Telegram Web Link
#ጥቆማ

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም በማስተርስ እና በፒ.ኤች.ዲ. ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ምዝገባ ላይ ይገኛል፡፡

ዩኒቨርሲቲው በ 33 የማስተርስ እና ዘጠኝ የፒ.ኤች.ዲ. የትምህርት መስኮች ተማሪዎችን ለመቀበል ምዝገባ እያደረገ መሆኑን አሳውቋል፡፡

(ዩኒቨርሲቲው በ2017 የትምህርት ዘመን በማስተርስ እና በፒ.ኤች.ዲ. ፕሮግራሞች የሚሰጣቸው የትምህርት አይነቶች እና አመልካቾች ሊወስዷቸው የሚመከሩ የድኅረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና ከላይ ተያይዘዋል፡፡)

@tikvahuniversity
#የሥራ_ቅጥር_ዕድል_ጥቆማ
#AASTU

አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ቴክኒካል አሲስታንቶች እና መምህራንን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

➤ የሥራ መደብ፦ በ12 የትምህርት ክፍሎች
➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 87
➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ የመጀመሪያ፣ 2ኛ እና 3ኛ ዲግሪ
➤ የሥራ ቦታ፦ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ

አመልካቾች ምዝገባ ለማድረግ የትምህርት እና የሥራ ልምድ ማስረጃችሁን በ PDF ፎርማት ይሄ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለአስር ተከታታይ ቀናት በ https://bit.ly/aastujobapplication2024 ላይ በመግባት በምታገኙት ቅፅ መላክ ይሞርባችኋል፡፡

(ዩኒቨርሲቲው ያወጣው ሙሉ ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
Tikvah-University
#Update "ለፋርማሲ ተማሪዎች እንዲሁም የብቃት ምዘና ፈተና በድጋሜ ለሚፈተኑ የጤና ባለሙያዎች ፈተናው በቅርቡ ይሰጣል፡፡" - ጤና ሚኒስቴር የፋርማሲ ተማሪዎች ባለፈው ሰኔ ከተሰጠው የብቃት ምዘና ፈተና (Licensure Exam) ጋር የተያያዙ በርካታ ቅሬታዎችን እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ በጤና ሚኒስቴር የጤናና ጤና-ነክ ተቋማትና ባለሙያዎች ቁጥጥር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ እንዳልካቸው ፀዳል በጉዳዩ ዙሪያ…
#ተጨማሪ

ከጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና (Licensure Exam) ጋር የተያያዙ በርካታ ጥያቄዎች ለቲክቫህ መድረሳቸውን ተከትሎ ተጨማሪ ማብራሪያ ጤና ሚኒስቴርን ጠይቀናል፡፡

የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና በዚህ ወር በድጋሜ የሚሰጥ ሲሆን፤ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ የምዝገባ ጥሪ ዛሬ ወይም ነገ እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡

ሀገረ አቀፍ የመውጫ ፈተና #ያለፉ እና ዲግሪ #ያላቸው ሁሉም የጤና ባለሙያዎች (በድጋሜ ተፈታኝ የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ) ለብቃት ምዘና ፈተናው መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል፡፡

ጤና ሚኒስቴር የሚጠቀመው የብቃት ምዘና ፈተና እርማት አሰራር በዓለም አቀፍ ደረጃ አገራት የሚጠቀሙበት መሆኑን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ የገለፁት በሚኒስቴሩ የጤናና ጤና-ነክ ተቋማትና ባለሙያዎች ቁጥጥር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ እንዳልካቸው ፀዳል፤ (Average Result) አማካይ ውጤት የሚባል ነገር አለመኖሩን አስረድተዋል፡፡

ጤና ሚኒስቴር የባለሙያዎችን የሙያ ብቃት ለመለካት የሚያስችልና በኅብረተሰቡ ላይ ምንም አይነት ጉዳት የማያደርሱ ባለሙያዎችን ለመለየት የሚያስችል 'ዝቅተኛ' የማለፊያ ነጥብ እንደሚቀመጥ ነው ኃላፊው ያብራሩት፡፡

የጤና ሚኒስቴር ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጠው የብቃት ምዘና ፈተና፣ አካታች የሆኑ 200 ጥያቄዎች ያሉት መሆኑንም ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡

የብቃት ምዘና ፈተናው ለመውሰድ የጤና ባለሙያዎች ምዝገባ ነበጥቂት ቀናት ውስጥ እንደሚጀመር ይጠበቃል፡፡

@tikvahuniversity
ቅናሽ ተገኝቶማ አንምረውም ፤ ዕለታዊውን M-PESA ኢንተርኔት ፓኬጃችንን ገዝተን እስከ 50% ቅናሹን ማጣጣም ነው እንጂ!

የ M-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉 https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://www.tg-me.com/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom #FurtherAheadTogether
#ጥቆማ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ #ነርሲንግና_ሚድዋይፈሪ ትምህርት ቤት በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በአራት የሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር እንደሚፈልግ አሳውቋል፡፡

የማስተርስ ፕሮግራሞች፦
- በ Adult Health Nursing
- በ Surgical Nursing
- በ Pediatrics and Child Health Nursing
- በ Clinical Midwifery

በተመሳሳይ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ #የዓሳ_ሃብትና_ውሃ_ሳይንስ ትምህርት ክፍል በአራት የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር እንደሚፈልግ አሳውቋል፡፡

የማስተርስ ፕሮግራሞች፦
- MSc in Fisheries and Aquaculture
- MSc in Aquatic and Wetland Ecosystem Management

የፒ.ኤች.ዲ. ፕሮግራሞች፦
- PhD in Fisheries and Aquaculture
- PhD in Aquatic and Wetland Ecosystem Management

በፕሮግራሞቹ ለማመልከት ብሔራዊ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) ማለፍ ያስፈልጋል፡፡ (የተቋማቱ ሙሉ መልዕክት ለከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አመራሮች ልዩ የክረምት አቅም ግንባታ ስልጠናቸውን አጠናቀዋል፡፡

የትምህርት ቤት አመራሮቹ ከሐምሌ 23/2016 ዓ.ም ጀምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ ስልጠናቸውን ሲከታተሉ ቆይተው፣ ለአስር ቀናት (60 ሰዓታት) የተሰጣቸውን አቅም ማጎልበቻ ስልጠና አጠናቀዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲዎቹ ከትናንት ጀምሮ በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀን የመለማመጃ ፈተና እየሰጡ መሆናቸው ታውቋል፡፡

የትምህርት ቤት አመራሮቹ በዛሬው ዕለት ዋናውን የምዘና ፈተና እንደሚወስዱ ይጠበቃል፡፡ የሚወስዱትን ምዘና ተከትሎ የምስክር ወረቀት ይሰጣቸዋል ተብሏል፡፡

በምዘና ፈተናው አጥጋቢ ውጤት ያላመጡ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች በቀጣይ የምዘና ሒደት ውስጥ የሚያልፉበት ዕድል እንደሚመቻች ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

ከሐምሌ 23/2016 ዓ.ም ጀምሮ በስልጠና ላይ የሚገኙ መምህራንም ለ20 ቀናት (120 ሰዓታት) የሚሰጣቸውን ስልጠና ሲያጠናቅቁ ተመሳሳይ ፈተና ይወስዳሉ።

ምስል፦ ወልድያ ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity
በአክሱም ዩኒቨርሲቲ በ2011 ዓ.ም በመንግሥት ስፖንሰርነት በክረምት ትምህርት መርሐግብር የ PGDT ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነበራችሁ ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም የክረምት ትምህርት ምዝገባ ነሐሴ 10 እና 11 / 2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦ በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ ሬጅስትራር
ለተጨማሪ መረጃ 👉 0927432569 / 0938197896

@tikvahuniversity
#ጥቆማ

ቦረና ዩኒቨርሲቲ በ2017 የትምህርት ዘመን በመደበኛ እና በተከታታይ መርሐግብር በ12 የሁለተኛ ዲግሪ የትምህርት መስኮች የመግቢያ መስፈርት ያሟሉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል።

አመልካቾች የሀገር አቀፍ የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ማለፍ ይጠበቅባቸዋል።

(ቦረና ዩኒቨርሲቲ በቀጣይ ዓመት የሚያስተምራቸው የሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም የትምህርት መስኮች ከላይ ተያይዟል።)

@tikvahuniversity
ዩኒቨርሲቲዎች ለሁለተኛ ደረጃ የትምህርት ቤት አመራሮች ሲሰጡት የቆዩትን ልዩ የክረምት አቅም ግንባታ ስልጠና አጠናቀዋል፡፡

የትምህርት ቤት አመራሮቹ ከሐምሌ 23/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለአስር ቀናት (60 ሰዓታት) የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲዎቹ ስልጠናውን በአግባቡ መከታተላቸውን የሚመዝን ፈተና ለትምህርት ቤት አመራሮቹ በዛሬው ዕለት መስጠት ጀምረዋል፡፡

ሠልጣኞቹ ከ70% የበየነ-መረብ ፈተና እንዲሁም ከ30% በአሠልጣኝ መምህራን የተዘጋጀ ምዘና ወስደው በድምሩ 70% እና ከዚያ በላይ የሚያመጡ ሠልጣኞች የምስክር ወረቀት ይሰጣቸዋል ተብሏል።

በምዘና ፈተናው አጥጋቢ ውጤት ያላመጡ መምህራን እና የትምህርት ቤት አመራሮች በቀጣይ የምዘና ሒደት ውስጥ የሚያልፉበት ዕድል እንደሚመቻች ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

ምስል፦ ጅማ ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity
2024/10/04 07:31:52
Back to Top
HTML Embed Code: