Telegram Web Link
እብድ አይፈቀርም ያለው ማነው?
-----------------------------------------

እንዲህ አልነበረምኮ ውላችን!ሊጠፋ እንደሚችል አልገመትኩም።ዩኒቨርስቲ ልንሄድ ምደባ የምንጠብቅ ሰሞን አንድ እብድ ሰፈራችንን ተቀላቀለ።እቁብ መጣልና የእድር መዋጮ መክፈል ላይ አልተሳተፈም እንጂ የማህበራዊ ህይወታችን አንዱ አካል ሆነ።ስሙን ሲጠይቁት "እንጃ"ነበር መልሱ።በዚያው ስሙ "እንጃዬ"ሆኖ ፀደቀ።

ቁርሱን አንዱ ቤት...ምሳውን ሌላ ቤት እየጠለፈ፣ራቱንም የራራ እያበላው ተጎራብተን መኖር ጀመርን።የሰፈሩ ጎረምሶች ተረባርበው መጠነኛ የላስቲክ ጎጆ አቆሙለት።

እና በመሀል እኔ የ 19 ዓመቷ ተስፈኛ ተማሪ ከእንጃዬ ለጠየቁኝ ሁሉ 'እንጃ!' የሚያስብል ፍቅር ነደፈኝ።ሲያመጣው ልክ የለው!
"አጃኢብ!....የሰለሞን ልጅ እብድ አፈቀረች"ተባለ።እብደቴ ሰርተፊኬት አገኘ።እናቴ ደነፋች!አባቴ ለያዥ ለገናዥ አስቸገረ።እገድላታለሁ ብሎ በእናቱ ስም ምሎ ሽጉጥ ደቀነብኝ።እኔም የልብ ልብ ተሰማኝና ጨርቄን ሳልል ማቄን እንጃዬ ቤት ከተምኩ።
እንጃዬ ብዙ አያወራም።ሳቅ ብቻ ነው መልሱ።ከስንት አንዴ ካወራም ምንም ይበሉት ምን "ይገርማል"ብቻ ነው የሚለው።
"እንጃዬ ግን ትወደኛለህ?

"ይ...ይገርማል"

"አባቴ'ኮ ሽጉጥ አወጣብኝ እንጃዬ ምን ላድርግ?"

"ሽጉጥ...ሽ...ሽጉጥ"መርበትበት የጀምራል።ሽጉጥ ካየ አልያም ስለሞት ከተወራ እንጃዬ የባሰ ሕመም አለበት።እኔም ነውር አልፈራም ነበር ቲሸርቴን አውልቄ ፊት ለፊቱ እቀመጥና ምላሹን ስጠብቅ

"ይ...ይገርማል "ይለኛል ። በዘመድ አዝማድ ብመከር አልሰማ አልኩ።እረዱኝ አልኩ።የዪኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሲሆን ጎንደር መመደቤን አወቅሁ።ጉዱ የመጣው ይሄኔ ነው።'እንጃዬን ትቼ የትም አልሄድም' አልኩ።ቤተሰቡና ዘመድ አዝማዱ ተረባርቦ የእንጃዬን ቤት አፈረሰው ። እሱ እንደነሱ ክፋት አያውቅ

"ይ...ይገርማል"ብሎ ዝምምም ነው።ክፍሌ ውስጥ ተቆለፈብኝ።አባቴ ቀኑ ሲደርስ ልብሴን በሻንጣ አስይዞ በግድ ጎንደር ሊልከኝ ሲል እጄን በምላጭ ከትፌ ራሴን ለመግደል ሞከርኩ።እናቴ ተንሰፈሰፈች...ግን ምንም ማድረግ አልቻለችም።ያው ተለክፌ አይደል?

እንዳወራ ቢፈቀድልኝ እኮ እንጃዬ ማለት መልዓኬ ነበር። እንደቅዱስ ገብርኤል ሰላምና ደስታን አብሳሪዬ!እሱ የቤት ኪራይ የለበት...የቀለብ ሸመታ አያስጨንቀው...ልብስ ልግዛ አይል ልጠብ የለ...የልጆቹ ነገር አያሳስበው... የቤተሰብ ክብር አይል!ብቻ በዚያ ኑረት ውስጥ ለኔ ብቸኛው ጥሩ ነገሬ እንጃዬ ብቻ ነበር።
የሆነ ምሽት ታዲያ ታላቅ ወንድሜ እና አባቴ ሊገድሉት ሲያሴሩ፣መልዐኬን ሊነጥቁኝ ሲዶልቱ ሰማሁ።ወፈፍኩ!ጨርቄን መጣል ቀረኝ።አብሮ እንደኖረ ቤተሰብ ሳይሆን መንገድ ላይ እንደተገኘ የማይታወቅ ሰው አቀለልኳቸው።ከስፍራቸው አነሱብኝ።የአባቴን ሽጉጥ አንስቼ ጭንቅላቴ ላይ ስደቅነው ወንድም ተብየው

"እስኪ ምላጩን በመሳብ ተባበሪን እስኪ!በፈጠረሽ ይህን ካረግሽ ውለታሽን አንችለውም!" አለኝ።አባትየው ግን ወደማባበሉ ዞረ።

"ህሊናዬ በፈጠረሽ እንዳታደርጊው ያስጠይቅሻል"ሲል ተማፀነኝ።እኔ ግን ብሶብኝ እርርርርፍ!

"ኧኧኧረ!ያስጠይቀኛል?አንተ እንጃዬን ስትገድል መላዕክት አይደሉ 'ሚቀበሉህ?"
እናቴ ከጓዳ ብቅ ብላ የያዝኩትን ስታይ በሚሰቀጥጥ ጩኸት ቤቱን አደበላለቀችው።አንጀቴ ተንሰፈሰፈ።የዚያን ቀኑን የእናቴን ሁኔታ ሳስብ ነው ምን ያህል ልክ እንዳለፍኩ የገባኝ።ልክፍቱ ግን አልተወኝም።

ስህተቴ ማፍቀሬ አልነበረም።ስህተቴ እብድ ማፍቀሬም አልነበረም።ስህተቴ ሰው እንደሚለው ከሆነ ደፋርነቴ ነበር።ለካ አንዳንድ ስሜቶች መዳፈናቸው የግድ ነ መሰለኝ!እንጃ!

መንደርተኛው ''ጉድ ጉድ ጉድ! ለየላት በቃ ይች ልጅ?እብድ አፍቅራ ራሷን ልታጠፋ?ምነው ደህና ልጅ አልነበረች?አይይ!ትልቁ ዳቦ ሊጥ ሆነ'' ሲለኝ ትልቁን ዳቦዬን ይዤ እንጃዬ ቤት ከተምኩኝ።ዳቦዬ ተባረከች።በእብዱ ካህን የክብር ካባዋን ገፈፈች።ለካ እንጃዬ ዳቦ መባረክ ያውቃል።የኔ ንፁህ!ጣጣችንን ጨርሰን እርቃኔን ከጎኑ ስጋደም ብርግግ ብሎ ተነሳ።ደንግጬ

"ምነው እንጃዬ?"ስለው

"ይ...ይገርማል"አለኝና መልሶ ተኛ።

ጠይም መልክ ከንፅህና ጋር ሲዋሀድ እንደዚህ ነው የሚያምረው?ገላውን የሰፈሩ ወጣቶች በሳምንትም ሆነ በሁለት ሳምንት አንዴ ያጥቡታል።ዳሩ እሱ ባይታጠብም ንፁህ ነው።ተባዮቹ ራሱ እሱጋ የሚመጡት ከየትም የማትገኝ ንፁሕ የደም ጠብታን ፈልገው ይመስለኛል።እርጋታ የሚዘዋወርበት ...ምቀኝነት የማያውቅ እንደ ምንጭ ውሀ የጠራ ደም ከሱ ሰውነት በቀር ሌላ የትም ያለ አይመስለኝም።ዝምታው ለሰሰሰስስስስ ያለ ንፋስ ነበር።ከቀትር ፀሀይ ቀጥሎ የሚመጣ!የሚያበርድ የሚያቀዘቅዝ...እያነቃ የሚያደነዝዝ ዓይነት!!

ልብ ከደነደነ ለካ ሽጉጥ እሾህ ይሆናል!ተተኩሶ የሚገድል ሳይሆን ወግቶ የሚነቀል ቀላል ህመም...እዚያ ሞገደኛ ስሜት ፊት ምንም ነገር ኮስሶብኝ ነበር...ቤተሰብ ኮሰሰብኝ...ሽጉጥ ኮሰሰብኝ...ክብር ኮሰሰብኝ...ዕውቀት ኮሰሰብኝ...ተስፋ ብቻ ነበር የገዘፈብኝ።እንጃዬ ስሜቴን ያውቃል ፣ፍቅራችን የጋራ ይሆናል የምትል የሞኝ ተስፋ!

ከዚያች ምሽት በሁዋላ ታሪኬ መልኩን ቀየረ።ብናስራት ራሷን ታጠፋለች በሚል ስጋት ቤት ውስጥ የሚቆጣኝ ቀርቶ ቀና ብሎ የሚያየኝ ስለሌለ ነፃነቴን እስከጥግ ኖርኳት።ቁርስ ከእንጃዬ ጋር...ምሳም ከሱ ጋር...ራትም እንደዛው...አልፎ አልፎ አዳሬም እዛች የፈራረሰች የላስቲክ ቤት ውስጥ ሆነ።እናቴ ጭንቅ ጥብብ ቢላት
"ህሊናዬ በፈጠረሽ አዳሩ እንኳን ይቅርብሽ...በፍርሀት እሞትብሻለሁ "

"እሜ እንጃዬን ነው የፈራሽው?ይልቅ አባቴንና ወንድሜን ፍሪያቸው"

"እሺ ቢያንስ..."
"ቢያንስ ምን?"አቀርቅራ ዝም አለችኝ።ጭንቀቷ ገባኝ።የዳቦው ነገር አሳስቧት ነበር።

"እሜ የኔ ክብር የሄደው ገና እንጃዬን ሳፈቅር ነው"አልኳት።የኔ አንጀታም!ብርድ ልብስ ሸጥታ ሸኘችኝ!ከዛ ንፁሕ ሰው ጋር ሞቆኝ የሰላም እንቅልፍ ተኛሁ።
የወር ደሜ እንዳልመጣ እያወቅሁ፣ ፀንሼ ሊሆን እንደሚችል እያወቅሁ፣ለሁለተኛ ጊዜ ሽጉጥ ሊደቀንብኝ እንደሚችል እያወቅሁ ዝምታን መረጥኩ ።ሆዴ ገፋ...ራሴው ፈቅጄ በፈፀምኩት ነገር ወንድሜ ፍቅሬን ሊገድልብኝ ሽጉጥ ይዞ ወጣ።እኔስ የዋዛ ነኝ?በረኪናዬን አንጠልጥዬ እየጮህኩ ተከተልኩታ!መንደርተኛው ግልብጥ ብሎ ከቤቱ ወጣ!ሌላ ወሬ ተገኘለት!

"ጉድ በል ሀገር!ህሊና የጋሽ ሰለሞን ልጅ ከእንጃዬ አረገዘች"ተባለ።ቡና እስከ ስምንተኛው እየተጣደ የምቦጨቅበት ርዕስ ተገኘ።በረኪናውን ሲቀሙኝ ዐለሙ ዞረብኝ...እናቴ ወንድሜን መማፀን ጀመረች።
"ዞር በይ እማዬ ፊት ለፊቷ ነው የምደፋላት!"ይላል።እንጃዬ ግራ ገብቶት በዝምታ እያየኝ አለቀሰ።

"ሽሽ...ሽጉጥ"አለ።
ሳለቅስም አባባሁት መሰለኝ።ያልተያዘው አፌ ብቻ ስለነበር የቻልኩትን ያህል ጮሄ ድምፄ ሰለለ።ወንድሜ በምልጃ ብዛት ምላጩን ሳይስብ ወደቤቱ ገባ።ከዚያች እርጉም ቀን በሁዋላ...ያ ሽጉጥ ከተደቀነበት በሁዋላ እንጃዬን በከተማው አየሁት ያለኝ የለም።ግን ተሳስቻለሁ እንዴ?የዛን ንፁህ ሰው ልጅ መግደል ነበረብኝ?
ስህተቴ ማፍቀሬ አልነበረም...ስህተቴ እንጃዬን ማፍቀሬም አልነበረም...ስህተቴ ልጄ አይደለችም...ስህተቴ የተገኘሁበት ቦታ ነበር።ስህተቴ ሰፈሩ ነበር።ለምኩራብ(ለልጄ)ስለአባቷ ሳወራት ገነትን እየጎበኘሁ ይመስለኛል።ስፍፍፍ እላለሁ።

"የዛሬ 6 ዐመት መኖር ጥሞኝ ነበር"እላታለሁ።
በማዕዶት ያየህ


@wegoch
@wegoch
@tizur_12
.....
ለእኔም እኮ አይገባኝም፤ ቆይ በሕይወታችን የምንፈልገው ትልቁ ነገር ፍቅር ነው አይደል? ያውም ጥልቅና ነጋሪ የማያስፈልገው እንዲው በአይን ብቻ የሚገባን? ይህንን የሁሉን መሻት እኮ ነው የኔ ሆኖ ያገኘሁት፤ ታዲያ ለምንድነው ማመሰገኑ የቸገረኝ? ለምን ይሆን ልቤን የጭነት ያህል የሚከብደው? ለምንድነው አሁንም ያልሞላ ክፍተት እንዳለ የሚሰማኝ?

ያኔ....
እሱ ወላጆቹን በሞት አጥቶ በሀዘን የተሰበረበት ጊዜ ነበር፤ በዛ ሁሉ ስቃይ ውስጥ ሆኖ የኔን አብሮነት ሲሻ የራስህ ጉዳይ የምልበት አቅም አልነበረኝም ግን ያውቀዋል አፍቅሬው አልነበረም።
በቆይታ እሱም ሀሳቡን የሚቀይር እኔም ልቤ የፈቀደውን የማደርግ መስሎኝ ነበር። ጊዜያት ባለፉ ቁጥር የሱ ፍቅር ሲጨምር እኔ ለሱ ያለኝ ክብርና የጓደኝነት መውደድ እንዳለ ከመዝለቁ ውጪ ልቤን ለፍቅር ማስረከብ አቃተኝ።

ራሴን እኮ እጠይቀዋለው "ያልወደድሽለትን አንድ ነገር ጥቀሺ" ብባል አፌ ይተሳሰራል እንጂ ይህ ነው የምለው አንዲት ሳንካ እንኳን የለበትም፤ ግን አላፈቀርኩትም።

ምንም ቢጠየቅ በሚገርም ብስለት ነገሮችን ያብራራል፤የእይታው አድማስ፣ የምልከታው ጥግ "ለካ ይህም አለ እንዴ?" እንዳስባለኝ ነው።

ቁጥብ ነው እናም ኮስታራ፣ ስክን ያለ፣ ልክ እንደ ውሀ የሚጋባ አይነት የእርጋታ መንፈስ ያለው፤ የልጅ አዋቂ።
በፊት በፊት ሰዎች የዚህ አይነት የስብዕና ጥልቀት የሚኖራቸው ከህይወት ብዙ ሲቀስሙ ይመስለኝ ነበር፤ እሱ ባለበት የእድሜ ልክ እንዴት ላስበው እችላለው?
በዚህ ለይ ደግሞ አፍቃሪነቱ፣ አይኑ ለይ የማየው መውደድ፣ አይን ያዝ ከሚያደርግ ግርማ ሞገሱ ጋር ልብን የመቆጣጠር ሀይል አለው፤ታዲያ እኔን
ማሸነፍ ለምን ተሳነው?

ብዙ ጊዜ ሁሉን እርግፍ አድርጎ ስለመተው እና ብቻዬን ስለመሆን አስባለው፤ እሱ ያንን እንዳደርግ አይፈቅድልኝም እንጂ።
"ራሴን አጠፋልሽና ትገላገያለሽ" ያለኝን ባሰብኩት ቁጥር ልቤ ይጨነቃል ለነገሩ እንደዛ ባይለኝም እንኳን ያንን ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይል እርግጠኛ ነኝ፤ ለሱ የመኖሩ ምክንያት ነኛ!
አንዳንዴ "ቆይ መውደድ ያልቻልኩት ሁሌም ቅርቤ ስለሆነ በእጅ የያዙት ሆኖብኝ ነው? ሳጣው እንደ እሳት ሊያንገበግብኝ?" ብዬ አስባለው።
ነገር ግን ተጣልተን በቆየንባቸው ጊዜያት ከፋኝ እንጂ ያንን ፍቅር ግን አልታመምኩትም።

አከብረዋለው፣ ለሱ ያለኝ መውደድ ከልብ ነው፤ አንዲት እንቅፋት እንኳን በህይወቱ እንድታጋጥመው አልፈልግም፤ ሳቁ ነው የሚናፍቀኝ፤ የወደደውና የሚያስፈልገው እንዲሆንለት ነው ምኞቴ፤ ይህን ለመሰለ ስብዕናው መቼስ ቢያንስበት እንጂ አይበዛም።

ፍቅር ግን ተሰርቶ አይመጣም አይደል? "ይህንን ሰው መውደድ አለብኝ!" ማለት ነበረብኝ? ብልስ ይሆንልኛል?፤ ነው ወይስ ልክ እንደ ተሰማኝ ማስመሰል አለብኝ? ማንም ሰው እኮ ከራሱ አያመልጥም።
እንዳልወደድኩት ማሰቡ ለራሱ የጥፋተኝነት ስሜት ይፈጥርብኛል ግን እውነታው እሱ ነው ካልሆነ ከራስ ጋር ድብብቆሽ ይሆናል።
ፍቅር ደግሞ ይሰጠናል እንጂ በስራ አናመጣውም፤ በማንቆጣጠረው ልክ ውስጣችንን ሞልቶት እናገኘዋለው ያኔ ከዛ ሰው ጋር መሆን አማራጭ የሌለው ብቸኛው ውሳኔያችን ነው።

ግን ማናችን ነን የተሳሳትነው?
ያ ጥልቅ ስሜት ሳይሰማኝ ለሱ ስል ባላመንኩበት ህይወት ውስጥ እየዳከርኩ የራሴን ስሜት ለማዳፍን የምሞክረው፣ በገዛ ህይወቴ ለይ የመወሰን ስልጣኔን የተነጠኩት፣ ደስተኛ እንደማልሆን እያወኩኝ በተቀመረልኝ አብሮነት ውስጥ ማለፍ ግድ የሆነብኝ እኔ? ወይስ.....
ያለ ልክ የሚያፈቅራት ሴት እሷ ጋር ያ ስሜት እንደሌለ እያወቀ እንኳን መውደዱ ያልቀነሰበት፣ ከሷ ጋር ለመሆን የሷ መኖር እንጂ መልካምነቷ ግድ የማይሰጠው፣ የነገው ህይወቱ ከሷ መኖር ጋር የተሳሰረበት፤ እውነተኛው አፍቃሪው እሱ?
ማናችን ነን ልክ?.....የቱስ ጋር ነው የተሳሳትነው?
.
.
ለዚህ እኮ ነው... ለኔም አይገባኝም የምለው።

@wegoch
@wegoch
@paappii

By mahlet
እንደሚሞት እያወቅሁ አክመዋለሁ(ክፍል 7)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ሰው በደስታ ብዛት የሚያደርገው ጠፍቶት እናንተ እዚያ ደስታ ላይ ሳትፈልጉ የክህደትን ቀዝቃዛ ውሀ እንደምትቸልሱበት ማሰብ ይከብዳል አይደል?በረሀብ ሰውነቱ ከመነመነ ህፃን ላይ ወተት እንደመንጠቅ፣ጉልበታቸው የሚንቀጠቀጥን አዛውንት ገፍትሮ ቦታቸው ላይ ሄዶ እንደመቀመጥ፣ የነፍሰጡርን ጭንቅ እንደማየት ያህል ይጨንቃል።

ስለስዩም ተጨነቅሁ...ስለእናቴ ተጨነቅሁ...ስለዳንኤል ተጨነቅሁ...15 ቀናት ለቀሩት ሰርጌ የኔ ስሜት ከበረዶም የቀዘቀዘ ነበር።ቤተ ዘመዱ እረፍት አጥቶ ይዋከባል...ሙሽራው በሀሴት ይገባበት ጠፍቶታል።ሚዜዎቹ ሽርጉዳቸው ለጉድ ነው።የኔ በሀሳብ መሰነግ "ወግ ነው ሲዳሩ ማልቀስ"በሚባል የአባባል ካባ ተድበስብሶ ጠያቂ አጣ።እናቴ በበኩሏ ጭንቀቴ ቢገባትም ምንም ማድረግ እንደማይቻል አምና የሰርጉን ዝግጅት እያሽሞነሞነችው ነው።

በሰርጉ ዝግጅት ምክንያት ስራ ከገባሁ ዛሬ 10 ኛ ቀኔ በመሆኑ ዳንኤልን ለ 10 ተከታታይ ቀናት አላየሁትም።ስጨነቅ ደሲለዋል መሰለኝ ስልኬን አይመልስም።የጽሁፍ መልዕክቶቼም ምላሽ አያገኙም።እንዳብድ ነው እንዴ የሚፈልገው?

መከረኛው ሰርግ ቀናት ሲቀሩት የሚዜና የጓደኛ ትውውቅ በሚል ሰበብ ሰው እንዲሰባሰብ ተወሰነ።ያው እንደምስል መቀመጥ እንጂ እንደሙሽራ የውበቴ፣የአለባበሴ...የሰርጉ ጭፈራ የመሳሰሉት ነገሮች ላይ በሰፊውና በትኩረት ማውራቱ ባይሳካልኝም እዚህ ላይ ዋናዋ ተዋናይት እኔ እንደመሆኔ መሳተፌ የግድ ነበር።

"ሙሽሪት ኧረ ፊትሽን ፍቺው!ያለላርጎ ዘፈዘፍሽው'ኮ ሃ...ሃ...ሃ...መዳር እንደዚህ የሚያስደብር ከሆነማ I will stay single forever....ሃ....ሃ....ሃ..."ትላለች ከሚዜዎቼ አንዷ የሆነችው ሶልያና።

"ባክሽ ተያት የወጉ ነው...ስንት የሚያሳስባት ነገር ይኖራል ጎጆ ወጪ ነች'ኮ አንቺ ደግሞ" ትቀጥላለች ሌላኛዋ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የተጠራው ሰው ቀስ በቀስ ቤቱን መሙላት ጀመረ።ሁሉም መጥተው አንድ ሰው ብቻ ጎደለ።የወንዱ ሙሽራ ስር ሚዜ...

ሁሉም እርስበራሱ ማን ይሆን እያለ በሹክሹክታ ይነጋገራል ።ስዩም አብሮአደግ ጓደኛውን የመጀመሪያ ሚዜው እንደሚያደርገው ነግሮኛል ።

"ሙሽር ስር ሚዜህ ዘገየሳ ምነው?"የተሰበሰበው ሁሉ በየተራ ስዩምን ይጠይቁታል ።

"ይመጣል ይመጣል!አንድ ጉዳይ ገጥሞኝ ነው ያረፈድኩት ብሎኛል እየመጣ ነው ተጫወቱ"ይላል ፈገግ እያለ።በመሀል ሰረቅ እያረገ ሲያየኝ የተዘፈዘፈ ፊቴ ስቅቅ ያረገኝና ድንጋጤና ሀፍረት የተነባበረበት ፈገግታዬን እለግሰዋለሁ።መጨነቄ ገብቶታል።ግን አልጠየቀኝም።ቢጠይቀኝስ ምን እላለሁ?

'ላንተ የነበረኝን ፍቅር ዳንኤል የሚባል መልዐክ በክንፉ ሰብስቦ ወሰደብኝ' ልለው ነው?ወይስ ደግሞ

'ስዩም ከዚህ ጋብቻ የምታተርፈው ፀፀትን ብቻ ነው ....ልቅርብህ ...ልቤ ውስጥ የነበረህ ቦታ አሁን በሌላ ተይዟል...በሀሳቤ ከወሰለትኩብህ ቆየሁ....ከማገጥኩብህ ሰነባበትኩ...ሰርጉ እንዲራዘም የፈለኩት ለዚህ ውስልትናዬ ዕድሜ ለመጨመር እንጂ የሰርጉ ሽርጉድ ፋታ ነስቶኝ አልነበረም።የምትመጣው ልታስረኝ እንጂ ልታገባኝ አልመስልሽ አለኝ...ጣቴን እንጂ ሌላ የተመኘ ልቤን በወርቅ ቀለበትህ አታስረውም....
ላረኩብህ ነገር ምንም ብትቀጣኝ ሲያንሰኝ ነው...ለማደርስብህ የሞራል ስብራት ጌታ መጥቶ 'ከመሀላችሁ ሀጥያት የለብኝም የሚል ይውገራት' ቢል እንኳን ምድር ላይ ያለው ሰው ሁሉ ከኔ ክህደት አንፃር ፃድቅ ነውና ማንም ይወግረኝ ዘንድ ፈቃዴ ነው' ብለው ኩነኔዬ ይፋቅልኝ ይሆን?እንጃ!

ዘመናይ ማርዬ...
ዘመናይ ማርዬ...
ስም አወጣሁልሽ...
ሁለት ልብ ብዬ...
ወላዋይት ብዬ...

የኛ ሙሽራ ዶክተሪቱ...
ማን ያውጣሽ ከመዓቱ...

የሚል ይመስለኛል ለሰርጉ የተከፈተው ዘፈን!

ይቀጥላል!

በማዕዶት ያየህ

15/04/2014 ዓ.ም.

@wegoch
@wegoch
@paappii
እንደሚሞት እያወቅሁ አክመዋለሁ(ክፍል 8)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።


ቆይ ግን እግዜር አይስትም አይደል?🤔እኔን የፈጠረኝ በ system ችግር አይደለም አይደል?ለምንድነው ደስታ እኔጋ ሲደርስ ራሱን የሚያጠፋው ብዬ ማበድ ቀረኝ።ምን አይነት ከንቱ ነሽ ጊዜ?ይቺም ፈተና ሆና ስታለቃቅሺ ቢያይሽ እዮብ እንዴት ይሆን የሚታዘብሽ?

ስር ሚዜው መጣ ተባለ።የሁሉም ዐይን እሱን ለማየት አሰፈሰፈ ።የኔ ዐይኖች ግን ለምንም ስላልጓጉ ይቅርታ ጠይቄና በራስ ምታቴ አሳብቤ ክፍሌ ገብቼ ልቀረቀር ስል አንድ ድምፅ መለሰኝ።

"ሙሽሪት ወዴት ነው?እንግዳ አትቀበይም እንዴ?"የሚል የመልዐኩ የዳንኤል ድምፅ!ዞር ያልኩበት ፍጥነት ቢለካ ከብርሀን ፍጥነት ሳይወዳደር ይቀራል?ዐይኔ የሚያየውን ለማመን አዳገተው።አፌን ከፍቼ ቀረሁ።ዳንኤል ሙሉ ሱፉን ግጥም አድርጎ ለብሶ ከስዩም ጎን ቆሟል።ሁለቱም በፈገግታ ተሞልተው ያዩኛል ።የኔ ድንጋጤ ግን ልክ አጧል።ጴጥሮስ ራሱ መቼም አልከዳህም ያለውን ጌታ በአንድ ሌሊት ሶሰት ጊዜ አላውቀውም ብሎ ሲሸመጥጥ እንዲህ የደነገጠ አይመስለኝም።ምንድነው እነዚህ ሰዎች ከጀርባዬ የጠነሰሱት?እናቴን ባይኔ ፈለኳት...አየሁዋት...ደንግጣለች።ዐይኗን አይቼ ስለጉዳዩ የምታውቀው አንዳች እንደሌለ ተረዳሁ።

"እንግዲህ ሲጠበቅ የነበረው ስር ሚዜዬ ይኸው!"ሲል ስዩም ቤት ውስጥ ያለው ሁሉ ሞቅ አርጎ አጨበጨበ።ጭንቅላቴ ላይ አንዳች የበረዶ ግግር የወደቀብኝ ይመስል ከቁሜ ወድቄ ሶፋው ላይ ዘጭ አልኩበት።የዚህን ሶፋ ውለታ መቼም ከፍዬ አልጨርሰው!በዚህ ግርግር ውስጥ እጅጉን የተጠቀምኩት በዙሪያዬ ካሉት ሰዎች በላይ እሱ ከአጠገቤ በመሆኑ ነው። መሬት ላይ ብዘረርስ ኖሮ?እንደዛ ከቁሜ ወድቄም የኔን ጥያቄአዊ አስተያየትና ድንጋጤ ምክንያት ከእናቴና ከዳንኤል ውጭ ያወቀ አልነበረም መሰለኝ እንግዳ የሆነ አስተያየትና ጥያቄ አልገጠመኝም።ወይም እኔ አላስተዋልኩም መሰለኝ።የሁሉም ትኩረት ሚዜው ላይ ነበር።ሴቶቹ በውበቱና በግርማሞገሱ እየተደነቁ እርስበርሳቸው ይንሾካሾካሉ።ቀሪዎቹ የወንድ ሚዜዎች በቁመናው ስላስከነዳቸው ነው መሰለኝ በግርምት ተውጠው ያዩታል።

"እንኳን ደስ አለሽ ዶክተር!"አለና እጁን ለሰላምታ ዘረጋልኝ።ከምኔው የተቀመጥኩበት እንደደረሰ አላውቅም።ክው አልኩ።የሰላምታውን አፀፋ ረስቼ ዐይኖቹ ላይ አፈጠጥኩ።ያ አስማታም ዐይኑ ትኩርርርር አርጎ እያየኝ ነው።ያ የሚያርበተብተው አስተያየት...

መታመሙን አሁን ገና ከልቤ አመንኩ።ምን አይነት ድንበር ዘለል ፍቅር ነው ለሚያፈቅሩት ሰው የሰርግ ሽርጉድ ላይ እስከመገኘት የሚያደርሰው?እንዴት እንዳስበው ፈልጎ ነው?ይሄ ምናይነት የዞረ ድምር ነው?እኔ በሱ ቦታ ብሆን ይህንን ማድረግ ቀርቶ አስበዋለሁ?ኧረ ማንም ይህንን አያስብም!ማንም!

"አ...አ...መሰግናለሁ ግ...ግን ምንድነው እየሆነ ያለው አልገባኝም"አልኩት።ሲያየኝ የሚሰማኝ መርበድበድ አሁን በድንጋጤና ግራ በመጋባት ተተክቷል።እሱም ገብቶታል።ያው ዳንኤል አይደል?ፊት ቀርቶ ልብ ማንበብን የተካነ አይደል?

"በሁዋላ አስረዳሻለሁ...አሁን ጊዜው የመደሰት እንጂ የጥያቄ አይደለም።ተደሰቺ ሙሽሪት"አለና በጂፓሱ ከሚደመጠው የሰርግ ዘፈን ጋር አብሮ እያንጎራጎረ ከፊት ለፊቴ ካለው የሶፋ ወንበር ላይ ተቀመጠ።

"አይዞሽ ሙሽሪት ...
አይበልሽ ከፋ አይበልሽ ከፋ...
ሁሉም ያገባል በየወረፋ በየወረፋ..."

ሲል ለኔ የሚሰማኝ

"አይዞሽ ሙሽሪት
አይበልሽ ከፋ አይበልሽ ከፋ
ሁሉም ይሞታል በየወረፋ በየወረፋ..." እንደሚል ሆኖ ነው።

ተደሰቺ ማለት ምን ማለት ነው?ይህ ቃል እኔ የማላውቀው ሌላ ዳንኤልኛ ትርጉም አለው እንዴ?ፍቅር እንደዚህ ነው እንዴ በሞቴ?እንደዚህ አስተሳሰብ አዛብቶ ለእብድ አምስት ጉዳይ ያደርጋል በክርስቶስ?ሲገባኝ ለኔ ፍቅር እግዚአብሔር ነው።ፍቅር ክርስቶስ ነው።ራስን ገድሎ ሌላን ማዳን እንጂ ሰውን በቁም መግደል ከመቼ ወዲህ ፍቅር ሆነ?ከመቼስ ጀምሮ መሲሁን ወከለ?

የምር ይህ ሰው እንደሚለው ይወደኛል?እንጃ!ከወደደኝ ለምን ያሳዝነኛል?ለምን ያቆስለኛል?ይህ እንደሚያም ጠፍቶት ነው?ለሱ የሚሰማኝ የሆነ ውሉን የማላውቀው ሞገደኛ ስሜት እንዳለ ቃል በቃል ሳልናገር መረዳት አቆቶት ነው አጨብጭቦ ሊድረኝ የተሰናዳው?ዕድሜ ዘለዐለሜን ሰው ስመርቅ "ከዳንኤል ዓይነት ሰው ፈጣሪ ይሰውራችሁ!"እንድል ይፈልጋል ልበል?

እናቴ በዐይኗ ምልክት ሰጥታኝ ወደክፍሏ ሄደች።ተከትያት ገባሁ።በጥያቄ ልታጣድፈኝ ተዘጋጅታ ጠበቀችኝ። ከመግባቴ ለሴኮንዶች እንኳን ሳትታገስ

"ሚጡ ምንድነው ነገሩ? ልታብራሪልኝ ትችያለሽ?"

"አልችልም ምክንያቱም ምንም አላውቅም"

"እንዴት አታውቂም? "

"እንደዚህ ነዋ እማዬ ልክ እንደዚህ?"እምባዬ አመለጠኝ።ሳግ ፋታ ነሳኝ።ያልጠበቀችውን ስሆንባት ደነገጠችና

"ቀስ በይ ሚጥሻ ሰው ይሰማሻል!"አለች ድምፁዋን ዝቅ አድርጋ ጠቋሚ ጣቷን ከንፈሯ ላይ አድርጋ!እንደጮህኩ አልታወቀኝም ነበር።

"Who cares!ምናገባኝ ይስሙአ!እማ የነሱ ወሬ ከኔ ስብራት ይበልጣል?ማንም....ማ...ንም ምንም ቢል አሁን ከ...ከደማው በላይ ልቤ መቼም አይደማም ገባሽ?"የባሰ ጮህኩ።

"እሺ በቃ እሺ!ልክ ነሽ አንቺ...እኔኮ የማይሆን ነገር አውርተው የባሰ እንዳታዝኚብኝ ብዬ ነው።እንጂማ ተራ ሀሜት እኔ እናትሽ ግድ እንደማይሰጠኝ ታውቂያለሽ...ነይ እስኪ ጋደም በይና እናውራው"እቅፏን እየጠቆመች እተኛበት ዘንድ ጋበዘችኝ።እቅፏ ፈውሴ ነው።እጇ የሆነ ዓይነት የመድሀኒትነት ይዘት አለው።ስትነካኝ ሰላሜ ሲበዛ ይታወቀኛል ።


እቅፏ ላይ ተጋድሜ መነፍረቅ ጀመርኩ።ከከፋኝ ሳላለቅስ እንደማይወጣልኝ ስለምታውቅ ዝም በይ አላለችኝም።እላዩአ ላይ ጣል ያረገቻትን ፎጣ በጥርሴ ነክሼ ምርርርር ብዬ አለቀስኩ።መነፍረቁ ሲበቃኝ ቀና ብዬ

"እምዬ ተጫወተብኝ ይሄ የተረገመ!"አልኳት።

"ማነው እሱ?"

"ዳንኤል!"አልኩ ጥርሴን በእልህ ነክሼ።

"ምን ብሎ ነው የተጫወተብሽ?"

"እወድሻለሁ ብሎ ዋሸኝ!ሰ...ሰ ...ሰራልኝ!እምዬ ይቅር በይኝ ዋሽቼሻለሁ"እምባዬን ላስቆመው ተሳነኝ።

"ምንድነው የዋሸሺኝ እስኪ ተረጋጊ ሳታለቅሺ ንገሪኝ"አለች እንባዬን እያበሰች።

"ሰ...ሰርጉ ይራዘም ያልኩሽ እ...እውነትም የመዘጋጃ ጊዜ አጥቼ አልነበረም።ምክንያቴ ሌላ ነበር"

"ምክንያትሽ ዳንኤል ነበር አውቃለሁ"ስትለኝ እምባዬ ደረቀ።ወሰን በ
የሌለው ድንጋጤ መዳፉ ውስጥ ከቶ ሲያሸኝ ተሰማኝ።

"ም...ምን?ምንድነው የምታውቂው እማ?ደ...ደግሞስ ሳልነግርሽ እንዴት ልታውቂ ቻልሽ?ማወቅሽንስ ለምን አልነገርሽኝም? ይህንን ሁሉ ጊዜ ለብቻዬ ሁሉንም ስጋፈጥ ዝም ያልሽው ልጄ ምን ያህል ጠንካራ ናት ብለሽ experiment እየሰራሽብኝ ነበር?"በጥያቄ ላይ ሌላ ማለቂያ የሌለው ጥያቄን እየደረብኩ አዋከብኳት።


ይቀጥላል

#ማዕዶት #ያየህ

16/07/2014 ዓ.ም.

@wegoch
@wegoch
@paappii
እንደሚሞት እያወቅሁ አክመዋለሁ(ክፍል 9)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

"ቆይ ራስሽ አልነበርሽ እንዴ የነገርሽኝ?"ስትለኝ እያወራን ያለነው በአንድ ዓይነት ቋንቋ አለመሆኑ ተገለጠልኝ ።

"ምኑን ነው ደግሞ እኔ የነገርኩሽ እምዬ?"

"ለዳንኤል የፍቅር ስሜት ምላሽ ሳይሰጡ መቀመጡ የህክምናው አንድ አካል ነው አላልሽኝም ራስሽ?"

"እእእእ....እ...እሱን ነው እንዴ 'ምትይው?አዎ ነግሬሻለሁ ልክ ነሽ ኧረ እኔ ነኝ ደነዟ"አልኩ ምንተ ሀፍረቴን እየተቅለሰለስኩ።ለዳንኤል ስሜት እንዳለኝ እንዴት አወቀችብኝ ብዬ ስጨነቅ እሷ ለካ ያሰበችው ሌላ ነበር! 'አይ እምዬ! ቀልቤን ገፈፍሽው የስራሽን ይስጥሽ' ስል በልቤ

"ለሱ ስሜት እንዳለሽምአውቃለሁ!"ብላ እጥፉን ቀልቤን ገፈፈችው።ብርግግ ብዬ ተነሳሁና

"ምን አልሽ?ም...ምንድነው ያልሽው?"አልኳት ወገቤን ይዤ።ተውረገረግሁባት ቢባል ይቀላል።አላፍርምኮ ልክድ ነው?

"ምነው ዋሸሁ?" ስትናገር ከልክ በላይ ዘና ብላ ነው። ወዲያው ቀጠል አረገችና

"እናትሽ'ኮ ነኝ!እ?ይህን ዕውነት የመካድ ሀሳቡ አለሽ?" ስትለኝ

"ሁሁሁሁሁፍፍፍፍፍፍፍፍ!የለኝም" በረጅሙ ተንፍሼ አልጋው ላይ ከቁሜ ወደቅሁበት።አፍታም ሳልቆይ ፈትለክ ብዬ ተነሳሁና

"እና እያወቅሽ ነው ይህን ሁሉ 'ምታደርጊው?" በድጋሚ ጮህኩ።

"አዎ" አሁንም ዘና ብላለች።እኔ ግን ባሰብኝ

"እውነት ነበር ለካ!"አልኩኝ።

"ምኑ?"

"አባዬ እናትሽ አንዳንዴ ክፉ ናት ያለኝ...እንዴት ለማላፈቅረው ሰው ልዳር መሆኑ ሰላም ሰጠሽ?"ስል ፊቷ ተለዋወጠ።አትኩራ ለሴኮንዶች አየችኝና ለዘብ ባለ አንደበት እንዲህ አለችኝ...

"እየውልሽ ሚጥሻዬ...አባትሽ ክፋትና ለራስ ማወቅ የሚባሉት ሁለት ሀሳቦች ይምታቱበት ነበር።ለሞት ያበቃው ከልክ ያለፈ ርህራሄውና ሰው አማኝነቱ እንደሆነ ታውቂያለሽ።ስለራስህ አስብ...ላንተ ሳትሆን ለሰዎች መሆን አትችልም ማለቴ ክፉ ያስብለኝ ነበር።የዋህነቱን ስለሚያውቁ ሞልቶ የተረፋቸው ሳይቀሩ ችግረኛ መስለው አበድረን ይሉታል።አበድሮ አይረካም ነበር...የሁዋላ የሁዋላ እሱ ራሱ ነፍሱን አስይዞ በማይሆን ብድር ውሀ ሆኖ ቀረ እንጂ..."እንባዋን ታግላ ማስቀረት ተሳናት።

"...ሰማሽ ሚጡ ለራስሽ እወቂበት!ያንቺን አጥር በጅምር ትተሽ የጎረቤት አጥር ስታጥሪ ጎረቤትሽ ጀሌውን ልኮ በጀርባ ያዘርፍሻል።በሁዋላ አብሮሽ የጠፋሽን ንብረት ሊያፋልግሽ ይመጣል።ከዘረፈሽ ገንዘብ የሩቡን ሩብ 'ለአንዳንድ ነገር ትሁንሽ' ብሎ ሸጎጥ ያደርግልሻል።ብታምኚም ባታምኚም የምትኖሪበት ዐለም Reality ይህ ነው"

አሁን ደግሞ እንባዋ ቆሞ ወደሆነ ወደማላውቃት አይነት አስፈሪ ሴት ተቀየረችብኝ።የምትነግረኝ ነገር ከኔ ህይወት ጋር ምን እንደሚያገናኘው ባላውቅም ልክ መሆኗን አልክድም።ለህይወትሽ የሚበጅሽ ስዩምን ማግባቱ ነው ለማለት ነው ይሄ ሁሉ? ራሷን አረጋግታ ስትቀመጥ ጨከን ባለ አንደበት እንዲህ አለችኝ።

"ዕውነታውን ተጋፈጭው ጊዜ!"

"የምኑን ዕውነታ?"

"የዳንኤልን ሞት መቀበል ከብዶሻል አውቃለሁ።"

"ማን ያውቃል እኔ ቀድሜው እንደማልሞት?እ?"

"እየውልሽ ሚጥሻዬ..."ልትቀጥል ስትል የክፍሉ በር ተንኳኳ።

"ይግቡ"አልኩ በደመነፍስ።ዳንኤል ነበር።እናቴ ሲያለቅሱ የቆዩ ዐይኖቿን እየጠራረገች

"ልጅ ዳንኤል!ና ግባ እስኪ"አለችው።ገብቶ ከጎናችን ተቀመጠ።ዝምታ በመሀከላችን ነገሰ።እናቴ

"እ...እናንተ መነጋገር ሳይኖርባችሁ አይቀርም እኔ ልሂድ!"ብላ ስትነሳ እጇን ይዤ በተማፅኖ አስተያየት

"እማ አትሂጂ አብረሽኝ ሁኚ!"አልኳት።ከዳንኤል ጋር ለብቻችን አንድ ክፍል ውስጥ የመቀመጡን ሀሳብ አልወደድኩትም።እምዬ እንዴት እንዳሰበችው አላውቅም።

"ስጋትሽ ገብቶኛል ግን ሁለታችሁም ላይ ዕምነት አለኝ።በነፃነት አውሩ"ብላ ጥላን ወጣች።እኔኮ ግን እሷ የምታምነኝን ያህል ራሴን አላምነውም።ከመውጣቷ

"አታስቢ ዶክተር! ከበሽታዬም በላይ ስብዕናሽ ወሰኔን እንዳላልፍ ያስገድደኛል"አለኝ።ምን ዐይነት ጦር የሆነ ንግግር ነው?

"እ...እኔ እንደዛ አላልኩም...ለማለት የፈለኩት..."ጠቋሚ ጣቱን ከንፈሬ ላይ አድርጎ በምልክት ዝም እንድል ነገረኝ።ዝም አልኩ።ትኩርርርርርር አርጎ ሊያየኝ ነው ብዬ ስፈራ ጣቱን አነሳና በዝግታ ሳቀብኝ።

"አሃሃሃ...ሃሃሃሃሃ...ሃሃሃ"

"ምን ያስቅሀል?"

"ትፈሪኛለሽ አ?ምኔ ነው ሚያስፈራሽ ቆይ?"

"ኧ...ኧረ እኔ አልፈራህም!ለምን እፈራሀለሁ?"ነጭ ውሸት ዋሸሁ።ሲጠጋኝ እፈራለሁ...የሆነ የማላውቀው ንዝረት መላ ሰውነቴን ይሰማኛል...በአካል ስንራራቅ ደግሞ ንዝረቱ ወደጭንቅላቴ ይወጣል...የምናብ ንዝረት...ከሀሳብ ተነስቶ ሰውነትን የሚያናውጥ ንዝረት።ይሄንን ይመስለኛል "ኤክስፐርቶቹ" የስሜት ፍቅር የሚሉት።የስሜት ፍቅር ሲራራቁ የሚደበዝዝ አካላዊ ቅርርብ ላይ ብቻ የተመሰረተ "ፍቅር-ቅብ" እንጂ ፍቅር አይደለም ሲባል ሰምቻለሁ። ምናውቄ?ኧረ በሆነልኝና ዳንኤል በጊዜ ሂደት የምረሳው የሆነ ጊዜ ላይ በህይወቴ የተከሰተ ጥሩ ነገር ሆኖ ባለፈልኝ!

"እህህህህም!ካልሽ እሺ...ግን ከአንደኛ ሚዜ'ኮ ምንም አይደበቅም...ንገሪኝ?"

"ያምሀል ግን?ንክ ነገር ነህ አይደል? "አልኩ ሌባ ጣቴን ጭንቅላቴ አካባቢ ከጆሮዬ ከፍ አድርጌ ቡለን እንደማላላት እያጠማዘዝኩ።

"እንግዲህ ሐኪሟም አንቺ ነሽ እኔ ምናውቄ!"

"ቀልዱ እዚህ ጋ ቢያበቃና ወደቁምነገሩ ብንገባስ?"አልኩ በመሰላቸት።

"በዛች ቀን ከጎንሽ መሆን እፈልጋለሁ!በሰርግሽ ቀን!ደስታሽን ባልካፈል ይፀፅተኛል" ከምሩ ነው?

"ኧረ ተው የኛ ክርስቶስ!ፍቅርህስ የት ገባ?የመኖሬ ምክንያት ነሽ የተባልኩትስ?ወይስ ስሜቱ ሰርጌ ላይ አንደኛ ሚዜ እስከመሆን አጀግኖሀል??ፍቅርህ የት ሄደ?"እየጮህኩ አፈጠጥኩበት።የሚደነግጥ ዐይነት አይደለም።

"እሱንማ ሸጥኩት"

"ዳንኤል ክፉ ነገር እንዳደርግ አታስገድደኝ እባክህን!"የደም ስሬ ሲግተረተር ይሰማኛል።

"ምን?ልትገይኝ ነው?ትንሽ ነውኮ የቀረኝ ታገሺ ሰበብ እንዳልሆንብሽ"

"እስኪ እየኝ"አልኩ ዐይኑ ላይ አፍጥጬ።ጉንጭና ጉንጩን በሁለት እጆቼ ይዤ አፈጠጥኩበት።

"ንገረኝ"

"ምን ልንገርሽ?"

"ውሸት ነው በለኝ"

"ምኑ?"

"አ...አሁን የሚሰ...ሰማኝ"...እንባዬን ማን መቶ ተው ይበልልኝ!

"ምንድነው የሚሰማሽ?" ትኩርርርርር ብሎ አየኝ።

"ታውቀዋለህ...ሳ...ሳ..ልነግርህ ታውቀዋለህ" እንባዬን በአይበሉባው ጠረገና

"እባክሽን ተይ ጊዜ!"አለኝ እጆቼን ከጉንጮቹ እያስለቀቀ

"ምኑን ልተወው?"

"የሚሰማሽን"

"አንተ ትተኸዋል?"በድጋሚ እንባዬ ወረደ።

"በፍፁም ልተወው አልችልም"

"እንጥፋ"አልኩ ሳላስበው።

"ከዛስ?"ፈገግ አለ።

"ከዛማ በቃ አብረን እንኖራለን!"

"አንቺ ሴት ጅል ስትሆኚም ያምርብሻል ልበል!?"

"መብትህ ነው በል!በነካ አፍህ እንጥፋ ላልኩህም እሺ በል"

ይቀጥላል

ደራሲት:- ማዕዶት ያየህ

@wegoch
@wegoch
@paappii
የአጠባውን ጉዳይ አልተነጋገርንም....የማቆሸሹን ነገርም አልተማከርንም። በውርጩ ቀን ውሃ ውስጥ ዋልኩ...በፀሀይ ቀን ለመልበስ እና ለመሽቀርቀር ግን አልታደልኩም። ምክክሩም ክርክሩም የሚመጣው ያንን ስሞክር ነው። የምረታውም ያኔ ነው።
...........
ፎቶ: አዲስ አበባ/ 2014
@wegoch
@wegoch
@wegoch
@ribkiphoto
..........
እጅ ለእጅ ተያይዘን እንደልጅ
ስናዘግም በቀትር ያልታዘበን ማን ነበር?
ከእነኚህ ትንፋሽ አልባ ግትሮች ውጭ
የእኔና ያንተን መኮራረፍ የዘነጋስ ማን ነበር?

የእኛ ጉልበት ከግትሩም ከህያውም እየላቀ ያጨነቀው ማንን ነበር?
...........
ፎቶ: Dire Dawa/ March/2022
@wegoch
@wegoch
@ribkiphoto
..........
እንደሚሞት እያወቅሁ አክመዋለሁ (ክፍል 10)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ነፍሴም ስጋዬም እሽታውን አሰፍስፈው ሲጠብቁ በዚያ ጦረኛ ዐይኑ ሲያተኩርብኝ ቆይቶ

"አይሆንም ጊዜ"አለኝ።

"ል...ል...ለምን?"ከንፈሮቻችን መነካካት እስኪቀራቸው ቀርቤ አፍጥጬ ጠየቅሁት።

"ትጎጃለሽ"

"ከዚህ በላይ ምንም አይጎዳኝም"

"ሞቴ ከዚህ በላይ እንደማያስለቅስሽ እርግጠኛ ነሽ?"አለኝ እንባዬን በድጋሚ እየጠረገ።

"አስሬ ሞ...ት ሞ...ት አትበልብኝ ካንሰር የያዘህ ይመስል!...የምትሞትበትን ቀን የነገረህ አለ?ንገረኝ አለ?"ቆጣ አልኩ።

"የስጋ ሞትን'ኮ ይዘገያል እንጂ ሁላችንም እንሞተዋለን We don't have to be cancer patients to die.No one is eternal on this stupid planet."

(ለመሞት የግድ የካንሰር ታማሚ መሆን አይጠበቅብንም።እዚህ ደደብ ዐለም ላይ ዘለዓለሚዊ ማንም የለም) ማለቱ ነበር።

"እና ምንድነው 'ምትለኝ ዳኒ?"

"My inside is already dead"

(ውስጤ ከሞተ ቆየ)

"እኔ ያንተን ስጋዊ ሞት ለመቋቋም የሚሆን ፅናት እንዳለኝ ብነግርህ የሞተው ውስጥህ አይነሳም?"

"የኔ ውስጥ ክርስቶስ ነው እንዴ ከሞተ በሁዋላ የሚነሳው?"

"እሺ የገደልኩት እኔ ነኝ እንዴ?"

"ማንን ውስጤን?"

"እ"

"ኧረ ቫይረሱ ነው ኪ...ኪ...ኪ...ኪ...ኪ"
በዚህ ሰዓት ሲስቅ ታድሎ!

"ታድለህ በናትህ!ሳቅህ ሲታዘዝልህ!እስኪ የሆነ ነገር ንገረኝ ምናልባት እስከወዲያኛው ደህና እሆን ይሆናል።"

"ምን ልንገርሽ?"

"እንደምትጠላኝ"

"እንኳን አንቺን ቀርቶ አንቺን ማፍቀሬን ራሱ ለአፍታ ጠልቼው አላውቅም"

"እና ምናባህ ነው አርጊ 'ምትለኝ?"እንባዬን እያዘራሁ ክንዱ ላይ ደካማ ቡጢ አሳረፍኩበት።

"ደስተኛ ሁኚ"

"እንዴት?"

"ልክ እንደዚህ..."ብሎ ጉንጬን በስሱ ሳመኝና ከተቀመጠበት ተነስቶ ሊሄድ ሲል እጁን ይዤ አስቆምኩት።ዘወር ሳይል

"በጣም ቆየሁ ዶክተር !ሰዎች አጉል ጥርጣሬ እንዳይገባቸው"አለኝ በር በሩን እያየ።አውቅበት የለ!ወደኔ ያልዞረው እያለቀሰ ስለሆነ ነው።ተነሳሁና ፊት ለፊቱ ስቆም አንገቱን ደፋ።አገጩን ይዤ ቀና ሳደርገው በምን ቅፅበት እንዳፈሰሰው ግራ የሚያጋባ የእንባ ማዕበል ፊቱን አጥለቅልቆታል።ምናይነት ሰው ነው ይሄ እንባውም ፈገግታውም አሽከር ሆነውት እንዳሻው የሚያዝዛቸው?

"ለማን ነው የምታለቅሰው?"

"ላንቺ"

"እኔ ምን ሆንኩ?"

"የሞተ ሰው ማፍቀርሽ አሳዝኖኝ ነዋ!"

የምለው ሲጠፋኝ እኔም እንባዬን አዘነብኩት።ሳግ ትንፋሼን ከላይ ከላይ እየነጠቀ ያሰቃየኝ ጀመር።ለደቂቃዎች አቅፎኝ አለቀሰ።ደረቱ ላይ ተለጥፌ በትኩስ እንባዬ ሸሚዙን አራስኩት።ለቅሶው ተገስ ሲልልን ተፋጠጥን።እኔም የሱን አስተያዬት ኮረጅኩና አንዳችን ሌላችንን የምንሸመድድ ይመስል ዓይኖቻችንን ለአፍታ ሳናርገበግብ ተያየን።ከእንግዲህ በሁዋላ አትገናኙም እንደተባሉ ሰዎች ነበር የተያየነው።ጮክ ያለ...ጠለቅ ያለ...ከቃላት ምልልስም በላይ ጉልበተኛ አስተያየት አይቶኝ ከክፍሉ ወጣ።

ፊቴን ታጥቤ ከመቀመጤ ስዩም መጣ።

"ደህና ነሽ ጊዜ?ምሽቱን ሙሉ ፊትሽ ጥሩ አልነበረም"

"ኧረ ደህና ነኝ...ትንሽ ራሴን ስላመመኝ ነው አታስብ ስዩሜ"

"ታካሚሽ በጣም ነው የሚያከብርሽ"

"ማን ዳንኤል?"

"አዎ!እሱን ስር ሚዜዬ በማድረጌ ዕድለኛ ነኝ።ከማንም በላይ ምርጫዬ ትክክል መሆኑን ነው ያረጋገጠልኝ"

"የምን ምርጫ"

"የሚስት ምርጨረዬን ነዋ!እንዲያውም በጊዜ ማግባቴ በጀህ እንጂ እጠልፍልህ ነበር እያለ ሲያስቀኝ ነበር ሂ...ሂ...ሂ..."

"ማን?"ክው አልኩ።

"ዳንኤል ነዋ!ምን ሆንሽ ግዝሽ?ስለማን ነው የምናወራው?"

"አ...አይ ዳ...ዳንኤል ባለትዳር መሆኑን አላውቅም ነበር ለዛ ነው"

"እየቀለድሽ ነው?እንደምታውቂ ነግሮኛልኮ" ምንድነው እየተፈጠረ ያለው?

"ም...ምናልባት ለኔ አለመንገሩን ረስቶት ይሆናል።ግን እንዴት ነው ባለትዳር ሊሆን የቻለው?አልኩ ሳላስበው።

"ለምን አይችልም?"ኮስተር ብሎ ጠየቀኝ።

"No...የህክምና ዶክመንቶቹ ላይ Marital Status Single እንደሚል አስታውሼ ነው።"ለካ ስዩም ወደውጪ ከሄደ በሁዋላ ነው የኤች.አይ.ቪ ህሙማንን ማከም የጀመርኩት!

"ምናልባት የማናውቀው ነገር ይኖራል።ስለሱ ልልሽ የምችለው ነገር ግን በጣም smart እንደሆነ ነው።'ትኩረትና ጊዜዋን ሳትሰስት ለሰጠችኝ ሀኪሜ በደስታዋ ቀን ከጎኗ ከመሆን የላቀ ልሰጣት የምችለው ስጦታ የለኝም' አለኝ።ታውቂ የለ አንደኛ ሚዜ ላረገው የነበረው ዘመኑን አንደነበር።ዳንኤል ላናግርህ እፈልጋለሁ ሲለኝ ከዘሜ ጋር አብረን ነበር ያገኘነው።አልክድም መጀመሪያ ሀሳቡ ጎርብጦኝ ነበር።አብሮ አደግ ጎደኛዬን ትቼ አይቼው እንኳን የማላውቀውን ሰው ያውም ስር ሚዜ ማድረግ የማይታሰብ ነበር።በሁዋላ ግን ራሱ ዘሜ ነው ወትውቶ ያስማማኝ።እንደዚህች ዓይነት የሰው መውደድ ያላት ሚስት ስለሰጠኝ ፈጣሪ ይመስገን።"አለና ወደኔ ተጠጋ።ስሜቴን ሸከከኝ የሚለው ቃል አይገልፀውም።በዚህ መሸከክ ላይ ደግሞ የዳንኤል የባለትዳርነት ሀሳብ ተደምሮ አዕምሮዬን እንደቅቤ ቅል ናጠው።

ስዩም ሊስመኝ ሲጠጋኝ ትንፋሹ የሲኦልን ወላፈን ሆነብኝ።ያ የዳቢሎስ የኩነኔ ጥሪ ዳግም አቃጨለብኝ።ብርግግ ብዬ ስነሳ ደነገጠና...

"ምነው?"አለኝ።

"እ...እንትን ነው...እንግዶቹ ሄደው አለቁ እንዴ?"

"ኧረ አሉ...ምነው?"

"ጥያቸው ጠፋሁኮ!ሄጄ ልቀላቀላቸው" ብዬ በነፍስ ድረሽ የተባልኩ ይመስል ክፍሉን በፍጥነት ለቅቄው ወጣሁ።

ወደ ሳሎን ሳመራ እጄ እየተንቀጠቀጠ ነበር።ቆም ብዬ ራሴን አረጋጋሁና እንግዶቼን ተቀላቀልኩ።ሁሉም ወይኑን እየተግነጨ የቡድን ወሬውን እያሟሟቀ ነው።ዙሪያ ገባውን ቃኘሁት።ዓይኔን አንድ ነገር ሳበኝ።ጥግ አካባቢ ያለው ስፋ ላይ ዳንኤል ከትዝታ(የቅርብ ጓደኛዬ ናት)ጋር ተቀምጦ ያወራል።ከልቧ ያስቃታል።አንድ እጇን በእጁ ይዞ በሌላኛው ወይኑን ጨብጦ ፉት እያለ የሆነ ለኔ የማይሰማኝን ነገር ይነግራታል።አሁንም ትስቃለች።ሳቋ ከልቧ መሆኑ ከልቤ አናደደኝ።ምን እያላት ነው እንደዚህ የምትገለፍጠው?😡

ሄድኩና ከአጠገባቸው ተቀመጥኩኝ።

"ሰላም ዶክተር"አለኝ ዘና ብሎ።

"ሰላም ክቡር አርክቴክት"አልኩት ብሽቅ ብዬ።ንዴቴ ግራ የገባት ትዝታም

"ግዝሽ ደህና ነሽ?"አለችኝ።

"ኧረ...ሁሉ ሰላም!እንዲህም ደህና ሆኜ አላውቅም ትዙ"


ይቀጥላል

ደሞ ትንሽ ተረጋጉ አታዋክቡኝ!

ማዕዶት ያየህ(@tizur_12)

21/07/2014 ዓ.ም.

@wegoch
@wegoch
@paappii
እንደሚሞት እያወቅሁ አክመዋለሁ(ክፍል 11)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

አስተያየቴና ቁጣ የቀላቀለ ንግግሬ ግራ ያጋባት ትዝታም

"በሉ ተጫወቱ እኔ ነፋስ ተቀብዬ ልምጣ" ብላ ከመሀላችን ተነስታ ሄደች።አፈጠጥኩበት...አፈጠጠብኝ

"ምን?"አለ ግንባሩን ከስክሶ እጆቹን እያወናጨፈ።

"አንተ ራስህ ምን?"

"እንዴ ምን ሆንኩ?"

"ከዚህ በላይ ምን ትሆን?"

"ከምኑ በላይ"

በግልምጫ ከአፈር ደባልቄው በተቀመጠበት ትቼው ተነሳሁ።ምንም ነገር እንዲያብራራልኝ አልፈለግሁም።ልሰማውም ትዕግስት አጣሁ።በንዴትና በሌላ በማላውቀው ጤነኛ ባልሆነ ስሜት እየተነዳሁ ወደ ውስጠኛው ክፍል ገብቼ ከቆይታ በሁዋላ ከስዩም ጋር እጅ ለእጅ ተያይዤ ስመለስ ዳንኤል በቦታው አልነበረም።ሰው ሁሉ እስኪታዘበኝ ጮክ ብዬ

"ዳኒ የት ሄደ?"አልኩ።ገሚሱ ዙሪያ ገባውን ይቃኛል።ገሚሱ ደግሞ ቀደም ሲል ተቀምጦበት የነበረውን ወንበር እየጠቆመ "አሁን'ኮ እዚህ ጋ ነበር...ምናልባት ስልክ ሊያናግር ወጦ ይሆናል"ይለኛል።በሚያወዛግብ ፍጥነት እየተራመድኩ ወደ በረንዳ ወጣሁ።

የበረንዳውን የመደገፊያ አጥር ተደግፎ ቆሞ ጠርሙስ ሙሉ ውስኪውን እየለጋ ይተክዛል።ጠርሙሱን መንትፌ እያፈጠጥኩበት

"ምን ማድረግህ ነው?"አልኩት።

"ት...ተይ እን...ጂ ዛሬ እ...ንኩዋን ል...ጠጣ ዶ...ክተር....የደ...ስታ ቀን ነ..ውኮ ዛሬ...አይደለም እንዴ?"


"በምን ቅፅበት ነው እንደዚህ የዘበዘብከው ቆይ?"የነጠቅሁትን ጠርሙስ ሳየው ውስኪው ከግማሽም አልፏል።ደነገጥኩ አይገልፀውም።

"እ...እየውልሽ ማነሽ የኛ ምሁር....የኛ ዶክተር"

"እሺ የኛ አርክቴክት "ደግፌ እንዲራመድ ልረዳው ስል አመናጨቀኝ

"ልቀ...ቂኝ ብየሻለሁ ሙሽሪት...ብት...ከበሪ አ...አይሻልሽም?ሰው እ...እንደዚህ ሆነን ቢ...ያየን ም..ኒላል?ኧ?"

አስችለኝ ብዬ ዝም አልኩ።

"ምንድነው ጊዜ ችግር አለ?"ከሁዋላዬ የመጣው የስዩም ድምፅ ነበር።

"ኧ...ትንሽ ጠጥቶ ነው ሳይጣላው አይቀርም"አልኩ በአንድ እጄ ዳንኤልን ደግፌ ጠርሙሱን የያዘውን ሌላኛውን እጄን ከፍ አድርጌ እያሳየሁት።

"My God!ምንድነው addiction አለበት እንዴ?"

"ኧ...የ...ምን add...iction ነው?የኔ ሱ...ስም በሽ...ታም አን...ድ ነገ...ር ብቻ ነው....እ...ሱም ምን መ...ሰለህ"በደመነፍስ አቋርጬው።

"በቃህ ዳንኤል በቃህ!ለመሆኑ መድሀኒትህን እየወሰድክ ነው?"በዚህ የለየለት ስካር ውስጥ ሆኖ ይሄንን መጠየቄ እኔ ራሱ መስከሬን ነው የሚያሳየው።ለነገሩ ፍርሀቴ አስክሮኛል።ባላቋርጠው ምን ሊል ነበር?ያመመኝ የሚስትህ ፍቅር ነው ሊል?በኢየሱስ ስም!

"የም...ን መ...ድሀኒት ነው ም...ትይው አንቺ...ሴትዮ...እ...እኔ በሽተኛ ነኝ እንዴ?"ስዩም ላይ አፈጠጠበት።ስዩም ግር ብሎት

"ኧረ በፍፁም!You r so good"ሲል መለሰ።ምፀት መሆኑ ነው መሰለኝ።


"ስዩሜ በናትህ ቤት አድርሼው ልመለስ እናቱ ይሄኔ ተጨንቀዋል።እንዲህ ሆኖ ብቻውን መድረስ ይከብደዋል።"

ስዩም ነገሮችን በበጎ ጎናቸው የማየት አባዜው ከፍ ያለ ስለሆነ ትንሽ ቅር ቢለውም እስክመለስ ከእንግዶቹ ጋር እንዲቆይ ተነጋግረን ወደ ቤት ገባ።እንደገባ የያዝኩትን ውስኪ ዐይኔን ጨፍኜ በቁሜ ሶስት አራት ጊዜ በጉሮሮዬ አወረድኩት።

"በ...ስመአብ አቺ! እንዴ...ት ነው ምጠጪው?😳"

"ዝም ብለህ ተራመድ!" እየተደነቃቀፍን ወደ መኪናዬ አመራን።ገብተን ከጎኔ ተቀመጠና

"እ...እኔ ነ...ኝ የምነዳው"አለኝ እጄን ይዞ።

"ልቀቀኝ አትጃጃልብኝ"

"አላ...ሳዝንሽም?"

"ለምን ታሳዝነኛለህ?ንገረኝ እስኪ ለምን ልዘንልህ?"

"ሟች ነኝ'ኮ...አንቺ ደግሞ ነፍሰ ገዳይ"

"እንዴት ነው እኔ ነፍሰ ገዳይ የምሆነው?"

"አየሽ አ?በቃ አትወጂኝም...ከኔ መሞት በላይ ያ...ንቺ ነፍሰ ገዳይ መባል ነው የሚጨንቅሽ!ክ...ክፉ ነሽ ክፉ!"እንባው መንታ መንታ እየሆነ መውረድ ጀመረ።

"በፈጠረህ!...ስለሞት አታውራብኝ"

"የፈጠረኝማ ረ...ስቶኛል"

"እሺ በቃ አሁን እንሂድ"ብዬ ሞተሩን ላስነሳው ስል

"በናትሽ...ስ...ስሞትልሽ..."

"ምንድነው?"

"እ...እናቴ እንደዚህ ሆኜ እንዳ...ታየኝ"

"So what?"

"የ...ሆነ ቦታ ጥለ...ሽኝ ጊቢ "

"የት ነው የሆነ ቦታ?

"አ...አላውቅም የሆነ ሆ...ሆቴል ነገር"

"እ...እንዴ ማዘር አ...አትጨነቅም?"

"ደ...ውዬ እነግ...ራታለሁ"

የመኪናዬ ጎማ ወደመራኝ ሄድኩ።ሆቴል ያለበት አካባቢ ስንደርስ ቆምኩና አትኩሬ አየሁት።ፊቱ ብዙ ስሜት ይታይበታል።ተስፋ...ተስፋ ማጣት... ሀዘን...ስቃይ...ጨለማ...ደግሞ እንደገና ብርሀን...ሞት...ወዲያው ደግሞ ትንሳኤ...

"ደርሰናል ዳኒ"

"እ?"አለኝ ብንን ብሎ።በጥቂቱም ቢሆን አሁን ስካሩ ተገስ እያለ ነው።

"ደረስን?"

"አዎ ደርሰናል...እኔ ልቅደምህና Room book ላስደርግ"ብዬ ልወርድ ስል እጄን ያዘኝ ። ጥያቄአዊ አስተያየቴን ሰነዘርኩ

"ይቅርታ"አለኝ አንጀት በሚበላ አስተያየት።

"ምንም አይደል"

"መቼ እንዳትጠይኝ ይህንን ብቻ ነው የምጠይቅሽ"

"እንዴት እጠላሀለሁ?"

"ከኔና ከሱ ማንን ነው የምትወጂው?"

"ማነው እሱ?

"ስዩም ነዋ"

"ሰዐቱ እየሄደ ነው room ልያዝልህ"ትቼው ልወርድ ስል በድጋሚ ያዘኝ።

"መልሺልኝ"

"ስር ሚዜው አይደለህ ለምን ራሱን አትጠይቀውም ምን ያህል እንደምወደው?"

"ካንቺ አፍ መስማት ነው ምፈልገው"

"እየውልህ ዳኒ"

"ወዬ"

"እየመሸ ነው room ልያዝልህና ልሂድ "

"ልክ ነሽ ባልሽ ይጠብቅሻል"

ምን እንደሰማኝ አላውቅም ጉንጩን ሳምኩት።

"ሴቷ ይሁዳ ነሽ አንቺ"

"ማለት?"

"ስመሽ ለስቃይ የምትሸጪ!ደግነቱ ስቃዩ ደስ የሚል መሆኑ ነው...አልገረፍም ...አልቸነከርም...አልሰቀልም....ክፋቱ ደግሞ ያው እኔጋ ምፅዓት እንጂ ትንሳዔ የለም...ሂጂ በቃ room ያዢ"

የአልጋ ከፍዬና የክፍሉን ቁልፍ ይዤ ስመለስ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወስዶታል።

"ዳኒ ተነስና ገብተህ ተኛ room ይዣለሁ" ዝምምም...

"አንተ ሰካራም ተነስ ግባና ነኛ ነው'ኮ እምልህ"አልኩት ትከሻውን እየወዘወዝኩ።ዝምምምም


"ዳኒ ተነስ ትዕግስቴ እያለቀ ነው።"ዝምምምምም...


ይቀጥላል

(የሚቀረው አንድ ክፍል ብቻ ነው)

በማዕዶት ያየህ(@tizur_12)

24/07/2014 ዓ.ም.

@wegoch
@wegoch
@paappii
እኔስ ወደ ቤቴ ነበር የምጓዘው። አብሮኝ ያለውንም አለየሁትም ነበር።
ነገር ግን ሞገሱ ከቦኛል። በፅሞናም እራመዳለው።
የኤማሁስ መንገድም ለፅሞና የተሰጠ ነውና።
ፅሞናም ከእርሱ ብቻ የሚገኝ ነውና ልቤም ፍሰሀ አደረገች። መንፈሴም ተረጋጋልኝ።

........................
Photo: Addis Ababa/April/2022
© Ribka Sisay
@ribkiphoto
@wegoch
@wegoch
.......................
እንደሚሞት እያወቅሁ አክመዋለሁ(ክፍል 11 የመጨረሻ ግማሽ)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ማን አይዞሽ እንዳለኝ እንጃ ዕይታዬ ከስርቆት ወደ ማፍጠጥ ተዘዋወረ።እየተጫወተብኝ ያለው ጨዋታ ቀመሩ ዐይኖቹ ውስጥ የተፃፈልኝ ይመስል ፍጥጥጥጥ አድርጌ ባየውም ቀመሩ አልገባኝም።

ይስቃል...ይዘፍናል...ይዘላል....ይጨፍራል...ይህን ሁሉ ደስታ የምር የሚወደኝ ከሆነ ከየት አመጣው?ከግርግሩ(ከሰርጉ) ማብቂያ በሁዋላ ድንገት ካይኔ ተሰወረብኝ።የት ገባ ብዬ መጠየቅም ፈራሁ።ሙሽራ ነኛ!'ባሌ' ካለ ምን ጎደለኝ?

ከወከባው ፈንጠር ብዬ ደወልኩለት።ድክምምምም...ስልልልል ባለ ድምፅ መለሰልኝ።

"ሀይ ዶክተር"

"ድምፅህ ልክ አይደለም ልበል?"

"በይ...በጣም ደክሞኛል ብታይ"

"እንዴት አይደክምህ እንዲያ እየዘለልክ!?"

"ምነው አጨፋፈሬ ይደብር ነበር እንዴ?"

"ኧረ አንተ ምን በወጣህ የኔ ካህን!ምን ያልተካንክበት ነገር አለ አንተ ቆይ?ማፍቀር ላይ ተክነሀል...ማስመሰል ብትል ሰውን ማትከን የግልህ ነው...አንተኮ ትለያለህ ሸዋዬ ትሙት"

"በእናትሽ ስም ምለሽ ክህነቴን ካፀደቅሽውማ የምር አድናቂዬ ነሽ ማለት ነው ሃ...ሃ...ሃ"

"በል በቃህ ዳንኤል...የያዝከው ጨዋታ ግልፅ አልሆነልኝም...የሚሆንልኝም አይመስለኝም....ከዚህ በሁዋላ በቻልከው አቅም እንዳላይህ ተጠንቀቅ! ቢበቃን ይሻላል!አንተ በኔ ህይወት ውስጥ ስም ስጭው ብባል እንኳን ስህተቴ ብዬ የምጠራህ ሰው ነህ!"መልስ ሳልጠብቅ ንግግራችንን ጆሮው ላይ አቋረጥኩት።

ከመቼውም በላይ አሁን ልክ እንደሆንኩና መስመር እንደያዝኩ ተሰማኝ።ራሴን ታማኝ ባለትዳር ሴት አድርጌ ሾምኩት።የማትበገረዋ ዶክተር...ኮስታራዋን ሀኪም ከተኛችበት የቀሰቀስኳት መሰለኝ።ለጊዜውም ቢሆን ጭንቀት ሽው ያለበት ሰላም ተሰማኝ።ዳንኤልን እንደአንድ አላስፈላጊ እጢ ከሀሳቤ ቆርጬ እንደጣልኩት ተሰማኝ...እሱን ቆርጦ መጣል ያን ያህል ቀላል ባይሆንም!


በማግስቱ ጠዋት የጊቢያችን በር በሀይል ተንኳኳ።ሀይሉ የሰው ሳይሆን የዳይኖሰር ይመስላል።ልብ ብዬ ሳዳምጠው ደግሞ እየጮኸ የሚያወራ ሰው ድምፅም የሰማሁ መሰለኝ።በደመነፍስ እየተነዳሁ ከፈትኩት።ስዩም ግራ በመጋባትና በድንጋጤ ተውጦ ከሁዋላዬ ይከተለኛል።

ልክ በሩን ስከፍተው ዕድሜዋ በእናቴ ዕድሜ የሚሆን ደርባባ ባልቴት ከአንዲት ሕፃን ጋር ከፊት ለፊቴ ቆማለች።የሴቲቱን ፊት ልክ እንዳየሁት የሆነ ዳንኤልን የሚመስል ነገር እንዳላት ለማስተዋል ደቂቃ አልፈጀሁም።እሷም ፋታ አልሰጠችኝም።

"አንች ነሽ የማሙሽ ሀኪም?"ደንግጬ ዝም አልኩ።ጮክ ብላ ደገመችው...

"አንች ነሽ ወይ ነውኮ 'ምልሽ አትናገሪም?"

"ይ...ይቅርታ ማነው ማሙሽ?" ሁኔታዋ እጅግ ያስደነግጣል።

"ዳንኤል! "ስሙ ሲጠራ መብረቅ እንደመታው ሰው ድርቅ ብዬ ቀረሁኝ።ስዩምም የሚካሄደው ነገር አልገባው ቢል አፈጠጠብኝ።በለሆሳስ

"ስዩሜ አንተ ግባ እኔ ላናግራቸው"አልኩት።ክርክርና ንዝንዝ ጠላቱ አይደል?ሳያቅማማ ወደቤት ተመለሰ።
እንደምንም ቀልቤን ሰብስቤ ለሴቲቱ መለስኩላት።

"አ...አዎ"

"የባባ ሀኪም አንቺ ነሽ?ጊዜ ማለት አንቺ ነሽ?"አለቺኝ ህፃኗ።የምለው ጠፋኝ. ...ዳንኤል ልጅ አለው ወይስ ሌላ ዳንኤል የሚባል ታካሚ አለኝ?ኧረ የለኝም።

"ነይ ተከተይኝ"አለችኝ ባልቴቲቱ እጄን ይዛ እየጎተተች።

"ቆይ እንጂ እናቴ ወዴት ነው 'ምከተልሽ?"እጄን በሀይል ከእጇ መንጭቄ አወጣሁት ።መለስ ብላ ወደኔ ቀረበችና

"አንቺ ግን ሰው ነሽ?የምር ሰው ነሽ?ምነው መወደድ እንዲህ ጨካኝ ያረጋል?ወየው ልጄጄጄጄጄጄን!እኔ ልድከምልህ ልጄጄጄጄጄን"ማልቀስ ስትጀምር የቆምኩበት ሁሉ ዞረብኝ።ቀጠለች

"ምናይነት አንጀት ነው ኸረ የወለደሽ?ኧረ እንዴት ያለሽውን ጉድ ነው የጣለብኝ!ልጄን ነጠቅሽን....አንድ ልጄን ገና በደንብ ሳልመርቀው. ....እኔ ልቃጠልልህ ልጄጄጄጄጄን...አሁን ነይ ተከተይኝ አታስጩኺኝ"ያስለቀቅሁዋትን እጄን መልሳ ይዛ ጎተተችኝ።ድጋሚ ለመመንጨቅ የሚሆን ጉልበት አልነበረኝም።አዕምሮዬ 'ዳንኤል ምን ሆነ?'በሚል ሀሳብ ተሞልቶ ሰውነቴን ማዘዝ ተሳነው።ወደቀልቤ የተመለስኩት የመንደሩን የኮብልስቶን መንገድ ጨርሰን በባልቴቲቱ መሪነት ዋናው የአስፋልቱ መንገድ ላይ ደርሰን ታክሲ ውስጥ እንድገባ ስታዘዝ ነው።

ወዴት ነው የምትወስደኝ?

ስለየቱ ዳንኤል ነው የምታወራኝ??

ሕፃኗ ልጅስ ማናት የማናት??

ጥያቄዎቹ ጭንቅላቴን ሊያፈነዱት ደረሱ።በጥያቄ ከመፈንዳት ቁርጥን አውቆ መፈንዳት ብዬ

"ዳንኤል ምን ሆኖ ነው?አሞት ነው?"
መልስ የሰጠኝ የለም።ቢጨንቀኝ ወደ ህፃኗ ዞሬ

"ሚጣዬ ዳንኤል ምንሽ ነው?"ስል ጠየቅሁዋት።

"ልጄ"አለችኝ።ዕድሜዋን ስገምተው ከ5-7 ዐመት ትመስለኛለች።

"የዳንኤል አባት ማነው ስሙ?"የማረጋገጫ ጥያቄዬ ነበር።

"ዳንኤል ደለጀ ምንይሁን"
የኔው ጉድ ነው😳

ባልቴቲቱ በዝምታ እያለቀሱ ነው።የምናወራውንም የሚሰሙ አልመሰለኝም።

"እና ልጅሽ...ማለቴ ዳንኤል ምን ሆኖ ነው?"ስላት ከነዚያ የሚያማምሩ የልጅ አይኖቿ የእንባ ጎርፍ መውረድ ጀመረ።አቀፍኳት...አንጀቴ ተላወሰ።ባልቴቲቱ ገርመም አድርጋ አየቻትና ወዲያው ዘወር ብላ

"ዝም በይ አንች የገፊ ዘር ልጄ ላይ አታሟርችበት"አለች።ልጅቱ ከላይ ከላይ ከሚነጥቃት ሳግ ጋር በሀይለኛው እየታገለች ታክሲው የሆስፒታላችን በር ላይ ሲደርስ ለቅሶዋን አቆመች።ባልተረዳሁት ተውኔት ውስጥ ዋነኛዋ ተዋናይት ሆኛለሁ።ከቤቴ የወጣሁት በሌሊት ልብሴ መሆኑን ራሱ ያስተዋልኩት ሆስፒታሉ ጊቢ ውስጥ ያለው ሰው በሙሉ ዐይኑ እኔ ላይ ሲሆን ነው።ትዕዛዝ እንደሚጠብቅ ሮቦት ተገትሬ መቆሜን ያስተዋለችው ሴቲቱም

"ምን ይገትርሻል ተከተይኝ እንጂ!"ብላ በማንባረቅ ወደ ድንገተኛ ክፍል የሚወስደውን ኮሪደር ተከትላ ፈጠን ፈጠን እያለች ተራመደች።ልክ ባለፈ መደንዘዝ ውስጥ ሆኜ ተከተልኳት።ህፃኗ ሴትዮዋን ተከትላ ከፊት ከፊቴ ቱስ ቱስ እያለች ትራመዳለች።እፍፍፍ ቢሉባት የምትወድቅ ነው የምትመስለው።አረማመዷ ትክክል አይደለም።እንቅልፍ እንደራቃት ግልፅ ነው።

የድንገተኛ ክፍሉ በህክምና ፈላጊዎች ተጨናንቋል።ከዚያ ሁሉ ሰው መሀል ዳንኤልን አንዱ አልጋ ላይ ተጋድሞ ሳየው በቁሜ ልወድቅ ምንም አልቀረኝም።ተዝለፍልፌ ልዘረጋ ስል አንዷ ነርስ አፈፍ አድርጋ ያዘችኝና

"ምነው ዶክተር ሰላም አይደለሽም እንዴ?"አለችኝ።

"ሲ...ሲስተር ይሄ 'ፔሸንት' ም...ምን ሆኖ ነው?"ወደዳንኤል ጠቆምኳት።አየት አረገችውና

"በጣም ያሳዝናል ዶክተር!ለ 20 ቀን የሚሆነውን መድሀኒት ነው ባንዴ የዋጠው...ተስፋ ያለው አይመስለኝም"ብላ በቆምኩበት ጥላኝ ወጣች።እየተጎተትኩ ወደ አልጋው ሳዘግም የሆነ ነገር እግሬን ወደሁዋላ ይስበዋል።ትናንት ማታ በስልክ የተናገርኳቸው ቃላት...

ያቺ ብላቴና የተኛበት አልጋ ጠርዝ ላይ ያለውን የዳንኤልን እጅ ጠቅጥቃ ይዛ እንባዋን ለጉድ ታዘንበዋለች።እንደልማዱ አይኖቹን ሳያርገበግብ ቡዝዝዝዝዝዝ ብሎ አያትና ወደኔ ዞረ።ደነገጥኩ።ዐይኑ ይበላኝ ይመስል ውስጤ ' ወጠሽ ሩጪ አምልጪ' የሚለኝ ነገር መጣ።

የተከለብኝን ዐይኑን አንስቶ ወደእናቱ ዘወር አለና የሆነ ምልክት ሲሰጣት ህፃኗን ይዛ ከክፍሉ ወጣች።በድጋሚ አየኝ።ወደኔ ቅረቢ የሚል ዐይነት አተያይ...ስፈራ ስቸር ቀረብኩትና የአልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጥኩ።እያማጠ 4 ቃላትን ወረወረልኝ።

"አ...ንቺ ም...ንም ስህተት አልሰራሽም"

ከዚህ በላይ ልሰማው አቅም አጣሁ እየሮጥኩ ከክፍሉ ወጣሁና በረንዳው ላይ ቆምኩ።
እንደሚሞት እያወቅሁ አክመዋለሁ(የመጨረሻ ክፍል)
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

እናቱና ህፃኗ እየተንደረደሩ ገቡ።እኔ የራሴ ትንፋሽ አፍኖኝ... እየተነፈስኩ ያለሁት አየር ጭስ ጭስ እያለኝ ቀዝቃዛው ሴራሚክ ላይ ተንበርክኬ ማንባት ጀመርኩ።በእንባዬ መሀል ከኔ ለቅሶ ጎልቶ የሚሰማ ስቅጥጥጥጥጥጥ የሚያደርግ ጩኸት ሙሉ ቅጥር ጊቢውን ናጠው።

"ኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡኡይ! ወይኔ ልጄጄጄጄጄጄጄጄን!"

ከዚህ ድምፅ በሁዋላ የዚያንን ሆስፒታል ጊቢ አልረገጥኩትም። 9 ወራት ተቆጠሩ።ከጅምሩ የነካከተው ትዳሬ በሙት ፍቅር ፍፃሜው ተፈረመ።ስዩምን በዚህ ውጥንቅጥ ውስጥ ብቸኛው ተበዳይ ማድረጌን ሳስበው ራሴን እጠላዋለሁ።ፍቺውን ሲፈርምልኝ እንኳን ግንባሬን ስሞ "ይቅናሽ"ነበር ያለኝ ።


ሰው ምን ቢያዝን...ምን ቢሰበር ጊዜ ሲነጉድ የሀዘን ቀለሙ ይደበዝዝ የለ?ግልፅኮ ነው! እናትም ልጇን ቀብራ መኖር ከተባለ ትኖራለች።እኔ ዳንኤልን ቀበርኩ ብዬ እንደሱ ራሴን ባጠፋ ሰው አይስቅም?

ከዘጠኝ ወራት እዬዬ በሁዋላ የዳንኤል እናት ዘንድ ጥያቄዎቼን አንግቼ ሄድኩ።በሩን ከፍታልኝ ከፊት ለፊቷ ቆሜ ስታየኝ ቁስሏን ስለነካሁባት ወዲያው ጠርቅማብኝ ገባች።ደግሜ አንኳኳሁ።መልስ የለም።ትንሽ ቆይቼ በድጋሚ አንኳኳሁ።ብላቴናዋ ነበረች የከፈተችልኝ።ጎንበስ ብዬ ልስማት ስል

"አባቴን ገደልሽብኝ"አለችኝ ።እንደጨው አምድ ተተክዬ ቀረሁ።

"ማ...ማን እኔ?"

በቆምኩበት በሩን ሳትዘጋ ጥላኝ ገባች።ተከትያት ገባሁ።ባልቴቲቱ በተማፅኖ

"እንደው በወለዱሽ ልለምንሽ እባክሽ አትምጪብኝ...ስጋውንስ በቁሙ ጨረስሽው ባይሆን ነፍሱ ትረፍ ስለፈጠረሽ"አለችኝ ግድግዳ ላይ የተሰቀለውን የዳንኤልን የምርቃት ፎቶ እያየች።የሳሎኑ በር ላይ ቆሜ ፎቶውን አየሁት።ነፍስ ያለው ፈገግታው ውልብ አለብኝ።


"ቆይ እኔ አላሳዝናችሁም እንዴ?እኔን ማን ሰምቶኛል?የኔን ስቃይ ታውቂዋለሽ አንቺ እትዬ?"እንባዬ ቀደመኝ።ማልቀሴን ስታይ ደንገጥ አለች።ማንንም ሳላስፈቅድ ገብቼ ሶፋው ላይ ተቀመጥኩ።ለቅሶ አላቆም ያለ ዐይኗን በነጠላዋ ጫፍ እየጠረገች ከፊት ለፊቴ ተቀመጠች።

"ልጅስ ኤድስ አለበት አሉኝ።የልጄ ኤድስ እሷ ናት አልኳቸው።የልጄ በሽታ አንቺው ነሽ"አለችኝ ፈርጠም ብላ።

"እኔኮ ባለትዳር ነበርኩ ምንም ማድረግ አልችልም ነበር።"

"ትችይ ነበር"

"ምን ማድረግ እችል ነበር?"

"ቢያንስ እስኪሞት አብረሽው መሆን ትችይ ነበር"

"ትዳሬስ?"

"ከትዳርና ከነፍስ?ይህች አንዲት ፍሬ ልጅ አባቷን ብታጣ ይቀላል ወይስ ያንቺ ትዳር ቢፈርስ ይቀላል?"ልጅቷን እያየሁ ዝም አልኩ።ቆየት አልኩና እረፍት የነሳኝን ጥያቄ ሰነዘርኩ።

"ለመሆኑ እናቷ የት ናት?"ልጅቷን እያየሁ ጠየቅሁ።

"እሷ በደህናው ጊዜ አባቷ ጋር ሄዳለች"

"አብረው ነበር የሚኖሩት?ማለቴ ከዳንኤል ጋር?"ጥያቄዬ መልሶ አሳፈረኝ።

"ስትወልድ ነው የሞተችው።'ኢንበርስቲ' እያሉ ነው ያረገዘችው ልጅቱ ገና 6 ዐመትም አልሞላትም።"አንድ ነገር አሰብኩ።ዳንኤል ለቫይረሱ የተጋለጠው ከልጁ እናት ጋር በነበረው ግንኙነት ሊሆን እንደሚችል።ስፈራ ስችር

"እ...እኔምለው እናቴ...ዳኒ እንዴት በሽታው እንደያዘው ነግሮሻል?"እንባቸውን እያዘሩ

"ከዚህቸው ከልጁ እናት ነው።ደግነቱ ልጅቱ ነፃ ናት።በእርግዝና ጊዜ አስመርምራት ነው አሉ።ወልዳ ጥላለት ነው የሄደችው መልኳንም አላውቃት።እህህህህ...ልጄን!አዬ ሽታዬን!ወዜን ሰረቀችብኝ...እሱም እንዲችው ልጁን እናቴ እያለ ሲንሰፈሰፍላት ኖሮ ተቀጨብኝ!እኔ ልቀጭልህ የኔ ለፊ!"ይህን እንባ እንደጉድ ያወርዱታል።

ከዚህ በላይ መጠየቅም መስማትም አልቻልሁም ።እያለቀስኩ ወደቤቴ ተመለስኩ።ዳንኤልን ሳስብ ሁሌ ወደ ህሊያዬ የሚመጣው ለመጨረሻ ጊዜ በስልክ ስናወራ የተናገርኳቸው ቃላት ናቸው።ምናለ "ስህተቴ ነህ"ሳይሆን "ከክርስቶስ በታች የህይወት መምህሬ ነህ"ብየው ቢሆን!ምናልባትም ቀብሬው አልፀፀትም ነበር።

ተፈፀመ!

ማዕዶት ያየህ

27/08/2014 ዓ.ም.

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት

(ሜሪ ፈለቀ)

«ሞቼ ቢሆን ኖሮ ደስ ይልሽ ነበር አይደል?» አለኝ በወጉ ማሽከርከር ያልለመደውን ዊልቸር እየገፋ ወደሳሎን ብቅ እንዳለ። ፊቱ ምሬት ወይ ጥላቻ በቅጡ ያልለየሁት ስሜት ይተራመስበታል። ዝም ያልኩት መመላለሱ ልቤን ስለሚያደክመኝ ነበር። በጎማው እየተንቀራፈፈ አጠገቤ ደርሶ « ንገሪኛ ደስ ይልሽ ነበር አይደል?»
«አይከፋኝም ነበር።» መለስኩለት። እግዚአብሔር ይሁን ሰይጣን አደጋውን ያደረሱበት አንዳቸው ምርጫ ሰጥተውኝ ቢሆን ኖሮ እንኳን የቱን እንደምመርጥ እንጃ! (ሰዎች በህይወታቸው የሆነ የከፋ ነገር ሲገጥማቸው <እግዜር ሊያስተምረው ነው!> ይሉን የለ? ያው ራሳቸው ሰዎች ደግሞ የክፉ ነገር ምንጭ ሰይጣን ነውም ይሉናል። ነገሩ ለእኔ ጭንቅላት የተሳከረ ነገር ስላለው ነው ከሁለቱ አንዳቸው ቢሆኑ ያልኩት!! አስቡት የመልካም ነገር ሁሉ ምንጭ የሆነው አምላክ ፣ ለሰው ልጅ በምርጫው እንዲኖር ነፃነትን የሰጠው የነፃነት አምላክ ሊያስተምር ሲፈልግ በክፉ ሲቀጣ? አንዳንዴ ፈጣሪ በክፉ አይፈትንም ብዬ ሳስብ ለራሴ የምሰጠው ማመሳከሪያ የመፅሃፍ ቅዱሱ እዮብ ነው። ፈጣሪ ጥበቃውን እንደእዮብ ያነሳብህና ለክፉ አባት አሳልፎ ይሰጥሃል እንጂ ራሱ አምላክ ክፉውን አያዘንብም! ከዛ ግን ሞትና የሲኦል መኖር ይሄን እሳቤዬን ከአፈር ያደባይብኛል። ብቻ ማናቸውም ይሁኑ የዛን ቀን እየነዳ የነበረውን ጣዖቱ የነበረ መኪና ከገደል ፈጥፍጠውልኛል። እግዜር ይስጣቸው!!_)
«እግዜሩ እንድትበቀዪኝ እድሉን እየሰጠሽ ይሆናልኮ! ለምን ደግ እየሆንሽ የተሰጠሽን እድል ታባክኛለሽ?» አለ የሰራሁለትን ምግብ ላጎርሰው እጄን ስዘረጋ! ከፍቅሬ ጥልቀት አይደለም የማጎርሰው። በአደጋው ምክንያት እጁ እንደፈለገው ስለማይታዘዝለት እንጂ።
«ከዛስ? በእኔ ክፉት ክፉትህን ልታቀል? በእኔ ሀጢያት በደልህን ልትሰርዝ? በእኔ በቀል ሀጢያትህን ልታወራርድ? በፍፁም ያን ደስታማ አልሰጥህም!!»
በቀል ዓይን ላጠፋ ዓይን ማጥፋት ፣ የገደለን መግደል …………… ባጠቃላይ በቀል ለክፋት ክፋትን መመለስ ነው ያለ ማን ነው? ለሰራው ስራ የስራውን መኸርማ መሰብሰብ የተፈጥሮ ህግም አይደል? ያጭዳል!! ምኗ እንከፍ ብሆን ነው <ወይ በገደልከኝ ወይ በገደልከው> ብዬ ስማፀን የከረምኩበትን ሰው እንዳይሞት እንዳይድን አድርጎ እጄ ላይ ሲያስቀምጠው በክፋት የምበቀለው?
ገብቶታል። ጤነኛ ሆኖ ሰራተኛ ያበሰለውን ምግብ የምንበላ ሰዎች ራሴ የሚበላውን ጓዳ ገብቼ ሳበስልለት በደሉን እንደማላቀልለት ገብቶታል። እልህ የሚይዘው ከእኔ ይሁን ከራሱ እንጃ ርሃብ አንጀቱን ካልፋቀው በቀር እሺ ብሎ አይበላም። አይጠይቅምም!! ከሆስፒታል እቤት የገባ ሰሞን <ነርስ ይቀጠርልኝ> ሲል <እኔ ሚስትህ እያለሁ እንዴት ገበናህን ባዳ ያያል?> ብዬው አልጋው ላይ ሲፀዳዳ እሱንም አልጋውንም ሳፀዳ በቀላሉ ይቅር እንደማልለው ገብቶታል። ከሀዘኔታ ልብ ወይም ከፍቅር ፅዋ ከፈለቀ ደግነት እንደማልንከባከበው ያውቃል። ግን ደግሞ በደሉን በበደሌ አላለቀልቅለትም። እሱም ያ ገብቶታል።
ሞቶ ቢሆንና እንደወጉ ነጠላዬን አዘቅዝቄ ከሬሳው ጋር ወደ ቀብር እየሄድኩ ምንድን ነበር የምለው? ሰው ምን ይለኛል ብዬ ደረቴን እደቃ ነበር? ወይስ <ተመስገን ገላገልከኝ> እያልኩ በፈገግታ ከአፈሩ ጋር የሰባት ዓመት ትዳራችንን ወደ ጉድጓዱ መልሼ እመለስ ነበር? የቱ የበለጠ ደስ ይላል? ሞቱ? ወይስ ስንክልክሉ የወጣ አካላቱን እና ከተሰበሩት አጥንቶቹ እኩል እንክትክት ያለ ትህምክቱን፣ ትእቢቱን፣ ሞራሉን ፣ አምላክ ነኝ ባይ ልቡን ………. ታቅፎ ……….. እንኳን እኔ ላይ ራሱ ላይ እንኳን የማዘዝ አቅም የሌለው ከንቱ ሆኖ ማየቱ? የቱ የበለጠ ደስ ይላል? ወይስ ከነጭራሹ ደስታ አለው? ካለመዋሸት አለው! የሆነ ደስ የሚል ስሜት አለው። አንዳንዴ በ7 ዓመት የዲያቢሎስ ሚስትነት ዘመኔ በደነደነ ክፉ ልቤ ውስጥ የተረፈው ሚጢጥዬ የርህራሄ ጭላንጭል ተስፋ ብቅ ይልና ደስታዬን ይበርዝብኛል።
ደስታዬን መደበቅ ግን አልችልም። በጠዋት ተነስቼ እንዲፀዳዳ እያገዝኩት ፈገግታዬ ያመልጠኛል። ጥርሱን እየቦረሽኩለት፣ ፀጉሩን እያበጠርኩለት፣ ልብሱን እየቀየርኩለት፣ የሚንቀጠቀጡ እጆቹ አስተካክለው ስልኩን መያዝ ስለማይችሉ ስልኩ ሲጠራ ሲንፈራገጥ ሳየው አንስቼ እያቀበልኩት ሁላ ከንፈሬን እንደተከደነ ማስቀረት ያቅተኛል። የሚወደውን ምግብ በዜማ እያፏጨሁ አበስልለታለሁ፤ሲዝረከረክ በሶፍት እያፀዳሁ አጎርሰዋለሁ፤ በጤነኛ ዘመኑ ሰራተኛዋ የማታጓድለውን የምሳ ሰዓት ቡና ከነጭሱ እሱ እንደሚወደው ራሴ አፈላለታለሁ፤ ፈገግታዬ በየቀኑ ከማፈነዳው ፈንድሻ ጋር ይፈካል። የየቀን ምኞቱ እዛው አልጋው ላይ እንድረሳው ወይ ትቼው እንድሄድ ወይም በእንክብካቤ ፈንታ ባንገላታው እንደሆነ አውቃለሁ።
በጤነኛ ዘመኑ ከሚያገኘው እንክብካቤ አንዳች አላጎልበትም እንደውም እንደ ሰሞንኛ ሙሽራ አቀበጥኩት እንጂ! አሁንም ፈጣሪ ይሁን ሰይጣን ሲቀጡት አጓጉል አድርገውት እንጂ በጤነኛ ዘመኑ በየቀኑ ማታ አጅበውት የሚመጡትን ለዛዛ ሴቶች ሁላ አመጣለት ነበር። የሚታገዝ ቢሆን እኔ መኝታ ቤት የሚሰማኝን ሴቶቹን የሚያስጮሃቸውን ልፋቱን እያገዝኩት አስከውነው ነበር። አለመታደሉ እንኳን ለጉድጉድ ለመሽናቱም በድጋፍ ሆነበት።
«እሺ ምን ብሰጥሽ ትተይኛለሽ? ከውላችን በተጨማሪ ባንክ ያለኝን ገንዘብ ልስጥሽ ተይኝ!» አለኝ ምግቡን አብልቼው እንደጨረስኩ።
ውላችን ያለው ስንጋባ ያስፈረመኝን ነው። ከኔ በፊት እንዳገባቸው ሁለት ሚስቶቹ እኔንም 8 ዓመት አብሬው ከኖርኩ የንብረቱ ተካፋይ እንደምሆን ፣ ከዛ ቀድሜ መለያየት ካማረኝ ቤሳቤስቲን እንደማላገኝ አስፈርሞኛል። እንደቀደሙት ሚስቶቹ ጨርቄን ማቄን ሳልል በአንዱ ቀን ብን እንደምል እርግጠኛ ነበር።
«ወይ አለመታደልህ! እንዲህ ተይዘህም ገንዘብህ ሁሉን ነገር የመግዛት አቅም እንዳለው ነው የምታስበው?»
«እሺ ምንድነው የምትፈልጊው?»
«ለጊዜው ምንም! ፍቅሬን መንከባከብ!» አልኩት ፈገግ ብዬ ጉንጩን እየዳበስኩት። ጥሎኝ ሊሄድ ተውተረተረ። የሚንቀጠቀጡ እጆቹ አስተካክለው የዊልቸሩን መንቀሳቀሻ ስላልተጫኑለት ስልኩ ሲጮህ እንደሚወራጨው ተወራጨ። ፈገግታዬን መደበቅ እያቃተኝ ረዳሁት!!
ዛሬ ላይ እንዴት ተገኘሁ? ይህችኛዋን እኔ አድርጎ እሱ በሰይጣናዊ እጁ አቡክቶ ሳያበለሻሸኝ በፊት እግዚአብሔር የሰራት እኔ ምን አይነት ነበርኩ?

አልጨረስንም …

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት
(ክፍል 2…………… meri feleke)

ከእኔ በፊት ሁለት ሚስት አግብቶ እንደነበር ሳላውቅ አይደለም ያገባሁት። አውቅ ነበር። ለሁለቱም ሚስቶቹ ልክ ከእኔ ጋር እንዳደረገው የሀብት ውርስ ኮንትራት አስፈርሟቸው እንደነበርም አልደበቀኝም ነበር። በፍቅሩ ነሁልዬ ከእኔ በፊት የነበረው ህይወቱ ገሀነም እሳት ጭስ ሳይሸተኝ ቀርቶም አይደለም። ወይም ፍቅሬ አቅሉን አስቶት በአበባና በስጦታ አንቆጥቁጦኝ ሚዛናዊነቴን አስቶኝም በፍፁም አይደለም። ገና ሳልገባበትም ትዳሬ ሲኦል ሊሆን እንደሚችል የሚንቀለቀል ፍም እሳት ነበልባሉ ሽው ብሎኛል። ገና ሳንጋባ

«ሴት ይሰለቸኛል። ለዛ ነው ትዳር በተወሰነ አመት ኮንትራት መሆን አለበት ብዬ የማምነው።»

«ኮንትራት ያበጀኸውኮ ለትዳሩ ሳይሆን ለውርስ ነው ታዲያ!»

«ያው ናቸው። ለሴት ልጅ ትዳር እና ገንዘብ ያው ናቸው። ቤተሰቦቿ ገና ሽማግሌ ስትልኪ የሚጠይቁት ምንድነው? ልጃችንን በምን ያስተዳድራታል? እሷስ ገና ስታውቅሽ የምትጠይቅሽ ምንድነው? ስራህ ምንድነው? ከስንት አንድ ሴት ናት ማነህ? ምን ትወዳለህ? ምን ትጠላለህ? ምን ትፈራለህ? ብላ የምትጠይቅሽ? ቤተሰቦቿ እሷን በምን እንደምታስተዳድሪ ይሰልሉሻል። እሷ ደግሞ ልጇን በምን እንደምታስተዳድሪላት ትሰልልሻለች። ይኸው ነው።»

ወላፈን አንድ ያዙልኝ!

«መመለስ የማትፈልገው ጥያቄ ከሆነ ይቅርታ አድርግልኝና በምን ተጣላችሁ ከበፊት ሚስቶችህ ጋር?»

«ኸረ ደስ ብሎኝ መልስልሻለሁ። የመጀመሪያዋ ልጅ ካልወለድን ብላ ስትነዘንዘኝ ……» ሳይጨርሰው ከአፉ ቀምቼ

«ልጅ አትፈልግም?»

«በፍፁም!»

«እስከመቼውም እስከመቼውም?»

«እስከመቼውም! እዚህ ብስብስ ዓለም ላይ ያለፈቃዱ ለምን አመጣዋለሁ? ለምን ሰው የመሆን አበሳን ያለፈቃዱ አስጨልጠዋለሁ? እስቲ አንድ ሰው randomly ጠይቂ! ሰው ሆነህ አሁን እየኖርክ ያለኸውን ህይወት ከመኖርና ባለቤቷ ጭኗ ላይ አስቀምጣ እያሻሸቻት የምታስተኛት ነገ እና ትላንት ህይወቷን የማያመሳቅሉባት ድመት ሆኖ ከመፈጠር ምርጫ ቢኖርህ የቱን ትመርጥ ነበር በይው!»

ወላፈን ሁለት ያዙልኝ!!

«ሁሉም ሰው አንድ ዓይነት የህይወት ፈተና እንደማይገጥመው ሁላ ድመትም ሆኖ ባለቤቷ በማማሰያና በፍልጥ የምታራውጣት ድመት መሆን አለኮ!»

«ማን እድሉን ሰጥቶን መረጥን? እናትና አባቶቻችን ወደዝህች ዓለም መከራ ከሚማግዱት ነፍስ ይልቅ ቅንዝራቸው በልጦባቸው ሲላፉ ያረግዙናል። ደህና ስጦታ የሰጡን ይመስል እልልልል ብለው ውልደት ግርዘት ክርስትና ልደት እያሉ ያከብሩልናል። በይፋ welcome to hell !» እጁን በሰፊው ወደፊቱ እያወናጨፈ ዘርግቶ

«ህይወትን እና ተፈጥሮን እንዲህ እንድትጠላ ያደረገህ ምንድነው?»

«ያለውን እውነታ እንጂ ስለግሌ አይደለም ያወራሁት! እና ደግሞ ብዙ personal የሆነ ጥያቄ የምትጠይቀኝ ሴት አትመቸኝም።»

እዚህኛው ላይ ለህይወት ካለው ጨለምተኛ እና መራራ ምልከታ በላይ የጭንቅላቱ ጤንነት ሊያሳስበኝ አይገባም ነበር? መቼም ቢሆን አልፌ እንድረዳው የማይፈቅድልኝ ጥቁር አለት በልቡ ደብቆ እንደሚኖር ሳላገባውም እዚህ ቀን ላይ አውቃለሁ።

ወላፈን ሶስት ቁጠሩ !!

«ፍቅር የሚባል ነገር የለም! ሰዎች ለምግባራቸው የተቀደሰ ስም ሰጥተው ራሳቸውን ሲነሸግሉ ግንኙነታቸውን የሚያሞካሹበት መጠሪያ ነው። በዚህ ዓለም ላይ ያሉ ግንኙነቶች ወይ ሀላፊነነት ናቸው ወይ መጠቃቀም ናቸው። ሀላፊነቴን እየተወጣሁ ነው ላለማለት ወይም ስለሚጠቅመኝ ነው አብሬው ያለሁት ከማለት <ፍቅር> ብለን እንቀባባዋለን።»

«በምንም ጥቅም ላይ ያልተመሰረተ ወይም በሃላፊነት ግዳጅ ያልታጠረ ግንኑነት አኮ!»

«ምሳሌ ጥቀሺ!»

«ለምሳሌ ጓደኝነት! የቤተሰብ ትስስር፣ እንዴ ሁሉም የተቃራኒ ፆታ ፍቅርም በጥቅም ላይ የተመሰረተ አይደለም። የአምላክ ፍቅርስ?»

«አምላክን ተይው! …… (ቡም! 💣🔥🔥🔥ይሄ ወላፈን ብቻ አልነበረም! ፍንዳታ ነበር! ፍንጥርጣሪው ለዓመታት የሚባጅ መርዝ የነበረው ፍንዳታ!) ፈጣሪን እንኳን ተይው! ጓደኝነት በስሜት መጠቃቀም ላይ ነው መሰረቱ! ጓደኛዬ የምትዪው ሰው ወይ ስሜትሽን የሚረዳ፣ በሃሳብ የምትግባቢው፣ ጥሩ ልብ ያለው፣ ወይም ግማሽ አንቺን ውስጡ ያገኘሽበት name it እንደጓደኛ የሚያቆራኝሽን ነገር? ያን ኳሊቲ ውስጡ ባታገኚ ጓደኛሽ ይሆን ነበር? አንድ በስሜት የምትመጋገቢው ነገር እየፈለግሽ ባትቆራኚ ኖሮ ዓለም በሙሉ ጓደኛሽ ይሆን ነበር። አየሽ የስሜት መጠቃቀም ነው። ቤተሰብ ላልሽው ……. ዌል እናትና አባት ግዴታም ሀላፊነትም ነው። የእናት ፍቅር ብለው እንደተኣምር ይሞዝቁለታል። ግዴታዋን ነው የተወጣችውኮ። እንደውም በጣም abuse ሲያደርጉሽ የራሳቸው ንብረት እንጂ የራስሽ ሀሳብና ፍላጎት ያለሽ ሙሉ ሰው አትመስያቸውም! አድገሽ ራስሽን ችለሽ ሁላ ወይ እነሱን የመደጎም እና የማኖር ግዴታ ያለብሽ ፣ ሳትፈልጊ ወልደው ስላሳደጉሽ ውለታ የዋሉልሽ እና ያን ውለታ የመመለስ ግዴታ ያለብሽ ያስመስሉታል። (ይሄን ሲያወራ ምን ዓይነት ልጅነት ይሆን የነበረው? እንዴት ያለ ቤተሰብ ነበር ያሳደገው? ራሴን ጠይቃለሁ። ሴት ልጅ ስትጠይቀው ከማይወዳቸው ጥያቄዎች ዋነኛው ስለሆነ አልጠይቅም!) …………..ልጅ (እዚህጋ ቆየት ብሎ ቀጠለ) እስኪ ልጅሽን ሀላፊነትሽን አትወጪና አስርቢው አስጠሚውና ቀጥቅጪው እና ከዛም ያለምንም ቅድመ ሁኔታ አብሮሽ ይቆይ እንደሆነ እዪ (በፌዝ ፈገግ አለ) ባገኘው የመጀመሪያ አጋጣሚ ካንቺ ለማምለጥ ነው የሚፈረጥጠው (የመጨረሻው ገለፃ የሚያስበው ብቻ ሳይሆን የኖረው ዓይነት ስሜት ነበረው)……… ተቃራኒ ፆታውን እንኳን አንሸነጋገል። እድለኛ ከሆንሽ በጎደኝነት መሃል ያለው የስሜት መጠቃቀም ሲደመር ወሲባዊ ስሜት መጠቃቀም ሲደመር የቁስ መጠቃቀም!! ብቻውን ፍቅር የሚባል ነገር የለም!!»

ሌሎች ብዙ የወደፊቱ የትዳር ህይወቴን ሲኦልነት የሚገልፁ <ማሳያ ትኩሳቶች> እያወቅኩ እና ፍንጣሪውን እየተለማመድኩ ሰንብቼ ነው ያገባሁት። ሶስት ዋና ዋና ምክንያቶች እና ሌሎች ፍርፋሪ አባሪ ምክንያቶች ነበሩኝ። አንዱ ከሌላኛው ጋር በቀጥታም በጓሮም ይጋመዳል።

ከዋንኞቹ አንደኛው

እንደአብዛኛዋ ማህበረሰቡ <ሳታገባ እድሜዋ አለፈ> የሚባልበትን በህግ ያልተፃፈ የእድሜ ቁጥር እንዳለፈች ሴት ለቤተሰብ እና ለጎረቤት ፣ ለማህበረሰብ፣ ለጓደኛ ………….. ወላ ገና ለሚወለደው ልጄ ስል ነው ያገባሁት!

እንደዛ እኮ ነው! ለእነሱ ነው የምናገባላቸው! ከዛ ኑሮውን እኛ እንኖራለን እነሱ ደግሞ ገሚሱ አገባች ብለው ይደሰታሉ። (አንቺ ደስተኛ ሆነሽ ይሁን አይሁን ግድ የማይለው ይበዛል) የተቀረው ገሚሱ ወደሌላኛዋ ተረኛ እጩ ቋሚ ቀር ምላሱንና ፊቱን ያዞራል!! .... እስክታገባላቸው በምላስም በጥያቄም በነገርም ያንፍሯታል:: ስታገባላቸው ... ይህችኛዋንም አጨብጭበው ይድሩና ደሞ ወደ ቀጣይዋ..... የእኔን ግን ላብራራልሽ ...

አልጨረስንም……………….

@wegoch
@wegoch
@wegoch

#Meri feleke
ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት
(ክፍል ሶስት…………… meri feleke)

ከሳምንታት በኋላ ዝም አለ። በቃ ዝም! በእኔ ቁጥጥር ስር መሆኑን ላለመቀበል መፍጨርጨሩን ተወው። የእኔ እርዳታ የሚሰጠውን የተሸናፊነት ስሜት ላለመዋጥ የሚያደርገውን መንፈራገጥ ተወው። ሳጎርሰው ከምግቡ ጋር የሚውጠውን እልህ ተወው። ሰውነቱን ሳጥበው ከጡንቻው ጋር የሚያፈረጥመውን ትዕቢት አተነፈሰው። መለፍለፉንም ተወው። ዝም ጭጭ አለ። ልክ እንደሌለ ነገር። እንደማይሰማ ፣ እንደማያይ ፣ ምንም ስሜት እንደማይሰጠው ፣ ጭራሽ እዛ እንደሌለ…………. ዝምታው ደስ አይልም ይሸክካል። የተሸነፈ ሲመስል የበቀሌን ጥፍጥና ይቀንሰዋል። ደስ አይልም!

«ወደኋላ ተመልሰሽ ድጋሚ የህይወት ምርጫሽን የማስተካከል እድሉ ቢኖርሽ ታገቢኝ ነበር? ማለቴ ይሄን ትዳር ትመርጪ ነበር?» አለኝ ከብዙ ቀናት ዝምታ በኋላ የገና ቀን ጠዋት መኝታ ቤታችን መስታወቱ ፊት የበዓል ነጭ ልብስ እያለበስኩት ሳለ

«አዎ ሁለቴ ሳላስብ!» አልኩት በልቤ «ያውም መጨረሻው ይሄ መሆኑን አውቄ?» ብዬ ሳልጨርስ የሰማኝ ይመስል

«ላለፉት ዓመታት ስትዪ ወይስ ለመጨረሻዎቹ ወራት?» አለኝ መልሱን እንደሚያውቀው ሁላ ተረጋግቶ

«ለሁለቱም! በእርግጥ መጨረሻው እንደየዋህ ደራሲ ድርሰት መስመሩ ምርጫዬን ያቀልልኛል።» አልኩት! አልከፋውም! እንደውም ፈገግ ነገር አለ። የሆነ የማውቀውን ፈገግታ ፈገግ አለ። የሆነ የድሮው እሱ የሆነ ፈገግታ፣ ያሸነፈኝ ያሸነፈኝ ሲመስለው ፈገግ የሚለው ዓይነት ፈገግታ፣ የሆነ ተንኮል ሲያስብ ፈገግ የሚላት አይነት ፈገግታ………….

«ምን አስበህ ነው?»

«ምንም! ምነው?»

«አውቅሃለሁኮ! የአሁኗን ፈገግታ የምታመጣት ከዲያቢሎስ ጋር የሆነ ነገር ስታንሾካሹክ ነው!»
ከት ብሎ ሳቀ። ከአደጋው በኋላ ለአራት ወራት እንዲህ ስቆ አያውቅም! ዊልቸሩን ወደሳሎን እየገፋሁ እሱ ሳቁን አላቆመም። እንዲህ የሚስቀው ስራ ቦታ የሆነ ፈታኝ እቅድ አቅዶ ሲሳካለት ነው። ወይም በውጤቱ እርግጠኛ የሆነበትን ንድፍ ሲጨርስ

«ምን አስበህ ነው?»

«ራስሽን ግን አይተሽው ታውቂያለሽ? እኔን አንቺ ውስጥ አይተሽው አታውቂም?» አሁንም ሳቁን አላቆመም። «ራሴን አንቺ ውስጥ ሳየው እንዴትኮ ደስ እንደሚለኝ! ያው ክፋትም ደግነትም በሚታየው ድርጊት እንጂ ውስጣችን በተቆለለው ልክ ስለማይመዘን እንጂ ሃሃሃሃሃሃሃ ሙች እኔ እንኳን የምቀናብሽ ክፉ እኮ ነሽ!»

ተመስገን! ከአራት ወር በኋላ ዲያቢሎሱ እሱ ተመለሰ። ዝም ከሚለው ወይም ከሚንፈራገጠው እሱ ይሄ ይሻለኛል። ቢያንስ ይፈትነኛል። እንዳስብ ያደርገናል። ጤንነት አይመስልምኣ? ከምጠላው ሰውዬ ጋር ማውራት መናፈቅ? ለማንም ጮክ ብዬ ባወራው ጤንነት አይመስልም። ጭንቅላቴን የሚፈትነኝ ወሬው ዝም ሲል ይናፍቀኛል።

«ማንም በድርጊቱ እንጂ በሃሳቡ አይዳኝም! ወይም ቢያንስ ሀሳብህ የአፍህን በር ለቆ ካልወጣ ማንም ላይ የክፋት በትርህ አሻራ አያርፍም!»

«ያ ልክ ነው ትያለሽ ታዲያ? ሰው መዳኘት የነበረበት በሃሳቡ እንጂ በድርጊቱ ነበር? ምን እሩቅ ወሰደሽ ራስሽን ምሳሌ አድርጊኣ? አሁን ፀሃይ (ሰራተኛችን ናት። ሳሎን ውስጥ ጉዝጓዙን እየጎዘጎዘች ስሟን ሲጠራ ቀና ብላ አየችን) እንዴት ያለች መልአክ ሴት ብትሆን ነው ይሄን ሰይጣን ባሏን ፈጣሪ ጀምሮ ሰጥቷት እንደማጠናቀቅ እንዲህ የምትንከባከበው? ብላ ነው የምታስበው! አይደለም ፀሃይ? (ፀሃይ ምን መመለስ እንዳለባት ግራ ገብቷት አይኗን ስታጉረጠርጥ እሱ ቀጠለ።) ድርጊትሽ አልሸወዳትም ታዲያ? አንቺ በመልካምነት ጅራፍ በቀልሽን እያሳረፍሽብኝ እንደሆነ እኔም አንቺም ሰይጣንም እግዜርም እናውቃለን። (ሳቅ ብሎ) በነገርሽ ላይ ነገሩን ለምሳሌ አመጣሁት እንጂ እየወቀስኩሽ አይደለም። ታዲያ የሚዳኘው አካል ፈጣሪ በይው ሊዳኝሽ የሚገባው በየትኛው ነው? በድርጊትሽ እንዲዳኝሽ ምኞቴ ነው (ሳቅ ብሎ) ካለበለዚያ እንደተባለው ሲኦል ካለ እዛ ስንሄድ አለቃዬ ሁሉ ልትሆኚ እንደምትችዪ አስበሽዋል?»
ፀሃይ ወሬው ይሁን ግራ የገባት ወይም እኔ ግራ የገባኋት መጎዝጎዟን አቁማ አይኗን ጎልጉላ ቆማ ታየኛለች። እንደማማተብም አደረገች ነገር።

እንዲህ አይነት ወሬዎቹ ናቸው እየጠላሁት እንዲናፍቀኝ ፣ ደሜን በብስጭት እያንተከተከው እንኳን ዝም እንዳይል እንድመኝ የሚያደርጉኝ። አንዳንዴ የሱን ጭንቅላት ሌላ ልብ ላለው ሰው ቢሰጠው ብዬ ተመኝቼ አውቃለሁ። እሱ ጭንቅላት እንጂ ልብ የለውም! ለነገሩ ሰይጣንምኮ ስማርት ነው።

«የሰው ልጅ የሀሳቡ ውጤት ነው። ድርጊቱ የሀሳቡ ልጅ ነው። ያ ማለት መልካምን የሚያደርጉ ሰዎች ሀሳባቸው ውስጥ ክፋት የለም ማለት አይደለም። ተፈጥሮ በሙሉ ሁለቱንም ፅንፎች የያዘች ናት። ውልደት እና ሞት፣ መነሳትና መውደቅ፣ ውሸትና እውነት፣ ፍቅርና ጥላቻ፣ ጨለማ እና ብርሃን፣ ቀንና ማታ፣ ክፉና መልካም……….. የሰውም ልጅ የእነዚህ ነገሮች ስብጥር ነው የጥሩ እና የመጥፎ ፣ የክፉና የመልካም፣ የጨለማ እና የብርሃን……… ጥያቄው የትኛው ያመዝናል ነው። የትኛው አሸንፎ በተግባርህ ይገለፃል ነው ጥያቄው! ሲጥ አድረሽ ጨርሺው የሚለኝን ክፉ ሀሳቤን አቅፈሽ ሳሚው በሚል መልካም ሀሳቤ ከረታሁት ሊቆጠርልኝ የሚገባው ያ ነው። አቅፌ ስስምህ አንተጋ በሚፈጠረው ስሜት ጥቂት ደስታን መቃረሜን ፈጣሪም ይቅር ይለዋል።» ይስቃል።

ከእርሱ ጋር ባሳለፍኩት ሰባት ዓመት የተማርኩት አንድ ነገር የማንም ሀሳብ አሸናፊ የማንም ሀሳብ ተሸናፊ አይደለም። በአብዛኛው ተስማምተን አናውቅም። ለሰዓታት ልንጠቃጨቅ እንችላለን። መጨረሻው ሁለት ፅንፍ ነው። የማሸነፍ እና የመሸነፍ አይደለም። ሙግታችንም የእኔን ልክነት እመን ወይ ተቀበል ግብ ግብ አይደለም። በቃ በህይወት ውስጥ ስላሉን የተለያዩ ምልከታዎች ሀሳብ መቀያየር ነው። ላለመሸነፍ ግብ ግብ የለውም።

«አንቺ ግን ፈጣሪ ብለሽ የምታምኚው በከረሜላ እንደምትደልዪው ህፃን ጅል ነው እንዴ የሚመስልሽ?»

« እ እ! ጅል ሳይሆን መሀሪ ......ተደልሎ ሳይሆን ራርቶ ይቅር የሚል ......እንደዛ ነው የሚመስለኝ።» ብዬ ቁርስ ላበስል ወደጓዳ ልሄድ ስል

«እስኪ ተያት ዛሬ ፀሃይ ትስራው ቁርሱን! »

«ለምን? ምን የተለየ ነገር ተገኘ ዛሬ?» በጥርጣሬ አየሁት

«ምንም! እንጫወት ብዬ ነው። አንቺም የምትፈልጊውን ላታገኚ ድካምሽ በዛ እና አሳዘንሽኝ!»

«ምንድነው የምፈልገው?»

«አንቺ የምታውቂኝን ያህል አውቅሻለሁኮ! »

«እኮ ምንድነው የምፈልገው?»

«ይቅርታ አድርጊልኝ የምትለዋን አረፍተ ነገር ሃሃሃሃ ተሳስቻለሁ! አንቺ መልካም ሴት ነሽ ይቅር በይኝ እንድልሽ? አይደለም በይኝና ተሳስቻለሁ እልሻለሁ።» አሁን መሳቁ የእኔ ተራ ሆነ።

«ስለእውነት የምፈልገው ምን እንደሆነ በትክክል አላውቅም። የሆነኛው ቀን ግን አዎ ይቅርታ ትጠይቀኛለህ ብዬ እጠብቃለሁ።»

«በፍፁም አላደርገውም! <ለምን ደግ እየሆንሽ ለበቀል የተሰጠሽን እድል ታባክኛለሽ? ስልሽ ያልሽን ታስታውሻለሽ? በእኔ ክፉት ክፉትህን ልታቀል? በእኔ ሀጢያት በደልህን ልትሰርዝ? በፍፁም ያን ደስታማ አልሰጥህም!!> ነበር ያልሽኝ። እራሴን አንቺ ውስጥ አየዋለሁ የምልሽኮ ለዚህ ነው። እኔም ያን ደስታ በፍፁም አልሰጥሽም! ተሳስቻለሁ ስልሽ በእኔ ስህተት ያንቺን ልክነት ልታደምቂ? አጥፍቻለሁ ስልሽ በእኔ ጥፋት ያንቺን ፅድቅ ልትፅፊ? በፍፁም ያን ደስታ አልሰጥሽም! Come on you know me better!»
«ፀሃይ ቁርሱን አብስይልንማ!» አልኳት ጉዝጓዙን መጎዝጎዙን ከጨረሰሽ ብትቆይም ንፁሁን ጠረጴዛ እየፈተገች እያፀዳች የነበረችውን ፀሃይ

«ምን ላብስል?»

«ከአራት ወር በፊት ለበዓል ሳትጠይቂኝ ታበስዪ እንደነበረው የበዓል ቁርስ!» አልኳት ወደወሬዬ ለመመለስ ቸኩዬ ሶፋው ላይ እግሬን ደራርቤ እየተቀመጥኩ። ለወሬ ፊቴን ወደ እርሱ ስመልስ ድክም ብሎ እየሳቀ

«ነርቭሽን ነካሁት አይደል?»

«በተዘዋዋሪ እንደበደልከኝ ማመንህ ግን ገብቶሃል? ይቅርታ በአፍህ አልጠየቅከኝም እንጂ በደልህን እኮ ታውቃለህ! ከደቂቃዎች በፊት አመንክ!» አልኩት

«እ እ! ራስሽን አታፅናኚ እኔ መጀመሪያም እንዳንቺ ጥሩ ሰውነቴን ለመግለጥ ራሴን የማሰቃይ ሰው አልነበርኩም ታውቂኛለሽ። ጥሩም መጥፎም አይደለሁም ራሴን ነኝ! የእኔ ምርጫ እና ድርጊት ከጎዳሽ ተጠያቂዋ ራስሽ እንጂ እኔ አይደለሁም! በምርጫሽ እንጂ አስገድጄሽ የዚህ ህይወት አካል አላደረግኩሽም! ማዘን ካለብሽ በምርጫሽ እዘኚ! በምርጫዬ ተሳስቻለሁ ብለሽ ካመንሽ ራስሽን ይቅርታ ጠይቂው። አንቺ ለራስሽ ያላመንሽውን ጥፋትሽን በእኔ አሳበሽ ራስሽን ነፃ አታውጪ! ይቅርታ የምትጠይቂው ለስህተት ነው። ተሳስቼ ያደረግኩት ነገር የለም። አውቄ እንጂ።» ይሄን ካለ በኋላ እያንዳንዱ ቃላት እኔጋ የሚሰጠኝን ስሜት ስለሚያውቅ ፈገግ አለ በድል አድራጊነት።

«የሰይጣን ጭንቅላት እንዳለህ ግን ታውቃለህኣ?»

«እንዳንቺ የምትፈትነኝ ሴት ኖራ እንደማታውቅ እንደምታውቂው!»

«ብትሞት!»

«እመኚኝ ይደብርሻል። ማን እንዲህ ያለ ሰይጣናዊ ጨዋታ ያጫውትሻል?»

«እመነኝ አይደብረኝም። ሰይጣናዊ ጨዋታህን ለ7 ዓመት ተግቼዋለሁ።»

«እና በተዋዋሪ ደቀመዝሙሬ መሆንሽን አመንሽ ማለት ነው?»

በሩ ተንኳኩቶ ፀሃይ የሆኑ የማላውቃቸው ሴትዮ አስከትላ ገባች። ማን እንደሆኑ ከመጠየቄ በፊት የእሱ ድንጋጤ ማንም ይሁኑ ምኑ ብቻ ቅዠቱ እንደሆኑ ነገረኝ!!

«አስወጧት! አስወጡልኝ!» ጮኸ ……..

በሚችለው ሁሉ ተወራጨ። እየሆነ ያለውን ነገር ከመረዳቴ በፊት ዘሎ ከዊልቸሩ ተነስቶ ሴትየዋጋ መድረስ ይችል ይመስል ደምስሮቹ ተገታትረው ባለ በሌለ ሀይሉ ተወናጭፎ ወደፊቱ ወደቀ። ቢችል በዝህችው ቅፅበት አንቆ የሚገድላቸው ነው የሚመስለው! ሴትየዋን ከማስወጣት እሱን ከማንሳት እየሆነ ያለውን ከመረዳት ምኑን እንደማደርግ ግራ ገብቶኝ መሃል ላይ ስዋልል

«በናትሽ አስወጫት! እባክሽ?» አለ አቅም ባጣ ስሜት። ፀሃይ ሴትየዋን እያዋከበች ልታስወጣት ስትሞክር ለሰከንዶች የሴትየዋን ፊት አየሁት። ምንም ስሜት የሌለው ሙልጭ ያለ ፊት ……….. ተከትያቸው ልሄድ አሰብኩ። ያሰብኩት ገብቶታል።

«እባክሽ?» አለኝ። ተስፋ በቆረጠ የልመና ድምፅ

ተመልሼ አጠገቡ መጣሁ። ሴትየዋ ሄደች። ላነሳው ስሞክር። «ተይኝ!» አለኝ።

«እሺ አልተጎዳህም?» አልኩት እንዳወዳደቁ ከአደጋው ሳይሰባበር የተረፈ አጥንት ካለ እንክትክት የሚል ነበር የሚመስለው።

«ደህና ነኝ! እግሬን ብቻ ዘርጊልኝ» አለ! ሲወድቅ የታጠፈ እግሩን ዘርግቼለት ምንጣፉ ላይ በጀርባው ተስተካክሎ እንዲተኛ አድርጌው አጠገቡ በጀርባዬ ጋደም አልኩ። ፀሃይ «አስወጥቻቸዋለሁ» እያለች ወደሳሎን ስትገባ ወለል ላይ በጀርባችን ተጋድመን ስታየን ሳትፈልገው የግርምት ድምፅ አመለጣት። <ሰዎቹ ለይቶላቸዋል> አይነት ነው ግርምቷ።

«እባክሽ? በናትሽ? ቀድቼ ሁላ ደጋግሜ ብሰማው ደስ የሚለኝ ቃል! ጆሮዬን እኮ ነው ያላመንኩት! አንተ? እባክሽ?»

«ደስ አለሽ?» ድምፁ ቅድም እንደዛ የተሸነፈው ሰው ድምፅ አይደለም።

«አልዋሽህም ደስ የሚል ስሜት አለው። ካወቅኩህ ጀምሮ ማንንም ስለምንም ለምነህኮ የምታውቅ ሰው አይደለህም! እኔና አንተ አንወሻሽማ? የሆነ ቦታ ድክመት እንዳለህ ማወቅ ደስ የሚል ስሜት አለው። ተሸንፈህ አይቼህ አላውቅም። እሱኛው የሰጠኝን ስሜት አላውቀውም።»

«እና ተሳሳትኩ? ሲኦል ብንገናኝ አለቃዬ አትሆኚም?»

«ማናቸው ሴትየዋ?»

«ሲዖሌ ናት። ገሃነም! »

«ምንህ ናቸው? እናትህ?»

«ሲዖሌ አልኩሽኮ!»

አውቀው የለ?? በቃ አይመልስልኝም! አይነግረኝም። በጀርባዬ እንደተንጋለልኩ እጁን ፈልጌ እየያዝኩት እሱ ሳያውቅ ሴትየዋን እንዴት ላገኛቸው እንደምችል አስባለሁ።

«እ እ አታባብዪኝ! አትዘኚልኝ! እረፊ !! እኔና አንቺ ይሄን ጨዋታ አንጫወትም!» አለ።እንደሌላ ጊዜው እጁን ሊያስለቅቀኝ ግን አልተወራጨም። ቀጠል አድርጎ «የምታስቢውን ተይው። አይጠቅምሽም ልታገኛት አትሞክሪ»

....... .......አልጨረስንም…………………………

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሰይጣን ወይ እግዜር የጀመሩት ….. እኔ የቀጠልኩት
(ክፍል አራት ………. ሜሪ ፈለቀ)

ለመጀመሪያ ጊዜ በተያየን በአስረኛው ደቂቃ ነው <ላግባሽ> ያለኝ። የሶስተኛ ታናሼን ሰርግ ልታደም አንደኛው የከተማችን ሆቴል ነበርኩ። የምሳ ቡፌ ከተነሳ በኋላ ማንም ሳያየኝ ከአዳራሹ ውልቅ ብዬ እዛው ህንፃ ላይ ያለ ሬስቶራንት ውስጥ ገባሁ። ቢያድለኝኮ የአክስቶቼን ውግምት የሆነ ዓይን መሸሼ ነበር። ገና ወንበር ስቤ ከመቀመጤ ከየት መጣች ሳልላት አንዷ አክስቴ

«ምነውሳ ያን ከመሰለ ፌሽታ ተነጥለሽ እዚህ ብቻሽን?»

«ቡና መጠጣት ፈልጌ ነው! አንቺስ?»

«እኔማ ስልክ ላወራ ወጥቼ ስትዘልቂ አይቼሽ ነው። በይ እኔ ልመለስ እናቴ!» ብላ ፊቷን አዙራ ስትሄድ በግልግል ልተነፍስ የጀመርኩትን ትንፋሽ መለስ ብላ ስቅታ አደረገችብኝ። «እንግዲህ ሚጡዬ ታናናሾችሽን ሁሉ ድረን ጨረስን። ለሴት ልጅኮ ተፈጥሮም ገደብ ይጥላል! እንደው ምርጫው ይቅርብሽና ከአንዱ ሰብሰብ በይ ለእናትሽ ስትዪ……….ላንቺምኮ ዓለም ነው» (የሆነ ያዘነችልን ታስመስለዋለች። <ላንቺ ብዬ ነው> የሚሏት ዓይነት ቅብ)

«የሚመረጥ አምጥታችሁ ያማረጣችሁኝኮ ነው የምትመስሉት በእርግጠኝነት ስታወሩ። ካላገባሽ እያልሽ በገባች በወጣች ቁጥር በነገር ስትነድፊያት ልጅሽ መጨረሻዋ የሆነው አምስት ማቲ ታቅፋ ተመልሳ ያንቺ ጉያ መታከክ አይደል? ድንቄም ዓለም! ይሄንን ነው ዓለም የምትሉኝ?» ከጀርባዬ ፍቅፍቅ ብሎ የሚስቅ ሰው ድምፅ ስሰማ ነው ሬስቶራንቱ ውስጥ ያለው ገሚሱ ተጠቃሚ ሊሰማኝ በሚችል ድምፅ እየጮህኩ እንደሆነ የታወቀኝ። እሱ ነበር!

ለወትሮ ምንም ቢሉ መልስ አልነበረኝም። ምክር፣ ወቀሳ፣ ሽርደዳ ……… <እፈልግሻለሁ> ብለው እቤታቸው ጠርተውኝ ሁላ ሲግቱኝ ዝም ነበር መልሴ። <ለትልቅ ሰው መልስ አይሰጥም> ፣ <ቢሰድቡሽም ፣ ቢገርፉሽም፣ ጭንቅላትሽ ውስጥ ተደፍድፎ ቀስ በቀስ የሚሸርፍሽን መርዝ በቃላት ቢያቀብሉሽም አዋቂዎች ላንቺ ብለው ነው…….> ተብዬ ነዋ ያደግኩት። ለአክስቴ ሌላ የምትለጥፍልኝ ስም ሰጠኋት። ደንግጣ የጎስት በመሰለ ሽውታ ሽውውው ብላ ወጣች። ሳቁን ሳያቋርጥ አጠገቤ ያለውን ወንበር ስቦ ተቀመጠ።

«ሚጡ ብለውሽ ደግሞ ካላገባሽ ሄዶላቸው ነው?»

«ሁሉንም እየሰማህ ነበር ማለት ነው?»

«እንደዛ ነገር። ሴትየዋንኮ ቆሌዋን ነው ያበነንሽባት። ለሚቀጥሉት ተከታታይ ቀናት በህልሟ ሁሉ ነው የምትመጪባት። እና አንቺ ያላገባሽው ሴትየዋ እንዳሉት ስታማርጪ ነው? ለትዳር ያለሽ ምልከታ ስለሚለይ ነው? ማግባት ስለማትፈልጊ ነው?»

«ዝም ብሎ ትዳር ውስጥ ይገባል እንዴ? በእርግጠኝነት አምነህ ህይወትህን የምታጋራው ሰው በህይወትህ ካልተከሰተ እድሜ ስለሄደ፣ ታናናሾቼ ስላገቡ፣ ቆማ ቀረች ላለመባል …….. ያገኘሁትን አፍሼ አገባለሁ? ቆይ ትክክለኛው ሰው ካልተገኘ ሳያገቡምኮ መኖር ይቻላል። » የመጨረሻውን ዓረፍተ ነገር ስጨርስ ለማላውቀው ሰውዬ ማወቅ የሌለበትን እየዘበዘብኩ እንደሆነ ገብቶኛል።

«ሳያገቡ መኖር ይቻላል!! የቻሉ ሴቶችም ይኖራሉ። አንቺ ትችያለሽ ወይ ነው ጥያቄው? መቻልና አማራጭ በማጣት ሁኔታን መቀበል የተለያየ ነገር ነው። ትዳርን ልመሰርት የምመኘው ትክክለኛ ሰው በህይወቴ ካልተከሰተ ትዳር እንዲኖረኝ አልፈልግም የሚል አቋም ኖሮሽ ሳታገቢ ስትኖሪ በውሳኔሽ ደስተኛ ነው የምትሆኚው። ባልየው ቢመጣ ደስ ይልሻል ቢቀርም ግን በውሳኔሽ አትፀፀቺም።< ያ የባለፈው ሰውዬ እኮ ትንሽም ቢሆን ይጠጋጋ ነበር ምንአለ እሱን ባገባሁት?> አትዪም። እንደቅድሟ ዓይነት ሴትዮ መጥተው ሲወርፉሽ እንደቅድሙ አትጨሺም። የቤተሰብ ወይ የማህበረሰብ expectation ግድ አይሰጥሽም። ምርጫ አጥተሽ ሲሆን መጀመሪያ ነገር ውሳኔሽን አታምኚውም። ሰርግ ባየሽ ቁጥር የምትቆዝሚ ፣ አዳራሽ ለቀሽ ወጥተሽ ሬስቶራንት ውስጥ የምትደበቂ፣ ደስታ የራቀሽ ሰው ነው የምትሆኚው።»

የተናገረው እውነት ከመሆኑ በላይ ትንተናው ለወሬ የሚጋብዝ ስለነበር አልጎረበጠኝም። ይልቅስ እንደአብሮ አደግ ወዳጃማቾች ጨዋታ መቀባበል ጀመርን።

«እሱ ልክ ነህ ግን ምርጫ ስታጣም ያለህበትን ሁኔታ ተቀብሎ መኖር ሽንፈት አይደለም እንደውም ብርታት ነው። መንነህ ገዳም ካልገባህ ወይም የተለየ ባህልና እምነት ያለው ማህበረሰብ ያለበት ቦታ ካልተሰደድክ በቀር ግን እንዴት ነው <የማንም expectation ግድ አይሰጠኝም> የሚባለው። ልክ የሆነ አካሌ የጎደለ ያህል እኮ ነው ባል የሚባለው ፍጡር ስለጎደለ ከምድር በረከት የጎደልኩ የሚያስመስሉት! በግልፅ <እስኪ ተጠመቂ> ፣ <ለአምላክ የሚሳነው የለም በንፁህ ልብ ፁሚ ፀልዪ> ይሉኛል። ዞር ስትልላቸው <ይህቺን የመሰለች ልጅ ቆማ መቅረቷ ነው ምፅ!! > ይባባሉብሃል።»

«እንዴ ቆይ ግን ምን ያህል ብታረጂ ነው?»

«34»

«ያነሳሽበትን ስንደምረው ገፍተሻል!»

«ባክህ ሳልኖርበትም ቀንሼበትም አያዋጣኝም!»

« ላግባሽ!» ጥያቄ አይደለም። ኮስተር ያለ፣ እርግጠኝነት ያለበት እንደጥቆማ አይነት ነገር……… ልክ የሆነ ባለሙያ <እንዲህ ብታደርግ ይጠቅምሃል!> ብሎ እንደሚሰጠው አይነት ምክር አዘል ጥቆማ!

«ጭራሽ?»

«የእውነቴን ነው! መቼም በ34 ዓመት የሰው ልጅ ተጠንቶ የሚታወቅ ፍጡር አለመሆኑን አልደረስኩበትም አትይኝም እና ሳንጠናና ሳንፈታተን አትዪኝም! አልጋ ላይ እንዴት ነሽ?»

«አንተ? ጤናም የለህ እንዴ?» ከማፈሬ የተነሳ የሰማው ሰው እንዳይኖር ዞር ዞር አልኩኝ። እሱ ምንም ወጣ ያለ ነገር እንዳላወራ ሁላ ቀጠለ።

« ኦህ ለካ ስም አልተለዋወጥንም። አዲስ እባላለሁ ፣ በሚቀጥለው ሳምንት 42 ይሆነኛል። አልጋ ላይ ጎበዝ ነኝ! ከፈለግሽ አሁኑኑ ወጥተን ላሳይሽ እችላለሁ። (ኮስተር ብሎ ነው የሚያወራው እንደልክ) ፣ ስራዬን ማወቅ ከፈለግሽ ዝርዝሩን ወደፊት አስረዳሻለሁ በጠቅላላው ነጋዴ ነኝ። ይሄ ችርቻሮ ነጋዴ ነገር አይደለሁም። ሀብታም ነኝ፣ በቁስ የምትደሰቺ ዓይነት ሰው ከሆንሽ አብረኸኝ ሾፒንግ ውጣ አትበይኝ እንጂ የተዘባነነ ኑሮ አኖርሻለሁ። እ እ እ ምን ቀረ ምን ቀረ? የትምህርት ደረጃዬን ማወቅ ከፈለግሽ ደረጃ የለኝም! ከዘጠኝ ነው የተውኩት……….በተለያየ ምክንያት ከሀገር ስለምወጣ ቋንቋ ተምሬያለሁ። ሁለቴ አግብቼ ነው የፈታሁት። ሀይማኖት የለኝም! ዋና ዋናው ይኼ መሰለኝ። ማወቅ የምትፈልጊውን እነግርሻለሁ።»

የሚያወራው ከልቡ መሆኑን አልተጠራጠርኩም። ጤንነቱን እንጂ። አፌን ከፍቼ ነው በከፊል ድንጋጤ በከፊል ግርምት በብዙ ግራ መጋባት የማየው። ከእኔ መልስ እየጠበቀ መሆኑ ሲገባኝ ሳቄ መጣ

«ምን? እንደስራ ሲቪ ስለራሴ እንድነግርህ አይደለም አይደል እየጠበቅህ ያለኸው?»

«ትዳርን ምን ለየው? እንተዋወቅ እንጠናና የምትሉት ከዚህ የተለየ የሚያሳውቃችሁ ነገር አለ? ያው ሳታገቢ የምትኖሪውን ህይወት ከማራዘም ውጪ! ያውኮ ነው ይሄን ይሄን ያሟላ ብለሽ ልክ እንደ ስራ ቀጣሪ መስፈርት ታስቀምጫለሽ የሚመጣው ሰውዬ መስፈርትሽን ካለፈ ባል ሆኖ ይቀጠራል። ቆይ እስኪ አንቺ አጋሬ ነው ብለሽ እየጠበቅሽው ያለሽው ሰውዬ ምን አይነት ነው?»

«definitely እንዳንተ ዓይነት አይደለም። ጉረኛ፣ ሲያወራ ግልብ፣ ሁለት አግብቶ የፈታ …….. የለበትም!!»

ከት ብሎ እየተንፈራፈረ ሳቀ።
« ቅድም ስላላገባሽ እንደጎደሎ በመቆጠርሽ ይህን ማህበረሰብ ስትወቅጪው ነበር። ራስሽው ግን አግብቶ መፍታትን የሆነ ተላላፊ በሽታ ይመስል ግፍግፍ እያደረገሽ እንደጉድለት አየሽብኝ ሃሃሃሃሃሃ»
«ይሄና ያ ይለያያል። በ42 ዓመት ሁለቴ አግብቶ መፍታት ቀይ መብራት ነው።»

«ልዩነቱ ኩነኔውን ተቀባይ ቦታ መሆንና ኮናኝ ቦታ መቆም ነው። እንቁላል የሰረቀ ሌባ እገሌ በሬ ሰረቀ ቢሉት <እና ለቀቃችሁት?> ይላል። ለራሳችን ይገባናል ብለን የምናምነው ምህረት ለሌላ ሰው ሲሆን ምህረት ለእርሱ በደል ውድ ናት ብለን እናስባለን። አየሽ ልዩነቱ የቆምንበት ቦታ ብቻ ነው።» የእውነት የጥፋተኝነት ስሜት ተሰማኝ። የሆነ ቁስሉ ላይ ጨው የነሰነስኩ መሰለኝ።

«በጣም ይቅርታ ………» ብዬ ከመቀጠሌ በፊት እየተርገፈገፈ ስቆ

«ኸረ እኔ እውነታውን ነው እንጂ የነገርኩሽ ከፍቶኝ አይደለም። ፈልጌ ነው የፈታኋቸው። ስለፈታኋቸውም ደስተኛ ነኝ።» ብሎ የሆነ ልክ የሆነውን ዓለሜን ልክ ባልሆነው ዓለሙ ቀላቀለብኝ። በውስጤ ተነስቼ ደህና ሁን ብዬው መሄድ አስባለሁ ግን ተጎለትኩ።

………………አልጨረስንም…………………

@wegoch
@wegoch
@paappii
2024/09/22 20:20:54
Back to Top
HTML Embed Code: