Telegram Web Link
#RayaUniversity

ራያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 497 ተማሪዎች አስመረቀ።

ከተመራቂዎቹ መካከል 141 ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ሲሆን፤ ቀሪዎቹ 356 ደግሞ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች ናቸው፡፡

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታና የራያ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ፤ የፌዴራል መንግሥት የዩኒቨርሲቲውን አቅም ማጎልበት የሚያስችል ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል።

@tikvahuniversity
#SalaleUniversity

ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 1,197 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

@tikvahuniversity
የግል የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ውጤት መቼ ይፋ ይሆናል?

የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የ2016 ዓ.ም ዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ውጤት ሰኔ 21/2016 ዓ.ም ይፋ መደረጉ ይታወቃል።

የመውጫ ፈተናውን የወሰዱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ውጤት እስካሁን ይፋ አልተደረገም። ይህንንም ተከትሎ የግል ተፈታኞች በርካታ ጥያቄዎችን ለቲክቫህ አድርሰዋል።

በጉዳዩ ዙሪያ በትምህርት ሚኒስቴር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልገሎት ዴስክን ጠይቀናል።

"ከግል ተፈታኞች ውጤት ጋር በተያያዘ ያልተጠናቀቁ ነገሮች በመኖራቸው ውጤቱ ይፋ አለመደረጉን" የዴስኩ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) ለቲክቫህ ተናግረዋል።

"ቀሪ መጠናቀቅ ያለባቸው ጉዳዮች እንዳለቁ የግል ተፈታኞች የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ ይደረጋል" ብለዋል።

የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ማኅበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ገበየሁ በበኩላቸው፤ "ከግል ተፈታኞች አጠቃላይ መረጃ እና ክፍያ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ሲጠናቀቁ ውጤቱ በቀጣይ ቀናት እንደሚለቀቅ" ለቲክቫህ ተናግረዋል።

ማኅበሩ 178 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በአባልነት ይዟል፡፡

ዘንድሮ 124 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን የመውጫ ፈተና ማስፈተናቸው ይታወቃል።

@tikvahuniversity
#DillaUniversity

ዲላ ዩኒቨርሲቲ በቡና ሳይንስና ኢኮኖሚክስ የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመርቃል።

ዩኒቨርሲቲው ነገ ሰኔ 27/2016 ዓ.ም የተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት ያካሒዳል።

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ 2,800 በላይ ተማሪዎችን የሚያስመርቅ ሲሆን፤ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ 127 ተማሪዎች ይገሀኙበታል፡፡

@tikvahuniversity
Active and graduate UG and PG student datasheet.xlsx
21.9 KB
#ETA

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ2015 ዓ.ም እና በ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ወስደው ያለፉ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎችን ዝርዝር እንዲልኩ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን አሳስቧል።

ተቋማቱ ፈቃድ በተሰጣችሁ የትምህርት መስኮች፣ የትምህርት ደረጃ፣ መርሐግብር እና ካምፓስ ያስመረቋቸውንና ከዚህ በፊት ያልተላኩ የተመረቁ ተማሪዎች መረጃንም እንዲልኩ ተብሏል።

በዚህም መረጃዎቹን እስከ ሰኔ 30/2016 ዓ.ም በሶፍት እና በሀርድ ኮፒ እንድትልኩ ባለሥልጣኑ አሳስቧል።

የተመራቂ ተማሪዎችን ዝርዝር መረጃ መላኪያ ቅፅ ለውጥ ማድረጉን ባለሥልጣኑ ገልጿል።

(አዲሱ መረጃ መላኪያ ቅፅ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
#MizanTepiUniversity

ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 279 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

የዩኒቨርሲቲው ቴፒ ካምፓስ በ 16 የትምህርት ክፍሎች በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመርቋል፡፡ ከተመራቂዎቹ መካከል ሰባቱ የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች መሆናቸው ተገልጿል፡፡

የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ (ሚዛን ካምፓስ) በተለያዩ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ነገ ሰኔ 27/2016 ዓ.ም ያስመርቃል።

@tikvahuniversity
በዲላ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ግዜ የወሰዱ የአንስቴዥያ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ የማለፊያ ውጤት አስመዝግበዋል።

በተመሳሳይ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ግዜ የወሰዱ የአንስቴዥያ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ የማለፊያ ውጤት ማስመዝገባቸው ተሰምቷል። #HakimEthio

@tikvahuniversity
#JigjigaUniversity

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 1,381 ተማራዎች አስመረቀ፡፡

ዩኒቨርሲቲው ያስመረቃቸው ተማሪዎች በመጀመሪያ ዲግሪ እና በሁለተኛ ዲግሪ መርሐግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው፡፡

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ በልዩ ሁኔታ በጤና ስፔሻሊቲ ዘርፍ አምስት የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስቶችን አስመርቋል። #SMMA

@tikvahuniversity
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከ 800 በላይ በቅድመ እና በድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ያስተማራቸውን ተማሪዎች ያስመርቃል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ነገ ሰኔ 27/2016 ዓ.ም በሚያካሒደው 16ኛ ዙር የምረቃ ሥነ-ስርዓት፤ 446 የድኅረ ምረቃ እና 409 የቅድመ ምረቃ ዕጩ ምሩቃን በድምሩ 855 ተማሪዎችን እንደሚያስመርቅ ይጠበቃል።

@tikvahuniversity
#BoranaUniversity

ቦረና ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዙር የተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት አካሒዷል።

ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የትምህርት መስኮች በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም ያሰለጠናቸውን 135 ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ አስመርቋል።

ቦረና ዩኒቨርሲቲ በሰኔ 2013 ዓ.ም ተመርቆ፥ በ2014 የትምህርት ዘመን በ15 የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር መጀመሩ ይታወሳል።

@tikvahuniversity
#WallagaUniversity

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ በጊምቢ እና በሻምቡ ካምፓሶች ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።

ጊምቢ ካምፓስ 385 ተማሪዎችን ሲያስመርቅ፥ ሻምቡ ካምፓስ 449 ተማሪዎችን አስመርቋል።

ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና ተከታታይ መርሐግብር ከመጀመሪያ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ነቀምቴ ከተማ በሚገኘው ዋናው ግቢ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ 2,335 ተማሪዎችን ትናንት ማስመረቁ ይታወቃል፡፡

@tikvahuniversity
#SamaraUniversity

ሠመራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 1,478 ተማሪዎች አስመረቀ።

15ኛ ዙር ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

@tikvahuniversity
#InjibaraUniversity

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ እና በድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ያስተማራቸውን ተማሪዎች ነገ ያስመርቃል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ነገ ሰኔ 27/2016 ዓ.ም በሚያካሒደው 5ኛ ዙር የምረቃ ሥነ-ስርዓት፥ 268 የድኅረ ምረቃ እና 428 የቅድመ ምረቃ ዕጩ ምሩቃን በድምሩ 696 ተማሪዎችን እንደሚያስመርቅ ከተቋሙ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahuniversity
* National Exam

የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተናን በኦንላይን የሚፈተኑ ተማሪዎች ልምምድ እያደረጉ እንደሚገኙ ይታወቃል።

ተማሪዎች እና ወላጆች / መምህራን ሲስተሙን እንዴት አገኛችሁት ? ለዋናው ፈተና ምን አሳሳቢ ጉድለት ተመለከታችሁ ? ምን ጥሩ ነገር ተመለከታችሁ ?

በአስተያየት መስጫው አጋሩን።

@tikvahuniversity
🎓🏥 ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ሐኪሞችን አስመርቋል።

16ኛ ዙር የምረቃ ስነ-ስርዓቱን ትናንት ያከናወነው ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፤ በውስጥ ደዌ ህክምና የስፔሻሊቲ ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ስድስት ስፔሻሊስት ሐኪሞችን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ አስመርቋል።

ስፔሻሊስቶቹ (Internal Medicine Specialists) በዩኒቨርሲቲው ጤና ሳይንስ ኢንስቲትዩት ሼክ ሐሰን ያባሬ ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ስልጠናቸውን ተከታትለው ማጠናቀቃቸው ተገልጿል።

ይህም ለዩኒቨርሲቲው እንዲሁም ለአካባቢው ማኅበረሰብ ትልቅ ትርጉም ያለውና በዘርፉ የሚሰጠውን ሕክምና ክፍተቶች መሙላት የሚችል ነው ተብሏል።

@tikvahuniversity
2024/09/30 11:33:40
Back to Top
HTML Embed Code: