥራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ከተማ ባደረገው በተልምዶ "ታታ" ተብሎ በሚጠራ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ እና በሦስት ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች ሲጓዙ በነበሩ መንገደኞች ላይ እንደኾነ ምንጮች ጠቁመዋል።

ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ፣ ታፍነው የተወሰዱት ሰዎች በታጣቂ ቡድኑ ቁጥጥር ስር መኾናቸውንም ዋዜማ ባደረገችው ማጣራት መረዳት ችላለች።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ኢሠማኮ፣ ዘንድሮ ሚያዝያ 23 ቀን በኢትዮጵያ ለ49ኛ ጊዜ የሚከበረው የዓለም ሠራተኞች ቀን በአዳራሽ ውስጥ ብቼ እንዲከበር መወሰኑን አስታውቋል። ኢሠማኮ፣ በበዓሉ የአከባበር ሁኔታ ላይ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው፣ "የአገሪቱን አጠቃላይ ኹኔታ" እና "በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ" ሥር የሚገኙ አከባቢዎችን ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደኾነ ገልጧል።

ኾኖም ይህ የበዓሉ አከባበር፣ ባሕርዳር፣ ኮምቦልቻና በአዲስ አበባ ዙሪያ የሚገኙ ከተሞችን እንደማይጨምር ኢሠመኮ አመልክቷል።

የኢሠማኮ ፕሬዝዳንት፣ እስከ በዓሉ ድረስ ጠቅላይ ሚንስትሩ የሠራተኞችን ተወካዮች በሠራተኛው ጥያቄዎች ዙሪያ እንዲያነጋግሩ መወሰኑንና ጥያቄው ለጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት መቅረቡን ኢሠማኮ ጨምሮ ገልጧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
አጫጭር መረጃዎች‼️ ሌላ ጦርነት የአማራ ህዝብ ተነስ:
ወሎ ህዝባዊ ሀይሉ ፖሊስ ጣቢያ ገባ; አሜሪካ እና እስራኤል ተጋጩ:

መረጃዎቹን በዝርዝር ይመልከቱ👇😢

https://youtu.be/wwRm2A2-U4Y
https://youtu.be/wwRm2A2-U4Y
በአቡዳቢና ዱባይ የሚገኙ ኢትዮጲያዉያን ከጉዞ ሰነድና ቪዛ ጋር ተያይዞ ያሉ የአገልገሎት አሰጣጥ ችግሮች እንዲፈቱ ተጠየቀ

በአቡዳቢና ዱባይ አካባቢ እየተሰጠ ባለው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎቶች ከዚህ ቀደም የሚነሱ ቅሬታዎች እየተፈቱ መሆኑን የኮሚኒቲ አባላት፣ ተወካዮችና አመራሮች ተናግረዋል።በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት የተመራ ልዑክ በአቡዳቢና ዱባይ ሚሲዮኖች የሚሰጡ የዜግነት አገልግሎቶችን ያሉበትን ሁኔታ ተመልክቶ ከሚሲዮን መሪዎችና ኮሙኒቲ ተወካዮች ጋር ተወያይቷል።

በውይይቱ በሚሲዮኖቹ ከፓስፖርት እድሳትና ተያያዥ አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ ዜጎች ላቀረቡት ጥያቄ የተሰጠው ምላሽ የሚደነቅ ቢሆንም፤ ከጉዞ ሰነድና ቪዛ ጋር ተያይዞ ያሉ የአገልገሎት አሰጣጥ ችግሮች እንዲፈቱ ተጠይቋል፡፡በተጨማሪም የመረጃ ልውውጥ ክፍተት፣ ሐሰተኛ ማስረጃ፣ የጉዞ ሰነድ (ሊሴ ፓሴ)፣ የበይነ-መረብ አጭበርባሪዎች መበራከት እንዲሁም ከዜግነት አገልግሎት ጋር ያሉ ክፍተቶች መኖራቸው ተጠቁሟል፡፡

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት÷ ተቋሙ 11 የሪፎርም አጀንዳዎችን ቀርጾ ወደ ስራ በመግባቱ ከዜጎች አገልግሎት ጋር በተያያዘ እየታዩ ያሉ ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴዎች መታየታቸውን ተናግረዋል።የሪፎርሙ ስራ ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ በዘርፉ የተስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚያስችልም ገልጸዋል።

ከሰነድ አልባና ከዜግነት አገልግሎት ጋር ያሉ ስራዎች ከሀገር ደህንነት ጋር በጥብቅ የተቆራኘ በመሆኑ በጥንቃቄና በህግ አግባብ ብቻ መሰራት እንዳለበት አስገንዝበዋል።ልዑኩ ባደረገው ጉብኝት የዱባይ ሚሲዮን ቴክኖሎጂን በመጠቀም ረገድ የሚከተለው አሰራር እንደተሞክሮ ሊወሰድ የሚገባ መሆኑን እንደተመለከተ ዋና ዳይሬክተሯ ተናግረዋል።
65 በመቶው የሚሆኑ እስራኤላዉያን ጦርነቱ ከተቀሰቀሰ በኋላ ጥሩ እንቅልፍ እንደማይተኙ አንድ ጥናት አመላከተ

የእስራኤል ዬዲዮት አህሮኖት ሚዲያ እና የሪችማን ዩኒቨርሲቲ የነፃነት እና ኃላፊነት ተቋም ባደረጉት የህዝብ አስተያየት 85 በመቶ የሚሆኑ እስራኤላውያን በመንግስታቸው ላይ እምነት የላቸውም።64 በመቶ ያህሉ እስራኤላውያን አገራቸው የህልውና ስጋት እንዳለባት የሚያምኑ ሲሆን 65 በመቶው ደግሞ ጦርነቱ ከተቀሰቀሰ በኋላ ጥሩ እንቅልፍ እንዳልተኙም ገልጿል።

ቢያንስ 73 በመቶ የሚሆኑት እስራኤላውያን ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ በጭንቀት ተውጠዋል።በሌላ በኩል የዮርዳኖስ ሃሺሚት መንግሥት በሁለት ክልላዊ ኃይሎች እስራኤል እና ኢራን መካከል ክልላዊ ውጥረቱ እየጠነከረ ከቀጠለ ከባድ ማህበራዊ፣ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ መዘዞች ሊገጥማቸው ይችላል በሚል የማሸማገል ሚናዉን እየተወጣ ይገኛል።

ዮርዳኖስ ማንኛውም ክልላዊ እርምጃ በኢራን እና በእስራኤል መካከል ያለው ጠላትነት መባባስ ወይም እስራኤል ራፋህ ከወረረች በአገር ውስጥ ተቀጣጣይ ምላሾች ሊኖሩት ይችላል ብላለች።በሴናጎህ ዩኒቨርሲቲ የዮርዳኖስ ኤክስፐርት እና ከሬሲሊየንስ ቱ ሪቮሊሽን ፀሃፊ ሼን ዮም "ማንኛውም የማይቀር የኢራን እና የእስራኤል ጦርነት ዮርዳኖስን በጠባብ ገመድ ላይ ሊያስቀምጣት እንደሚችል ለአልጀዚራ ተናግሯል። ከአደባባይ ውዝግብ መራቅ እንዳለበት ከየትኛውም ተዋጊ ጋር መቆም እንደማይቻል ገልጸዋል፡፡
ሕወሓት ብልፅግናን ለመቀላቀል በድርድር ላይ ነው ተባለ

ሕወሓት ከአራት ዓመት በፊት “ሕገ – ወጥ ነው” ያለውን ገዥውን ፓርቲ ብልፅግና ለመቀላቀል ተከታታይ ድርድሮች እያደረገ መሆኑን ዳ፤ ዋዜማ ከተለያዩ ምንጮች አሰባስቤ ሰራሁት ያለችዉ ዘገባ ያመለክታል።

ከሁለት ዓመት ደም አፋሳሽ ጦርነት በኋላ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት የፈረመው ሕወሓት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ በሊቀመንበርነት የሚመሩትን ብልፅግናን በመቀላቀል በሀገራዊ ጉዳዮች አብሮ ለመስራት መስማማቱን ቢገልፅም ፓርቲውን ለመቀላቀል ቅድመ ሁኔታ አስቀምጧል።

ከብልፅግና በፊት የነበረው ኢሕአዴግ እኩል የስራ አስፈፃሚና ማዕከላዊ ኮሚቴ ውክልና ያላቸው አራት ንዑስ ፓርቲዎች ጥምረት ሲሆን ብልፅግና ግን አንድ ወጥ ፓርቲ ነው። የብልፅግና የፓርቲ ውክልና በህዝብ ብዛት የሚወሰን እንጂ እንደ ኢሕአዴግ አባል ድርጅቶች እኩል ውክልና አይኖራቸውም።

አሁንስ እየተደረገባቸው ባለው ድርድር ሕወሓት የብልፅግና ፓርቲ ሕገ-ደንብ ተሻሽሎ በፓርቲ ውስጥ አባል ድርጅቶች እኩል የማዕከላዊ ኮሚቴና የስራ አስፈፃሚ ውክልና እንዲኖራቸው ይፈልጋል። ብልፅግና ግን ሕወሓት የተናጠል ህልውናውን አክስሞ ብልፅግናን እንዲቀላቀልና ውክልናውም በትግራይ ህዝብ ቁጥር ልክ የሚወሰን መሆኑን ይገልፃል።

የሕወሓት ሊቀ መንበር ደብረፅዮን ገብረሚካዔል በአዲስ አበባ ተገኝተው ይህን ድርድር የጀመሩት ሲሆን ከሁለት ሳምንት በኋላ የብልፅግና ምክትል ሊቀመንበር አደም ፋራህ ወደ መቀሌ ተጉዘው በጉዳዩ ላይ በስፋት ተነጋግረዋል።

በሕወኋት በኩል ብልፅግናን መቀላቀል “ስህተት ነው …አስፈላጊም አይደለም” ብለው የሚያምኑ አመራሮች ቢኖሩም ፣ ውህደቱ ለትግራይ ችግሮች መፍትሄ ለማምጣት ጠቀሜታ አለው፣ በተለይም የትግራይን ፀጥታና ደህንነት ለመስጠበቅ ከብልፅግና ጋር አብሮ መቆም አስፈላጊ ነው ብለው የሚያምኑም አሉ።

Via ዋዜማ
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ከአላማጣ እና አከባቢዋ ተፈናቅለው ቆቦ እና ሰቆጣ የተጠለሉ ሰዎች ቁጥር 50 ሺ መሻገሩ ተገለጸ

በቅርቡ በራያ አላማጣ አከባቢ ተከስቶ በነበረው አለመረጋጋት ሳቢያ ከቀያቸው ተፈናቅለው በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ እና በዋግ ህምራ ዞን ሰቆጣ ከተማ ተጠልለው የሚገኙ ሰዎች ቁጥር ከ50 ሺ በላይ መሆኑን  የመንግስታቱ ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ) ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

የተፈናቃዮቹ ቁጥር ያገኘሁት ከሁለቱ ዞኖች አስተዳደር ነው ያለው የቢሮው መግለጫ በአከባቢው ከሚያዚያ 5 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በተፈጠረው አለመረጋጋት እስከ ሚያዚያ 11 ቀን 2016 ዓ.ም ሪፖርት የተደረገ ተፈናቃዮች ቁጥር 29 ሺ እንደሚጠጋ አስታውሷል።

በቆቦ ከተማ ተጠልለው የሚገኙ ተፋናቃዮች ቁጥር 42 ሺ መድረሱን የጠቆመው ቢሮው በሰቆጣ የሚገኙ ተፈናቃዮች ቁጥር 8 ሺ 300 መሆኑን ገልጿል።

አብዘሃኛዎቹን ተፈናቃዮች የቆቦ ከተማ ማህበረሰብ አስጠልሏቸው እንደሚገኝ የጠቆመው ቢሮው ሌሎቹ ደግሞ ከከተማዋ በሶስት ኪሎ ሜትር ርቆ በሚገኝ ጋሪያ ሌንጫ በተባለ ቦታ ላይ የድንኳን መጠለያ ዘርግተው እየኖሩ መሆኑን ገልጿል።

ምንጭ፦ አዲስ ስታንዳርድ

@ethio_mereja_news
በትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ሕይወት አለፈ

በሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ሊባኖስ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ሕይወት አለፈ።

አደጋው ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም እየተጓዘ የነበረ የቤት አውቶሞቢል ከኮሶበር ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ ከነበር የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ጋር ቀሲም በተባለ ልዩ ቦታ በመጋጨቱ የደረሰ ነው።

በአደጋው የአራት ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ ሲያልፈ በ14 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት፤ በስምንት ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

የደብረ ሊባኖስ ወረዳ ትራፊክ ደህንነት አስተባባሪ ረዳት ኢንስፔክተር ኃይለማርያም ደባሌ÷ የአደጋው መንስኤ በፍጥነት ማሽከርከር እና ቅድሚያ አለመሰጠት መሆኑን መናገራቸዉን ከወረደዉ ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ሰውዬው ተገኝተዋል

ኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ለገጣፎ አቅራቢያ 44 ማዞሪያ ጅዳ ኩራ በተባለ ፖሊስ ጣቢያ መታሰራቸው ታውቋል።

እኝህ ሰው በተደበደቡ፣በተበደሉ፣ጥቃት በደረሰባቸው እንደት ሊታሰሩ ቻሉ ለሚለው ምላሽ አልተገኘም።

በወቅቱ እሳቸውን ከፍ ዝቅ እያደረኩ ርካሽ የዘረኝነት ተግባር ሲፈፅሙባቸው የነበሩ ወጣቶች ተሰብስበው መታሰራቸውም ተሰምቷል።(wasu)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
Breaking ‼️

ህወሓት ብልፅግናን ሊቀላቀቀል ነዉ መባሉን ተከትሎ ከብልፅግና ጋር የጀመርኩት ንግግር የለም ሲል አስተባበለ

የህወሓት እና የብልፅግና ድርድር ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ የተፈጠረውን አንፃራዊ ሰላም ለማስፋት እና ለማጠናከር ያለመ ነው ያለው ህወሓት ፤ ህወሓት እና ብልፅግና መሰረታዊ የዓላማ እና የአስተሳሰብ ልዩነት ያላቸው ፓርቲዎች መሆናቸውን ገልጿል።

አክሎም ልዩነቱ እንዳለ ሆኖ ሁለቱ ፓርቲዎች ሊወያዩባቸው የሚገቡ ብዙ አጀንዳዎች አሉና በነዛ ዙርያ ውይይት እያደረግን ነው ማለቱን ዳጉ ጆርናል ከፓርሪዉ መግለጫ ተመልክቷል። ከዚህ ውጭ ግን እንደሚወራው ህወሓት ብልፅግናን ለመቀላቀል ንግግር ጀምሯል የተባለው ጉዳይ ሐሰት ነው ሲልም በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ ፓርቲዉ አጋርቷል።

በዛሬዉ እለት ህወሓት ብልጽግና ፓርቲን ሊቀላቀል መሆኑን ዳጉ ጆርናል የዋዜማ ሚዲያ ዘገባን ዋቢ በማድረግ መረጃ ማድረሱ ይታወሳል። ይህንኑ ተከትሎም ህወሓት ይፋዊ መግለጫ አዉጥቷል።

@sheger_press
@sheger_press
2024/10/01 04:14:47
Back to Top
HTML Embed Code: