Telegram Web Link
#HarariEducatiomBureau

የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ አድርጓል፡፡

ተፈታኝ ተማሪዎች ከዚህ በታች በተቀመጠው ሊንክ በመጠቀም ውጤታቸውን ማየት የሚችሉ መሆኑን ቢሮው አሳውቋል፡፡

ውጤት ለማየት 👇
https://harari.ministry.et/

በክልሉ የ8ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 4 እና 5/2016 ዓ.ም መሰጠቱ ይታወሳል።

@tikvahuniversity
#የሥራ_ቅጥር_ጥቆማ

የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኢንስቲትዩት የህክምና ዶክተሮችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡

➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 12
➤ የሥራ ቦታ፦ ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ
➤ የማመልከቻ ጊዜ፦ ከሰኔ 24/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት
➤ የምዝገባ ቦታ፦ ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የሰው ሀብት አስተዳደር ቢሮ ቁ. 2 ወይም በኢሜል አድራሻ [email protected]

ለተጨማሪ መረጃ፦ 0575553618 / 0575553628

(የተቀመጡ መስፈርቶችና አስፈላጊ ሰነዶችን የተመለከተ መረጃ ከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity
#2024_Commencement

19 የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠኗቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት ያስመርቃሉ፡፡

ዛሬ ሰኔ 27/2016 ዓ.ም ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ያሉት ዩኒቨርሲቲዎች የትኞቹ ናቸው?

አምቦ ዩኒቨርሲቲ
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ
ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ
ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ
ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ
ዲላ ዩኒቨርሲቲ
ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ
ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ
ወራቤ ዩኒቨርሲቲ
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
ወልድያ ዩኒቨርሲቲ
ጂንካ ዩኒቨርሲቲ
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
ወሎ ዩኒቨርሲቲ
አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity
#JinkaUniversity

ጂንካ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 871ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

ከተመራቂዎቹ መካከል 85ቱ ዩኒቨርሲቲው ለመጀመሪያ ጊዜ በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም አሰልጥኖ ያስመረቃቸው መሆኑ ተገልጿል።

ነፃ የትምህርት ዕድል አጊኝተው በዩኒቨርሲቲው ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ የደቡብ ሱዳን ዜጎችም በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀዋል።

@tikvahuniversity
#DillaUniversity

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ በቡና ሳይንስ ኢኮኖሚክስ በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።

ዲላ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ድግሪ ፕሮግራም ያሰለጠናቸውን 2,356 ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

ከተመራቂዎቹ መካከል ከ 120 በላይ የሚሆኑት በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው፡፡

@tikvahuniversity
#ArbaMinchUniversity

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 2,544 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

ተመራቂዎቹ በቅድመ እና በድኀረ ምረቃ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቀቁ ናቸው፡፡

@tikvahuniversity
#WolaitaSodoUniversity

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 859 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

ምሩቃኑ 4 በዶክትሬት ዲግሪ፣ 446 በማስተርስ ዲግሪ እንዲሁም 409 በመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቀቁ መሆናቸው ተገልጿል።

@tikvahuniversity
#WolloUniversity

ወሎ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 814 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

ተመራቂዎቹ በቅድመ እና በድኅረ ምረቃ ፕሮግራም በመደበኛ፣ በርቀት እና በተከታታይ መርሐግብሮች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቀቁ ናቸው።

@tikvahuniversity
#DebreBerhanUniversity

ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 1,248 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

ዩኒቨርሲቲው በመደበኛ፣ በማታ እና በተከታታይ መርሐግብር ያስተማራቸውን በመጀመሪያ ዲግሪ 882 እና በሁለተኛ ዲግሪ 366 በድምሩ 1,248 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

በምርቃት መርሐግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ፕሬዝዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር)፣ ዩኒቨርሲቲው የኢንዱስትሪ ትስስር አማካሪ ቦርድ መስርቶ ሥራ መጀመሩንና 14 ኢንዱስትሪዎች ከዩኒቨርሲቲው ጋር እየሠሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

@tikvahuniversity
#InjibaraUniversity

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ እና በድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ያስተማራቸውን ተማሪዎች አሰመረቀ ።

ዩኒቨርሲቲው 268 በድኅረ ምረቃ እና 428 በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም በድምሩ 696 ተማሪዎችን አስመርቋል።

ዩኒቨርሲቲው በዛሬው ዕለት ባካሔደው 5ኛ ዙር የምረቃ ሥነ-ስርዓት፥ ከተመረቁ የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች ውስጥ 32 ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በሕግ (LLB) ማስመረቁ ተገልጿል፡፡

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ካስፈተናቸው የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች መካከል 83 በመቶዎቹ የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡

@tikvahuniversity
#WolkiteUniversity

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 1,868 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

ዩኒቨርሲቲው 1,760 ተማሪዎች በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም እንዲሁም 108 ተማሪዎች በድኅረ ምረቃ ፕሮግራም በድምሩ 1,868 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል፡፡

በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ እጅግ ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ልዩ ልዩ ሽልማቶች የተበረከተ ሲሆን፤ ተማሪ ከፋለ ጸጋዬ ከኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል 3.98 CGPA በማምጣት የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል፡፡

@tikvahuniversity
#AdigratUniversity

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በ10ኛ ዙር ያስተማራቸውን 1,589 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡

ከተመራቂዎቹ መካከል 122 ተማሪዎች በድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ሲሆን፤ ቀሪዎቹ 1,467 ተማሪዎች የመጀመሪያ ዲግሪ ምሩቃን ናቸው፡፡

@tikvahuniversity
#WoldiaUniversity

ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ የመውጫ ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የሁለተኛ ዲግሪ ነፃ የትምህርት ዕድል ሰጠ፡፡

ዩኒቨርሲቲው በቅድመ እና በድኅረ ምረቃ ፕሮግራም ያስተማራቸውን 544 ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል፡፡ ከተመራቂዎቹ መካከል 103 ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቀቁ ናቸው፡፡

በምርቃት መርሐግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ፕሬዝዳንት አበበ ግርማ (ዶ/ር)፣ ዩኒቨርሲቲው በቅርቡ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን የመውጫ ፈተና ካስፈተናቸው ተማሪዎች መካከል 93 በመቶ የማለፊያ ውጤት ማምጣታቸውን ገልፀዋል፡፡

@tikvahuniversity
#AASTU

አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ 1,067 ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡

ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቀቁ ናቸው፡፡

ዩኒቨርሲቲው ዘንድሮ የመውጫ ፈተና ካስፈተናቸው የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ውስጥ 97.6 በመቶዎቹ የማለፊያ ውጤት ማስመዝገባቸውን የተቋሙ ፕሬዝዳንት ደረጀ እንግዳ (ዶ/ር) ተናግረዋል።

@tikvahuniversity
#WerabeUniversity

ወራቤ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 1,112 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው 5ኛ ዙር ተመራቂዎች፤ በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቀቁ ናቸው፡፡

@tikvahuniversity
#MizanTepiUniversity

ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በአማን እና ቴፒ ካምፓሶቹ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 1,290 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡

ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቀቁ ናቸው፡፡

@tikvahuniversity
2024/09/30 09:30:48
Back to Top
HTML Embed Code: