Telegram Web Link
ረመዳን 17
የበድር ጦርነት ከነፍስ ፍላጎቶች በላይ የማህበረሰቡ የመብት ጥያቄዎች የተረጋገጡበት፤ ተበዳይ ወደ ፈጣሪው ጮክ ብሎ የተጣራበት፣ እውነተኞች ለቆሙበት ሃቅ ማረጋገጫ ያገኙበት ከምንም በላይ ደግሞ ፈጣሪ ሃያልነቱን በቀጥታ ያሳየበት መሆኑ ይህን ቀን ለየት ያደርገዋል።
በያዝከው ሃሳቦችና አስተያየቶች ብዙም እርግጠኛ አትሁን.
ትዕቢት እና ኩራት በአስራዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ ያሉትን ጊዜያት ይገልፃሉ ፣ እናም አንድ ወጣት በተለይም በሃያ ዕድሜው ውስጥ የሚገኝ በእውነቱ በአሥራዎቹ ዕድሜ ውስጥ ካለ ወጣት ጋር ፣ አንድ ነው ፡፡ እንዴት መኖር እንዳለባቸው ፣ ሃይማኖትን የሚተረጉሙበት መንገድ ፣ ዓለም ላይ ካሉ ሰዎች በተለየ ሁኔታ ነገሮችን ለማየት መሞከር ያላደጉ ጥሬ ወጣቶችን ይገልጻል - እነዚህ አመለካከቶች በተለምዶ የሚመነሱት ሌሎችን ካለማዳመጥ እና ልምድ ካለማካበት ነው፡፡ ከመጠን በላይ ቅናት እና ጠርዝ የያዙ አስተያየቶች ወጣት የመሆን ምልክቶች እንደሆኑ መገንዘብ ይቻላል። በአስተያየታችን ማይስማሙትን እኛን ጠላት አርገው ከማሰብ ነው ብሎ ማሰብም ሞኝነት ነው : - በጥቂት ዓመታት ወይም አሥርተ ዓመታት ውስጥ እነዚህን ተመሳሳይ አመለካከቶች ይዘን መስመር የሳትንባቸውን አጋጣሚዎች ማስተዋል የቻልን ሰዎች ምን ለውጥ አምጥተን ይሆን? ከ 40 አመት በታች ሃሳብ መስጠት አይችልም!!
Dr Yasir Qadih
translator Brook F.( too much edited☺️😁)
ተግባራዊው የእውቀት ምንጭ ሕይወት ነው ፡፡
ከትላንቱ ነጥብ በመቀጠል ብቸኛውን የጥበብ ምንጭ የምንማረው ከራሱ ከሕይወት ነው ፡፡ የቱንም ያህል ጉባኤዎች ላይ ብንገኝ ፣ መጽሐፍትን ብናገላብጥ ፣ ወይም ጥልቅ የሆነ ማሰላሰል ውስጥ ብንሰርግ ፣ በቀላሉ ዓለምን ዞረን ከምናገኘው ጥበብ ጋር ሚስተካከል የለም ፡፡ለትዳር አጋራችን ጥሩ ለመሆን በትዳር ውስጥ ውጣ ውረድ መጓዝና መማር ያስፈልጋል ፡፡ጥሩ ወላጅ ለመሆን ልጆችን አፍርተን በልጅነት ዕድሜያቸው ሚያልፉትን ሂደቶች በመንከባከብ መማር ያስፈልጋል ፡፡ጥሩ ሰው ለመሆን የሰውን ልጅ መልካም እና መጥፎነት መለማመድ ያስፈልጋል፡፡
መጽሐፎቶች ውስጥ ያሉ ‘እውነታዎች’ አስደማሚ ቢሆኑም ፣ እነሱን ቅርፅ ማስያዝና ወቅታዊ በሆኑ በህይወት መጫወቻ ስፍራዎች ላይ መሞከር አለባቸው። በሁሉም ነገር ላይ ለመፍረድ መቸኮል ባልኖርነው ህይወት ላይ ጉዳትን ሊያስከትል እንደሚችል መገንዘቡ መልካም ነው ፣ በተለይም ከዚያ በፊት እንደዚህ አይነት ችግሮች አጋጥመውን ስለማያውቁ በስህተት ሁሉንም ዓይነት ችግሮች ለመቋቋም የሚረዱ ዘዴዎችን ሊያሳጣን ይችላል።
ከእድሜያችን በላይ የሆኑ ሰዎችን አክብሮት በመስጠት ከነሱ መጠቀም ያስፈልጋል ምናልባት ስለ አንድ ጉዳይ ከትላልቅ ሰዎች በላይ ምናውቃቸው ጉዳዮች መኖራቸው ይታወቃል......... ስለ ኳንተምና መካኒክሶች አሊያም ሳሂህ ሀዲሶችን መመርመር ፣ ወይ ደሞ ከመማሪያ መጽሐፍትዎ የቅርብ ጊዜውን የስነ-ልቦና ፍልስፍናዎች ብንረዳ እንኳ የሰውን ልጅ ግንኙነቶች አልፎም የሰዋዊ ስሜቶችን ውስብስብነት መዳሰስ በቀላሉ ከሴት አያትዎ ጥበብ ጋር መወዳደር አይችሉም
https://www.tg-me.com/Assefaboku/48
Dr Yasir Qadih
Translator Brook F.
ጓደኞች ይመጣሉ ይሄዳሉ; ቤተሰብ ሁሌም ከኛ ጋር ይቆይል!!!!
ብዙ ወጣቶች ጓደኞቻቸው ከቤተሰቦቻቸው የበለጠ አስፈላጊ እንደሆኑ አድርገው ይመለከታሉ፡፡ ከቤተሰቦቻቸው ይልቅ የጓደኛቸውን ስሜት በመጉዳታቸው የበለጠ ሲጨነቁ ይስተዋላሉ፡፡ በእውነቱ በእዚያ ዕድሜ ውስጥ ያለው አብዛኛው ግጭት በቤተሰብ እና በጓደኞች መካከል በመግባባት እንዴት እንወስን ከሚል ውዝግብ የመነጨ ነው ፡፡ ሆኖም ከእድሜያችን በላይ የሆነ ማንኛውም ሰው ሊነግረን የሚችለው ነገር ጓደኞቻችን በሕይወታችን ውስጥ ቋሚ እንዳልሆኑ ነው። እነሱ ይመጣሉ ፤ ይሄዳሉ ፣ ከእኛ የሕይወት ክፍል ውስጥ ተከራይተው ይለቃሉ ፣ እና በጥቂት ቀናት ወይም ወሮች አሊያም ዓመታት ፣ ያንን የክፍል ዙሪያ መመልከት እንጀምራለን። ሌላ ቡድን የያዘ ስብስብ ወዳለበት ቦታ ሙሉ በሙሉ የተለየ የጓደኞች ስብስብ ውስጥ እንገኛለን። ግና ከበስተጀርባ ተደብቀው ፣ በጭራሽ ሳይጠፉ (እስከ ሞት!) በሁሉም የህይወት ክፍላችን አብረውን ሚቆዩት ቤተሰቦች እንጂ ፤ጓደኞቻችን አይደሉም።
እውነት ነው ፣ በወላጆች ፣ በእህቶች ፣ በአጎቶች እና በአክስቶች እና በመሳሰሉት ላይ የራሳቸው የሆነ የውስጥ ችግሮች አሉባቸው። ሆኖም በቤተሰብ መካከል የሚደረግ ጠብ መኖሩ ፍጹም የተለመደ ነው (በተለይም ባልተለመደ ሁኔታ በትዳሮች ወቅት!) ፡፡ ይህ ነገር ምንም እንኳን እስላማዊ ይዘት ባይኖረውም ከቅርብ የቤተሰብ አባላት ጋር በትንሹም ከፍ ሲልም ጎላ ብሎ ለረጅም ጊዜ መሄዱ የተለመደ ነው ፡፡ የቤተሰባችን ደም ከማንኛውም በበለጠ ወፍራም ነው እና ሁሌም ከቤተሰብ ጋር እንገናኛለን። ጊዜ ሁሉንም ቁስሎች ይፈውሳል በጣም የከረሩ የቤተሰብ ክርክሮች እንኳን መፍትሄ ያገኛሉ ፤ስለዚህ ወዳጄ ለጓደኞችክ ብለክ ቤተሰብክን በጭራሽ አትናቅ ፡፡
Dr Yasir Qadih
Translator Brook F.https://www.tg-me.com/Assefaboku/48
በዚህ ዕድሜ የተገነቡ ልማዶች ከእኛ ጋር ይኖራሉ።
በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የሁለት የመጀመሪያ ዲግሪዎችን እንዲሁም 4 የድህረ ምረቃ ትምህርቴን ስከታተል ታላቅ ስኬት እንዲሁም መጥፎ ዕድሎች ገጥመውኛል ፡፡ በጣም አስገራሚ ሆኖ ያገኘሁት የመጀመሪያ ድግሪ ትምህርቴን ሳጠና ያዳበርኳቸው ልምዶች ለሁለት አስርት ዓመታት ከእኔ ጋር መቆየታቸው ነበር (በእርግጥ የተወሰኑ ማሻሻያዎች እና ለውጦች አሉ) ፡፡ አልፎ አልፎም በዕለት ተዕለት ተግባሮቼ እና በሌሎች የሕይወት ልምዶቼ ላይ የተወሰነ ተጽዕኖ አሳድረዋል፤ የመጀመሪያ ልጄ ሲወለድ የነበረኝ ጸባይ በኋለኞቹ ልጆቼ ላይ ባዳበርጉት ልማድ ተጽዕኖ ፈጥሯል።እውነት ነው በህይወት መንገዴ ላይ አንዳንድ ሱሶች ገብተዋል (የወጣትነት ጅማሪዬ ላይ ካፌይን ጠጥቼ አላውቅም ፤ አሁን በየቀኑ ጠዋት ትኩስ ሻይ እና ከሰዓት በኋላ ደግሞ የኤስፕሬሶ መጠጥ ሱሰኛ ነኝ፡፡ ወለል ላይ መተኛትም እወድ ነበር የተሻለ ምቾትን ይሰጠኛል - ይህም ደግሞ ያላገቡ ሰዎች ልማድ ነው! ግን በአጠቃላይ የእኔ ‘አኗኗር’ ተመሳሳይ ነው።
ስለሆነም በዚህ የእድሜ ክልል ውስጥ የሚኖሩን ልምዶች ጠንካራ እና መልካም መሆን ይገባቸዋል፤ ምክኒያቱም በቀሪው የሕይወት ጊዜያችን ሁሉ አብረውን ስልሚቆዩ፡፡ በወጣትነታችን ጥሩ ጥሩውን ማዳበር እድሜ ከሄደ በኋላ መጥፎውን ከመጣል ይቀላል፡፡
Dr yasir Qadih
Translator Brook F. https://www.tg-me.com/Assefaboku
ህ ይ ወ ት
አይ ህይወት ገፅ የላት አትፃፍ ነገር ቀለም የላት አይከተብባት ነገር ምን አለ ቀለም ኖሯት ድርቅ እስኪል ከትቤ የልቤን ባገኘሁባት በቃ ደስ ባለኝ ኖሮ! ደሰታ ነው ብዬ ሳላጣጥመው የሀዘን ድሪቶዋን ቸብ ታደርግብኛለች በተቀላቀለ ስሜት ውስጥ ከታ ታንገላታኛለች የሂሳቡን ስሌት እንደፈለገች undefined ስታደርገው የትኛው ሳይንቲስት prove አደረገላት? 1ድን ሰው ወደ 2 ተቀይሮ የሂሳብ ቀመሩን ሲያበላሸው ማንስ ተቸው? ማንም! እንዴት እኔስ እንዲህ አልኩኝ? እያልኩ የሂሳብ ስሌቱን እኩል ይሆናል እንደዚህ ብዬ ትክክለኛ መልስ ለማምጣት እጥራለሁ................ልፋት ብቻ 😳😳
አንዳንዴ በእጃችን የገባች እየመሰለን ጮቤ ብንረግጥም በሌላ ጊዜ ግን ጥፍር አድርጋ አስራ የቁም እስረኛ ታደርገናለች.....እኔን የገባኝ ግን formula የሌላት ሂሳብ መሆኗ ነው። ......መጨረሻ ላይ ተሰርታ ትክክለኛ መልስ ማምጣቷ ደግሞ ይበልጥ ያስገርማል......
ቁም ነገሩ ወዲህ ነው እኔም አንተም ህይወት የምትባለውን ቀመር በራሳችን ቀምረን አንጓዝም የሰማዩ ባለቤት ጣልቃ ገብነት ሁሌም አለ ግን ሆሌም እየረሳነው ህይወት surprise በምታደርገን ነገር አንዴ ስንደሰት ሌላ ጊዜ ስንቆዝም እንኖራለን.....ደስታችን አና ሀዘናችን ህልም እና እቅዳችን ህይወትና ሞታችን እውነትና ውሸታችን ድክመት እና ጥንካሬያችን .... መሰሎቻቸው ሁሉም የህይወት operation ናቸው።ደስታ ከሌለን ሀዘን ጥንካሬ ከሌለን ድክመት እውነት ከሌለን ውሸት መከተሉ ግድ ነው። ስለዚህማ ሀዘናችንን ወደ ደስታ መቀየር ካልቻልን ድክመታችንን ወደ ጥንካሬ ካልወሰድን ውሸታችን በእውነት ካልተተካ የምርም ህይወትን አልኖርንም...
Hayat
የጠዋት ፀሃይ
በእግር ኳስ ድካም እረፍት ያደሰው መገጣጠሚያዬ፣ በእናቴ ናፍቆት የተጨፈደደው ፊቴ፣ ቸልትኝነት የታከለበት ሳምንት ዛሬም ሌላ ቀን ነው ብዬ………ከአልጋዬ ወረድኩ። የጠዋት ስግደቴን ለመፈጸም ከተዘበራረቀው የሃይላንድ ማሳ ውስጥ ከዶሮም ጓደኛዬ በተረፈ ጭላጭ ውሃ እንደሎሽን ተቀባብቼ፧ ወደ መስገጃዬ አመራው። የጠዋት አዝካሬን ብዬ ውጪውን ለማየት ከብሎኬ ወረድኩ የአየሩ ቅዝቃዜ፣ የአእዋፋቱ ፉጨት፣ ተስፋን ያቀፈ ሚመስለው ውቡ የወልቂጤ ሠማይ ጎርነን ባለ ድምጽ ሠውዬ ነቃ በል ምንድነው ሚያፈዝክ ብሎ ካቀፈው ተስፋ ላይ ሊያጋራኝ መልሴን ሚጠብቅ ይመስላል። ሠዎች በሠማይ ውበት ሚደመሙት ቀኑን ሙሉ ስትነድ ውላ በምትገባው ፀሃይ ላይ መሆኑ ግርምትን ይጭርበኛል፤ ሁለት ተስፋ የቆረጡ ፍጥረታት ሚሸርቡት ዲስኩር አልያም ተባብረው መጪው ተስፋ ላይ የሴራ ፖለቲካ ሚቀምሩም ይመስላል ብቻ ወደ ጠዋቷ ፀሃይ ስመለስ እድሉ ተስፋው፣ ብርሃኑ፣ ልምላሜው እና ብልጽግናው (ፓርቲውን አይደለም) በፈጣሪ እዝነት የተቸረን ድንቅ ስጦታ ነው።
ብሩክ ፈቃዱ
one of the greatest scholar of Islam said that "Ihsan is to work more than what is required from you and expect less what people are to give you" such a stunning saying subhanAllah
Channel photo updated
In studies, whatsoever a man commandeth upon himself, let him set hours for it.
Bacon
ከሰዎች ጋር ባለን ግንኙነት ድንበር ማበጀት ሁሌም የኛን ስኬት ለማረጋገጥ ሰፊ እድል አለው። የሰዎችን ድንበር ለመጣስ ማናምንበትን አስተሳሰቦች ልክ ነው ብለን መቀበሉ በራሱ ከዛ ሰው ጋር ስንለያይ የት አባቱ ሰራንለት የሚል መልዕክት ለጨቅላ አእምሮአችን ይመጸውተዋል፤ ስለዚህ ጥላችን ክብሩን ለመንካት ከሞከርነው ሰው ጋር መሆኑ ይቀርና በእልህ ከተቀበልነው ምክኒያታዊ ያልሆነ ሃሳብ ጋር ይሆናል።
የትዕግስት ፍሬዎች
በበረከቶች የተከበበው የሠው ልጅ “ትዕግስት” ማድረግን አማራጭ ስላጣ የሚተገብረው ልማድ አድርጎት እንመለከታለን። መታገስ በትንንሽ ድሎቼ ላይ ምን ያህል ዋጋ እንዳላቸው አስተውያለው; ከማያልቀው የሠው ልጅ ፍላጎቶች አንጻር ትዕግስት በማድረጉ የሚረጋገጡት ድሎች ሳይፈልግ ለትዕግስት ዋጋ እንዲሰጥ ያስገድደዋል። የዓለም በፍጥነት መጓዝ ታጋሽ ላለመሆናችን አስተዋጽኦ ቢያደርግም በዕለት ተዕለት እንቅሳሴያችን ላይ መታገስ ነገ ላይ በሚመዘገቡት ስኬቶች አሻራችን ጎልተው እንዲታዩ ሠፊ እድል ይቸራል። ይህን አስደሳች የህይወት ትዕይንት በፈካ መስኮት ለመመልከት መጀመሪያ ከተቀመጥንባት ጠባብ ክፍል ውስጥ ብርሃኑን ከመፈለግ ይልቅ እኛው ብርሃን ሆነን አቅጣጫዎችን መመልከቱ የተሻለ ነው፤ ላለፉት 3 ዓመታት ከብዙ ስኬታማ ሰዋች ጋር ተቀምጦ የመወያየቱ እድል ገጥሞኝ ብዙ ተምሬኧለው። ሚገርመው ሁሉም ስኬታማ የሆኑት ታጋሽ ስለነበሩ ብቻ ነው;🥰
ዓሚር ኢብኑ በህደላ [ረሒ] ሐጃጅ ኢብኑ ዩሱፍ በስቅላት በገደላቸው ሰዎች አጠገብ ሲያልፉ በልባቸው እንዲህ አሉ: ‐ «ጌታዬ ሆይ! በዳዮችን መቻልህ ተበዳዮችን ጎዳ!»
:
ከዚያም ወደቤታቸው ተመልሰው ሲተኙ በህልማቸው ቂያማ ቆሞ ተለመከቱ። እርሳቸው ጀነት የገቡ ይመስላቸዋል። በስቅላት የተገደለውን ሰውም ከሁሉም ከፍ ካሉት የላይኛዎቹ የጀነት ሰዎች ዘንድ የሚያዩት መሰላቸው። ከወዲያ ደግሞ እንዲህ የሚል አዋጅ ይነገራል:‐ «በዳዮችን መቻሌ ተበዳይን ከበላይኞቹ የበላይ አድርጎታል!»
:
ነገሩ ተበዳይ ተሰቅሎ ሲገደልኮ በገሀድም እግሮቹ ከሰቃዮቹ አናት በላይ ነው!
የዓሹራ ጾም ትሩፋት
============
🔸 ዐሹራ የሙሐረም ወር ዐስረኛው ቀን ነው። የዐሹራን ቀን መጾም ተወዳጅ ነው። በርካታ ትሩፋቶች እንዳሉት በሐዲሶች ተዘግቧል። ነገርግን በተጨማሪነት ዘጠነኛውን ቀን ወይም/እና ዐስራ አንደኛውን ቀን ጨምሮ መጾምም ተወዳጅ ነው። ይህንን በተመለከተ በሶሒሕ ሐዲሶች የተገኙትን ተከታዮቹ ዘገባዎች እንመልከት። በመልካም ኒያ እንጹም። ቤተሰቦቻችንንም እንቀስቅስ!
:
⚀ ከዐብዱላህ ኢብኑ አቢ የዚድ እንደተዘገበው: ‐
«ኢብኑ ዐባስ ስለ ዐሹራ ጾም ተጠይቀው እንዲህ ሲሉ ሰምተዋቸዋል: ‐ «እንደዚህ ቀን የአላህ መልክተኛ [[ﷺ]] ከሌሎች ቀናት አስበልጠው፣ ትሩፋቱን ከጅለው ሲጾሙት የማውቀው ቀን የለም። ከዚህ ወር (ከረመዳን) በላይ ከወራት መካከል አስበልጠውት የጾሙት ቀንም አላውቅም።»
በሌላ ዘገባ ኢብኑ ዐባስ [ረዐ] እንዲህ ብለዋል: ‐ «እንደ ዓሹራእ ከሌሎች ቀናት አስበልጠውት ተጠባብቀው የሚጾሙት ቀን አይቼ አላውቅም።» ቡኻሪ ዘግበውታል።
:
⚁ ከአቡ ቀታዳ [ረዐ] እንደተዘገበው ነቢዩ [[ﷺ]] እንዲህ ብለዋል: ‐ «የዓሹራእ ጾም ያለፈውን ዓመት ኃጢኣት ያሰርዛል ብዬ ከአላህ እከጅላለሁ።» ሙስሊም ዘግበውታል።
:
⚃ ከዐብዱላህ ኢብኑ ዐባስ [ረዐ] እንደተዘገበው: ‐ «የአላህ መልክተኛ [[ﷺ]] መዲና ሲገቡ አይሁዶች የዓሹራን ቀን ሲጾሙ ተመለከቱና «ለምንድን ነው የምትጾሙት?» በማለት ጠየቁ። «ይህ መልካም ቀን ነው። አላህ ሙሳን [[ﷺ]] እና የእስራኤል ልጆችን ከጠላቶቻቸው ያዳነበት ቀን ነው። ሙሳ [[ﷺ]] ጾመውታል።» በማለት መለሱላቸው። «እኔ ከእናንተ የበለጠ ለሙሳ [[ﷺ]] የቀረብኩኝ ነኝ።» አሉ። የአላህ መልክተኛ ዓሹራን ጾሙ። ሌሎች ሰዎች እንዲጾሙም አዘዙ።» ቡኻሪ ዘግበውታል።
:
⚄ ከኢብኑ ዐባስ [ረዐ] እንደተዘገበው የአላህ መልክተኛ [[ﷺ]] እንዲህ ብለዋል: ‐ «እስከመጪው ዓመት ከቆየሁ ዘጠነኛውን ቀንም እጾማለሁ።»
በሌላ ዘገባ: ‐ «የአላህ መልክተኛ [[ﷺ]] የዓሹራን ቀን ሲጾሙ እና እንዲጾም ሲያዙ ሰዎች እንዲህ አሉ: ‐ «ይህ ቀን አይሁዶች እና ነሷራዎች የሚያከብሩት ቀን ነው። (ከነርሱ ጋር መመሳሰል አይሆንብንም?)» አሏቸው።
እርሳቸውም: ‐ «አላህ ከሻ‐ በመጪው ዓመት ዘጠነኛውን ቀንም እንጾማለን።» አሉ። ነገርግን መጪው ዓመት ሳይደርሱ የአላህ መልክተኛ [ﷺ] አረፉ።» ሙስሊም ዘግበውታል።
ከዓመት አመት ያድርሰን!
ustaz Tofiq Bahru
2024/09/26 04:52:56
Back to Top
HTML Embed Code: