Telegram Web Link
በአንድ የቁርአን አያ ደንግጦ የሞተዉ ወጣት
አሚር ሰይድ

አቡበከር ወራቅ ቁርአን የሚያጠና አንድ ትንሽ ልጅ ነበራቸዉ፡፡ አንድ እለት ከመማሪያ ቦታዉ ፊቱ ገርጥቶ ጠዉልጎና እንየተንቀጠቀጠ በጊዜ ተመለሰ፡፡ አቡበከር የልጁን ሁኔታ ሲያስተውል በመደነቅ፡- “ምን አጋጠመህ የእኔ ልጅ? ምንድን ነው ሰውነትህን እንዲህ የቀያየረው? በጊዜስ የተመለስከው ለምንድን ነው?'' በማለት ጠየቀው፡፡

በልጁ ትንሽዬ ልብ ውስጥ የአላህ ፍራቻ እያቆጠቆጠ ስለነበር እንደ በጋ ቅጠል ሁለመናውን አጠውልጎት እንዲህ አለ፡- “አባቴ ሆይ! ዛሬ መምህራችን አንድ የቁርዓን አንቀጽ አስተማሩን፡፡ እኔም ትርጉሙን ሳሰላስል እንዲህ ለመሆን በቃሁ። ''

“የትኛው አንቀጽ ነው የእኔ ልጅ?” አለ አባት፡፡ ልጁ የሚከተለውን አንቀጽ አነበበ፡-

{ فَكَیۡفَ تَتَّقُونَ إِن كَفَرۡتُمۡ یَوۡمࣰا یَجۡعَلُ ٱلۡوِلۡدَ ٰ⁠نَ شِیبًا }

ብትክዱ ልጆችን ሸበቶዎች የሚያደርገውን ቀን (ቅጣት) እንዴት ትጠበቃላችሁ፡፡(አል ሙዘሚል 17)


ቆየት ብሎ ይህ ልጅ በዚህ የቁርአን አያ ትርጉም ምክንያት ታመመ:: የአልጋ ቁራኛ ሆኖ ከቆየ በኋላ ብዙም ሳይቆይ ሞተ😔፡፡ አባትዬው በዚህ ክስተት ክፉኛ ነበር የተናጠው። በተደጋጋሚ ወደ ልጁ መቃበር እየሄደ በማልቀስ ለራሱ እንዲህ ይል ነበር-

"አቡበከር ሆይ! ልጅህ ቁርዓንን አንብቦ መልዕክቱን በመገንዘብ አላህን በመፍራት ነፍሱን አስረከበ፡፡ ይሁን እንጂ አንተ ግን ይህን ሁሉ ዘመን ስታነበበው ብትቆይም የልጅህን ያክል እንኳን አላህን ልትፈራ አልቻልክም እያለ ሁሌ ራሱን ይወቅስ ነበር

ምን ያህሎቻችን ነን የቁርአን አያ ትርጉም አዉቀን እራሳችንን የምንፈትሸዉ⁉️



ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አላህ እኔ አፍቃሪያቸዉ ነኝ ይላል
#ለሒጃብ_መገፈፍ ነብዩ ﷺ #የተዋጉበት_ጦርነት
አሚር ሰይድ


በነብዩ ﷺ ዘመን አንዲት ሂጃቧን አስተካክላ በምትለብስ ሴት ላይ በደረሰ በደል ምክንያት
ነብዩ ﷺ ጦር መዝመታቸዉን ምን ያህላችን እናቃለን??
እስከ ወደ ታሪኩ እንለፍ

    የበኒ ቀይኑ ቃዕ አይሁድ ማህበረሰብ በመዲና አካባቢ ይኖሩ የነበሩና ወርቅ በማንጠር የሚተዳደሩ ስስታም ማህበረሰብ ነበሩ:: የጐሳው አባላት ያነጠሯቸውን የወርቅ ጌጣቸዉንም ሆነ ሌላ የወርቅ እጅ ሥራ ውጤታቸውን የሚሽጡበት ልዩ ስፍራ ነበራቸው፡፡በአንድ ወቅት ከነቢዩ ﷺ
ልደረባዎች አንዷ የነበረች ሴት ወደዚያ የወርቅ ገበያ ትሄዳለች።  አንድ እርጉም የሆነ የአይሁድ ሰው የሴትዬዋን ጅልባብ ጫፍ ጭንቅላቷ ጋር በሆነ ነገር ያያይዘዋል፡፡ ይህን ተንኮል ያልተገነዘበችው ሴት ከተቀመጠችበት ስትነሳ ሰውነቷ ለባዕድ ወንዶች በመጋለጡ ሁሉም ሳቁባት፡፡

ይህን ርኩስ ድርጊት የተገነዘበና በአቅራቢያ የነበረ አንድ የነቢዩ ﷺባልደረባ ተንኮል የሰራውን የአይሁድ ሰው ወዲያውኑ እርምጃ በመውስድ የገደለው ሲሆን በአፀፋውም የአይሁዱ ሰው ወገኖች ሙስሊሙን ስው ተረባርበው ገድሉት፡፡


    ይህ የፊትናን እሳት የቆስቆሰው ውዝግብም ጦርነትን ይወልድና ነቢዩ ﷺሰራዊታቸውን አስከትለው የበነ ቀይነ-ቃዕን መንደር ይከቡታል። ከዚያ በኋላም የጐሳው አባላት በሙሉ መዲናን ለቅቀው እንዲወጡ የተገደዱ ሲሆን ከዚያ አካባቢ ድምጥማጣቸው እንዲጠፋ ተደርጓል።

ከዚያ ሁሉ ታላቅ ተጋድሏቸው በኋላ ነቢዩ ﷺ እና ባልደረቦቻቸው የዛሬውን የእኛን ሁኔታ ቢመለከቱ ምን ይሉ ነበር😔? በፍርዱ ቀን ጌታችን አላህ ፊት ስንቀርብ ምን ይሆን የምንመልሰው? ሁሉን አዋቂ ለሆነው አላህ ምን የምንደብቀው ነገር ይኖራል?

⚡️⚡️ሙስሊም ሴቶች ሆይ! ከዚህ ቀጥሎ ደግሞ በጥንቃቄ ልታሰላስሉት የምትችሉትን ታሪክ አቀርብላችኋለሁ:: አንድ ዕለት ኢማም አህመድ ኢብን ሐንበል በመንገድ ላይ ሲጓዙ አንዲት በሚገባ ሒጃቧን የለበሰች ሴት ይመለከታሉ:: በዚያው ቅፅበት ንፋስ እየተግለበለበ መጥቶ ቀሚሷን ተረከዟ እስኪገለጥ ድረስ ወደ ላይ ያነሳዋል:: በዚህ ጊዜ ኢብን ሐንበል በመጐናጸፊያቸው ጠርዝ ፊታቸውን በመሸፍን የሚከተለውን ተናገሩ፡፡
ይህ የፈተና ጊዜ ነዉ!!!
ተመልከቱ! ይህ ሁኔታ እርሳቸው  አስበውት ሳይሆን በአጋጣሚ የተከሰተ ነው፡፡ እንደዚያም ሆኖ ምን ያህል ስሜታቸው እንደተጉዳ ከታሪኩ መገንዘብ አይከብድም፡፡ እኚህ ሰው በአሁነ እኛ ባለንበት ዘመን ቢኖሩ ኖሮ ምን ይሉ ነበር???


⚡️⚡️98% ሴቶች ሂጃብን በራሳቸዉ አመለካከትና የኑሮ ዘይቦ አለባበስ ለእነሱ አለባበስ እንዲመቻቸዉ አድርገዉ ሲተረጉሙት እና እንደሚመቻቸዉ ሲለብሱት የምናየዉ ሀቅ ነዉ ግን አላህ እና ነብዩ ﷺ ሂጃብን እንዴት ነዉ በቁርአንና በሀዲስ የገለፁት??

☞አላህ በቁርአኑ ስለ ሂጃብ ሲገልፅ
ይህ እንዲታወቅና በባለጌዎች እንዳይደፈሩ ለመሆን በጣም የቀረበ ነዉ(አል አህዛብ 59)

☞ለምእምናትም ንገራቸው፡- ዓይኖቻቸውን ይከልክሉ፡፡ ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ፡፡ ጌጣቸውንም ከእርሷ ግልጽ ከኾነው በስተቀር አይግለጡ፡፡ ጉፍታዎቻቸውንም በአንገትጌዎቻቸው ላይ ያጣፉ፡፡(አን-ኑር31)

ሒጃብን መልበስ ለሴቶች በላጭና ምትክ የማይገኝለት የመከላከያ ጋሻ ነው፡፡ ሴት ልጅ ሒጃቧን አስተካክላ ከለበሰች በሰይጣን ግፊት እየታገዙ ከሚፈታተኗት ወንዶች ጉትጕታ ሙሉ በመሉ ማለት ይቻላል ትገላገላለች። ሁሉም ሰው የሚያከብራት ሲሆን የመረጠችው የክብር መንገድ የመጭውን ዓለም ስኬትና ሽልማት የምታገኝበት ነዉ፡፡

   ሙስሊም ሴት ከፀጉሯ ጀምራ አንገቷንና ትከሻዋን፣ ደረቷን የመሸፈን ግዴታ አለባት፡፡ እንግዲህ እነዚህንና ሌሎች መሸፋፈን ያለባቸውን የሰውነት ክፍሎቿን ከባሏ ውጪ ለሆነና ከእነርሱ ጋር ጋብቻ ሊያስመሰርታት የሚችል ባዕድነት ላላቸው ወንዶች ማሳየት አይፈቀድላትም፡፡

⚠️ በነብዩ ﷺ ጊዜ የነበሩ ሴቶች ስለ ሂጃብ የቁርአን አያ ሲወርድ ሱሀቦች መልሳቸዉ ምን ነበር??

    የአላህ መልዕክተኛ ﷺባልደረባዎች ክስተቱን ሲተርኩ እንዲህ ይላሉ፡- "የሴቶችን መሸፋፈን ግዳጅ የሚያደርገው የቁርአን አንቀፅ በወረደበት ጊዜ በአላህ ይሁንብን እያንዳንዷ ሴት ይህን ጉዳይ እንደሰማች ቀሚሷን ለሁለት እየቀደደች በአንደኛው ፀጉሯን፤ በሌላኛው ደግሞ አንገቷንና ደረቷን ያልሽፈነች አንድም አልነበረችም፡፡ ይህንን ያደረጉትም ከፀጉራቸው ጀምሮ ወጥ ሆኖ እስከታችኛው የሰውነታቸው ክፍል ድረስ የሚሽፍን ልብስ ለማግኘት ችግር ስለነበረባቸው ነበር።
ዛሬ ግን ልብስ ሞልቶ ለባሽ በፈለገዉ ፋሺን ሲለበስ ሂጃብን በራሳቸዉ ስሜት በሚያዛቸዉ  ልክ አላህ ካዘዘዉ መመሪያ ዉጭ ለባሽ 98% በላይ ነዉ


ነቢዩ ﷺበተጨማሪም እንዲህ ብለዋል- ከሴቶቻችሁ ሁሉ በላጮቹ
☞ወላድ የሆኑት፣
☞መልካም ፀባይ ያላቸው፤
☞ስታማክሯቸው ምክራቸውን የሚለግሱና
☞ አላህን ፈሪዎቹ ናቸው::''

ከሴቶቻችሁ መጥፎቻቹ ደግሞ
መተበሪጃት (ተገላልጠው የሚሄዱ) የሆኑት
ሙተኸይላት (በኩራት ተወጥረው የሚራመዱና በንግግር የሚደነፉት) ሲሆነ እነርሱ መናፍቃን ናቸው::"

እና አህቴ ሆይ አሁን ባለሽበት አለባበስ ነብዩ ﷺ
እንዳሉት መናፍቃን ሁኜ ይሆን እንዴ ብለሽ አስበሽ ታቂያለሽ??

የአላህ መልዕክተኛ ﷺእንዲህ በማለት ተናግረዋል፦

አሁን የማያቸው ሁለት ዓይነት ሰዎች በጀሃነም ውስጥ ክፉኛ ይቀጣሉ::
#የመጀመሪያዎቹ ቡድኖች ሁልጊዜም ቢሆን ከእጃቸው የበሬ ጅራት (መግረፊያ) የማይለያቸውና በዚያ ያገኙትን ሁሉ የሚገርፉና

#ሁለተኛዎቹ ልብስ የለበሱ ሴቶች ሆኖም ግን የተራቆቱ ከቀናው መንገድ የተዘናበሉ ሌሎችንም እንዲዘናበሉ የሚያደርጉ እንዲሁም ፀጉራቸውን እንደ ግመል ሻኛ የሚቆልሉ ናቸው፡፡ እነዚህ በእርግጥም ጀነት ሊገቡ ቀርቶ ሽታዋን እንኳን አያገኙም። ሽታዋ ከዚህ እስከዚህ ያህል ርቀት የሚገኝ ቢሆንም።
እህቴ ሆይ የአንቺ አለባበስ ከጀነት ሽታ ከሚያገኙት ወይስ ከማያገኙት ነሽ??


✏️ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ይህን የመሰለ ሁኔታ የሚያንፀባርቁ ሰዎች እርሳቸው በነበሩበት ዘመን እንዳላዩ በዚህ ሐዲስ መግቢያ አካባቢ ተጠቅሷል፡፡በአሁን ዘመን ደግሞ ሞልቶ ተትረፍርፏል

ከዚህ አስደንጋጭ ሐዲስ በቀላሉ መገንዘብ እንደምንችለው እነዚያ የጀሃነም እድምተኞች የሆኑት ሴቶች ዋነኛ መለያ የለበሱ ሆኖም ግን ልብሳቸው መላ አካላቸውን ሊሸፍንላቸው ባለመቻሉ የተራቆቱ ናቸው፡፡ እነዚህ ሴቶች ለራሳቸው ጠማማ የሆነውን ይህን የሰይጣን መንገድ ለመከተል መምረጣቸው ሳያንሳቸው ሌሎች ሰዎችም የእንርሱን ፈለግ እንዲከተሉ ብርቱ ጥረትና ግፊት የሚያደርጉ እንደሆኑም ተገልጿል፡፡ አሁን በዘመናችን የፋሽንና የሞዴሊንግ ዓለም ውስጥ በሒጃብ ስም ..ሒጃብ አስመስሎ የሴት ልጅ ቅርስን የሚያሳይ ጉልህ ስፍራን እየተቆጣጠሩ የመጡ እንስታት በትክክል ይህን መንገድ እየተከተሉ እንደሆነ በቀላሉ መገንዘብ አይገድም፡፡ እነዚህ እንስታት ፀጉራቸውን ፈፅሞ የማይሸፍኑ ሲሆን ከዚያም በባሰ እንደ ግመል ሻኛ እየከመሩና የተለያዩ የፀጉር አሰራር ዘዴዎችን፣ እየተከተሉ ሰውን ሁሉ የሚያማልሉ ፍፁም የሰይጣን ደቀ መዛሙርት ናቸው፡፡ እነዚህ ፈፅሞ ጀነት የማይገቡ ናቸዉ



⚠️⚠️ሴቶች ሆይ አለባበሳችንን እንፈትሽ...ወንድ ሆይ የእህትህን የልጅህን የሚስትህን የእናትህን ሂጃብ አለባበስ ፈትሽ የዉመል ቂያማ ላይ እሷም በአለባበሷ አንተም ባለመከልከልህ ተጠያቂ እንዳትሆን¡¡¡

ለሌሎች ያካፍሉ
Join👇👇


www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ጋዛ😔 በዱአ እንበርታ
#ኑዓይም_ኢብኑ_መስዑድ
         አሚር ሰይድ

ስለ ኑዓይም ኢብኑ መስዑድ ምን ያህሎቻችን እናቃለን??

    ኑዓይም ኢብኑ መስዑድ አዕምሮውንና በሳልነቱን በኸንደቅ ዘመቻ ጊዜ ሙስሊሞችን ለማጥፋት የተሰበሰቡትን አህዛቦች (ሙሽሪኮች ገጥፋኖችን፤ በኒ ቁረይዟዎችን) ለመበታተንና አንድነታቸውን ለማፈራረስ ተጠቅሞበታል፡፡ ታሪኩን ኢብኑ ኢስሀቅ እንዲህ ይተርክልናል

በአህዛብ ዘመቻ ጊዜ ረሱል ﷺ ባልደረቦቻቸዉ እጅግ በአስቸጋሪና አስጨናቂ ሁኔታ ላይ ሆነዉ ቆዩ፡፡የሁኔታዉን አስቸጋሪነት አላህ ሱ.ወ በቁርአን እንዲህ በማለት ገልፆታል፡-

{ إِذۡ جَاۤءُوكُم مِّن فَوۡقِكُمۡ وَمِنۡ أَسۡفَلَ مِنكُمۡ وَإِذۡ زَاغَتِ ٱلۡأَبۡصَـٰرُ وَبَلَغَتِ ٱلۡقُلُوبُ ٱلۡحَنَاجِرَ وَتَظُنُّونَ بِٱللَّهِ ٱلظُّنُونَا۠ }

ከበላያችሁም ከናንተ በታችም በመጡባችሁ ጊዜ፣ ዓይኖችም በቃበዙ፣ ልቦችም ላንቃዎች በደረሱና በአላህም ጥርጣሬዎችን በጠረጠራችሁ ጊዜ ያደረገላችሁን አስታውሱ፡፡(ሱራህ አህዛብ 10)

    በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ ኑዓይም ኢብኑ መስዑድ ከረሱል ﷺ ዘንድ መጥቶ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! እኔ ሰልሜያለሁ ህዝቦቼ መስለሜን አያወቁም የፈለጉትን ይዘዙኝ አላቸው፡፡ ረሱልም ﷺ “አንተ በእኛ ውሰጥ አንድ ሰው ነህ ከእኛ ጋር ሆነሃል ከቻልክ ከእኛ እነሱን አጣላልን በታትንልን።ጦርነት ማለት ማታለል ነው›› አሉት፡፡
....ከዚያም ኑዓይም በኒቁረይዟዎች ዘንድ መጣ እሱ በጃሂሊያ ጊዜ መጠጥ አጣጫቸውና ወዳጃቸው ነበር። ከዚያም “በኒቁረይዟዎች ሆይ! ለእናንተ ያለኝን ፍቅር ታውቃላችሁ በተለይ በእኔና በናንተ መካከል ያለውን ፍቅር ታውቃላችሁ አላቸው፡፡ እውነት ብለህል አንተ ከእኛ ጋር የምትጠረጠር አይደለህም አሉት:: ከዚያም እንዲህ አላቸው፡-ቁረይሾችና ገጥፋኖች እንደናንተ አይደሉም። ጦርነት የጀመራችሁበት ሀገር ሀገራችሁ ነው:: ገንዘቦቻችሁ ልጆቻችሁ ሴቶቻችሁ ያሉት እዚሁ ነው:: ከዚህ ሀገር ወደ ሌላ ሀገር መቀየር (መሸሽ) አትችሉም:: ቁረይሾችና ገጥፋኖች ሙሀመድን ለመዋጋት መጥተዋል፡፡ እናንተም አግዛችኋቸዋል:: ነገር ግን የእነሱ ገንዘባቸው ልጆቻቸውና ሴቶቻቸው ያሉበት ቦታ ራቅ ያለ ነው:: በጦርነቱ መልካም ድል ካገኙ ይጠቀሙብታል። ከዚህ ውጭ ከሆነ ወደ ሀገራቸው ይሸሻሉ፡ እናንተን ለሙሀመድ አጋፍጠው ይተዋችኋል፡፡ ስለሆነም እነሱ እንዳይከዳችሁ አብራችሁ ለመጋደል መተማመኛ የሚሆኗችሁ ከተከበሩ ሰዎቻቸው ማስያዣ የሚሆኑ ሰዎች እስክትይዙ ድረስ አነዚህ ህዝቦች ጋር ሆናችሁ እንዳትጋደሉ አላቸው:: እነሱም በጣም የሚገርም ሀሳብ አመላከትከን አሉት፡፡፡

ከዚያም ኑዓይም ቁረይሾች ጋር መጣ:: ለአቡሱፍያንና ከእሱ ጋር ለነበሩት የቁረይሽ ሰዎች እንዲህ አላቸው፡- “ለእናንተ ያለኝን ፍቅርና ሙሀመድ ጋርም የተቆራረጥኩ መሆኔን ታውቃላችሁ እኔ የሆነ መረጃ ደርሶኛል፡፡ ይህም ለእናንተ እንዲሆናችሁ ለእናንተ ማሳወቅ በእኔ ላይ ግዴታ ሆኖ አግኝቻቸዋለሁ:: በሚስጥር ያዙልኝ, አላቸው:: እነሱም እሺ እንደብቅልሃለን አሉት።ከዚያም እንዲህ አላቸው- አይሁዶች በሙሀመድ ላይ በሰሩት ነገር እንደ ተፀፀቱ ታውቃላችሁ። - እንዲህ ብለው ልከውለታል፡- «እኛ በሰራነው ስራ ተፀፅተናል፡፡ ከፈለግክ ከሁለቱ ጎሳዎች ከቁረይሾችና ከገጥፋኖች የተከበሩ ከሆኑ ወንዶቻቸው ይዘን እንሰጥህና አንገታቸውን ትቀላቸዋለህ፡፡ ቀሪዎቹን ደግሞ እስኪበታተኑ ድረስ ከአንተ ጋር ሆነን እንታገላቸዋለን›› ብለውታል፡፡ እሱም እሽ ብሎ ልኮላቸዋል፡፡ ስለሆነም አይሁዶች ከእናንተ ከወንዶቻችሁ ማስያዣፈልገው ከላኩ አንድም ሰው እንዳትሰጧቸው አላቸው፡፡

ከዚያም ገጥፋኖች ጋር መጣና እናንተ የገጥፋን ስብስቦች ሆይ! እናንተ ዘሮቼ ዘመዶቼ ከሰዎች ሁሉ የምወዳችሁ ናችሁ። እኔን ትጠረጠጥሩኛላችሁ ብዬ አላስብም አላቸው:: እውነት ብለሃል አንተ የምትጠረጠር አይደለህም አሉት። እሱም ሚስጥሬን ደብቁልኝ ብሎ ለቁረይሾች የነገራቸውን አይነት ለእነሱም ነገራቸው፡፡ ያስጠነቀቃቸውን ለእነሱም አስጠነቀቃቸዉ

    ከዚያም በ5ኛው ዓመተ ሃጅራ በዛው ወር ቅዳሜ ሌሊት ቁረይሾችና ገጥፋኖች ወደ በኒቁረይዟዎች እንዲህ ብለው ላኩባቸው፡- እኛ ያለነው በሰው ሀገር ነው፤ ግመሎቻችንና ፈረሶቻችን እየጠፉብን ነው ሙሀመድን ተፋልመነው እንድንገላገል ነገ በጧት ተነሱ፡፡››

   በኒ ቁረይዟዎችም እንዲህ ብለው ላኩባቸው ቀኑ ቅዳሜ ነው:: በእዚህ ቀን ምንም የማንሰራበት ቀን ነው:: ከአሁን በፊት ከእኛ የሆኑ ሰዎች ቅዳሜ ቀን ስርተው ምን መከራ እንደመጣባቸው ከእናንተ የተደበቀ አይደለም:: ከዚህ በተጨማሪ መተማመኛ ይሆኑን ዘንድ ከእናንተ ማስያዣ እስክትሰጡን ድረስ ወደ ጦርነቱ አንገባም ምክንያቱም ፍልሚያው ሲበረታባችሁ ወደ ሀገራችሁ ሸሽታችሁ እኛ ብቻችንን ልንፋለመው ለማንችለው ለሆነው ሙሀመድ አጋፍጣችሁን እንዳትሄዱ እንፈራለን ብለው ላኩባቸው:: መልዕክተኞቹም በኑቁረይዟዎች ያሉትን ይዘው ሲመለሱ ቁረይሾችና ገጥፋኖችም በፈጣሪ እንምላለን ኑዓይም የነገራችሁ ነገር ትክክል ነው >> አሉና ወደ በኒ ቁረይዟዎች፡- እኛ አንድም ወንድ አንልክላችሁም ከፈለጋችሁ ውጡና ተጋደሉ›› ብለው ላኩባቸው::
.... በኒ ቁረይዟዎችም መልዕክቱ ሲደርሳቸው «ኑዓይም የነገረን እውነት ነው.. አሉ:: ወደ ቁረይሾችና ገጥፋኖች  ማስያዣ እስክትሰጡን ድረስ እኛ ከእናንተ ጋር ሆነን ሙሀመድን አንዋጋም ብለው ላኩባቸው፡፡ በእነሱ ላይም አመፁባቸው:: አላህ በመሀከላቸው አጣላቸው፤ አንድነታቸውን በታተነው:: ከዚያ አስፈሪ ከሆነው ጭንቀት ተገላገሉ:: ቁረይሾይችና ገጥፋኖች እርስበርሳቸው ተጣልተው ድል ሳይቀናቸው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ:: በዚህ ኑዓይም በተጠቀመው ብልሃት ሰበብ ረሱል ﷺባለድል ሆኑ።

ለዚህ ድል እንዲበቁ ያደረጋቸዉ ኑዓይም(ረ.ዐ)ነበር


ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
#ቅን_ትዉልድ
              አሚር ሰይድ

🔰🔰በአቡበክር (ረ.ዐ) የኸሊፋነት ዘመን ዑመር ኢብነ አል-ኸጣብን (ረ.ዐ) አቡበክር (ረ.ዐ) መዲና ውስጥ በዳኝነት ሾመዋቸው ነበር፡፡

ዑመር ከተሾሙበት እለት አንስቶ አንድ ዓመት እስኪሞላቸው ድረስ አንድም የሚካሰስ ሰው ጠፋ፡፡ ከዚያም ዑመር (ረ.ዐ) ከተሰጣቸው ኃላፊነት እንዲያወርዷቸው አቡበክርን ሲጠይቁ
.....“ዑመር ሆይ! ሥልጣን መልቀቁን የጠየቅከው ፍትሕ ከመስጠቱ አንፃር ነውን?'' አሏቸው፡፡ ዑመርም (ረ.ዐ) “አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ምትክ ሆይ! ፍጹም አይደለም፡፡ ነገር ግን በአማኝ ሕዝቦች መካከል ምንም ጉዳይ ስለሌለኝ ነው፡፡ ሁሉም ለእሱ የሚገባውን በሚገባ አውቋል፡፡ ከሚገባው በላይም ለመጠየቅ አይፈልግም፡፡ ሁሉም በየራሱ ላይ የተጣለበትን ግዴታ አውቋል፡፡ ስለዚህም ግዴታውን ከመወጣት ወደ ኋላ አይልም፡፡ ሁሉም ለራሱ የሚወደውን ሁሉ ለወንድሙ ወድዷል፡፡ በዚህም የተነሳ ወንድማቸው ለአንዲት ቀን ከተሰወረባቸው ይፈልጉታል፡፡ ከታመመም ይጠይቁታል፡፡ ከተቸገረም ይረዱታል፡፡ ከእነሱ አንዳች ነገር ከፈለገ ይሰጡታል፡፡ አንዳች መከራ ወይም ሀዘን ከደረሰበት አብረው ይካፈሉታል፡፡ ሃይማኖታቸው መመካከር ነዉ፡፡ስነ ምግባራቸዉ በጥሩ ነገር ማዘዝ ከመጥፎ ነገርም መከልከልን ነዉና በምን ላይ ተጣልተዉ ይካሰሱ??አሏቸዉ
==========\=========\=========\===

🔰🔰 ዑመር ኢብነ አል ኸጧብ (ረ.ዐ) ስለ አበብክር አስ-ሲዲቅ (ረ.ዐ) እንዲህ ብለዋል-

አቡበክር ሁልጊዜ ፈጅር ከሰገዱ በኋላ መዲና ውስጥ አንድ ቤት ያመሩ ነበር። ወደዚያ ቤትም ሄድኩ፡፡ እዚያ ቤት ወስጥ ዓይኑ ስውር የሆነችና በእድሜ የገፋች ሴት ትኖራለች፡፡ ሄድኩና "አንቺ ማን ነሽ? አልኳት፡፡ "እኔ የሽመገልኩ ሴት ነኝ ስትል መለሰችልኝ
.... "ይህ ሰው ማን ነው? ስል ጠየቅኳት "ይህ ሰው ወደቤታችን እየመጣ ፍየላችንን ያልብልናል። ልብሳችንንም ያጥብልናል። ምግባችንንም ካዘጋጀ ቡኋላ ይሄዳል" አለችኝ፡፡ ይህን ጊዜ ዑመር (ረ.ዐ) ስቅስቅ ብለው አለቀሱና አጉንብለው ከእርስዎ ቡኋላ ያሉትን ኸሊፋዎች በእርግጥ በጣም እድክመዋል አሉ፡፡
====\======\========\======\=====

 🔰🔰 በአንድ ወቅት ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር ኢብነ አል-ኸጧብ (ረ.ዐ) ታመው ሳለ ወይን መብላት አስኛቸውና እንዲመጣላቸው አዘዙ፡፡ ነገር ግን ወቅቱ ወይን የሚፈራበት ወቅት ባለመሆነ ሰ.ፈለግ ታጣ፡፡ ከብዙ ጊዜያት በኋላ አንድ ሰው ዘንድ ተገኝቶ ሰባት የወይን ፍሬዎችን በአንድ ዲርሃም ገዝተው አመጡላቸው፡፡ እሳቸው አምሮታቸውን ለማርካት ሊመገቡ ወደ አፋቸው ገና እንዳስጠጉት አንድ ምስኪን መጥቶ ለመናቸው እሳቸውም መብላታቸውን በመተው የወይኑን ጣዕም ሳይቀምስ ሁሉንም ለምስኪኑ እንዲሰጥ አደረጉ፡፡
=====\======\======\======\=====

🔰🔰 ከዕለታት አንድ ቀን ዘይነል-ዓቢዲን (ረ.ዐ) “አንተ በእርግጥ ከሰዎች የበለጠ እናትህን በማገልገል ቅን ነህ፡፡ ነገር ግን ለምንድን ነው ከእሷ ጋር በአንድ ማእድ ላይ የማትበላው?" ተብለው ሲጠየቁ ከኔ በፊት ዓይኖቿ ቀድመው ያረፉበትን ቦታ እጆቼ እጆቿን ቀድመዋቸው ዋልጌ እንዳልሆንባት አላህን ፈርቼ ነው" በማለት መለሱ፡፡


ሱብሀነሏህ!!!

✏️እስልምና ይህን ትዉልድ አፍሮቶ ነበር ዛሬስ ለሙስሊም ወንድም እህቶቻችን ለጎረቤት ለቤተሰቦቻችን እንዴት ነን?


ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
#ምን_የቀረ_ምክር_አለ⁉️
     አሚር ሰይድ

ኻሊድ ኢብኑ ወሊድ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት አንድ የገጠር ሰው ወደ አላህ መልዕክተኛ ﷺ መጣና “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! በምድርም ሆነ በዘልአለማዊው ዓለም (አኺራህ) የሚጠቅመኝ ነገር ልጠይቅህ መጣሁ” አላቸው፡፡ እሳቸውም “ያሻህን ጠይቅ" አሉት፡፡

እሱም
ከሰዎች በላይ አዋቂ ለመሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡ እሳቸውም
>>“አላህን ፍራ ከሰዎች በላይ አዋቂ ትሆናለህ' አሉት፡፡

ከሰዎች የበለጥክ ሀብታም ለመሆን እፈልጋለሁ” አላቸው፡፡
>>“አላህ የሰጠህን ነገር በፀጋ የምትቀበል ሁን፤ ከሰዎች የበለጥክ ሁብታም ትሆናለህ" አሉት፡፡

“ከሰዎች የበለጠ ፍትሀዊ  ሰው መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“ለራስህ የምትወደውን ለሌሎች ሰዎች ውደድ! ከሰዎች የበለጠ ፍትሀዊ ሰው ትሆናለህ' አሉት፡፡

ከሰዎች የበለጥኩ መልካም መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>"ለሰዎች ጠቃሚ ሁን፤ ከሰዎች በበለጠና መልካም ትሆናለህ" አሉት፡፡

ከሰዎች በበለጠ ወደ አላህ የቀረብኩ መሆን እፈልጋለሁ” አላቸው፡፡
>>“አላህን ማስታወስን አብዛ፣ ከሰዎች በበለጠ ለአላህ የቀረብክ ትሆናለህ" አሉት፡፡

እምነቴ ምሉእ እንዲሆን እፈልጋለሁ” አላቸው፡፡
>>“ሥነ-ምግባርህን መልካም አድርግ ! እምነትህ ምሉእ ይሆናል" አሉት፡፡

መልካም ከሚፈፅሙት መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>"አላህ የማታየው ብትሆንም እንኳ እሱ ያይሃልና እንደምትመለከተው አድርገህ ተገዛው፧ መልካም ከሚፈጽሙት ሰዎች መሆን ትችላለህ" አሉት፡፡

“አላህን በቅን ከሚታዘዙት መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው::
>>“አላህ ግዴታ ያደረገብህን ተግባራት ፈፅም፣ አላህን በቅን ከሚታዘዙት ትሆናለህ" አለት፡፡

“አላህን ከኃጢአት የጠራሁ ሆኜ ለመገናኘት እፈልጋለሁ አላቸው፡፡
>>“ሚስትህ ጋር ግብረ-ሥጋ ግንኙነት ከፈፀምክ በኋላ ለመንፃት ብለህ ታጠብ፤ ከኃጢአት የፀዳህ ሆነህ አላህን ትገናኘዋለህ" አሉት፡፡

“በትንሳኤ ቀን (የውመል ቂያማህ) ብርሃን ውስጥ ሆኜ ከሞት መቀስቀስ እፈልጋለሁ'' አላቸው፡፡
>>“ራስህን አትበድል፤ ማንንም ሰው አትበድል፡ በትንሳኤ ቀን በብርሃን ውስጥ ሆነህ ትቀሰቀሳለህ" አሉት፡፡

ጌታዬ በትንሳኤ ቀን እንዲያዝንልኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>> “ለራስህ እዘን፤ ለባሪያዎቹም እዘን፤ በትንሳኤ ቀን ጌታህ ያዝንልሃል" አሉት፡፡

ኃጢአቶቼ እንዲያንስልኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>> “ምሕረት መጠየቅን አብዛ፤ ኃጢአቶችህ ያንሱልሃል" አሉት፡፡

"ከሰዎች በበለጠ ቸር ለመሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“ችግሮችህን ለፍጡራን አቤት አትበል፤ ከሰዎች በበለጠ ቸር ትሆናለህ" አሉት፡፡

"ከሰዎች በበለጠ ብርቱ መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>"በአላህ ላይ ተመካ፤ ከሰዎች በበለጠ ብርቱ ትሆናለህ" አሉት፡፡

“አላህ ሲሳዬን እንዲያሰፋልኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“ንፅሕናን አብዛ፤ አላህ ባንተ ላይ ሲሳይህን ያሰፋልሃል'' አሉት፡፡

“አላህንና መልዕክተኛውን ከሚወዱ ሰዎች መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“አላህና መልዕክተኛ የሚወዱትን ውደድ፤ አላህንና መልዕክተኛውን ከሚወዱ ሰዎች ትሆናለህ" አሉት፡፡

“በትንሳኤ ቀን ከአላህ ቅጣት የተጠበቅኩ መሆን እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>> “አላህ ከፈጠራቸው ፍጡራኖች በአንዱም ላይ አትበሳጭ" አሉት፡፡

“ዱዓዬ ተቀባይነት እንዲያገኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>>“ሁሉንም ክልክል የሆኑ ነገሮች ከመመገብ ራቅ፧ ዱዓህ ተቀባይነትን ያገኛል" አሉት፡፡

“ጌታዬ በትንሳኤ ቀን እንዳያጋልጠኝ እፈልጋለሁ" አላቸው፡፡
>> “በትንሳኤ ቀን ጌታህ እንዳያጋልጥህ ከፈለግክ ብልትህን ከዝሙት ጠብቅ” አሉት፡፡

“ጌታዬ በትንሳኤ ቀን ገመናዬን እንዲደብቅልኝ እፈልጋለሁ” አላቸው፡፡
>>የወንድሞችህን ገመና ደብቅ፡ አላህ ያንተን ገመና በትንሳኤ ቀን ይደብቅልሃል" አሉት፡፡

ከኃጢአቶችና ከስህተት ነፃ የሚያደርግ ነገር ምንድን ነው?” አላቸው፡፡
>>"እንባ፣ ቅን ታዛዥነትና በሽታዎች ናቸው" አሉት፡፡

በአላህ ዘንድ በላጩ ምንዳ የትኛው ነው? አላቸው፡፡
>>“መልካም ሥነ-ምግባር፣ መተናነስና በመከራ ጊዜ ትዕግስት ማድረግ ናቸው˚ አሉት፡፡

በአላህ ዘንድ በጣም ትልቁ ኃጢአት የትኛው ነው?" አላቸው፡፡
>>መጥፎ ሥነ-ምግባርና ስግብግብነት ናቸው አሉት፡፡

በምድራዊውና በዘልዓለማዊጡ ዓለማት የአላህን ቁጣ የሚያበርዱ ነገሮች የትኞቹ ናቸው?" አላቸው::
>> "በድብቅ የምትሰጥ ሰደቃህ (ምፅዋት) እና ዝምድናን መቀጠል ናቸው" አሉት፡፡

በትንሳኤ ቀን የጅሀነምን እሳት የሚያጠፋ ነገር ምንድን ነው?" አላቸው፡፡
>>“በምድራዊው ዓለም ችግርና መከራ ሲያጋጥም ትዕግስት ማድረግ ነው” አሉት፡፡"

ሀምሌ17/11/2016
ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
#ትልቅ_አስተምህሮ
  አሚር ሰይድ

ዐብዱረሕማን ኢብኑ ሰሙራህ (ራዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ ﷺአንድ ቀን ወደኛ መጥተው የሚከተለውን ነብያዊ ንግግር አደረጉልን። እንዲህም አሉን-

“ዛሬ ቀን አንዳች የሚገርም ሕልም አይቻለሁ እርሱም

➊. ከሕዝቦቼ መካከል አንዱ የሞት መልአክ ሕይውቱን ሊነጥቀው ወደርሱ _ መጣ _ ለወላጆቹ የነበረው ቅን ታዛዥነት ወደርሱ በመምጣት የሞት መልአክ የሰውየውን ሕይወት እንዳይወስድ ሲከለክልለት ተመልክቻለሁ !

➋. ከሕዝቦቼ መካከል አንዱ ሰይጣኖች ከበውት ሳለ የአላህ ማስታወስ ወደርሱ በመምጣት ሰይጣኖችን ከርሱ አባረረለት፤

➌. ከሕዝቦቼ መካከል አንዱ የጀሀነም መላእክት ከበውት ሳለ የሚሰግዳት ሰላት ወደርሱ በመምጣት ከእጃቸው ስትነጥቀው ተመልክቻለሁ

➍. ከሕዝቦቼ መካከል አንዱ በጥም ሳቢያ ከአንድ ኩራ አጠገብ ሊጠጣ ሲል ተባረረ፡፡ ጾም ወደርሱ በመምጣት ሲያጠጣው ጥሙንም ሲያረካለት ተመልክቻለሁ

➎. ከሕዝቦቼ መካከል አንዱ ነብዮች በቡድን በቡድን ተቀምጠው ሳለ ወደ አንድ ቡድን በሄደ ቁጥር እንዳይቀመጥ ይከለከልና ይበረር ነበር፡፡ ለጀናባ ያደረገው ትጥበት ወደርሱ በመምጣት ከኔ ጐን ሲያስቀምጠው ተመልክቻለሁ !

➏. ከሕዝቦቼ መካከል አንዱ ከፊት ለፊቱም፣ ከጀርባውም፤ ክቀኙም ከግራውም _ ከሁሉም : አቅጣጫው : ጨለማ አካብቦት ነበር፡፡ ያደረጋቸው ሐጅና ዑምራ መጥተው ከጨለማ አውጥተው ወደ ብርሃን ሲያስገቡት ተመልክቻለሁ

➐. ከሕዝቦቼ መካከል አንዱ በእጆቹ የእሳት ነበልባልን ሲከላከል የሰጣት ምጽዋት ወደርሱ መጥታ በእሱ ላይ ጥላ ስትሆን ተመልክቻለሁ

➑. ከሕዝቦቼ መካከል አንድ ሙእሚኖችን ሲያናግር እነሱ ግን አያናግሩትም ነበር። ሲቀጥለው የነበረው ዝምድናን የመቀጠል ተግባር ወደርሱ በመምጣት ሙእሚኖች ሆይ! እሱ ዝምድናውን ሲቀጥል የነበረ ሰው ነውና እናግሩት ጨብጡትም ሲላቸው ተመልክቻለሁ

➒. ክሕዝቦቼ መካከል አንዱ የጀሀነም ዘበኞች አዋክበውት ላለ ሲፈፅመው የነበረው በመልካም የማዘዝና ከመጥፎ የመከልከል ተግባር ወደርሱ በመምጣት አከዘበኞቹ እጅ ነፃ ሲያደርገውና ወደ እዝነት መላእክት ሲያስረክበው ተመልክቻለሁ!

➓.ከሕዝቦቼ መካከል አንዱ ከፊት ለፊቱ አንዳች ግርዶሽ ኖሮ ሳለ መልካም ሥነ-ምግባሩ ወደርሱ በመምጣት እጁን ይዞ ወደ ጌታው ሲያስገባው ተመልክቻለሁ

➊➊.ከሕዝቦቼ መካከል አንዱ የሠራው ሥራ መዝገብ በግራ እጁ መጣለት፡፡ ለአላህ ያለው ፍራቻ ወደርሱ በመምጣት መዝገቡን በቀኝ እጁ ሲያደርግለት ተመልክቻለሁ፤

➊➋.ከሕዝቦቼ መካከል አንዱ የመልካም ሥራዎቹ ሚዛን ክብደት ሲያንስ ከአብራኩ የተገኙት ልጆቹ ሲሞቱ ያደረጋቸው ትዕግስቶች ወደርሱ በመምጣት ክብደቱ ከፍ እንዲል አደረጉ፡፡ በዚህም ከቅጣት ሲድን ተመልክቻለሁ፤

➊➌.ከሕዝቦቼ መካከል አንዱ በእሳት ላይ ሲንሳፈፍ አላህን ፈርቶ ያፈሰሳት እንባው ወደርሱ መጥታ ያለበትን እሳት በማጥፋት ከእሳት ነፃ ስታወጣው ተመልክቻለሁ፣

➊➍.ከሕዝቦቼ መካከል እንዱ በጀሀነም አፋፍ ላይ ሳለ አላህን በፅኑ የመፈለጉ ባሕሪው ወደርሱ  በመምጣት ከጀሀነም እንዲርቅ ሲያደርገው ተመልክቻለሁ፤

➊➎.ከሕዝቦቼ መካከል አንዱ በሲራጥ ላይ ልክ ኃይለኛ ነፋስ ሲመጣ ከወዲያ ወዲህ እንደምትወዛወዝ የቴምር ዛፍ እሱም ሲንቀጠቀጥ በአላህ ላይ ያለው መልካም ጥርጣሬ ወደርሱ በመምጣት እንዲረጋጋና ባለበት እንዲረጋ ሲያደርገው ተመልክቻለሁ፤

➊➏.ከሕዝቦቼ መካከል አንዱ ሲራጥ ላይ በደረቱ ሲሳብና ሲድህ በኔ ላይ ያደረገው ሶላት (አላሁመ ሶሊ ዐላ ሙሐመድ) ወደርሱ በመምጣት በትክክል በሲራጥ ላይ እንዲሄድ ስታደርገው ተመልክቻለሁ፤

➊➐.ከሕዝቦቼ መካከል አንዱ ከፊት ለፊት የጀነት በሮች ሲዘጉ በእርግጥ ከአላህ በስተቀር አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም እኔም የአላህ መልዕክተኛ መሆኔን አረጋግጦ የሰጠው ምስክርነት ወደርሱ በመምጣት የጀነት በሮችን ከፍታ ጀነት እንዲገባ ስታደርገዉ ተመልክቻለሁ ብለዉ ተናግረዋል፡፡


ይህ ነብያዊ ሐዲስን አቡ ሙሳ አል-መድየኒይ (ረ.ዐ) “አት-ተር ጊቡ ፈር-ል- ኺሷል አል-መንጂይያህ" በተሰኘው መፅሀፋቸው የዘገቡት ሲሆን ኢብኑ ተይሚይያህ (ረ.ዐ) ይህን ነብያዊ ሐዲስ ትልቅ ቦታ ከመስጠታቸው ባሻገር "ለትክክለኛነቱ በርካታ ማስረጃዎች አሉ'' በማለት ተናግረዋል፡፡

ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
💚 #ሀቢቡና_ሙሀመድ

    አሚር ሰይድ

ኢብኑ ኢስሀቅ እንደዘገቡት ሐሊመንት ቢንት አል ሀሪስ ስለ ሀቢቡና ሙሀመድ ﷺ አስተዳደግ እንዲህ ሰትል አስተላለፈች


    «ድርቅ በሆነበት ዓመት ከሌሎች የበኒ ሰዕድ እንስቶች ጋር ሆኜ የማደጎ ልጅ ፍለጋ ወደ መካ መጣን፡፡ ከደከመች ነጭ አሀያ ላይ ሁኜ ነበር የመጣሁት። ልጄ እና አንዲት ያረጆች ግመል አብራን ነበረች። ምንም ወተት አትታለብም ነበር። ልጃችን ሲርበው ስለሚያለቅስ ሌሊቱን ሙሉ እንቅልፍ የለንም። ጡቴ ምንም ነገር የለውም፡፡ ግመሌም ጋቷ ደርቋል" አላህ ከዚህ ጭንቅ እንደሚገላግለን ተስፋ እናደርግ ነበር።

መካ ደረስን። የአላህ መልዕክተኛ ﷺበማደጎ ልጅነት ቀርበውላት አልወስደውም ያላለች ሴት አላውቅም። የቲም ነው ሲባሉ ሴቶች ሁሉ ይተዉታል። «እናቱ ምን ታደርግልኛለች?» በማለት። ምክንያቱም የማደጎ ልጅ የምንወስደውም ከአባቱ አንዳች በጎ ነገር ፍለጋ ነው፡፡

ሁሉም ባልንጀሮቼ የማደጎ ልጅ አገኙ። እኔ ብቻ ቀረሁ። ከነቢዩ ውጭ ሌላ አጣን። ባዶ እጃችንን ልንመለስ ስንል ባሌን ሁሉም ባልንጀሮቼ የማደጎ ልጅ አግኝተው እኔ ባዶ እጄን አልመለስም» አልኩት፡፡ እናም ይህን የቲም ልጅ ለመውሰድ መወሰኔን ነገርኩት።

«ጥሩ አስበሻል። ምናልባትም አላህ በርሱ ስበብ በረከትን ይስጠን ይሆናል» አለ። ሄድኩና ያዝኩት። ሌላ ልጅ ስላጣሁ ብቻ ነው ይህን የቲም ለመውሰድ የተገደድኩት። ይዤው ወደ መኖሪያዬ ስሄድ ጡቴ ወተት ቋጠረ። ይህ ልጅ እስኪጠግብ ጠጣ። ወንድሙም እንዲሁ ጠጣ። ባለቤቴ ወደ ግመሏ ሄደ። ጋቷ ሞልቶ አገኘው፡፡ አለባትና ለኔም ለርሱም ጠጣን።

ጥሩ ሌሊት አሳለፍን። ሲነጋ “ሐሊማ ሆይ! የተባረከ ልጅ ያገኘሽ ይመስለኛል። እርሱን ካገኘን በኋላ እንዴት ዓይነት ደግና በረከታማ ሌሊት እንዳሳለፍን አላየሽምን?» አለኝ።

አላህ በረከቱን ያክልልን ጀመር። ወደ አገራችን ስንመለስ አህያዬ ጉልበት ጨመረች። ፈጥና ትገሰግስም ገባች። ባልንጀሮቼL «ይቺ የመጣሽባት አህያ አይደለችምን?» ይሉኝ ነበር። እርሷው መሆኗን ስነግራቸው አንዳች ነገር እንዳገኛት ይነግሩኛል። በዚህ ሁኔታ ከበኒ ሰዕድ ምድር ደረስን አገራችንን ገባን"

በአላህ እምላለሁ በዚሀች ምድር ላይ እንደቀያችን ደረቅ ወይም ምድራ በዳ የሆነ ምድር ያለ አይመስለኝም። ይህም ሆኖ ግን ፍየሎቼ ውለው ሲገቡ ጠግበውና ወተታቸው ሞልቶ ነው፡፡ በዙሪያችን ያሉ ሰዎች የፍየሎቻቸው ጋቶች ደርቀው ጠብታ ወተት እንኳ በማይሰጡበትና በሚራቡት ሁኔታ የኔ ፍየሎች ይጠግባሉ፡ ይታለባሉ፡፡ ከኔ ፍየሎች ጋር እንዲያሰማሩ ይመክሯቸው ነበር"

እረኞችም ፍየሎቻቸውን ከኔ ፍየሎች አጠገብ ያሰማራሉ። ግን የነርሱ ተርበው ይመለሳሉ" ጠብታ ወተት እንኳ አይሰጡም። የኔዎቹ ግን ጋቶቻቸው ሞልተውና ጠግበው ይመለሳሉ፡፡አላህ የተለያዩ በረከቶችን እያሳየን ይህ ልጅ አደገ"


አስተዳደግ ከሌሎች ልጆች የተለየ ነው። ሁለት ዓመት ሲሞላው ምግብ መመገብ የሚችል ሆነ። ጡት መጥባቱን አቆመ። ልጁን ባየንበት በረከት የተነሳ በጣም ብንፈልገውም ለእናቱ መመለስ ስለነበረብን ይዘነው ሄድን።
.... እናቱ ስታየው ሌላ አንድ ዓመት ከኛ ጋር ይቆይ ዘንድ ፍቀጅልን! የመካ ወረርሽኝ እንዳያገኘው እንሰጋለታለን» አልናት። በአላህ እምላለሁ! ደጋግመን ጠየቅናት። በመጨረሻ ፈቃደኛ ሆነች። መልሼ ወሰድኩት። ሦስት ወራት ያህል ቆየን።



      አንድ ቀን ከቤታችን ጀርባ ከልጅ ጋር በመጫወት ላይ እያለ ልጁ በድንጋጤ ተዉጦ መጣ...ሙሐመድን ሁለት ነጭ ልብስ የለበሱ ሰዎች መጥተው ካስተኙት በኋላ ሆዱን ቀደዱት» አለ።
....እኔና ባሌ ደንግጠን ወደርሱ በረርን። ቆሞ አግኘነው። ገፅታው ተለውጧል።ባሌ አቀፈውና ምን አገኘህ?» ሲል ጠየቀው፡ ነጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች መጡና

አስተኝተውኝ ሆዴን በመቅደድ አንዳች ነገር አውጥተው ጣሉት። ከዚያ በኋላ እንደነበር መለሱለት» አለን። ወደቤት መለስነው።
....ባሌም ሐሊማ ሆይ! ልጁ አንዳች ነገር አግኝቶት እንዳይሆን እሰጋለሁ» አለኝ። የምንፈራው ነገር ከመከሰቱ በፊት ለቤተሰቦቹ ልንመልሰው ተስማማን። ተሸከመን ወሰድነው፡፡ ከእናቱ ዘንድ ስንደርስ፣ ምን ሆናችሁ አመጣችሁት? ከናንተ ጋር እንዲቆይ ጓጉታችሁ አልነበረምን?» አለችን።

«አዎ፣ በእርግጥ ብለን ነበር። አላህ ፍላጎታችንን ሞልቶልናል። አንዳቸ ክፉ ነገር ሳያገኘው በፊት ወደናንተ እንመልሰው ብለን ነው» አልን።
«ምን ሆናችሁ ነው? እውነቱን ንገሩኝ?» አለች። እንድንነግራት አጥብቃ ጠየቀችን። የሆነውን ነገርናት። «ሰይጣን ሰግታችሁለት ነውን? ይህን ልጅ ሰይጣን አያገኘውም። የተለየ ተሰጥኦ ያለው ልጅ ነው.

በማለት በእርግዝናዋ ወቅት ያጋጠማትን አጫወተችን «እርግዝናዬ በጣም ቀላል ነበር። አንድ ቀን በሕልሜ አንዳች ብርሃን ከኔ ዘንድ ወጣ። የሻምን ሕንፃዎች ሲያበራ አየሁ፡፡ አወላለዱም ከሌሎች ልጆች የተለየ ነው፡፡ እጆቹን ተመርኩዞና ራሱን ወደሰማይ አቅንቶ ነበር» አለችን።»

ሀቢቡና ሙሀመድ ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም

ይህ ሐዲስ በበርካታ የሐዲስ መስመሮች ተላልፏል። እጅግ ሰፊ ተቀባይነት ካላቸው ሐዲሶች መካከል አንዱ ነው፡፡



join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
#አላህን_የት_ትወነጅለዋለህ??
አሚር ሰይድ


ከዕለታት አንድ ቀን እንድ ሰው ወደ ኢብራሃም ኢብኑ አድሀም( አላህ ይዘንላቸውና) በመምጣት ለመፈፀም የሚፈልገውን የኃጢአት ዓይነት ጠቀሰላቸው፡፡
....እሳቸውም “አላህን ለመወንጀል ከፈለግክ እሱ በፈጠራት ምድር ላይ እንዳትኖር፤ እሱ በፈጠራት ሰማይ ሥርም አትቁም' አሉት፡፡

ሰውየውም በመገረም “አላህ ከፈጠራት ምድር ሌላ ምድር አለን? እንዲሁም ከፈጠራት ሰማይ ሌላ ሰማይ አለን?" ሲል ጠየቃቸው፡፡ እሳቸውም “ታዲያ ይህን ካወቅክ በእሱ መሬት ላይ እየኖርክ በርሱ ሰማይም ስር እየተጠለልክ ልትወነጅለው ይቻልሃልን?!' አሉ፡፡ ሰውየውም ፈፅሞ አይቻለኝም በማለት በሁለተኛ ደረጃ የሚሰጡትን ምክሮ አዲለግሱት ጠየቀ፡፡


እሳቸውም “አላሁን ለመወንጀል ከፈለግክ ከሲሳዩ አንዳች ነገር አትመገብ አሉት፡፡ ሰውየው እንደገና በመልሳቸው በጣም በመገረም “ለአላህ ጥራት ይገባው! ከአላህ ሲሳይ ውጭ ሌላ ሲሳይ ይገኛልን?” ሲል ጠየቃቸው፡፡
.....እሳቸውም በምድሩ ላይ እየኖርክ፤ በሰማዩም እየተጠለልክ፤ ከሲሳዩም እየተመገብክ ልትወነጅለው ይቻልሃልን?!' አሉት::


ሌላ ምክር ይጨምሩልኝ አላቸው፡፡
....እሳቸውም ምክራቸውን ቀጥለው "አላህን (ሱ.ወ) ለመወንጀል ከፈለግክ መለከል መዉት ወደ አንተ ሲመጣ ንስሀ እስከማደርግ ድረስ ትንሽ ጊዜያት ጠብቀኝ" በለው ወይም ከርሱ አምልጥ" አሉት።

ሰውየውም  በጣም  የሚገርም ነው! የሰው ልጅ የሕይወት ፍፃሜ ሊዘገይ ይችላል?! ፍፁም የማይመስል ነገር ነው:። ምክንያቱም አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ብሏል አይደለምን?

فَإِذَا جَاۤءَ أَجَلُهُمۡ لَا یَسۡتَـٔۡخِرُونَ سَاعَةࣰ وَلَا یَسۡتَقۡدِمُونَ

"ጊዜያቸውም በመጣ ወቅት ጊዜ አንዲትን ሰዓት ‎ አይቆዩም አይቀድሙም(አን ነህል 61)

“አራተኛውን ምክርዎትን ይጨምሩልኝ" አላቸው፡፡ እሳቸውም "በአላህ (ሱ.ወ) ምድር ላይ እየኖርክ በሰማዩም እየተጠለልክ ሲሳዩንም እየተመገብክ እሱን ልትወነጅል ይቻልሃልን!? ካሉት በኋላ "አላህን (ሱ.ወ) ለመወንጀል ከፈለግክ የጀሀነም ዘበኞች ወደ ጀሀነም እሳት ይዘውህ ሊሄዱ ሲሉ ከነርሱ አምልጥ ወይም ወደ ጀነት ሽሽ አሉት፡፡ ሰውየውም “ለአላህ ጥራት ይገባው! እነሱ እኮ


عَلَیۡهَا مَلَـٰۤىِٕكَةٌ غِلَاظࣱ شِدَادࣱ لَّا یَعۡصُونَ ٱللَّهَ مَاۤ أَمَرَهُمۡ وَیَفۡعَلُونَ مَا یُؤۡمَرُونَ
በእርሷ ላይ ጨካኞች፣ ሀይለኞች የሆኑ መላእክት አሉ፡፡ አላህን ያዘዛቸውን ነገር (በመጣስ) አያምፁም፡፡ የሚታዘዙትንም ሁሉ ይሠራሉ(አት ተህሪም6)

የተባሉት መላእክት ናቸው" አላቸው፡፡ እሳቸውም “በርሱ ምድር ላይ እየኖርክ፣ በሰማዩ እየተጠለልክ፤ የመሞቻ ቀን እየተቃረበ መሆኑን እያወቅክ፤ ከጀሀነም ዘበኞች ማምለጥ እንደማትችል እየተረዳህ አላህን (ሱ.ወ) ልትወነጅል ይቻልሃልን?" አሉት፡፡ ሰውየውም “ፍፁም አይቻለኝም ካላቸዉ ቡሀላ በዚህ የኢብራሂም ኢብኑ አድሀም ምክር ወደ አላህ(ሱ.ወ)ተዉባህ አድርጎ አላህ(ሱወ)በመታዘዝ ላይ በርትቶ ብዙ አመታት ከቆየ ቡሀላ ሞተ፡፡


⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️

#አላህን_ምህረት_ጠይቅ

አንድ ሰው ወደ ሐሰነ-ል-በስሪይ (ረ.ዐ) መጥቶ የዝናብ መቋረጥን በምሬት ነገራቸው እሳቸውም “አላህን ምሕረት ጠይቅ" አሉት፡፡
....ሌላ ሰው መጣና የውሀ ማነስን በምሬት ነገራቸው፡፡ ለእሱም “አላህን ምሕረት ጠይቅ” አሉት፡፡
......ሶስተኛ ሰው መጣና የልጆቹ ቁጥር ማነስ በምሬት ነገራቸው፡፡ ለእሱም እንደሌሎቹ "አላህን ምሕረት ጠይቅ" አሉት፡፡
.....አራተኛ ሰው መጣና “ምድሪቱ ምርት ከመስጠት ደርቃለች" በማለት በምሬት ነገራቸው፡፡ እሱንም ለአንደኛው ለሁለተኛውና ለሶስተኛው ሰው እንዳሉት “አላህን ምሕረት ጠይቅ" አሉት፡፡



ሰዎቹ ከሄዱ በኋላ አብረዋቸው የነበሩት “ሐሰነል-በስሪይ ሆይ! የሚጠይቅዎት ስው በመጣ ቁጥር “አላህን ምሕረት ጠይቅ" ይላሉን?" በማለት በግርምት ጠየቋቸው፡፡ እሳቸውም ይህ የአላህ ቃል አልገባችሁምን? ብለው የሚከተለውን የቁርአን አንቀጽ ለሰዎቹ አነበቡላቸው፡፡


{ فَقُلۡتُ ٱسۡتَغۡفِرُوا۟ رَبَّكُمۡ إِنَّهُۥ كَانَ غَفَّارࣰا }{ یُرۡسِلِ ٱلسَّمَاۤءَ عَلَیۡكُم مِّدۡرَارࣰا
{ وَیُمۡدِدۡكُم بِأَمۡوَ ٰ⁠لࣲ وَبَنِینَ وَیَجۡعَل لَّكُمۡ جَنَّـٰتࣲ وَیَجۡعَل لَّكُمۡ أَنۡهَـٰرࣰا }


አልኳቸውም፡- ጌታችሁን ምሕረትን ለምኑት፡፡ እርሱ በጣም መሐሪ ነውና፡፡በእናንተ ላይ ዝናምን ተከታታይ አድርጎ ይልካል፡፡በገንዘቦችና በልጆችም ይለግሰላችኋል፡፡ ለእናንተም አትክልቶችን ያደርግላችኋል፡፡ ለእናንተም ወንዞችን ያደርግላችኋል፡፡»(ኑህ10-12)


ወንድሜ እህቴ ሆይ አላህን ምህረት መጠየቅ እናብዛ


join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
#ዲናሩል_ከዕቢይ
አሚር ሰይድ

ዲናሩል-ከዕቢይ (አላህ ይዘንላቸውና) በኃጢአትና በወንጀል ላይ የተዘፈቁ ሰው ነበሩ፡፡ ከልጅነታቸው አንስቶ የምትመክራቸው እናት የነበራቸው ቢሆንም የእናታቸውን ምክር ፈፅሞ አይቀበሉም ነበር፡፡

    ከዕለታት አንድ ቀን ብዙ የአስክሬን አጥንቶች ባሉበት የቀብር ስፍራ  በኩል ሲያልፉ አንዱን አጥንት አንስተው ካደቀቋት በኋላ " #አንቺ_ነፍሴ_ሆይ! ወየውልሽ!" አሉ፡፡ ለትንሽ ጊዜያትም ፍፃሜያቸውንና መመለሻቸውን በምናባቸው አስታወሱ፡፡


ለራሳቸውም “ #ነፍሴ_ሆይ! እስከ አሁንም ድረስ በስሜት ላይ ነሽን?'' ካሉ በኋላ "ጌታዬ ሆይ! በራሴ ላይ የፀፀትኩ ሆኜ አግኝቻለሁ፡፡ የሕይወቴን ቁልፎች ላንተ አስረክቤያለሁና ተቀበለኝ፤ ሸሽገኝም፤ አንተ ከአዛኞች በላይ እጅግ አዛኝ የሆንክ ጌታ ሆይ!" ብለው መፀፀታቸውን ለአላህ (ሰ.ወ) ተናገሩ፡፡ ተውባህ አድርገው ጠባያቸውን አርመው ለሊትን በሰላት የሚያሳልፉ ሆነው፣ ሰውነታቸው እስኪደክም ድረስ አላህን (ሱ.ወ) በመገዛት ወደ እናታቸው ተመለሱ፡፡

ዘወትር " #ዲናር_ሆይ! የጀሀነም እሳትን የምትሸከምበት ኃይል አላህን?! እንደለለህ ካወቅክ እንዴት ራስህን ለአላህ ቁጣ አጋለጥክ?" በማለት ራሱን እየጠየቀ ተንሰቅስቆ ያለቅስ ነበር፡፡

     በዚህ ሁኔታ ለብዙ ጊዜ ከቆየ በኋላ አንድ ቀን እናታቸው “ለራስህ ትንሽ እዘን አሏቸው፡፡ እሳቸው ግን
" #እናቴ_ሆይ! ትንሽ እንድደክም ተይኝ ምናልባት ለረዥም ጊዜያት ላርፍ እችላለሁና፡፡

እናቴ ሆይ! አላህ (ሱ.ወ) ፊት እቆማለሁ፣ የሚያስጠልል ጥላ አገኝ ወይም አላግኝ አላውቅም፡፡ እረፍት የሌለበት ችግር እንዳያጋጥመኝ እፈራለሁ" አሏቸው፡፡

....እናታቸውም “ #ልጄ_ሆይ! እጅጉን በጣም ራስህን አድክመሀል” በድጋሚ አሏቸው፡፡ እሳቸውም “እናቴ ሆይ! እረፍት እፈልግ ነበር.
.. እናቴ ሆይ! ምናለ እኔን ከመውለድ መኻን በሆንሽ ኖሮ! ለልጅሽ ረዥም ጊዜያት የሚፈጅ እስር ቀብር ውስጥ ተዘጋጅቶለታል፡፡ ከዚያም አላህ ፊት ለረዥም ጊዜ የመቆም ኃላፊነት አለበት” አሏቸው፡፡ ዲናር አብዛኛውን ጊዜ ሶላት ውስጥ

{ فَوَرَبِّكَ لَنَسۡـَٔلَنَّهُمۡ أَجۡمَعِین
{عَمَّا كَانُوا۟ یَعۡمَلُونَ
በጌታህ እንምላለን!ሁላቸዉንም እንጠይቃቸዋለን፡ይሰሩት ከነበሩት ነገር ሁሉ(አል-ሐጀር 92-93)

የሚለዉን የቁርአን አንቀፅ እያነበቡ ራሳቸዉን ስተዉ ይወድቁ ነበር፡፡


#Share
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አሏሁ አክበር 10 ጊዜ
አልሀምዱሊላህ 10ጊዜ
ሱብሀን አሏህ 10ጊዜ ካልክ ቡሀላ ዱአህን ጀምር
አላህ ዱአህን ይቀበልሀል!!


https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAESAIxFIdM3tYVwa1g
#አሳፋሪ_ጥያቄና_አጥጋቢ_መልስ
      አሚር ሰይድ


    ከዕለታት አንድ ቀን ሮማዊው _ ቄሳር _ ለሙዓዊያህ (ረ.ዐ) የሚከተለውን የደብዳቤ መልዕክት ላከለት፡፡ “አቅጣጫ፣ አባት የሌለዉ፣ ወላጅ ስሌለው፥ ቀብሩ ውስጥ ደስተኛ ስለሆነው በማህፀን ውስጥ ስላልተፈጠሩ ሶስት ነገሮች ሙሉ፣ ግማሽና ባዶ ስለሆነ ነገሮች ንገረኝ። የማናቸውንም ነገሮች መፈጠሪያ ዘር የሆነችውንም በብልቃጥ አድርገህ ላክልኝ።''

ሙዓዊያህ (ረ.ዐ) የደብዳቤውን መልዕክት ካነበበ በኋላ መልስ ይሰጡበት ዘንድ መልዕክቱን ለዑብደላህ ኢብነ ዐብባስ (ረ.ዐ) ላከው፡፡



    ዐብደላህ ኢብነ- ዕብባስ (ረ.ዐ) የደብዳቤውን መልዕክት አንብበው የሚከተለውን ምላሽ ለሮማዊው ቄሳር ፃፉለት፡፡
☞“አቅጣጫ የሌለው ነገር የተከበረው ከዕባህ ነው፡፡
☞ አባት የሌለው ዒሳ(ዐሰ) (ኢየሱስ)ናቸው፡፡
☞ወላጅ የሌለው አደም (ዐ.ሰ) ናቸው፡፡
☞በቀብሩ ውስጥ ደስተኛ የሆነው ዩኑስ (ዐ.ሰ) ናቸው።
☞ በማህፀን ውስጥ ያልተፈጠሩት ሦስት ነገሮች
➊ የነብዩላህ ኢብራሂም (ዐ.ሰ) በግ
➋የነብዩላህ ሷሊሕ ሴት ግመልና
➌የነብዩላህ ሙሳ (ዐ.ሰ) ዘንዶ ናቸው።
☞ሙሉ የሆነው ነገር አእምሮ ኖሮት በዚህ አእምሮው የሚጠቀም ሰው ሲሆን፥ ግማሹ ነገር አእምሮ የሌለው ግን አእምሮ ባላቸው ሰዎች የሚሠራ ሰው ነው፡፡
☞ ባዶ ነገር ደግሞ አእምሮ የሌለውና አእምሮ በሌላቸው ሰዎች አእምሮ የሚሠራ ነው፡፡

ከዚያ በአንዲት ብልቃጥ ውስጥ ውሀ ከሞሉ በኋላ “ይህች የማናቸውም ነገሮች መፈጠሪያ ዘር ነች በማለት ከፃፉለት በኋላ መልዕክቱን ወደ ቄሳር ላኩት።

ቄሳሩ ዐብደላህ ኢብኑ ዐብባስ (ረ.ዐ) በሰጡት ምላሽ በጣም ተደነቀ።


join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
2024/09/22 16:28:06
Back to Top
HTML Embed Code: