Telegram Web Link
ጠላትዎ ከወዳጅዎ የበለጠ ሊጠቅምዎት ይችላል!
አንተን የሚጠሉ ፣ ስምህን ሚያጠፉ ፣ከጀርባክ የሚያሙክ ሰዎች ከጓደኞችክ በበለጠ ሊጠቅሙክ ይችላሉ?
ታዋቂው ምሁር አል-ፉደይል ኢብን. ኢያድ (187 ዓ.ሂ) እንዲህ ይላሉ፣ “ከጠላት የሚመጡት መልካም ተግባራት ከወዳጅ ከሚመጡት የበለጠ ሊሆኑ ይችላሉ! ምክኒያቱም ጠላት ባማን ቁጥር ያለምንም ልፋት የእነርሱን ጥሩ ስራ መሰብሰብ እንችላለን።
በጭራሽ ‘አላህ ያጥፋው!’ ማለት የለብንም ፡፡ ይልቁንም ‘አላህ ሆይ! ይህንን ግለሠብ ወደ ቀናው መንገድ ምራው ብለን አላህ የስራዎቹን ምንዳ ለእኛ በመጻፍ ለሰውየው ስራውን ተመላሽ ያደርግለታል።
ማለትም-እሱን ከረገምነው የራሳችንን ጥቅም ቀንሰነዋል ፣ እናም በቂያም ቀን ዋጋ አይሰጠንም ምክኒያቱም የበቀል በርን በመክፈታችን፤በሌላ በኩል ለሱ ከፀለይን እኛ ላይ ለፈጸመው ሃሜት ምንዳን እናገኛለን። ከዚያ ያሰው ከተፀፀተ ንስሃውን በማመቻቸት (በጸሎትዎ) ምክኒያት ድርብ ምንዳ ይቸረናል።
አዎን ጉዳት ባደረሰብዎት ሰው ላይ ዱዓ ማድረግ ይፈቀዳል ፡፡ ነገር ግን በዚህ ዓለም ላይ ታግሠን በትንሳኤ ቀን ትልቅ ደረጃ ማግኘቱ ለኛ የተሻለ ነው።
አንድ ሰው ለዑመር ኢብኑ አብዱልአዚዝ (101 ዓ.ሂ) ቅሬታ አቀረበ ስለጎዳው እና ስላበሳጨው አንድ ግለሠብ መጥፎ ነገሮችን መናገሩን ቀጠለ ፡፡ ኡመር (ረዐ) እንዲህ አሉት: - አንተ ላይ ያደረገው መጥፎ ነገሮች ሳይነኩ አላህን ብትገናኙ እኮ፣ ከምታደርገው የበቀል እርምጃ (ስለሱ በመናገር) በበለጠ ለአንተ የተሻለ ይሆናል ፡፡
የጎዱንና ያበሳጩንን አማኞች ሁሉ አላህ ይምራልን!
Dr Yasir Qadih
እርግጠኛነትን ማሳካት (የቂን)
ኢብኑ ተይሚያህ “እንዲህ ጽፈዋል
በእምነት ዙርያ (የቂን) እርግጠኝነት በሶስት ጉዳዮች የተገኘ ነው-
1) በአላህ መጽሐፍ ላይ ማሰላሰል
2) በአላህ ፍጥረት ላይ ማሰላሰል ይህም የአላህን ታላቅነት ያስታውሳል
3) እውነት መሆኑን ባወቅነው ጉዳይ ላይ እንቅስቃሴ መጀመር፡፡
ሁላችንም እምነታችን እየከሰመ የሚሄድባቸው የሕይወት ጊዜያት ይኖራሉ፡፡ ኢብኑ ተይሚያህ እምነታችንን ለማጠንከር ሦስቱ ምርጥ መንገዶችን ያስታውሱናል ፡፡
፠የመጀመሪያው ቁርአንን ለማንበብ ፣ ለማዳመጥ እና ለማሰላሰል ዝግጁ መሆን ያስፈልጋል፤ ምክኒያቱም እንደ ቁርዓን ኢማንን ሚሞላ ስለሌለ ፡፡ *ምንም*.
፠ሁለተኛ የፍጥረታትን ውበት እና ፍጹምነት መገንዘብ ወደ ፈጣሪ ግርማ እና ኃይል የሚወስደን ትልቅ ድልድይ ነው ፡፡ በእርግጥም ሰማያትንና ምድርን በመፍጠር እንዲሁም በሌሊትና በቀን መካከል ያለው መለዋወጥ ለብልህ ሰዎች ተዓምራት ናቸው፡፡ ይህ ፍጥረት በፈጣሪ በኩል ካልሆነ በቀር ሊገለፅ አይችልም፤ የትኛውም እምነት ፈጣሪን እና ስነ መለኮትን እንደ እስልምና እምነት ቀላል እና ቆንጆ አድርጎ የሚያረጋግጥ የለም ፡፡
፠በመጨረሻም በእምነታችን ስንኖር ፣ጌታችንን ስናመልክ በህይወት የመኖር ዓላማንና የሰላም ስሜትን እናጣጥማለን።
፨የሃይማኖታችንን እውነተኝነት ለማረጋገጥ ጽኑ እምነትም ተሰጥቶናል ፡፡
አላህን እርግጠኝነት (የቂን) እና የእምነት ጣፋጭነት እንጠይቃለን!🤲
Dr Yasir Qadih😁😁😁☺️☺️☺️☺️
9ኛው የበጎ ሰው ሽልማት የእጩዎች ጥቆማ ከየካቲት 1 /2013 ጀምሮ መቀበል ቀጥሎአል::
ለሀገርና ለሕዝብ አርያነት ያለው ታላቅ ተግባር ያከናወኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በየዓመቱ ዕውቅና የሚሰጠው የበጎ ሰው ሽልማት በ2013 ዓ/ል ለሚያካሂደው ዘጠነኛው መርሐ ግብሩ የእጩዎችን ጥቆማ ከየካቲት 1 ቀን 2013 ዓ/ል አንስቶ ከሕዝብ መቀበል ጀምሮአል።
የዘንድሮው ሽልማት እጩዎችን ተቀብሎ ለመሸለምና ለማመስገን ዐሥር ዘርፎችን አዘጋጅቷል።ከነዚህም ዘርፎች መካከል አንደኛዉ በጎ አድራጎት (ርዳታና ሰብአዊ አገልግሎት) ይገኝበታል ,እኛም ወንድማችን ኡስታዝ በድሩ ሁሴን በ የኔ ቤተሰብ ፕሮጀክት ላይ ባደረገዉ ትልቅ የሀገር ዉለታ ይገባዋል በማለት ድምፅ እንስጠው ለጥቆማው በተመደበው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሕዝቡ ለእዚህ ሽልማት ብቁ ናቸው የሚላቸውን እጩዎች እንዲጠቁም ጥሪ ቀርቧል።
ጥቆማው በስልክ ፣በቫይበር ፣በቴሌግራም፣ በዋትሳፕ፣ በኢሜይልና በፖስታ ነው።
አድራሻዎቹ፦ 0977232323 (ቫይበር ፣ ታሌግራምና ዋትሳፕን ጨምሮ)
ኢሜይል፦ [email protected]
ፖስታ፦ 150035📸 ናቸው::
የጥበብ ቃላት
የመጀመሪያዎቹ የተሰውፍ ምሁራን በጥልቅ ግንዛቤዎችና ማስተንተን ላይ የታወቁ ናቸው፡፡ እነሱ የኢህሳንን እውነተኛ እሴቶች ያቀፉ ፣ አንዲሁም ከተዛባ ሥነ-መለኮታዊ አመለካከቶችና የአምልኮ ሥርዓቶች የራቁ ነበሩ ፡፡
ከእነዚህ ምሁራን መካከል አንዱ ኢብራሂም ኢብን ሻይባን (330 ሂ. አ.) ፡፡እንዲህ ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል
ጥበብ የሚመጣው ከትህትና ነው ፣ ክብር ደግሞ ከእምነት ይመነጫል፤ ነፃነትም በእርካታ ያገኛል ፡፡
الشرف في التواضع ، ولعز في التقوىا ، والغنى في القناعة
ይበልጥ ትሁት በመሆን በሌሎች ዘንድ አላህ በረከቱን ይቸረናል፡፡
ይበልጥ በተጠነቀቅን ቁጥር ከዚህም አልፎ በሚቀጥለው ዓለም ላይ በጌታችን ዘንድ ክብር እናገኛለን፡፡
ባለን ላይ ተብቃቅተን ንፍሳችንን ይበልጥ ነጻ ካረግናት ነፍሳችን በምትፈልግው የእስር ስሜቶች ከመታጠር ነጻ እንድናወጣት ያስችለናል።
ከቀደምት ጀግኖቻችን ተውስተው ካለፉ ምርጥ ቃላቶች ፡፡
ስለ ትህትና
•እናታችን አኢሻህ(ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስታወሱን “ትልቁ የአምልኮ ተግባር የሆነውን ትህትና እና መተናነስን ችላ ትላላቹ” [በኢብኑ አል-ሙባራቅ ኪ. አል-ዙህድ ተዘግቧል]
•ቃታዳህ ደግሞ እንዲህ ብለዋል “ሀብት ፣ ውበት ፣ ጥሩ ልብስ ፣ እውቀት ተችሮት ትሑት ያልሆነ ሰው በፍርድ ቀን በእነዚህ በረከቶች ይጸጸታል” ፡፡
•የአነስ ኢብኑ.ማሊክ(ራ.ዐ)ተማሪ የሆነው ያሂያ ኢብን.አቢ ከቲር ፣ “ሦስቱ የትህትና ምሰሶዎች እኒህ ናቸው ሲሉ መክረዋል:- እርስዎ ከእርስዎ ያነሱ ናቸው ብለው ከሚያስቡዋቸው ሰዎች ጋር ቁጭ ብለዋል ብለው ሰዎች ባሰቡ ጊዜ ያገኙትን ሰው ሁሉ ቅድሚያ ሰላምታ በመስጠት ማንኛውምየተመሰገኑበት ተግባር ላይ ራስን ማውገዝ ፡፡
oአላህን ትህትና መተናነስን እንጠይቃለን ፤ ከእብሪትና ከትምክህትም መጠጊያውን ከአላህ እንሻለን ፡፡
ስኬት የአንድ ቀን ውጤት አይደለም
በዚህ ዘመን ብዙ ሠዎች ስኬትን ሳያዩ ስለ ስኬት ይመክሩናል ምናልባት እኛን በመምከር ውስጥ ይሆን እንዴ ስኬታቸው ሚረጋገጠው አላውቅም😕 የሰው ልጅ ከተሰጡው ምርጥ ጸጋዎች መሃከል አእምሮው አንዱ ነው ይህን ትልቅ ጸጋ ያለ መታከት ሚያንቀሳቅሰው ደግሞ መንፈስ ሳይሆን አይቀርም😉 ስሜቶች ደግሞ ምቾትን ይፈልጋሉ ስለዚህ የሠው ልጅ የሶስት ነገሮች ውቅር ነው ብል ስህተት አይሆንም። ታድያ ሶስቱን እንዴት እናስማማ?????
አእምሮ ለስኬት ሚያስፈልጉትን ግብዓቶች በማከማቸት የሁለቱን ፍልሚያ ለመዳኘት ዙፋኑ ላይ በግርማ ሞገስ ተደላድሏል። የትግል ሜዳው ላይ የነፍስ ፍላጎቶች ፤ የስኬት ማማ ላይ ለመድረስ ከሚታገሉት መንፈሶች ጋር ለመፋለም ወደሜዳው ዘልቀዋል። እኒህ የስራ መንፈሶች ያሸነፉ ለታ አእምሮ ያከማቸውን ግብዓት ለመጠቀም አይሳሳም; ብዙሃኑ ግን በነፍስ ፍላጎቶች ስለሚረካ እውነተኛውን ስኬት ሳያይ አእምሮው ውስጥ ያሉትን በተግባር ያልወረዱ ሃሳቦችን በመስበክ የእርካታን ጭላንጭል ያያል። ስለዚህ ስኬትን ለማየት በኛ ውስጥ ራሱ ብዙ የቤት ስራዎች አሉ; ስለዚህ ስኬት ማለት እኔም ስላላየሁት ምንም ማለት አልችልም!!!
ወንጀል ለመስራት እድሉን ማግኘት ያስፈልጋል።
ከትላንት ወዲያ ዶርም ውስጥ ከተነሱ አወያይ ርዕሦች መሃከል
ከባድ ወንጀል ማንሰራው በእውነትም ጥሩ ሠው ስለሆንን ነው?ወይስ ያ ዕድል ወደኛ ስላልመጣ ብለን ብዙ አውግተን አደርን፤ በኔ እይታ ጥሩ ሰው ለመባል መፈተን ያስፈልጋል። የኛ ማንነት ክብዙ ነገሮች ይቀረጻል። ከቤተሰብ፣ ከአካባቢው ባህል፣ ከጓደኛ፣ከስራ ባልደረባ፣ከአየር ጸባይ፣ከሃይማኖት......ወዘተ; ማንነታችን በነዚህ ሁሉ ነገሮች ይገነባል። ከምንሰጠው ምንቀበለው እንደሚበዛ ድፍን እውነት ነው፤ የምንቀበልበት ቦታ ደግሞ የወንጀል ፍሬዎች ሲያብቡ ሚኮተኩት ማህበረስብ ውስጥ አልያም ደግሞ ወንጀል ሰርተን የኩራት ካባ አልብሶ በሞቅታ ሚያጅብ ህዝብ መሃል ከተፈጠርን ከዚህ ምቹ ጣጣ ወጣ ብለን ለማሰብ በተግባር ላይ ያጠነጠነ የሠው ስብዕና አደራጅተን ከእውነት ጎን መቆም ከቻልን ያኔ እውነትም ጀግና አማኝ ለመባል ብቁ ነን፤ ያ ዕድል ሳይመጣ በሌሎች መሳለቅ ግን ርቦኛል ጠግቤዓለው እንደሚል ሰው ................ይመስለኛል።
Forwarded from Nadia.B
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በካ ኮሚኒቲ ዲቨሎፕመንት አሶሴሽን


#ሁሉም_ወገን_ደና_ኑሮ_ይገባዋል!
#ሁሉም_ቤት_ጠግቦ_ማደርን_ይሻል!
#ለአንድ_ቤተሰብ #በወር_2500ብር
#ለ567_ተፈናቃይ_አባወራዎች_ይድረሱ!

#እኔ_ወገኖቼን_እታደጋለሁ!
#እናንተስ?

ለበለጠ መረጃ

በስልክ ቁጥሮቻችን:
+251977627478
+251922581090
+251934447320

ኢሜል አድሬስ: [email protected]

የባንክ አካውንቶች:
Backa community devt Asso.

የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000050398653
አዋሽ ባንክ
01304009538200

#ወገኖቼን_እታደጋለው
#Backa_Aid

#ረመዳን_ሙባረክ
Forwarded from M.Neja
የምርጫ ካርድ በመውሰድ የዜግነት ኃላፊነቶን ይወጡ። ቢያንስ ለ10 ሰው መልዕክቱን ያድርሱልን እናመሰግናለን(ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ)
Yemerecha Card Bmewesede Yezegenete Halafintown Yewetu Beyanse Meleketun L10 Sew Yaderesulen Enamesegenalen(Freedom and Equality Party)። የዚህ ግሩፕ አባላት ይህን sms ቴክስት ለምታውቁት ሰው በማድረግ አግዙን
065
065
Great voice wellah you have to hear it😉🥰🥰
2024/09/26 22:12:07
Back to Top
HTML Embed Code: