Telegram Web Link
እንደሚሞት እያወቅሁ አክመዋለሁ(የመጨረሻ ክፍል)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

እናቱና ህፃኗ እየተንደረደሩ ገቡ።እኔ የራሴ ትንፋሽ አፍኖኝ... እየተነፈስኩ ያለሁት አየር ጭስ ጭስ እያለኝ ቀዝቃዛው ሴራሚክ ላይ ተንበርክኬ ማንባት ጀመርኩ።በእንባዬ መሀል ከኔ ለቅሶ ጎልቶ የሚሰማ ስቅጥጥጥጥጥጥ የሚያደርግ ጩኸት ሙሉ ቅጥር ጊቢውን ናጠው።

"ኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡይ! ወይኔ ልጄጄጄጄጄጄጄጄን!"

ከዚህ ድምፅ በሁዋላ የዚያንን ሆስፒታል ጊቢ አልረገጥኩትም። 9 ወራት ተቆጠሩ።ከጅምሩ የነካከተው ትዳሬ በሙት ፍቅር ፍፃሜው ተፈረመ።ስዩምን በዚህ ውጥንቅጥ ውስጥ ብቸኛው ተበዳይ ማድረጌን ሳስበው ራሴን እጠላዋለሁ።ፍቺውን ሲፈርምልኝ እንኳን ግንባሬን ስሞ "ይቅናሽ"ነበር ያለኝ ።


ሰው ምን ቢያዝን...ምን ቢሰበር ጊዜ ሲነጉድ የሀዘን ቀለሙ ይደበዝዝ የለ?ግልፅኮ ነው! እናትም ልጇን ቀብራ መኖር ከተባለ ትኖራለች።እኔ ዳንኤልን ቀበርኩ ብዬ እንደሱ ራሴን ባጠፋ ሰው አይስቅም?

ከዘጠኝ ወራት እዬዬ በሁዋላ የዳንኤል እናት ዘንድ ጥያቄዎቼን አንግቼ ሄድኩ።በሩን ከፍታልኝ ከፊት ለፊቷ ቆሜ ስታየኝ ቁስሏን ስለነካሁባት ወዲያው ጠርቅማብኝ ገባች።ደግሜ አንኳኳሁ።መልስ የለም።ትንሽ ቆይቼ በድጋሚ አንኳኳሁ።ብላቴናዋ ነበረች የከፈተችልኝ።ጎንበስ ብዬ ልስማት ስል

"አባቴን ገደልሽብኝ"አለችኝ ።እንደጨው አምድ ተተክዬ ቀረሁ።

"ማ...ማን እኔ?"

በቆምኩበት በሩን ሳትዘጋ ጥላኝ ገባች።ተከትያት ገባሁ።ባልቴቲቱ በተማፅኖ

"እንደው በወለዱሽ ልለምንሽ እባክሽ አትምጪብኝ...ስጋውንስ በቁሙ ጨረስሽው ባይሆን ነፍሱ ትረፍ ስለፈጠረሽ"አለችኝ ግድግዳ ላይ የተሰቀለውን የዳንኤልን የምርቃት ፎቶ እያየች።የሳሎኑ በር ላይ ቆሜ ፎቶውን አየሁት።ነፍስ ያለው ፈገግታው ውልብ አለብኝ።


"ቆይ እኔ አላሳዝናችሁም እንዴ?እኔን ማን ሰምቶኛል?የኔን ስቃይ ታውቂዋለሽ አንቺ እትዬ?"እንባዬ ቀደመኝ።ማልቀሴን ስታይ ደንገጥ አለች።ማንንም ሳላስፈቅድ ገብቼ ሶፋው ላይ ተቀመጥኩ።ለቅሶ አላቆም ያለ ዐይኗን በነጠላዋ ጫፍ እየጠረገች ከፊት ለፊቴ ተቀመጠች።

"ልጅስ ኤድስ አለበት አሉኝ።የልጄ ኤድስ እሷ ናት አልኳቸው።የልጄ በሽታ አንቺው ነሽ"አለችኝ ፈርጠም ብላ።

"እኔኮ ባለትዳር ነበርኩ ምንም ማድረግ አልችልም ነበር።"

"ትችይ ነበር"

"ምን ማድረግ እችል ነበር?"

"ቢያንስ እስኪሞት አብረሽው መሆን ትችይ ነበር"

"ትዳሬስ?"

"ከትዳርና ከነፍስ?ይህች አንዲት ፍሬ ልጅ አባቷን ብታጣ ይቀላል ወይስ ያንቺ ትዳር ቢፈርስ ይቀላል?"ልጅቷን እያየሁ ዝም አልኩ።ቆየት አልኩና እረፍት የነሳኝን ጥያቄ ሰነዘርኩ።

"ለመሆኑ እናቷ የት ናት?"ልጅቷን እያየሁ ጠየቅሁ።

"እሷ በደህናው ጊዜ አባቷ ጋር ሄዳለች"

"አብረው ነበር የሚኖሩት?ማለቴ ከዳንኤል ጋር?"ጥያቄዬ መልሶ አሳፈረኝ።

"ስትወልድ ነው የሞተችው።'ኢንበርስቲ' እያሉ ነው ያረገዘችው ልጅቱ ገና 6 ዐመትም አልሞላትም።"አንድ ነገር አሰብኩ።ዳንኤል ለቫይረሱ የተጋለጠው ከልጁ እናት ጋር በነበረው ግንኙነት ሊሆን እንደሚችል።ስፈራ ስችር

"እ...እኔምለው እናቴ...ዳኒ እንዴት በሽታው እንደያዘው ነግሮሻል?"እንባቸውን እያዘሩ

"ከዚህቸው ከልጁ እናት ነው።ደግነቱ ልጅቱ ነፃ ናት።በእርግዝና ጊዜ አስመርምራት ነው አሉ።ወልዳ ጥላለት ነው የሄደችው መልኳንም አላውቃት።እህህህህ...ልጄን!አዬ ሽታዬን!ወዜን ሰረቀችብኝ...እሱም እንዲችው ልጁን እናቴ እያለ ሲንሰፈሰፍላት ኖሮ ተቀጨብኝ!እኔ ልቀጭልህ የኔ ለፊ!"ይህን እንባ እንደጉድ ያወርዱታል።

ከዚህ በላይ መጠየቅም መስማትም አልቻልሁም ።እያለቀስኩ ወደቤቴ ተመለስኩ።ዳንኤልን ሳስብ ሁሌ ወደ ህሊያዬ የሚመጣው ለመጨረሻ ጊዜ በስልክ ስናወራ የተናገርኳቸው ቃላት ናቸው።ምናለ "ስህተቴ ነህ"ሳይሆን "ከክርስቶስ በታች የህይወት መምህሬ ነህ"ብየው ቢሆን!ምናልባትም ቀብሬው አልፀፀትም ነበር።

ተፈፀመ!

ማዕዶት ያየህ

27/08/2014 ዓ.ም.

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት

(ሜሪ ፈለቀ)

«ሞቼ ቢሆን ኖሮ ደስ ይልሽ ነበር አይደል?» አለኝ በወጉ ማሽከርከር ያልለመደውን ዊልቸር እየገፋ ወደሳሎን ብቅ እንዳለ። ፊቱ ምሬት ወይ ጥላቻ በቅጡ ያልለየሁት ስሜት ይተራመስበታል። ዝም ያልኩት መመላለሱ ልቤን ስለሚያደክመኝ ነበር። በጎማው እየተንቀራፈፈ አጠገቤ ደርሶ « ንገሪኛ ደስ ይልሽ ነበር አይደል?»
«አይከፋኝም ነበር።» መለስኩለት። እግዚአብሔር ይሁን ሰይጣን አደጋውን ያደረሱበት አንዳቸው ምርጫ ሰጥተውኝ ቢሆን ኖሮ እንኳን የቱን እንደምመርጥ እንጃ! (ሰዎች በህይወታቸው የሆነ የከፋ ነገር ሲገጥማቸው <እግዜር ሊያስተምረው ነው!> ይሉን የለ? ያው ራሳቸው ሰዎች ደግሞ የክፉ ነገር ምንጭ ሰይጣን ነውም ይሉናል። ነገሩ ለእኔ ጭንቅላት የተሳከረ ነገር ስላለው ነው ከሁለቱ አንዳቸው ቢሆኑ ያልኩት!! አስቡት የመልካም ነገር ሁሉ ምንጭ የሆነው አምላክ ፣ ለሰው ልጅ በምርጫው እንዲኖር ነፃነትን የሰጠው የነፃነት አምላክ ሊያስተምር ሲፈልግ በክፉ ሲቀጣ? አንዳንዴ ፈጣሪ በክፉ አይፈትንም ብዬ ሳስብ ለራሴ የምሰጠው ማመሳከሪያ የመፅሃፍ ቅዱሱ እዮብ ነው። ፈጣሪ ጥበቃውን እንደእዮብ ያነሳብህና ለክፉ አባት አሳልፎ ይሰጥሃል እንጂ ራሱ አምላክ ክፉውን አያዘንብም! ከዛ ግን ሞትና የሲኦል መኖር ይሄን እሳቤዬን ከአፈር ያደባይብኛል። ብቻ ማናቸውም ይሁኑ የዛን ቀን እየነዳ የነበረውን ጣዖቱ የነበረ መኪና ከገደል ፈጥፍጠውልኛል። እግዜር ይስጣቸው!!_)
«እግዜሩ እንድትበቀዪኝ እድሉን እየሰጠሽ ይሆናልኮ! ለምን ደግ እየሆንሽ የተሰጠሽን እድል ታባክኛለሽ?» አለ የሰራሁለትን ምግብ ላጎርሰው እጄን ስዘረጋ! ከፍቅሬ ጥልቀት አይደለም የማጎርሰው። በአደጋው ምክንያት እጁ እንደፈለገው ስለማይታዘዝለት እንጂ።
«ከዛስ? በእኔ ክፉት ክፉትህን ልታቀል? በእኔ ሀጢያት በደልህን ልትሰርዝ? በእኔ በቀል ሀጢያትህን ልታወራርድ? በፍፁም ያን ደስታማ አልሰጥህም!!»
በቀል ዓይን ላጠፋ ዓይን ማጥፋት ፣ የገደለን መግደል …………… ባጠቃላይ በቀል ለክፋት ክፋትን መመለስ ነው ያለ ማን ነው? ለሰራው ስራ የስራውን መኸርማ መሰብሰብ የተፈጥሮ ህግም አይደል? ያጭዳል!! ምኗ እንከፍ ብሆን ነው <ወይ በገደልከኝ ወይ በገደልከው> ብዬ ስማፀን የከረምኩበትን ሰው እንዳይሞት እንዳይድን አድርጎ እጄ ላይ ሲያስቀምጠው በክፋት የምበቀለው?
ገብቶታል። ጤነኛ ሆኖ ሰራተኛ ያበሰለውን ምግብ የምንበላ ሰዎች ራሴ የሚበላውን ጓዳ ገብቼ ሳበስልለት በደሉን እንደማላቀልለት ገብቶታል። እልህ የሚይዘው ከእኔ ይሁን ከራሱ እንጃ ርሃብ አንጀቱን ካልፋቀው በቀር እሺ ብሎ አይበላም። አይጠይቅምም!! ከሆስፒታል እቤት የገባ ሰሞን <ነርስ ይቀጠርልኝ> ሲል <እኔ ሚስትህ እያለሁ እንዴት ገበናህን ባዳ ያያል?> ብዬው አልጋው ላይ ሲፀዳዳ እሱንም አልጋውንም ሳፀዳ በቀላሉ ይቅር እንደማልለው ገብቶታል። ከሀዘኔታ ልብ ወይም ከፍቅር ፅዋ ከፈለቀ ደግነት እንደማልንከባከበው ያውቃል። ግን ደግሞ በደሉን በበደሌ አላለቀልቅለትም። እሱም ያ ገብቶታል።
ሞቶ ቢሆንና እንደወጉ ነጠላዬን አዘቅዝቄ ከሬሳው ጋር ወደ ቀብር እየሄድኩ ምንድን ነበር የምለው? ሰው ምን ይለኛል ብዬ ደረቴን እደቃ ነበር? ወይስ <ተመስገን ገላገልከኝ> እያልኩ በፈገግታ ከአፈሩ ጋር የሰባት ዓመት ትዳራችንን ወደ ጉድጓዱ መልሼ እመለስ ነበር? የቱ የበለጠ ደስ ይላል? ሞቱ? ወይስ ስንክልክሉ የወጣ አካላቱን እና ከተሰበሩት አጥንቶቹ እኩል እንክትክት ያለ ትህምክቱን፣ ትእቢቱን፣ ሞራሉን ፣ አምላክ ነኝ ባይ ልቡን ………. ታቅፎ ……….. እንኳን እኔ ላይ ራሱ ላይ እንኳን የማዘዝ አቅም የሌለው ከንቱ ሆኖ ማየቱ? የቱ የበለጠ ደስ ይላል? ወይስ ከነጭራሹ ደስታ አለው? ካለመዋሸት አለው! የሆነ ደስ የሚል ስሜት አለው። አንዳንዴ በ7 ዓመት የዲያቢሎስ ሚስትነት ዘመኔ በደነደነ ክፉ ልቤ ውስጥ የተረፈው ሚጢጥዬ የርህራሄ ጭላንጭል ተስፋ ብቅ ይልና ደስታዬን ይበርዝብኛል።
ደስታዬን መደበቅ ግን አልችልም። በጠዋት ተነስቼ እንዲፀዳዳ እያገዝኩት ፈገግታዬ ያመልጠኛል። ጥርሱን እየቦረሽኩለት፣ ፀጉሩን እያበጠርኩለት፣ ልብሱን እየቀየርኩለት፣ የሚንቀጠቀጡ እጆቹ አስተካክለው ስልኩን መያዝ ስለማይችሉ ስልኩ ሲጠራ ሲንፈራገጥ ሳየው አንስቼ እያቀበልኩት ሁላ ከንፈሬን እንደተከደነ ማስቀረት ያቅተኛል። የሚወደውን ምግብ በዜማ እያፏጨሁ አበስልለታለሁ፤ሲዝረከረክ በሶፍት እያፀዳሁ አጎርሰዋለሁ፤ በጤነኛ ዘመኑ ሰራተኛዋ የማታጓድለውን የምሳ ሰዓት ቡና ከነጭሱ እሱ እንደሚወደው ራሴ አፈላለታለሁ፤ ፈገግታዬ በየቀኑ ከማፈነዳው ፈንድሻ ጋር ይፈካል። የየቀን ምኞቱ እዛው አልጋው ላይ እንድረሳው ወይ ትቼው እንድሄድ ወይም በእንክብካቤ ፈንታ ባንገላታው እንደሆነ አውቃለሁ።
በጤነኛ ዘመኑ ከሚያገኘው እንክብካቤ አንዳች አላጎልበትም እንደውም እንደ ሰሞንኛ ሙሽራ አቀበጥኩት እንጂ! አሁንም ፈጣሪ ይሁን ሰይጣን ሲቀጡት አጓጉል አድርገውት እንጂ በጤነኛ ዘመኑ በየቀኑ ማታ አጅበውት የሚመጡትን ለዛዛ ሴቶች ሁላ አመጣለት ነበር። የሚታገዝ ቢሆን እኔ መኝታ ቤት የሚሰማኝን ሴቶቹን የሚያስጮሃቸውን ልፋቱን እያገዝኩት አስከውነው ነበር። አለመታደሉ እንኳን ለጉድጉድ ለመሽናቱም በድጋፍ ሆነበት።
«እሺ ምን ብሰጥሽ ትተይኛለሽ? ከውላችን በተጨማሪ ባንክ ያለኝን ገንዘብ ልስጥሽ ተይኝ!» አለኝ ምግቡን አብልቼው እንደጨረስኩ።
ውላችን ያለው ስንጋባ ያስፈረመኝን ነው። ከኔ በፊት እንዳገባቸው ሁለት ሚስቶቹ እኔንም 8 ዓመት አብሬው ከኖርኩ የንብረቱ ተካፋይ እንደምሆን ፣ ከዛ ቀድሜ መለያየት ካማረኝ ቤሳቤስቲን እንደማላገኝ አስፈርሞኛል። እንደቀደሙት ሚስቶቹ ጨርቄን ማቄን ሳልል በአንዱ ቀን ብን እንደምል እርግጠኛ ነበር።
«ወይ አለመታደልህ! እንዲህ ተይዘህም ገንዘብህ ሁሉን ነገር የመግዛት አቅም እንዳለው ነው የምታስበው?»
«እሺ ምንድነው የምትፈልጊው?»
«ለጊዜው ምንም! ፍቅሬን መንከባከብ!» አልኩት ፈገግ ብዬ ጉንጩን እየዳበስኩት። ጥሎኝ ሊሄድ ተውተረተረ። የሚንቀጠቀጡ እጆቹ አስተካክለው የዊልቸሩን መንቀሳቀሻ ስላልተጫኑለት ስልኩ ሲጮህ እንደሚወራጨው ተወራጨ። ፈገግታዬን መደበቅ እያቃተኝ ረዳሁት!!
ዛሬ ላይ እንዴት ተገኘሁ? ይህችኛዋን እኔ አድርጎ እሱ በሰይጣናዊ እጁ አቡክቶ ሳያበለሻሸኝ በፊት እግዚአብሔር የሰራት እኔ ምን አይነት ነበርኩ?

አልጨረስንም …

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት
(ክፍል 2…………… meri feleke)

ከእኔ በፊት ሁለት ሚስት አግብቶ እንደነበር ሳላውቅ አይደለም ያገባሁት። አውቅ ነበር። ለሁለቱም ሚስቶቹ ልክ ከእኔ ጋር እንዳደረገው የሀብት ውርስ ኮንትራት አስፈርሟቸው እንደነበርም አልደበቀኝም ነበር። በፍቅሩ ነሁልዬ ከእኔ በፊት የነበረው ህይወቱ ገሀነም እሳት ጭስ ሳይሸተኝ ቀርቶም አይደለም። ወይም ፍቅሬ አቅሉን አስቶት በአበባና በስጦታ አንቆጥቁጦኝ ሚዛናዊነቴን አስቶኝም በፍፁም አይደለም። ገና ሳልገባበትም ትዳሬ ሲኦል ሊሆን እንደሚችል የሚንቀለቀል ፍም እሳት ነበልባሉ ሽው ብሎኛል። ገና ሳንጋባ

«ሴት ይሰለቸኛል። ለዛ ነው ትዳር በተወሰነ አመት ኮንትራት መሆን አለበት ብዬ የማምነው።»

«ኮንትራት ያበጀኸውኮ ለትዳሩ ሳይሆን ለውርስ ነው ታዲያ!»

«ያው ናቸው። ለሴት ልጅ ትዳር እና ገንዘብ ያው ናቸው። ቤተሰቦቿ ገና ሽማግሌ ስትልኪ የሚጠይቁት ምንድነው? ልጃችንን በምን ያስተዳድራታል? እሷስ ገና ስታውቅሽ የምትጠይቅሽ ምንድነው? ስራህ ምንድነው? ከስንት አንድ ሴት ናት ማነህ? ምን ትወዳለህ? ምን ትጠላለህ? ምን ትፈራለህ? ብላ የምትጠይቅሽ? ቤተሰቦቿ እሷን በምን እንደምታስተዳድሪ ይሰልሉሻል። እሷ ደግሞ ልጇን በምን እንደምታስተዳድሪላት ትሰልልሻለች። ይኸው ነው።»

ወላፈን አንድ ያዙልኝ!

«መመለስ የማትፈልገው ጥያቄ ከሆነ ይቅርታ አድርግልኝና በምን ተጣላችሁ ከበፊት ሚስቶችህ ጋር?»

«ኸረ ደስ ብሎኝ መልስልሻለሁ። የመጀመሪያዋ ልጅ ካልወለድን ብላ ስትነዘንዘኝ ……» ሳይጨርሰው ከአፉ ቀምቼ

«ልጅ አትፈልግም?»

«በፍፁም!»

«እስከመቼውም እስከመቼውም?»

«እስከመቼውም! እዚህ ብስብስ ዓለም ላይ ያለፈቃዱ ለምን አመጣዋለሁ? ለምን ሰው የመሆን አበሳን ያለፈቃዱ አስጨልጠዋለሁ? እስቲ አንድ ሰው randomly ጠይቂ! ሰው ሆነህ አሁን እየኖርክ ያለኸውን ህይወት ከመኖርና ባለቤቷ ጭኗ ላይ አስቀምጣ እያሻሸቻት የምታስተኛት ነገ እና ትላንት ህይወቷን የማያመሳቅሉባት ድመት ሆኖ ከመፈጠር ምርጫ ቢኖርህ የቱን ትመርጥ ነበር በይው!»

ወላፈን ሁለት ያዙልኝ!!

«ሁሉም ሰው አንድ ዓይነት የህይወት ፈተና እንደማይገጥመው ሁላ ድመትም ሆኖ ባለቤቷ በማማሰያና በፍልጥ የምታራውጣት ድመት መሆን አለኮ!»

«ማን እድሉን ሰጥቶን መረጥን? እናትና አባቶቻችን ወደዝህች ዓለም መከራ ከሚማግዱት ነፍስ ይልቅ ቅንዝራቸው በልጦባቸው ሲላፉ ያረግዙናል። ደህና ስጦታ የሰጡን ይመስል እልልልል ብለው ውልደት ግርዘት ክርስትና ልደት እያሉ ያከብሩልናል። በይፋ welcome to hell !» እጁን በሰፊው ወደፊቱ እያወናጨፈ ዘርግቶ

«ህይወትን እና ተፈጥሮን እንዲህ እንድትጠላ ያደረገህ ምንድነው?»

«ያለውን እውነታ እንጂ ስለግሌ አይደለም ያወራሁት! እና ደግሞ ብዙ personal የሆነ ጥያቄ የምትጠይቀኝ ሴት አትመቸኝም።»

እዚህኛው ላይ ለህይወት ካለው ጨለምተኛ እና መራራ ምልከታ በላይ የጭንቅላቱ ጤንነት ሊያሳስበኝ አይገባም ነበር? መቼም ቢሆን አልፌ እንድረዳው የማይፈቅድልኝ ጥቁር አለት በልቡ ደብቆ እንደሚኖር ሳላገባውም እዚህ ቀን ላይ አውቃለሁ።

ወላፈን ሶስት ቁጠሩ !!

«ፍቅር የሚባል ነገር የለም! ሰዎች ለምግባራቸው የተቀደሰ ስም ሰጥተው ራሳቸውን ሲነሸግሉ ግንኙነታቸውን የሚያሞካሹበት መጠሪያ ነው። በዚህ ዓለም ላይ ያሉ ግንኙነቶች ወይ ሀላፊነነት ናቸው ወይ መጠቃቀም ናቸው። ሀላፊነቴን እየተወጣሁ ነው ላለማለት ወይም ስለሚጠቅመኝ ነው አብሬው ያለሁት ከማለት <ፍቅር> ብለን እንቀባባዋለን።»

«በምንም ጥቅም ላይ ያልተመሰረተ ወይም በሃላፊነት ግዳጅ ያልታጠረ ግንኑነት አኮ!»

«ምሳሌ ጥቀሺ!»

«ለምሳሌ ጓደኝነት! የቤተሰብ ትስስር፣ እንዴ ሁሉም የተቃራኒ ፆታ ፍቅርም በጥቅም ላይ የተመሰረተ አይደለም። የአምላክ ፍቅርስ?»

«አምላክን ተይው! …… (ቡም! 💣🔥🔥🔥ይሄ ወላፈን ብቻ አልነበረም! ፍንዳታ ነበር! ፍንጥርጣሪው ለዓመታት የሚባጅ መርዝ የነበረው ፍንዳታ!) ፈጣሪን እንኳን ተይው! ጓደኝነት በስሜት መጠቃቀም ላይ ነው መሰረቱ! ጓደኛዬ የምትዪው ሰው ወይ ስሜትሽን የሚረዳ፣ በሃሳብ የምትግባቢው፣ ጥሩ ልብ ያለው፣ ወይም ግማሽ አንቺን ውስጡ ያገኘሽበት name it እንደጓደኛ የሚያቆራኝሽን ነገር? ያን ኳሊቲ ውስጡ ባታገኚ ጓደኛሽ ይሆን ነበር? አንድ በስሜት የምትመጋገቢው ነገር እየፈለግሽ ባትቆራኚ ኖሮ ዓለም በሙሉ ጓደኛሽ ይሆን ነበር። አየሽ የስሜት መጠቃቀም ነው። ቤተሰብ ላልሽው ……. ዌል እናትና አባት ግዴታም ሀላፊነትም ነው። የእናት ፍቅር ብለው እንደተኣምር ይሞዝቁለታል። ግዴታዋን ነው የተወጣችውኮ። እንደውም በጣም abuse ሲያደርጉሽ የራሳቸው ንብረት እንጂ የራስሽ ሀሳብና ፍላጎት ያለሽ ሙሉ ሰው አትመስያቸውም! አድገሽ ራስሽን ችለሽ ሁላ ወይ እነሱን የመደጎም እና የማኖር ግዴታ ያለብሽ ፣ ሳትፈልጊ ወልደው ስላሳደጉሽ ውለታ የዋሉልሽ እና ያን ውለታ የመመለስ ግዴታ ያለብሽ ያስመስሉታል። (ይሄን ሲያወራ ምን ዓይነት ልጅነት ይሆን የነበረው? እንዴት ያለ ቤተሰብ ነበር ያሳደገው? ራሴን ጠይቃለሁ። ሴት ልጅ ስትጠይቀው ከማይወዳቸው ጥያቄዎች ዋነኛው ስለሆነ አልጠይቅም!) …………..ልጅ (እዚህጋ ቆየት ብሎ ቀጠለ) እስኪ ልጅሽን ሀላፊነትሽን አትወጪና አስርቢው አስጠሚውና ቀጥቅጪው እና ከዛም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ አብሮሽ ይቆይ እንደሆነ እዪ (በፌዝ ፈገግ አለ) ባገኘው የመጀመሪያ አጋጣሚ ካንቺ ለማምለጥ ነው የሚፈረጥጠው (የመጨረሻው ገለፃ የሚያስበው ብቻ ሳይሆን የኖረው ዓይነት ስሜት ነበረው)……… ተቃራኒ ፆታውን እንኳን አንሸነጋገል። እድለኛ ከሆንሽ በጎደኝነት መሃል ያለው የስሜት መጠቃቀም ሲደመር ወሲባዊ ስሜት መጠቃቀም ሲደመር የቁስ መጠቃቀም!! ብቻውን ፍቅር የሚባል ነገር የለም!!»

ሌሎች ብዙ የወደፊቱ የትዳር ህይወቴን ሲኦልነት የሚገልፁ <ማሳያ ትኩሳቶች> እያወቅኩ እና ፍንጣሪውን እየተለማመድኩ ሰንብቼ ነው ያገባሁት። ሶስት ዋና ዋና ምክንያቶች እና ሌሎች ፍርፋሪ አባሪ ምክንያቶች ነበሩኝ። አንዱ ከሌላኛው ጋር በቀጥታም በጓሮም ይጋመዳል።

ከዋንኞቹ አንደኛው

እንደአብዛኛዋ ማህበረሰቡ <ሳታገባ እድሜዋ አለፈ> የሚባልበትን በህግ ያልተፃፈ የእድሜ ቁጥር እንዳለፈች ሴት ለቤተሰብ እና ለጎረቤት ፣ ለማህበረሰብ፣ ለጓደኛ ………….. ወላ ገና ለሚወለደው ልጄ ስል ነው ያገባሁት!

እንደዛ እኮ ነው! ለእነሱ ነው የምናገባላቸው! ከዛ ኑሮውን እኛ እንኖራለን እነሱ ደግሞ ገሚሱ አገባች ብለው ይደሰታሉ። (አንቺ ደስተኛ ሆነሽ ይሁን አይሁን ግድ የማይለው ይበዛል) የተቀረው ገሚሱ ወደሌላኛዋ ተረኛ እጩ ቋሚ ቀር ምላሱንና ፊቱን ያዞራል!! .... እስክታገባላቸው በምላስም በጥያቄም በነገርም ያንፍሯታል:: ስታገባላቸው ... ይህችኛዋንም አጨብጭበው ይድሩና ደሞ ወደ ቀጣይዋ..... የእኔን ግን ላብራራልሽ ...

አልጨረስንም……………….

@wegoch
@wegoch
@wegoch

#Meri feleke
ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት
(ክፍል ሶስት…………… meri feleke)

ከሳምንታት በኋላ ዝም አለ። በቃ ዝም! በእኔ ቁጥጥር ስር መሆኑን ላለመቀበል መፍጨርጨሩን ተወው። የእኔ እርዳታ የሚሰጠውን የተሸናፊነት ስሜት ላለመዋጥ የሚያደርገውን መንፈራገጥ ተወው። ሳጎርሰው ከምግቡ ጋር የሚውጠውን እልህ ተወው። ሰውነቱን ሳጥበው ከጡንቻው ጋር የሚያፈረጥመውን ትዕቢት አተነፈሰው። መለፍለፉንም ተወው። ዝም ጭጭ አለ። ልክ እንደሌለ ነገር። እንደማይሰማ ፣ እንደማያይ ፣ ምንም ስሜት እንደማይሰጠው ፣ ጭራሽ እዛ እንደሌለ…………. ዝምታው ደስ አይልም ይሸክካል። የተሸነፈ ሲመስል የበቀሌን ጥፍጥና ይቀንሰዋል። ደስ አይልም!

«ወደኋላ ተመልሰሽ ድጋሚ የህይወት ምርጫሽን የማስተካከል እድሉ ቢኖርሽ ታገቢኝ ነበር? ማለቴ ይሄን ትዳር ትመርጪ ነበር?» አለኝ ከብዙ ቀናት ዝምታ በኋላ የገና ቀን ጠዋት መኝታ ቤታችን መስታወቱ ፊት የበዓል ነጭ ልብስ እያለበስኩት ሳለ

«አዎ ሁለቴ ሳላስብ!» አልኩት በልቤ «ያውም መጨረሻው ይሄ መሆኑን አውቄ?» ብዬ ሳልጨርስ የሰማኝ ይመስል

«ላለፉት ዓመታት ስትዪ ወይስ ለመጨረሻዎቹ ወራት?» አለኝ መልሱን እንደሚያውቀው ሁላ ተረጋግቶ

«ለሁለቱም! በእርግጥ መጨረሻው እንደየዋህ ደራሲ ድርሰት መስመሩ ምርጫዬን ያቀልልኛል።» አልኩት! አልከፋውም! እንደውም ፈገግ ነገር አለ። የሆነ የማውቀውን ፈገግታ ፈገግ አለ። የሆነ የድሮው እሱ የሆነ ፈገግታ፣ ያሸነፈኝ ያሸነፈኝ ሲመስለው ፈገግ የሚለው ዓይነት ፈገግታ፣ የሆነ ተንኮል ሲያስብ ፈገግ የሚላት አይነት ፈገግታ………….

«ምን አስበህ ነው?»

«ምንም! ምነው?»

«አውቅሃለሁኮ! የአሁኗን ፈገግታ የምታመጣት ከዲያቢሎስ ጋር የሆነ ነገር ስታንሾካሹክ ነው!»
ከት ብሎ ሳቀ። ከአደጋው በኋላ ለአራት ወራት እንዲህ ስቆ አያውቅም! ዊልቸሩን ወደሳሎን እየገፋሁ እሱ ሳቁን አላቆመም። እንዲህ የሚስቀው ስራ ቦታ የሆነ ፈታኝ እቅድ አቅዶ ሲሳካለት ነው። ወይም በውጤቱ እርግጠኛ የሆነበትን ንድፍ ሲጨርስ

«ምን አስበህ ነው?»

«ራስሽን ግን አይተሽው ታውቂያለሽ? እኔን አንቺ ውስጥ አይተሽው አታውቂም?» አሁንም ሳቁን አላቆመም። «ራሴን አንቺ ውስጥ ሳየው እንዴትኮ ደስ እንደሚለኝ! ያው ክፋትም ደግነትም በሚታየው ድርጊት እንጂ ውስጣችን በተቆለለው ልክ ስለማይመዘን እንጂ ሃሃሃሃሃሃሃ ሙች እኔ እንኳን የምቀናብሽ ክፉ እኮ ነሽ!»

ተመስገን! ከአራት ወር በኋላ ዲያቢሎሱ እሱ ተመለሰ። ዝም ከሚለው ወይም ከሚንፈራገጠው እሱ ይሄ ይሻለኛል። ቢያንስ ይፈትነኛል። እንዳስብ ያደርገናል። ጤንነት አይመስልምኣ? ከምጠላው ሰውዬ ጋር ማውራት መናፈቅ? ለማንም ጮክ ብዬ ባወራው ጤንነት አይመስልም። ጭንቅላቴን የሚፈትነኝ ወሬው ዝም ሲል ይናፍቀኛል።

«ማንም በድርጊቱ እንጂ በሃሳቡ አይዳኝም! ወይም ቢያንስ ሀሳብህ የአፍህን በር ለቆ ካልወጣ ማንም ላይ የክፋት በትርህ አሻራ አያርፍም!»

«ያ ልክ ነው ትያለሽ ታዲያ? ሰው መዳኘት የነበረበት በሃሳቡ እንጂ በድርጊቱ ነበር? ምን እሩቅ ወሰደሽ ራስሽን ምሳሌ አድርጊኣ? አሁን ፀሃይ (ሰራተኛችን ናት። ሳሎን ውስጥ ጉዝጓዙን እየጎዘጎዘች ስሟን ሲጠራ ቀና ብላ አየችን) እንዴት ያለች መልአክ ሴት ብትሆን ነው ይሄን ሰይጣን ባሏን ፈጣሪ ጀምሮ ሰጥቷት እንደማጠናቀቅ እንዲህ የምትንከባከበው? ብላ ነው የምታስበው! አይደለም ፀሃይ? (ፀሃይ ምን መመለስ እንዳለባት ግራ ገብቷት አይኗን ስታጉረጠርጥ እሱ ቀጠለ።) ድርጊትሽ አልሸወዳትም ታዲያ? አንቺ በመልካምነት ጅራፍ በቀልሽን እያሳረፍሽብኝ እንደሆነ እኔም አንቺም ሰይጣንም እግዜርም እናውቃለን። (ሳቅ ብሎ) በነገርሽ ላይ ነገሩን ለምሳሌ አመጣሁት እንጂ እየወቀስኩሽ አይደለም። ታዲያ የሚዳኘው አካል ፈጣሪ በይው ሊዳኝሽ የሚገባው በየትኛው ነው? በድርጊትሽ እንዲዳኝሽ ምኞቴ ነው (ሳቅ ብሎ) ካለበለዚያ እንደተባለው ሲኦል ካለ እዛ ስንሄድ አለቃዬ ሁሉ ልትሆኚ እንደምትችዪ አስበሽዋል?»
ፀሃይ ወሬው ይሁን ግራ የገባት ወይም እኔ ግራ የገባኋት መጎዝጎዟን አቁማ አይኗን ጎልጉላ ቆማ ታየኛለች። እንደማማተብም አደረገች ነገር።

እንዲህ አይነት ወሬዎቹ ናቸው እየጠላሁት እንዲናፍቀኝ ፣ ደሜን በብስጭት እያንተከተከው እንኳን ዝም እንዳይል እንድመኝ የሚያደርጉኝ። አንዳንዴ የሱን ጭንቅላት ሌላ ልብ ላለው ሰው ቢሰጠው ብዬ ተመኝቼ አውቃለሁ። እሱ ጭንቅላት እንጂ ልብ የለውም! ለነገሩ ሰይጣንምኮ ስማርት ነው።

«የሰው ልጅ የሀሳቡ ውጤት ነው። ድርጊቱ የሀሳቡ ልጅ ነው። ያ ማለት መልካምን የሚያደርጉ ሰዎች ሀሳባቸው ውስጥ ክፋት የለም ማለት አይደለም። ተፈጥሮ በሙሉ ሁለቱንም ፅንፎች የያዘች ናት። ውልደት እና ሞት፣ መነሳትና መውደቅ፣ ውሸትና እውነት፣ ፍቅርና ጥላቻ፣ ጨለማ እና ብርሃን፣ ቀንና ማታ፣ ክፉና መልካም……….. የሰውም ልጅ የእነዚህ ነገሮች ስብጥር ነው የጥሩ እና የመጥፎ ፣ የክፉና የመልካም፣ የጨለማ እና የብርሃን……… ጥያቄው የትኛው ያመዝናል ነው። የትኛው አሸንፎ በተግባርህ ይገለፃል ነው ጥያቄው! ሲጥ አድረሽ ጨርሺው የሚለኝን ክፉ ሀሳቤን አቅፈሽ ሳሚው በሚል መልካም ሀሳቤ ከረታሁት ሊቆጠርልኝ የሚገባው ያ ነው። አቅፌ ስስምህ አንተጋ በሚፈጠረው ስሜት ጥቂት ደስታን መቃረሜን ፈጣሪም ይቅር ይለዋል።» ይስቃል።

ከእርሱ ጋር ባሳለፍኩት ሰባት ዓመት የተማርኩት አንድ ነገር የማንም ሀሳብ አሸናፊ የማንም ሀሳብ ተሸናፊ አይደለም። በአብዛኛው ተስማምተን አናውቅም። ለሰዓታት ልንጠቃጨቅ እንችላለን። መጨረሻው ሁለት ፅንፍ ነው። የማሸነፍ እና የመሸነፍ አይደለም። ሙግታችንም የእኔን ልክነት እመን ወይ ተቀበል ግብ ግብ አይደለም። በቃ በህይወት ውስጥ ስላሉን የተለያዩ ምልከታዎች ሀሳብ መቀያየር ነው። ላለመሸነፍ ግብ ግብ የለውም።

«አንቺ ግን ፈጣሪ ብለሽ የምታምኚው በከረሜላ እንደምትደልዪው ህፃን ጅል ነው እንዴ የሚመስልሽ?»

« እ እ! ጅል ሳይሆን መሀሪ ......ተደልሎ ሳይሆን ራርቶ ይቅር የሚል ......እንደዛ ነው የሚመስለኝ።» ብዬ ቁርስ ላበስል ወደጓዳ ልሄድ ስል

«እስኪ ተያት ዛሬ ፀሃይ ትስራው ቁርሱን! »

«ለምን? ምን የተለየ ነገር ተገኘ ዛሬ?» በጥርጣሬ አየሁት

«ምንም! እንጫወት ብዬ ነው። አንቺም የምትፈልጊውን ላታገኚ ድካምሽ በዛ እና አሳዘንሽኝ!»

«ምንድነው የምፈልገው?»

«አንቺ የምታውቂኝን ያህል አውቅሻለሁኮ! »

«እኮ ምንድነው የምፈልገው?»

«ይቅርታ አድርጊልኝ የምትለዋን አረፍተ ነገር ሃሃሃሃ ተሳስቻለሁ! አንቺ መልካም ሴት ነሽ ይቅር በይኝ እንድልሽ? አይደለም በይኝና ተሳስቻለሁ እልሻለሁ።» አሁን መሳቁ የእኔ ተራ ሆነ።

«ስለእውነት የምፈልገው ምን እንደሆነ በትክክል አላውቅም። የሆነኛው ቀን ግን አዎ ይቅርታ ትጠይቀኛለህ ብዬ እጠብቃለሁ።»

«በፍፁም አላደርገውም! <ለምን ደግ እየሆንሽ ለበቀል የተሰጠሽን እድል ታባክኛለሽ? ስልሽ ያልሽን ታስታውሻለሽ? በእኔ ክፉት ክፉትህን ልታቀል? በእኔ ሀጢያት በደልህን ልትሰርዝ? በፍፁም ያን ደስታማ አልሰጥህም!!> ነበር ያልሽኝ። እራሴን አንቺ ውስጥ አየዋለሁ የምልሽኮ ለዚህ ነው። እኔም ያን ደስታ በፍፁም አልሰጥሽም! ተሳስቻለሁ ስልሽ በእኔ ስህተት ያንቺን ልክነት ልታደምቂ? አጥፍቻለሁ ስልሽ በእኔ ጥፋት ያንቺን ፅድቅ ልትፅፊ? በፍፁም ያን ደስታ አልሰጥሽም! Come on you know me better!»
«ፀሃይ ቁርሱን አብስይልንማ!» አልኳት ጉዝጓዙን መጎዝጎዙን ከጨረሰሽ ብትቆይም ንፁሁን ጠረጴዛ እየፈተገች እያፀዳች የነበረችውን ፀሃይ

«ምን ላብስል?»

«ከአራት ወር በፊት ለበዓል ሳትጠይቂኝ ታበስዪ እንደነበረው የበዓል ቁርስ!» አልኳት ወደወሬዬ ለመመለስ ቸኩዬ ሶፋው ላይ እግሬን ደራርቤ እየተቀመጥኩ። ለወሬ ፊቴን ወደ እርሱ ስመልስ ድክም ብሎ እየሳቀ

«ነርቭሽን ነካሁት አይደል?»

«በተዘዋዋሪ እንደበደልከኝ ማመንህ ግን ገብቶሃል? ይቅርታ በአፍህ አልጠየቅከኝም እንጂ በደልህን እኮ ታውቃለህ! ከደቂቃዎች በፊት አመንክ!» አልኩት

«እ እ! ራስሽን አታፅናኚ እኔ መጀመሪያም እንዳንቺ ጥሩ ሰውነቴን ለመግለጥ ራሴን የማሰቃይ ሰው አልነበርኩም ታውቂኛለሽ። ጥሩም መጥፎም አይደለሁም ራሴን ነኝ! የእኔ ምርጫ እና ድርጊት ከጎዳሽ ተጠያቂዋ ራስሽ እንጂ እኔ አይደለሁም! በምርጫሽ እንጂ አስገድጄሽ የዚህ ህይወት አካል አላደረግኩሽም! ማዘን ካለብሽ በምርጫሽ እዘኚ! በምርጫዬ ተሳስቻለሁ ብለሽ ካመንሽ ራስሽን ይቅርታ ጠይቂው። አንቺ ለራስሽ ያላመንሽውን ጥፋትሽን በእኔ አሳበሽ ራስሽን ነፃ አታውጪ! ይቅርታ የምትጠይቂው ለስህተት ነው። ተሳስቼ ያደረግኩት ነገር የለም። አውቄ እንጂ።» ይሄን ካለ በኋላ እያንዳንዱ ቃላት እኔጋ የሚሰጠኝን ስሜት ስለሚያውቅ ፈገግ አለ በድል አድራጊነት።

«የሰይጣን ጭንቅላት እንዳለህ ግን ታውቃለህኣ?»

«እንዳንቺ የምትፈትነኝ ሴት ኖራ እንደማታውቅ እንደምታውቂው!»

«ብትሞት!»

«እመኚኝ ይደብርሻል። ማን እንዲህ ያለ ሰይጣናዊ ጨዋታ ያጫውትሻል?»

«እመነኝ አይደብረኝም። ሰይጣናዊ ጨዋታህን ለ7 ዓመት ተግቼዋለሁ።»

«እና በተዋዋሪ ደቀመዝሙሬ መሆንሽን አመንሽ ማለት ነው?»

በሩ ተንኳኩቶ ፀሃይ የሆኑ የማላውቃቸው ሴትዮ አስከትላ ገባች። ማን እንደሆኑ ከመጠየቄ በፊት የእሱ ድንጋጤ ማንም ይሁኑ ምኑ ብቻ ቅዠቱ እንደሆኑ ነገረኝ!!

«አስወጧት! አስወጡልኝ!» ጮኸ ……..

በሚችለው ሁሉ ተወራጨ። እየሆነ ያለውን ነገር ከመረዳቴ በፊት ዘሎ ከዊልቸሩ ተነስቶ ሴትየዋጋ መድረስ ይችል ይመስል ደምስሮቹ ተገታትረው ባለ በሌለ ሀይሉ ተወናጭፎ ወደፊቱ ወደቀ። ቢችል በዝህችው ቅፅበት አንቆ የሚገድላቸው ነው የሚመስለው! ሴትየዋን ከማስወጣት እሱን ከማንሳት እየሆነ ያለውን ከመረዳት ምኑን እንደማደርግ ግራ ገብቶኝ መሃል ላይ ስዋልል

«በናትሽ አስወጫት! እባክሽ?» አለ አቅም ባጣ ስሜት። ፀሃይ ሴትየዋን እያዋከበች ልታስወጣት ስትሞክር ለሰከንዶች የሴትየዋን ፊት አየሁት። ምንም ስሜት የሌለው ሙልጭ ያለ ፊት ……….. ተከትያቸው ልሄድ አሰብኩ። ያሰብኩት ገብቶታል።

«እባክሽ?» አለኝ። ተስፋ በቆረጠ የልመና ድምፅ

ተመልሼ አጠገቡ መጣሁ። ሴትየዋ ሄደች። ላነሳው ስሞክር። «ተይኝ!» አለኝ።

«እሺ አልተጎዳህም?» አልኩት እንዳወዳደቁ ከአደጋው ሳይሰባበር የተረፈ አጥንት ካለ እንክትክት የሚል ነበር የሚመስለው።

«ደህና ነኝ! እግሬን ብቻ ዘርጊልኝ» አለ! ሲወድቅ የታጠፈ እግሩን ዘርግቼለት ምንጣፉ ላይ በጀርባው ተስተካክሎ እንዲተኛ አድርጌው አጠገቡ በጀርባዬ ጋደም አልኩ። ፀሃይ «አስወጥቻቸዋለሁ» እያለች ወደሳሎን ስትገባ ወለል ላይ በጀርባችን ተጋድመን ስታየን ሳትፈልገው የግርምት ድምፅ አመለጣት። <ሰዎቹ ለይቶላቸዋል> አይነት ነው ግርምቷ።

«እባክሽ? በናትሽ? ቀድቼ ሁላ ደጋግሜ ብሰማው ደስ የሚለኝ ቃል! ጆሮዬን እኮ ነው ያላመንኩት! አንተ? እባክሽ?»

«ደስ አለሽ?» ድምፁ ቅድም እንደዛ የተሸነፈው ሰው ድምፅ አይደለም።

«አልዋሽህም ደስ የሚል ስሜት አለው። ካወቅኩህ ጀምሮ ማንንም ስለምንም ለምነህኮ የምታውቅ ሰው አይደለህም! እኔና አንተ አንወሻሽማ? የሆነ ቦታ ድክመት እንዳለህ ማወቅ ደስ የሚል ስሜት አለው። ተሸንፈህ አይቼህ አላውቅም። እሱኛው የሰጠኝን ስሜት አላውቀውም።»

«እና ተሳሳትኩ? ሲኦል ብንገናኝ አለቃዬ አትሆኚም?»

«ማናቸው ሴትየዋ?»

«ሲዖሌ ናት። ገሃነም! »

«ምንህ ናቸው? እናትህ?»

«ሲዖሌ አልኩሽኮ!»

አውቀው የለ?? በቃ አይመልስልኝም! አይነግረኝም። በጀርባዬ እንደተንጋለልኩ እጁን ፈልጌ እየያዝኩት እሱ ሳያውቅ ሴትየዋን እንዴት ላገኛቸው እንደምችል አስባለሁ።

«እ እ አታባብዪኝ! አትዘኚልኝ! እረፊ !! እኔና አንቺ ይሄን ጨዋታ አንጫወትም!» አለ።እንደሌላ ጊዜው እጁን ሊያስለቅቀኝ ግን አልተወራጨም። ቀጠል አድርጎ «የምታስቢውን ተይው። አይጠቅምሽም ልታገኛት አትሞክሪ»

....... .......አልጨረስንም…………………………

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት
(ክፍል አራት ………. ሜሪ ፈለቀ)

ለመጀመሪያ ጊዜ በተያየን በአስረኛው ደቂቃ ነው <ላግባሽ> ያለኝ። የሶስተኛ ታናሼን ሰርግ ልታደም አንደኛው የከተማችን ሆቴል ነበርኩ። የምሳ ቡፌ ከተነሳ በኋላ ማንም ሳያየኝ ከአዳራሹ ውልቅ ብዬ እዛው ህንፃ ላይ ያለ ሬስቶራንት ውስጥ ገባሁ። ቢያድለኝኮ የአክስቶቼን ውግምት የሆነ ዓይን መሸሼ ነበር። ገና ወንበር ስቤ ከመቀመጤ ከየት መጣች ሳልላት አንዷ አክስቴ

«ምነውሳ ያን ከመሰለ ፌሽታ ተነጥለሽ እዚህ ብቻሽን?»

«ቡና መጠጣት ፈልጌ ነው! አንቺስ?»

«እኔማ ስልክ ላወራ ወጥቼ ስትዘልቂ አይቼሽ ነው። በይ እኔ ልመለስ እናቴ!» ብላ ፊቷን አዙራ ስትሄድ በግልግል ልተነፍስ የጀመርኩትን ትንፋሽ መለስ ብላ ስቅታ አደረገችብኝ። «እንግዲህ ሚጡዬ ታናናሾችሽን ሁሉ ድረን ጨረስን። ለሴት ልጅኮ ተፈጥሮም ገደብ ይጥላል! እንደው ምርጫው ይቅርብሽና ከአንዱ ሰብሰብ በይ ለእናትሽ ስትዪ……….ላንቺምኮ ዓለም ነው» (የሆነ ያዘነችልን ታስመስለዋለች። <ላንቺ ብዬ ነው> የሚሏት ዓይነት ቅብ)

«የሚመረጥ አምጥታችሁ ያማረጣችሁኝኮ ነው የምትመስሉት በእርግጠኝነት ስታወሩ። ካላገባሽ እያልሽ በገባች በወጣች ቁጥር በነገር ስትነድፊያት ልጅሽ መጨረሻዋ የሆነው አምስት ማቲ ታቅፋ ተመልሳ ያንቺ ጉያ መታከክ አይደል? ድንቄም ዓለም! ይሄንን ነው ዓለም የምትሉኝ?» ከጀርባዬ ፍቅፍቅ ብሎ የሚስቅ ሰው ድምፅ ስሰማ ነው ሬስቶራንቱ ውስጥ ያለው ገሚሱ ተጠቃሚ ሊሰማኝ በሚችል ድምፅ እየጮህኩ እንደሆነ የታወቀኝ። እሱ ነበር!

ለወትሮ ምንም ቢሉ መልስ አልነበረኝም። ምክር፣ ወቀሳ፣ ሽርደዳ ……… <እፈልግሻለሁ> ብለው እቤታቸው ጠርተውኝ ሁላ ሲግቱኝ ዝም ነበር መልሴ። <ለትልቅ ሰው መልስ አይሰጥም> ፣ <ቢሰድቡሽም ፣ ቢገርፉሽም፣ ጭንቅላትሽ ውስጥ ተደፍድፎ ቀስ በቀስ የሚሸርፍሽን መርዝ በቃላት ቢያቀብሉሽም አዋቂዎች ላንቺ ብለው ነው…….> ተብዬ ነዋ ያደግኩት። ለአክስቴ ሌላ የምትለጥፍልኝ ስም ሰጠኋት። ደንግጣ የጎስት በመሰለ ሽውታ ሽውውው ብላ ወጣች። ሳቁን ሳያቋርጥ አጠገቤ ያለውን ወንበር ስቦ ተቀመጠ።

«ሚጡ ብለውሽ ደግሞ ካላገባሽ ሄዶላቸው ነው?»

«ሁሉንም እየሰማህ ነበር ማለት ነው?»

«እንደዛ ነገር። ሴትየዋንኮ ቆሌዋን ነው ያበነንሽባት። ለሚቀጥሉት ተከታታይ ቀናት በህልሟ ሁሉ ነው የምትመጪባት። እና አንቺ ያላገባሽው ሴትየዋ እንዳሉት ስታማርጪ ነው? ለትዳር ያለሽ ምልከታ ስለሚለይ ነው? ማግባት ስለማትፈልጊ ነው?»

«ዝም ብሎ ትዳር ውስጥ ይገባል እንዴ? በእርግጠኝነት አምነህ ህይወትህን የምታጋራው ሰው በህይወትህ ካልተከሰተ እድሜ ስለሄደ፣ ታናናሾቼ ስላገቡ፣ ቆማ ቀረች ላለመባል …….. ያገኘሁትን አፍሼ አገባለሁ? ቆይ ትክክለኛው ሰው ካልተገኘ ሳያገቡምኮ መኖር ይቻላል። » የመጨረሻውን ዓረፍተ ነገር ስጨርስ ለማላውቀው ሰውዬ ማወቅ የሌለበትን እየዘበዘብኩ እንደሆነ ገብቶኛል።

«ሳያገቡ መኖር ይቻላል!! የቻሉ ሴቶችም ይኖራሉ። አንቺ ትችያለሽ ወይ ነው ጥያቄው? መቻልና አማራጭ በማጣት ሁኔታን መቀበል የተለያየ ነገር ነው። ትዳርን ልመሰርት የምመኘው ትክክለኛ ሰው በህይወቴ ካልተከሰተ ትዳር እንዲኖረኝ አልፈልግም የሚል አቋም ኖሮሽ ሳታገቢ ስትኖሪ በውሳኔሽ ደስተኛ ነው የምትሆኚው። ባልየው ቢመጣ ደስ ይልሻል ቢቀርም ግን በውሳኔሽ አትፀፀቺም።< ያ የባለፈው ሰውዬ እኮ ትንሽም ቢሆን ይጠጋጋ ነበር ምንአለ እሱን ባገባሁት?> አትዪም። እንደቅድሟ ዓይነት ሴትዮ መጥተው ሲወርፉሽ እንደቅድሙ አትጨሺም። የቤተሰብ ወይ የማህበረሰብ expectation ግድ አይሰጥሽም። ምርጫ አጥተሽ ሲሆን መጀመሪያ ነገር ውሳኔሽን አታምኚውም። ሰርግ ባየሽ ቁጥር የምትቆዝሚ ፣ አዳራሽ ለቀሽ ወጥተሽ ሬስቶራንት ውስጥ የምትደበቂ፣ ደስታ የራቀሽ ሰው ነው የምትሆኚው።»

የተናገረው እውነት ከመሆኑ በላይ ትንተናው ለወሬ የሚጋብዝ ስለነበር አልጎረበጠኝም። ይልቅስ እንደአብሮ አደግ ወዳጃማቾች ጨዋታ መቀባበል ጀመርን።

«እሱ ልክ ነህ ግን ምርጫ ስታጣም ያለህበትን ሁኔታ ተቀብሎ መኖር ሽንፈት አይደለም እንደውም ብርታት ነው። መንነህ ገዳም ካልገባህ ወይም የተለየ ባህልና እምነት ያለው ማህበረሰብ ያለበት ቦታ ካልተሰደድክ በቀር ግን እንዴት ነው <የማንም expectation ግድ አይሰጠኝም> የሚባለው። ልክ የሆነ አካሌ የጎደለ ያህል እኮ ነው ባል የሚባለው ፍጡር ስለጎደለ ከምድር በረከት የጎደልኩ የሚያስመስሉት! በግልፅ <እስኪ ተጠመቂ> ፣ <ለአምላክ የሚሳነው የለም በንፁህ ልብ ፁሚ ፀልዪ> ይሉኛል። ዞር ስትልላቸው <ይህቺን የመሰለች ልጅ ቆማ መቅረቷ ነው ምፅ!! > ይባባሉብሃል።»

«እንዴ ቆይ ግን ምን ያህል ብታረጂ ነው?»

«34»

«ያነሳሽበትን ስንደምረው ገፍተሻል!»

«ባክህ ሳልኖርበትም ቀንሼበትም አያዋጣኝም!»

« ላግባሽ!» ጥያቄ አይደለም። ኮስተር ያለ፣ እርግጠኝነት ያለበት እንደጥቆማ አይነት ነገር……… ልክ የሆነ ባለሙያ <እንዲህ ብታደርግ ይጠቅምሃል!> ብሎ እንደሚሰጠው አይነት ምክር አዘል ጥቆማ!

«ጭራሽ?»

«የእውነቴን ነው! መቼም በ34 ዓመት የሰው ልጅ ተጠንቶ የሚታወቅ ፍጡር አለመሆኑን አልደረስኩበትም አትይኝም እና ሳንጠናና ሳንፈታተን አትዪኝም! አልጋ ላይ እንዴት ነሽ?»

«አንተ? ጤናም የለህ እንዴ?» ከማፈሬ የተነሳ የሰማው ሰው እንዳይኖር ዞር ዞር አልኩኝ። እሱ ምንም ወጣ ያለ ነገር እንዳላወራ ሁላ ቀጠለ።

« ኦህ ለካ ስም አልተለዋወጥንም። አዲስ እባላለሁ ፣ በሚቀጥለው ሳምንት 42 ይሆነኛል። አልጋ ላይ ጎበዝ ነኝ! ከፈለግሽ አሁኑኑ ወጥተን ላሳይሽ እችላለሁ። (ኮስተር ብሎ ነው የሚያወራው እንደልክ) ፣ ስራዬን ማወቅ ከፈለግሽ ዝርዝሩን ወደፊት አስረዳሻለሁ በጠቅላላው ነጋዴ ነኝ። ይሄ ችርቻሮ ነጋዴ ነገር አይደለሁም። ሀብታም ነኝ፣ በቁስ የምትደሰቺ ዓይነት ሰው ከሆንሽ አብረኸኝ ሾፒንግ ውጣ አትበይኝ እንጂ የተዘባነነ ኑሮ አኖርሻለሁ። እ እ እ ምን ቀረ ምን ቀረ? የትምህርት ደረጃዬን ማወቅ ከፈለግሽ ደረጃ የለኝም! ከዘጠኝ ነው የተውኩት……….በተለያየ ምክንያት ከሀገር ስለምወጣ ቋንቋ ተምሬያለሁ። ሁለቴ አግብቼ ነው የፈታሁት። ሀይማኖት የለኝም! ዋና ዋናው ይኼ መሰለኝ። ማወቅ የምትፈልጊውን እነግርሻለሁ።»

የሚያወራው ከልቡ መሆኑን አልተጠራጠርኩም። ጤንነቱን እንጂ። አፌን ከፍቼ ነው በከፊል ድንጋጤ በከፊል ግርምት በብዙ ግራ መጋባት የማየው። ከእኔ መልስ እየጠበቀ መሆኑ ሲገባኝ ሳቄ መጣ

«ምን? እንደስራ ሲቪ ስለራሴ እንድነግርህ አይደለም አይደል እየጠበቅህ ያለኸው?»

«ትዳርን ምን ለየው? እንተዋወቅ እንጠናና የምትሉት ከዚህ የተለየ የሚያሳውቃችሁ ነገር አለ? ያው ሳታገቢ የምትኖሪውን ህይወት ከማራዘም ውጪ! ያውኮ ነው ይሄን ይሄን ያሟላ ብለሽ ልክ እንደ ስራ ቀጣሪ መስፈርት ታስቀምጫለሽ የሚመጣው ሰውዬ መስፈርትሽን ካለፈ ባል ሆኖ ይቀጠራል። ቆይ እስኪ አንቺ አጋሬ ነው ብለሽ እየጠበቅሽው ያለሽው ሰውዬ ምን አይነት ነው?»

«definitely እንዳንተ ዓይነት አይደለም። ጉረኛ፣ ሲያወራ ግልብ፣ ሁለት አግብቶ የፈታ …….. የለበትም!!»

ከት ብሎ እየተንፈራፈረ ሳቀ።
« ቅድም ስላላገባሽ እንደጎደሎ በመቆጠርሽ ይህን ማህበረሰብ ስትወቅጪው ነበር። ራስሽው ግን አግብቶ መፍታትን የሆነ ተላላፊ በሽታ ይመስል ግፍግፍ እያደረገሽ እንደጉድለት አየሽብኝ ሃሃሃሃሃሃ»
«ይሄና ያ ይለያያል። በ42 ዓመት ሁለቴ አግብቶ መፍታት ቀይ መብራት ነው።»

«ልዩነቱ ኩነኔውን ተቀባይ ቦታ መሆንና ኮናኝ ቦታ መቆም ነው። እንቁላል የሰረቀ ሌባ እገሌ በሬ ሰረቀ ቢሉት <እና ለቀቃችሁት?> ይላል። ለራሳችን ይገባናል ብለን የምናምነው ምህረት ለሌላ ሰው ሲሆን ምህረት ለእርሱ በደል ውድ ናት ብለን እናስባለን። አየሽ ልዩነቱ የቆምንበት ቦታ ብቻ ነው።» የእውነት የጥፋተኝነት ስሜት ተሰማኝ። የሆነ ቁስሉ ላይ ጨው የነሰነስኩ መሰለኝ።

«በጣም ይቅርታ ………» ብዬ ከመቀጠሌ በፊት እየተርገፈገፈ ስቆ

«ኸረ እኔ እውነታውን ነው እንጂ የነገርኩሽ ከፍቶኝ አይደለም። ፈልጌ ነው የፈታኋቸው። ስለፈታኋቸውም ደስተኛ ነኝ።» ብሎ የሆነ ልክ የሆነውን ዓለሜን ልክ ባልሆነው ዓለሙ ቀላቀለብኝ። በውስጤ ተነስቼ ደህና ሁን ብዬው መሄድ አስባለሁ ግን ተጎለትኩ።

………………አልጨረስንም…………………

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት
(ክፍል አምስት ………. ሜሪ ፈለቀ)

«እኔ ደስ የሚለኝ ጓደኛሞች ብንሆን ነው።» አልኩት እቤቱ ይዞኝ የሄደ ቀን

«እረፊ! እኔ አንዴ ልብስሽን አውልቄ ጭንቅላቴ ውስጥ ስዬሻለሁ። ጓደኛሞች እንሁን ብልሽ ውሸቴን ነው። ገና ሳይሽ የቀሚስሽን ሶስት ትንንሽዬ ቁልፎች ፣ ቀጥሎ ዚፑን …….. ወደታች ባወልቀው ወይ ወደላይ የቱ ይፈጥናል? አስቤ ጨርሻለሁ!» የገረመኝ ክፍት አፍነቱ አይደለም። እሱን እየለመድኩት ማፈር ትቻለሁ፣ በዛ ላይ ሌላ ሰው ሲያወራው የሚያሳፍረኝን ነገር እሱ ሲያወራው አለው የሆነ ልከኛ ወሬ የሚያስመስለው ድምፀት። በትክክል ቀሚሴ ከጀርባው የዚፑ መጨረሻ ማጅራቴ ጋር ትንንሽዬ ሶስት ቁልፎች መኖራቸው ነው። ከላይ ደርቤ የነበረውን ኮት ካወለቅኩት 5 ደቂቃ አይልፍም ነበር። ገርሞኝ አፍጥጬ ሳየው። <ነግሬሻለሁኮ> አይነት ፊቱን እና ትከሻውን ሰበቀ።

ቤቱ <እንደማንኛውም ፊልሞች ላይ እንደምናያቸው የሀብታም ፎቆች> ከሚባሉት በይዘትም በስፋትም በጥራትም በሶስት ክፍል ቤት እናትና አባቴን ጨምሮ ለስምንት ላደግኩት እኔ (በዝህችም ጥበቷ ክረምት ላይ የአክስት ልጅ ፣የአጎት ልጅ ፣ የክርስትና ልጅ ፣ የአበልጅ ………… የልጅ ብዛት ቤቷን እንደጉንዳን ይወራታል።) አፌን ከፍቼ የምፈዝበት አይነት ነው። አልተገረምኩም። እንደዛ ዓይነት ቤት እንዳለው ነግሮኛል። የገረመኝ እሱም ያልነገረኝ ሁለት የቤቱ ክፍሎች ናቸው። አንደኛው የአንድ ትልቅ ትምህርት ቤት ላይብረሪ የሚያክለው ሰፊው የቤቱ ውስጥ ላይብረሪ ነው። መሃከሉ ላይ ሰፋ ያለ ኮምፒውተሮችን የተሸከመ ጠረጴዛ በአራት ምቹ ወንበሮች ተከቦ ተንጣሏል። አትርገጡኝ የሚለውን የመሬቱን ምንጣፍ ጫማውን አውልቆ ሲገባ አውልቄ ተከተልኩት። የሆነ የተቀደሰ ቦታ የሚገባ ነው የሚመስለው። ከምን ጀምሬ የቱን እንደምነካ ግራ ገባኝ። በቋንቋ ፣ በይዘት፣ በፀሃፊው ስም ……… በስርዓት ተደራጅተው ነው የተቀመጡት። እስካሁን ያላየሁበትን መጀነን ፊቱ ላይ አገኘሁት።

«ምን ያህሉን አንብበሃቸዋል?»

«ቢያንስ 35%! አማርኛዎቹ በቁጥር ነው የቀሩኝ።» አማርኛዎቹጋ ሄጄ ያነበብኳቸውን ለመቁጠር ሞከርኩ። ያው እንደማንኛውም ማንበብ እንደሚችል ኢትዮጵያዊ <ፍቅር እስከመቃብር> እና <ዴርቶጋዳ> ን ሁለት ብዬ ከሀምሳ የማይበልጡ መፅሃፍትን በዓይኔ ቆጠርኩ። እንግሊዘኛውን ያው ተውኩት።

ሌላኛው ክፍል የወንበሩ ቁጥር ከማነሱ ውጪ በሲኒማ ቤት ቅርፅ የተሰራው ፊልም ማሳያ ክፍል ነው።

«ዶክመንተሪ ፊልሞች እወዳለሁ። ማየት ከፈለግሽ መርጬ ልጋብዝሽ?»

«በኢቲቪ ከታዩት <የጀግናው ሰራዊታችን ፍዳ ዶክመንተሪ፣ የታላቁ ኢህአዲግ ወደር የለሽ ትዕግስት፣ ህገመንግስቱን ለመናድ የታጠቁት ሀይሎች ሴራ …..> ምናምን ከሚሉት ውጪ ዶክመንተሪ ማየቴንም እንጃ። ወይም አይቼ ሊሆን ይችላል። ዶክመንተሪ ይሁን ዶክመንቴሽን ወይም ጥናታዊ ፅሁፍ ልዩነታቸው ምን እንደሆነ ስለማላውቅ እኔእንጃ!» ፈገግ ብቻ ነው ያለው። ብዙ ሰዎች እነሱ በብዙ የሚያውቁትን ነገር የማያውቅ ሰው አለማወቁን ሲነግራቸው የሚስቁትን <ከእኔ በላይ ላሳር> ዓይነት ሳቅ አልሳቀም። በአንደኛው ጥግ ለዓይን እሩቅ ሆነው ከኔ ቁመት በጣም በላይ ከተቆለሉት የሸክላ ሲዲዎች ውስጥ አንዱን እያነሳ

«ከቆዩት ውስጥ ልጋብዝሽ! » ብሎ «night and fog» የሚለውን መረጠ። ማጫወቻው ላይ አድርጎ ሲዲውን የምትጫነዋን ቀጭን አናቷ ድርብ ብረት ሲዲው ላይ ለቆት መብራቱን አጠፋፍቶ እጄን ይዞኝ ከፊት ለፊት ካሉት ወንበሮች መደዳ አስቀመጠኝ። በሹክሹክታ

«የሚጠጣ ምን ትፈልጊያለሽ? መብላት የምትፈልጊውስ ነገር?»

«ፈንድሻ ቢኖር፣ ከዛ ደግሞ ኮካ!» ያልኩት ለጨዋታ ነበር። በስልኩ መልእክት ላከ። አስር ደቂቃ ሳይሆን ቅድም ጓዳ ያየኋት ሴት ያዘዝኩትን ይዛ መጣች።


**
የዛን እለት ………. መጀመሪያ ያየሁት እለት ……… ጤንነት እንደጎደለው ሰው ያየኝ ቀን ላግባሽ ያለኝ እለት…….. እንደእኔ ሀሳብ ጥዬው በሄድኩ፣ እንደእኔ እምነት <ልክ ካልሆነ ሰው> ጋር ተጨማሪ ደቂቃ ባላባከንኩ ፣ እንደእኔ ልምድ ከአፉ የሚወጡት ቃላት አርባ ክንድ ከእርሱ ባራቁኝ ፣ እንደ እኔ አስተዳደግ ይሄ ሰው የብዙ የህይወት መርሆቼ ፉርሸት ነበር። ተጎለትኩ አላልኳችሁም? ለሰዓታት ስለተለያዩ የማህበረሰባችን ምሰሶ አስተሳሰቦች እና እምነቶች ስናነሳ እና ስንጥል ለሰዓታት ተጎለትኩ።

«አልተሳሳትኩም አየሽ! መልክ ብቻ አይደለሽም ታስቢያለሽ!» አለኝ በመሃል

«ደሞ ይሄ ምን ማለት ነው?»

«ቆንጆ ሴት ሳይ ከራሴ ጋር አስይዛለሁ። እወራረዳለሁ። ይህችኛዋ መልክ ብቻ ናት፣ ይህችኛዋ ግድ የለህም ከመልኳ ጀርባ አሪፍ ጭንቅላት አለ፣ ውይይይ ይቺኛዋ ደግሞ የራሷ ሀሳብ የላትም የሰዎችን ጭንቅላት ተውሳ ነው የምታስበው ……… ዓይነት ውርርድ! አንዳንዱ እምነትሽን ብትጠይቂ የሚናድብሽ ስለሚመስልሽ በፍርሃት ያለምክንያታዊነት ሙጭጭ ከማለትሽ ውጪ ታሰላስያለሽ!»

«የሴት ቁንጅና ላንተ በምንድነው የሚለካው?»

«ቁንጅናውን ለምንድነው የምፈልገው? የሚለው ነዋ የሚወስነው? የውስጥ ውበት ምናምን ብዬ እንድዋሽሽ አትጠብቂ! የፊዚካል ውበት አድናቂ ነኝ። አልጋ ላይ ይዣት ለመውደቅ ከምጣደፍባት ሴት ሀሳቧ መንፈሷ አይነት ዝባዝንኬ ትዝ አይለኝም። ችግሩ ከተኛኋት በኋላ የማወራው ስለሚጠፋኝ ቶሎ እንድትለየኝ እፈልጋለሁ። ምናልባት ግን በሌላ ጊዜም ላገኛት እፈልግ ይሆናል። ከወዳጄ ጋር ተማክረን (ወዳጄ ያለው ታች ቤቱን መሆኑን ለማሳየት በእጁ ወደታች ጠቆመኝ) እሷ ትሻለናለች ተባብለን ላገኛት እችላለሁ። የምታሰላስል፣ የምትጠይቅ ሴት ግን ደስ ትለኛለች። ከእራት እስከአልጋ ሳትሰለቸኝ ጊዜ ሰጣታለሁ። አብሮ እስከመኖርም አይከፋኝም። »

የሆነ ……… እየጠሉ የሚወዱት፣ እየፈሩ የሚደፍሩት፣ እንደሚፋጅ እያወቁ የሚሞክሩት ፣ መሸሽ እየፈለጉ የሚቀርቡት ፣ እየረገሙ የሚመርቁት ፣ በአንዴ ልክም ስህተትም የሚሆን ፣ ሲኦልም ገነትም ዓይነት ስሜት ያለው፣ ህመምም እርካታም ዓይነት ስሜት ያለው ……… በቃ በየትኛውም ጎራ የማያቅፉት አይነት ሰው ነበር። የዛን ቀን እቤቴ ከሸኘኝ በኋላ

«ደውዪልኝ!» ብሎ ስልኩን ሰጥቶኝ ሄደ። እኔው ራሴ ያላወቅኩት እብደት ውስጤ መኖሩን ያወቅኩት <ላግባሽ> ያለኝን ደግሜ ከነአመክንዮዎቹ ሳስብ ራሴን ሳገኘው ነው። የሆነ ቀን <ለምንድነው የምደውልለት?> የሚለውን ሳላስብበት ደወልኩለት። ስልኩን እንዳነሳ እኔ መሆኔን ሲያውቅ

« ከሰው ጋር ነኝ በኃላ ልደውልልሽ?» አለኝ። በስልኩ ውስጥ በሹክሹክታ የምታወራ ሴት ድምፅ ሰማሁ።

«እሺ ይቅርታ!» ብዬው ስልኩን ዘጋሁት። ከዛ በራሴ ተናደድኩ። መደወል አልነበረብኝም!! የሆነ ክብሬን ዝቅ ያደረግኩ አይነት ስሜት ተሰማኝ። <ምን አስቤ ነው የደወልኩለት?> ራሴን በወቀሳ ስቀጣ ቆይቼ ከሰዓታት በኋላ ደወለ።

«ከሰው ጋር ነበርኩ።» አለኝ ስልኩን እንዳነሳው

«አወቅኩኝ።» አልኩኝ
«ደብሮሽ ባልሆነ?» ብሎ ድክም ብሎ ሳቀ። ጭራሽ ደበረኝ። ዝም አልኩ። «ኦህህህ አግቢኝ ያልኩሽን አስበሽበታል ማለት ነው። (በእርግጠኛነት ነው የሚያወራው) አሰብሽው እንጂኮ ታዲያ ለእኔ አልነገርሽኝም። ከማንም ጋር ብሆን በእኔ የመናደድ መብት የለሽም» ወሬ ውስጥ ሳቅ ይሰማል? እንደሱ ነው የሰማሁት። «ነገ እራት ልጋብዝሽ?» አለ

«ነገ? » ብዬ ላለመሄድ የምሰጠውን ሰበብ ሳስብ ሳቁ አቋረጠኝ

«እሺ ቅድም ምን ልትዪኝ ነበር የደወልሽው?»

«እኔ እንጃ? ላዋራህ? እኔ እንጃ ለምን እንደደወልኩ!» አሁንም ሳቅ ባጀበው የወሬ ለዛው።

«ነገ አስራ ሁለት ሰዓት ላይ መጥቼ ፒክ አደርግሻለሁ። እሺ ካልሽ ማለት ነው! ከሴት ጋር ነበርኩ። አብሬያት ሆኜ ሌላ ሴት ላላወራ ቃል ገብቼላታለሁ። ቃሌን ደግሞ የምጠብቅ ሰው ነኝ።»

«አሁን እኔን ስታወራ ቃልህን እያፈረስክ አይደለም?»

«አይደለም! ፊዚካሊ አብረን ስንሆን ነው ውላችን …… ይቅርብሽ ዲቴሉ አትወጂውም። አይጠቅምሽምም! ካንቺምጋ ብሆን ለሚኖሩን ህጎች ቃሌን እጠብቃለሁ። የማልጠብቀውን ቃል አልገባልሽም። እራት እንብላ?»

«እሺ» አልኩት። ምንም አስቤ አይደለም። እራት ከእርሱ ጋር ለመብላት ካለመፈለጌ መፈለጌ ስላየለ ብቻ እሺ አልኩት።

ድጋሚ <ላግባሽ> የሚለውን ነገር ለተወሰኑ ቀናት አላነሳቸውም። በትዳር ዙሪያ ያሉንን ሀሳቦች ግን ማውራት አላቆምንም። ለምሳሌ የሆነኛው ቀን

«ቆይ ሁለት ሰዎች ተጋብተው ወይም ሳይጋቡ ለመኖር ዋነኛው መስፈርት ምንድነው?»

«ፍቅር ዋነኛው ነው። ነገር ግን ፍቅርን የሚያጠነክሩት ……… መከባበር፣ አንዱ የአንዱን ስሜትና ሃሳብ ለመረዳት የሚሄድበት ርቀት፣ መደጋገፍ ……. ብዙ ነገሮች አሉ።»

ፍቅር የሚባል ነገር ስላለመኖሩ ረዥም ማብራሪያ ከሰጠኝ በኋላ

«ይሁንልሽ ፍቅር የምትዪው ስሜት አለ እንበል እና መገለጫው ምንድነው? ሚስተር አፍቃሪ እንዳፈቀረሽ በምን ታውቂያለሽ? አበባ ይዞልሽ የሚመጣ? በ24 ሰዓት 26 ጊዜ የሚደውል? ስለፍቅሩ ስድስት ልብ ወለድ መፅሃፍ የሚወጣው ዲስኩር የሚዘበዝብ? የሚያቅፍሽ? የሚስምሽ? ራቁትሽን ስትሆኚ የማታፍሪው? በየሰርግ ውልደት ግብዣ ላይ ይዞሽ በኩራት የሚዞር? ምን አለ ከዚህ ሌላ? ከዚህ የተለየ የፍቅር ማሳያ ነው የምትዪው ካለ እ?»

ለደቂቃዎች የእውነት ከነዚህ በተጨማሪ አንድ ሰው ፍቅሩን የሚገልፅበት ነገር ያለ እንደሆነ አሰብኩ። ከአፌ የወጣው ግን ሌላ ጥያቄ ነበር።

«አንተ ግን በ42 ዓመት ዘመንህ ፍቅር ይዞህ ያውቃል? ወይም እሺ እንዴት ላስቀምጠው? የጓደኝነት ስሜት መጠቃቀም ሲደመር የወሲብ ስሜት መጠቃቀም ሲደመር ወይ ሳይደመር የቁስ መጠቃቀም ያልከውን የተቃራኒ ፆታ ትስስር ዓይነት ኖሮህ ያውቃል?»

ፊቱ ድንገት እንደመዳመን ዓይነት ሆነ ። «ማናት? መቼ? እንዴት ? ለምን የሚል ጥያቄ አስከትለሽ እንዳትጠይቂኝ። አዎ ኖሮኝ ያውቃል።» አለኝ በደፈናው። ለማውራት አፌን ሳሟሽ «እስከመቼውም የማልነግርሽ ድሮ አለኝ። አትልፊ። ማውራት አልፈልግም!»

የማይተነበይ አይነት ሰው ነው። ሲያወራ ካለመሰልቸቱ እና በእውቀት ላይ ከተመሰረቱት ምክንያታዊ ጨዋታዎቹ በተጨማሪ መኪና አቁሞ ዝናብ ላይ ቆሞ አፉን ከፍቶ ዝናብ እየተደበደበ የዝናብ ጠብታ የሚጠጣ ንቅል ነው። ልክ እንደልከኛ ነገር «ይህቺ ሁለተኛ ሚስቴ ነበረች።» ብሎ እራት እየበላን በአጠገባችን ከሌላ ወንድ ጋር እራት ለመብላት የምትገባን ሴት የሚያስተዋውቀኝ ልክ ያልሆነ ሰው ነው። <እገሌ የፃፈው ገፀባህሪ በፍፁም እንዲህ ሊያደርግ አይችልም። ደራሲው ገፀባህሪውን በደንብ አልተረዳውም።> ብሎ የሚሟገት ንክ ነው። ባጠቃላይ በእኔ ዓለም፣ በእኔ እምነት ፣ በእኔ ባህል፣ በእኔ ልምድ ፣ በእኔ አስተዳደግ አይደለም ባል ብለው ሊመርጡት ለአንድ ቀን እንግዳ አድርገው ሊመርጡት ጤንነቱ የሚያጠራጥር ዓይነት ሰውኮ ነው። እንደሚፋጅ እያወቅኩ ካልነካሁት ብዬ የነካሁት እሳት

«ቤቴን ላሳይሽ?» ሲለኝ እንቢ ለማለት ወይም ለመሽኮርመም ሀሳቡም አልመጣልኝም። ወደእርሱ ዓለም እየተሳብኩ እንደሆነ ያኔ ገባኝ። እሱ ሲያደርገው ወይም ሲያወራው እብደት ወይም ብልግና ሲመስለኝ የነበረው ነገር እኔ ውስጥም ያለ ግን ልኖረው ያልደፈርኩት ልክነት መሆኑ የገባኝ ዶክመንተሪ ፊልሙን አይተን ከጨረስን በኋላ መብራቱን ሲያበራው ሞቆት ይሁን እኔን መፈታተን ፈልጎ የለበሰውን ሸሚዝ አውልቆ ከላይ ፈርጣማ ሰውነቱን ሳየው ልነካው መመኘቴን መደበቅ አቅቶት ሳላዘው እጄ ሲዘረጋ ነው.........

………….. አልጨረስንም.........

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት
(ክፍል ስድስት ………. ሜሪ ፈለቀ)

የዛን ቀን …….. እንኳን ዶክመንተሪ ፊልሙን አይተን ስንጨርስ በሙቀቱ ወዝቶ ቅባት የተቀባ የመሰለውን ጠይም ፈርጣማ ደረቱን እጄ ሲንቀለቀል ሄዶ የነካው ቀን……… እጄን ደረቱ ላይ በእጁ ደግፎ እንዳላንቀሳቅሰው ይዞት

«እርግጠኛ ነሽ?»

«ቨርጅን አይደለሁምኮ።»

«አውቃለሁ!! በኋላ የፀፀትሽ ምክንያት መሆን አልፈልግም።» እያለኝ ትንፋሹ ከንፈሬጋ ደርሷል። አሁን ማን ይሙት ሀሳቤን መቀየር እንኳን ብፈልግ የቱን ሀሳቤን እንደምቀይር አስተካክዬ ማስታወስ እችል ነበር? እየሳመኝ እያቋረጠ ያወራል። አንዳንዱን ቃል እየሳመኝም እያወራም ነው ልበል? ወይም መስሎኝ ነው።

« ለምን እፀፀታለሁ?» አልኩኝ ከንፈሬን ነፃ ባደረገልኝ ቅፅበት። ደረቱ ላይ ይዞት የነበረውን እጄን አንስቶ እንደዋልዝ ዳንስ አሽከርክክሮ በጀርባዬ እያዞረኝ

«የሴት ልጅ ክብሯ እግሯ መሃል ነው ብለው ነግረዋችኋል።r (ቅድም የቆጠራቸውን ሶስት ቁልፎች እየፈታ አንገቴ ስር ነው የሚያወራው) አብዛኛዋ ሴት እግሯን ከፍታ ስትዘጋ ከክብሯ የሆነኛውን ያህል እንደገመሰች ነው የሚሰማት። (በቃላቱ በየመሃል አንገቴን ይስመኛል።) ፈልጋ እንኳን አድርጋው ዝቅ ያለች ስሜት ይሰማታል። ራሷን ትጠላለች።» ዚፑን ከፍቶ ቀሚሴን ወደታች እያወለቀው። ከትንፋሼ እና ከምውጠው ምራቅ ጋር እየታገልኩ

«ወሬህን ማቆም አትችልም?»

«አፋችን ስራ ካልያዘ (እንደቅድሙ ደግሞ ወደፊቱ አዙሮኝ ክንፈሬን እየሳመኝ) ብናወራበትሳ! (ሳቅ ባለበት ለዛው ነው የሚያወራው።)»

«ቢያንስ ወሬው (ከንፈሩ አቋረጠኝ) ከሰዓቱጋ የሚሄድ (እጁ አጓጉል ቦታ ደርሶ አቋረጠኝ) »

«እኔ የኔ ፍቅር፣ ወድጄሽ ፣ ሞቼልሽ …… አይነት ቃላቶች አልችልም። » እጁም ከንፈሩም ሰውነቴ ላይ መርመስመሳቸውን አላቆሙም።

«እና ዝም ማለት አይቻልም?»

«እንዴ? ምን በወጣን? ቅጣት ነው የምንወጣው? አልተጣላን ለምን ዝም እንባባላለን?(መሬቱ ላይ እየተዋደቅን) መኝታ ቤት ይሁንልሽ?»

«አልፈልግም! ወሬህ ግን እየረበሸኝ ነው።»

«ያለመድሽው ነገር መሆኑን እርሺውና (ለከንፈሩ ስራ ሰጥቶት መለስ ይልና) ራንደም ወሬ አውሪኝ። ምግብ እያበሰልሽ ስለውሎሽ ማውራት እንደምትችዪው ፣ ፊልም እያየሽ ስለተዋናዩ ጫማ አስተያየት እንደምትሰጪው ፣ መፅሃፍ እያነበብሽ ፋታ ወስደሽ ሻይ ፉት እንደምትዪው ……..»

«እና ስለሶቅራጠስም ቢሆን እያወራን እናልብ?»

ከተጋባን ከዓመታት በኋላ አንዲት የተረገመች ቀን ላይ አፌ የማይገባውን ለፍልፎ እሱን ሌላ ጭራቅ ሰው እስካደረገው ቀን ድረስ ሁሌም እንዲህ ነበር። የጦፈ ልፋታችን መሃል ስላነበብነው መፅሃፍ እንጨቃጨቃለን ወይም ቀን ላይ ስራ ቦታ ስለገጠመው ደንበኛው ያወራኛል ወይም ትምህርት ቤት ስለገጠመችኝ ደም አፍዪ የተማሪ ወላጅ ወይም ደግሞ አዲስ ወጥቶ ስላየነው ዶክመንተሪ ፊልም ……. ብቻ ከልፋታችን ጋር የማይገናኝ ወሬ እያወራን እናልብ ነበር። አፌ ከአዕምሮዬ ጋር ሳይማከር እስከዘባረቀበት እስከዛች ቀን ድረስ……

የወደፊቱ የትዳር ህይወቴን ሲኦልነት የሚገልፁ <ማሳያ ትኩሳቶች> እያወቅኩ እና ፍንጣሪውን እየተለማመድኩ ሰንብቼ ነው ያገባሁት። ሶስት ዋና ዋና ምክንያቶች እና ሌሎች ፍርፋሪ አባሪ ምክንያቶች ነበሩኝ። አንዱ ከሌላኛው ጋር በቀጥታም በጓሮም ይጋመዳል። ብያችሁ አልነበር። አንደኛውን ነገርኳችኋ?

ሁለተኛው እሱ ወደህይወቴ ሳይመጣም በፊት ይናድብኛል የምለው ጠንካራ የተገነባ የኑሮ ዘይቤ አልነበረኝም። ለቤተሰቦቼ አምስተኛ ልጅ ነኝ። እንዳለመታደል ሆኖ ከእኔ በላይ የተወለዱት ታላላቆቼ በትምህርታቸው ጎበዝ ፣ በዓመላቸው በትምህርት ቤትም በጎረቤትም በቤትም የተመሰገኑ ሲሆኑ እግዚአብሄር እኔጋ ሲደርስ ዓመሉን ዘለለኝ።

አሁንም እንዳለመታደል ሆኖ እውቀት በሂሳብ እና እንግሊዝ ውጤት የሚገለፅ ሆነና በእሱም አልታደልኩም። እንደው ለምኑም ሳትሆን ከምትቀር ብሎ ነው መሰለኝ ለዓይን ማራኪ አድርጎ ሰራኝ። ከታላላቆቼ የተለየሁ በመሆኔ እንደጥፋት፣ እንደእርግማን ታየብኝ። በልዩነቴ ምክንያት ስቀጣ አደግኩ። ቀኔን ሲያከብድብኝ ታናናቼም ቤተሰቦቼ እንደሚሉት የእኔን አርአያ ተከትለው ትምህርቱን እርግፍ አድርገው ትተው ቦዘኔዎች ሆኑ። ለእነርሱም ጥፋት እኔ ተቀጣሁ።

የአብዛኛዎቻችን ወላጆች ልጅ አዋቂ እንዲሆን ከበላ ፣ትምህርት ቤት ከተላከ፣ የሚያድርበት ማደሪያ ካለው፣ ካልታረዘ በቃ የተቀረው አድጎ አዋቂ፣ ሀላፊነት ተቀባይ ለመሆን የልጁ የራሱ ሀላፊነት እንደሆነ ያስባሉ።

አባትሽ ትምህርት ቤት ሲጠራ «አንቺ መቼም ሰው አትሆኚም! ሁሌም እንዳዋረድሽኝ» የሚልሽ ተደጋጋሚ ወቀሳ ሰው እንዳትሆኚ ወደታች እንደሚጎትትሽ አያስተውልም።

አጎትሽ ድንገት ከአምስት ዓመት አንዴ መጥቶ «ውይ እቴቴ በዝህችኛዋስ አላደለሽም! ትልልቆቹን ይባርክልሽ እንጂ እቺ መቼም ሰው አትሆንም!» ብሎ ለእናትሽ ባዘነ ሙድ ሲነግራት አንቺ ይዘሽው የምታድጊው ከንቱነት እያቀበለሽ እንደሆነ አይገነዘቡልሽም።

አፏ የማያርፍ አክስትሽ «እቴትዬ ይህቺኛዋስ ደህና አማች ታመጣልሽ እንደው እንጂ ትምህርቱስ አልሆናትም!» ስትልሽ እናትሽ አብራ ትስቃለች እንጂ በማንም ፊት የማትረቢ እንደሆንሽ እያመንሽ ራስሽን እንደምትቀጪ አትገነዘብም!

ወላጆች ልጆቻቸውን በዱላ ሲቀጡ የሚታያቸው ዱላው ደም አለማፍሰሱ ነው። ወይም አጥንት አለመስበሩ፣ እዛ ደረጃ ካልደረሰ ልጁ እየተቀጣ እንጂ እየተጎዳ አይደለም። ትምህርት እየሰጡት ነው።

ዱላው ሰውነቱ ላይ ሊያርፍ በተዘረጋ ቁጥር ከሰውነቱ መሸማቀቅ ጋር በዘመኑ ሁሉ አብሮት የሚጓዝ በራስ ያለመተማመን እያሳጨዱት እንደሆነ አያውቁም። ሰውነቱ ላይ ባረፈው ዱላ ልክ ፈሪ እና ሸምቃቃ ልጅ እያፈሩ እንደሆነ አያውቁም! ሲቀጠቅጡት ያሳደጉትን ልጅ አድጎ በሰዎች ፊት መብቱን አንገቱን ሳይደፋ የሚጠይቅ ኩሩ ባለመሆኑ ይወቅሱታል። ከነዛ የዱላ ሰንበሮች ጋር በራስ መተማመኑ መክሰሙን አያስተውሉም። የዱላው ቁስል አይደለም ከልጁ ጋር አብሮ የሚኖረው ስሜቱ ነው። ፍርሃቱ፣ አንገት መድፋቱ፣ እንዳያስረዳ እንኳን <ዝም ጭጭ!> ተብሎ የዋጠው የመጠየቅ እና የመናገር መብቱ፣ ሰቀቀኑ ………… ያ ነው አብሮት የሚያድገው።

ሁል ጊዜ ለራሴ ሳይሆን ለእነርሱ ስል ጥሩ ልጅ ለመሆን እሞክራለሁኮ፣ ለአባቴ ጎበዝ ተማሪ ሆኜ ውርደቱ እንዳልሆን ፣ ለእማዬ ጨዋ ልጅ ሆኜ ሰው እንድሆንላት ፣ ለዘመዶቻችን ከታላላቆቼ እኩል ሆኜ ላኮራቸው። ለራሴ ስል ሳይሆን ለእነርሱ ስል እሞክራለሁ። ያለመታደል ሆኖ ውጤት እንጂ ትግል አይቆጠርማ? እፎርሻለሁ። አስረኛ ክፍል ደርሼ በእነሱ መለኪያ ሰው ያለመሆኔን ተቀብዬ ሙከራዬን ትቼ በራሴ ዓለም መኖር እስከጀመርኩበት ጊዜ ድረስ ሞክሬያለሁ።

መኖሬን ቀጥዬ የረባ ውጤት ሳላመጣ የሆነ መዋዕለ ህፃናት አስተማሪ ሆኜ እየሰራሁ። ሁሌም ልደበቀው የማልችለው ሀሳብ ጭንቅላቴ ጓዳ አለ። የሆነ ቀን ቤተሰቦቼን ማኩራት፣ በሙሉ አፋቸው « የእኔ ልጅ እኮ!» ሲሉኝ መስማት። እንግዲህ ሌላኛው ምክንያቴ ይሄ ነው። እናቴ «የልጄ ሰርግ ነው!» ብላ ለዘመዶቿ በኩራት መጥሪያ እንድትልክላቸው ፣ አባቴ «በመጨረሻም ልብ ገዛች! ልጄኮ ምን የመሰለ ባል አገባች መሰላችሁ!» እያለ ለወዳጆቹ እንዲያወራ ፣ ታላላቆቼ በትምህርታቸው ቁልል ያላደረጉላቸውን አድርጌ «ድሮምኮ ልጄ!» መባል።
ሶስተኛው ምክንያቴ እሱ ራሱ ነው። በ34 ዓመት ካገኘሽው ጋር ተጠቃለዪ የምትባዪበት እድሜሽ ነው። ያገኘሁት ሰው ቢያንስ ከዚህ በፊት እንደማውቃቸው ወንዶች ጅል አይደለም። ከአዎ እና አይደለም ውጪ የተለመደ እኝኝ የሚያወራ ወንድ ጅል ነው የሚመስለኝ። አዲስ እንደዛ አይደለም። የሚወደድ እና የሚጠላ ባህሪ ቢኖረውም አንድ ነገር ልዩ ያደርገዋል። አይሰለችም። ሁሉም ቀን ከእርሱ ጋር አድቬንቸር ነው።

«ከተጋባን ሰርግ እፈልጋለሁ! ትልቅ ሰርግ!» አልኩት የሲኒማ ክፍሉ ወለል ላይ እርቃናችንን እንደተጋደምን

«done!»

«በቁስ የምትደሰቺ ሴት ከሆንሽ አንቀባርሬ አኖርሻለሁ። አላልከኝም?»

«አዎ»

«ለራሴ ምንም እንድታደርግልኝ አልፈልግም! የሆነ ቀን ላይ ለእናት እና አባቴ ቤት እንድትገዛልኝ ብቻ ነው የምፈልገው። ከፈለግክ ከ8 ዓመት በኋላ የምታካፍለኝን ውርስ ሰርዘው።»

«እሺ!» አለ በምን አገባኝ ትከሻውን ሰብቆ

«በቃ እንጋባ! ሚዜዎችህን አዘጋጅ ለዘመዶችህ ለጓደኞችህ ንገራቸው።»

«እኔ ዘመድም ጓደኛም የለኝም። ሚዜ ብለሽ አታስጨንቂኝ። ሰርጉን የሚታደም የኔ ወገን የለም። » እያለኝ እየሰራሁት ያለሁት እብደት እንደሆነ ጠርጥሪያለሁ።

«የምርህን ነው? እንዴት አንድ ዘመድ አይኖርህም? ጓደኛስ? ቢያንስ የስራ ባልደረቦች አሉህ አይደል?»

«ዘመድ ጓደኛ የለኝም! የስራ ባልደረቦች አሉኝ ግን የግል ህይወታችንን አንነጋገርም! እና ማንንም ሰው ለግሌ ጉዳይ እንዲህ አድርጉልኝ ብዬ አልጠይቅም!»

............. ..... አልጨረስንም …………………..

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት
(ክፍል ሰባት ………. ሜሪ ፈለቀ)

ሰርጉ የራሴ ሆኖ ፣ በሰው ሰራሽ ፋብሪካ የተመረተ ሮቦት ይመስል ዘመድ አልባ ባል ላገባ የተዘጋጀሁት እኔ ሆኜ ሳለሁ፣ ሰርጉ ላይ ሚዜ እንኳን የሚሆን ጓደኛ የሌለው ባል ለማግባት ራሴ አምኜ ………. ምን ይሉ ይሆን ብዬ የምጨነቀው ለቤተሰብ ፣ ሰርጉ እንከን እንዳይኖረው ቁጭ ብድግ የምለው ለታዳሚው ……ሙሽራዋ ግን እኔው …… ቀኑ መሆን የነበረበት የኔ

«ለምን ራስሽን አትሆኝም?» አለኝ አዲስ የሰርጉ ውጥረት ቀልቤን ሲነሳኝ አይቶ

«ይሄ ነገር ስለሚባል ነው አይደል የምትሉት? ራስህን መሆን እኮ …… የምትወደው ራስህ ሲኖርህ ነው! እኔን መሆን እንዴት እንደሚያስጠላ ብታውቅ <ራስሽን ሁኚ> አትለኝም! ራሴን አልወደውም አዲስ! የማልወደውን ራሴን እንድሆን አትንገረኝ! እኔን መሆን ይቀፋል! ሌላን ሰው መልበስ ይሻለኛል። ያ ሰው ማን እንደሆነ ሳታውቁ <ራስህን ሁን> እያላችሁ አትምከሩት! የማነቃቂያ ንግግራችሁ ማስዋቢያ ወይም ንግግር ማሳመሪያ ብቻ ነው። መጀመሪያ ራሱ የሚወደው ማንነት ይኖረው እንደሆነ ጠይቁት እስኪ!! ራሱን ሲሸሽኮ ነው ሌላ ሰው የሚሆነው! » እየጮህኩ እና ስሜታዊ ሆኜ እያወራሁ እንደሆነ የገባኝ አዲስ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከራከርበት ሀሳብ ሰጥቼው በመከራከር ፈንታ በጣም ረጋ ብሎ ሁለቱን እጆቼን ሲይዘኝ ነው

« ቤተሰብ ፣ ማህበረሰብ፣ እኔ ፣ ሀይማኖት ……… ብቻ ምንም በዙሪያሽ ባይኖር ፣ ማንም ካንቺ ምንም ባይጠብቅ ፣ ማንንም ማስደሰት ወይም የማንንም expectation ማሟላት ባይኖርብሽ ………. ምን አይነት ሰው ነው መሆን የምትፈልጊው? ምን ማድረግ ነው የምትፈልጊው የነበረው?»

« ደስተኛ ሴት መሆን ብቻ ነበር የምፈልገው!! ማንም ሳያዋክበኝ ፣ ማንም < ሴት መሆን ያለባት፣ ወጣት መሆን ያለበት፣ ቆንጆ መሆን ያለበት፣ የእቴቴ ልጅ በመሆንሽ መሆን ያለብሽ፣ የዳግም እህት በመሆንሽ መሆን ያለብሽ፣ ክርስቲያን መሆን ያለበት ……… > እያለ የኑሮ ዘይቤዬን ሳያሰምርልኝ ከህሊናዬ እና ከአምላኬ ጋር ሰላሜን እየጠበቅኩ ራሴን መፈለግ ብቻ ነው የምመኘውኮ! ራሴን ማግኘት!! ፍለጋዬን ገና ድሮ ስላጠፉብኝ ማን እንደሆንኩ እንኳን አላውቀውምኮ!!» አሁንም እየጮህኩ ነው የማወራው። እስከዛሬ ለራሴ ራሱ ለማስረዳት በውል የቸገረኝን መሻቴን ሳብራራ ራሴን አገኘሁት። ለደቂቃ ያህል ዝም ካለኝ በኋላ

«ሰርጉን መሰረዝ ትፈልጊያለሽ? ማንንም የማታዪ የማትሰሚበት ቦታ ሄደሽ ከራስሽ ጋር ብቻ ጊዜ እያሳለፍሽ ራስሽን መፈለግ ትፈልጊያለሽ? ያን ላሳካልሽ እችላለሁ። ነገር ግን ሁሉንም ከኋላሽ የመተው አቅሙ አለሽ?»

«አቅሙ የለኝም! አልፈልግምም! አየህ ወፍ መብረር እችላለሁ ብላ የፈለገችበት ዝም ብላ አትበርም። ስደተኛ ወፎች የሚባሉትን ታውቃቸዋለህ? ተፈጥሯዊው የአየር እና ወቅት ለውጥ የኑሮ ዘይቤያቸውን እነርሱ ወደፈለጉበት ሳይሆን ምግብ ወደሚገኝበት፣ መኖሪያቸውን በረዶና ንፋስ ሳያፈርስባቸው ወደሚኖሩበት አቅጣጫ እንዲበሩ ያስገድዳቸዋል። አየህ ህብረተሰብ ቤተሰብ ሀይማኖት ባህል ምናምን የማይዛት ወፍ እንኳን ተፈጥሮ በሆነ መልኩ ያጥራታል። ወደድንም ጠላንም የምትታሰርበት ሸምቀቆ እንደግለሰቡ ከመጥበቁ እና ከመላላቱ ውጪ ሁላችንም በአንደኛው ገመድ ተጠፍንገናል። ምክንያቱም የዚህ ማህበረሰብ አካል ነና! የምንኖረው ከዚሁ ማህበረሰብ ጋር ነዋ! የምንኖረው ለዚሁ ማህበረሰብ ነዋ! እንደአለመታደል ሆኖ አንዳንዶቻችን የታሰርንበት ገመድ አንቆ ሊገድለን አንገታችን ሰልሎ እንኳን ለማምለጥ አቅሙ የለንም!» አይኔ ይሁን እንጃ ያዘነልኝ መሰለ? የሆነ ውሳኔ ለመወሰን ያመነታ መሰለ። ግንባሩ ላይ ስሜቶቹ ተቁነጠነጡ።

«እሺ በተወሰነ መልኩ ውጥረትሽን ከቀነሰልሽ ስራ ቦታ ያሉ ሰዎችን ሚዜ እንዲሆኑልኝ ጠይቃቸዋለሁ። የተወሰኑትንም ሰርጉን እንዲታደሙ የጥሪ ወረቀት እሰጣቸዋለሁ። ይሄ የሚያቀልልሽ ነገር አለ?»

«አዎ በጣም! በጣም እንጂ! በጣም ብዙ ነገር ያቀልልኛል። አመሰግናለሁ!» እንደህፃን ልጅ መጨፈር ቃጣኝ። ማድረግ የፈለግኩት ከንፈሩን መሳም ነበር ግን ጉንጩ ላይ አረፍኩ። ሰርጌ ሳምንታት እየቀሩት የማገባውን ሰውኮ በጭራሽ አላውቀውም! እሱ ላይ ስልጣንና መብቴ ምን ድረስ እንደሆነ እንኳን አላውቅም።

«የሰውን ልጅ ልወቀው ብለሽ እድሜሽን አትፍጂ ይልቅ ያንን ኢነርጂ ራስሽ ላይ አውዪው። እመኚኝ ራስሽን ለማወቅ የምታደርጊው ፍለጋ በራሱ እንኳን እድሜ ልክ ይፈጃል እንኳን የውስጥ ሀሳቡን ልታውቂ የማትችዪውን ሌላ ሰው ማወቅ» ይለኛል ላውቀው እንደምፈልግ ስነግረው።

«እውነት ነው የሰው ልጅ ሙሉ በሙሉ ልታውቀው የምትችለው ፍጡር አይደለም። ግን ሁሉም ሰው የማይቀየሩ ወይም ቢቀየሩም ሙሉ በሙሉ የማይጠፉ መሰረታዊ የሆነ የማንነት ምሰሶ አለውኮ!»

«አትሳሳቺ! ፐርሰናሊቲ ካዳበርሽው የሚያድግ፣ ከተውሽው የሚሞት፣ ወይም በማህበረሰብ ሚዛን ጥሩ ወይም መጥፎ ከሆኑት ፅንፎች ከሌላው ሰው የሚቀዳ ነው። ሰው ማሰብ ካላቆመ በቀር ይቀየራል። እንደቁስ እዚህጋ አስቀምጬሃለሁ እና ከዝህችው አንተነትህ ፈቅ እንዳትል ልትዪው አትችይም! ያስባላ! ሰዎች ባላቸው የተለያየ ግንኙነት የሚጣሉት ለምን ይመስልሻል? በአብዛኛው በጊዜ ሂደት የሚመጣውን የዛኛውን ሰው ማንነት መቀበል ስለሚያቅታቸው ነው። ወንድ እና ሴት ይጋቡ እና ከአስር ዓመት በኋላ ይለያያሉ። ለምን ብትያቸው <ሳገባው የነበረው ዓይነት ሰው አይደለም> ትልሻለች ወይም ይልሻል። ከዓመታት በፊት የተመቸው ነገር ተመችቶት እንዲቀጥል ትጠብቃለች። የሌላን ሰው ለውጥ መቀበል አንወድም! ወደ ራሳችን ብናይ ግን በነዛ ዓመታት ራሳችንም ተለውጠናልኮ! ለምን ነገ ሊቀየር የሚችል እኔነቴን ለማወቅ ጊዜ ታባክኛለሽ? አወቅኩት ብለሽ ስታስቢ ተቀይሬ ብታገኚኝ ጊዜና ጉልበትሽን አባከንሽ ማለትም አይደል?»

ተውኩት። ያለፈውን የእምነት መሰረቱን ለማወቅ መቆፈሬን ተውኩት። ዛሬ ላይ ብቻ አተኮርኩ። አብሬው ስሆን ያለው አዲስ ላይ ብቻ አተኮርኩ። ዛሬ የትናንታችን ውጤት መሆኑን ልቤ እያወቀ ትናንትን ከእኔና ከእርሱ መሃከል አሽቀንጥሬ ጣልኩት። ትናንት ምን ያህል ቢገፉት አራሙቻውን በጣጥሶ ዛሬ ላይ የመንገስ አቅም እንኳን እንዳለው ልቤ እያወቀ። ትናንትን እንደአሮጌ ሸማ አጣጥፌ የማልከፍተው ያረጀ ሳጥን ውስጥ ቆልፌ ከአዲስ ጋር አዲስ ኑሮ ጀመርኩ።

ሽማግሌዎቼን ራሴ መርጬ አስላኩኝ። ሰርጌ ደመቀ። «አሁን ደመቅሽ የኛ ልጅ !» ተባለልኝ። በቤተሰባችን ታሪክ ያልታየ የተባለለትን ደማቅ ሰርግ ደገሰልኝ። «የማታ ትዳር ሰጣት » ተባለልኝ። ቆማ ቀረች ያለኝ ዘመድ አዝማድ «እንኳንም ታግሰሽ ጠበቅሽ! ትዕግስት ፍሬዋ …..» እያለ አገላብጦ ሳመኝ። «ውለዱ ክበዱ !» ተባልንልን! ላለመውለድ ላለመክበድ ፈርሜ እንደገባሁ አያውቁም! የቤተሰብ ቅልቅል፣ መልስ አንጃ ግራንጃውን « ቤተሰቦቹ እዚህ ሀገር አይደሉም!» እያልኩ ስዋሽ ከረምኩት። አዲስ ዝም ብሎ አላለፈኝም። በየመሃሉ ሀሳብ ከመስጠት አይቦዝንም። ግን ባይዋጥለትም ለእኔ ከማዘን ውጪ ቀኔን አላበላሸብኝም።

«ኸረ ተይ ሰዎች በህይወትሽ ውስጥ ያላቸውን ስልጣን ገደብ አበጂለት? ቤተሰቦችሽም ቢሆኑ ህይወትሽን የሚያማስሉበት ገደብ አለው። ዛሬ ለእነሱ ብለሽ ሰርግ ደገስሽ፣ አገባሽ፣ ዋሸሽ …… አያቆምምኮ አንቺ የማስቆም ሀሳብ ከሌለሽ» ብሎኝ ነበር የቅልቅሉ ቀን።
እኔም የተገላገልኩ መስሎኝ ነበር። ገና መጀመሪያው መሆኑ የገባኝ አግብቼ ብዙም ሳልቆይ ሁሉም በየፊናው <ሴት ልጅ ጠቢብ ናት። ያዝ ቆንጠጥ ማድረግ ልመጂ> አይነት የጨዋ የሚመስል ግን ሀብቱ በእጅሽ እያለ ስረቂው አይነት ምክር መምከር ሲጀምሩ፣ <ገንዘብ አይሰጥሽም እንዴ? ይሄን ያህል ሀብት ላይ እየዋኘሽ መዋዕለህፃናት የምታስተምሪው ለምንድነው?> ዓይነት ጥያቆዎች ሲጠይቁኝ ፣ <እንዴ እስከመቼ ነው? ለምን የግልሽ ስራ እንዲከፍትልሽ አትጠይቂውም?> እያሉ በእኔ ባል ገንዘብ ምን ቢከፍትልኝ እንደሚያዋጣኝ ትርፍ እና ኪሳራውን እያሰሉ እንቅልፍ ሲያጡብኝ ፣ በአመቱ «ምንድነው የምትጠብቂው ሁሉ እያላችሁ ልጅ የማትወልዱት ለምንድነው?» እያሉ ሲነተርኩኝ ነው። ………. ገደብ እንደሌለው ገባኝ! እድሉን ከሰጠኋቸው ከባሌ ጋር የማደርገውን የአልጋ ልፊያ ፖዝሽን እንምረጥልሽ እንደሚሉኝ ገባኝ።

በተጋባን በወራት ውስጥ አዲስ ለቤተሰቦቼ በሀሳባቸው እንኳን ሽው ብሎ ሊያውቅ የማይችል ትልቅ ዘመናዊ ቤት ገዛልኝ። አባቴ ስምንት ልጅ ወልዶ ያሳደገበትን የቀበሌ ቤት ያስረከበ ቀን ቀበሌ ለሚሰሩት ለእያንዳንዳቸው እየዞረ « ህልም የመሰለ ቤት ልጄ ገዛችልኝ! ልጅ ማለት እንዲህ ነውይ!» እያለ የቤቱን ፎቶ ሲያሳያቸው ዋለ። ትምህርት ቤት በተጠራ ቁጥር «አንቺ መቼም እኔን ከማዋረድ የተሻለ ስራም የለሽ። ደግሞ ምን አጥፍተሽ ነው?» ያለኝን እልፍ ቀን በዝህች አንድ ቀን ሙገሳ አጣፋሁት!! እማዬ ቤቴን መርቁልኝ ብላ ጎረቤቶቿን እና ገጠር ያሉ ዘመዶቿን ሁላ ሳይቀር ጠርታ አዲሷ ቤቷ ውስጥ ከአንድ ክፍል ወደሌላው ክፍል ሽር ብትን እያለች «እልልልልልልል እንደው ልጄ በመድከሚያዬ ማረፊያዬን እንዳሳመርሽልኝ ትዳርሽን ያሳምርልሽ!» እያለች ስትመርቀኝ ዓለሜ የሞላ መሰለኝ። በቃ ከዚህ በኋላ ለእነርሱ ኩራት ለመሆን መንፈራገጤን የማቆም መስሎኝ ነበር።

«ራስሽ ለማቆም ካልወሰንሽ ማብቂያ የለውም! የሆነ ቦታ መወሰን ካልቻልሽ ሁሌም እነሱን ለማስደሰት ብቻ ነው የምትኖሪው።» የሚለኝ የአዲስ ቃል እየቆየ ነው የሚገባኝ። ምንም ቢጠይቁኝ <እንቢ> <አልችልም> ማለት ሲያቅተኝ። ሁሌም «የእኔ ልጅኮ!» ለመባል የማይቻለውን ለመቻል ስዳክር፣ እየቆየ <ይሄን አሁን ማድረግ አልችልም! ጊዜ ስጡኝ> ስል ማኩረፍ ሲዳዳቸው፣ አለፍ ሲልም <ቤተሰብሽን እንኳን ለመርዳት ካልቻልሽ እያዩ የማይበሉት ሀብት ለጉራ ካልሆነ ምን ይሰራል?> አይነት ወቀሳ ጣል ሲያደርጉ ሳልፋቸው፣ ለቤተሰብ እና ለዘመድ ከማደርገው መቶ ነገር ይልቅ አንድ ያላደረግኩት ሲቆጠርልኝ ፣ ላደረግኩት እልፍ ነገር ከመመስገን ይልቅ ላላደረግኩት አንድ ነገር ዓመቱን ሙሉ ስረገም ……. ዘግይቶም ቢሆን ገባኝ። የተባረኩኝ ልጅ ወይም ጥሩ እህት መሆኔን ለእነሱ ለማስመስከር ስዳክር ጉልምስናዬ ላይ መድረሴ ሳያንስ ራሴን ለማስደሰት ሳልኖር ላረጅ መሆኑን አወቅኩ። ማድረግ ከምችለው በላይ ራሴን ላለማስጨነቅ ወሰንኩ። የምችለውን በእነሱ ለመሞገስ ሳይሆን ለነሱ ማድረግ በመቻል ውስጥ ስላለው እርካታ ስል አደርጋለሁ።

አዲስ ገንዘብን በተመለከተ ስግብግብ የሚባል ሰው አይደለም። ያለምክንያት ግን ሽራፊ ሳንቲም አያወጣም። አንደኛውን የባንክ አካውንቱን በሁለታችን ስም አድርጎታል። ከ50 ሺህ ብር በላይ ማውጣት ስፈልግ ግን የግድ እሱ መፈረም አለበት። በራሴ ምክንያት ከፍ ያለ ገንዘብ አውጥቼ አላውቅም። ሁሌም በቤተሰብ ምክንያት ነው። ካላሳመነው አይስማማም። ካሳመነው ዝም ይላል። አንዳንዴ ሲመስለኝ ባይዋጥለትም ለእኔ ብሎ ያልፈኛል።

ከቤተሰቦቼ አዙሪት ውጪ ትዳሬ እንደተለመዱት የትዳር አይነቶች ቅርፅ ሳይዝ ቀጠለ። በፍቅር ወይም በተለመደው የትዳር ህግ ሳይሆን የሚተዳደረው ራሳችን በተስማማንባቸው ህጎች ነው። ያልፃፍናቸው ግን የተስማማንባቸው ብዙ ህጎች አርቅቀናል። በትንሹ ሀኒ፣ ቤቢ፣ ማሬ ውዴ የሚሉትን የቁልምጫ ቃላቶች ካለመጠቀም ጀምሮ ልጅ እስካለመውለድ ድረስ........ያለፈ ህይወታችንን (አንደኛው አካል ፈቃደኛ ሆኖ መናገር እስካልፈለገ ድረስ) ለመቆፈር ምንም አይነት እርምጃ ካለማድረግ እስከ አንደኛው አካል ትዳሩን ለቆ ለመሄድ በፈለገው ጊዜ መብቱ እንደሚከበርለት። ብዙ ህጎች …….. ሁለታችንም ያልገባን ወይም ማመን ያልፈለግነው ህግን የሚጥስ ስሜት መኖሩን ነው። ሳላውቀው፣ ሳላሰላ፣ ምንም አይነት ሂሳብ ሳልሰራ ህግ ጣስኩ።

ዛሬ ላይ ለምቀጣው ቅጣቴ ሁላ ጥፋቴ ያ ነበር………. አብሬው ስኖር ያወቅኩትን አዲስ በአዕምሮዬ ትግል የልቤን ስሜት አሸንፌ አለመውደድ አቃተኝ። በእያንዳንዷ ቀን አፍኜ እስከማልይዘው ድረስ ፍቅሩ ልቤ ውስጥ ተቆለለ። መቼ እንደሆነ አላውቅም ብቻ ግን የሆነኛው ቀን ላይ እሱ ልብ ውስጥ ለመቀመጥ ምንም ነገር መስዋዕት የማደርግ አቅመ ቢስ ሆኜ ራሴን አገኘሁት። ይኸው ነበር ጥፋቴ! እንዳገባው ለራሴ ለማሳመን ምክንያቶችን የደረደርኩለትን ሰው እንዳላጣው የትኛውን ምክንያት እንደማደረጅ ቸገረኝ።

«ምንድነው?» አለኝ የሆነ ቀን ማታ ልንተኛ ወደአልጋችን ሄደን እየተሳሳምን አቋርጦኝ።

«ምኑ?» አልኩት ግራ ገብቶኝ

«አሁን የሳምሺን መሳም! ልክ ያልሆነ ነገር አለው።» አለኝ።

ያለው ገብቶኛል። <አዎ ፍቅር አለበት> ብለው ደስ ይለኝ ነበር። ምላሹ ምን እንደሚሆን ልቤ አስቀድሞ አውቆ ነው መሰለኝ ፈራሁት። ባሌን ፣ አብሬው ኑሮ የምጋራውን አጋሬን፣ አቅፌው የምተኛውን ፍቅሬን፣ ምንም የማልደብቀውን የልብ ጓደኛዬን ……….. ማፍቀሬ በደል ሆነብኝ። ስለየትኛውም ስሜቴ ይዳኘኛል ብዬ የማላፍረውን ባሌን ፍቅሬን ዋሸሁት። ከንፈሮቹ እሱ እንደሚለው ከስሜት መጠቃቀም ልቀው መለኮታዊነት ያለበት ዓለም ውስጥ እንደሚከቱኝ መንገር አፈርኩ።

........ አልጨረስንም……………..

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት
(ክፍል ስምንት ………. ሜሪ ፈለቀ)

ጥፋቴ ማፍቀሬ ነበር አላልኳችሁም? የትኛው ዓመት ፣ መቼ ላይ እንዳፈቀርኩት እንኳንኮ አላውቅም! ቀስ በቀስ ……. መሰረቱን ሲጥል ….. ግድግዳውን ሲገነባ ….. ጣራውን ሲከድን …… ቀለም ሲቀባባባ ፣ ወለሉን ሲያሳምር …… ገዝፎ ገዝፎ ተሰርቶ አልቆ …… በአራተኛው ዓመት በራሴ ላይ ማዘዝ የማልችል ሆኜ ሽምድምድ ካልኩ በኋላ ነው ከእንቅልፉ እንደባነነ ሰው የማደርገው ጠፍቶኝ ጥፋት እንዳጠፋ ህፃን ባየሁት ቁጥር ልቤ ከአቃፊዋ ካላመለጥኩ ትል የጀመረችው:: ሰርቆ መች ከመቼ ተነቃብኝ እንደሚል ሌባ ..

መሰረቱን ሲጥል

በተጋባን በሆኑ ወራቶች ውስጥ የሆነ ቅዳሜ ከሰዓት ሁሌም ላይብረሪ ሲቀመጥ እንደሚያደርገው ስልኩን አጠፋፍቶ እያነበበ ነበር። ሁሌም ማንበብ ሲጀምር በስርዓቱ ወንበሩ ላይ ተቀምጦ መፅሃፉን ጠረዼዛው ላይ አስቀምጦ ነው።
ከሆነ ሰዓት በኋላ ተነስቶ እየተንጎራደደ ማንበብ ይጀምራል። ይቆይና ደግሞ ምንጣፉ ላይ ቁጭ ብሎ መደርደሪያውን ተደግፎ ያነባል። ቀጥሎ በደረቱ ምንጣፉ ላይ ይተኛል። ወይም በጀርባው። ሁሌም ቅደም ተከተሉ ይለያያል እንጂ እንዲህ ይመሳቀላል። የዛን ቀን ራሴን አሞኛል ብዬው ምንጣፉ ላይ ተቀምጦ እግሮቹ ላይ አስተኝቶኝ እያነበበ ፀሃይ ስትጣደፍ ገባች

«የሆነ ሰውዬ እየፈለገህ ነው! » አለች።

ተከታትለን ወደሳሎን ገባን። ቤታችን እኔን ብሎ የሚንጋጋው የእኔ ዘመድ እንጂ ማንም ሰው እሱን ፈልጎት መጥቶ አያውቅም። ከሰውየው ጋር እንደተያዩ እንደሚግባቡ ያስታውቃሉ።

«ህሊና በጣም ታማለች። ስልክህን ደጋግሜ ብደውል አታነሳም። ይቅርታ የነፍስ ጉዳይ ባይሆንብኝ እቤትህ ድረስ መጥቼ አልደፍርህም!» አለው ሰውየው።

አዲስ ምንም ቃል አልተነፈሰም። ዞር ብሎም አላየኝም። ሊያስረዳኝም አልሞከረም። ከነቱታው በሲሊፐር ዋሌቱንና ጃኬት ብቻ አንስቶ ወጣ! ህሊና ማናት? ስልኩን እንኳን አልያዘም! እንዲህ አለት ልቡን የነቀነቀችው ማናት? እህቱ? ሚስቱ? እናቱ? ልጁ? አላውቅማ!! ስለእርሱ ከግምት ውጪ የማውቀው የለማ!! ብቻ ማንም ትሁን ቀናሁባት! የዛን ቀን ማታ ምንም ቢፈጠር ከቤቱ ውጪ የማያድረው ሰው እቤት አልመጣም አደረ። ምኑ ልትሆን እንደምትችል እያንዳንዱን ምርጫ እያሰላሁ መኝታ ቤቱን በእርምጃዬ ስመትር ነጋ!! ጠዋት የዛለ ሰውነቱን እየጎተተ መጣ!

«ማናት?»

«ህፃን ልጅ ናት! ታማ ነው።»

«እኮ ማን ናት? ምንህ ናት? ከቀድሞ ትዳርህ ልጅ አለህ?»

«ያልነገርኩሽ እንጂ የዋሸሁሽ ነገር የለም! ልጅ ኖሮኝ ለምን ዋሽሻለሁ?»

«አላውቅም አዲስ! አላውቅህምኮ! ምንም ስላንተ የማውቀው ነገርኮ የለም።»

«እኔ ያለፈ ታሪኬ ውስጥ የለሁም! እኔ ይሄ ዛሬ የምታዪው አዲስ ነኝ። ድሮዬ ውስጥ አትፈልጊኝ። ማወቅ ኖሮብሽ ያልነገርኩሽ ምንም የለም! የምዋሽበት ምንም ምክንያት የለም! ራስሽን አታድክሚ! ብሎኝ ልብሱን አወላልቆ አልጋ ውስጥ ገባ! «ይልቅ ነይ ተኚ! በኃላ አስረዳሻለሁ»

ከእንቅልፉ ሲነሳ ህሊና የተኛችበት ሆስፒታል ወሰደኝ። የ12 ዓመት ህፃን ናት። ማታ እቤት የመጣው ሰውዬ አጠገቧ ነበረ። ከህፃኗ ጋር ሲጫወት ሳየው የሆነ የማላውቀው ሰው ነው። ግራ መጋባቴ ገብቶት ይሆን ሰውየው አዲስን በፈገግታ እያየ ። «መቼም እሱ ባይኖር እነዚህ ህፃናት ምን ይውጣቸው እንደነበር? ቅድም ስታቃስት ሁሉ ነበር አሁን እሱን ስታይ ዳነች።» አለኝ።

«ልጅ መውለድ አልፈልግም ማለት ልጅ አልወድም ማለት አይደለም። እነዚህ ወላጆቻቸው ያለሃላፊነት ወልደው ለቁር እና ለጠኔ የዳረጓቸው፣ ያለጥፋታቸው የተቀጡ ህፃናት ናቸው።» አለኝ እየወጣን። የመገረም አስተያየቴ ምን ማለት እንደሆነ ገብቶት።

«ለምን አልነገርከኝም?»

«ምን ብዬ? ደግሞስ ምን ይጠቅምሽ ነበር? ወላጅ የሌላቸውን ልጆች የሚረዳ መልካም ሰው ነው የሚለውን ካባ እንድትደርቢልኝ? ነውር አይደል? ምርጫ ባጡ ህፃናት ሆድ ውዳሴ መሰብሰብ ነውር አይደል?»

ዝም አልኩ!! በምቾት የተቀመጠበት ልቤ ውስጥ መሰረቱን አስፍቶ ቁልል አለ። ደሞ የሆነኛው ቀን ከስራ ደወለልኝና

«ፀዲ ታማ ብር ፈልጋ ጠይቃኝ ነበር። በዚህ ጉዳይ አውርተን ባናውቅም ሳልነግርሽ መስጠቱ ምቾት ስላልሰጠኝ ልንገርሽ ብዬ ነው። ይደብርሻል?» አለኝ

ፀዲ የመጀመሪያ ሚስቱ ናት። አሁን እሷ አግብታ ወልዳለች። የሆነ ቀን ሞል እቃ እየገዛን ልጇን በእጇ ይዛ ተገናኝተን አስተዋውቆኛል። የዛን ቀን

«ይገርማልኮ መቼም የሰው ልጅ ይቀየራል። አዲስ የሰርግ ግርግር ተመችቶት ደግሶ አገባ? ማመንኮ ነው የሚያቅተው? » እያለች ስታበሽቀው፣ እየሞላበት ያለበት ልቤ ውስጥ ገዘፈ። <ለእኔ ብሎ ነው ያደረገው!> ብዬ ማመን ፈለግኩ።

«አትስጣት ይደብረኛል ብልህ አትሰጣትም?» አልኩት።

«እሰጣታለሁ። አትስጣት የምትዪበት በቂ ምክንያት ካለሽ እናውራበት!» ሁሌም ይኸው ነው ፊት ይሰጠኝና ደግሞ ይኮሳተርብኛል። ያቀብጠኝና ደግሞ ይገፋኛል።

«አይ ዝም ብዬ ነው። ታገኛታለህ?» ድምፄ እሱ ላይ ስልጣን ስለሌለኝ ከመቅዘዝ ውጪ ምርጫ እንዳልነበረኝ አሳበቀብኝ።

«አዎ ሄጄ ነው ብሩን የማቀብላት። ታማለችኮ! (ትዝብት ያለበት አይነት ለዛ) መጥቼ ልውሰድሽ አብረን እንሂድ?» ይኸው ደግሞ ሲያቀብጠኝ። መጥቶ ይዞኝ እየሄደ

«ለምንድነው ያላመንሽኝ? ከፀዲጋኮ ተበቃቅተን ነው በምርጫችን የተለያየነው። ለምን የምመለስ መሰለሽ?»

«እኔ እንጃ! ዛሬም ላይ ግን ሲቸግራት የምትጠራህ ሰው ነህ! ምንም ማሰብ አልነበረብኝም? የእኔና ያንተ ትዳር እኮ በህግ እንጂ በፍቅር የቆመ አይደለም። ህግ ያለፍቅር አቅም ያጣል።»

«አብረሽኝ ደስተኛ አይደለሽም? እኔኮ ደስተኛ ነኝ ሌላ ሴትጋ የምሄድበት ምክንያት የለኝም። ለምን ታወሳስቢዋለሽ? አንቺጋ ጎድሎብኝ ሌላ ሴት የምፈልገው ጉድለት የለኝም።»

ይኼኛው ሁለት አይነት ስሜት ሰጠኝ። ደስተኛ መሆኑ ደስ አለኝ። አታወሳስቢው ያለበት ድምፅ ማስጠንቀቂያ መሰለኝ። እናም ላለማወሳሰብ ዝም አልኩ። በየሆነ ጊዜው የሚያስገርመኝ ባህሪውን አውቃለሁ። ላልወደው አልችልም ነበር። ግን ዝም አልኩ።

«ለምንድነው ይሄን ያህል ኢሞሽናልይ ከሰዎች ጋር መቆራኘትን የምትፈራው? ታዝናለህ ግን እንዳዘንክ ማንም እንዲያውቅብህ አትፈልግም፣ ትራራለህኮ ግን ድክመት ስለሚመስልህ ትሸፍነዋለህ፣ ትወዳለህ ግን መሸነፍ ስለሚመስልህ ትደብቀዋለህ።» አልኩት የሆነ ቀን እሁድ ህፃናቶቹጋ ውለን እየተመለስን።

«ሁሉም በድርብቡ ጥሩ ነው! ኢሞሽን በገዛ እጅሽ ነፃነትሽን በሸምቀቆ መጠፍነግ ነው። ለሀሴትሽ የተደገፍሽው ሰው የነገ ሀዘንሽ ምክንያት እንዲሆን ስልጣን እየሰጠሽው ነው። ማንም ሉጋም እንዲያበጅልኝ አልፈልግም። ተደግፌህ ጥለኸኝ ስትሄድ ወድቄ ተሰበርኩ ብለሽ ማንንም መውቀስ መብት የለሽም። የሰው ልጅ ይቀየራል። ሁሌ ላንቺ ደስታ ምክንያት ለመሆን ሲል ድጋፍሽ ሆኖ ተገትሮ አይቀርም። ይሄዳል። ማወቅ ያለብሽ በህይወትሽ ውስጥ ሰዎች ይመጣሉ። ይሄዳሉ። አብረሻቸው ስትሆኚ ጥሩ ጊዜ አሳልፊ! ሲሄዱ ተንቀሳቀሺ!! ያስተሳሰራችሁ መጠቃቀም ሲሳሳ ኢ,ሞሽን የምትዪው ብን ይላል። »
በተደጋጋሚ በየጨዋታው በኢሞሽን መጠለፍ እንደማይፈልግ እያስረገጠ ይነግረኛል። በቃ ምንም ስሜት የለውም እንዳልል እያንዳንዱ ድርጊቶቹ ለእኔ የሚታዩኝ በፍቅር ተጠቅልለው ነው። ምንም ስሜት የሌለው ሰው ከአራት አመት በኋላ እንኳን የሚስቱን ፀጉር ያጥባል? ምንም ስሜት የሌለው ሰው <ዛሬ የበላሁት ምግብ አልተስማማኝም መሰለኝ። አስመለሰኝኮ> ስለው በደቂቃ ቢሮ ድረስ መጥቶ ደህና መሆኔን ቼክ ያደርጋል? እሺ ምንም ስሜት የሌለው ሰው ከደረጃ ወድቄ እጄ የተሰበረ ቀን የታሸገውን እጄን ደረቱ ላይ አድርጎ ሳይንቀሳቀስ ያድራል? እሺ ምንም ስሜት የሌለው ሰው አራት ዓመት ሙሉ ነፍስ ከስጋዬ የሚያስቃትተኝ ፍቅር ይሰራል? እሺ ምንም ስሜት የሌለው ሰው <አይንሽ ላይ እንባ ሳይ ቀኔ ይበላሻል!> ይላል? እሺ ምንም ስሜት የሌለው ሰው <ጠዋት ሳትስሚኝ ሄጄ ሰራተኞቹ ላይ ተቀየርኩባቸውኮ! ለምን ሳትስሚኝ ሄድሽ?> ይላል።

ከዛ ደግሞ ዓለሜን ድብልቅልቁን ያወጣውና እኔ ከቀኑ ብጎድል ምንም እንደማይጎድልበት ይሆናል። በቃ ምንም እንደሆንኩ። የሆነኛው የህይወቱን ቀኖች አካሂያጅ ብቻ እንደሆንኩ። ምንም እንደማልመስለው። በዚህ ሁሉ ውስጥ የእኔ ነፍስ አንዲት ቀን ብቻ ተሳስቶ «ወድሻለሁኮ» እንዲለኝ ትፀልያለች። በስህተት እንኳን! ከፈለገ አይድገመው። አንዴ ብቻ! እሺ እሱ አይበለኝ እኔኮ «የእኔ ፍቅር » እንድለው እፈልጋለሁ። እሱ አይበለኝ ለምን እኔ የሚነድ ፍቅሬን መግለፅ እከለከላለሁ? ጠዋትኮ ስሜህ ወጥቼ ማታ እስክመለስ እንደቲንኤጀር እቅበጠበጣለሁ> ልለው እፈልጋለሁኮ። መስማት የማይፈልገው ነገር መሆኑን አውቃለሁ። ከአፌ እንዳያመልጠኝ ተጠነቀቅኩ፣ እቅፉ ውስጥ ሆኜ የምትደልቅ ልቤ የምታሳብቅብኝ ይመስል ተሳቀቅኩ!

ከአራት ዓመት በኋላ እንደለመድነው የቀን ውሏችንን እያወራን መኝታችን ላይ እየለፋን የሞላው ስሜቴ ገነፈለ፣ ያባበልኩት ፍቅሬ አመፀ

«እኔ ከዚህ በላይ ማስመሰል አልችልም! ከአቅሜ በላይ ነው የምወድህ!» እያልኩት እናቱ ናፍቃው እንዳገኘ ህፃን መንሰቅሰቅ ጀመርኩ።

................. አልጨረስንም……………………………

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት
(ክፍል ዘጠኝ ………. ሜሪ ፈለቀ)

«እኔ ከዚህ በላይ ማስመሰል አልችልም! ከአቅሜ በላይ ነው የምወድህ!» እያልኩት እናቱ ናፍቃው እንዳገኘ ህፃን መንሰቅሰቅ ጀመርኩ።

የሚያስለቅሰኝ ምኑ እንደሆነ ለራሴ ምክንያት መስጠት አልቻልኩም። ፍቅሩ፣ ፍርሃቴ፣ ሳልናገር መታፈኔ ……… አላውቅም። እንደህፃን ድምፅ አውጥቼ እዬዬ ማለት ጀመርኩ። እሱ መጀመሪያ እየከወነ ያለውን ልፋት በቀስታ አቆመ።

«አውቃለሁኮ! » አለ ለእኔ ይሁን ለራሱ የተናገረው በማያስታውቅ አወራር። <አውቃለሁኮ!> ያለበት አባባል <አውቄልሻለሁኝኮ! ፍቅርሽ ገብቶኛል፣ ተረድቼሻለሁ።> ዓይነት አይደለም። የሆነ የቁጭት ዓይነት፣ የብስጭት ዓይነት ነበር። …….. መንሰቅሰቄ ሲብስበት በጎኑ ተኝቶ ደረቱ ላይ አጣብቆ አቅፎኝ ዝም አለ። የሳጌ ድምፅ ከፍ ሲልበት እቅፉን ጠበቅ ያደርገዋል። እንደማባበል ዓይነት። ደቂቃዎች ካለፉ በኃላ ………….. ለቅሶዬን ያለከልካይ ካስነካሁት በኃላ………. እንባዬ ደረቱን ካራሰው በኋላ ………. ከዚህ ሁሉ ደቂቃ በኋላ ጭንቅላቴን ከደረቱ ወደ ክንዱ አሸጋግሮ ቀና አለ። ባላቀፈኝ እጁ ፀጉሬን ከግንባሬ ላይ አሸሸው፣ በእንባ የተጨማለቀ ፊቴን ጠራረገ ፣ የስስት ይሁን የፍቅር ይሁን መግለፅ በማልችለው ስሜት ዓይኔን ፣ ጉንጬን ፣ አፍንጫዬን፣ አገጬን ፣ ግንባሬን ፣ አንገቴን ……… ፊቴ ላይ ስማቸውን ሁላ የማላውቃቸውን ቦታዎቼን በቀስታ እና በተመስጦ ሳማቸው። ከንፈሬን ስሞኝ እንደማያውቀው ፤ ተሰምቶኝ እንደማያውቀው እና የእርሱ እንዳልሆነ አሳሳም እየሳመኝ አቋርጦ

«ልትዪኝ ፈልገሽ ያላልሺኝን፣ ልትነግሪኝ ፈልገሽ ያልነገርሽኝን ንገሪኝ፣ ማድረግ ፈልገሽ የቆጠብሽውን አድርጊኝ! » ይሄን ያወራበትም ድምፀት የእርሱ አልነበረም። የሆነ ፊልሞች ላይ ያለ ያፈቀረ ሰውዬ ድምፀት ነበር።

«ያ ማለት በፈለግኩት ቁልምጭ መጥራትንም ጭምር ያካትታል? (ፈገግ እንደማለት ብሎ በጭንቅላቱ ንቅናቄ አዎ አለኝ) እሺ እያደረግንም እንዴት እንደማፈቅርህ ማውራትንም ይጨምራል?»

«የፈለግሽውን! ያለምንም ገደብ!»

ለምን ብዬ አልጠየቅኩም። ሊሰማው የማይፈልገውን ሁሉ በነፃነት እንድለፈልፍ ለምን ነፃነቱን እንደሰጠኝ የምጠይቅበት ማሰቢያ እንዳይኖረኝ ፍቅሩ አቃቂሎኛል። ነገርኩት። ምንም ነገር በዝህች ምድር ላይ ቀርቶብኝ እሱን እንደምመርጥ ነገርኩት፣ ከእርሱ ጋር እስከሁሌውም የመኖር ልዋጭ ከሰጠኝ እናት መሆንን በሱ ፍቅር ለመለወጥ እንደማላመነታ ነገርኩት፣ አብሬው እየኖርኩ ሁላ አቅፌው እየተኛው ሁላ እቅፉ ውስጥ ሆኜ ሁላ እንደምሳሳ ነገርኩት፣ እኔ እንደማፈቅርህ አፍቅረኝ ብዬ አልልህም ምላሹን አልጠብቅም ግን የእኔ ብቻ ሁንልኝ አልኩት፣ አንተ አታፍቅረኝ እኔ ግን በፍቅርህ ስለተሸነፍኩ እንድፈራህ አታድርገኝ አልኩት………. አልኩት …….. ብዙ ነገር አልኩት። በማውቀው የፍቅር ቁልምጭ ሁላ ጠራሁት። እየደጋገመ ያን የእርሱ ያልሆነውን አሳሳም ከመሳም ውጪ ምንም ነገር አላለኝም። ለብዙ ደቂቃ ያለከልካይ ባለኝ አቅምና ችሎታ ሁላ ፍቅሬን ደስኩሬ ሳበቃ የእርሱ ያልሆነ ዓይነት ፍቅር ሰራን …… ምንም ወሬ የሌለው፣ ግን ያለወሬ ወሬ ያለው፣ በጣም ለስላሳ አይነት ነገር ……. በወሬው ምትክ ብዙ መሳም ያለው….. በዓይኖቼ ውስጥ አድርጎ ልቤጋ የሚያደርሰው ዓይነት አስተያየት በየመሃሉ ያየኛል። በሰዓቱ ያልገባኝ ሀዘን እና ስስት ዓይኑ ውስጥ ነበረ። ስንጨርስ እንደቅድሙ ደረቱ ላይ አጥብቆ አቀፈኝ።

ደስ ሊለኝ ነበር የሚገባው አይደል? በምትኩ ነፍሴ ድረስ የዘለቀ የሚያርድ ፍርሃት ነበር የተሰማኝ። አቅፎኝ አስባለሁ። ያስባል። ከብዙ ሀሳብ በኋላ እንቅልፍ ወሰደኝ። ስነቃ ስንተኛ እንደነበረው። የራስጌው መብራት እንደበራ ፣ የምበር ይመስል አጥብቆ እንዳቀፈኝ ፣ዓይኖቹ እንዳፈጠጡ ነው።

«እንቅልፍ አልወሰደህም?»

«አዎ! አልተኛሁም! አሁንማ ነጋ!»

«ምን እያሰብክ ነው?»

«አንቺን!»

«እቅፍህ ውስጥ ሆኜ ስለእኔ ምን ያሳስብሃል?»

አልመለሰልኝም። ተነስቶ ገላውን ተጣጥቦ ሳይስመኝ ቀድሞኝ ወጥቶ ወደስራ ሄደ። ቀኑን ሙሉ መብላትም ማሰብም ልጆቹን ማስተማርም በትክክል ማሰብም ሳይሆንልኝ አሞኛል ብዬ አስፈቅጄ ወደቤት ተመለስኩ። ከስራ እስኪመለስ ጓጓሁም ፈራሁም። የጠዋቱን ሳይሆን የማታውን አዲስ ቢመልስልኝ ፀለይኩ። እየደጋገምኩ <ምናለ ባልነገርኩት?> እላለሁ። ደግሞ መልሼ <አልችልም ነበር> እላለሁ። የሆነኛው እኔ አዲስን ላላገኘው እንደሸኘሁት ነግሮኛል። የሆነኛው እኔ ያን ማመን ስላልፈለገ ጥሩ ጥሩውን ሰበብ ይጎነጉናል። ያልበላሁት ምግብ ሊያስመልሰኝ ያቅለሸልሸኛል። እጄን ያልበኛል። ስቀመጥ ስነሳ ውዬ መጣ። ሲገባ እንደሌላው ቀን አልሳመኝም። ያ የምፈራው አዲስ ሆነ። ጠበቅኩት ከአፉ የሆነ ነገር እንዲወጣ። ምንም ቃል ሳይተነፍስ እራት ቀርቦ በላን።

«ውሎህ ጥሩ ነበር።»
«የተለመደው ዓይነት»

ደሞ የማወራው እፈልግ እፈልግና
«ዛሬኮ አሞኝ ጠዋት ነው አስፈቅጄ የመጣሁት።»

አሞኛል ስለው አጠገቤ ዘሎ ደርሶ የሚነካካኝ አዲስ ምንም ስሜት በሌለው ቀና ብሎ እንኳን ሳያየኝ

«ምነው? ጠዋት ደህና አልነበርሽ?»

እራቱን ሲጨርስ ወደ ላይብረሪው ሄደ። መኝታዬ ላይ ተኝቼ ከአሁን አሁን መጣ ብዬ ስጠብቀው እና በሃሳብ ስባዝን እንቅልፍ ይዞኝ ሄደ። ለሊት 10 ሰዓት ስባንን አጠገቤ የለም። ተነስቼ ላይብረሪው ስሄድ እዛም የለም። ክፍሎቹን እየከፋፈትኩ የሆነኛው ሌላ ክፍል ተኝቶ አገኘሁት። ማልቀስ አማረኝ። እሪሪሪሪ ብዬ ማልቀስ ……. የመብራት መብሪያ እና ማጥፊያ ቀጭ ሲል የሚነቃ ንቁ ሰውዬ በሩን ከፍቼ ስገባ እንዳልነቃ ሰው ረጭ ብሎ የተኛ መሰለ። በሩን መልሼ ዘግቼለት ወጣሁ። ይሄ ቂል ልቤ ደግሞ <አምሽቶ እንዳይረብሽሽ ነው ሌላ ክፍል የተኛው> ይለኛል። ሄጄ አልጋዬ ላይ ተገላበጥኩ እና ነጋልኝ። የተኛበት ሄጄ

«አውራኝ ምንድነው ያደረግኩህ? ማፍቀሬ ሃጥያት ነው? ቆይ እሺ ደግሞስ ላፍቅርህ ብዬ መሰለህ ያፈቀርኩህ? ለየትኛው በደሌ ነው የምትቀጣኝ? ታውቅ ነበርኮ አይደል እንዳፈቀርኩህ? አፌ ላወራቸው ቃላት ነው የምትቀጣኝ?»

ጥያቄም አልነበረም። ልመና ነበር። መጨረሻ ላይ ከአፉ የወጣው ቃል።

«እንፋታ!» የሚል ነበር። ራሴን የምስት መሰለኝ። የሰማሁትም ቃል እኔ ጆሮጋ ሲደርስ አበላሽቼ ሰምቼው መሰለኝ

«ምን? እንፋታ አይደለም አይደል ያልከው?»

«ነው! እንፋታ ነው ያልኩሽ!» ቃላቶቹን ሁሉ ሲላቸው በጭካኔ ነበር።

«እህህ ቆይ ምንድነው ያደረግኩህ? ንገረኝ ምንድነው ምክንያትህ?»

«ምክንያቴን ልነግርሽ አልችልም! »

« በእኔ መፈቀር የዚን ያህል የሚያስጠላ ነገር ነው? ፍቺን የሚያስመርጥ ነው? በመነጋገር ታምን የለ? የማንነጋገረው ነገርኮ ኖሮ አያውቅም! እሺ ፍታኝ ግን ቢያንስ ምክንያቱን እንኳን ማወቅ የለብኝም?»

ተነስቶ ከአልጋው እየወረደ ያሳዘንኩት በሚመስል ሁኔታ በሚያባብል ድምፅ
«ላንቺ ምክንያቴን ለማስረዳት መቼም አልነግርሽም ያልኩሽን ድሮዬን ማስረዳት አለብኝ። እሱን ማድረግ ደግሞ አልፈልግም። ምክንያቱ ለእርሱ በቂ ቢሆን ነው ብለሽ አስቢው። ደግሞ ውላችን አንደኛው አካል መፋታት ከፈለገ……… » ሳይጨርስ ጮህኩኝ እንባ ያነቀው ጩኸት ፣ እልህ ያነቀው ንዴት

«ውል ህግ አትበልብኝ። ውልና ህግ ብቻውን የሰውን ህይወት ቢመራ ዛሬ ያንተ መጫወቻ አልሆንም ነበር።» ጥዬው ወጣሁ።
ከዛ ቀን በኋላ እንደፈለገው እንዲሆን ተውኩት። ጭራሽ ሊያየኝ አለመፈለጉን አከበርኩለት። እኔ ግን በየቀኑ አለቅኩ። በ50 ኪሎሜትር ርቀት ዓይነት እየገፋኝ በ100 ኪሎሜትር ዓይነት ርቀት ወደእርሱ እወነጨፋለሁ። ሁሉ ነገር አቃተኝ። በሳምንታት ውስጥ እያየሁት ሰውነቴ ቀነሰ። መልበስ፣ መብላት፣ መስራት፣ መተኛት …….. ሁሉ ነገር ታከተኝ። ከሳምንታት በኋላ ስለእርሱ ላወራው የምችለው ሰው ትዝ አለኝ። ፀዲ! የመጀመሪያ ሚስቱ! ያኔ ብር ልናቀብላት እቤቷ ሄደን አልነበር?

«እመኚኝ አንቺ ከምታውቂው የተለየ ስለእርሱ የማውቀው ነገር የለም። እኔ የመጀመሪያው ስለሆንኩ የማውቀው ነው የሚመስላችሁ?» ስትለኝ በብዙ ቁጥር የጠራችኝ ከማን ጋር ደርባ እንደሆነ ሳስብ ሁለተኛ ሚስቱ ልክ እንደእኔ ግራ ሲገባት መጥታ አዋርታት እንደነበር ነገረችኝ።

«እኔ ሳገባውም በፍቅሩ ጧ ብዬ ነው ያገባሁት። እንደምታውቂው ነገረ ስራውን ላትወጂው አትችዪም። አስብ የነበረው ፍቅሩን መግለፅ ስለማይችል እንጂ ያፈቅረኛል ብዬ ነበር። ስህተቴ የነበረው ታውቂያለሽ < ብልህ ሴት ወንድን ልጅ ትቀይራለች> በሚል እሳቤ ነው ያደግኩት እና ከትዳር በኋላ ይቀየራል የሚለው እምነቴ ነበር። ተጋብተን መኖር ከጀመርን በኋላ ግን የሚያደርግልኝን የሚያደርገው በባህሪው ጥሩ ሰው ስለሆነ እንጂ በፍቅር አለመሆኑን አወቅሁ። በዛ ላይ ለማያፈቅረኝ ሰው ስል እናት የመሆን ስጦታን መዝለል ልቀበለው አልቻልኩም። የሆነ ቀን እንደምለየው እርግጠኛ ስሆን ተነጋገርን እና ተፋታን!!»

ስለእርሱ ሳወራ ከሚገባው፣ እሱን አብሮ ኖሮ ከሚያውቀው ሰው ጋር ስለእርሱ ማውራት የሆነ ደስ የሚል ስሜት ስለሰጠኝ ከእኔጋር የተፈጠረውን ስነግራት።

«በቃ?» ብላ ጮኸች

«አዎ በቃ!»

«የሆነ ነገርማ አለ። እንደምታፈቅሪው ስለነገርሽው እንፋታ አይልም አዲስ! ሳንጋባ በፊት ጀምሮ እስከምንለያይ ድረስ እንደማፈቅረው በየቀኑ እነግረው ነበር። ከእርሱ ምንም ምላሽ አታገኚም እንጂ ያንቺን ስሜት አይከለክልሽም! Come on ሰውየውኮ አዲስ ነው። የሰው ልጅ ሀሳቡን ሳይበርዝ በነፃነት መግለፅ አለበት ብሎ የሚያምን ሰው ነው። ያመነውን ደግሞ እንደሚኖር ታውቂያለሽ።»

«በእናቴ እምልልሻለሁ ያልነገርኩሽ ነገር የለም። ከዚህ የተለየ ያደረግኩት ምንም ነገር አልነበረም።!»

«ሰብለን ከፈለግሽ ጠይቂያት (ሁለተኛ ሚስቱ ናት) እሷም እንዳንቺ ከገባች በኋላ ነው በፍቅር የበሰለችው። ምላሹን እንደማታገኝ ተስፋ ቆርጣ ፍቺ እስከፈለገች ቀን ድረስ እንደምትወደው ነግራዋለች። ምንም ሊገባኝ አልቻለም። ohhh my God ማሰብ እንኳን አልችልም! ምናልባት የራሱን ስሜት እንዳይሆን መሸሽ የፈለገው? » ብላኝ የሆነ ግኝት እንዳገኘ ሰው ጮኸች።

…………. አልጨረስንም ……………………….

@wegoch
@wegoch
@paappii
Forwarded from Sunset Hiking
#Sunsethiking is hosting a day hike to " Lake Dembel(Ziway)"

💡Hiking Date :- May 22, 2021 (Ginbot 14, 2014)

💵 Hiking Cost:- 874.99 ETB only

🛫Departure: Piasa (Taitu Hotel)
@1:00 Am LT

🎉🎊Package includes🎋🎊

🚣‍♀️ Boat trip
🚍 Transportation
🌲 Bottled water
🌺 Guide + scout
🍂 photography 📷
💐 Breakfast
🏖 lunch
🧜‍♂️ Swimming
🐠 Eating fish(self sponsered)


💦Sanitizer & facemask mandatory!
☘️walking hour: 3 hour (up to 5 km of walking)
Hiking Level: Medium !

for more join the
🎸@sunsethiking👣
🏓@sunsetphotography📸
🍿@sunsethikers

🎫 tickets available at
@Paappii ( +251922303747)
አከራዬ ጋሽ ፋንቱን ፈጣሪ እጄ ላይ ጣላቸው።
ለዛን ቀን ባለቤታቸው እትዬ ዘነቡ ቤተስክያን ሄደው ነበር። እጅግ ሲበዛ አማኝ ናቸው። ከዓመታት በፊት የዓለም ዱብ ዱብ በቃኝ ብለው ቆረቡ ።
ጋሽ ፋንቲሽ ቁረቡ ቢባሉ ወይ ፍንክች እቴ!
ሰው እንዴት ሲሸመግል ፍንዳታነት ይብስበታል። በተለይ አመሻሽ ላይ አንድ ሁለት ብለው ሲመጡ ሀገር ምድሩን በብልግና ይሳደባሉ ። ደግሞ በዛ ላይ ፖለቲካ አይፈሩም... ብልፅግና ን ሙሽልቅ አድርገው ይራገማሉ ። የሰከሩ ጊዜ መንግስትን መራገም ብቻ ሳይሆን ግቢያቸው የበቀሉ የዳማከሴ ችግኞችን እየነቃቀሉ "ይኸው ችግኝ ነቀልኩኝ.. .ምናባህ ታመጣለህ? " እያሉ የሆነ ሰውዬን ይሞሸልቃሉ ። ከዛሬ ነገ ይታሰራሉ ብዬ ብጠብቅም ዝንባቸውን እሽ የሚል አንድ ደህንነት እንኳ የለም (ሼባ አስሮ ማን ይቀልባል? ")- ብለው ንቀዋቸው ነው መሰል !
መንግስት ባያስራቸውም እኔ ግን ትልቅ ጅራፍ ገመድኩላቸው ።
አይናለምን (-የቤት ሰራተኛቸው ነች) ...መቀመጫዋን እንደ ጠንቋይ ድቤ ሲነርቱት እጅ ከፉ ያዝኳቸው። አይናለም የኔን ማየት ስታይ ከበረንዳው ዘላ ወደ ማጀት ገባች (በረረች ብል ይቀለኛል)
ጋሼ ፈገግ ብለው "ልጄ መቼም የወንድ ልጅን ነገር ታውቀዋለህ። ይሄ የራስ ዳሽን ተራራ የሚያህል መቀመጫዋን ስትንጥብኝ አልቻልኩም...አቀለለችኝ" አሉ ።
"ኸረ ያለ ነው አባባ...ትንሽ ግን አመታቱን ከበድ አደረጉት ። ታይሰን እንኳ ይሄን ያህል ቡጢ የሚሰነዝር አይመስለኝም " ብዬ አጫወትኳቸው።
"ኸረ የሷ የጉድ ነው። እንዲህስ ተነርቶ መቼ ይተነፍሳል ? አሁንማ ስፋቱ ብሶበት አንተ የተከራያሀትን ክፍል ሊያክልልህ ነው" አሉኝ ።
በርግጥ ጋሼ ሀቅ አላቸው። ምፕንግስት የአይናለም መቀመጫን ቢያየው አዲስ የፓርክ ፕሮጀክት ይነድፍበት ነበር።
ከዛች ቀን በኋላ ደረት አነፋፌን ላየው ግቢው የኔ የሆነ ነበር የሚመስለው።
እንደ በፊቱ ጋሼ ፊቴን ሲያዩ ቤት ኪራይ ጨምር ይሉኛል የሚል ስጋት የለብኝም። አንዳንዴ እንደውም ማለዳ ላይ በራቸውን ቆፍቁፌ ራሱ "ሰላም አደሩ?" እላቸዋለሁ ።
ለዓመት ያህል እንኳን ቤት ኪራይ ጨምር ሙዚቃህን ቀነስ አድርግ የሚል ግልምጫ እንኳ የለም።
አንድ ቀትር ላይ ግን እትዬ መጡ.. .
የቤቷን ደረጃ እንደ ኤሊ ተንቀራፈው ወጥተው
"ልጄ" ሲሉ ጠሩኝ።
"አቤት ማዘር ..."
"እኔ ምልህ ኑሮ እኮ ደመና ጠቀሰ ...ጢያራ ተሳፍረህ ካልሆነ መልኩ አልታይ ብሏል " አሉኝ። ይህች የዘፈን ዳርዳርታ ቤት ኪራይ ጨምር ሊሉ እንደሆነ ነፍስያዬ ሹክ አለችኝ።
"መንግስታችን ፓርክ ውስጥ ለሚያረባቸው አንበሶች መኖ ብሎ ይሆን ሁሉ ነገር የጨመረብን?" አሉኝ ለጥቀው።
"እንጃ ይሄ የኑሮ ውድነት ለአሳ ነባሪ እንጅ ለአንበሳ መኖ ነው ብለው ነውን?"
ቂ....ቂ...ቂ
እትዬ ተፍለቀለቁ።
"መቼም ትረዳኛለህ.. .ዛሬ አንድ ሺህ ብርም ዋጋ የላት ...ባይሆን ቀጣይ ወር ላይ የበፊቱ ኪራይ ላይ ሺህ ተሁለት ጨምርባት " አሉኝ።
"ማዘር እኔ ዘንዳም እኮ ነው ኑሮ የጨመረው "
"አይ አንተ ትሻላለህ.. . ከቢሮ ስራ በተጨማሪ እንደ ደብተራ ግጥም ምናምን ሞጫጭረህ ትሸጥ የለም ? ራድዮ ላይ እኮ ስትተርክ ሰምቼህ አውቃለሁ "
"ግድየለም ማዘር...እርሶ ብቻዎትን ከሚጨናነቁ... ስለዚህ ጉዳይ አባባን ያማክሯቸው። እሳቸው ይጨምር ካሉ ምን ገዶኝ? " ብዬ መለስኩላቸው።
"ይሁና.. ." እንደ ኤሊ እየተንቀራፈፉ የወጧትን ደረጃ እንደ ጥንቸል ብር ብለው ወረዷት (ንዴት እኮ ነው!)
በነጋታው ከስራ መልስ ቦርሳዬን አንግቼ ወደ ግቢ ስገባ እትዬን በረንዳ ላይ ቡና ሲያፈሉ አገኘኋቸው ።
"እስቲ ሚካኤል አንዴ ትመጣ? " አሉኝ.. .ተጠጋኋቸው ።
"ሽማግሌው ባንተ ጉዳይ ምን እንደነካው አላውቅም ... ተይው ብሎኛል " አሉኝ።
እጅግ አመስግኛቸው ወደ ቤቷ ጀርባ መጓዝ ስጀምር.. .
"ይሄ ምናምንቴያም ደብተራ ባሌን ምን እንዳስነካብኝ እንጃ! " የሚል ማጉረምረም ሰማሁ ።

(ሚካኤል .አ)

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት
(ክፍል አስር ………. ሜሪ ፈለቀ)

«የእናቱን ለቀናት የቆየ የሚሸት ሬሳ ታቅፎ ከጎሮሮው የማይወጣ ጩኸት ጮኸ። ድምፁ ከጉሮሮው እንደማይወጣ ቢያውቅም በሆነ ተዓምር የሆነ ሰው እንዲደርስለት ተመኘ። በማይሰማ ድምፅ ሊደርስለት የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ እንደሆነ ስላወቀ አይኞቹን ጨፍኖ <አምላኬ ሆይ እባክህ ድረስልኝ? እባክህ ድረስልኝ? እባክህ? ……… > እያለ በልቡ የፀለየውን ባይሰማው እንኳን እንባውን አይቶ እንዲራራለት እራሱ እግዚአብሔር ቢያጠራቅመው ለአንድ ክረምት የሚበቃውን እንባ አነባ። እግዚአብሔር ግን ለልቡም ፀሎት ለዓይኑም እንባ መልሱ ዝም ነበር! ዝም!! » የመጨረሻዎቹ ቃላት ላይ ድምፁ እየቀነሰ፣ እየሻከረ መጣ። ከመጀመሪያው ዓረፍተ ነገር በኋላ አልፃፍኩም። ጣቶቼ አደጋ ከደረሰባቸው የእርሱ ጣቶች በላይ ተንቀጠቀጡ።

«ስንት ዓመቱ ነበር?» አልኩት ቀና ብዬ

«አስራ ሁለት» አለኝ። ስሜቱ መረበሹ በግልፅ እያስታወቀበት አስተካክሎ መግፋት የለመደውን ዊልቸር እየገፋ ላይብረሪ ውስጥ ወዲህ ወዲያ እያለ። የህይወት መርሆቹ እና የሚያስብበት ጥግ፣ ሀሳብን የሚገልፅበት መንገድ ሁሌም ሲያስገርመኝ <አንተኮ መፅሃፍ መፃፍ ነበረብህ!> እለዋለው። ሁሌም መልሱ ተመሳሳይ ነበር። <መስራት ሲደክመኝ ወይ ማቆም ስወስን …… በደንብ ጊዜ ሲኖረኝ እፅፋለሁ። አንድ መፅሃፍ ይኖረኛል። እሱም የራሴ ባዮግራፊ ነው የሚሆነው።>

ከቀናት በፊት ከተለመደው የፊዚዮቴራፒ ህክምናው እየተመለስን ድንገት የሆነ መገለጥ እንደበራለት ሰው።

«አሁን ጊዜው አይመስልሽም?» አለኝ። ቀጠል አድርጎ ግራ በመጋባት ለጥያቄ የተሰናዳ አፌን ከመክፈቴ በፊት « መፅሃፌን ለመፃፍ?»

«ጣቶችህ አሁንም ቢሆን ይቀራቸዋል። ዶክተሯን አልሰማሃትም? 100 ፐርሰንት እስኪሆን ጫና እንዳታበዛበት ብላሃለችኮ!»

«አውቃለሁ! እኔ እየነገርኩሽ አንቺ ትፅፊልኛለሽ ብዬ ነበር ተስፋ ያደረግኩት!!»

«መቼ እንጀምር?»

ሚስጥር ማወቅ ነው ያጓጓኝ። እንጂ ከእርሱ ትናንትጋ ራሴው ተላትሜ አዙሪት እንደሚሆንብኝ አላሰብኩም። ሚስጥር ማወቅ የሆነ የመለኮታዊነት ዓለም ተቋዳሽ የመሆንን ስሜት ስለሚፈጥር ይመስለኛል ደስ የሚለው። ስለሆነሰው ከአምላክ ውጪ ማንም ሰው አያውቀውም ብለን የምናስበውን ማወቅ …………

ያቺ ባለፈው የመጣችው ሴት ማንናት? ያቺ ድሮዬ ውስጥ ነበረች ያላት ሴት ምን አይነት ነበረች? በቃ ስለእርሱ ማወቅ። እሱ ድሮዬ ውስጥ አትፈልጊኝ ይለኛል እንጂ ድሮ ቢቀብሩት እንኳን አራሙቻውን በጣጥሶ ዛሬን የማነቅ ጉልበት እንዳለው አውቃለሁ። አንዳንድ ድሮ ይብሱኑ ክስተቱ ከሆነበት ጊዜ ይልቅ ዛሬ ላይ ይበረታል።

«አንቺ ብትሆኚ ታሪክሽን ከምንድነው የምትጀምሪው?»

«ከጡዘት! በህይወቴ ውስጥ ወሳኙ ነው ከምለው ምእራፍ! ከዛ ታሪኩን ወደፊትና ወደኋላ አጫውተዋለሁ። ሲጀመር ግን አንባቢን ሰቅዞ ከሚይዝ ቦታ ነው የምጀምረው።»

«ዝግጁ ስሆን እነግርሻለሁ።» ካለኝ ከቀናት በኋላ ነው ላይብረሪው ውስጥ የተከሰትነው። የምለው ጨነቀኝ። ያለፈውን ለማወቅ ከመጓጓቴ በላይ ገና ሳልጀምረው ልቤ ቀዘቀዘ።

«ለምን አሁን?» አልኩት ጭንቅላቴ ያሰበውን አፌ ሳያስፈቅደኝ

«ለምን አሁን ምን?»

«ለምን አሁን እንዳውቅ ፈለግክ? እንደዛ ላውቅህ ስቧችር ድሮዬ ውስጥ አትፈልጊኝ ብለኸኝ እኔን ግን በድሮህ እየቀጣኸኝ እንደዛ ስለምንህ ዝም ብለህ…….. ዛሬ ለምን?»

በረዥሙ ተነፈሰ እና እየመሰለው ምንም እንዳልመሰለው ሲሆን የሚያመጣትን ፈገግታ ፈገግ ብሎ
«መፃፉን ብትቀጥዪ ታውቂው የለ?»

«እሺ በቃ ወይ ደስ ከሚለው ህይወቱ እንጀምር?» አልኩት።

«ኦኬ! ደስ ከሚለው? ደስ ከሚለው ሆኖ አሁንም ጡዘት ያለበት? » እንደማሰብ ብሎ

« ሰውነቱ ከመቀዝቀዙ የተነሳ ለሰዓታት የተኛበት አንሶላ እንኳን ሳይሞቅ ድጋሚ ተመልሳ በሩን ከፍታ ገባች። እንደቅድሙ በሩን አላባበለችውም። ሆነ ብላ በሩን አስጩኻው ገብታ <ምንድነው ያደረግኩህ? ንገረኝ ምንድነው ጥፋቴ?> (ከዚህ በኋላ ያለውንም አልፃፍኩትም። አቁሜ ግን ቀና ማለት አቅቶኝ እየሰማሁት ነው።) <እንፋታ!> ሲላት ራሱን ሰማው»

ከተቀመጥኩበት ዘልዬ ተነሳሁ። «ይሄ ነው ደስ የሚለው ዘመኑ? ……. እሺ በቃ እኔ ለመፃፍ ዝግጁ አይደለሁም።!» ብዬ ከላይብረሪ ወጣሁ። ማልቀስ ካቆምኩ እጅግ ሰንብቼ ነበር። ማልቀስ አማረኝ።

እሱ የደስታው ጡዘት ብሎ የጀመረበት ታሪካችን የእኔ የመድቀቅ ጡዘት ነበርኮ! በቃ አለም ሁላ ከእርሱ ጋር በአሻጥር ትሰራ ይመስል ቀስ በቀስ የመኖር ማገሮቼ የምላቸው ሲመዘዙ ዓቅም አጥቼ ከማየት ውጪ ምርጫ አጥቼ ተምዘግዝጌ የወደቅኩበት ጡዘት ……

የዛን እለት

«እንዴት ቻልሽው? እንዴት ረሳሽው?» አልኳት ፀዲን

« የማትክጂው ሀቅ <ሰዎች ከአጋራቸው ጋር የሚያስተሳስራቸው የስሜት መጠቃቀም ሲጎድል ለዛ ሰው ያላቸው ስሜት ይጎድላል > የሚለው ነገሩ ልክ ነው። (ሳቅ አለች እዚህጋ የድሮውን በማስታወስ ዓይነት) የሆነ ጊዜ ላይ የተከራከርሽውን ፍልስፍናውን ሁሉ በራስሽ ላይ prove ስታደርጊለት ራስሽን ታገኚዋለሽ። ያለምንም ምላሽ ማፍቀር ይደክማል። የሆነ ቀን ራስሽን ሲደክምሽ ታገኚዋለሽ። ከፍ ሲልም በተጎዳሽው ልክ ስትጠዪው ራስሽን ታገኚዋለሽ።!»

«ይቅርታ አድርጊልኝና the most romantic የምትዪውን ቅፅበት ንገሪኝ? እባክሽ እንደድፍረት አትውሰጂብኝ በቃ ጭንቅ ብሎኝ ነው»

«ኸረ ችግር የለውም በናትሽ ይገባኛል!» ብላ እጄን ስትይዘኝ እንባዬን እንዴት ቁም ልበለው? ደንግጣ አቀፈችኝ። ከሳጌ ጋር እየተናነቅኩኝ አስሬ «ይቅርታ!» እላታለሁ።

«ወይኔ ፀደይ! አዲስ ምንድነው ያደረግከው?» አለች የሆነ ጣሪያው ላይ ሆኖ የሚሰማት ትንሽዬ አምላክ ይመስል። አባብላኝ ስታበቃ።

«የመጨረሻ የምንለያይ ቀን (እሩቅ የተጓዘ ፈገግታ ፈገግ አለች) <ለነበረን የሚታወሱ ትዝታዎች በጣም ነው የማመሰግነው። ለምትወልጃቸው ልጆች የምትገርሚ እናት እንደምትሆኚ አውቃለሁ! ካስፈለግኩሽ የልጅ ልጆች ወልደሽም ቢሆን አስታውሰሽ ከደወልሽልኝ የምችለውን አለሁ። ከእኔ ጋር ላሳለፍሽው ምርጥ ጊዜ እስካሁን ሰጥቼሽ ለማላውቀው ስጦታዎች ምትክ እና ለወደፊት ህይወትሽ መጀመሪያ ይሆንሻል።> ብሎ ንብረቱ ቢሰላ የሚያወጣውን እኩሌታ ገንዘብ የሰጠኝ።» ዝም ስትል ቀጣዩን እየጠበቅኩ እንደሆነ ገብቷት እንደመባነን ዓይነት« that was the most romantic day I ever had with him» ብላ ጨረሰችው።

«አላውቅም! ውላችሁን ስላፈረስሽ ንብረቱን ያልተካፈልሽ ነበር የመሰለኝ!»

«አዲስ ጥሩ ነገር ሰራሁ ብሎ አይነግርሽም! ራስሽ ካልደረስሽበት በቀር! ጥሩ ስለሆነ እንድትወጂው አይፈልግም ራሱን ስለሆነ እንድትቀበዪው ነው የሚፈልገው። ሲመስለኝ ለማንም ሰው ደስታ ሀላፊነት መውሰድ አይፈልግም። ችግሩ ደስታው አይደለም። ቀጥሎ ለሚመጣው ሀዘን ራሱን ተወቃሽ ማድረግ ስለማይፈልግ ይመስለኛል። ለደስታው ሰበብ የሆንኩትን ሰው የሆነ ቀን ለሀዘኑ ሀላፊ ነኝ ብሎ ስለሚያምን ይመስለኛል።»

«ደስተኛ ነሽ?» የሚለው ጥያቄ ከአፌ ከወጣ በኋላ ስላለፈው ይሁን ስለአሁኑ ህይወቷ የጠየቅኳት ራሴው ግራ ገባኝ።
2024/09/22 15:38:32
Back to Top
HTML Embed Code: