Telegram Web Link
18 K Telegram chanal የሚገዛ እውነተኛ ገዢ በውስጥ መስመር ያናግረኝ
👉መሸጫ ዋጋ 15K

@yesadikusitota
ይህ ትልቅ መንፈሳዊ ቻናል ችግር ቢደርስበት መቆያ አልያም መጠባበቂያ የሚሆነን #መዝገበ ሐይማኖት #የተሰኘ ቻናል ከፍቻለሁ! እናም አብሮነታችሁን join በማለት እንድታሳዩኝ በትህትና እጠይቃለሁ🙏🙏

@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
Audio
እነሆ ዛሬ ሹሜሃለሁ 
                                                  
Size:- 31.8MB
Length:-1:31:15
       
     በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
http://www.tg-me.com/abagebrekidan
http://www.tg-me.com/abagebrekidan
18 K Telegram chanal የሚገዛ እውነተኛ ገዢ በውስጥ መስመር ያናግረኝ
👉መሸጫ ዋጋ 15K

@yesadikusitota
ይህ ትልቅ መንፈሳዊ ቻናል ችግር ቢደርስበት መቆያ አልያም መጠባበቂያ የሚሆነን #መዝገበ ሐይማኖት #የተሰኘ ቻናል ከፍቻለሁ! እናም አብሮነታችሁን join በማለት እንድታሳዩኝ በትህትና እጠይቃለሁ🙏🙏

@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
#ንስሓ_የማያድነው_ኀጢአት

ከእግዚአብሔር ምህረት ቸርነት። ከእመቤታችን በስተቀር ከሰው ኀጢአት አይታጣም።

የዘመናችን የአጥማቅያን ቡድን አድናቂዎች እና ተከታዮች ሳያውቁት እና ሳይመስላቸው አምልኮተ ሰብእ እየፈጸሙ ይገኛሉ። ይህ ደግሞ ንስሓ የሌለው ኀጢአት ነው። ንስሓ የማያስተሰርየው በደል ኑሮ አይደለም፦ የጻድቅ ተከታይ ስለሆነ ጻድቃንን ይዘነጋል የእሱ ጻድቅ ከፊቱ ያለው አያ እንተና ብቻ ነው።

የፈዋሽ ተከታይ ስለሆነ ፈውሰ ነፍስ አያስፈልገውምና። ለፈውስ ደጅ የሚጠናው አቶ እንተናን ነው። የቅዱስ አጥማቂ ቸከታይ ስለሆነ ቅድስና አያስፈልውምና። የካህን ፊት እንዳያይ መተተኞች ጠንቋዮች እያሉ የልብ ጆሮውን ይዘጉበታል። ንስሓቸውን የጨረሱ ፈዋሾች ተከታይ ስለሆነ እነሱን በማገልገል ጊዜውን ያባክናል።

በፍርሀት ልቡናው እንዲርድ ጋኔን ወረረህ አሠረህ ተበተበህ እያሉ መውጫ ቀዳዳ ያሳጡታል። ሳያውቀው ያመልካቸዋል። ምክንያቱም እነሱ ከሌሉ በሕይወት የማይኖር ይመስለዋል። የዛር አድናቂ የልብ ተመጻዳቂ ያደርጉታል። ጻድቅ ሲባል አቶ እንተና ነው ትዝ የሚለው።
የማያድን ለንስሓ የማያበቃ ተከታይነት ይሄ አይደለምን??

አሁን አሁን ክፍት የሥራ ፈጠራ መንገዶች አራት ናቸው፦
#ባህታዊነት#አጥማቂነት#ሰባኪነት#ዘማሪነት ናቸው።

#ማንም ተነሥቶ ስማ ወገን ዓለም ሊናድ ነው ከበረሃ የመጣ መልእክት ነው... ካለ ባህታዊ እንተና ይሆናል። እውነተኛ ነው? ከየትኛው በረሀ? ከየትኛው ገዳም ማለት የለም መከተል ነው እንጂ ማን ያጣራዋል።

#ማንም ተነሥቶ ውጣ ልቀቅ ምናምን ቅብጥርጥር ካለ አጥማቂ እንተና ይሆናል። በዛር ነው? በእግዚአብሔር? መከተል ነው እንጂ ማን ያጣራዋል።

#ማንም ተነሥቶ ጎርነን ባለ ድምጽ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ...ካለ ሰባኪ እንተና ይሆናል። ተምሯል?አልተማረም? መከተል ነው እንጂ ማን ያጣራዋል።

#ማንም ተነሥቶ ያላንተ ለኔ፣ ካመድ ያነሣኸኝ...ካለ ዘማሪ እንተና ይሆናል። ሦስቱን የዜማ ልኮች ጠብቋል?አልጠበቀም? መከተል ነው እንጂ ማን ያጣራዋል።

አያችሁ? በደንባራ በቅሎ ቃጭል ተጨምሮ ሆነና ይነዱን ጀመር። ሰውን የእውር አፍጣጭ የጨለማ ገልማጭ አደረጉት።
ለንስሓ የማያበቃ በደል ይሄ አይደለ?

(#መምህር ገብረ መድኅን እንየው)
@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
“ወዳጄ ሆይ! የትዕቢት መርዝ ተጠራቅሞ አብጦብሃልን? እንኪያስ ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ስለ ወዳጆቹ ሲል አርአያ ገብርን የነሣ ትሑቱ ጌታም ትሕትናን ያስተምርሃል፡፡ የስግብግብነት ትኩሳት አስቸግሮሃልን? ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ደግነትንም ትማራለህ፡፡ የምቀኝነት ብርድ አስቸግሮሃልን? እንኪያስ ወደ ሰማያዊው መዓድ ቅረብ፤ ምህረት ማድረግንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡ ትዕግሥትን የማጣት እከክ ይዞሃልን? እንኪያስ ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ራስን መግዛትንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወትህ ልል ዘሊል ብትሆን ይህን መንፈሳዊ መዓድ ተመገብና ብርቱ ትሆናለህ፡፡ ቆሽሸሃልን? እንኪያስ ወደዚሁ መብልና መጠጥ ቅረብ ብዬ እመክርሃለሁ፤ ንጽሕናንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡”

ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ
@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
#ክህነት_እሳት_በተባለ_በቃለ_እግዚአብሔር_ነጥሮ_የሚገኝ_ማዕረግ_ነው !!!
༺◉❖═──────◉●◉🌹🌹🌹◉●◉──────═❖◉༻
#ክህነት የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ትምህርታዊ ፣ መንፈሳዊ ፣ ሐዋርያዊና ማኅበራዊ አገልግሎት በሚገባ ለመፈጸምንና የዘለዓለም ሕያው ቃል በሆነው በወንጌል ያለሥጋዊ ዋጋና ጥቅም የክህነትን ተልእኮን በብቃት ለመወጣት ነው ።
ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን አሟልቶ በመፈጸም ነፍስና ሥጋን መቀደስ በእግዚብሔርና በሰው ፣ በሰውና በመላእክት ፣ በሰውና በሰው መካከል ያለው ሰላማዊ ግንኙነት እንዳይቋረጥ ተግቶ ማስተማር ።
በኀጢአት የራቀውን በንስሐ አስታርቆ ቀኖና ሰጥቶ ፣ አንጽቶ እንደ ሕጉ ማቁረብ ነው መሥዋዕት እየሠዉ ጸሎት እያደረሱ አምልኮተ እግዚአብሔርን ማከናወን ነው ።
#የክህነት ምንጩ እግዚአብሔር ሲሆን ክህነትን ለመጀመሪያ ጊዜ የሰጠው ለአባታችን ለአዳም ነው ፤ አዳም ከእግዚአብሔር ያገኘውን ሀብተ ክህነትን ተጠቅሞ በገነት መሥዋዕት ያቀርብ ነበር ኋላም በበደለ ጊዜ ደሙን አፍሶ ከፍሬ በለስ ጋር ለውሶ መሥዋዕት በማቅረብ የእግዚአብሔርን ምሕረት ተማጽኗል ። ( ኩፋ 5 ፥ 1 )
#ክህነት በቅድስት ቤተ ክርስቲያን የአገልግሎት ሁሉ ልዕልና ዋልታና ምሰሶ ሲሆን ይኸውም በቅዱስ ወንጌል ትእዛዝ መሠረት ዐላማው በትክክል ሲፈጸም በእግዚአብሔር ዘንድም ሆነ በሰው ዘንድ ያሾማል ፣ ያሸልማል ያስመሰግናል ፤ ያስከብራል (ማቴ 25 ፥ 20 ) ባለሟልና ፈራጅ ያደርጋል እጥፍ ዋጋ ያሰጣል ።
#ክህነት ርኩሱን የሚቀድስ ፤ ስደተኛን ባለርስት የሚያደርግ መውረሻ መቀደሻ ነው መክበሪያ ፣ መወደጃ ነው በክርስቶስ የማዳን ሥራ ተሳታፊ ያደርጋል ‹‹ አማልክት ዘበምድር ›› ለመባል ያበቃል ከሕዝባዊነት አውጥቶ ከመላእክት ያስቆጥራል ስለዚህ ካህናት ከሕዝብ መካከል ለሕዝብ ተመርጠው በሕዝብ ላይ የተሾሙ ምድራውያን መላእክት ናቸው ። ( ዮሐ 10 ፥ 34 ) (መዝ 81 ፥ 6) ( ያዕ 60 ፥ 26 )
#ክህነት ከምድራዊ አባር ቸነፈር ከዕታዊ ኀጢአት ከሥጋዊ መቅሰፍት ብቻ የሚያድን አይደለም ሰማያዊ ጸጋ ምድራዊ ክብር የሚያጎናጽፍ የመንግሥተ ሰማያት ቁልፍ የማዕርጋት ሁሉ ጫፍ ነው ለሰዎች ከተሰጡት ምሥጢራት ትልቁ ምስጢር ክህነት ነው ። ስለዚህም
#ክህነት ምድራዊ ሳይሆን ሰማያዊ ጊዜያዊ ሳይሆን ዘለዓለማዊ ሥጋዊ ሳይሆን መንፈሳዊ ምሥጢር ነው የድኅነት አገልግሎት የሚረጋገጥበት የአምላክ ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም የሚቀርብበት የእሳት ገበታ ፣ የመለኮት ማዕድ የሚስተናገድበት ሰውንና እግዚአብሔርን የሚያገናኝ ትልቅ ሥልጣን ነው በምድርና በሰማይም የማሰርና የመፍታት ሥልጣን ያለው ሰማያዊ ስጦታ ነው ። ( ማቴ 16 ፥ 18 ) ( ማቴ 18 ፥ 18) (1ኛ ቆሮ 4 ፥ 1 ) (1ኛ ቆሮ 5 ፥ 20 )
#ክህነት ምን ያህል ክብር እንዳለው ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ሲናገር ፦ ❝ የካህናት የክነታቸው ሹመት ከወርቅና ከብር ይልቅ የተፈተነ የጠራ ነው ወደ መጋረጃ ውስጥ ይገባል ለመላእክት ያልተገለጠ ሥውር ምሥጢር ሰማያዊ ማዕድ ለካህናት ገለጠላቸው ።❞ በማለት ዘምሯል ።
ወርቅ ከማዕድናት ሁሉ እንደሚበልጥ #ክህነትም ከማዕረግ ሁሉ ይበልጣልና #አንድም ወርቅ በእሳት ነጥሮ እንደሚወጣ ክህነት እሳት በተባለ በቃለ እግዚአብሔር ነጥሮ የሚገኝ ነው ። ( ዮሐ 1 ፥ 52 )

@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
18 K Telegram chanal የሚገዛ እውነተኛ ገዢ በውስጥ መስመር ያናግረኝ
👉መሸጫ ዋጋ 15K

@yesadikusitota
ይህ ትልቅ መንፈሳዊ ቻናል ችግር ቢደርስበት መቆያ አልያም መጠባበቂያ የሚሆነን #መዝገበ ሐይማኖት #የተሰኘ ቻናል ከፍቻለሁ! እናም አብሮነታችሁን join በማለት እንድታሳዩኝ በትህትና እጠይቃለሁ🙏🙏

@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁
ስርዓተ ማሕሌት ዘሣልሳይ ጽጌ በዓለ ቅድስት ሐና
🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃
ነግሥ (የማንኛውም ወርኃ  በዓልና ክብረ በዓል ሥርዐተ ማኅሌት መጀመሪያ)
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።

መልክዓ ሥላሴ
ሰላም ለኵልያቲክሙ እለ ዕሩያን በአካል፤ዓለመክሙ ሥላሴ አመ ሐወፀ ለሣህል፤እምኔክሙ አሐዱ እግዚአብሔር ቃል፤ተፈጸመ ተስፋ አበው በማርያም ድንግል፤ወበቀራንዮ ተተክለ መድኃኒት መስቀል፡፡

ዚቅ
ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሐረገ ወይን፤እንተ በምድር ሥረዊሃ ወበሰማይ አዕፁቂሃ ሐረገ ወይን፤እንተ በሥሉስ ትትገመድ ወታፈራ ለነ አስካለ በረከተ፤ሐረገ ወይን፤ሲሳዮሙ ለቅዱሳን፤ሐረገ ወይን፤ሠርዓ ሰንበተ በቃሉ ወጸገወ ሰላመ ለኩሉ።

ማኅሌተ ጽጌ
ትመስል እምኪ ማርያም ዕለተ ሣልስተ ወራብዕተ፤ዘወለደት ጽጌ ወፀሐየ ዓለም ብርህተ፤ካዕበ (ወካዕበ) ትመስል ሳብዕተ ዕለተ፤እስመ ፈረየት ኪያኪ ተአምረ ግዕዛን ሰንበተ፤ ለእለ በሰማይ ወምድር ዘኮንኪ ዕረፍተ።

ወረብ፦
ትመስል እምኪ ማርያም ዕለተ ሣልስተ ወራብዕተ ትመስል እም/፪/
ዘወለደት ጽጌ ጽጌ ጽጌ ወፀሐየ ዓለም/፪/

ዚቅ
እምኲሉ ዕለት ሰንበተ አክበረ ወእምኲሎን አንስት ማርያምሃ አፍቀረ ከመ ትኩኖ ማኅደረ ለመንፈስ ቅዱስ ወምስጋድ ለኲሉ ዓለመ።

ማኅሌተ ፅጌ፦
ከመ ታቦት ሥርጉት በወርቀ ዓረብ ወተርሴስ፤በድንግልና ማርያም ሥርጉተ ሥጋ ወነፍስ፤ ተአምረ ነቢር አርአይኪ በቤተ መቅደስ፤ኢያቄም ወሐና ቀንሞስ ቀናንሞስ፤ እምዘ ጸገዩኪ ለጳጦስ በዓመት ሠላስ

ወረብ
እምዘ ጸገዩኪ ለጳጦስ በዓመት ሠላስ  ኢያቄም ወሐና ቀንሞስ ቀናንሞስ/፪/
ተአምረ ነቢር አርአይኪ ተአምረ ነቢር አርአይኪ በቤተ መቅደስ/፪/

ዚቅ
ሰአሉ ለነ ኢያቄም ወሐና ዘፈረይክሙ በቅድስና መሶበ ወርቅ እንተ መና

ማኅሌተ ፅጌ፦
እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ፤አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፤ንዒ ርግብየ ትናዝዝኒ እምላህ፤ወንዒ ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፤ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ።

ወረብ፦
እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ/፪/
ንዒ ርግብየ ወንዒ ሠናየትየ ምስለ ገብርኤል ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ/፪/

ዚቅ
ዕፀ ጳጦስ ይዕቲ እንተ በአማን ለእንተ ይብልዋ ቅድስተ ቅዱሳን ንዒ ርግብየ ሠናይት ወይቤላ መልአክ ተፈስሒ ፍስሕት ቡርክት አንቲ እምአንስት

ማኅሌተ ፅጌ፦
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቄ ባሕርይ ዘይኀቱ፤ዘተጽሕፈ ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፤አክሊለ ጽጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀጸላ መንግሥቱ፤አንቲ ኩሎ ታሰግዲ ሎቱ ፤ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ።

ወረብ፦
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ ዘየሐቱ እምዕንቄ ባሕርይ/፪/
አክሊለ አክሊለ ጽጌ ማርያም ቀጸላ መንግሥቱ ለጊዮርጊስ/፪/

ዚቅ
ይእቲ ተዓቢ እምአንስት እሞሙ ለሰማዕት ወእኅቶሙ ለመላእክት መድኃኒቶሙ ለነገሥት አክሊል ንጹሕ ለካህናት ብርሃኖሙ ለከዋክብት

ሰቆቃወ ድንግል
ተንሥኢ ወንኢ ሌዋዊት ሐና፤ትጼውዓኪ ወለትኪ ከመ ትርአዪ ኃዘና፤ እምርስትኪ ወፅአት ወተሰደት በድክትምና፤ትበኪ እምዋዕየ ሐጋይ ኃጢኣ በፍና፤ ሕፍነ ማይ ዘታሰትዮ ለፅሙዕ ሕፃና

ወረብ፦
ተንሥኢ ወንኢ ሌዋዊት ሐና ተንሥኢ ወንኢ/፪/
ትጼውዓኪ ወለትኪ ኃዘና ከመ ትርአዪ /፪/

ዚቅ፦
ኢሀለዉ አሜሃ አቡኪ ወእምኪ፤ከመ ይርአዩ ድክትምናኪ፤ወይስምዑ ገዓረኪ፤እስመ ሞቱ እምንእስኪ ወኃደጉኪ ባሕቲተኪ

ዓዲ (ሌላ) ዚቅ፦
አመ ወጽአት በፍርሃት እምሀገረ ዳዊት ዘይሁዳ በብሥራተ መልአክ ዕንግዳ ኢረከበት ማየ በፍኖት ዘታስትዮ ለወልዳ

መዝሙር፦
ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፣ወመኑ መሐሪ ዘከማከ ምስለ ኖኅ ኪዳነ ዘዓቀምከ፤  ወመኑ መሐሪ ዘከማከ ምስለ ኖኅ ኪዳነ ዘአቀምከ ለደቂቀ እስራኤል መና ዘአውረድከ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጎከ፤ወመኑ መሐሪ ዘከማከ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጎከ ወስነ ገዳምኒ ምስለ ቅዱሳኒከ ፤ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ ወከመ ወሬዛ ኀይል መላትሒሁ፤ ጉርዔሁ መዓርዒር አምሳሉ ዘወይጠል፤  ወመኑ መሐሪ ዘከማከ ሰማይ ወምድረ ዘአንተ ፈጠርከ ፀሐየ ወወርኃ ዘአስተዋደድከ፤ወመኑ መሐሪ ዘከማከ  በከዋክብት ሠማይ ዘከለልከ ወበጽጌያት ምድረ አሠርጎከ፤  ወመኑ መሐሪ ዘከማከ ቀደሳ ወአክበራ አዕበያ ለሰንበት ወአልዓላ እምኩሉ ዕለት፤ማ፦ ወመኑ መሐሪ ዘከማከ፥ ወኩሉ ይሴፎ ኪያከ።

አመላለስ

ወመኑ መሐሪ ዘከማከ/፪/
ወኩሉ ይሴፎ ኪያከ ወኩሉ ይሴፎ ኪያከ/፪/

@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
@mezigebekidusan
+ በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ +

ይድረስ ለተከፋኸው ወንድሜ
መኖር ለደከመህ ፣ ሕይወት ለታከተህ ፣ የሚሰማህ ላጣኸው ፣ የሚረዳህ ሰው ላላገኘኸው መከረኛው ወዳጄ!

ከሞት ውጪ ሌላ መፍትሔ አልታይ ካለህ የአንተ ቢጤ መከረኞቹ ጳውሎስና ሲላስ እስር ቤት ውስጥ ሆነው እንዲህ ይሉሃል::

"በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ" ሐዋ. 16:28

አውቃለሁ ዙሪያው ገደል ሆኖብሃል:: ምነው ባልተፈጠርሁ እስክትል ድረስ ተጨንቀሃል::
ግን ይህ ስሜት በአንተ አልተጀመረም:: ሰው ሆኖ ተፈጥሮ ኑሮ ያልመረረው ማን አለ? መሞት ያልተመኘስ ማን አለ?

ሞት ያማረህ አንተን ብቻ መሰለህ?

" ስለ ምን ከማኅፀን አወጣኸኝ? ዓይን ሳያየኝ ምነው በሞትሁ" ያለውን ጻድቅ ኢዮብ አልሰማህም? (ኢዮ. 10:18)

"ከአባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰድ" ብሎ እንዲሞት የለመነውን ኤልያስን አላየኸውም? 1ነገሥ. 19:4

ዮናስንስ "አሁንም፥ አቤቱ፥ ከሕይወት ሞት ይሻለኛልና እባክህ፥ ነፍሴን ከእኔ ውሰድ፡ አለው" ሲል አልሰማኸውም? (ዮናስ 4:3)

ወንድሜ እመነኝ ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን መኖር ያላስጠላው ሰው በታሪክ ፈልገህ አታገኝም::

ሞት ሞት የሸተተው ልቡ የተሰበረ ብዙ ነው:: አንተ ላይ ብቻ የደረሰ ልዩ ፈተና የለም:: "ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል" ይላል መጽሐፍ:: 1ኛ ቆሮ. 10:13

ምናልባት የልብህን መሰበር የኀዘንህን ጥልቀት አይቶ ምቹ ጊዜ አገኘሁ ብሎ ራስህን እንድትጎዳ ሰይጣን ሊገፋፋህ ይችላል:: እንዴት እንዲህ ዓይነት ሃሳብ በልቤ ሊመጣ ቻለ ብለህ አትረበሽ:: ሰይጣን ይህንን ክፉ ሃሳብ ላንተ ብቻ ሳይሆን ለክርስቶስም አቅርቦለታል::

"የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ፥ ወደ ታች ራስህን ወርውር" ብሎ ክርስቶስን እንኳን [ማንነቱን ሳያውቅ] ራሱን እንዲወረውር ሊገፋፋው የሞከረ ደፋር ነው:: የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ሰው ግን ራሱን አይጎዳም:: "ጌታ አምላክህን አትፈታተነው" "ሒድ አንተ ሰይጣን" ብለህ ሰይጣንን ገሠፀው::

ሰይጣን ክርስቶስን "ከሕንፃ ጫፍ በመወርወር የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህን አሳይ" ሲለው ክርስቶስ ሰይጣንን ሒድልኝ ብሎ በመገሠጹ በክብር ወደ ሰማይ ዐርጎ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ::
ወንድሜ ሆይ አንተም ሰይጣንን አትስማው ሃሳቡ ራስህን ጎድተህ ከፈጣሪህ እንድትጣላ ሊያደርግህ ነው:: ሰይጣንን ከገሠጽከው በእግዚአብሔር ቀኝ ከበጎቹ ጋር ትቆማለህ::

አሁን ያለህበት ችግር ያልፋል:: የሚሰማህ ክፉ ስሜት መቼም የማይለወጥ አይምሰልህ:: ኀዘኑም ፣ ብቸኝነቱም ፣ ተስፋ ቢስነቱም ያልፋል:: ጨለማው ይነጋል:: የተዘጋው በር ይከፈታል:: ችግሩ ሲፈታ አንተ ከሌለህ ግን ትርጉም የለውም::

ስለዚህ ለሚፈታ ችግር የማይቀለበስ ውሳኔ አትወስን:: ራስን ማጥፋት ከጊዜያዊ ችግር ለመሸሽ ሲሉ ዘላቂ ችግር ውስጥ መግባት ነው:: ጊዜያዊ ሕመምን ለማስታገስ የዘላለም ሕመምን ለምን ትመርጣለህ? "የሞተ ተገላገለ" ሲሉ ሰምተህ እንዳትታለል ሞት ዕረፍት የሚሆነው ራሱ እግዚአብሔር ሲጠራህ ብቻ ነው::
"እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ" ያለው ጌታ ሳይጠራህ ራስን ማጥፋት የዘላለም ስቃይ ያመጣል::

ወዳጄ "በራስህ አንዳች ክፉ አታድርግ"

የሕይወትህን ዋጋ ታውቅ ይሆን? አንተ እኮ የእግዚአብሔር ልጅ ለአንተ ሲል የሞተልህ ነህ:: ሊፈውስህ የቆሰለ ፣ ሊያከብርህ የተዋረደ ፣ ሊያረካህ የተጠማ ፣ ሊያለብስህ የተራቆተ ለአንተ እኮ ነው::
ክርስቶስ ስለ አንተ ሞቶአል:: አንተን ግን የጠየቀህ እንድትሞትለት ሳይሆን እንድትኖርለት ነው::
ለሞተልህ አምላክ እንዴት መኖር ያቅትሃል?

ወዳጄ ሆይ ሰውነትህ በአምላክ ደም የተገዛ ክቡር ሰውነት ነው:: አካልህ "አንተ" እንጂ "ያንተ" አይደለም:: "በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ" ይላል

ስለዚህ በከበረ የእግዚአብሔር ልጅ ደም የተገዛ ሰውነትህን ለሰይጣን በርካሽ አትሽጠው:: አትግደል የሚለው ሕግ ራስህንም ይጨምራል:: ቤተ መቅደስ የሆነ ሰውነትህን ለማፍረስ አታስብ::
"ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ" 1ኛ ቆሮ. 3:17

ሰዎች አስቀይመውህ ይሆን?

"አሳያቸዋለሁ ፤ ስሞት የእኔን ነገር ይገባቸዋል" ብለህ በሰዎች ተቀይመህ ራስህን አትጉዳ:: እመነኝ ብትሞት ሰዎች ከሳምንት በላይ አያስታውሱህም:: ለሕይወትህ ዋጋ ያልሠጡ ሰዎች ለሞትህ ዋጋ አይሠጡም:: ፈጥነውም ይረሱሃል:: ለሚረሱህ ሰዎች ብለህ የማይረሳህን አምላክ አታሳዝን:: ሰው ስለ አንተ ግድ የለውም እግዚአብሔር ግን የራስህን ቁጥር ሳይቀር በቁጥር ያውቀዋል :: እንኳንስ ራስህን ልትጎዳ አንዲት ጸጉር እንኳን ከአንተ እንድትወድቅ አይፈልግም::

እግዚአብሔርን በኃጢአት ብታሳዝነው እንኳን ኖረህ ንስሓ እንድትገባ እንጂ እንድትሞት አይፈልግም:: አባትህ ነውና ከእርሱ ጋር ባትሆንም እንድትኖር ይፈልጋል:: በምሳሌ ልንገርህ :-

ሁለት ሴቶች አንድን ሕፃን "የኔ ልጄ ነው" ብለው እየተከራከሩ ጠቢቡ ሰሎሞን ፊት ቀረቡ:: ጠቢቡ ሰሎሞን ሰይፍ አመጣና "ልጁን ቆርጬ ለሁለት ላካፍላችሁ" አላቸው:: አንደኛዋ ሴት "እሺ እንካፈል" ስትል እውነተኛዋ እናት ግን "ልጄ ከሚሞት እርስዋ ትውሰደው" አለች:: እናት መሆንዋም በዚህ ታወቀ::

ወዳጄ ያንተም ኑሮህ ከእግዚአብሔር ጋር ላይሆን ይችላል:: ዓለም የራስዋ አድርጋህም ይሆናል:: በሱስ ውስጥ ትዘፍቀህ ፣ እንደ ሶምሶን በደሊላ እቅፍ ፣ እንደ ዴማስ በተሰሎንቄ ውበት ተማርከህ ይሆናል:: እግዚአብሔር ግን አባትህ ነውና ሞትህን አይፈልግም::

"ልጄ ከሚሞት እርስዋ ትውሰደው" እንዳለችው እናት ፈጣሪህ ከነኃጢአትህም ቢሆን እንድትሞት አይፈልግም:: ከእርሱ ጋር ባትኖርም መኖርህን ይፈልጋል:: "የሟቹን ሞት አልፈቅድምና፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ስለዚህ ተመለሱና በሕይወት ኑሩ" ሕዝ. 18:32

የይሁዳ ኃጢአቱ ጌታውን መሸጡ አልነበረም:: ራሱን መግደሉ ነው:: እግዚአብሔር የሚያዝነው ከበደልህ በላይ በእርሱ ተስፋ ቆርጠህ ራስህን ስትጎዳ ነው::

ወዳጄ የአንተን መኖር የሚፈልጉ ብዙ ናቸው:: ፈጣሪ ወደዚህች ዓለም ያለ ምክንያት አላመጣህም:: በአንተ አለመኖርም የሚጎድል ነገር አለ:: አንተን የሚመስል ሌላ ሰው አልፈጠረምና ለዚህ ዓለም አንተን የሚተካ የለም:: በክብር ወደዚህ ዓለም ያመጣህ አምላክ በክብር ወደራሱ እስኪወስድህ ድረስ "በራስህ ላይ ክፉ ነገር አታድርግ"

"የወኅኒውም ጠባቂ ከእንቅልፉ ነቅቶ የወኅኒው ደጆች ተከፍተው ባየ ጊዜ፥ እስረኞቹ ያመለጡ መስሎት ራሱን ይገድል ዘንድ አስቦ ሰይፉን መዘዘ።
ጳውሎስ ግን በታላቅ ድምፅ፦ ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ፡ ብሎ ጮኸ" ሐዋ. 16:27-28

ይህ ሰው እስረኛ ያመለጠ መስሎት ራሱን ሊያጠፋ ሲል ጳውሎስ "ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ" አለው::

ወዳጄ አንተስ ተስፋ የቆረጥኸው ምን ያመለጠ መስሎህ ነው?
2024/09/24 20:34:32
Back to Top
HTML Embed Code: