Telegram Web Link
#የሱን_እሬሳ_ምድር_አትቀበለዉም
          

ሀቢቡና ሙሀመድ ﷺከኢስላም ያፈነገጠውን ሰው ሬሳ ምድር እንደማትቀበል መናገራቸው
የነብዩﷺ ተአምር ጭምር ነዉ፡፡

      ኢማም አህመድ እንደዘገቡት አነስ ኢብኑ ማሊክ የሚከተለውን አስተላልፈዋል

    የበኒ ነጃር ጎሣ አባል የሆነ አንድ ሰው   ከመካከላችን ነበር። አል. በቀራህንና አል ዒምራንን ምዕራፎችን አጠና (ቀራ)፡፡ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ፀሐፊ ነበር። ከሙስሊሞች ሸሽቶ ሄደና ከክርስቲያኖች ጋር ተቀላቀለ"

ክርስቲያኖቹም የሙሐመድ ራዕይ ፀሐፊ ነበር» በማለት የክብር ቦታ ሰጡት፡ብዙም ሳይቆይ ሞተ። ጉድጓድ ቆፍረው ቀበሩት። ምድር ግን አልተቀበለችውም ተፋችው። እንደገና ቀበሩት አሁንም ተፋችው። ከዚያ በኋላ ግን ሳይበብሩ ተውት።


     ይህ የሆነበትን ምክንያት ዐብባስ ሲናገሩ፡ ይህ ሰው በቀራንና አል ዒምራንን ያጠና (የቀራ) በመሆኑ እኛም ለርሱ ልዩ ክብር ነበረን። የአላሀ መልዕክተኛ ﷺ «መሐሪና አዛኝ» የሚል ቃል እንዲፅፍ ሲያዙት «መሐሪና ጥበበኛ» እያለ ይፅፋል። ወዋቂና ጥበበኛ» ብሎ እንዲጽፍ ሲያዙት፡ «ሰሚና ተመልካች» ብዬ ልፃፍ ይላቸዋል...

«ይህ ሰው ከኢስላም አፈነገጠና ከጣዖታውያን ወገነ። «ስለ ሙሐመድ ልንገራችሁ። ራዕይ ፀሐፊው ነበርኩ። የፈለግኩትን ነበር የምጽፈው» በማለት የነቢዩን ስም ማጥፋት! የሐሰት ጥላሸት መቀባት ጀመረ።

ይህ ሰዉ ሲሞት ነብዩ ﷺ ምድር አትቀበለዉም በማለት ተናገሩ።

አነስ እንዳሉት አቡ ጦልሐ ሰውየው ወደሞተበት ሀገር መሄዱን ነግሮኛል። ሜዳ ላይ ተጥሎም አገኘው። «የዚህ ሰዉ ነገር ምንድን ነው?» ሲል ጠየቀ። «ደጋግመን ብንቀብረውም ምድር ልትቀበለው አልፈቀደችም። መልሳ እየተፋች አስቸገረችን» አሉት



ቡኻሪ አነስን በመጥቀስ እንደዘገቡት፡ ሰውየው ክርስቲያን ነበር ሰለመ። በቀራንና አል ዒምራንም አጠና። የነቢዩ ፀሐፊም ሆነ። ተመልሶም ወደ ክርስትና ገባ። ሙሐመድ እኔ የፃፍኩለትን ብቻ እንጅ ሌላ ነገር አያውቅም» ይል ነበር። አላህ ይህን ሰው ገደለው፡፡ ቀበሩት። ምድርም ተፍታው አደረች።

«ይህ የሙሐመድና የባልንጀሮቹ ድርጊት ነው። ከነርሱ ስለሽሽ ከመቃብሩ አውጥተውት ነው» አሉ፡፡ ይበልጥ ጥልቅ ጉድጓድ ቆፍረውም ቀበሩት። ምድር በድጋሜ ተፍታው አደረች። «ይሀ የሙሐመድ እና የባልንጀሮቹ ድርጊት ነው። ከነርሱ ስለሽሽ ሬሳውን አውጥተው ጣሉት» አሉ። ይበልጥ ጥልቅ የሆነ ጉድጓድ ቆፈሩና ቀበሩት። ምድር ለሶስተኛ ጊዜ ተፋችው" በዚህ ጊዜ የሰው ድርጊት እንዳልሆነ አወቁና ሬሳውን ወረወሩት፡፡


ሱበሀነሏህ!!!


https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAESAIxFIdM3tYVwa1g
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
መላኢካዉ አላህን ጀነትን አሳየኝ ያለበት ታሪክ

Join👇👇

https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAESAIxFIdM3tYVwa1g
#ቤት_እንግዳ_የመዉሰድ_ጥቅም


   ሚስት ባሏ እንግዳ ይዞ እየመጣ ስልችት ብሏት ስሞታ ለማቅረብ ወደ ረሱል ﷺ መጣች ችግሯን ዘርዘር አድርጋ  ነገረቻቸው፡፡ ነብዩ ﷺ ዝም ብለው ሰምተዋት ምንም አልመለሱላትም

ሴትዮዋ ከሄደች በኋላ ለባሏ አስጠርተው ዛሬ አንተ ቤት እንግዳ ነኝ አሉት ....ባል በጣም ተደስቶ ለሚስት ነገራት ሚስትም በጣም ተደሰተች ራሕመተል ዓለም እቤቷ ሊገቡ ነዋ ቤት  ያፈራው ነገር በደስታ አዘጋጀች

ነብዩ ﷺ ገብተው ከተስተናገዱ በኋላ ለባልየው ስወጣ ሚስትህ እኔ በምወጣበት በር ወደዛ እንድትመለከት ንገራት አሉት
    ረሱል ﷺ ሲወጡ ሚስት ትመለከታለች ከኋላቸው ጊንጥ እንሽላሊት ሌላም ጎጂ ነፍሳቶች ተከትሏቸው ሲወጡ አየች ሚስት ደንግጣ ዞረባት
....ከዚያም ነብዩ ﷺ እንዲህ አሉ:- "አንድ እንግዳ ከተጠራበት ቤት ሲወጣ ልክ እንደዚህ ከዛ ቤት ችግር በላ እና ጎጂ ነፍሳቶች ተከትለዉት ይወጣሉ"
  እንግዳ የሚበዛበት ቤት አላህ የሚወደው ቤት ነው አሉ

በሌላ ዘጋባ ረሱል ﷺ እንዲህ ይላሉ
አላህ ኸይር የፈለገለት ሰው ስጦታ ይልክለታል ሲሉ
... ያስጦታ ምንድን ነው???ተብለው ሲጠየቁ እንግዳ ብለዉ መለሱ

በሌላ ሀዲስ
☞ "እንግዳ የማይገባበት ቤት መላኢካ አይገባበትም"
☞"እንግዳ ወደ ጀነት አመላካች ነው"
☞"በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ እንግዳውን ያክብር" ብለዋል ሀቢቡና ሙሀመድ ﷺ

 ⚡️⚡️⚡️ እንግዳ መጋበዝ አለብኝ ብለን የግድ ከአቅማችን በላይ መጣጣር የለብንም ቤት ባፈራው ሊላህ ብለን ብቻ እንግዳውን ቀልቡ ለማስደሰት በኢኽላስ ከሆነ እንግዳው የሚያስደስተው የምግቡ አይነት ሳይሆን እሱን አክብረን መጥራታችን ነው!



አላህ እንግዳን የምናከብርበት ተውፊቅ አላህ ይስጠን


Join👇👇

https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAESAIxFIdM3tYVwa1g
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ዱአ ስታደርግ በአሏህ በተቀደሰ ስሙ ጠርተህ ዱአ አድርግ
Join👇👇

https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAESAIxFIdM3tYVwa1g
#ቁርአን_በዚና_ጉዳይ_ለምን_ሴቶችን_ተጠንቀቁ_ብሎ_አስቀደመ??
            አሚር ሰይድ
         

#ምንጭ☞በዝሙት አንዘምን መፅሀፍ

     
     የሰው ልጆች ወደ ዚና አብዝተው የሚሳቡባቸው ሁለት አበይት ምክንያቶች አሉ፡፡

#አንድኛዉ የሴቶች ወሲብ ቀስቃሽ አለባበስ ነው፡፡
#ሁለተኛዉ ሰይጣን የሰው ልጆችን ከምንም በላይ ጸያፍ ድርጊቶችን እንዲሠሩ ይገፋፋቸዋል፡፡ ከፀያፍ ድርጊቶች መካከል ግንባር ቀደሞቹ ደግሞ ዝሙትና ግብረ ሰዶማዊነት ናቸው፡፡

ዋናዉ የዝሙት መንደርደሪያ ሁለት ናቸዉ

1⃣ የሴቶች አለባበስ
በተፈጥሮ ለወንዶች ሲበዛ ከተሸላለሙለት ነገሮች መካከል ቀዳሚዎቹ ሴቶች ናቸው፡፡ ወንዶችን በማሳሳትና በማማለል እነርሱን ይበልጥ የሚፈታተናቸው ነገር ደግሞ የሴቶች ወሲብ ቀስቃሽ አለባበስ ነው፡፡ እናም ዛሬ ዛሬ አብዛኞቹ ሴቶች አለበበሳቸው  መረኑን የለቀቀና አሳሳች በመሆኑ ወንዶች ሲበዛ በሴቶች እየተፈተኑና ወደዝሙትም እየተሳቡ ይገኛሉ፡፡

ማረስረሻው ሒጃብ ስለተነሳ ሒጃብም ሲለበስ አላህ ያዘዘዉን ሒጃብ ባለመሆኑ የዝሙት ዛሩ በየቦታው ተስፋፍቷል፡፡ ዝሙትም በየሜዳው እየተሰበከ ነው፡፡

ዛሬ ዛሬ የሴቶች አለባበስ እጅግ አሳሳችና ወሲብ ቀስቃሽ ከመሆኑ የተነሳ በርካቶች በቀላሉ ዝሙት ላይ እየወደቁ ይገኛሉ፡፡ የሴቶች አለባበስ ወሲብ ቀስቃሽ ሆነ ማለት እነርሱ በቀላሉ ይከፋፈታሉ፤ ጥብቆችና ንፅሕቶች አይደሉም፤ ጨዋዎችና ታማኞች አይደሉም፤ ገላቸው ለአላፊ አግዳሚው አምሮት መውጪያ ቅምሻ የቀረበ ነው፤ ወዘተ የሚል መልዕክትን ያስተላልፋል፡፡

የሴት ልጅ አለባበስ ወሲብ ቀስቃሽ ከሆነ ወንዱ በገላቸው ፍቅር ይሰከራል፤ ምክንያቱም የወንድ ልጅ ወሲባዊ ፍላጎት የሚነሳሳው በዕይታው ነውና፡፡  በዚህን ጊዜ
☞ ለሴት ልጅ ተገቢውን አክብሮት ከመስጠት ይልቅ እነርሱን እንደ ወሲባዊ ዕቃ አድርጎ መመልከት ይጀምራል፡፡
☞ለሴቶቹ ሰብአዊ ማንነት ግን ምንም ክብር አይሰጥም:: ሴቶችን ያራከስና ገላቸውን ለመደሰቻነት ይጠቀማል፡፡
☞እነርሱን እራቁቶ በገላቸው መዝናናትን ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ሴቶች ተሳስተው ላለማሳሳት፣ ጠፍተው ላለመጥፋትና ነድደው ላለማቃጠል ከወሲብ ቀስቃሽ አለባበስ መራቅ አለባቸው፡፡


2⃣/ ሰይጣን የሰውን ልጆች ከምንም በላይ እንዲሠሩት የሚገፋፋቸው ወንጀል ቢኖር ዝሙትን ነው፡፡ ይህንኑ አስመልክቶም አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፦
«እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የሰይጣንን እርምጃዎች እትከተሉ፡፡ የሰይጣንንም እርምጃዎች የሚከተል ሰው (ሀጢአትን ተሸከመ)፡፡ እርሱ በመጥፎና በሚጠላ ነገር ያዛልና (አን-ኑር24:21)



🔰🔰#ሴቶች_በዚና_ሳቢያ_እንዴት_ከወንዱ_የበለጠ_እንደሚጎዱ_የሚከተሉትን_ነጥብ_እንመልከት



✏️✏️ ዚና ላላገባች ሴት ለድንግልናዋ መገርሰስ ዋናው መንስኤ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከዚህም የተነሳ ሴቷ በዚና ድንግልናዋን ስታጣ ከወንዱ የበለጠ ተጎጂ ትሆናለች፡፡ ይኸው ጠባሳም ዕድሜ ልኳን አይሽርላትም፡፡

በተለምዶም ሴቶችና ዝሆኖች ጠባሳቸውን ፈፅሞ አይረሱም” ይባላል፡፡ ለጋብቻ ላትመረጥ ትችላለች። ስታገባም ለባሏ የምታበረከተው ትልቁ ወሲባዊ ስጦታዋ (ከብረ ንፅህናዋ) አብሯት አይኖርም፡፡ እናም በዚህ ሳቢያ መላው የጋብቻ ሕይወቷ ይጎዳል፡፡

⚡️⚡️ ዝሙተኛይቱ ያገባች ሴት ከሆነች ደግሞ ለባሏ ትልቅና ቀጣይነት ላለው ውርደት መንስኤ ትሆነዋለች፡፡ በተለምዶም “አንድ እውነተኛ ባል የሚስቱን ምንዝርነት ከሚሰማ ተገድላ መርዶውን ቢሰማ ይሻለዋል» ይባላል፡፡

✏️✏️ ያገባች ሴት ከዚና አርግዛ ልጅን ብትወልድ የባል ቤተሰብ የዘር ሐረግ ንፅህናቸው ይበላሻል፡፡ ያላገባች ከሆነች ደግሞ በቤተሰቧ ላይ ታላቅ ሀፍረትንና ውርደትን ታስከትላለች፡፡ ይህም ቤተሰቦቿን ለበቀልና ለአፀፋዊ እርምጃዎች ያነሳሳቸዋል፡፡ አንዱ ቤተሰቡ ከሌላው ጋር ለመፋጀትም ይበቃል፡፡

⚡️⚡️ በሴት ልጅ ወሲባዊ ሕይወት ውስጥ ትልቅ ስህተት ተፈፀመ የሚባለው እርሷ ዜናን ለመሥራት ውሳኔዋን ባሳለፈች ቀን ነው፡፡ ይህንኑ ተከትሎ የሴት ልጅ ወሲባዊ ሕይወቷ የመበላሸት ዕድሉ ሰፊ ነው:: ዝሙተኛ ሴት ለወደፊቱ የሕይወት አጋሯ እራሷን ጠብቃ ማቆየት አትችልም፡፡ ትዳር ወደተባለው ተቋም ስትገባ ዋናው የመግቢያ መስፈርት (ድንግልናው) አብሯት የለም፡፡

✏️✏️ በተለምዶ ሴቶች አራት ዓይነት ናቸው ይባላል፡- ➊ድንግል፤
➋ ዝሙተኛ፡
➌ፈት እና
➍ ፈትም የልጆች እናትም የሆነች፡፡ ድንግሏን ካገበሀት ያንተ ብቻ ናት፡፡ ፍቺም አይኖርም፤ ደባል ባልም አያሰጋህም፡፡ ዝሙተኛዋ ያንተ ልትሆንም ላትሆን ትችላለች፡፡ ሌላው ቢቀር ደባል ባል ይዛብህ ልትመጣ ትላለች:: ዝሙተኛ ሴቶች በቁርኣን አገላለጽ «አል-ኸቢሣት›› (መጥፎዎቹ ሴቶች፣ቆሻሾቹ) ተበለዋል።

ፈት ሴት ያንተ መሆን ብትችልም፣ ግና የቀድሞ ባሏን አትረሳውም፡፡ ፈትም የልጆች እናትም የሆነች ደግሞ ያንተ ብትሆንም ልጆቿንም የቀድሞ ባሏንም አትረሳቸውም፡፡

አሁንም ሴቶችን በአለባበስ ረገድ ወሲብ ቀስቃሽ አለባበስን የሚከተሉና ሒጃባቸውን በወጉ የሚለብሱ ብለን ለሁለት መከፈል እንችላለን። ታዲያ የዚህ ኡማ ወንዶች ትልቁ ፈተናም እነዚህ ወሲብ ቀስቃሽ አለባበስን የሚከተሉ ሴቶች (ቀበጥ ሒጃቢስቶች) መሆናቸው ሊታወቅ ይገባል፡፡

⚡️⚡️ ዝሙተኛይቱ ከዚና አርግዛ ለውርጃ ልትዳረግ ትችላለች፡፡ ይህም በወንጀል ላይ ወንጀልን ያሸከማታል፡፡ ከዚና ከወለደችም ልጁን ለማሳደግ በርካታ ፈተናዎች ታያለች፡፡ በልጁ አስተዳደግና እነፃ ላይ ትልቅ ከፍተት ይፈጠራል፡፡ ይህም በተራው አሳዳጊ የበደለው ልጅ ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀል ያደርጋል።

✏️✏️ ሴት በዚና ሳቢያ ከወንዱ የበለጠ ለአባላዘር በሽታዎችና ለኤድስ የመጋለጥ ዕድሏ ሰፊ ነው፡፡ ወንዱ ኮንዶምን እንዲጠቀምና ጥንቃቄ የተሞላበት ወሲብን እንዲያደርግ የማስገደድ አቅሟም አነስተኛ ነው፡፡ ስለዚህ ዚናው የሚካሄደዉ ከሞላጎደል በርሱ ፍላጎት መሠረት ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ማሕፀኗ ሊጎዳና የማሕፀን ግድግዳዋ ሊደማ ይችላል፡፡ ለፊስቱላ በሺታም ልትጋለጥ ተላለች፡፡

⚡️⚡️ ሴት በዚና ሳቢያ ከማንኛውም የወሲብ መንገደኛ ጋር አስሬ በአፍጢሟ ስትድፉ ከብሯ ሁሉ ይቀንሳል፡፡ ዝሙተኛውም ፈፅሞ እንደሰው እይቆጥራትም።

✏️✏️ ሴት በዚና ሳቢያ ለተለያዩ ወሲባዊ አብደቶች ልትጋዝጥ ትችላለች በዝሙተኛውና በዝሙተኛይቱ መካከል ፍቅርና ውዴታ ስለሚይኖር እርነሱ ፈፅሞ አይራራላትም፡፡ ከዚህም የተነሳ የፊንጢጣ ወሲብን ሊሠራባት ይችላል፡፡ የአፍ ወሲብንም ሊሠራባት ይችላል፡፡ የነዚህ ወሲባዊ እብደቶች ጉዳት ደግሞ እጅግ የከፋ ነው፡፡ መላውን ወሲባዊ ሕይወቷን ሊያበላሽ ይችላል፡፡

⚡️⚡️ በተለይ የዘመናችን ዝሙተኞች የተለያዩ የወሲብ ማነቃቂያ ነገሮችን በመውሰድ ሴቶችን እንደሚያሰቃዩ እሙን ነው፡፡ ለምሳሌ ሱስ አስያዥ ዕፅን የወሰደ ወንድ ሴቷን በአንድ የወሲብ ዙር ብቻ እስከ 40 ደቂቃዎች ሊያሰቃያት ይችላል፡፡ ከዚህም የተነሳ ሴቷ በቀላሉ ትዳከማለች፡፡ አካሏም ሆነ መንፈሷ ሲበዛ ይጎዳሉ፡፡ ይህም በርሷ ምርታማነት ላይ ትልቅ ተጽዕኖ አለው፡፡👇👇👇
✏️✏️ ሴት ልጅ በተለይ አሁን ቴከኖሎጂው በብዛት ለመጥፎ ነገር ማስፋፈያነት በሚውልበት አግባብ ውስጥ በለየለት እኩይ ወንድ እጅ ከገባች እርሱም ዚናውን እየፈጸመባት በተጓደኝነትም ያንን ትዕይንት ቀርፆት ያስቀምጠዋል፡፡ ወንዱ ይህንን ካደረገ ደግሞ ከዚህ በኋላ የርሷ ነገር በርሱ እጅ ውስጥ ገባ ማለት ነው፡፡ እንደፈለገ ይጫወትባታል፡፡ ያስፈራራታል፤ ያስለቅሳታል፡፡ ከዚህም የተነሳ ሴቷ ለብላክሜይሊንግ (ማስፈራሪያ) ትጋለጣለች፡፡ ይህም ነገር በተውበት ወደ አላህ (ሱ.ወ) እንዳትለመስ ሁሉ ደንቃራ ይሆንባታል፡፡ በዚያ ቪዲዮ ሳቢያም ሴቷ ወደ ጌታዋ ሁሉ መሸሽ የማትችልበት ሁኔታ ያጋጥማታል፡፡

⚡️⚡️ ዝሙተኛ ሴት ለአስከፊው የሴተኛ አዳሪነትና ለወሲብ ንግድ የመጋለጥ ዕድሏ ሰፊ ነው፡፡ በተለይ ጉንተላ የሚበዛባት ከሆነ በቀላሉ ወደዚህ ሥራ ልትገባ ትችላለች፡፡ የሴተኛ አዳሪነት ሥራ ጭንቅላት፣ ተያዥ፣ የሕከምና ማስረጃ፣ የሥራ ፈቃድና የመነሻ ካፒታል ስለማይጠይቅም የዝሙት ሱስ ያለባቸውን ሴቶች የመሳብ ችሎታው ከፍ ያለ ነው፡፡

በአጠቃላይ ሴት ልጅ በዝሙተኛ ወንድ እጅ ገባች ማለት የትዳር አጋሯ ባልሆነ፣ በማይወዳት፣ በማያፈቅራት፣ በማይጠነቀቅላትና በማያዝንላት ሰው እጅ ገባች ማለት ነው፡፡ ይህ የወሲብ መንገደኛም ለራሱ ስሜት እንጂ ለርሷ ደህንነት አንዳችም ነገር አይጨነቅላትም፡፡ ለሚመጣው መዘዝም ኃላፊነቱን አይወስድም፡፡ ጉዳት ሲደርስባትም አብሮነቱን አያሳያትም፡፡ ከዚህም የተነሳ በወሲብ መንገደኛ እጅ የገባች ሴት ለአውሬያዊ አያያዝ ትዳረጋለች፡፡ ይህም ሴቶችን በሁሉም መልኩ ይጎዳቸዋል፡: ዚና ሴቶችን የወሲብ ሕይወታቸውን ብቻ ሳይሆን ሁለንተናዊ ማንነታቸውን ጭምር ያራክሳል፡፡ ከብራቸውን ዝቅ ያደርጋል፡፡በገላቸዉ እንጂ በጭንቅላታቸው እንዳያስቡ ያደርጋቸዋል፡፡ እራሳቸውን እንዲያሻቅጡና አስከፊውን የሴተኛ አዳሪነት ሕይወትን እንዲቀላቀሉ ምከንያት ይሆናቸዋል፡፡ ይህም በመሆኑ ሴቶች በዚና ሳቢያ ከወንዶች በላይ ተጠቂዎችና ተጎጂዎች ሆነው ይገኛሉ፡፡ ለዚህም ሲባል ነው ቁርኣን በዚና ጉዳይ ሴቶችን ያስቀደማቸው፡፡


⚠️⚠️በዚና መስመር ላይ ያለን፡በመንደር ደር ላይ ያለን ከአላህ ጋር እየተጣላን እርዚቃችንን ደስታችንን ከማሸሽ ከዚህ ከዚና አስከፊ በሽታ ሞት ሳይቀድመን ቶብተን እንጠብቀዉ

መታወቅ ያለበት የሴቶች አለባበስ ለራሱ የዚና መንደርደሪያ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል፡፡


👌የዚና ጉዳይ ሲነሳ ተፈራርቶ አይሆንም ለሌሎች ሼር ያርጉ አይታወቅም አንድ ሰዉ ወደ ቀልቡ ተመልሶ ከዚና ቢቶብት ሼር ባደረግንበት ከአጅሩ ተጠቃሚ ሆን ማለት ነዉ

ስለዚና ያተኮሩ ርዕሶች ኢንሻ አላህ ይዘጋጃሉ
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
ሉቅማን አል-ሐኪም ልጁን እንዲህ ሲል መክሮታል፡፡

>> “ልጄ ሆይ ከሰው ልጅ ጀርባ ያለውን ነገር ሳታውቅ ፈገግታው እንዳያታልልህ !! ምክንያቱም የሰው ልጆች የማንነት መቃብር ልቦናቸው ውስጥ ሲሆን የሚያስጐመዥ ፍሬያቸው ደግሞ ፊታቸው ላይ ይገኛል፡፡

ስለዚህ እሮሮህና አቤቱታ ዘውትር ይህን ዘመን ወደ ፈጠረው አላህ (ሱ.ወ) ይሁን፡፡ አላህ (ሱ.ወ) ጥሩውንም ሆነ መጥፎውን ነገር ባንተ ላይ ከሻተ ሰዎች ወደዱም ጠሉም አንተ ላይ ከመከሰት ወደኋላ እንደማይል ጠንቅቀህ እወቅ፡፡"

@አሚር ሰይድ


https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAESAIxFIdM3tYVwa1g
#በሰባት_ጣዖታውያን_ላይ_ያደረጉት_ዱዓ

ቡኻሪና ሙስሊም ኢብኑ መስዑድን በመጥቀስ እንደዘገቡት፡

«ነቢዩ ﷺ ከዕባ ውስጥ ይሰግዱ ነበር። አቡ ጀሀልና ባልደረቦቹ ተቀምጠዋል። «ሙሐመድ ሱጁድ ሲያደርግ ፈርስ የሚያፈስበት ማን ነው?» ተባባሉ። ከመካከላቸው ይበልጥ ተንኮለኛው ፈርስ ይዞ መጣ። ሱጁድ እስኪያደርጉ ጠበቀና ከጀርባቸው ላይ አፈሰስባቸው፡፡ እኔ ሁኔታውን እከታተል ነበር። ምንም ላደርግ አልቻልኩም። ጉልበት ቢኖረኝ ኖሮ ይህ ነገር በነቢዩ ላይ እንዳይደርስ በተከላከልኩ ነበር።

ሰዎቹ ይሳላቁ ጀመር። አንተ ነህ አንተ ነህ እየተባባሉም ይቀልዱ ጀመር። የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ሱጁድ እንዳደረጉ ናቸው" ራሳቸውን ከሱጁድ አላቀኑም። ልጃቸዉ ፋጡማ(ረ.ዐ) መጣችና ቆሻሻውን ከጀርባቸው አስወገደችላቸው። ራሳቸውን ቀና አደረጉና፡ «አላህ ሆይ! ቁረይሾችን ተበቀልልኝ» በማለት ሦስት ጊዜ በመደጋገም ዱዓ አደረጉ።

እርግማኑን ሲስሙ ሰዎች ተጨነቁ። በዚያ ሀገር ውስጥ የሚደረግ ዱዓ ተቀባይነት እንዳለው ያምኑ ነበር። ነቢዩ በመቀጠልምሰዎችን በስም ጠርተው ዱዓ አደረጉባቸው፡፡ እንዲህ አሉ  «አላህ ሆይ!
>አቡ ጀህልን ተበቀልልኝ።
> ዑትበት ኢብኑ ረቢዓህን'
>ሸይበት ኢብኑ ረቢዓህን፡
>ወሊድ ኢብኑ ዑትባህን
>ኡመያ ኢብኑ ኸለፍንና
> ዑቅበት ኢብኑ አቢ ሙዒጥን ተበቀልልኝ»
አንድ ሰውም ጨምረው ጠሩ። ስሙን አላስታወስኩትም።

ነፍሴ በእጁ በሆነችው ጌታ እምላለሁ፣ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ስማቸውን ጠቅሰው የረገሟቸው እነዚህ ሰዎች በድር ላይ ተገደሉ። ገደል ውስጥም ተጣሉ።


ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ያአሏህ😢

አረ በዱአ አንዘንጋቸዉ ልብ ይሰብራል😔

ይቺ ህፃን ልጅህ(ልጅሽ) ወይም እህትህ(እህትሽ)ብትሆን የስቃይ ስሜታችን መቆጣጠር እንችል ይሆን😔
⚠️#ኢስላምን_በዉርስ_ያገኘነዉ_ሀይማኖት_ስለሆነ_ዝሙትን_ተዳፈርን
     አሚር ሰይድ

«በአሜሪካ ያሉ ሰለምቴ ሙስሊሞች ከምንም በላይ ከሁለት ወንጀሎች በግልፅ እንደራቁ አስረግጦ መናገር ይቻላል፡፡ አዎን! ማንኛውም ሰለምቴ አሜሪካዊ ሙስሊም ከሪባ የራቀ ነው፡፡ እንዲሁም ማንኛውም ሰለምቴ አሜሪካዊ ሙስሊም ከዝሙት የራቀ ነው፡፡» (ኑእማን አሊ ካን - አሜሪካዊ ዳዒይና የቁርኣን ተንታኝ)


         እንደሚታወቀው አብዛኛው የሀገራችን ሙስሊም ኢስላምን የሚወርሰው ከቤተሰብ ነው፡፡ ቤተሰቡ ሙስሊም የሆነ ልጅ እርሱም ሙስሊም ይሆናል፡፡ ከዚህም የተነሳ ኢስላምም በውርስ የሚያገኝ ሃይማኖት ይሆናል፡፡ ኢስላምን በውርስ የሚያገኝ ልጅ ደግሞ ስለእምነቱ ይህንን ያህል የበዛ ትኩረት ሰጥቶት ላያጠናው ይችላል፡፡

ነገር ግን አሜሪካዉያን ሙስሊሞችን በምሳሌነት ብንወስድ እነርሱ ዘንድ አብዛኞቹ ኢስላምን የተቀበሉት አንብበው፣ አጥንተው፣ ተመራምረው፣ አነፃፅረውና እዉነቱን አንጥረው ካወቁ በኋላ ነው፡፡ ከዚያም በዚህች ምድር ላይ ብቸኛው እውነት ብቸኛው መለኮታዊ ሀይማኖትና ታላቁ ፀጋ ኢስላም መሆኑን ስለሚረዱ ወደ ኢስላም ሲመጡ ዲኑን በሚገባ ለመተግበር ነው፤ በሙሉ ልባቸው፡፡

በተለይም ምዕራባዉያን ዜጎች ሙስሊም ከሆኑ በኋላ አንዳች ሲሠሩት የነበረው ነገር በኢስላም የተከለከለ መሆኑን ካወቁ ወዲያው ያንን ነገር ይተውታል፡፡

⚡️⚡️አሜሪካዊው ታላቁ ዳዒይና በቁርኣን ተፍሲር ትልቅ ዕውቅናን ያገኘው ኑእማን አሊ ካህን በበኩሉ በምዕራቡ ዓለም እጅጉን የተንሰራፉ ነገሮች በተለይ ወለድና ዝሙትን የመሳሰሉ ኃጢአቶች እነሱ ዘንድ ከሞላ ጎደል እንደማይታወቁ ይናገራል፡፡ በተለይም ከጥቂት ዓመታት በፊት የደረሰውን የምዕራቡን ዓለም የገንዘብ ቀውስን አስመልክቶ ቀውሱ ሙስሊሞችን እምብዛም እንዳላጠቃቸው በመጥቀስ አሜሪካዊው ሙስሊም ከወለድ የራቀ መሆኑን እንደማሳያ ያነሳል፡፡

#ቀጥሎም ዝሙትን አስመልከቶ አሜሪካዉያን ሙስሊሞች ከዚህ መራቃቸውን እንደ ማሳያ የሚያነሳው ነገር ቢኖር የመስሊም ሴቶችን ታላቅ ግብረገብነትና የሒጃብ አለባበሳቸውን በመጥቀስ ነው::

በዚህች ሀገር የሴቶች ትልቁ መከበሪያቸው ሒጃብ ነው:: የራስ መተማመናቸውና ለኢስላም ያላቸው ፍቅር ያስደንቅሃል፡፡ ሴቶቹ እንዴ ከሰለሙ በኋላ ወሲብ ቀስቃሽ አለባበስን ሊከተሉ ቀርቶ ከቶውኑ አያስቡትም፡፡ ቀድሞውኑ ኢስላምን አጥንተውትና መርጠው ስለሚመጡ ሰዉ ምን ይለኛል የሚለውን ነገር ከመጤፍ አይቆጥሩትም፡፡ ወንዶቹም ቢሆኑ አብዛኞቹ ያገቡ ስለሆኑ ስለዝሙት አይነሳባቸውም፡፡

እንደውም በአንድ አጋጣሚ የተከሰተውን ነገር ለምን አልነግራችሁም? በአንድ ወቅት አንዲት ደምቃና የሰዎችን ትኩረት ለመሳብ ተሸሞንሙና የወጣች እንስት ከአንድ ወጣት ሙስሊም ጋር በባቡር ላይ ይገናኛሉ፡፡ ሰዉ ሁሉ አተኩሮ ያያታል፡፡ እርሷም እየተገማሸረች የምትወጣው ለዚህ ነው፡፡ ወንዱ ሁሉ በአድናቆትና በምኞት ይመነጥራል፡፡ ይህ ወጣት ግን አንዳችም ትኩረት ላይሰጣት ቀረ፡፡ እርሷ ግን አልፎ አልፎ ትገረምመዋለች፡፡ እርሱ ወይ ፍንክች አላለም፡፡ ታዲያ ተሳፋሪው ቀስ በቀስ እየወረደ ሲቀንስ እርሷ አውቃ የወጣቱ ዓይን ውስጥ ለመግባት ተጠጋችው፡፡ እርሱ ግን አሁንም ከምንም አልቆጠራትም፡፡ ወዲያ ወዲህ ብትቀበጥም አላተኮረባትም፡፡
..... በመጨረሻም በኃይለኛው ተቆጥታ ለመሆኑ አንተ ወደኔ አንዴም የሚታየው እኔ ይህን ያህል ቀፋፊ ነኝ እንዴ? ቆይ እንዲህ ከሆነ እኔ ለማነው ተጋጊጬ የምወጣውን ስትል አቧረቀችበት፡፡

እርሱ ግን በተረጋጋና የራስ መተማመን መንፈስ በተሞላበት ሁኔታ ይህንን ለምን እንደማያደርግ አስረዳት፡፡ አየሽ! እኛ ሙስሊሞች ዕይታችንን እንድንቆጣጠር ታዘናል፡፡ ስለዚህ ወደ ባዳ ሴት ሆነ ብሎ መመልከት የተከለከለ ነው፡፡ ለዚህ ስል ብቻ ነው እኔ ወደ አንቺ የማላየው፡፡ ከዚህ ውጭ በግል ምንም ያደረግሸኝ ነገር የለም፡፡ የእምነት ጉዳይ ሆኖብኝ ነው ወዳንቺ የማልመለከተው አላት፡፡ ልጅቷ በሰማችሁ ነገር ተገረመች፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰውና እምነት እንደዚያ ሰይጣንን አብዝታ በምታበረታታው ሀገረ አሜሪካ መኖሩ አስደነቃት፡፡ እምነት ሰውን ከብልግና ሲታደግ አስተዋለች፡፡ እናም ለመሆኑ ያንተ እምነት ምንድነው? ስትል ወጣቱን ጠየቀችው፡፡ እርሱም እምነቱ ኢስላም መሆኑን ነገራት፡፡ ስለኢስላምም አንዳንድ ነገሮችን ነገራት፡፡ ከዚያም ስልክ ተለዋወጡና በዚሁ ተለያዩ፡፡

ልጅቷ በሰማቸውና ልጁ ላይ ባየችው እፁብ ድንቅ ምግባር እጅጉን ተደምማለች፡፡ እንዲህ ዓይነት ወጣት ገጥሟት ስለማያውቅ ስለርሱ እምነት ልታጠና ጓግታለች፡፡ ወዲያው በነጋታው ደውላ የቁርአንን ኮፒ እንዲሰጣት ጠየቀቸው:: እርሱም የቁርአን ኮፒ ሰጣት ልጅቷም ቁርአንና ሌሎችንም ኢስላማዊ መጻሕፍት ለስድስት ወራት አከታትላ አጠናችው፡፡ ስድስት ወሩ እንዳለቀም ለልጁ ደወለችና ኢስላምን መቀበል እንደምትፈልግ አበሰረችው፡፡ እሱም ወደመስጊድ ወሰዳትና ሰለመችም፡፡ የአላህን አንድነትና ብቸኛ አምላክነቱን መሰከረች፡፡ገና ልትሰልም ስትመጣ እራሱ ሒጃቧን በወጉ ለብሳ ነበር፡፡ እናም አሁን በኛ ማዕከል ውስጥመደበኛ ሴት ዳዒይ ስትሆን በርሷ ሰበብም በርካታ ሴቶች ወደ ኢስላም መጥተዋል፡፡
(ምንጭ፡- ቮይስ ኦፍ ኢስላም - አሜሪካ)

በመጨረሻም ኑእማን አሊ ካን አያይዞም እንዲህ ይላል፡-
«በአሜሪካ ፊትናው ከባድ ነው:: ግና የሰለምቴው ንቃተ ሕሊና ከፍተኛ ነው::

ሙስሊሙ ሐራምና ሐላልን በሚገባ ለይቶ ያውቃል፡፡ እዚህ በአላህ (ሱ.ወ) ሕግ ማቻቻል የሚባል ነገር የለም፡፡ አንዳች ነገር ሐራም መሆኑን ካወቁ ከቤተሰብ ጋር የሚያለያይ እንኳን ቢሆን ለኢስላም ሲሉ ያደርጉታል፡፡,, (ምንጭ፡- ቮይስ ኦፍ ኢስላም - አሜሪካ)

✏️አላዋቂነት ለሁሉም ኃጢአት አብይ ምክንያት ነው፡፡ በተለይ ዝሙት ላይ የድንቁርና አሻራ እጅጉን ይጎላል፡፡ የሰው ልጅ ዓይን ስላለው በጭለማ ውስጥ እንደማያይ ሁሉ ጭንቅላት ስላለው ብቻ ዕውቀት አለው ማለት አይቻልም፡፡ ዕውቀት ከሌለው ደግሞ ድንቁርና መጥቶ እንደ ወቃቢ ይሰፍርበታል፡፡ በርግጥም ከድንቁርና የበለጠ ክፉ ውቃቢ የለም፡፡ ታዲያ የድንቁርና ውቃቢ ያለበት ሰው ቢያንስ በአራት መንገዶች ዝሙት ላይ የወድቃል በአይኑ በምላሱ በእጁ...

🙄እኛ ኢትዮጲያን የነጃሺ ሀገር በአለም ሁለተኛ ሙስሊም የተቀበልን የኢትዮ ግማሽ ፐርንሰት በላይ ሙስሊም ነን ..ዲነኛ ነን ኪታብ ቀርተናል ..መስጊድ ተነካ..ኢስላም ተደፈረ ..ወዘተ በምላስ እንላለን በጎን ዚና እንሰራለን🤔

☞ክርስቲያኖች ኢትዮ የሙሴ ፅላት አለ ..አርባ አራት ታቦት አለ ..ኢትዮ ገማደ መስቀሉ አለ ይሄን ያህል ገዳም አለን ኢትዮ የኛ ናት በጎን ዚና እንሰራለን🤔

ለወደፊት የማዘጋጀዉ ፁሁፍ አዲስ አበባ ከአፍሪካ አንደኛ ከአለም አራተኛ የዝሙት ሀገር መሆኗን በአለም ተረጋግጧል በዚህ ሰፋ ያለ ፁሁፍ ጊዜ ሳገኝ አዘጋጃለሁ፡፡

ግን ኢትዮጲያ አዲስ አበባ ያለዉ ሀይማኖተኛ ሀይማኖት ያለዉ ነዉ ግን ከአፍሪካ 1ኛ የዝሙት ሀገር ነዉ...ኢንሻ አሏህ ስለ አዲስ አበባ  የማይታመኑ 100% እዉተኛ ነገሮች በፁሁፍ ይቀርባሉ፡፡ሀይማኖት በልብም በተግባር ነዉ

ፈጣሪ የምላስ ሀይማኖተኛ አስመሳይ ከመሆን ይጠብቀን፡፡
ከዝሙት እንጠንቀቅ ..በዝሙት መስመር ያለን እንቶብት!!!

#ምንጭ ☞በዝሙት አንዘምን መፅሀፍ



ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
አንድ ብቻውን የሚኖር አቅመ ደካማ ሽማግሌ ነበር፡፡ ሁሌም አላህን ሲለምን ...አላህ ሆይ!!! ለቡጋስ እንደምትለግሰው ሁሉ ለኛም ለግሰን፡፡› ይላል፡፡

ቡጋስ የወፍ ዝሪያ ሲሆን ሲወለድ ምንም ዓይነት ፀጉር የሌለው ሆኖ ነጭ ሰውነት ይዞ ነው፡፡ ጥቁር ባለመሆኑ ምክንያት እናትና አባቱ የኛ ነው ብለው ስለማያስቡ ይመስላል አይቀልቡትም፡፡ እሱም ቢሆን የመብረር አቅም ስለሌለው ሄዶ ሪዝቁን ማምጣት አይችልም፡፡

ነገርግን ሪዝቅ ቢርቅም አርረዛቅ አለ፡፡ ቡጋስ ሽታው አንዳንድ ጉንዳኖችን የመሳብ ሀይል አለው፡፡ ፀጉሩ እስኪበቅልለት ድረስ እነኚህኑ ይመግባል፡፡ በዚህ ጊዜ እናቱ ታውቀውና እሱን መመገብ ትጀምራለች፡፡


#እውነትም_ለቡጋስ_እንደምትለግሰው_ሁሉ_ለኛም_ለግሰን፡፡

@አሚር ሰይድ

join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
#የኪፍል_ተዉበትና_የአሏህ_አቀባበል
    አሚር ሰይድ


  ማንኛወም ሰዉ ከተዉበት ተዘናግተናል..በተለይ ብዙዎቻችን አሁን ላይ ቦይፍሬድ ገርልፍሬንድ ስም በተጨማለቅንበት  በዝሙት ላይ ሁነን ለመቶበት አንዴ ገብተንበታል በሚል አስተሳሰብ የብስ በወንጀል ላይ ወንጀል እየደራረብን ነዉ፡፡ነገ ይሄን ዛሬ ሞቻችንን ሳናቀዉ በጊዜያዊ ደስታ ዱንያችንን  አኼራንም እያጣን ነዉ...እስኪ ዝሙት የሚሰራዉ በአራጣ በቁማር ወንጀል ላይ የነበረዉ ኪፊል  ለሊት ሙቶ አደረ አላህም ተዉበቱን ተቀበለዉ በምን ይሆን ተዉበተን የተቀበለዉ??እስኪ የሀቢቡና ሙሀመድ የተናገሩትን ሀዲስን ልጋብዛችሁ



ዐብደሏህ ቢን ዑመር(ረ.ዐ)እንዳወሩት እኔ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ  ከሰባት ጊዜ በላይ እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ:-

    በበኒ አስራኤል ውስጥ ኪፍል የሚባል ሰው ነበረ:: ይሄ ሰው ማንኛዉም ወንጀል በመሥራት ይታወቃል። አላህን የማይፈራ የለየለት ሙጅሪም ሰው ነበረ፡፡ ያገኘውን ሀጥያት የሚሠራ ሰው ነበረ፡፡

አንድ ቀን አንዲት ሴት ተቸገረችና (መቼስ አላህ ድህነትን ያላለጠበት ሰው ፈተናው ከባድ ነውና) እርሱ ጋ መጥታ ገንዘብ ጠየቀችው፡፡ እርሱ ሃብታም ሰው ነበር፡፡ ወንጀል የሚባል ግን አንድም የቀረው ነገር የለም፡፡ ከዚያም ስድሳ ዲናር ሊሰጣትና እርሷ ደግሞ ለዚና እራሷን ልታመቻችላት ዘገድ እነጋገራት፡፡ እንግዲህ አስቡት! በዚያን ጊዜ 60 ዲናር ማለት  በጣም ከፍተኛ ብር ነው፤ በኃይለኛው ያማልላል፡፡

ይህች ሴትም ፈቃደኛ ሆነች  ተቸግራለችና ድህነቱ አስገደዳት)፡፡ ከዚያም ስድሳወጣም ዲናር ሰጣት፡፡ ከዚያም እርሷ እራሷን አመቻቸች፡

እርሱም ዚና ለመስራት  እላይዋ ላይ ተቀምጦ ሳለ  ይህች ሴት ከመቅፅበት ተንቀጠቀጠች አለቀሰች😢 ተርገበገበች፤ ተንዘፈዘፈችና በኃይለኛውም አነባች፡፡
.... ኪፍልም ምን ነካሽ? ብዙ ገንዘብ አይደል እንዴ የሰጠሁሽ? አስገድጄሻለሁ እንዴ? በፍላጎትሽ አይደለም እንዴ? እናም ምን ሆነሽ ነው የምታለቅሺዉ?? አላት፡፡
....ከዚያም ይህች ሴት ወሏሂ! እኔ ይህንን የዚና ኃጢአት በዕድሜዬ እኮ ሠርቼው አላውቅም፤ ችግሩ አስገድዶኝ ነው እንጂ። ፈፅሞ ሠርቼው የማላውቀው ወንጀል ስለሆነ አሁን አላህን ፈርቼ ነው የማለቅሰው አለቸው፡፡ ......አርሱም አላህን ፈርተሽ ነው የምታለቅሺውን??
...... አላት፡፡ አዎ› አለችው፡፡

አስቡት አንግዲህ! ይሄ ዕድሜ ልኩን ወንጀል ሲሠራ የኖረ ሰው ነው፡፡ መች ይህ ብቻ እንድም መልካም ሥራ ሠርቶ አያውቅም፡፡  የዚህች ሴት ተቅዋና የርሷ መንቀጥቀጥ ልቡን ነካውና ወዲያው ይህንን ሁሉ ስድሳውን ዲናር ውሰጂው፡፡ እኔ አሁን ተወብት ገብቻለው እናም አልነካሽም ዚና አልሰራሽም፡፡ እኔ ካሁን ጀምሮ አበደን አላህን አልወነጅልም፡፡ ኃጢአት፣ ዝሙት፣ ፀያፍ ድርጊት የሚባል ነገር ካሁን ወዲያ ምንም አልሠራም፡፡ አንቺ ችግሩ እያለብሽ፣ ገንዘቡንም ለመውሰድ እየፈለግሽ ግን የአላህ ፍራቻው ገታሽ፡፡ አኔም ከዚህ በኋላ አላህን ፈፅሞ አላምፅም አለ፡፡


ከዚያም ነብዩ ﷺ እንደተናገሩት ይህ ሰው በዛቸው ለሊት ሞቶ አደረ፡፡ መሞቱም በበሩ ላይ ተፅፎ በተገኘዉ ፁሁፍ  ተረዳ፤ በአላህ መላእክት አማካኝነት፡፡


አላህ ለኪፍል ምሮታል የሚል ዐ.ነገር በበሩ ላይ ለየት ባለ ጽሑፍ ተፅፎ ተገኘ፡፡» (ቲርሚዚ ዘግበዉታል)


⚠️⚠️  ከዝሙት እንቶብት አሁን ዝሙትን መሥራት ውሃን የመጠጣት ያህል እና እጮኛን መያዝ ሻንጣን የመያዝ ያህል ቀላል በሆነበት ዘመናዊት ዓለም ውስጥ በመዘናጋት ያለተዉበት ሞትን እየጠበቅን ነዉ...ይቺ ነገ እንቶብታታለን ያልናት ቀን ነገ ሳትደርስ ሞት ቀድማን ከነገ ወዳ ያለዉን የአኼራ ህይወት  የቀብር ህይወት የነኪርና ነኪር ጥያቄ ...አላህ ፊት ያለ አስተርጓሚ ለጥያቄ ለመቅረብ  ምን ያህላችን ዝግጁዎች ነን??
ምን ያህሎቻችን ለመቶበት ዝግጁዎች ነን??


ሼር በማድረግ ኢስላማዊ ግዴታዉን ይወጡ..በዚህ ፁሁፍ የተነሳ አንድ ሰዉ ቢቶብት ትልቅ ነገር ነዉና...


join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
ድል ያለ ሰርግ ተደግሶ ባል እና ሚስት ቃለ መሀላ ለመፈጸም እየተዘጋጁ ሳለ ነው ባል ቃል ከመግባታችን በፊት መናገር የምፈልገው ነገር አለ በማለት ማይኩን የተቀበለው።

ቀጠለናም የታሸገ ፖስታ ለሁሉም የሰርጉ ታዳሚዎች እንዲሰራጭ እና ታዳሚዎቹም ፖስታውን ከፍተው እንዲመለከቱት ያደርጋል፡፡ 

የታሸገው ፖስታ ውስጥ ያለው ሚስቱ ለመሆን ቃለመሃላ ለመፈፀም እየተቁነጠነጠች ካጠገቡ የቆመችው ሴት እና አንደኛ ሚዜው የኔ ፍቅር የኔ ውድ እየተባባሉ ሲማግጡ የሚያሳይ ፎቶ ነበር፡፡ 

ሙሽራው አሁንም ማይኩን እንደያዘ  “በፎቶው ላይ የምትመለከቱት ምስል ውዷ እጮኛየ እና የልብ ጓደኛዬ ማንም አያየንም ብለው ተደብቀው ሲማግጡ የሚያሳይ ነው። ታዲያስ  ከእንደዚች አይነት ሴት ጋር ትዳር ባልመሰርት የሚፈርድብኝ አለ?!"ብሎ ታዳሚውን ጠየቀ።መልስ አላገኘም።

ኋላም ሙሽሪት በድንጋጤ በቆመችበት ደህና ሁኚ ብሏት ከቤተሰቦቹ ጋር የሰርጉን አዳራሽ ጥሎ ወጥቷል፡፡
☞ የዴይሊ ሜይል ዘገባ ነው

#ከዝሙት እንጠንቀቅ እንቶብት...ዝሙት ዛሬም ነገም ከነገ ወዳም መዘዙ ሰፊ ነዉ፡፡ለ15 ሰከንድ የሀራም እርካታ የ40 የ50 አምት ፕላናችንን አናበላሽ፡፡
አላህን አምፀን አላህ በዱንያ ዋጋችንን ያስከፍለናል ብድር በምድር‼️

ነገ እኛም በዝሙት ላይ ያለን እኛን በምን እንደሚያዋርደን አይታወቅም፡፡

ወላሂ ዝሙተኛ ሰዉ ሰላም የለዉም...በዱንያ ድህነት ጭንቀት ነዉ፡፡ሴቷም እራሷን ዝቅ ታደርጋለች.ዝሙተኛ ሴት ቤተሰብ የማያቃት ሴተኛ አዳሪ ማለት ነች..ለምን ዚና ስትሰራ ቤተሰቧ ሳያያት ነዉ፡፡ልጄ ጎበዝ ናት ዲነኛ ናት ይላል ቤተሰብ..እሷ ግን ቤተሰብ የማያቃት ሴተኛ አዳሪ ነች


ለሌሎች ያካፍሉ
join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
#አይነስዉሩ_ልጅ
አሚር ሰይድ

አንድ ሰውዬ ነበር ሁለት ልጆች አሉት በዲኑ ላይ ብዙም አይደለም፡፡ብዙን ጊዜ በሰዎች በማሾፍና በማላገጥ የተጠመደ ነው።አንድ ቀን መንገድ ላይ የሚሄድ ዐይነ ሥውር አጋጠመው ሰዎችን ሊያስቅበት ብሎ ከጎኑ  እየሄደ በዚህ ሰው ማላገጥ ጀመረ፡፡በዚህን ጊዜ ዐይነ ስዉሩ ሰው ልቡ ተሰበረበ እጅጉ😔ተሰማው፡በውስጡ ያለውን ደግሞ አላህ ይወቅ፡፡ከወራት በኋላ ይህ ሰው ዐይነ ስውር የሆነ ልጅ ተወለደለት፡፡ በዚም የተነሳ ተደናግጦና ሃሳብ ገብቶት ከዚህ ልጅ ጋር ግንኙነቱን አቋረጠ፡፡ እሱን ትቶ ለሌሎቹ ሁለት ልጆች ትኩረት ሰጠ፡፡ አዲሱን ልጁን ለእናቱ በመተው የሚያስፈልገውንም ወጭ ለሷ መስጠት ያዘ።ሆኖም ግን ውስጡ በእጅጉ ተጎድቶ ነበር፡፡ ይህ ልጅ ለመጥፎ ድርጊቶቹ መቀጫ ይሆን ዘንድ የተላከበት መሰለው፡፡የአባትነትን ፍቅር ለልጁ ነፈገዉ


ህፃኑ ልጅ ስድስት ዓመት ሞላው።አንድ ቀን እናት ከሁለት ልጆቹ ጋር ወጣ ብላ ስለነበር አባት ከዐይነ ስውር ልጁ ጋር ብቻውን ቤት ውስጥ ቀረ፡፡ቀኑ ጁሙዓ ነውና ልጁ አባቱ ወደ መስጊድ እንዲወስደው ጠየቀ፡አባት የስድስት ዓመት ልጁ የሚሰግድ መሆኑን ባወቀ ጊዜ ደነገጠ፡ከዚህ በፊት መስጅድ ይወስደው የነበረ ማን እንደሆነ ጠየቀው። ልጁም እናቱ እንደሆነች ነገረው፡፡ አባት ልጁን ወደ መስጅድ ይዞት መሄድ ጀመረ።

አንድ የሚያውቀው ትልቅ ሽማግሌ ይዞ የሚሄድ ዓይነት ተሰማው። ልጁ ከቁርአን የአል ከህፍን ምዕራፍ እያነበበ ነበር፡፡ አባት ይህን ሲሰማ ማልቀስ ጀመረ፡፡ በልጁ ሰበብ አላህን አወቀ፡፡ ልጁ በቃሉ ቁርኣንን መሸምደዱ ገረመው፡፡

ስብራቱ የነበረው ልጅ በዚህ መልኩ ወደ ፀጋ የተለወጠ ሆኖ አገኘው:: ሱብሀነሏህ፡
ትበድልና  ይሰብርሃል፡፡ ትግጎዳለህም፡፡ወደሱ ተጠግተህ በለመንከው ጊዜ ግን ስብራቱን ወደ ፀጋ ይለውጥልሀል፡፡
💚እናትነት ይህ ነዉ
🔴🔉🔉ታላቅ የምስራች ተጅዊድን መማር ለምትፈልጉ ተማሪዎች🟡📢📢

🔊
#ዚክራ_ኦንላይን_የቁርአን_ማእከል
የተጅዊድ ትምሀርት  ይዞላችሁ መጥቷል

🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘🔘

   
#የሚሰጠው_ኪታብ📚
البرهان في تجويد القرآن📚

    
#የሚሚሰጡ_ትምህርቶች📜📜

🔶
#የቁርአን አነባበብ ህጎች
🔶
#የቁርአን መጀመሪያና ማቆምያ ህጎች
🔶
#የፊደላት መውጫ (መኻሪጁል ሁሩፍ
🔶
#የፊደላት ባህሪያት (ሲፋቱል ሁሩፍ)
🔶
#የኑነ ሳኪና ወተንዊን ህጎች
🔶
#የመድ (የመሳብ) ህጎች
🔶
#የ ''ሯ'' ህጎች
🔶
#የሚመሳኪና ህጎች
🔶
#የሀምዘተል ወስል እና ቀጥእ ህግ
🔶
#የኢድጋም ህጎች
🔶
#የቀልቀላ ህጎች

📚📚📚📚📚
#የትምህርቱ_አሰጣጥ📘📕

1,በዙም አፕልኪሼን
2,በቴሌግራም አፕልኬሽን
    
       
#የቆይታ_ጊዜ 🕙

በሳምንት 4 ቀን


#ትምህርቱን_ለመከታተል_የሚያስፈልጉ

🔹ዋይፋይ(ፈጣን ኔትወርክ)
🔸ስማርት ስልክ

ይህን ሁሉ ደርስ በ #500 ብር ብቻ ይማሩ

ለመመዝገብ
👇👇👇👇
@zikra0835


👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/zikraquran



   በተጨማሪም
👉 ቁርአንን በተጅዊድ ማንበብ
👉  ለጀማሪዎች ቃኢዳ
👉  ሀዲስ እና የአቂዳ ኪታቦችን በግል(VIP)  እና በግሩፕ እናስቀራለን።
በግል ለመመዝገብ
https://www.tg-me.com/+251931800835

#ዚክራ_የቁርአን_መድረሳ
#ምድራዊውና_ዘልዓለማዊው_ዓለም

ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ “በርግጥ አላህ ሲሳያችሁን በመካከላችሁ እንዳከፋፈለ ሁሉ ሥነ-ምግባራችሁንም በመካከላችሁ ከፋፍሏል፡፡ አላህ ለሚወደው ሰውም ሆነ ለማይወደው ሁሉ ሁበት ይሰጣል፡፡ ሃይማኖትን ኢስላምን ለሚወደው ሰው ካልሆነ በስተቀር አይሰጥም፡፡
አላህ ሃይማኖት የሰጠው ሰው በርግጥ አላህ ወድዶታል፡፡


ነፍሴ በእጁ በሆነችው ጌታ እምላለሁ! የአንድ የአላህ ባሪያ ልብና ምላስ ኢስላምን በወጉ እስካልተቀበሉ ድረስ ኢስላምን አይቀበልም፡፡ ጐረቤቱንም ከችግሮቹ ካልጠበቀ አያምንም፡፡" ሰዎችም "የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ችግሮቹ ምንድን ናቸው?" ሲሉ ጠየቋቸው፡፡ እሳቸውም “ተንኮሉና በደሉ ናቸው፡፡ አንድ ሰው ገንዘብ አያግኝ፡ በእሱም ይባረክለት ዘንድ ያገኝ ዘንድ ከእሱ አይመፅውት፡፡ ከበስተጀርባውም አይተወውም፡፡ ይህ በራሱ ወደ እሳት የሚከተው ካልሆነ በስተቀር፡፡ አላህ መጥፎ ነገርን በመጥፎ አያጠፋም፡፡ ነገር ግን መጥፎ ነገርን በመልካም ነገር ያጠፋል።"

አሚር ሰይድ



join👇👇👇
www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
  www.tg-me.com/IslamisUniverstiy_public_group
2024/09/22 18:29:48
Back to Top
HTML Embed Code: