Telegram Web Link
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት አዲስ ለሚሰራው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን መሠረት ባርከው አኖሩ !
••
ቅዱስነታቸው ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ከድሬዳዋ ከንቲባ ከአቶ ከድር ጁሀር ጋር በመሆን በድሬዳዋ ከተማ ኢንዱስትሪ መንደር አዲስ ለሚሰራው የመካነ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ ወልደታ ለማርያም ወአቡነ ሳሙኤል ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን የመሠረተ ደንጊያ አኑረዋል።
••
በተያያዘም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ጋር በመሆን በድሬዳዋ መልካ ጀብዱ ጌቴሴማኒ መካነ ቅዱሳን አቡነ አረጋዊ ወአርሴማ የሴቶች ገዳም ጉብኝት አድርገዋል።
••
ቅዱስነታቸው ለገዳሙ መነኮሳይያትና በገዳሙ ለሚያድጉ ሕፃናት ሰፊ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል ።
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
👉 ሴት በወር አበባዋ ጊዜ መጸለይ ትችላለች?
👉​​ ግለ አውናን / ሴጋ /ማስተርቤሽን/ የፈጸመ ሰው ተክሊል ማግባት ይችላልን?
👉 በሱባኤ ወቅት ህልመ ሌሊት (ዝንየት) ቢመታን ምን እናደርጋለን?
👉 ሕልመ ሌሊት በራሱ ኃጢአት ነውን?
👉 ሕልመ ሌሊት በምን ይከሰታል?
👉 ከዝሙት አጋንንት እና ከዝንየት በተጨማሪ በሕልመ ሌሊት የሚፈትነን አጋንንት የትኛው ነው?
👉 የሕልመ ሌሊት መፍትሔ ምንድን ነው?

ለእነዚህ ሁሉ መልስ ለማግኘት ይቀላቀሉ
Channel link
@tewahdo_haymanotea
#በመዲናችን_በአዲስ_አበባ__የቅዱስ_ገብርኤል_ በዓል_የሚከበሩባቸው  #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩) ፠ (መ.መ.ገ.) መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤ በ1889 ዓ.ም. የተመሠረተ፤
፠ አስኮ ቅዱስ ገብርኤል፤
፠ ጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል፤
፠ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል (ብሥራተ ገብርኤል)
፭) ፠ ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል
፠ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ኮተቤ ደብረ ልዑል ዳግማዊ ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል በ.ክ.
፠ ደብረ ገነት ፉሪ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት አርሴማና አቡነ አዳም ቤ.ክ.
፲) ፠ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ መካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ አለም ባንክ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ አየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፲፭) ፠ ደብረ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ጋራ ኦዳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ አንቆርጫ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ጉራራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፠ ፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፳፠ አቃቂ ፈለገ ግዮን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ኤረር ጎሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ቦሌ ሃራብሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ቦሌ ቡልቡላ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፳፭) ፠ ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ (የቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. በድርብነት በውስጥ አለ)
፠ ቦሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፠ ቦሌ መንበረ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ ገሊላ አማኑኤል ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፴) ፠ ጀሞ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት አርሴማ ቤ.ክ.
፠ አቃቂ ጃቲ መካነ ሕይወት ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፠ ቃሊቲ መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ የካ አባዶ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ኮልፌ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅዱስ ገብርኤል
፴፭) ፠ ኮልፌ ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤ/ክ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ. (አዲሱ ሚካኤል) (በድርብነት ይከብራል)
፠ ካራ ቆሬ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ድልበር መካነ ጎልጎታ መድኀኔዓለም (በድርብነት ይከብራል)
፠ አዲስ አምባ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና ደብረ ፍስሐ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ (አዲስ ሰፈር)
፵)፠ ደብረ ቀራንዮ መድኀኔ ዓለም ስር የሚገኘው ሙት አንሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ መንበረ ልዑል ገብርኤልና ማርያም ቤ.ክ.፤
፠ አየርጤና ደብረ ብሥራት ገብርኤልና አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ.ክ.
፠ ቱሉ ዲምቱ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፠ ቀበና ምዕራፈ ጻድቃን አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅ/ገብርኤል ቤ.ክ.
፵፭) ፠ መጠሊ ደብረ አሮን ፍልፍል ዋሻ ቅዱስ ገብርኤልና አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ.ክ.
፠ ቂሊንጦ ደብረ ብሥራት ገብርኤልና ማርያም፤
፠ ደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)፡፡
፠ አንቀጸ ምሕረት (ራስ ካሣ) ቅዱስ ሚካኤል፤ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ ዕንቊ ልደታ ለማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል)
፶) ፠ ቦሌ ቡልቡላ ድብረ መድኀኒት መድኀኔ ዓለም፤ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በድርብነት ይከብራል)
፠ ፈጬ ደብረ ገነት ቅድስት ድንግል ማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል)
፶፬) ፠ ብሥራተ ወንጌል ቅድስተ ማርያም ቤ.ክ.፤ (በድርብነት ይከብራል)
#በሃገራችንና_በዓለም_አቀፍ__በዓላቸው_የሚከበሩባቸው_ጥንታውያን  #፰   #ገዳማትና_አድባራት፡፡
፩) ቁልቢ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል
፪) ወይቅን ቅዱስ ገብርኤል (ቆላ ተንቤን)
፫) ክብራን ገብርኤል
፬) ቦሎ ገብርኤል (መርሐ ቤቴ)
፭) ጎንደር አቡን ቤት ገብርኤል
፭) ደሴ ገብርኤል
፮) ናዝሬት ገብርኤል
፯) መቀለ ገብርኤል
፰) ባሕር ዳር ዐባይ ማዶ ገብርኤል
፱) ሐዋሳ ገብርኤል
፲) ድሬደዋ ሳባ ገብርኤል
፲፩) ሆለታ ደብረ ኤዶም ገብርኤል
  
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
እንኳን ለቅዱስ ቂርቆስ ወኢየሉጣና ለሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ)

#ሐምሌ_፲፱#በዓለ_ቅዱስ_ገብርኤል_ወቅዱስ_ቂርቆስ_ወቅድስት_ኢየሉጣ_ወሥርዐተ_ማኅሌት፡፡
  በቀጨኔ ደ/.ሰ/መድኀኔ ዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል.ቤ.ክ የፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ

    ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት

✼ ነቢዩ ዳንኤል “ዐይኖቼንም አነሣሁ” አለና አስከትሎ “እነሆም በፍታ የለበሰውን ጥሩም የአፌዝን ወርቅ በወገቡ ላይ የታጠቀውን ሰው አየሁ፡፡
አካሉም እንደ ቢረሌ ይመስል ነበር፤ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ ነበረ፤ ዐይኖቹም #እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም #ድምፅ እንደ ብዙ #ሕዝብ ድምፅ ነበረ፡፡… ይህንንም ታላቅ ራእይ አየሁ፤ ኃይልም አልቀረልኝም፤ ክብሬም ወደ ውርደት ተለወጠብኝ #ኃይልም አጣሁ፡፡ የቃሉንም ድምፅ ሰማሁ፤ የቃሉን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ደንግጬ በምደር ላይ #በግምባሬ_ተደፋሁ” አለ፡፡(ዳን.10፥5-9) ነቢዩ ዳንኤል እንዲህ ብሎ የተናገረው የመላእክትአለቃ የቅዱስ #ገብርኤልን አስፈሪ ግርማ በተመለከተ ጊዜ ነበር፡፡
✤ ገብርኤል የሚለው ቃል የሁለት ቃለት ጥምር ነው እነዚህም #ገብር እና #ኤል ሲሆኑ ትርጕማቸውም ገብር #አገልጋይ ማለት ሲሆን ኤል ማለት ደግሞ አምላክ ማለት ነው፤ በተገኛኘ ገብርኤል ማለት #የአምላክ_አገልጋይ /የእግዚአብሔርን ልጅ የሚመስል የአምላክ አገልጋይ ማለት ነው።

“እነሆ ከዋነኞቹ አለቆች” አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ”(ዳን.10፥13) ብሎ በተናገረው ንግግሩ በመላእክት ላይ የተሾሙ ሌሎች አለቆች እንዳሉ ማስተዋል እንችላለን፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በቅዱሳን መላእክት ዘንድ ስላሉት ነገዶች ሲገልጽ “… በሰማይ ያለውን በምደር ያለውን የሚታየውንና የማይታየውን መናብርትም ቢሆኑ አጋእዝትም ቢሆኑ መኳንንትም ቢሆኑ ቀደምትም ቢሆኑ ሁሉም በእጁ ሆነ፤ ሁሉም በእርሱ ለእርሱ ተፈጠረ” (ቈላ.1፥16) በማለት ይዘረዝራቸዋል፡፡ ከዚህ ተነሥተን መላእክት በተለያዩ ዐበይት ነገዶች የተከፈሉና ለእያንዳንዱም ነገድ የራሱ የሆነ አለቃ እንዳለው ማስተዋል እንችላለን፡፡
ቅዱስ ገብርኤልም ከእነዚህ ዐበይት የመላእክት ነገዶች መካከል አንዱ በሆነው #እርባብ በሚባለው ዐቢይ ነገድ ላይ የተሾመ ሲሆን ከ100ው ነገደ መላእክት መካከል ከበታቹ የሚመራቸው ዐሥር ነገደ መላእክት አሉት፤ ከተማቸውም በሰማየ #ራማ ነው፡፡

✼ ቅዱሳን መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ፊት አውራሪነት የሰው ልጆች ጠላት የሆነውን ዲያብሎስን ተዋግተው ድል ከመንሳታቸው አስቀድሞ ቅዱስ ገብርኤል፣ እንደ አምላክ ሊመለክ የወደደውን ሳጥናኤልን በመቃወም ‹‹#ንቁም_በበህላዌነ_እስከ_ንረክቦ_ለአምላክነ - “አይዞአችሁ ፈጣሪያችን እስክናገኘው፣ እስክናውቀው ድረስ በያለንበት ጸንተን እንቁም፡፡” (አክሲማሮስ ገጽ.35) በማለት
#መላእክትን_ያረጋጋ_መልአክ_ነው፡፡ በተወዳጁ መልአክ በቅዱስ ሚካኤል መሪነት የሰው ልጆች ጠላት የሆነውን ዲያብሎስን ተዋግተው ድል እንዲያደርጉ ወደ ጥልቁ እንዲጣል አድርጓል ራእ12፥7፤ ነቢዩ ኢሳይያስ በሰማያት የሳጥናኤል ትዕቢትና ውድቀት ምን እንደሚመስል ሲጽፍልን “አንተ በንጋት የሚወጣ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! ወደ አሕዛብ መልእክትን የላክ አንተሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቀጠቀጥህ! አንተም በልብህ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደረጋለሁ፤… በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ ዛሬ ግን ወደ ሲኦል ትወድቃለህ፤ ወደ ምድር ጥልቅም ትወርዳለህ” (ኢሳ.1416) በማለት ገለጠልን፤ ወደ ምድር የጣሉት በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል  እና በቅዱስ ገብርኤል  መሪነት   ነበር፡፡

✼ ቅዱስ ገብርኤል ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ከሊቃነ መላእክት አንዱና በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው ብሏል ሉቃ 1፥19፤ ታላቁ ነቢይ ሄኖክም ስለ ነገረ
መላእክት በተናገረበት አንቀጽ እንዲህ ሲል መስክሯል ‹‹በአበቦች ላይ በገነትም በጻድቃን ላይ #በኪሩቤልም ላይ የተሾሙ ከከበሩ መላእክት አንዱ #ገብርኤል ነው፡፡›› ሄኖክ 6፥7፤ ‹‹በሦስተኛውም በመላእክት ሁሉ ላይ የተሾመ ቅዱስ ገብርኤል ነው››ሄኖክ 10፥14 እያለ የመልአኩን ክብር ተናግሯል፡፡

ቅዱስ ገብርኤል ቅዱሳን ይሆኑ ዘንድ ለተጠሩት መንፈሳዊ እውቀቱን የሚያካፍላቸው መልአክ ብቻ አይደለም፤ ለእግዚአብሔር በመገዛታቸው ምክንያት ከአላውያን ገዢዎች ከሚደርስባቸው መከራም የሚታደጋቸው መልአክም ነው፡፡ ነገር ግን ያደረጋቸው ተዓምራቶች በመጽሐፍ ቅዱስ፣ በመልክኡ፣ በድርሳኑ፣ በገድሉ፣ በተዓምሩ የተጻፉ ቢሆንም ሐምሌ 19 እና ታኅሣሥ 19 ያደረጋቸውን ተራዳኢነት  ፡-

✤✤✤ ሐምሌ 19 ቀን ሕፃኑ ቅዱስ #ቂርቆስና እናቱ ቅድስት #እየሉጣ በሰማዕትነት መከራ የተቀበሉበት፤ ሊቀ መላእክት  ቅዱስ #ገብርኤል ደግሞ #ከእቶን እሳት ያዳናቸው እለት ነው::
✤✼፠ #ታኅሣሥ_19 አናንያና(ሚሳቅ)፣ አዛርያ(ሲድራቅ) እና ሚሳኤል(አብደናጎ) ያዳናቸው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ አናንያና(ሚሳቅ)፣ አዛርያ(ሲድራቅ) እና ሚሳኤል(አብደናጎ) የፋርስ ባቢሎን ንጉሥ የነበረው ናብከደነፆር በዱራ(አዱራን) በሚባል ስፍራ ላይ ላቆመው ጣዖት አንሰግድም በማለታቸው ወደ እቶን እሳት እንዲጣሉ አድርጓቸዋል ፤ በመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት ግን ከእቶን እሳቱ የልብሳቸው ዘርፍ እንኳን እሳት ሳይነካው ድነዋል፡፡ (ይህንን በዓል የምናከብረው ታኅሣሥ 19 ስለሆነ ታሪኩን በስፋት ለመረዳት የታኅሳስ 19 ስንክሳርን ወይም የታኅሣሥ ወር ልጥፈችንን ወደ ሃሏ  በመመለስ ይመልከቱ ፡፡)
✤ ቅዱስ #ቂርቆስ እድሜው የሦስት ዓመት ሳለ እናቱ ቅድስት እየሉጣ ከሮሜ ወደ ሌላ ሃገር ሸሽታ ይዛው ሄደች በዚያም የሸሸችውን መኮንኑን አገኘችው። የሚያውቋትም ሰዎች ሸሽታ እንደመጣች ስለተረዱ ለመኮንኑ ነገር ሰሩባት። መኮንኑም ቅድስት አየሉጣን አስጠራትና ስለ አምልኮ ጠየቃት። ቅድስት ኢየሉጣም መኮንን ሆይ፡ እድሜው ሦስት አመት የሆነው ሕፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እርሱን ጠይቅ አለችው። መኮንኑም ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ወደ አለበት ጭፍራውን ልኮ ወደ እርሱ አስመጣው ሕፃኑንም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ሕፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው። ሕጻን ቅዱስ ቂርቆስም መለሰለት እንዲህም አለው። አዎ እኔ በጣም ደስተኛ ነኝ ደስታየም ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ኀዘንና ለቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው፤ መጽሐፍ ቅዱስም ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏልና አለው። እግዚአብሔር አምላክ ኃይልንና ንግግርን ሰጥቶታልና በዚያ ለተሰበሰቡት ሰዎች እስኪደነግጡ ድረስ ብዙ ተናገረ። ሕፃን ቅዱስ ቂርቆስም ንጉሱን መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሳ አደነቁ። መኮንኑም በአፈረ ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ስቃይ፡ ታላላቆች አንኳ የማይችሉትን ታላቅ አስጨናቂ የሆነ ስቃይን አሰቃየው። እናቱ ቅድስት እየሉጣንምከእርሱ ጋር እንደ እርሱ በጣሙን አሰቃያት። እግዚአሔብሔር ግን ያለ ምንም ጉዳት ያነሳቸው ነበር። ብዙዎች አህዛብም ይህን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት አምነው በሰማእትነት ሞቱ የሰማእትነትንም አክሊል ተቀበሉ። በሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ላይም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት። ታላላቅ ድንቅ ተአምራቶችንም ያደርግ ነበር። ብዙዎች በሽተኞችንም ያድናቸው ይፈውሳቸው ነበር

። ይህንን ያየ መኮንን በታላቅ የነሃስ ጋን ውስጥ ውሃ ጨምረው በእሳት ያፈሉት ዘንድ አዘዘ። የፍላቱም ድምጽ እንደ ክረምት ነጎድጓድ ሆነ ድምጹም በጣም ያስተጋባ ነበር። ይህን ያየችና የሰማች እናት ቅድስት እየሉጣም ፍርሃትና የሃይማኖት ጉድለት ታየባት። ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን እናቱ ቅድስት እየሉጣን ሁኔታዋን አይቶ ወደ አምላኩ እግዚአብሔር ጸለየ። ያን ጊዜ ልዑል እግዚአብሔር ልቧን ወደ ሰማይ አሳርጎ ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁ የብርሃን ማደሪያዎችን አሳያት። ቅድስት እየሉጣም እንደገና በሃይማኖቷ ጸናች። እግዚአብሔር አምላኳንም አመሰገነችው። ልጇን ሕፃኑን ቅዱስ ቂርቆስንም ልጄ ሆይ አንተ ከእንግዲህ አባቴ ነህ እኔም ልጅህ ነኝ አለችው። ቅድስት እየሉጣም ለልጇ ያች የተወለድክባት እለት ቀኗ የተባረከችና የተቀደሰች ናት አለችው። የመኳንንቱ ጭፍሮችም እሳት ወደ አለበት ጋኖች ውስጥ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱን ቅድስት እየሉጣን በጨመሯቸው ጊዜ የውሃው ፍላት ወደያውኑንቀዘቀዘ። ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና። ይህን ያየ መኮንን ሥጋቸው ተቆራርጦ እስከሚወድቅ ድረስ በመቃጥን ውስጥ አድርገው አንዲጎትቷቸው አዘዘ። ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል አዳናቸው። መኮንኑም በታላቅ ስቃይ ያሰቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው። በዚህን ጊዜ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስን አረጋጋው አጽናናው። ስሙን ጠርተው መታሰቢያ ለሚያደርጉለትም በረከትን እንደሚያገኝ ቃል ኪዳን ሰጠው ። እግዚአብሔር አምላካችን የሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት ኢየሉጣን በረከታቸውንና ረድኤታቸውን ያድለን አሜን።

ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት ኢየሉጣ በእግዚአብሔር ቸርነት በቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት በእሳት ከመጣል በንፍር ውሃ ከመለብለብ ከዳኑ በኋላ እለስክንድሮስ መከራውን ፈርተው ይመለሳሉ ብሎ በሀብለ ሰናስል እያሰረ በችንካር እየቸነከረ ሲያሰቃያቸው ቆየ፡፡ የማይሆንለት ሲሆን እጅ እግራቸውን አስሮ ከዝግ ቤት አስቀመጣቸው፡፡ ጌታም የመከራቸውን ጽናት የትዕግስታቸውን ብዛት አይቶ ከመከራ ሊያሳርፋቸው ሽቶ በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ፤ በመጣ ጊዜ “ሰላም ለከ ኦ ፍቁርየ ቂርቆስ” ወዳጄ ቂርቆስ ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን፤ ብሎ ሠላምታ ከሰጠው በኋላ የመከራህን ጽናት፣ የትዕግስትህን ብዛት አይቼ ቃል ኪዳን ልገባልህ ነው።” “ዘመጠነዝ ገድለ ተጋዲልየ ምንተኑ ትዔስየኒ” በሕፃንነቴ ይህን ያህል ተጋድዬ የምትሰጠኝ ምንድነው?” አለው። “አዐሥየከ ዘሀሎ ውስተ መልብከ” በልብህ ያለውን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው። እንኪያስ በስሜ ቤተ ክርስቲያን ከታነጸበት ረሃብ፣ ቸነፈር፣ የሰው በሽታ፣ የከብት እልቂት፣ የእኅል የውሃ ጥፋት፣ አይሁን አለ። ጌታም ይሁንልህ በማለት ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡ ደግሞም “ኢትቅብር ሥጋየ በዲበ ምድር” ሥጋዬ በምድር አይቀበር አለው። “አልቦ ዘይፈደፍደከ ዘእንበለ መንበረ መንግሥትየ ወማርያም ወላዲትየ ወዮሐንስ መጥምቅየ” (ከመንበረ መንግስቴ፣ ከማርያም እናቴ ከዮሐንስ መጥምቅም በቀር በመንግሥተ ሰማያት የሚበልጥህ የለም።)
“ወዓዲ ከመ ኢይስማን ሥጋከ ዲበ ሠረገላ ኤልያስ አነብረከ”
(ሥጋህን እንዳይፈርስ በኤልያስ ሠረገላ አኖርልሃለሁ) ብሎ ተስፋውን ነግሮታል። እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ በመኮንኑ በሰይፍ ጥር ፲፮ በሰማዕትነት ያረፈች ሲሆን ቅዱስ ቂርቆስን ግን ተመለስ ቢለው አልመለስም እምነቴንም አልክድም ባለው ጊዜ ሰይፍ ጃግሬውን ጠርቶ በጥር ፲፭ አስገድሎት ሰማዕትነትን ተቀብሏል፡፡ የእናቱ የቅድስት ኢየሉጣ መታሰቢያዋ ዕለት በየወሩ በ፲፮ እመቤታችን ቃል ኪዳን በተቀበለችበት ቀን በሚታሰብበት የቅድስት ኪዳነ ምህረት ቀን ይታሰባል።
የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ምልጃና ጸሎት፤ የቅዱስ ቂርቆስና የቅድስት ኢየሉጣ በረከታቸው ቃል ኪዳናቸው ይድረሰን በእውነት ይጠብቀን ለዘለዓለሙ አሜን፨

@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
Audio
ክፉና በጎ የሚያሳውቀው ዛፍ

Size:-22.6MB
Length:-1:04:45

   በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
2024/09/23 20:17:42
Back to Top
HTML Embed Code: