Telegram Web Link
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም ነባር የክረምት ትምህርት መርሐግብር ተማሪዎች ምዝገባ ሐምሌ 12 እና 13/2016 ዓ.ም የሚካሔድ መሆኑን አሳውቋል፡፡

የምዝገባ ጥሪው ለነባር የክረምት ትምህርት መርሐግብር የቅድመ ምረቃ እንዲሁም የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች የተደረገ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

ትምህርት ሐምሌ 15/2016 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል፡፡ (ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity
ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም ነባር የክረምት ትምህርት መርሐግብር ተማሪዎች ምዝገባ የሚከናወነው ሐምሌ 15 እና 16/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡

የምዝገባ ጥሪው የመጀመሪያ ዲግሪ፣ የሁለተኛ ዲግሪ እና የፒጂዲቲ ፕሮግራሞች የክረምት መርሐግብር ነባር ተማሪዎችን እንደሚመለከት ተገልጿል፡፡

የነባር ተማሪዎች ቲቶሪያል ከሐምሌ 17-19/2016 ዓ.ም ይሰጣል ተብሏል፡፡ (ተጨማሪ መረጃ ከላይ ተያይዟል፡፡)

@tikvahuniversity
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል ለሰባት ወራት ያሰለጠናቸውን 17 ተማሪዎች አስመርቋል።

ሰልጣኞቹ ለሳይንስና ፈጠራ ሥራዎች ዝንባሌ ያላቸው የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሲሆኑ፤ በበጋ መርሐግብር በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት ለ 224 ሰዓት ስልጠናቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

ስልጠናው በመሰረታዊ ሳይንስ፣ በኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ፣ በPCB እና 3D ፕሪንቲንግ፣ በመሰረታዊ ኤሌክትሮኒክስ፣ በመሰረታዊና አድቫንስድ ኮምፒውቲንግ ላይ ትኩረት በማድረግ የተሰጠ መሆኑን ከዩኒቨርሲቲው የተገኘ መረጃ ያሳያል፡፡

@tikvahuniversity
40A+ ያሳካው የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በሳምንቱ መጨረሻ ካስመረቃቸው ተማሪዎች መካከል ሀሰን መሀመድ አንዱ ነው፡፡

ሀሰን ከኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል 4.00 አጠቃላይ አማካይ ውጤት (CGPA) በማስመዝገብ በማዕረግ ተመርቋል፡፡ ሀሰን ከወሰዳቸው ኮርሶች ውስጥ 40 የትምህርት አይነቶችን A+ ውጤት በማሰመዝገብ ማጠናቀቅ ችሏል፡፡

በተጨማሪም በቅርቡ የተሰጠውን የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና 81 ነጥብ ውጤት በማምጣትም አጠናቋል፡፡ ሀሰን ዩኒቨርሲቲ ከገባ በኋላ ሙሉ ትኩረቱን ትምህርት ላይ በማድረግ ተምሮ ለውጤት መብቃቱን ይናገራል፡፡
(https://www.facebook.com/yibeltal.gizaw)

@tikvahuniversity
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ከቅዳሜ ሰኔ 29/2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደሚፈተኑበት ተቋማት ገብተዋል።

ዛሬ በርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ለተፈታኞች ገለፃ ሲሰጡ የዋሉ ሲሆን ሌሎች ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ነገ ኦረንቴሽን እንደሚሰጡ ይጠበቃል።

የመጀመሪያው ዙር የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ከሐምሌ 3-5/2016 ዓ.ም ይሰጣል።

@tikvahuniversity
ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የ2ዐ16 ዓ.ም የክረምት ተማሪዎች ምዝገባ የሚከናወነው ሐምሌ 18 እና 19/2016 ዓ.ም መሆኑን ገልጿል።

ትምህርት ሐምሌ 20/2016 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል።

@tikvahuniversity
ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም ነባር የክረምት ትምህርት ምዝገባ የሚካሄደው ነሐሴ 2 እና 3/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

የምዝገባ ጥሪው ነባር የክረምት የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን የሚመለከት መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahuniversity
2024/09/30 21:28:51
Back to Top
HTML Embed Code: