Telegram Web Link
#ዜና

Tesla Cybertruck ተጨማሪ 6 የቀለም አማራጮች ይዞ ቀረበ።


የቴስላው ሳይበር ትራክ እስቴንለስ እስቲል ቦዲ ያለው መኪና ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በቅርብ ጊዜ እየተለመደው ከመጣው በቀለም ፊልም wrap ካልተደረገ/ ካልተሸፈነ በቀር የቀለም አማራጮች የሉትም።

ለዚህም የቴስላ ካምፓኒ መኪናቸውን customize ማድረግ ለሚፈልጉ ደንበኞቹ wrap የሚደረጉ ወደ 5 አይነት የቀለም ፊልም አማራጮችን አቅርቦ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ ተጨማሪ 6 የቀለም አማራጮችን ጨምሮ በድምሩ 11 የሚሆን የቀለም አማራጮችን አቅርቦዋል።

አዲስ ያስተዋወቃቸው ቀለሞች
-Forest Green
-Satin Crimson Red
-Iridescent Purple
-Tactical Green
-Satin Dark Grey
-Copper Tinted Clea
እነዚህ ሲሆኑ የሁሉም ዋጋ 6,500 የአሜሪካን ዶላር ነው።

በከለር ፊልም መኪናችንን መሸፈን የመኪናችንን ቦዲ እንደ መጫጫር እና ዝገት ካሉ ችግሮች ሲከላከልልን የቴስላ ኢንጂነሮች እንደተናገሩት ከሆነ ግን cyber truck ላይ እንደዚህ ችግሮች አይኖሩም። ምክንያቱም ቦዲው የተሰራው ከstainless steel ስለሆነ በከለር ፊልም መሸፈናችን ለውበት ለመጨመር ብቻ ነው የሚጠቅመን ።


#Cyber_truck
#color_film_wrapping
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

Seat መኪኖቹን ማምረቱን የሚቀጥለው አስከ 2035 ብቻ ነው።


የቮልስ ዋገን ግሩፕ አካል የሆነው በሃገረ እስፔን የሚመረተው Seat መኪኖችን ማምረቱን የሚቀጥለው እስከ 2035 ማለትም አውሮፓን ጨምሮ ብዙ ሃገራት የነዳጅ መኪና ላይ ሙሉ በሙሉ እገዳ እስከሚያደርጉበት ጊዜ ነው።

በፕለጊን ሃይብሪድ እና በነዳጅ መኪኖች ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየሰራ ያለው seat የነዳጅ መኪኖች ዘመን ሲያልቅ ምርቱን አቁሞ ማምረቻውን የሚዘጋ ይሆናል። ለዚህም ምክንያት የሆነው ምንም አይነት የኤሌክትሪክ መኪኖችን እያመረተ አለመሆኑ ነው።

ቮልስ ዋገን ግሩፕ ሌሎች ብራንዶቹ ትኩረቱን ፕለጊን ሀይብሪድ እና የኤሌክትሪክ መኪኖች ማምረት ላይ አድርጎ እየሰራ ቢሆንም Seat ላይ ግን በኤሌክትሪክ መኪኖች ዘርፍ እንዲሰራ ምንም አይነት ኢንቨስትመንት እያደረገ አይደለም። ይህም የSeat ብራንድ የፍፃሜው ጅማሬ ሆኖዋል።

#Seat
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

Volkswagen፣ BMW፣እና Renault የአውሮፓ ህብረት የ2035 የነዳጅ መኪኖች እገዳን ተቃወሙ።


Volkswagen፣ BMW፣ እና Renault በአውሮፓ ህብረት የካርበን ልቀት ጋር ተያይዞ በ2035 ሙሉ በሙሉ የነዳጅ መኪኖችን ከገበያ ለማውጣት እና በምትኩ የኤሌክትሪክ መኪኖችን እንዲስፋፉ በማሰብ የወጣውን ህግ ተቃወሙ።

የመኪና ካምፓኒዎቹ ይሄ ህግ ፍትሃዊ አደለም የመኪና ምርት ኢንዱስትሪው ላይ ከፍተኛ ጫና ያሳድራል። ኢንዱስትሪውንም እንደ ድንገት ሊለዋወጥ በሚችል የደንበኞች የኤሌክትሪክ መኪና መግዛት ወይም ያለመግዛት ፍላጎት ያለ ሪስክ ላይ ይጥለዋል ያሉ ሲሆን በአውሮፓ የሚገኙ እሽከርካሪዎችም ያን ያህል የኤሌክትሪክ መኪኖች እየገዙ አይደለም ሲሉ ሞግተዋል።

የአውሮፓ ህብረት 2035 ላይ ሙሉ በሙሉ የነዳጅ መኪኖችን ከማገዱ በፊት 2025 ላይ 2021 ላይ ከነበረው አዲስ የነዳጅ መኪና ሽያጭ ቁጥር ላይ በ25% ቅናሽ እንዲያደርጉ የወሰነ ሲሆን ይህም ለቴስላ ካምፓኒ ጥሩ ትርፍን ፈጥሮለታል።

ባለፉት 4 አመታት ብቻ በቻይና እና በአውሮፓ ከካርበን ልቀጥ ጋር ተያይዞ ቅጣት እንዳይጣልባቸው ሲሉ ብዙ ትላልቅ የነዳጅ መኪና አምራቾች ከቴስላ ካምፓኒ የ9 ሚሊየን ዶላር (Carbon credits) ገዝተዋል።

#ICE_law_of_European_union
#Volkswagen #Renault #BMW
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

የቻይናው LM Motor የመጀመሪያው solid state ባትሪን የተጠቀመ የመኪና አምራች ሆኖዋል።


የቻይና የመኪና አምራች የሆነው LM Motors ለመጀመሪያ ጊዜ በብዛት ultra fast charging የሆኑት solid state ተብለው የሚጠሩትን የባትሪ አይነቶችን የሚጠቀሙ መኪኖችን ያመረተ ካምፓኒ የሆነ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ይሄን ያደረገውም በቅርቡ ለገበያ በሚወጣው L6 በተባለው ሴዳን መኪናው ላይ ነው።

L6 ላይ የተገጠመው 130kwh ባትሪ ፓክ መኪናውን በአንድ ቻርጅ እስከ 1000 km  ድረስ እንዲጓዝ ያስችለዋል። Im Motors እንዳለው ከሆነው ምስጋና ለsolid state ባትሪ ቴክኖሎጂ የ L6 ባትሪ እስከ 900 ቮልት ማስተናገድ የሚችል ፋስት ቻርጂግ ባትሪ ነው። 

ባትሪው በምን ያህል ፍጥነት ቻርጅ እንደሚያደርግ ያልገለፁ ሲሆን April 8 ላይ ስለመኪናው ቴክኒካል ነገሮች በዝርዝር ይፋ የሚያደርጉ ይሆናል።

#Im_Motors
#Solid_State_Battery
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

የኤሌክትሪክ መኪናዎች ባትሪ የአገልግሎት እድሜ 15አመት መሆን አለበት።


አሜሪካ፣ ቻይና፣ እና የአውሮፓ ህብረት የኤሌክትሪክ ባትሪዎች ዋራንቲ ቢያንስ 8 አመት መሆን አለበት ብለው የወሰኑ ሲሆን የባትሪ ኤክስፐርቶች ግን ይሄ የዋራንቲ ጊዜ ወደ 15 አመት ገፋ መደረግ አለበት፤
እንዲሁም አሁን ላይ ከ8 አመት በሗላ ከነበራቸው ሃይል የመያዝ አቅም በ 30% ቀንሰው በ70% ሃይል ማገልገል መቻል አለባቸው የተባለው ከ15 አመት ሁላ እራሱ ቢሆን መጀመሪያ ከነበራቸው ሃይል 15% በላይ  እንዳይቀንሱ እና 85% ሃይላቸውን ማስጠቀም መቻል እንዲኖርባቸው መወሰን አለበት ብለዋል።

የቀድሞ የቴስላ ካምፓኒ chief technology officer የነበረው እና አሁን ላይ የራሱ Redwood የተባለ የባትሪ ሪሳይክል ካምፓኒ ባለቤት የሆነው JB Straubel እንደተናገረው የኖርማል ባትሪ ፓክ እድሜ ቀድሞውኑም ወደ 15 አመት የተጠጋ ነው። አሁን ላይ የባትሪ አምራች የሆነው CATL የዋራንቲ እድሜውን ወደ 15 አመት ለማድረስ እየሰራ ይገኛል።

Recurrent የተባለው ካምፓኒ ባደረገው ጥናት መሰረት የኤሌክትሪክ መኪኖች ባትሪ ከ8 አመት በሗላ ከነበራቸው የኪሎሜትር ሬንጅ ላይ 32 ኪሎሜትር ብቻ ነው ሚቀንሱት። ይህም እንደ Chevrolet Bolt እና Hyundai Kona ላይ ከተደረጉ ትላልቅ (Recall) ውጪ የባትሪ ቅያሪን መመልከት እድላችን በጣም ትንሽ ነው ብሎዋል።

#Battery #electric
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

በከተማችን የመጀመሪያ በኤሌክትሪክ ሃይል የሚሠሩ የሕዝብ ትራንስፖርት አውቶቡሶች አገልግሎት መስጠት ጀመሩ ::


ኢትዮጵያ ውስጥ የመጀመሪያ የሆኑት የህዝብ ትራንስፖርት አውቶቡሶች ከሳምንታት ሙከራ በሗላ ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል :: እነዚህ ባሶች የተገጣጠሙት በ በላይነህ ክንዴ ግሩፕ ሲሆን 370 ኪሎሜትር በአንድ ቻርጅ መጟዝ ይችላሉ ::

ይህንንም አገልግሎት መስጠት የጀመሩት ከ ቦሌ - እስጢፋኖስ - 4 ኪሎ - 6 ኪሎ ሽሮሜዳ የሆነው መንገድ ላይ መሆኑን ገልፀዋል :: ለመጠቀም የሚያስከፍሉትም በፊት ከነበሩት ባሶች እኩል መሆኑን አሳውቀዋል ::

ምንጭ - FBC

#electric #buses #AddisAbaba
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

Xpeng የVOLT(የበረራ) ሰርተፍኬት ለማግኘት እየተቃረበ ነው።


የቻይና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች አምራች ካምፓኒ የሆነው Xpeng የVOLT(vertical takeoff and landing) እንደ ሂሊኮፕተር ከቆሙበት ቀጥታ ወደላይ ተነስተው መብረር እና በዛው መልክ ማረፍ የሚችሉ (Aircraft) መስራቱ ላይ እድገት እና መሻሻልን እያሳየ ነው።

የቻይና መንግስትም የ Xpeng (land carrier) በራሪ መኪናውን ለአየር ብቁ ነው ሲል የበራራ ሰርተፍኬት ሰጥቶታል።

Land carrier ከጀርባው ባለው ክፍል ውስጥ ትንሽዬ (aircraft) የተሸከመ ባለ 6 ጎማ ተሽከርካሪ ሲሆን መብረር በምንፈልግበት ወቅት የመኪናው ጎኖቹ እና ጣራው በመከፈት (aircraft) ያወጣልናል።

aircraft ተሸካሚ የሆነው land carrier ከ 4 እስከ 5 ሰው መያዝ የሚችል ሲሆን Aircraft ደግሞ 2 ሰው ብቻ ነው መያዝ የሚችለው።
Aircraftቱን ማንዋሊ እኛ እያበረርነውም ሆነው በራሱ autonomous ሲስተም ሲበር ዝቅተኛ በሆነ ከፍታ ላይ ሲሆን ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ ሃይል ነው የሚሰራው።

#Xpeng #Flying_Cars
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

የ Hyper Car አምራች ካምፓኒ የሆነው McLaren አሁን በBahrain 🇧🇭  ባለቤትነት ስር ነው።


ኒውዝላንዳዊው Bruce McLaren የዛሬ 59 አመት ገደማ McLaren ሬሲንግን ሲመሰርት በእርግጠኝነት ይሄ ይፈጠራል ብሎ አልገመተም።

የMcLaren ግሩፕ አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ በBahrain sovereign wealth fund ባለቤትነት ስር የወደቀ ሲሆን
ካምፓኒው ከአዲስ መደራጀቱ የኤሌክትሪክ መኪኖችን ማምረት የሚያስችለውን አዳዲስ ፓርትነርሺፖችን እየፈጠረ ነው ብለዋል።

McLaren ኮቪድ 19 ከተቀሰቀሰበት ጊዜ ጀምሮ እያጣጣረ ያለ ሲሆን ባለፈው አመት የ3ኛ እሩብ አጋማሽ ላይ 186 ሚሊየን ዶላሮችን አጥቶዋል። ይህም ካምፓኒውን ዳግም በእግሩ ለማቆም ከሼር ሆልደሮቹ ወደ 566 ሚሊየን ዶላሮችን እንዲያሰባስብ አስገድዶታል።
በቀጣይ ወር ላይም የ 2023 ሙሉ ሪፖርት ይፋ ያደርጋል።

#McLaren #Bahrain
@OnlyAboutCarsEthiopa
#ዜና

BYD Yuan Up ቻይና ውስጥ በ 13,400 ዶላር የመነሻ ዋጋ ለገበያ ቀረበ።


ከብዙ ጊዜ ማስጠበቅ በሗላ በመጨረሻም የቻይናው የኤሌክትሪክ መኪኖች አምራች የሆነው BYD Yuan Up የተባለውን ኮምፓክት SUV መኪናው በ13,000 የአሜሪካ ዶላር መነሻ ዋጋ ለገበያ አቀረበው።

Yuan Up ከተማሪ ጀምሮ እስከ ባለትዳሮች ያለውን ሰፊውን የማህበረሰብ ክፍል እንዲያማክል ታስቦ የተሰራ ሲሆን የቻይናን ባህላዊ ገፅታ ከዘመናዊው ጋር አጣምሮ የያዘ መኪና ነው። ለምሳሌ የፊት LED መብራቶቹ ሃሳባቸው የተወሰደው የቻይና ባህል ላይ ትልቅ ቦታ ካለው ምናባዊው ፍጥረት ከ ድራገን ፊት ነው።

በ 2 የሞተር እና በ 2 የባትሪ ፓክ አማራጮች የቀረበ ሲሆን ባለ 70kw (kilowatt) ሞተሩ 93 የፈረስ ጉልበት ሲያመነጭ ባለ 130kw(kilowatt) ሞተሩ ደግሞ 174 የፈረስ ጉልበትን ያመነጭልናል።
ባለ 32kwh ባትሪ ፓኩ 301 ኪሎሜትር በአንድ ቻርጅ ሲጟዝ ባለ 45.1 kwh ባትሪ ፓኩ ደግሞ 401 ኪሎሜትር ይጓዛል።

ውስጡ ላይም ከስር ቀጥ ያለ መሪ፣ 12.8 inch የሚሽከረከር የመሀል እስክሪን፣ (latherette) የተባለ ሰው ሰራሽ ቆዳ የለበሱ ወንበሮች ከፓናሮሚክ ሰንሩፍ ጋር በውበት አዋህዶ ይዟል።

BYD እንዳስታወቀው Yuan Up በ3 ሞዴሎች የሚቀርብ ሲሆን አነሱም፦
- Lower Trim በ 301 ኪሎሜትር ሬንጅ በ13,400 ዶላር
-Lower Trim በ 401 ኪሎሜትር ሬንጅ በ15,200 ዶላር
-Upper trim በ 401 ኪሎሜትር ሬንጅ በ16,600 ዶላር

ነጭ፣ አረንጓዴ፣ ሮዝ፣ እና ግራጫ የቀለም አማራጮችም አሉት።

#BYD #Yuan_Up
#Electric
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

የቴስላ መኪና ባለቤቶች ለአንድ ወር የሚቆይ ነፃ የFSD(Full self driving) ሲስተም አንዲጠቀሙ የሙከራ ጊዜ ተሰጣቸው።


ደንበኞቹ ከሲስተሙ ጋር እንዲላመዱ በማሰብ ቴስላ የfull self driving ( ሙሉ በሙሉ መኪናው ያለሹፌር እራሱ በራሱ መንዳት የሚያስችለውን ሶፍትዌሩን በአሜሪካ ላይ ለአንድ ወር በነፃ እንዲጠቀሙ መፍቀዱን የቴስላ ባለቤት እና CEO የሆነው elon musk ይፋ አደረገ።

ለሲስተም ሶፍትዌሩ አዲስ ለሆኑ ደንበኞች FSD ሰርቪሱን እንዲጠቀሙ ፍቃድ ከማግኘታቸው በፊት የቴስላ ካምፓኒ ሰራተኞች ለእያንዳንዱ ደንበኛ ስለአጠቃቀሙ በተግባር የሚያሳዩአቸው ይሆናል።

Elon እንዳለው ከሆነው እንዲ ማድረጋችን ነገሮችን የሚያጓትትብን ቢሆንም በጣም አስፈላጊ እና ወሳኝ ቅድመ ሁኔታ ነው።

#Tesla #FSD
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

የቻይና የመኪና ገበያ ላይ ያለው የዋጋ ጦርነት ሁለተኛው ዙር ጀመረ።


በቻይና የመኪና ገበያ ላይ ያለው ጦርነት የሚቆም አይመስልም። እንደውም በተቃራኒው ብሶበታል።
የኤሌክትሪክ መኪና አምራቹ BYD ከሰሞኑን ሁሉም መኪኖቹ ላይ ማለት በሚቻል ደረጃ ወደ 100 የሚጠጉ የተለያዩ የመኪና ሞዴሎቹ ላይ ታላቅ የዋጋ ቅናሽን አደረገ።

ይህን ክስተት የቻይና ገበያ ላይ ኤክስፐርት የሆነው የAutomobility መስራች እና CEO የሆነው Bill Russol "የዋጋው ጦርነት ሁለተኛው ዙር" ሲል ሰይሞታል።

Bloomburg እንደዘገበው ከሆነው ይሄ የBYD ስትራቴጂ ብዙ ሰዎች ከነዳጅ መኪና ተጠቃሚነት ወደ ታዳሽ ሃይል የሚጠቀሙ መኪኖች ተጠቃሚነት የማምጣት ሲሆን በዋነኝነት በገጠራማ አካባቢ ያሉ የኤሌክትሪክ መኪኖችን የመግዛት አቅሙ የሌላቸው ሰዎችን ታሳቢ በማድረግ ነው።

ስትራቴጁው በተጨማሪ እንደ ቶዮታ፣ኒሳን እና ቮልስ ዋገን ያሉ የኤሌክትሪክ መኪኖችን ወደ ገበያው ይዘው ለመምጣት ዘግየት ብለው የነበሩ የመኪና አምራቾች ላይ ስጋት ሆኖዋል።

Bloomburg new energy finance እንደተናገረው ከሆነ አብዛኛው በቻይና የሚገኙ የኤሌክትሪክ መኪና አምራቾች ትርፋማ አይደሉም። ይህም መጨረሻ ላይ እንዲጣመሩ ወይም ኪሳራ ላይ እንዲወድቁ ያስገድዳቸዋል።

#China #Ev_Market
#BYD
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

Isuzu አንዲስ የፒክ አፕ መኪና conceptቱን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ቶዮታ የኤሌክትሪክ ፒክ አፕ መኪና ለታይላንድ ገበያ ሊያቀርብ ነው።


Isuzu D-MAX ብሎ የሰየመውን እስከ በጠቅላው እስከ 1 ቶን( 1,000 kg) ክብደት መሸከም የሚችል፣ ሙሉ በሙሉ የኤሌክትሪክ ሃይልን የሚጠቀም የፒክ አፕ መኪና ኮንሴፕቱን ይፋ አደረገ። Isuzu አንዳለው ከሆነም ቀጣይ አመት በአውሮፓ፣ በአውስትራሊያ፣ እና በታይላንድ ገበያ ላይ ይቀርባል።

ቶዮታም ይሄ ዜና ትንሽ ሳያስፈራው አልቀረም። ምክንያቱም እሱም ለታይላንድ ገበያ የሚቀርብ የኤሌክትሪክ ፒክ አፕ መኪና ይዞ እንደሚቀርብ አሳውቆዋል።
ሮይተርስ እንደዘገበው ከሆነ አዲሱ መኪና የHilux ኤሌክትሪክ ቨርዥን ነው የሚሆነው። በዚህ አመት መጨረሻም ለገበያ ሊቀርብ ይችላል።

#Isuzu #Toyota
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

የኤሌክትሪክ መኪና ባለቤቶች ጎማቸው ቶሎ ቶሎ በመበላቱ ቅር ተሰኝተዋል።


የኤሌክትሪክ መኪና ባለቤቶች መኪኖቻቸው ቻርጅ በማድረግ የነዳጅ ወጪን ሲያስቀሩ፤ እንዲሁም እንደ ዘይት፣ የነዳጅ ፊልትሮ፣ የዘይት ፊልትሮ፣ ስፓርክ ፕለግ፣... ያሉ ቅያሪ የሚፈልጉ ክፍሎች ላይ ይወጣ የነበረውን ወጪ በመቅረቱ ገንዘባቸውን ቢቆጥቡም ጎማ ቶሎ ቶሎ በመቀየር ከቀረላቸው ወጪ ከፊሉን ያካክሱታል።

የJ.D Power 2024 U.S. Original Equipment Tire Customer Satisfaction ጥናት ከኤሌክትሪክ መኪና ባለቤቶች ባገኘው መረጃ መሰረት ጎማዎቻቸው በመኪኖቹ ባላቸው ክብደት እና ጉልበት ምክንያት ቶሎ ቶሎ እየተበሉባቸው ነው።

Automotive news እንደዘገበው ከሆነው ደግሞ ይሄ ለሻጮች እና የጎማ ጥገና ላይ ለተሰማሩ ሰዎች ጥሩ የስራ እድልን ይፈጥራል ብሎዋል።

አሁን ላይ ከጎማ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ በካምፓኒዎቹ ትንሽ ልዩነት ያላቸው የአጠቃቀም ምክሮች አሉ።
የMustang Mach E ባለቤቶች ጎማቸውን በየ 16,000 ኪሎሜትር አዙረው እንዲያስሩት፣ የHyundai Ioniq 6 ባለቤቶች በየ 13,600 ኪሎሜትር፣ የኤሌክትሪኩ Hummer መኪናን በየ 12,000 ኪሎሜትር አዙረው እንዲያስሩት ተመክረዋል።

#Electric_car_Tires
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ጠቃሚ_መረጃ

ማሳሰቢያ ለአሽከርካሪዎች

(መጋቢት 19/2016 ዓ.ም)በመንገድ ግንባታ ላይ ያሉ በጊዜያዊነት ዝግ የሆኑ መንገዶች እና አማራጭ መንገዶችን ስለማሳወቅ:-

ከ4 ኪሎ እስከ ፒያሳ ባለው መስመር የራስ መኮንን ድልድይ እየተሰራ በመሆኑ የመንገድ ግንባታው እስከሚጠናቀቅ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ፍጹም መቆም የሚከለክሉ የትራፊክ ምልክቶች በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ መተከላቸው ይታወቃል።
እስከአሁን ባለው ሂደት በተለይም በስራ መግቢያ እና ከስራ መውጪያ ሰዓት በአካባቢው ላይ በመንገድ መዘጋጋት ህብረተሰቡ እንዳይጉላላ አሽከርካሪዎች ሌሎች አማራጭ  መንገዶችን በመጠቀም ተባባሪ እንዲሆኑ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ በአካባቢው በስፋት ሲሰጥ ቆይቷል።
በዚሁ መሰረት መቆም የሚከለክሉ ምልክት የተተከለባቸው መንገዶች ከመጋቢት 19/2016 ዓ.ም ጀምሮ ጥብቅ ቁጥጥር ይጀመራል።

የአድዋ ሙዚዬም ፓርኪንግ አገልግሎት መስጠት ስለጀመረ አሽከርካሪዎች እንደ አማራጭ መጠቀም ይችላሉ።
ሁሉም አሽከርካሪዎች በመንገድ ግንባታው ስራ በጊዜያዊነት ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሆኑ መንገዶችን አውቃችሁ ሌሎች አማራጭ ልትጠቀሙ የሚገቡ መንገዶች:-

* ከራስ መኮንን ድልድይ ወደ ደጎል አደባባይ
* ከአራት ኪሎ ወደ ራስ መኮንን ድልድይ፣ አማራጭ መንገድ ከአራት ኪሎ-አባድር 
* ከደጎል አደባባይ ትራፊክ መብራት ወደ 4 ኪሎ
* ከቅ/ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ራስ መኮንን ድልድይ
* ከደጃች ውቤ ወደ ራስ መኮንን ድልድይ
* ከአፍንጮ በር ወደ ራስ መኮንን ድልድይ
* ከባሻወልዴ ችሎት ወደ ራስ መኮንን ድልድይ እና ከቀበና ወደ ፒያሳ የሚመጡ አሽከርካሪዎች መንገዱ ግንባታ ላይ መሆኑን ተገንዝባችሁ ሌሎች አማራጭ መንገዶችን እንድትጠቀሙ እናሳውቃለን፡፡

ምንጭ - TMA

#AddisAbaba
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

Stellantis በጣሊያን የ2,500 ሰራተኞች ቅነሳ አደረገ።


የቤት እና ቀላል የንግድ መኪኖች አምራች የሆነው Stellantis ከነዳጅ መኪኖች ማምረት ወደ ኤሌክትሪክ መኪኖች ማምረት የሚደረገው ለውጥ እና በቻይና የመኪና አምራቾች በኩል ያለው ጠንካራ ፉክክር አስግቶታል። ለዛም የሰራተኞች ቅነሳ እያደረገ ነው።

ባለፈው ሳምንት አሜሪካ ላይ 400 የኢንጂነሪንግ ሰራተኞቹን የቀነሰ ሲሆን አሁን ላይ ከጣሊያን የሰራተኞች ማህበር ጋር በጣሊያን ከሚገኙ ከተለያዩ ማምረቻዎቹ ቢያንስ 2,500 ሰራተኞች ላይ ቅነሳ ለማድረግ ከስምምነት ደርሶዋል። ነገር ግን ቅነሳው በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ ነው።

Stellantis የጡረታ ጊዜያቸው ለተቃረቡ እና የተሻለ የስራ አማራጭን መሞከር ለሚፈልጉ ሰራተኞች የሰራተኛ ስንብት የአገልግሎት ክፍያ እንደሚፈፅም አሳውቆዋል። በመጪዎቹ ቀናቶችም በሌሎች ሳይቶቹ ላይ ተጨማሪ የስራ ቅነሳ ስምምነቶችን እንደሚያደርግም ተናግሮዋል።

Stellantis በ2021 ሲመሰረት ጣሊያን ላይ ከነበሩ 55,000 ሰራተኞች ቁጥር ወርዶ በአሁኑ ሰአት 43,000 ሰራተኞች ነው ያሉት።

#Stellantis
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

Hyundai የኤሌክትሪክ መኪኖች እና SDV (Software-Defined Vehicle) መኪኖች ላይ 51 ቢሊየን ዶላር ኢንቨስ ሊያደርግ ነው።


የኤሌክትሪክ መኪኖች ወደማምረት Transition ማረን ከፍተጫ ወጪ እንዳለው ምንም ጥያቄ የለውም። የHyundai ግሩፕ እንዳሳወቀው ከሆነ በመጪው 3 አመታት ውስጥ የኤሌክትሪክ መኪኖች እና Software Defined Vehicles ( ሶፍትዌርን በመጠቀም የራሳቸውን ኦፕሬሽን በራሳቸው መቆጣጠር፣ በዋነኝነት ደግሞ አዳዲስ አገልግሎቶችን መጨመር የሚችሉ መኪኖች) ን ለማበልፀግ 51 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ኢንቨስት አንደሚያደርግ እና አዲስ 81,000 ሰራተኞችን እንደሚቀጥር ተናግሮዋል።

ከግማሽ በላይ የሚሆነው ገንዘብ አዲስ የ Research & Development ጣቢያዎችን እና የኤሌክትሪክ መኪኖችን መገጣጠሚያዎችን ለመገንባት የሚውል ሲሆን ከተቀረው ገንዘብ አብዛኛው ክፍል ደግሞ የኤሌክትሪክ መኪኖች ፣ የ(SDV) እና የባትሪ ቴክኖሎጂ ላይ ለሚደረገው ጥናት እና ምርምር ይውላል።

#Hyundai
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

Honda አዲስ የ Formula 1 ማእከል በእንግሊዝ አቋቋመ።


የሆንዳ ሞተር(Engine) ላለፉት አመታት Formula 1 ውድድርን እየመራ የነበር ሲሆን ይህም በጣም ተፈላጊ አቅራቢ አርጎታል። አሁን ላይ ከ Red Bull ቡድን ጋር አጋርነትን የፈጠረ ሲሆን እስከ ቀጣይ አመት ድረስ ፓወር ዩኒት ያቀርብላቸዋል። ከ 2026 ጀምሮ ተግባራዊ በሚሆነው የ F1 መኪኖች አሁን ካለው በ3 እጥፍ ኤሌክትሪክን እንዲጠቀሙ የሚያስገድደው ህግ ተግባራዊ መሆን ሲጀምር ደግሞ ለ Aston Martin racingም ፓወር ዩኒቶቹን ማቅረብ ይጀምራል።

እነዚህ ጥረቶችን አጠናክሮ ለመቀጠል በእንግሊዝ Honda Racing Corporation UK የሚባል ማእከል የከፈተ ሲሆን የማእከሉ ዋና ስራ የሚሆነውም የድህረ ውድድር ጥገናዎችን ማድረግ እና የF1 Power ዩኒቶችን ማዘጋጀት ነው። በተጨማሪም በአውሮፓ ክልል ውስጥ የሎጅስቲክስ ስራዎችን ይሰራል።

#F1 #Honda
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

Fisker እስከ 24,000 ዶላር በ SUV መኪናው ላይ ቅናሽ አደረገ


Fisker ኪሳራ ውስጥ ላለመግባት ሲል Fisker Ocean SUV ላይ የ 39% ቅናሽ አድርጟል :: ቤዝ ሞዴሉ ላይ እስከ 14,000 ዶላር በመቀነስ አሁን 25,000 ዶላር ሲሸጥ ትልቁ ሞዴል ላይ ደግሞ 24,000 ዶላር በመቀነስ 37,500 ዶላር እየሸጠ ይገኛል :: Fisker አሁን እጁ ላይ 5,000 መኪኖች ሲኖሩ ሙሉ መኪኖቹን ሽጦ ከጨረሰ እስከ 160 ሚሊየን ዶላር ያገኛል :: ይህም ካምፓኒው ከመክሰር እና ከመዘጋት ይታደገዋል ::

እንዲሁም በጣም የሚታወቀው የቴክ ዩትዩበር MKBHD (Marques Brownlee) ከሳምንታት በፊት "The Worst Car I’ve ever reviewed” በሚል ቪዲዮ ሰርቶበት ነበር :: ነገር ግን ሰዉ ይህንን ሁሉ እያወቀ ዋጋው ስለቀነሰ ብቻ ይገዛ ይሆን?

#Fisker
@OnlyAboutCarsEthiopia
#ዜና

Ford ቤት ለቤት የሚሰጠው ጥገና በጣም በፍጥነት እያደገ ነው


አብዛኛው ሰው ጋራዥ ሄዶ ማሰራት ብዙም ደስ አይለውም :: Ford ይህንን በማሰብ ለደንበኞቹ ቤት ለቤት ጥገና እንዲሁም መኪኖቻቸውን ሰራተኞቻቸው መተው ወስደው ጠግነው እየመለሱ ነው :: Ford ካምፓኒም ይህ ቢዝነሴ በጣም እያደገ ነው ብሏል ::

ባለፈው አመት 2.4 ሚሊየን ቀጠሮዎችን ያስያዙ ተጠቃሚዎች ሲኖሩ በዚህ አመት በመጀመርያው ወር ብቻ 375,000 ደንበኞች ቀጠሮ አስይዘዋል :: 2022 ሲጀመር ከነበረው በ 4 እጥፍ አድጓል :: በተለይ ደግሞ ውድ መኪኖችን የሚገዙ ሰዎች ማለትም ከ 5 ሰው 1 የሊንከን መኪና ባለቤት ይህንን ሰርቪስ ይጠቀማል ::

#Ford #Lincoln
@OnlyAboutCarsEthiopia
#Ad

ለጉዞ የሚሆን መኪና
ከሁሌመኪና

የተለያዩ መኪኖቻችሁን በሁሌመኪና በማስተዋወቅ መሸጥ እና ማከራየትም ትችላላችሁ
በ 0911663121 ላይ በመደወል ወይም ቴሌግራም ላይ @Hulemekinaadmin ላይ የመኪኖቻችሁን ፎቶ (እስከ 10 ፎቶዎችን) በመላክ 300 ብር ብቻ ቴሌብር ላይ በመክፈል መሸጥ እና ማከራየት ትችላላችሁ ::

@hulemekina
2024/09/23 06:38:33
Back to Top
HTML Embed Code: