Telegram Web Link
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"የስራ ዋጋ በሚከፈልበት ቀንና የስራን ዋጋ በሚከፍለው አምላክ ያመነ ሰው መልካም ነገር ለማድረግ  ቀስቃሽ አይጠብቅም፡፡"
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🍎እስከዛሬ ካነበብኩት  በጣ ደስ የሚለኝ
.
ሰውዬው ከ ኢሻ ሰላት ብሃላ ወደ ቤቱ ሲገባ ልጆቹን ተኝቶ አገኛቸው ባለቤቱን ሰላት ሰግደዋሉ ወይስ አልሰገዱም በማለት ጠየቃት?
እሷም : እንዲ አለቺው...ቤት ውስጥ ምንም ምግብ አልነበረምና አታልዬ ሳይሰግዱ አስተኘዋቸው ብላ መለሰችለት
ባለቤቷም:እንዲሰግዱ ቀስቅሲያቸው አላት
እሷም:እንዳያስቸግሯት በመስጋት አሁን ከቀሰቀስኳቸው በራብ ብዛት ያለቅሳሉ ቤት ውስጥ ደግሞ ምንም ሚበላ ነገር የለም አለቺው
እሱም እንዲ አላት :አንቺ ሴት ሆይ አላህ እኔን ያዘዘኝ በሰላት እንዳዛቸው ነው የሪዝቃቸው ጉዳይ በኔ ላይ አይደለም...ቀስቅሺያቸው ሪዝቃቸው በ አላህ ላይ ነው አላት!!
አላህም እንዲህ ብሏል :-👇👇
{وَأْمُرْ أَهْلَكَ بِالصَّلَاةِ وَاصطبرْ عَلَيْهَا ۖ لَا نَسْأَلُكَ رِزْقًا ۖ نَّحْنُ نَرْزُقُكَ ۗ وَالْعَاقِبَةُ لِلتَّقْوَىٰ}
ቤተሰብህንም በስግደት እዘዝ፡፡ በእርሷም ላይ ዘውትር፤(ጽና)፡፡ ሲሳይን አንጠይቅህም፡፡ እኛ እንሰጥሃለን፡፡ መልካሚቱ መጨረሻም ለጥንቁቆቹ ናት፡፡
   ጣሃ 20፦13
እናቲቱም እጅ ሰጥታ እንዲሰግዱ ቀሰቀሰቻቸው ከዛም ሰገድው እንደጨረሱ የቤታቸው በር ተንኳኳ!...በሩን ሲከፍቱት አከባቢያቸው ላይ የሚኖር አንድ ባለ ሀብት በተለያዩ ምግቦችች የተሞላ ከረጢት ኢዞ ነበር ከዛ ሰውዬውን ይሄን ለቤተሰብህ ውሰድና ስጣቸው አለው🎈
ሰውዬም ደንግጦ እንዴት ልትመጣ ቻልክ አለው ...ባለሀብቱም አመጣጡን እንዲህ ሲል ተረከለት : አንድ የተከበረ ባለስልጣን እኔ ዘንድ በእንግድነት መጥቶ ነበረ አነዚህ ምግቦችም ለሱ የተዘጋጁ ነበሩ ግን ከመመገቡ በፊት  በሆነ ጉዳይ ላይ ትንሽ ተከራክረን ምግቡን አልበላም ብሎ በመማል ጥሎ ወጣ ከዛም እኔ  የቀረበውን ምግብ ያዝኩና እግሮቼ በቆሙበት ስፍራ ላለ ሰው እሰጣለሁ ብዬ ከቤት ወጣሁኝ ግን ወላሂ ልክ አንተ በር ከመድረሴ በፊት አንድም አልቆምኩኝም በ አላህ ይሁንብኝ እናንተ ዘንድ ምን እንዳመጣኝ አላውቅም በማለት ነገረው ...በዚህ ግዜ የቤቱ አባወራ እጁን ወደላይ ከፍ አድርጎ እንዲህ አለ 👇👇👇
: رَبِّ اجْعَلْنِي مُقِيمَ الصَّلَاةِ وَمِن ذُرِّيَّتِي ۚ رَبَّنَا وَتَقَبَّلْ دُعَاءِ.
«ጌታዬ ሆይ! ሰላትን አዘውትሬ የምሰግድ አድርገኝ፡፡ ከዘሮቼም (አድርግ)፡፡ ጌታችን ሆይ! ጸሎቴንም ተቀበለኝ። አለ!! ሱረቱ ኢብራሂም -40:
.http://www.tg-me.com/Islam_and_Science
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
በዘመነ ኺላፋ ዓባሲ የጠላቶችን መሸሸጊያ በሮች ለመስበሪያነት ያገለግል የነበረ መሳሪያ ነው።

ከላይ ጣሪያ መሳይ ባለ3 መአዘን ቅርፁ ከግንብ ላይ ጠላት ሊያዘንበው የሚችለውን ቀስት እና የፈላ ዘይት ሲከላከል መካከል ላይ ወጣ ብሎ የሚታየው ግንድ የጠላትን በር መደብደቢያነት ያገለግላል። በዘመኑ አቻ የሌለው የ«ታንክ» አይነት አገልግሎት ነበረው። መከላከልና ማጥቃት።
1979 በሀረም ላይ ምን ተፈጥረ?

በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ግለሰብ ጁሀይማን አልዑተይቢ እና ተከታዮቹ በሱዑዲ እስር ቤት ውስጥ የተነሱት ፎቶ ነው።

ጁሁይማን በቀደምት ዘመኑ የሳዑዲ ዓረቢያ ፖሊስን በመቀላቀል የ«ሳጅን»ነት ደረጃ መድረስ የቻለ ፤ በመዲና ዩኒቨርስቲ ተቀላቅሎም ዲን የቀማመሰ ወጣት እንደሆነ ይነገርለታል። ያኔ የመዲና ዩኒቨርስቲ ውስጥ እጅጉን ተፅኖ እንዳሳደሩበት ከሚነገርላቸው መምህራኖቹ መካከል አንዱ «ሙሐመድ ብን ዓብደላህ አልቀህጧኒ» የተባሉ ሸይኽ ነበሩ። ታሪኩ የሚጀምረውም እዚው ጋር ነው።

ሙሐመድ አልቀህጧኒ ራሳቸውን ልክ እንደ «መህዲ» አድርገው ያምኑ ነበር። የስማቸው መመሳሰል ፣ የአባታቸው ስም አብደላህ መሆን ቁርጥ መህዲን መምሰሉ አሞኝቷቸዋል። በዚህ የጦዘ ምልከታ ውስጥ የፖሊስ አዛዥ ከተማሪያቸው መካከል አንዱ ሲሆን ልባቸው ካዕባን ለመቆጣጠር ሸፈተ። አስበውም አልቀሩም ፤ ጁሀይማንን አሳምነው እና ሴት ልጃቸውን ድረውለት ተከታያቸው አደረጉት።

በአውሮጳዎች መቁጠሪያ ኖቬምበር 20 ቀን 1979 አመት ላይ ጁሀይማን በስውር ያደራጃቸውን ተከታዮች አስከትሎ በጠዋቱ ወደ ሀረም ዘለቀ። ተከታዮቹ በትከሻቸው ላይ አንዳች የጀናዛ ቃሬዛ የመሰለ ነገር ተሸክመዋል።

ድንገት ፈጅር ተሰግዶ እንዳለቀ ግን ጁሀይማን እና ተከታዮቹ የጀናዛ ቃሬዛውን ገለጥ አድርገው የተራቀቁ የጦር መሳሪያዎችን እየመዘዙ ሰጋጁን ያስጨንቁት ያዙ። «መህዲ መቷልና ቃል ግቡለት» ፣ «ኸሊፋቹ ተገልጧልና ተከተሉት» እያሉ አዋከቡት።

አስቀድሞ ትእዛዝ የተቀበሉት ተከታዮቹም በመስጊዱ ሚናራዎች ላይ ስናይፐራቸውን ጠምደው የሀረም ጠባቂ ፖሊሶችን አናት እያፈረጡ ደመ ከልብ አደረጓቸው። ሀረም ተጨነቀች። የመንግስት አካላት ሳይቀሩ መፍትሄው ግራ ሆነባቸው።

©ኢትዮ ሙስሊምስ

ክፍል 2 ይቀጥላል
1979 በሀረም ላይ ምን ተፈጠረ?
ክፍል 2

ሙሐመድ አልቃሕጣኒ እና ጁሀይማን አልዑተይቢ የሀረምን ማይኮሮፎን እያበሩ ውስጥ ላሉት የሐረም እንግዶች እና መስጂዱን ከበው ለተቀመጡት የፖሊስ አዛዦች የማስፈራሪያ እና መህዲን ተቀበሉ መልእክት ያስተላልፋሉ። በከባቢው ላይ የተሰማሩት ፖሊሶች ሀረምን መግባት እንችል እንደው ብለው ወደ በሩ ጠጋ ባሉ ቁጥር ሚናራዎች ላይ የተጠመዱት ስናይፐሮች ስራቸውን ይሰራሉ።

በቦታው ያሉት የፖሊስ ሀይላት ጉዳዩ በቀላል እንደማትፈታ ስለገባቸው የሀገሬው ሰራዊት ስራውን እንዲከውን ወደ መከላከያ ሚኒስትሩ ስልካቸውን አንቃጨሉና የሱዑዲያ ወታደሮች በተራቸው ሀረምን ከበው እገታውን ለመስበር ያላቸውን ሀይል ሁሉ አፈሰሱ። ሁኔታው ግን ምንም አልተለወጠም።

በመሆኑም አጋቾቹን ለማዳከም የሀረም ውሀ አገልግሎት እና የመብራት ስርጭት ሙሉ በሙሉ እንዲቋረጥ ተደረገ። ግን የተጠበቀው ውጤት ተቀልብሶ ከአጋቾቹ ይልቅ የሐረም እንግዶች በጥማት እና ረሐብ በየቦታው መወዳደቅ ጀመሩ። ንጉስ ዃሊድ ቢጨንቀው ሽማግሌ አስልኮ ከበዛ ንትርክ በኋላ በመጅጂዱ ክልል ያሉ ህፃናት እና ሴቶች ያለምንም መታኮስ ግቢውን ለቀው እንዲወጡ ተፈቀደላቸው። እርግጥ እነ ዑተይቢ ስንቅ እያለቃቸው ስለነበር ከዚህ የተለየ የመደራደሪያ መንገድ አልነበራቸውም።

ሀረም እንዲህ በእገታ በተሟሟቀችበት ወቅት አሜሪካ እና ኢራን የጉዳዩ ጠንሳሽ አንቺ ነሽ! አንቺ ነሽ! እየተባባሉ አጋጣሚውን ለፖለቲካ ጥቅማቸው መጓተቻ ለማድረግ በየሚዲያው ይንተፋተፋሉ።

እንዳይታኮሱበት ሀረም ፤ ዝም እንዳይሉም መንግስት ግልበጣ ሆኖባቸው የተወዛገቡት ባለስልጣናት ጉዳዩን ወደ ፈታዋ ምክር ቤት መርተው የሀረምን ክብር ለማስጠበቅ ሲባል ወታደራዊ እንቅስቃሴ በውስጡ ማድረግን የሚፈቅድ አዲስ ፈታዋ ተቀብለው በየጋዜጣው እና ሚዲያ ማሰራጨት ጀመሩ።
1979 ሀረም ላይ ምን ተፈጠረ?
ክፍል 3

«ሀይአት ኪባረል ዑለማ» የሰዑዲ ፈታዋ ምክር ቤት በሀረም ከባቢ ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንዲደረግ የሚፈቅድ ፈታዋ ሲሰጥ እንዲህ ቀላል አልነበረም። ምክኒያቱም ከአላህ መልእክተኛ (ሰዐወ) የተገኙ ትክክለኛ እና ግልፅ ሀዲሶች በሀረም ዙርያ ወታደራዊ እርምጃዎችን ይከለክላሉ።  ስለዚህ ፈታዋቸው ከትችት የነፃም ሆነ የዓለም ዑለማዎችን በ2 ጎራ ከፍሎ ከማነታረክ ሊተርፍ አይችልም።

ዞሮዞሮ ፈታዋው ከተሰጠም በኋላ በትንሽ ሰብአዊ ኪሳራ ሀረምን ከእገታ የማዳኑን ሀላፍትና ማን ይውሰድ የሚለው ለንጉስ ኻሊድ ሌላ ራስ ምታት ሆኖበታል። የሀገሬው ፖሊስ የሞከራቸውም ፤ የሀገሬው ሰራዊት አሳክቼዋለው የሚለው አንድም ፍሬ ነገር ማቅረብ አልቻለም።

ስለዚህ ከውጪ ሀገር ኮማንዶዎች ይህንን   ተግባር አቀላጥፎ የሚጨርስ መረጣ በጠረጴዛ ዙርያ ሲጣል ሲነሳ ከቆየ በኋላ የፈረንሳይ ኮማንዶ ተመረጠ። ኮማንዶው አለኝ የሚለውን ዘመናዊ መሳሪያ አንግቦ የሱዑዲያ ምድር ከተመ። ግን ስራውን ገና ሳይጀምር ከበድ ያለ ፈተና ገጠመው። የሀረም ክልል ውስጥ ሙስሊም ያልሆኑ ሰራዊቶች እንዴት ሊገቡ ይፈቀድላቸዋል? የሚል። ጥያቄው በምን መልኩ እንደተፈታ ብዙ መላምቶች ቢሰነዘሩም የፈረንሳይ ኮማንዲ ቡድን ሀረምን ከእገታ በማስለቀቁ ላይ የአምበሳውን ድርሻ እንደወሰደ የትኛውም ተራኪ የማይክደው እውነታ ነው።

ኮማንዶው ሀረም የገባው ሸሀዳ ይዞ ነው ፤ ኮማንዶው አመራር እና ሎጅስቲክ ላይ ብቻ ነው የተሳተፈው እና ሌሎችም ተብሏል።

ኮማንዶው በሀረም የመሬት ስር መንገድ በመግባት መርዛማ ጪሶችን ወደ ሀረም ክልል አስወነጨፈ። የሀረም እንግዶች በከባድ ሳል እየተጨነቁ የድረሱልን ሰቆቃ ድምፅ ያሰማሉ። በጪሱ ነቦልቧል የተጨነቀው ሀረም በላዩ ላይ የጥይት እሩምታ ታከለበት። ሰላማዊው ክልል የጦር አውድማ ሆነ።
1979 ሀረም ላይ ምን ተፈጠረ?

የመጨረሻ ክፍል

የመስጂደል ሀረም ግቢ እገታ እንደቀልድ 14 ቀናት ጨርሶ 15ኛ ቀኑን ይዟል። በአለም ዙሪያ ያሉ ሙስሊም በዝ ሀገራት ህዝቦችም የሀረምን መታገት በመቃወም በየቦታው የቁጣ ድምፅ ያዘሉ ሰላማዊ ሰልፎችን አጧጡፈውታል።ንጉስ ኻሊድ የመጨረሻ እምነቱን የጣለባቸው የፈረንሳይ ኮማንዶዎች ሙስሊም ናቸው ወይ? የሚለው ንትርክ ሳይቋጭ ወደ መስጂደል ሀረም ዘልቀው ስራቸውን «ሀ» ብለው የጀመሩትም እገታው ከተፈፀመ 15 ቀናት በኋላ ነበር።

ኮማንዶዎቹ በመስጂደል ሀረም የመሬት ለመሬት መንገድ እየተሽሎከሎኩ ገብተው መርዛማውን ጭስ ወደ ሀረም ካስወነጨፉት በኋላ ድንገተኛ እና ያልጠበቁት ጥቃት የደረሰባቸው የዑለይቢ ቡድኖች ባገኙት አቅጣጫ ሁሉ ይተኩሳሉ። ኮማንዶዎቹም ጭንብላቸውን እንዳጠለቁ አጋች ነው ብለው ያሰቡትን በጥይቅት ይቆሉታል። በመካከል ግን የሀረም እንግዶች ከቀኝ እና ግራ በሚተኮሱ ጥይቶች እና ሀረምን ባጠነው መርዛማ ጭስ ህይወታቸው ወደ ቀጣዩ አለም ትከንፋለች።

ከብርቱ ፍልሚያ በኋላ ከዑተይቢ ቡድኖች መካከል አንድ ጉምቱ ሰው በጥይት ተጠብሶ መሬት ላይ ተዘረረ። ብዙም ሳይቀለይ ስትንፋሱ ተቋርጣ ሽቅብ ጥላው ከነፈች። ዑተይቢና ተከታዮቹ ያዩትን ማመን አልቻሉም። እሱን እስከያዝን አለምን እንገዛበታለን ያሉት መህዲያቸው ገና በመጀመሪያው ፍልሚያ ህይወቱን ተነጠቀ። አዎን! የሞተው መህዲ ነው ብለው ያሰቡት ሙሐመድ ብን ዓብደላህ አልቀሕጧኒ ነበር።

ከዚህ ወዲያ ፍልሚያም ሆነ መስዋእትነት ለነዑተይቢ ትርጉም የለውምና ቀስበቀስ መሳሪያቸውን እየጣሉ እጃቸውን ለኮማንዶው እጃቸውን ሰጡ። ፍልሚያውም ከ15 ቀን አስጨናቂ ትግል በኋላ ተጠናቀቀ። አማፂያኑም ከጥቂት የፍርድ ሂደት በኋላ በአደባባይ የሞት ፍርዳቸውን ተቀብለው ወደ ቀጣዩ የአላህ ፍርድ ተሸኙ።
ዝምታም የሙእሚን ባህሪ ነው፡፡

ለተናገረው ሁሉ መልስ ቢሰጥ፣ የሰደበውን ሁሉ ቢሳደብማ ውረደት እንጂ አያተርፍም፡፡ ውሻኮ የተናቀው አላፊ አግዳሚው ላይ ሁሉ ስለሚጮህ ነው፡፡ እሱም ቢሆን ከአንድ ድንጋይ አላለፈም፡፡
ሙእሚን ዝምታን ይመርጣል፡፡ ከተናገረም ከመናገሩ በፊት ምን ማውራ እንዳለበት ያስባል፡፡ ክብሩንም ይጠብቃል፡፡ ከአፉ መልካም እንጂ ክፉ አይወጣም፡፡ ሙእሚን በዝምታው ውሰጥ ክብሩ አለ፡፡ አንበሳ ለምን ተፈራ? ለምንስ ተከበር? በዝምታው፡፡
ጨለማን ለምን አንደፍረውም? ለምንድነው የምንፈራው? ፀጥ ያለ ስለሆነ፡፡ ሬሳን ለምንድነው የምንፈራው?ስለማያወራ።
በቁርዓን ላይ የምናገኛቸው ምልክቶች እና የሚያስተላለፍት መልዕክት

ቁርዓን በምንቀራበት ወቅት እነዚህን ምልክቶች ሁል ጊዜ እናያቸዋለው፡፡ ግን አብዛኞው ሰው የምልክቶችን መልዕክት በአግባቡ አይረዳቸውም፡፡ ከዚህ በታች ያለው ምስል እያንዳንዱ ምልክት የሚያስታልፈውን መልዕክት ያስገንዝበናል

ይህን ጠቃሚ ማስታወሻ ያዘጋጀውን ወንድም አላህ ኸይር ስራውን ይቀበለው

ይህን ጠቃሚ ማስታወሻ ለሌሎችም እናዳርስ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አመት ሊሞላዉ የተወሰኑ ቀናት ሲቀረዉ ከ330 ቀን ቡሀላ ዛሬ ደሴ ከተማ  Data ተለቀቀ እንዴት ናችሁ

በመሀል ከአዲስ አበባና ከባቲ በሚመጡ Data አልፎ አልፎ አጫጭር ፁሁፍ አቅረቤ ነበር ..በአላህ ፍቃድ መልሶ data ካልተዘጋብን አልፎ አልፎ አንዳንድ ትምህርቶች የሚለቀቅ ይሆናል

አሚር ሰይድ
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#መይት_ዛዴ(የሙት ልጅ)
አሚር ሰይድ

መይት ዛዴ ስለሚባል ቱርካዊ ሰምታችሁ ታቃላችሁ??ይህ ሰዉ በሱልጣን ሙሀመድ ቀዳማዊ ዘመን የኖረና በመልካም ምግባሮቹ  የሚታወቅ የሀይማኖት ምሁር ነበር። መይት ዛዴ (የሙት ልጅ) የተባለበት ምክንያት በሚከተለው ክስተት አማካይነት የደረሰ ነው፡፡



   የመይት ዛዴ አባት የኦቶማን ቱርክ መንግሥት ወታደር ነበር። ልክ እንደ ሌሎቹ የሀገሩ ጀግኖች ሁሉ በ1596 በተደረገውና ሱልጣን ሙሐመድ ሳልሳዊው በመራው የኢግሪ ዘመቻ እንዲሳተፍ ጥሪ ተደረገለት፡፡ ይሁን እንጂ በዚያ ጊዜ ሚስቱ ልትወልድ ተቃርባ የነበረ ሲሆን ጤንነቷም አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኝ ነበር፡፡ ይህ ሁሉ ቢሆንም ያ ጀግና ወታደር በአላህ መንገድ ላይ መዋጋትን ከሁሉም ነገር በላይ ያፈቅር ስለነበር ሚስቱ ይቅርታ እንድታደርግለት ከጠየቃት በኋላ ለዘመቻው ዝግጅት ማድረጉን ተያያዘው፡፡ ከዚያም እጆቹን የአርሹ ባለቤት አላህ ወዳለበት ሰማያዊ ችሎት ዘርግቶ የሚከተለውን ፀሎት አደረሰ

ጌታዬ ሆይ! እኔ ባንተ መንገድ ልዋጋ መጓዜ ነው፡፡ ካንተ በቀር ሌላ ረዳት የለኝም። ጌታዬ ሆይ! ይህን ልጄን ለዚህች ታማኝና ብዙ ድካም የሚታይባት ባለቤቴ ስጥቸዋለሁ፡፡ እባክህን አንተ ጠብቅልኝ።"

ጀግናው ሰው ይህን ካለ በኋላ ከፈረሱ ላይ ወጥቶ በመጋለብ ከዓይን ተሰወረ። በአላህ እርዳታና ፀጋ የኦቶማን ጦር በውጊያው ድል አደረገ፡፡



    ወደ ሀገራቸው እንደተመለሱ ጀግናው ወታደር፣ አዛዦቹ ወደ ቤቱ እንዲሄድ ይፈቅዱለት ዘንድ ጥያቄ አቀረበ፡፡ በቀጥታ ወደ ቤት ጋልቦ እዚያ ሲደርስ ግን በቤቱ ውስጥ ማንም አልነበረም😔፡፡ ባለቤቱ የድሉን ወሬ ስምታ ከሆነ ቤቱን ሞቅ አድርጋ በደስታ ልትቀበለው በተገባት ነበር፡፡ ሆኖም እንኳን አቀባበል ልታደርግለት ይቅርና በቤት ውስጥ አልተገኘችም። በታላቅ ጭንቀትና ጥንቃቄ ወደ ጎረቤቶች ሄዶ ምን እንደተፈጠረ ጠየቃቸው፡፡

እነርሱም ሰውዬውን ሲያዩት በሀዘን እንደተዋጡ እንዲህ አሉት- “አንተ ጀግና ሆይ! አላህ ድልህን ይባርክልህ፤ እንዲሁም ሕይወትህን ፀጋ የተሞላበት ያድርግልህ፡፡" ከዚህ አባባል ጀርባ ያለውን ትርጓሜ እያሰላሰለ ልቡ መቃጠል ስለጀመረ ሳይፈልገው እምባ😢😢የታከለበት ሲቃ ፈንቅሎት እንዲህ አለ፡-

"ሊሆን አይችልም:: የታለች ሚስቴ? ተወዳጁ ልጄስ የታለ? የልጄን ነገር ለዓለማት ጌታ በአደራ ሰጥቼዋለሁ፡፡ እርሱ ከሁሉም ጠባቂዎችና ተንከባካቢዎች በላጭ ነው::” ይህን ካለ በኋላ በሀዘን ተኮማትሮ እምባዉን እያነበ  ለረዥም ጊዜ ፀጥ በማለት ቆየ። ከዚያም ዙሪያውን የከበቡትን ሰዎች እንዲህ አላቸዉ፡-

“እርግጥ ነው አላህ ከሁሉም በላይ አዛኝ የሆነ ጌታ ሲሆን አደራ በመጠበቅ በኩል ደግሞ እጅግ ታማኙ ነው፡፡ የባለቤቴን መቃብር አሳዩኝ አላቸዉ::"


....ከሰዎች ጋር ወደ መቃብር ሥፍራ አብሮ ከሄደ በኋላ የባለቤቱን መቃብር ሲያይ በመቃብሩ አፈር ላይ ጆሮውን ጣል አድርጎ ያዳምጥ ጀመር። ከዚያም፡- “አዎን! የልጄን የለቅሶ ድምፅ ሰማሁ!" በማለት እንደ እብድ ጮኸ፡፡

ይህን ካለ በኋላ ዶማና አካፋ እንዲመጣለት ጠይቆ መቃብሩን ይቆፍር ጀመር፡፡ ከእርሱ ጋር የመጡት ሰዎችም እያገዙት አፈሩ ሲወገድ የሕፃኑ ለቅሶ በግልፅ ይሰማ ጀመር፡፡ መቃብሩ ጨርሶ ከተከፈተ በኋላ በለህዱ (በጓዳው) ውስጥ አስደናቂ ተዓምር ተከሰተ፡፡

በሞተችው እናቱ ደረት ላይ ልጥፍ ያለ ወንድ ልጅ ታየ፤ የጦር ጀግና የሆነው ያ ወታደር ልጁን ወዲያውኑ ከእናቱ ደረት ላይ አንስቶ ወደ ደረቱ በማስጠጋት አቀፈው፡፡ ከዚያም የሚያምሩና ሮዝ መልክ ያላቸው ጉንጮቹን ደጋግሞ ይስመው ጀመር፡፡ ህፃኑን በጨርቅ ጠቅልሎ ለስዎች ከሰጣቸው በኋላ በውድ ባለቤቱ ላይ ሶላተል ጀናዛ ሰግዶ መቃብሩን እንደነበር በጥንቃቄ ዘጋው፡፡

ይህን ሁሉ ትዕይንት ዙሪያውን ከበው ሲመለከቱት የነበሩ ሰዎች በድንጋጤ ደርቀው ቀርተዋል። እየደጋገሙ የአላህን ተዓምራት በማስታወስ ስሙን ያወሳሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ምህረት ይጠይቃሉ፡፡

አባትዬው ግን ዓይኖቹ በእንባ እንደተሞሉ ልቡ በሚስቱ ሀዘንና በልጁ በሕይወት መትረፍ በተፈጠረበት የሀዘንና የደስታ ድብልቅ ስሜት ተውጦ ግራ እንደተጋባ ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡

    ይህ ልጅ ከዚያ ጊዜ በኋላ በታላቅ የእምነትና አላህን የመፍራት ድባብ ውስጥ እንዲያድግ ተደረገ፡፡ በመላው የኦቶማን ቱርክ ግዛትም የታወቀ አላህን ፈሪ ሰው ለመሆን በቃ:: 'መይት ዛዴ' በሚለው መጠሪያ ስሙ በሁሉም ሰው ዘንድ የታወቀ ነበር፡፡ ይህ ሰው በእርግጥም የእውነተኛ በአላህ የመመካት ውጤትና የኃያሉ አላህ ማለቂያ የሌለው ተዓምራት መገለጫ ሆኖ ለብዙ ዘመናት ኖሯል፡፡
እኛ አላህ ጋር ያለን መመካት ምን ያህል ይሆን??



ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
🔥🔥የጀሀነም ፍራቻ🔥🔥

ልቡ በጀሃነም ፍራቻ የተሞላ አንድ የአንሷር ወጣት ነበር። ስለ ጀሃነም በተነሳ ቁጥር ማልቀስ ይጀምራል። በመጨረሻም ክፍሉ ከውስጥ ዘግቶ በመቀመጥ ወደ ውጭ ላለመውጣት ወሰነ። የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ስለ ልጁ ሁኔታ ሲነገራቸው ሊጠይቁት ሄዱ። ወጣቱ የአላህን መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) በጉጉት ሲመለከታቸው ከቆየ በኋላ ወዲያው ተነስቶ በእጆቹ አቀፋቸው፡፡ በዚያው ሁኔታ ላይ እያለም ነፍሱ በመውጣቷ ወለሉ ላይ ተዘረረ፡፡ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በዚህ ጊዜ እንዲህ አሉ፡-

“ወንድማችሁን እጠቡትና ከፍኑት፡፡ የጀሃነም ፍራቻ ጉብቱን በታትኖታል፡፡ ነፍሴ በእጁ በሆነችው አላህ እምላለሁ፤ አላህ ከጀሃነም ቅጣት ጠብቆታል፡፡ አንድን ነገር የፈራ ከዚያ ነገር ለማምለጥ መንገድ ያገኛል።" (ሃኪም፣ አሊ አል-ሙተቂ)


ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
2024/09/22 18:20:19
Back to Top
HTML Embed Code: