Telegram Web Link
★★የባል ገበያ ★★
(ክፍል ሁለት)
ሜሪ ፈለቀ

ጥዬው ብሄድ ደስ ባለኝ። …… እንደምንም ለሁለት ሰዓታት ታግሼ አየር ማረፊያ ድረስ ሸኘሁት። …… እቅዳችን የነበረው ከወር በኋላ ተመልሶ መጥቶ ልንጋባ ነበር።…… ፊቴን ሳዞር የመጀመሪያ ስራዬ ሊያገኘኝ የሚችልበትን መንገዶች በሙሉ መዝጋት ነበር። ………
……
……
"አዚቲ እኮ ቪዛዋ ተሰጣት።" አለች አፀደ እንደ ልምዷ እየተቅለበለበች። ክላስ ውስጥ ያለው ሴት በሙሉ በቄንጥ ተንጫጫ

"ምን ያደርጋል ግን……" ቀጠለች ሴቱ ለ ‘ኦ ማይ ጋድ‘ ቄንጥ የሰቀለውን እጁን ከአየር ላይ ሳያወርድ

በአንድ የአውሮፓ ቋንቋ ትምህርት ቤት ውስጥ ቋንቋ ለመማር ነው የተሰበሰብነው። …… በሚገርም ሁኔታ ከአንድ ወንድ በቀር ሁላችንም ሴቶች መሆናችን ሲገርመኝ። ሁላችንም ለቪዛ ከትምህርት ቤቱ የቋንቋ ብቃት ሰርተፊኬት ስለሚያስፈልግ የምንማር ነን። ከዚህ በላይ የደነቀኝ ግን ከሁለት ሴቶች በቀር ሁላችንም በተመሳሳይ የሳይበር ጠበሳ ትዳር መስርተን በጋብቻ አመሃኝተን ከሀገር ለመውጣት የሚጠበቅብንን እያሟላን መሆናችን ነው።

አዚቲ (ቪዛዋ የተፈቀደላት) ከወራት በፊት ነበር ያገባችው። ጓደኞቿ ሲያላግጡባት
‘ባሏ ከመምጣቱ ሳምንት በፊት አስቀድሞ ከዘራውን ነው የላከው። ከዘራውን ይዛ ሄዳ ነው ቦሌ የተቀበለችው‘ ይሏታል። እሷ በራሷ የምትፎግር ፍሪክ ናት። ትስቃለች።
ያገባችው ሰው ከተጋቡ ጀምሮ ቪዛው እስኪፈቀድ ሀገሩን ትቶ ገስትሀውስ ተከራይተው አብሯት እየኖረ ነበረ።

አዚቲ እንኳን በደሞዝ በእቁብ የማትቻል ወመኔ ሱሰኛ ናት። …… ሰውየውን በስተርጅና ቃሚና ቀምቃሚ አደረገችው። …… እንደአፀደ ገለፃ ቪዛው መፈቀዱን በሰማ እለት በከፍተኛ ምርቃና ውስጥ ሆኖ አንድ ነገር ተከሰተለት። …… ኢትዮጲያን ወዷታል። …… አዚቲን የመሄዱን ሀሳብ ትተው እዚሁ እንዲኖሩ ቢያማክራት ‘ነብር አየኝ በል‘ አለች።(በእርግጥ በእንግሊዘኛ እንዴት እንዳለችው እንጃ!) በመጨረሻ ሰውየው ውሳኔውን አስተላለፈ።

"ከፈለግሽ አንቺ መሄድ ትችያለሽ! እኔ ከዝች ሀገር እግሬ ንቅንቅ አይልም!"
አፀደ ወሬውን ከአፏ ቀምቶ ሌላ ሰው የሚያወራባት ይመስል እየተሽቀዳደመች አውርታ ስትጨርስ ፍርፍር ብዬ መሳቅ አምሮኝ ነበር። ከሀብቴ(የክፍላችን ብቸኛ ወንድ) በቀር ሁሉም የለቅሶ ቤት ፍራሽ ላይ የተቀመጡ ያህል ተክዘው ሳይ ሳቄን ዋጥኩት። ……
……
……
ባለአንድ ፍሬውን ተጣማሪዬን ከተለየሁ በኋላ ለቪዛ እየተማርኩ የመገኘቴ ኋሊት እንዲህ ነው። ……
ሸኝቼው ስመለስ የምቀጥለው ኑሮ እንዳልነበረኝ ገባኝ። የሆነ መንገድ ላይ መኖሬን ቀጥ አድርጌዋለሁ…… የሆነ ሩቅ መንገድ ላይ…… መኖር ወደውጪሃገር መሄድ ሆኗል። …… እዛች ቦታ ላይ ኢትዮጲያ ውስጥ መኖር አቁሚያለሁ። …… መኖር ከሃገር ለመውጣት መሰናዳት ሆኗል። …… …… ይሄን አቁሜ እዛጋ የሰበርኩትን ድልድይ ገጥሜ መኖር እንደማልችል የገባኝ…… ፈረንጅ መጥበሴን እናቴ በሰማች ማግስት ስልክ ደውላ

"እልልልል ልጄ ከሰው እኩል ልታደርጊኝ ነው?" ስትለኝ

"ፈረንጅ ካገባሽ ሳይክል ትገዢልኛለሽኣ?" ታናሽ ወንድሜ በለሊት ቀስቅሶኝ ሲጠይቀኝ

"አሰይ ልጄ የአባትሽን መቃብር አሳድሽለት!" ስትለኝ አክስቴ

"መድሃኒያለም ሳልሞት ያንቺን ዓለም ሊያሳየኝ ነው።… …እንደው ልጄ የምትታለብ ላሜ ሞታብኛለች ደህና ላም አይተሽ ግዢልኝ። እመርቅሻለሁ።" ስትል አያቴ
ይሄኔ ለራሴ ወሰንኩ። በየትም መንገድ ከሀገር እወጣለሁ። …… ከውሳኔዬ እኩል መፃፃፍ አቁሜ ከነበረው አንደኛው ሰውጋ መፃፃፌን ቀጠልኩ። ……
መልኩ ምን እንደሚመስል አላውቅም።የውጪ ዜጋ ከመሆኑ ውጪ ስለራሱ የነገረኝ ነገር የለም። ሲያወራኝ (በፅሁፍ) ግን የማውቀው… … የሚያውቀኝ…… ረዥም ጊዜ አብረን የሆንን አይነት ነው የሚሰማኝ። …… ሰው የማያውቀውን ሰው ይለምዳል? ለመድኩት። …… የእውነት ያለ ሰው መሆኑን እንኳን ማረጋገጥ የማልችለውን ሰው አመንኩት። …… ጣቶቼ ከስልኬ ላይ ሳይነሱ ይመሻል። ……… ስለብዙ ነገር በማውራታችን የተዋወቅን መሰለ። …… ሰው ይሁን ማሽን፣ ሴት ይሁን ወንድ፣ እብድ ይሁን ጤነኛ… … የማላውቀው ሰው ትንፋሽ ይሞቀኛል። በህልሜ ሁሉ አየዋለሁ። …… ጠዋት ያየሁትን ፊት ለማስታወስ ብሞክር አይመጣልኝም። …… እበሳጫለሁ። …… ራሴ ያበድኩ ያበድኩ ይመስለኛል። ……
መጥቶ እንደሚያገባኝ ቃል ገባልኝ። …… ላላምነው ብፈልግም አመንኩት። …… ቋንቋውን እንድማር በአካውንቴ ብር አስገባልኝ። …… የማደርገው ሁሉ መጃጃል እንደሆነ እየገባኝ ተመዝግቤ መማር ጀመርኩ።……
እመጣለሁ ያለበት ቀን ስምንት ቀን ብቻ ቀርቶታል። …… መጃጃሌን አላቆምኩም። …… ስቀበለው ምን እንደምለብስ፣ የምሰጠውን አበባ፣ የቀኑን እርዝመት…… አስባለሁ። …… ባይመጣስ? እላለሁ መልሼ። ምን ስለመምሰሉ ቦታ ያለመስጠቴ ይገርመኛል። ላስብም ብሞክር ወዲያው ተወዋለሁ።
አራት ቀን……
ሶስት ቀን……
ሁለት ቀን……
አንድ ቀን……
አንድ ሰዓት ሲቀረው ቦሌ ተገኘሁ።…… ትምህርት ቤት ስለሰማኋቸው የሴቶች ገጠመኝ እያሰብኩ ‘እንዲህ ቢሆንስ?‘ ‘እንዲያ ቢሆንስ?‘ ሀሳብ እገምዳለሁ።
……
👉🏽👉🏽👉🏽አልጨረስንም👈🏽👈🏽👈🏽

@wegoch
@wegoch
@paappii
★★የባል ገበያ ★★
(ክፍል ሶስት)
ሜሪ ፈለቀ

"ሸሚዝ በከረቫት አይነት ሁሌ ሲጠነቀቁ አትመኛቸው። ወይ እጃቸው እስክትገቢ ነው አልያም የሆነ የሚያካክሱት አልባሌ አመል አለባቸው።" ያለችው ሳቢ ትዝ አለችኝ። …… ሳቢን የማውቃት በሀብቴ ነው።

ሳቢ ፈረንጅ የማግባት ፍቅር እንጂ ከሃገር የመውጣት ፍቅር አልነበረም ዴቲንግ ሳይት ላይ የጣዳት። እንኮኮ አድርጌሽ ልዙር የሚል ፈረንሳዊ ጠበሰች። …… ፊልም ላይ እንደምታየው እና እንደምትመኘው ውሃ ካልጠበስኩልሽ የሚላት ዓይነት ሆነ። …… ወደኢትዮጲያ መጥቶ እንዳያት የጋብቻ ጥያቄ አቀረበላት። ተጋቡ። …… እፍ አሉ። …… ከፍቅራቸው ምጥቀት በአንድ ቆርኪ ውሃ ገላችንን እንታጠብ አሉ። …… ሁሉም ፍፁም መሰለ። ……
እየቆየ ሳቢ አንድ ነገር እየከነከናት መጣ። ባሏ ከርሷ ጋር ባለው ወሲብ ደስተኛ አይደለም። … …… ጭራሽ ባያደርግም ደስተኛ ነው። የምታየው እንደዛ ቢሆንም በአፉ ደስተኛ እንደሆነ ይነግራታል። …… ሁሉን ለሚሆንላት ባሏ ደስታ መሆን ያለመቻሏ ህመም እየሆነባት ሳለ እንደተለመደው በሷ ቆስቋሽነት ካላቡ በኋላ እሷ ወደ መታጠቢያ ቤት ስትገባ እሱ ወደ ላይብረሪው ጋውኑን ደርቦ ሄደ።

…… ሳቢ ግራ ተጋባች። ምን ብትሆንለት ደስተኛ እንደሚሆን በማሰብ ናወዘች። …… ልታናግረው ፈልጋ ወደ ላይብረሪው እግሯን አነሳች። …… በሩን ከፍታ ያየችው መዓት ሲኦል ደርሶ መልስ ሆነባት። …… ሰው ብላ ያገባችው ባል ከሀገሩ ይዟት ከመጣ ውሻው ጋር የሚዳራ እንስሳ ሆኖ አገኘችው…… ራሷን ሳተች። …… ፈረንጅም ውሻም ጠላች። …… ሳባ መልሳ ራሷን ለመሆን ብዙ ከፈለች።……
……
……
በስመአብ! አሁን ይሄን ቀፋፊ ታሪክ ለምን አስባለሁ?
አውሮፕላኑ አርፏል። …… ሰወች እየወጡ ነው።……
ከመፍራቴ የተነሳ ባይመጣ ተመኘሁ። ውስጤ የሳልኩትን ስዕል ከሚያፈርስብኝ ቢቀር አለምኩ። …… በቃ ሁሌ እየጠበቅኩት ብኖር…… ለካንስ ተስፋ ከውጤቱ በላይ የሚያስደስተው ጥበቃው ነው። …… ወይም ጉዞው……
ሻንጣ እየገፋ የሚመጣ አስቀያሚ ሰው ባየው ቁጥር ‘እርሱ ባልሆነ‘ እላለሁ።…… ለአይኔ የሞላውን ‘እሱ ይሆን?‘ ብዬ አፈጣለሁ። … ከማርጀቱ የጎበጠ ነጭ ሲመጣ ባልሆነ ብዬ አይኔን ጨፈንኩ። ሳገኘው እንደምጠመጠምበት ነው የማስበው። …… ይሄ ሰውዬ ቢሆንስ? ሆ! ከአዛውንት ጋር እንጥልጥሎሽ ልጫወት? አይሆንም!

"እኔ አውቅሻለሁ። የቆምሽበት ድረስ ራሴ እመጣለሁ።" ነው ያለኝ ምስሉ የሌለኝን ሰው እንዴት እንደምቀበለው ስጠይቀው።
ስለእውነት ጥበቃዬን አቁሜ መሄድ ሁሉ ቃጥቶኝ ነበር። ……

"ሄላ……ኦህ ማይ ዲር ጋድ! እንዴት ነው የተለወጥሽው?" አለኝ የማውቀው የመሰለኝ ድምፅ

"እንዴ? መውደድ?" ተቃቀፍን። ……

"እንዳላግዝህ ሰው እየጠበቅኩ ነው።" አልኩት ሻንጣዎቹን እያየሁ። በሰላምታ ባጠፋሁት ደቂቃ ያለፈኝ ሰው ካለ ዙሪያ ገባዬን እያየሁ።

"ኢትስ ኦኬ!" አለኝ በእጄ የያዝኩትን ፅጌሬዳ እያየ ፈገግ ብሎ ቀጠለ

"ፍቅረኛሽን መሆን አለበት።"

"እ" አልኩኝ ቶሎ ካጠገቤ እንዲሄድ እየፈለግኩ። እኔ ምን እንደሚመስል ያላወቅኩትን ሰው እንዲያይብኝ አልፈለግኩም። ያውም መውደድ… …

"ፍቅርን ድጋሚ በማግኘትሽ ላንቺ ደስተኛ ነኝ።" አለኝ ሳይንቀሳቀስ
‘ጥለኸኝ ስትሄድ የቀበርከኝ ነበር የመሰለህ?‘ ልለው ነበር ያሰብኩት… … እሱን ማቆያ ስለመሰለኝ

"አመሰግናለሁ።“ ብዬው ፈንጠር ብዬ ቆምኩ። አይኖቼን ስራ ሰጠኋቸው።

"Am here" አለኝ መውደድ ፊቴ ቆሞ።

"መውደድ ሰው እየጠበቅኩ ነው አልኩህ አይደል? ምን እየሆንክ ነው?ለምን አትሄድልኝም።" ጮህኩበት

"እመኚኝ እኔን ነው እየጠበቅሽ ያለሽው።…… " ሊያሳምነኝ ያወራናቸውን ሁሉ ነገሮች ሲነግረኝ…… አንድ የሆነ የተዛባ ነገር የተፈጠረ መሰለኝ…… ወይም አይኔ አልያም ጆሮዬ ካልሆነም ህልም ነው…… መውደድ? አይሆንም!! አይሆንም!! ……
……
👉🏽👉🏽አሁንም አልጨረስንም👈🏽👈🏽

@wegoch
@wegoch
@paappii
★★የባል ገበያ ★★
(ክፍል አራት)
ሜሪ ፈለቀ

አይሆንም!! ……

"መውደድ እየቀለድኩ ነው በለኝ?"

"እየቀለድኩ አለመሆኔን ታውቂያለሽ!! ስትፃፃፊው የነበረው ሰው እኔ ነኝ።"

መውደድን ልጠብቀው አልችልም። …… በማትረባ ቅንዝራም አሮጊት የቀየረኝን መውደድ በፅጌሬዳ እንኳን ደህና መጣህልኝ ልለው በፍፁም አልችልም።…

… ለወራት በጠዋት ስነቃ በጉጉት ያነበብኩት "good morning ma sunshine" የሚለው ልቤን እንደጠዋት ፀሃይ የሚያሞቅ መልዕክት የመውደድ መሆኑን ሳስብ ያለፉ ጠዋቶቼ አንገሸገሹኝ። ዘወትር ምሽት ለወራት "darling u r in ma arms, hv a sweet dream" …የሚሉትን ቃላት የመውደድ ጣቶች እንደተየቡት ለማመን ሳሰላስል … አልጋዬ ላይ በምቾት የተገላበጠ ጎኔን ጠላሁት…… መውደድን ብበጫጭቀው እንኳን ንዴቴ የሚበርድ አልመሰለኝም።…… በእጄ የያዝኩትን አበባ መሬት ላይ ወርውሬ በእግሬ ደፈጠጥኩት!! ምንም ብናገረው ሁሉም ቃል ገለባ ነው። …… ዝም ብዬው ልሄድ እግሮቼን አነሳሁና… ብስጭት፣ እልህ፣ እንባ…… መላ አካላቴን ናጠኝ።

"ታውቃለህ? መቀለድህ ከነበር ጅላጅል ቀልድ ነው የቀለድከው። የማትረባ ዥልጥ ነህ!! ምን እንዳደረግክ ታውቃለህ? ለነገሩ ልታውቅ የምትችልበት ማሰቢያ አይኖርህም። አፈር ብላ!! ከንቱ!! ቂላ ቂል ከንቱ ነህ!" …… ምንም ያህል ልሰድበው ብሞክር ከተሰማኝ ብስጭት ጋር ሚዛን ላይ ሲሰፈር ያቆለጳጰስኩት ያህል ምርቃት መስሎ ተሰማኝ። …… ለዛሬ ቀን የሚሆን የክት ስድብ አጣሁ። …… አይኖቹን ከአይኖቼ ሳይሰብር ከቆመበት ሳይንቀሳቀስ ያየኛል። ………

"‘የምታፈቅሪው ሰው ደጋግሞ ግዙፍ በደል ቢበድልሽ ስንቴ ይቅር ትይዋለሽ?‘ ስልሽ የመለስሽልን መልስ ታስታውሻለሽ?" በረጋ ድምፅ ጠየቀኝ።

‘ድርጊቱን ያደረገበት ምክኒያት እንጂ በደሉ ብቻውን ትልቅም ትንሽም አይሆንም።‘ ብዬው እንደነበር አስታወስኩ።

‘በደሉን የሚያገዝፈው የትኛው ምክንያት ነው?‘ ላለኝ ጥያቄ

‘አንደኛ እኔን ለመጉዳት አስቦ ሲሆን ሁለተኛ ራሱን ለመጥቀም አስቦ ሲጎዳኝ። ባጠቃላይ የበደሉ ዘር የክፋት ጭማቂ ሲሆን ጥፋቱ ኢምንትም ቢሆን ይገዝፍብኛል።…… የማፈቅረው ሰው ያለምንም ክፋት፣ ሳያውቅ ወይም ተሳስቶ ለሚበድለኝ በደል ገና ሳይበድለኝ በፊት ሁላ ይቅር ብዬዋለሁ። …… ‘ ብዬ መልሼለት ነበር። …… እንዳስታወስኩት እርግጠኛ በመሆን ከንፈሩን ለመፍገግ እያሸሸ

"በደሌ ከይቅርታ በላይ ትልቅ መሆኑን ለማወቅ እድል ስጪኝና ምክኒያቱን ልንገርሽ።……ካለዚያ ምክኒያታዊነትሽ ከጥሩ አባባሎችሽ መሃል አንዱ ብቻ እንደሆነ ልመን? "

"ክህደት በምንም መልኩ ቢሆን ክህደት ነው። ቅን ምክንያት ልትለጥፍለት አትችልም። …… ምክኒያትህን ልሰማ ቢገባ እንኳን ያን ማድረግ የነበረብህ ከአራት ዓመት በፊት ነበር። ……" ለሱ ቆሜ ማብራሪያ መስጠቴ በራሱ አበሸቀኝ።

አባቴ ታሞ ለቀናት ባንገናኝ ፍጥረት የሚቀናበት ንፁህ ፍቅራችንን እንደምንም ሲተወው መች ምክኒያት ሰጠኝ? ከፊቷ ይልቅ ስትራመድ ወደ ታች ተረከዟን ወደ ላይ ማጅራቷን የሚነካ እስኪመስለኝ የምታስደንሰው የሚያሳቅቅ ትልቅ ቂጧ ትዝ የሚለኝን ሴትዮ ማግባቱን እንኳን መች ከሱ ሰማሁ? ለአንድ ቀን ድምፄን ካልሰማ ‘ሳልሞትብሽ ስልክሽን አንሺው‘ ይለኝ የነበረ ሰው ከሃገር መውጣቱን ከሄደ በኋላ ቤተሰቦቹ ሲነግሩኝ ሳሎናቸው መሃል ራሴን ስቼ መውደቄ ለሱ ምኑ ነበር? ከዛሬ ነገ መጥቶ ይቅርታ ይጠይቀኛል ብዬ ስጠብቀው መች ለአፍታ ትውስ አልኩት?
አባቴ ከሞተ በኋላ በየቀኑ ሳይደክመኝ ስለሱ አስብ ነበር። ……ቢያንስ ለማፅፅናናት ይደውልልኛል ፣ መከፋቴን ሲያይ አያስችለውም፣ እንባዬን ከሚያይ ከየትኛውም ዓለም ክፍል ይመጣልኛል፣ ከቂጣሟ አሮጊት ሚስቱ እንደምበልጥበት ይነግረኛል…… ሳኮርፈው ሁሌ ያደርግ እንደነበረው የታችኛው ከንፈሬን ብቻ እየደጋገመ ይስመኛል። …… ሲጣፍጠኝ በደሉ ይሸረፍብኛል። …… እጆቹ ወገቤን አልፈው ሲወርዱ ምን አድርጎኝ እንደነበር ይጠፋብኛል። …… ሰውነቱ ሰውነቴን ተጭኖ ሲዘልቀኝ እንኳን የአሮጊቷ ቂጥ ትዝ ሊለኝ ሰማይ በቂጡ ከምድር ቢጋጭ ጉዳዬ አይሆንም…… ከዛ የኔ ብቻ አደርገዋለሁ።…… እያልኩ አስብ ነበር።
ተስፋ ቆርጬ እስክደነዝዝ እሱ የት ነበር?

"ውዴ? እባክሽ ሁሉንም ነገር ያደረግኩት ላንቺ ስል ነበር።" ብሎ ‘አፌዘ‘
እንድናርፍበት የተከራየሁትን ሆቴል ቁልፍ ወርውሬለት ሊቀበለው የመጣውን የሆቴሉን መኪና ጠቁሜው በእግሬም በሃሳቤም ወደተውኩት ኑሮ ተራመድኩ። …… እንደማገባ የነገርኳት እናቴ ፣ ‘ልጄ ልታገባ ነው ግን ሚስጥር ነው‘ ብላ እናቴ የነገረቻቸው ቁጥር አልባ የማውቃቸው ሰወች፣ ከሀገር በመውጣት ስንድት ሰበብ የገተርኩት ኑሮዬ፣ ማንነቱን ለማያውቀው ሰው ጦሽ ያለው ገልቱ ልቤ፣ አርቄ ከሰቀልኩበት የተፈጠፈጠው ከሀገር የመውጣት ህልሜ፣ አከታትዬ የምወልዳቸው ድቅል ሁለት ወንድ ልጆቼ፣ ለእናቴ የምሰራላት ቪላ ቤት ………… የቧቸርኩባቸው ቅዠቶቼ ናቸው። ስነቃ የበነኑ። …… ለካንስ በቅዠት መፈንጠዙ አይከብድም። …… ቅዠቱን ማቆምም ብዙ አያታግልም። …… ወደ እውነታው መመለሱ ነው እብደት። …… ……
………
……
መውደድን ከኋላዬ ትቼው ከሚታገለኝ እንባዬ ጋር ግብ ግብ ገጥሜ ወደ ቤቴ መጓዝ ጀመርኩ። ……
👉🏽👉🏽 አልጨረስንም👈🏽👈🏽

@wegoch
@wegoch
@paappii
ከአቡሻ ጣሪያ ስር !
ትዝ ይለኛል ታላቅ እህቴ በጩኸት ግቢውን ስትደባልቀው ! “ኡ ኡ እማዬ ነይ ጉድሽን እይ” ነው ያለቻት ።
የምን ጉድ መጣ ደግሞ ። እኛ ቤት ከወር ቀለብ እኩል የማይጠፋ ጉድ የሚባል ሌላ የሚዘጋጅ አስቤዛ አለን ።
የጉዳችን ምንጮች ብዙ ቢሆኑም ዘጠና በመቶዎቹ ግን ከታናሽ ወንድማችን አቡሻ ክፍል የሚሰሙ ተዓምራት ናቸው።
ታናሽ ወንድሜ አቡሻ በመሀል አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በለሊት ተነስቶ ነብር ሊበላኝ ነው ብሎ ሲቀውጠው የነበረ የጉድ ማህደራችን ነው ። አቤት በሰዓቱ የነበረ የእናቴ ድንጋጤ ! እንዴት ከመኝታዋ እንደተነሳች ፣ ከመቼው ጋቢዋን ከበላይ እንደደረበች ሳናውቅ ከመቅፅበት አቡሻ ክፍል ተገኘች ።
ሌሎቻችን አቡሻ ባመሸበት እዳ እኛ ለምን በነብር እንበላ በሚል ፍርሀት ሁኔታውን በሳሎናችን በር በኩል ነበር ስንከታተል የነበረው ። በዛ ክፉ ሰዓት የእናትነት እና የእህትነት ድንበር ላይ የምትሰመረው ብቸኛ ቀጭን መስመር ለአይን ጎልታ መታየት ጀመረች። በርግጥ በወንድም እና ወንድም መሀከል መስመር መኖሩ አይን ላለው ሰው አይደለም ማየት ለተሳነውም በዳበሰ ለመለየት ያስችላል ። እናትና እህትነት መሀከል ግን መቀራረብ አለ ። እናት ለልጅዋ የምታስበውን አቅራቢያ እህት ለወንድሟ ታስባለች። እናት ልጇን የምትወደው አንድ ኪሎ ቢሆን እህት ሩብ ቀረሽ ለኪሎውን ያህል ወንድሟን ትወዳለች ። ብዙውን ጊዜ በእናትነት እና በመልካም እህትነት መሀከል ያለውን ልዩነትም አጥርቶ ለማየት የሚቸግርበት ወቅቶች አሉ። ስንቱ እህት ነው ለወንድሙ ከእናትነት በላይ ዋጋ ሲከፍል የሚኖረው ?ዛሬ ግን ያቺ ድንበር ተለየች ። አቡሻ ነብር ሊበላኝ ነው ብሎ ግቢውን ሲቀውጠው ሁለት ወዳጆቹ ደንግጠው ተነስተው ነበር። እህታችንም እናታችንም የአቡሻን አሰቃቂ ጩኸት ሰምተው ባንነዋል ። ልዩነቱ የመጣው የሳሎኑን በር ከፍቶ አቡሻን ለማዳን በሚደረገው ተጋድሎ ላይ ነበር ። እህቴ ወንድሟን ለመታደግ ከድርጊት ይልቅ ሳሎን ተቀምጣ ፀሎት ማድረጉን መርጣለች ። እናቴ ግን የሳሎኑን በር በዛ አስፈሪ ለሊት ከፍታ አቡሻ ክፍል በር ላይ ተገኘች ።
አቡሻ አየሁት ብሎ የሚጮኸው ነብር ልጇን ከሚነካው ይልቅ እሷን አጋድሞ እንደ ፍየል ቢቆረጣጥማት ትመርታጣለች ። የእናትነት ተፈጥሮአዊ ፍቅር እና ስስቱ በእንደዚህ ያለ ክፉ ቀናት ወለል ብሎ ይገለፃል ። እኔ አቡሻ ይተርፍ ዘንድ መልካም ምኞቴን ከማሳደር የዘለለ ለፀሎቱም ለድርጊቱም ተሳንፌ ቆሜ ትዕይንቱን እከታተላለሁ። “የታል ነብር ?” “ይኸው እማ ዬ ወይኔ ተበልቼልሽ ነበር “ አቡሽ ፊት ላይ የሚታየው ድንጋጤ ለተመልካች ሁሉ ሳይቀር ስጋትን ያጋባል ። እናቴ ልጄ አበደ መሰለኝ ብላ እንባዎቿ ተንዠቀዠቁ ። እኔ ይሄ ሀሽሻም ወንድሜ ምናምኑን አጫጭሶ መጥቶ አልጋ ልብሱ ላይ የነበረው የነብር ምስል እውነተኛው ነብር መስሎት እንደሚጮህ ግን ቀድሞውኑ ጠርጥሬ ነበር 🙂

@wegoch
@wegoch
@paappii

#mikael aschenaki
🏞 ከእንግዲህ #ስጦታ ምን እሰጣለው ብለው መጨናነቅ የለም። ለሚወዱት ሰው በመረጡት 𝕤𝕚𝕫𝕖 #ቆዳ_ላይ እንዲሁም #ሸራ(𝕔𝕒𝕟𝕧𝕒𝕤) ላይ ሥዕል አስለው ማቅረብ ብቻ ነው።


🟢#ለምርቃት 👨‍🎓

🔵#ለሰርግ 👰🤵

🔴#ለፍቅረኛዎ 👩‍❤️‍👨

እና ለወዳጅ ዘመዶ👨‍👩‍👧‍👦 በተመጣጣኝ 💵ዋጋ አስለው ያበርክቱ ።


🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂
ለበለጠ መረጃ
📱Inbox @gebriel_19
📱0984740577

@𝕤𝕖𝕚𝕝𝕠𝕔𝕙
@𝕤𝕖𝕚𝕝𝕠𝕔𝕙
ርዕስ አልባ ( አንዳንድ ድርሰቶች ከህይወታችን ርዕስ አልባነትን ይወርሳሉ)
ለሁሉም ሰው እንደምመስለው የዋህ ፤ አፍቃሪ እና ሚስኪን ብቻ አልነበርኩም ።
እንደማንኛዋም ሰው ትንሽ እብሪት እና ድድብና አላጣሁም ። እርሱ ግን ካለ ምክንያት ብቻ ሳይሆን ከነ እንከኔ ይወደኝ ነበር ፤ ባይወደኝ ቀንድ ያጠረኝ
አጋንንት መሆኔን እያወቀ ክንፍ ማቆጥቆጥ እንደቀራት መልዓክ አያየኝም ነበር ፤ ባይወደኝ የትም እንደምረግጥ የትም እንደምጋደም እያወቀ እንኳን ገላዬን ለማቀፍ አይቸኩልም ነበር ፤ ባይወደኝ ስመረቅን የማወራለትን ያን ሁሉ ዝባዝንኬ አፉን ከፍቶ አይን አይኔን እያዬ አይሰማኝም ነበር ። አሁን ከጊዜያት በኋላ ለምን እንደተራራቅን አስባለሁ ። ከእርሱ ያራቀኝ ሃጢያቴ
ነው። የዋህ አማኝነቱ ፤ በጭንቅላቱ ዙሪያ ቀለበት ሰርቶ አናቱ ላይ የሚውል
ቅዱስነቱ ፊት ለፊት መቆም ያቃተው ስራዬ ከእርሱ እንዳራቀኝ አውቃለሁ ።
ተቃቅፈን ባደርንባቸው ቀናት ጀርባውን ስዳብስ ስለምነካቸው ጤፍ መሰል
ትንንሽ ደቃቅ ሽፍታዎች በጠራራ ሌሊት ከእንቅልፌ ነቅቼ አስባለሁ ፤ ለስላሳ
ጀርባው ላይ የፈሰሱ ደቃቃ ጉጠቶች ይናፍቁኛል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር ፤
ግን ከአመታት በኋላ የጣቴ ጫፎች ሊዳስሱት ሲጓጉ ተሰማኝ። የተለየሁት በየቀኑ " የት ነሽ? " ይለኝ ስለነበር ፤ በየምሽቱ " ሰፈርሽ መጥቻለሁ ናፍቀሽኝ ነው አይቼሽ ልመለስ " ስለሚለኝ ነው ብል የሚያምነኝ እንደሌለ አውቃለሁ ። ግን በሰጠኝ ክብር ልክ ክብር የጠላብኝ ስለነበርኩ ለ "የት ነሽ? " ጥያቄው " ምን አገባህ " ለ " ከቤት ወጥተሽ ልይሽ" ልመናው " እንዴት ብትንቀኝ ነው በዚ ሰአት" መልሴ ሆነ ። አሁን ከረፈደ ታዲያ ምን ገባኝ? የፍቅር አንደኛ ደረጃ ጠላት እብሪት መሆኑ .......ሊገፋኝ ሲገባ ስላቀፈኝ ሊንቀኝ ሲገባ ስላከበረኝ እብሪቴ ቅጥ አጣ ። በሚሰጠኝ ፍቅር ልክ " የግል ንብረቱ አደረገኝ እንዴ?" የሚል እልህ ውስጥ ገብቼ ያከበረው ገላዬን ለገዛ ጓደኛው አሳልፌ ሰጠሁ። በማንአብኝነት 'በኩራት' ያደረኩት ነገር
የኋላ የኋላ በሃፍረት እና በፀፀት የሚያሸማቅቀኝ የሚሆን አልመሰለኝም ነበር ። ባደረኩት አፍሬ ለአመታት ከእርሱ ጠፋሁ ። ከብዙ ጊዜ በኋላ ያገኘሁት ከአንዱ ጋር አድሬ ከቤቱ ወጥቼ ወደ ሰፈሬ ስሄድ የያዝኩት ባጃጅ ውስጥ ነበር ። ሰላም ከተባባልን በኋላ ብዙም ሳይሄድ ደርሻለሁ ብሎ ከባጃጁ ወረደ ። እርሱ ከሄደ በኋላ እኩይ ስራዬን እና ዱርዬነቴን እግዜር ሊያስታውሰኝ ሲጥር በጧት ከእንቅልፉ ቀስቅሶ የማስቆመው ባጃጅ ውስጥ እንዳስቀመጠው አሰበኩ። የሆነ አንድ ቀን ተደዋውለን ተገናኘን። የምር ናፍቆኝ ነበር። ራቁቱን አቅፌው ጀርባው ላይ ያሉ እነዛን ነጠብጣቦችን ስዳስስ ሃዘንና ፀፀት ተባብረው በልቤ ሲያርፉ ተሰማኝ ። እንባ ስራዬን ባያጥብልኝም ማልቀስ ግን አምሮኝ ፤ አልቅሼም ነበር ቢሆንም በእንባዬ መሃል ልጠይቀው የሚገባኝን ይቅርታ አልጠየኩትም ፤ ለምን ይሄን ያህል እንደሚራራልኝ አልጠየኩትም ። ለምን በመልካምነቱ ሊቀጣኝ እንደሚያሰቃየኝ ፤ ለምን ሁሌ በፀጥታ እንደሚያቅፈኝ አልጠየቅኩትም ። በእንዲህ ያለው ጧት ድንገት ትዝ ሲለኝ ተማፅኖው ልብ የሚበላ Brett
Youngን እየሰማሁ የምጠይቀው ይቅርታ ውስጥ ያለ ምህረት ሰላም
እንደሚሰጠኝ አስባለሁ ።
" If you made up your mind, then make it
But make this fast
If you ever loved me
Have mercy "
ግን የቀደመ የአልፍላነት ድፍረቴ ዛሬ ይቅርታ ለመጠየቅ እንኳን የሚያስችል
እንጥፍጣፊ አቅም ስላልተወልኝ፤ በናፈቀኝ ቁጥር በዘፋኙ አሳዛኝ ድምፅ ውስጥ የራሴን ተማፅኖ ንፋስ ሽው የሚልበትን ልቤን ደግፌ አዳምጣለሁ ።

@wegoch
@wegoch
@paappii

#በኤልሳ ሙሉጌታ
#ቀበሮ_ገዳይ
( በእውቀቱ ስዩም)
.
ድሮ ልጅ እያለን ደብረማርቆስ ውስጥ ቀበሮ ገዳይ የሚባል የመቶ ሜትር ሩዋጭ ነበር፤እናቱ ያወጣችለትን ስም የሚያውቅ የለም፤ ከለታት አንድ ቀን ፤ቀበሮ በሩጫ አባርሮ ጅራቱን ይዞ በርግጫ ደቅድቆ ገድሉዋል እየተባለ ይወራለት ነበር፤ ደብረማርቆስ ስቴድየም ውስጥ ውድድር ላይ የሚያደርገው ነገር ትዝ ይለኛል፤ ገና ሩጫው ሊጀመር ሲል ከጎረቤት አውራጃ ከመጡ ተወዳዳሪዎች ተነጥሎ ወደ ደጋፊዎቹ ዞሮ እጁን ያውለበልባል! ረጅም ስለነበረ የምስራቅ ጎጃምን ሰማይ በፎጣ የሚወለውል ነው እሚመስል! ከዚያ ፤በአክሮባት ወደ ሁዋላ ይገለባበጣል ! ያባ ታምሩ ወፍጮ መዘውር ራሱ እንደዛ አይገላበጥም፤ ይቀጥልና ወደ ሌሎች ተወዳዳሪዎች ዞሮ ይገረምማቸዋል፤ “ አሁን ቢቸግር እንጂ እናንተን ከመሰለ ውርጋጦች ጋር መሽቀዳደም ነበረብኝ “ የሚል ይመስላል፤
ልክ ሩጫ ሲጀመር ቀድሞ ይወጣና ይፈተለካል፤ በጣም ከመፍጠኑ የተነሳ ፎቶግራፍ ለማንሳት እንኩዋን አይመችም! ሁለት ካሜራማኖች ከጎ ከጎኑ ተከትለን ፎቶ እናነሳለን ብለው በልብ ድካም ሞተዋል ባጭሩ፤ ልጁ ቀበሮ ገዳይ ብቻ ሳይሆን ጋዜጠኛ ገዳይም ነበር! ግን ችግሩ ምን መሰላችሁ? ቀበሮ ገዳይ ሩጫውን ለማጠናቀቀ አስር ሜትር ሲቀረው አቁዋርጦ ይወጣና ተመልካቹን ከሩዋጮች እሚለየውን የሽቦው አጥር ተደግፎ ያስመልሳል! እና አሁን ሳየው በህይወታችን ውስጥ ያሉት ብዙ ነገሮች እንደ ቀበሮ ገዳይ እንጂ እንደ ሃይሌ አይደሉም ፤ ነገሮችን ስንጀምርና ያለን ጉልበት እስከመጨረሻው አይቆየንም ፤ ኮረና የጀመረ ሰሞን፤ የዳንቴል ማስክ ሰርቼ በነፍስ ወከፍ ለህዝብ ካላዳረስኩ ብላ ስትገለገል የነበረች ሴትዮ፤ ዛሬ ዶክተር ሊድያ ገፅ ስር “ ይሄ ነገር ዛሬም አለ እንዴ ?’ የሚል ኮመንት ታስቀምጣለች፤ ጦርነትም እንዲሁ ነው፤ ውጊያ የተጀመረ ሰሞን የወኔ ችግር አይኖርም ባንድ ቀን ውጊያ ሁለት የጠላት ወታደር ገድለህ ፤ አምስት ማርከህ ሶስቱን ደግሞ እንዳይለመዳችሁ ብለህ ራሳቸውን ዳብሰህ ታሰናብታለህ፤ ጦርነቱ ካመት በላይ የሚቀጥል ከሆነ ግን ሌላ ጣጣ ይመጣል ፤ ወኔ በወይኔ ይተካል፤ በጥላሁን ገሰሰ ዘፈን ቀርቶ፤ ቂጥህን ራሱ በሳንጃ ብትወጋ ወደፊት መንቀሳቀስ ታቆማለህ፤ በሳንጃ የተወጋ ቂጥህን እንደ ሃብሃብ ፈንክተህ ጥለህ ፤ የተረፈ ቂጥህን አስከትለህ፤ ወደ ቤትህ መመለስ ነው የምትፈልገው!
የፍቅርም ነገር እንደዚያ ይመስለኛል፤ ሲጀምር በነበረው ጉልበት የሚቀጥል ፍቅር ያለን ሰዎች የታደልን ነን ንዋይ ደበበ አፍላ ሳለ፤ ባንድ ብርጌድ ማሲንቆ መቺ ታጅቦ የሚዘፍነው ዘፈን ነበር” ያላንቺ እኖራለሁ እኔ መች ወጣኝ’ ይላል፤ መላው የሰው ዘር ለኦክስጂን ሲጠቀምበት የኖረውን አገላለፅ ነው ንዋይ ለፍቅረኛው የሰጠው፤
ንዋይ በሌላ ዘፈን
“አትጥፊ በብዙ ከልቤ እንዳትወጭ
እንደዛም ስላልኩሽ ቶሎ ቶሎ አትምጭ”
ብሎ አረፈ፤
የመጀመርያው አገላለፅ ፍቅር የተጀመረ ሰሞን የነበረውን ስሜት ሲያንፀባርቅ ፤ ሁለተኛው ግጥም የሰነበተ ፍቅርን ይወክላል
.
.
@wegoch
@wegoch
★★ የባል ገበያ ★★
(ክፍል አምስት)
ሜሪ ፈለቀ

እንደሰፈሬ ልጆች ሲሊፐሬ ሲበጠስ በሚስማር አስይዤ ተጫምቼ ፣ ቄስ ትምህርት ቤት እስክገባ ፓንት ሳልታጠቅ፣ በባለኮፍያው ሚስማር ተበስቶ በሚስማሩ የተከደነ የፀጉር ቅባት ተቀብቼ፣ የተሰጣ የሽሮ ስጥ ሰርቄ ትምህርት ቤት እየቆረጠምኩ፣ የአባዬ ካልሲ አውራ ጣቱጋ ሲቀደድ ሰፍቼለት፣ እታባ ጎመን በጎድን የቀቀለች ቀን አመትበዓል እየመሰለኝ…… ……… ያደግኩኝ ነጭ የድሃ ልጅ ነኝ። ……… ለሰወች የምንሰጠው በፍቅር የታጨቀ ልብ እንጂ በገንዘብ የታጨቀ ኪስ አልነበረንም። ……
አስረኛ ክፍል ከምማርበት ከትምህርት ጉብዝናዬ እኩል በረብሻ ከምታወቅበት የመንግስት ትምህርት ቤቴ ፊት ለፊት …… የመውደድ ቤተሰቦች ለእይታ ርቆ አንጋጠው ወደ ላይ የሚያዩት ቤታቸውን ገዝተው የገቡ ሰሞን ከትምህርት ቤት ስወጣ አንደኛው ፎቅ በረንዳቸው ላይ ወንበር ላይ ተቀምጦ ተማሪ እየተንጫጫ ወደቤቱ ሲሄድ ያያል። አየሁት። በሚቀጥሉት ቀናት …… አየዋለሁ። ለጓደኞቼ አሳያቸዋለሁ።

…… ከሶስት ጓደኞቼ ጋር በሽቅድድም ‘ወጣ‘ ‘ያውና‘ ‘ገባልሽ‘ እያሉኝ እናየዋለን። …… እንደሚያየን እናውቃለን። ስንወጣ ካጣነው እንጠብቀዋለን።…… በአይን ፍቅር የተያዝኩት እኔ መሆኔን አምኜ ስለተናገርኩ እንጂ ሳያውቁት ሁሉም ካላዩት ከኔ የባሰ ይከፋቸዋል። …… ለሁለት ወራት አብረውኝ ጠብቀው እያዩት በአይን ፍቅር ወድቀዋል። …… ተቧድነን እንደወደድነው የማውቀው ቆይቶ በእርሱ ምክኒያት ሲያኮርፉኝ ነበር።

ለአራት ቀናት ድራሹ ጠፋ!! …… ብንጠብቀው ብቅ አልል አለ። …… እየከፋን ወደየቤታችን ገባን። ጠብቄ ላየው ወስኜ ተመልሼ መጣሁ። …… በሩጋ ከሴት ጋር እየሳቀ ሲያወራ ደረስኩኝ። …… እያመነታሁ ላልፋቸው ስቀርብ ጓደኛዬ መሆኗን አየሁ።…… እንደሷ ላስቀው መሞከር የማይረባ ፉክክር መሆኑ ወዲያው ገባኝ።ቅናት በየደምስሬ ሲሯሯጥ ሰውነቴ አብጦ የሚፈነዳ መሰለኝ።…… ምንም ቢፈጠር በዛ ቅፅበት ከሚሰማኝ መንደድና መበሳጨት እንደማይብስ አወቅኩ። ……

…… በመሃከላቸው ባለው ጠባብ ርቀት መሃል ራሴን አገኘሁት።…… ለማሰቢያ የሚሆነው ሽራፊ ሰከንድ ሳላባክን ራሴን እንኳን ባስገረመኝ ድፍረት የማርን ጥፍጥና የሚሽር ከንፈሩን ጎረስኩት። …… የቀኝ እጁ በወገቤ ዙሪያ አልፎ ወደራሱ ሲያጣብቀኝ… የጓደኛዬ ኮቴ እየራቀ ሲሰማኝ… መሳሳማችንን ስንገታ ማፈሬ ሲመጣብኝ…… ስሙንና የዩንቨርስቲ አንደኛ ዓመት አርክቴክቸር ተማሪ መሆኑን ሲነግረኝ……በዛ ሰሞን የጠፋው ፈተና ስለነበር ዶርም እያደረ መሆኑን ሲያስረዳኝ…… እኔን ለማዋራት ቀን ሲጠብቅ እንደገላገልኩት እየነገረኝ ወደ ቤቴ ሲሸኘኝ…… መለያየት አቅቶን እየተሰነባበትን ስንሳሳም ደሞ ስንሰነባበት ደሞ ስንሳሳም…… የፍቅር ታሪኬ ከመውደድ ጋር እንደተገመደ እርግጠኛ ሆንኩ።…………

ለምናልባቱ ለራሴ ያስቀረሁት አንድም ማንነት ሳይቀረኝ በመላ አካሌና በመላ ነፍሴ በፍቅር ወደቅኩለት። …… የየዕለት የአይኔ ሱስ፣ የልቤ ጌታ፣ የደስታ ስካሬ፣ የህልውናዬ ትርጉም…… በእያንዳንዱ የወደፊት እርምጃዬ መውደድ እየገዘፈ መዓት አክሎ ውስጤ ተቆለለ። …… ‘እኔ‘ ያለእርሱ ጠፋሁ። …… ከአመት በኋላ የራሱ የሆነን ነገር እንደሰጠሁት እየተሰማኝ ለማንም ያልተከፈቱ ጭኖቼን ከፍቼ የሰይጣን ይሁን የእግዜር ማረጋገጥ ወደማልችለው ሽቅርቅር ግዛት አብሬው ተሳፈርኩ።………

በብዙ መጎራበጦች ውስጥ እኔ እንደምበልጥበት አሳምኖኛል። …… ቤተሰቦቹ ክብራቸውን የማልመጥን አይነት ሴት መሆኔን ሲነግሩት ክብሩ እኔ መሆኔን ነግሯቸው ተጎራብጧል። …… አባቴ ለብዙ ነገር የሚጠብቃት ልጁን ስላባለገበት ጠብቆ ሲያንቀው ፣ እግሩ ስር ወድቆ በእንባ ህይወቱ እኔ እንደሆንኩ አሳምኖ እስከስኬቴ ጫፍ እንደሚገፋኝ ቃል ገብቶለታል። …… ደሳሳ ቤታችን ቤቱ ሆነ። …… አባዬና እታባ ከእኔ ለይተው የማያዩት ልጃቸው ሆነ።……

መውደድ
ቁም ነገር አጫውቶኝ የእውቀቱ አድማስ እያስደመመኝ አፌን ከፍቼ የምሰማው፣
ነገሮችን ባየ ቅፅበት ቀልድ ፈጥሮ የጉንጮቼ ጡንቻዎች እስኪዝሉ የሚያስቀኝ፣
ሲጠነቀቅልኝና ሲንከባከበኝ መላዕክት እቅፍ ውስጥ ሆኜ የምቀብጥ እንዲመስለኝ የሚያደርገኝ፣
ፍቅር ሲሰጠኝ ነፍሴን የፍቅር እንጉርጉሮ የሚያዜማት፣
ሲስመኝ ነፍሴን ብሰጠው እስካልሳሳ ድረስ የምወደው አባቴን የሚያስረሳኝ፣
እጆቹ ከእንብርቴ በታች ሲያልፉ እግዜርንም ሰይጣንንም ምድርንም ሰማይንም አስረስቶ ትንፋሼን የሚያቆማት፣
የሰው ልጅ በዛ መጠን እንዴት ፍፁም መሆን እንደሚችል በማይታመን ሁኔታ መውደድ እንደዛ ሆኖ እኔም ዩንቨርስቲ ገባሁ እሱም ተመረቀ። …… 5 እንከን አልባ ዓመታት አለፉን።


ተጋብተን ልንኖር እቅድ እያወጣን ሳለ አባዬ ታመመ። …… ከዚህ በኋላ የሆነው ሁሉ ድርሰቱን ጨርሶ ለመገላገል መጨረሻውን በአጫጭር አረፍተነገሮች እንደሚነዳ ብሽቅ ደራሲ በጣም ፈጣን ነበር።…… አባዬ ከሀገር ውጪ ወጥቶ መታከም ነበረበት። …… የሰፈር ሰው፣ ዘመድ አዝማድ፣ ጓደኛ፣ ጎረቤት… … የሚችለውን ያህል ብር አዋጣ። እቁብም እድርም ተባለ። …… የሚያስፈልገው ገንዘብ መጠን ንቅንቅ አልል አለ። ……
መውደድ ቤተሰቦቹም ዘመዶቹንም ቢያንስ እንዲያበድሩት ጠይቋቸው ነበር። …… ከኔ ጋር በነበረው ግንኙነት ቀድሞውኑም ደስተኞች ስላልነበሩ አላገጡበት።…… አባዬ ንጭንጩ እየበዛ መጣ…… እታባም በባሏ ሰቀቀን ታመመች። ገና ድክ ድክ የሚለው ታናሽ ወንድሜ ሰውነቱ ከሳ። ከትምህርት ቤት ይልቅ እቤት ማሳለፍ ጀመርኩ። … … ከስራ መልስ እቤት መጥቶ አባዬን ሳያየው የማይሄድ የነበረው መውደድ ለቀናት ሳይመጣ ቀረ። …… ደውሎ ስለአባዬ ከጠየቀኝ በኋላ ወዲያው ስልኩን ይዘጋዋል። …… ግራ ቢያጋባኝም እቤት ከነበረብኝ ጫና ጋር ምንም ማሰብ አልቻልኩም።

አንድም ናፍቆት ውስጤን ሲቆላው ሁለትም ሸክሜን ላጋራው ስራ ቦታው ሄድኩ። …… እሱ ወንበሩ ላይ ተቀምጦ ለኔ ጠረጴዛው ላይ ተንሰራፍቶ የተዘፈዘፈ ትልቅ ቂጧ ጎልቶ የሚታየኝ ሴት ከፊትለፊቱ በእግሮቹ መሃል ጠረጴዛው ላይ ተቀምጣ የእድሜዋ ያልሆነ ልዘት ትለዛለች።…… ግራ ተጋብቼ ቆሜ ሳያቸው አየኝ። ዘሎ ከወንበሩ ተነሳ። …… ፊቷን ሳየው አስታወስኳት።

ከአመት በፊት ‘አንቺን የሚያክል ቂጥ ያላት የአባቴ ጀለስ ከውጪ መጥታ እቤታችን አርፋለች።‘ ብሎ ያሳየኝ ሴትዮ ናት። ለመውደድ ከሀገር እንዲወጣ በርሷ በኩል ፕሮሰስ ተጀምሮለት ነበር። …… የእሷ የ‘ማነች?‘ አስተያየት ካየሁት የጠለቀ ግንኙነት እንዳላቸው ነገረኝ። …… እጁን ይዛ በቆመበት አስቀረችው። አልታገላትም። …… ጥፋት ሲያጠፋ እንደሚያየኝ ባለበት ቆሞ በልምምጥ ያየኛል። ማመን አልፈለግኩም።

" ጌትዬ ምንድነው? ማናት? ምን እያደረግክ ነው?" አልኩት ምንም ቢለኝ ከአይኔም ከስሜቴም በላይ የእርሱን ቃል አምነዋለሁና እንዲያስተባብልልኝ ጠበቅኩ።…… ዝም አለኝ።

"ጌትዬ ንረገኝ? ያሰብሽው ልክ አይደለም በለኝ?" ከየት መጣ ያላልኩት እንባዬ ከቃላቱ ጋር ፈሰሰ። አይኖቼን ሽሽት ፊቱን አዙሮ ዝም አለኝ።……
……………
…………
👉🏽አሁንም አልጨረስንም👈🏽

@wegoch
@wegoch
@paappii
★★ የባል ገበያ ★★
(ክፍል ስድስት)
ሜሪ ፈለቀ

"ጌትዬ ንረገኝ? ያሰብሽው ልክ አይደለም በለኝ?" ከየት መጣ ያላልኩት እንባዬ ከቃላቱ ጋር ፈሰሰ። አይኖቼን ሽሽት ፊቱን አዙሮ ዝም አለኝ።……

"ኦ…ህ ማ…ይ ዲ…ር ጋ…ድ! አዲሱ(የመውደድ አባት ነው) ያወራልኝ ልጅ እንዳትሆን?" መውደድን ነው የምትጠይቀው ቀጠል አድርጋ "አባቷ ሊሞት ነገር ነው ካልተሳሳትኩ?" እሱን እየጠየቀችው ቆሻሻ እንዳየ ሰው በመፀየፍ ስታየኝ ባንቃት ደስ ባለኝ። …… ክንፏን ያጣች ቢራቢሮ ሆኛለሁ። የኔ መውደድ እንዲህ ስንጓጠጥ ሰምቶ ዝም አይልም። ……

ማንም ቢሆን ዘሎ ይከመርበት ነበር። …… ትቻቸው ስወጣ አልተከተለኝም። የሴትየዋ ዝገት ዝገት የሚል ሳቅ ተከትሎኛል። …… የማውቀው ሁሉ ነገር ጠፋብኝ…… የማምነው ነገር ሁሉ ተንኮታኮተ… የማስበው ነገር አጣሁ…… አላለቀስኩም። ግራ ገብቶኛል። ……

እቤት ስደርስ "እመቤቴ ሁሉንም ነገር በቅርቡ አስረዳሻለሁ። በነፍሴ ልክ አፈቅርሻለሁ።" የሚል መልዕክት ደረሰኝ ምንም ማመዛዘን አልቻልኩም። መናደድም አቃተኝ። …… ጠበቅኩት። …… እራሴን ያለእርሱ ማሰብ በፍፁም አልቻልኩም። …… መጥቶ የሆነ ምክኒያት እንዲነግረኝ ጠበቅኩት። እንዳምነው…… ምንም እንዳልተፈጠረ ረስተን አብሬው ልሆን…… የሴትየዋን ለዛ ያጣ ቅብጠት መርሳት አቃተኝ። ……

ልጆቿ ከሚያካክሉ ወንዶች ጋር የመውጣት ልክፍት እንዳለባት ስለርሷ የነገረኝን አስታወስኩ።
ከኔጋር የሚያብደውን የፍቅር እብደት ከሷ ጋር ሲያብደው ማሰብ ጨርቄን ሊያስጥለኝ ይደርሳል። … መውደድ ትልቅ ቂጥ ይወዳል። … ከኔ ጋር ፍቅር ስንሰራ እንደሚያደርገው ትልቅ ቂጧን ማየት በሚችልበት አቅጣጫ እያደረገ ሲሰራት አስባለሁ። ……

ግዙፍ ሰውነቱ ላይ ስትፈነጭበት እስላታለሁ። እሪሪሪሪሪሪ ማለት ያምረኛል። …… መስታወቱ ፊት እቆማለሁ። ዞሬ ኋላዬን አያለሁ። ከዛች የተረገመች አሮጊት ጋር መቀመጫዬን አወዳድራለሁ::

ቀናት አለፉ። …… አልመጣም። የአባዬን ደህንነት ለማረጋገጥ እንኳን እታባጋ ሆነ የሚደውለው። ……

ብዙም ባልራቀ ቀን ያቺን ሴትዮ ማግባቱን ስሰማ አዞረኝ። …… ከእርሱ ለማረጋገጥ እቤታቸው ስሄድ ጭራሽ ከሴትየዋ ጋር ከሃገር መውጣቱን ነገሩኝ። …… ራሴን ስቼ ወደቅኩ:: ጎመዘዘኝ ..... ቀኑም ማታውም አንድ ሆነብኝ:: ጨለማ !!

የማታ የዞረ ድምሩ እንዳለቀቀው ሰካራም ስደነባበር የአባዬ ነፍስ አባት ለአባዬ መታከሚያ የሚሆን ብር መገኘቱን አበሰሩን። ታክሞ ግን መዳን አልቻለም። ገንዘቡ በጊዜው አልደረሰለትም። …… ከወራት በኋላ እቤቱ ተመልሶ አረፈ። …… እታባ ከአባዬ ሞት በኋላ ባሰባት። …… ቤቷን ማስተዳደር ስላለባት አየታመመች ለመስራት ብትሞክርም ከአቅሟ በላይ ነበር።

ይህቺ አለም የሌላውን ውድቀት መጠቀሚያ የሚያደርጉ ብሽቅ ሰወች የሞሉባት ናት። …… እንደውም አንዳንዱ ሌላው ካልወደቀ ከፍታው ደስ አይለውም። …… ስኬቱን የሚለካው በራሱ ስኬት ሳይሆን በሌላው ውድቀት ነው። …… አባዬን ልጅህን ካልዳርክልኝ እያለ የሚነዘንዘው ታደሰ የሚባል ነጋዴ አጋጣሚውን ተጠቅሞ እቤታችንን ይደግፍ ነበር። …… አብሬሽ ካልተጋደምኩ ብሎ ሲታገለኝ በብርጭቆ እስከፈነከትኩት ቀን ድረስ። … …

ትምህርቴን እንደነገሩ እየተማርኩ።እስከጨርስ ስራ በተጨማሪ መስራት ነበረብኝ። አዲስ ቤት ተከራየን።

የአይኑን ብርሃን በቅርቡ እንዳጣ ሰው በእያንዳንዱ ቀኖቼ ውስጥ አስተካክዬ የማልረግጥ ደንባራ ሆንኩ። …… እየቆየ መውደድን ብቻ ሳይሆን ፍቅርን፣ እምነትን፣ እውነትን አርቄ ቀበርኳቸው። …… የእታባንና የሚያውቁኝን ሰወች ሁሉ "ለአንድ ወንድ ብለሽ ቆመሽ ልትቀሪ ነው" ንዝንዝ በድንዛዜ ባልፈውም ጥሎኝ ለመሄዱ በቂ ምክኒያት ሊሰጠኝ ያላከበረኝን ወንድ በልቤ ዙፋን ላይ እንደሾምኩት ማኖር ከአቅሜ በላይ ከባድ ነበር። ……



በየቀኑ መልስ የሌለው ጥያቄ እጠይቃለሁ። ለምን?
……
……
"የጉድ ሃገር ገንፎ እያደር ይፋጃል!" አሉ… …
ክህደቱ ሳያንሰኝ ‘ላንቺ ስል ነው‘ ይበለኝ? ላንቺ ስል ነው ማለት ምን ማለት ነው? … ለኔ ሲል ነው ፍቅራችንን ገድሎ የቀበረው? ላንቺ ስል ነው የከዳሁሽ፣ ላንቺ ስል ነው የተውኩሽ፣ ላንቺ ስል ነው ልብሽን ያነካከትኩት፣ ላንቺ ስል ነው በሌላ ሴት የቀየርኩሽ… ማለቱ ነው?… …
ጭራሽ ምክንያቱ ለይቅርታ ሚዛን መብቃቱን ለማመዛን እንድሰማው ሲጠይቀኝ ምላሱን እንኳን ድንቅፍ አላለውም። ………
……
…… በሁለቱም ተቃራኒ የስሜት ጠርዝ የሚቸነክረኝ ሰው ነው መውደድ። …… በፍቅርና በጥላቻ፣ በክብርና በውርደት፣ በፈንጠዝያና በመሪሪ ሀዘን፣ በስኬትና በውድቀት፣ በፍሰሃና በህመም…… …… በነዚህ ሁለት ፅንፎች የሚያላጋኝ እሱ ነው። ……
አሁን ላይ ምንምና ስለማንም ባልሰማ፣ ባላይ፣ ባላስብ…… የሆነ ዓለም ጠርዝ ላይ ብቻዬን ብሆን…… ‘እገሌ ምን ይለኛል?‘ ‘እገሌን ምን እለዋለሁ?‘ የማልልበት… … ቦታ ላይ ብገኝ? የሰው ልጅ እንደሰው ሰራሽ ኮምፒውተር ‘undo‘ ጠቋሚ ቢኖረው ምንነበር? …… የምመልሳቸው ብዙ ውድቀቶች ነበሩኝ።…………
ስልኬን አጠፋፍቼ ኡኡታዬን ማዳመጥ ጀመርኩ። ………

ስለ መውደድ ማሰብ በሸሸሁ ልክ ምላሴ ጨው ጨው እስኪለኝ ክህደቱን እንደገና ማሰብ ጀመርኩ።…… አንዳንዴ የምር ግን ምክኒያቱ ምን ነበር? እላለሁ። ……

"ውሻዬ? አባ ይፈልጉሻል።" አለችኝ እታባ ከውጪ እየገባች።

"አባ? አባ? ………ወደውስጥ አይገቡም እንዴ?"
የአባቴ የነፍስ አባት ነበሩ። ወጥቼ እንዲገቡ ብወተውታቸውም አልገባ አሉኝ።

…… እዚህ ቤት ከገባን በኋላ መጥተው አያውቁም። የዛሬ ጉብኝታቸው ገርሞኛል። … ለምን እንደፈለጉኝ ሲነግሩኝ የሆነ ቅዠት እየቃዠሁ መሰለኝ።………

"የዛኔ ለምንድነው ያልነገሩኝ?" ብዬ ጮህኩባቸው

"አትንገራት ብሎኝ ነበር። የሆነውን ሁሉ ያወቅኩት አሁን ነው።" በቆሙበት ትቻቸው ወደውስጥ ገባሁ። ያገኘሁትን ለብሼ ስወጣ ከእታባ ጋር ቆመው እያወሩ ነበር።

"አይደለም። አባዬን ለማዳን ብለህ አይደለም ከዛች ሴትዮ ጋር የሄድከው። እንደዛ ቢሆን ትነግረኝ ነበር።" የሆቴሉን ክፍል በር እንደከፈተልኝ እየደነፋሁ ገባሁ።

"ብነግርሽ እሺ ትዪኝ ነበር? ከአባትሽና ከእኔ ምረጪ ብልሽ ማናችንን ትመርጪ ነበር? አንቺን እዛ አጣብቂኝ ውስጥ መክተት ያመኝ ነበር። አባትሽን ለማዳን እኔን አይሁን እንጂ ምንም ትከፍዪ ነበር።" አለኝ እርግት ብሎ

👉🏽አልጨረስንም ደግሞ👈🏽

@wegoch
@wegoch
@paappii
🏞 ከእንግዲህ #ስጦታ ምን እሰጣለው ብለው መጨናነቅ የለም። ለሚወዱት ሰው በመረጡት 𝕤𝕚𝕫𝕖 #ቆዳ_ላይ እንዲሁም #ሸራ(𝕔𝕒𝕟𝕧𝕒𝕤) ላይ ሥዕል አስለው ማቅረብ ብቻ ነው።


🟢#ለምርቃት 👨‍🎓
🔵#ለሰርግ 👰🤵
🔴#ለፍቅረኛዎ 👩‍❤️‍👨

እና ለወዳጅ ዘመዶ👨‍👩‍👧‍👦 በተመጣጣኝ 💵ዋጋ አስለው ያበርክቱ ።


🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂
ለበለጠ መረጃ
📱Inbox @gebriel_19
📱0984740577

@𝕤𝕖𝕚𝕝𝕠𝕔𝕙
@𝕤𝕖𝕚𝕝𝕠𝕔𝕙
★★ የባል ገበያ ★★
(የመጨረሻ ክፍል)
ሜሪ ፈለቀ

"ብነግርሽ እሺ ትዪኝ ነበር? ከአባትሽና ከእኔ ምረጪ ብልሽ ማናችንን ትመርጪ ነበር? አንቺን እዛ አጣብቂኝ ውስጥ መክተት ያመኝ ነበር። አባትሽን ለማዳን እኔን አይሁን እንጂ ምንም ትከፍዪ ነበር።"

"አላምንህም!! ስትዋሸኝ ነው። አራት አመት ሙሉ… …"

"ይሄን የምንነጋገረው አባትሽ መትረፍ ችለው ቢሆን ኖሮ ትርጉሙ ይቀየር ነበር። ፍቅሬን ከፍዬም ላድናቸው አለመቻሌን ስሰማ ሁሉንም ጥዬ መጥቼ ነበር። …… አንቺ የት ነበርሽ? እ? ከታደሰ ጋር…… ረስተሽኝ ነበር።" የሚያወራው ግራ ገባኝ

"እኔ? እኔ ከታደሰ ጋር? በወራት ውስጥ ፍቅሬን እንኳን ብረሳ ክህደትህ የሰጠኝን ቁስል ድኜ ከሌላ ሰው ያውም ከታደሰ… … ከየት ያመጣኸው ወሬ ነው?"

ሸሚዙን ከፍቶ ደረቱ ላይ ያለ ጠባሳውን አሳየኝ። …… ለቅፅበት ደረቱን ሳይ ሙቀት ተሰማኝ።

"አይንሽን ለማየት ጓጉቼ እቤት ስደርስ እታባን አገኘኋት። …… ስታየኝ ፊቷ ላይ የነበረው ጥላቻ እንደዛ ትንሰፈሰፍልኝ የነበረችው እታባ አትመስልም። … አልፈረድኩባትም። … ከታደሰ ጋር ልትጋቢ መሆንሽን እና እንዳልበጠብጥሽ ነገረችኝ። …… ተስፋ ሳልቆርጥ ላገኝሽ ሞከርኩ። … ሁሌም ከታደሰ ጋር ነበርሽ። ከቁርስ እስከ እራት……"

(አየሁሽ ያለኝ ቦታ ሁሉ ነበርኩ። ነገር ግን እሱ እንዳሰበው ከታደሰ ጋር ፍቅር ጀምሬ አልነበረም።)

"ታደሰ መምጣቴን ሰምቶ ነበር ላገኝሽ እንዳልሞክር አስጠነቀቀኝ። … እንደማገኝሽ ነገርኩት። ባገኝሽ ሀሳብሽን አስቀይርሻለሁ ብዬ እርግጠኛ ነበርኩ:: ይሄንን እርሱ የሰጠኝ ጠባሳ ነው:: ( የደረቱን ጠባሳ በእጁ እያሳየኝ) የሆነ እለት ማታ እራት አብረሽው በልተሽ ሸኝቶሽ ሲመለስ እኔ ሰፈር ስጠብቅሽ ተገናኘን:: .... ታውቂያለሽ የማይረባ ነው:: በሰፈር ጎረምሳ ሊያስገድለኝ ነበር:: ከሆስፒታል ስወጣ ቤት ቀይራችኋል። እታባ ማንም የቀየራችሁትን ቤት ለእኔ እንዳያሳይ ሰፈር አስጠንቅቃቸዋለች።እመኚኝ ላገኝሽ ያልሞከርኩበት መንገድ አልነበረም። እኔ አንቺን በመፈለግ ስባዝን ሄለን(ቂጣሟ ሚስቱ) የኔን ልጅ ስትወልድ ህይወቷ አለፈ። … ቢያንስ ለልጄ ስል መመለስ ነበረብኝ። ተመለስኩ።………"

" ምኑም እውነት አይመስልም። …… ሰበብህ ነው። ያገኘሃት ጊዜ ይሄን ሁሉ ለእታባ ልትነግራት ትችል ነበር። ልታገኘኝ የምትችልበት አንድ መንገድ አታጣም ነበር። …" ያለው ሁሉ እውነት ባይሆን ነው ደስ የሚለኝ ……

"ሞክሬ ነበር። …… በሩን ይዛ ቆማ ነው እንድወጣላት የጮኸችብኝ። ……አስጠልቻት ነበር።"

ከዚህ በኋላ ያለውን በትክክል አልሰማሁትም። የሸሚዙን ቁልፍ ከፍቶ ያጋለጠውን ደረቱን ፈዝዤ አየዋለሁ። …… መንካት ያምረኛል። ……

አብሮት የሚሰራ ነጭ ሰውዬ ሳይቱ ላይ ያለውን ፎቶ እያሳየው ቆንጆ መሆኔን እንዲያረጋግጥለት የጠየቀው ጊዜ እንዳገኘኝ የነገረኝን ሰምቼዋለሁ። ……

እጄን ሲይዘኝ በርግጌ መነጨቅኩት። ትቼው ስከንፍ እቤት ሄድኩኝ።ማሰብ ስላቆምኩኝ እንጂ የምጠይቀው ጥያቄ ነበረኝ። …… እታባ ስነግራት በእንባና በፀፀት ልትፈነዳ ደረሰች። …… ምን እንደተሰማኝ አላውቅም።

ማልቀስም መሳቅም አልቻልኩም። ዝም ብቻ… …… እገባለሁ ፣ እወጣለሁ፣ እተኛለሁ ፣ እነሳለሁ፣ እቀመጣለሁ……… የማስበው ምን እንደሆነ አላውቅም እኮ ግን ወጥሬ እያሰብኩ ነው። ያወራውን ሁሉ መርሳት ፈልጋለሁ። …… የታችኛው ቁልፍ ብቻ ቀርቶ የከፈተውን ሸሚዙን አስባለሁ። ……… ባሰብኩት ቅፅበት የቀረውን ቁልፍ በጥሼ ራቁቱን ማየት ያምረኛል።…… ወደ ውጪ ስወጣ መሽቷል። …… ለሊቱ ቶሎ እንዲነጋ ይናፍቀኛል። ነገ አዲስ ነገር ይዞ መምጣቱን አላውቅም። …… ተኛሁ። ማንቀላፋት አቃተኝ። ……

ጀርባዬ እስኪቀላ ተገላበጥኩ።… … አንዱን ስይዝ አንዱን ስለቅ እኩለ ለሊት ሆነ። …… መጨረሻ ላይ ማሰብ የቻልኩት መውደድ እቅፍ ውስጥ መገኘት መፈለጌን ብቻ ሆነ። …… በዛ ለሊት የሆቴሉ በር ላይ መገኘቴን ማመን የቻለ አይመስልም። …… ሸሚዙን ቀይሮታል። የሆቴሉን ጋውን ለብሶ ነው የከፈተልኝ። ……

(አንባቢ ሆይ ከዚህ በኃላ ያለው ይቅርብህ🤣🤣)

_____አሁን ጨረስን_________

@wegoch
@wegoch
@paappii
"ተኣምር አልፈልግም !"
.
በህይወት መኖር ራሱ ድንቅና ተአምር ነውና እንደ አልዓዛር ሞቶ መነሳት አልፈልግም። ሞትም ሆነ ሕይወት እንደማንም እንደምንም አንዴ ይበቃኛል ።
አይ ድጋሚ በቃኝ ጌታዬ አሁን ኖሬ መጣሁ። ጨጓራዬ ተልጦ ሁለት ወር ማቅቄ መልሶ ፀጉር ሲያቆጠቁጥ" አጀብ አጀብ አጀብ " እያልኩ ማጨብጨብ አልፈልግም፡፡ ቀድሞውኑ የጨጓራዬ ስራ የሚደንቀኝ ነኝ ፡፡ ኩላሊቴስ ፈሳሽ የማጣራቱ ነገር ግርም ድንቅ ይለኛል። ደክሞት እስኪያደክመኝ አልጠብቅም ። እንዲሁ ለታምራቱ አሳቻ ሸለቆ ውስጥ ቀርቅሮ በእጁ የሚያወጣው ነገር አለ።
በትሬ ወደ እባብ እንዲቀየርልኝ በፍፁም አልፈልግም (እራሱ የፈርኦንን ልብ አደንድኖ ሲያበቃ) ። ከሩቅ ተሳልሞ መሞት እንጂ ወደማልገባባት ከተማ ፤ እሺ ብሎ የማይታዘዝ ህዝብ መሪ መሆንም አልፈልግም እንዳውም ። በረቂቅ ውስብስብ ገመዶቹ ሊተነተን የማይቻለው የአንጎላችን አሰራሩ ግሩም ድንቅ መሆኑን … የእጃችን አሻራችን ልዩ ልዩ መሆኑን እንደቀላል አይቼው አላውቅም … ስለዚህ የሰለለች እጅ ፈጥሮልኝ በተአምሩ መተርተር አልሻም ፡፡ ቀድሞውንስ እንደ ሸክላ በእጁ አይደለሁም ? ዓይኔ ብርሃንን ከጨለማ ለይቶ የማየቱ ነገር ብቻ ተአምር ሆኖ ሳለ ከመወለዴ ጀምሮ አይነስውር አድርጎኝ ለክብሩ ሲል ከእለታት አንድ ቀን እንዲያበራልኝ አልፈልግም። ገና ድሮ ተአምር ሳላይ የፀናች እጁን የተዘረጋች ክንዱን አምኛለሁ። እኔ የምፈልገው ዝም እና ዝግ ያለ መደበኛ ህይወት፡፡ ስብራት እና መጠገን የሌለበት ፡፡ እንደማንም እንደምንም … ከእሳት እና ከውሃ ከአንበሳ እና ከድብ … ከፈርኦን እና ከናቡከደነፆር … መሳደድ ፣ ማምለጥ ፣ መትረፍ የሌለበት፡፡ "ምን አለፋው?" እላለሁ ከዚህ ሁሉ በፊት ወድጄ ፈቅጄ አምኜዋለሁ፡፡ በሰላም መድረስ እየተቻለ ፤ ጭራሽ አለመሄድም እያለ 12 ሜትር ተምዘግዝጎ ወደ ገደል ከገባው መኪና ብቸኛ ተራፊ መሆን አልፈልግም ። ማእበሉን አለማስነሳት እየቻለ በውሃ ላይ ለምን ያራምደኛል? አልፈልግም ካልኩ አልፈልግም ወደ ተርሰሴስ ለምን ይሰደኛል? አሳ ነባሪ ሆድ ውስጥ ውሎ ጉበቱን ተንተርሶ ማደር አልፈልግም ... በፈቃደኝነት የሚሄዱ እልፍ ታዛዦች ሞልተውት የለ ? ሁለት አሳ ጠብሰን በአምስት እንጀራ ለአምስት ከበላንኮ አመስጋኝ ነኝ ። አንድ ቀበሌ ህዝብ ካልመገብን አንልም። ቀድሞ እጁን ሰጥቶ የተማረከ ሰው … እጁ ተጠምዝዞ ቂጡ በካልቾ እየተጠለዘ ወደ ተአምር ጎዳና ለምን ይመራል ? ዳሩ ማን ጠይቆት? የህይወትን መንገድ
መቼ ያስመርጥና …የማይመረመረውን ታላቅ ነገር እንዳደረገ አውቃለሁ "የታምራት አምላክ ታምረኛ ፤ ዳንኤል አምላክ ተአምረኛ …" ብዬም ዘምሬአለሁ ፡፡ ያለ ቅጣትና ሽልማት ሰጥ ለጥ ብዬ ስለምኖር የኔ አምላክ ግን ዝም ብሎ ቢተወኝ ደስ ይለኛል ። ሰዎች ሳይጠቋቆሙብኝ ‘’ያቺት ዓይኗ የበራላት … ከማይድን ደዌ የተፈወሰችው … በቀደም ሞታ ተነሳች የተባለችው’’ ሳይባባሉብኝ … በዝምታ በዝግታ በሰላም መኖር አይቻልም ወይ? ያለ ተአምር ማቅ ለብሼ አመድ ነስንሼ ንሰሃ እገባለሁ ኧረ ! በ25 ዓመት ልጅ መውለድ በራሱ ድንቅና ተአምር አይደለም ወይ ? አጥንት ሆዴ ውስጥ እንዴት እንደሚዋደድ ሳላውቅ መውለዴ ተአምር ነውኮ … እንደ ሳራ በ90 አመቴ ወልጄ "እልልል ተአምራቱ አያልቅም" ማለት አልፈልግም ። እንዴ 90 አመት መኖር በራሱ ተአምር ነውኮ። እንደ ሰማይ ከዋክብት እንደ ምድር አሸዋ መብዛትስ ምን ያደርግልኛል ? እህህህ ለ38 አመታት በህመም ተቆራምጄ በመጨረሻም አልጋዬን ተሸክሜ
መሄድ አልፈልግም። በቃ አልፈልግም !!! የሠርጌ እለት ውሃ ወደ ወይን ጠጅ እንዲቀየርልኝ በጭራሽ አልፈልግም። ወይን ጠጅ ካለቀባቸው ውሃ ይጠጡ
እንግዶቹ ። በቃ! ውሃ በራሱ ተአምር ነውኮ! ምረጪ ብባል ... ዝም እና ዝግ ያለ መደበኛ ህይወት እንጂ ተአምር
አልፈልግም !

@wegoch
@wegoch
@paappii

#By_Teym_Tsigereda_Gonfa
ችግር ነው የስድስት ዓመት ልጅ መሆን። ሲሚንቶ ላይ ተዘርፍጬ፣ በእርሳስ ቀለም ኒኬል ሰሃን… የሚጣፍጥ ፍርፍር በወተት አወራርዳለሁ። አደይ ባለሙያ ናት። የሰራችው አደለም የነካችው ይጣፍጣል። ችግሩ ምንድነው… አካፋ በሚያክለው ማንኪያ ፍርፍር ዝቄ ሳነሳ፣ የሚበዛው ወደ ሰሃኑ ይወድቃል። የስድስት አመት ልጅ መሆን አንዱ ችግሩ ይሄ ነው። ሌላ ጊዜ እናቴ እያየቺኝ ትስቅና መታ ታጎርሰኝ ነበር፤ እንደሱ አላደረገችም። ሰሞኑን ሳቅ ረስታለች። አባቴ ግን የት ሄደ? መቐለ ነው የኛ ቤት። እንደውም ይሄ የሰማዕታቱ ሃውልት አለ አይደል? ግራና ቀኝ ያሉትን ህንፃዎች እንደ አምና ወደሁዋላ እየተወክ ቁልቁል ስትወርድ፣ የኛ ሰፈር አለ። እና ቤታችን። ከአዲሱ ስታዲየም ብዙ አይርቅም። ባለፈው አባቴ እሽኮኮ አድርጎ ወሰደኝ ወደ ስቴድየሙ። ቁልፍ ከኪሱ አውጥቶ በሩን ከፍተና ገባን…
“በጣም ሰፊ ነው ወንበር ደሞ አለው ብዙ” አልኩ “መስሎህ ነው… ስታድግ ትንሽ ይሆናል… ይበልጥ ትፈልጋለህ…”
አንዳንዴ ትልቅ ሰዎች ምንም ነው ደስ የማይሉት። የሚናገሩት እንዳለ ሚስጥር!
ሰሞኑን የሚያስፈሩና የሚጮሁ ድምፆች አሉ እኛ ሰፈር። ምናቸውም አያስፈራኝ። ብቻ እናቴ ስትፀልይ፣ ስትለማመን ሳይ መፍራት እጀምራለሁ። የሆነ ነገር ልክ
አይደለም ማለት ነው? “ምንድነው የሚጮኸው እማ?”
“አጆኺ… ፈንዲሻ ነው!”
“ስቴድዮሙን በሚያክል ብረምጣድ ነው እንዴ የሚቆሉት?”
“ግሩም ነው… እንዴት አወቅሽ?”
___
አንዳንዴ ደሞ ሰማይ ምድሩን የሚነቀንቅ ጉድ ሰፈራችን ላይ ይወርዳል። ግድግዳ ላይ የተሰቀለው፣ አንድ ቦታ ጥቁር ሽታ ያለበት ትሪያችን እስኪወድቅ ድረስ ቤቱ ይወዛወዛል። በጣም ያስደነግጣል። “እሺ ይሄስ?” እላታለሁ ማማን “ከበሮ ነው… አይዞሽ…” እማ ደሞ ታበዛዋለች… ምነው የፈለገ የስድስት ዓመት ልጅ ብሆን ይሄ ይጠፋኛል? ምነው እነ ትርሓስ አሸንዳ ሲጨፍሩ ከበሮ አላየንም? ምነው
ከጡቶቿና ጥንቅቅ ተደርጎ ከተሰራ ጠጉሯ ሌላ፣ የተናጠና የተናወጠ ነበር?
ቤታችንን ሊያፈርስ የደረሰው ጉድ በጭራሽ ከበሮ አልነበረም። እንዳ ኪዳነምረት በተስክርትያን ያየሁት ዓይነት ትልቅ ከበሮ ከሆነ አላውቅም እንግዲ። ማማና ማማ ትብለፅ ሲያንሾካሽኮ ነበር ትናንት። የሆነ ችግር አለ ማለት። አንሾካሽከው ሁለት ሰዓት እንኳን አልቆየም። ማታ ከምሽቱ ልተኛ ስል አከባቢ፣ አንዳች ድብደባ በራችንን ሊገነጥል ደረሰ። “እንዴት አመሻችሁ” አለ ከውጭ ያለ ድምፅ፣ አንድ ሰው ብቻ አልነበረም…
“መስገኖ… መንኻ?”
“አይዟችሁ… ወታደሮች ነን ክፈቱ!” ባታየኝ ይሻል ነበር። እናቴ ባታየኝ ይሻል ነበር። ችግሩ ዞር አለችና አየችኝ። ዐይኖቿ ካቅም በላይ ከባድ ነበሩ። ተጫኑኝ።
“አጆኺ… እቶም ሰላም አስከባሪ ኢዮም” አለች እናቴ እንደምንም። በሩን እያንገራገረች ስትከፍት፣ በሰደፍ አሏት። እናቴ ወደቀች። ምንም እንዳልተፈጠረ ቤታችንን በርብረው፣ የባባን ፎቶ ፍሬም ሰባብረውና፣ ዕቃውን አተራምሰውና የማማን ወርቆች ይዘው ሄዱ። ይህ ሁሉ ሲሆን ከተጋደምኩበት ስንዝር ፈቅ አላልኩም። ምክንያቱም ከዓለት የሚከብዱ የናቴ ዓይኖች እኔው ላይ ነበሩ

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Yonas Angesom Kidane
"ጫማሽ ሲያምር"
"ከሜክሲኮ አደባባይ በ100 ብር ነውኮ የገዛሁት"
"ሱሪሽ ሲያምር"
"ወይ ስድስት አመቱ ከዛሬ ነገ ለልዋጭ እቀይረዋለሁ እያልኩ"
"ፀጉርሽ ሲያምር"
"ሁለት ሳምንቱ ከተሰራ ተንጨባርሬአለሁ"
"ቀሚስሽ ውብ ነች"
"ከመገናኛ መንገድ ላይ በ150 ብር የተገዛች ነች"
"ምግብሽ ይጣፍጣል ባለሙያ ነሽ"
"አይይ ዘይት አልቆብኝ የይድረስ ይድረስ ነው የሰራሁት ባክሽ"
"ጥዑም ነው ቡናሽ"
"መፍጫዬ ተበላሽቶ ... በትንሽ የቡና ዱቄት ነው ያፈላሁትኮ እንዳውም ቀጥኗል"
"ቲሸርትሽ ውብ ነው"
"ወይኔ ውስጡ ለቄስ እዚጋ ተቀዷልኮ እየተሳቀቅኩ ነው የምለብሰው
አይታይም?"
"ጎበዝ ነሽኮ ስራሽን ጥንቅቅ አድርገሽ የምትሰሪ"
"አርፍጄ እየገባሁ ምን ዋጋ አለኝ ብለሽ ነው"
"ትምህርት ላይ ጥሩ ነሽ የኔ ሰቃይ"
"አላጠናምኮ ብታይ"
"ሸሚዝሽ ያምራል"
"ቁልፉ ተገንጥሎ በመርፌ ቁልፍ ነውኮ ያስያዝኩት"
"የቤትሽ ፅዳት"
"ወይ ተዝረክርኳል እንዳውም"
.
.
.
የኔ ቆንጆ እስቲ ፈገግ ብለሽ "አመሰግናለሁ" ማለትን ብቻ ልመጂ። ዝርዝሩ
አያስፈልግም ።

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Teym Tsigereda Gonfa
ሴት እና ትዳር (1)
‹‹እርቃን››
ፀሃፊ፡ ቢኮዙሉ ‹‹The Emperor’s Naked”
ትርጉም፡ ሕይወት እምሻው
---------------
የሶስት ወንዶች እና ሁለት ሴት ልጆች እናት ነኝ፡፡ ይህ ማለት፣ ከእንቅልፌ ከምነሳባት ሰከንድ አንስቶ መሽቶ የቤታችን የመጨረሻዋ መብራት እስክትጠፋ ድረስ ቀኑን ሙሉ ስተራመስ ነው የምውለው፡፡ ሌሊቶቼ አጭርና ቶሎ የሚያልቁ ናቸው፡፡ ንጋት ጠላቴ ነው፣ ያልጠገብኩት እንቅልፌን ቀምቶ ለማያባራ የቤት ውስጥ ስራ አሳልፎ ይሰጠኛል፡፡ ቀኖቼ እረፍት አልባ ናቸው፡፡ ቀኖቼ በጩኸት የተሞሉ ናቸው፡፡ ሁሌም አንድ ነገር እንደተሰበረ ነው፡፡ መአት ብርጭቆ እገዛለሁ ግን ሁሉንም አንድ በአንድ ሰብረዋቸው አሁን ሁላችንም በፕላስቲክ ኩባያ ነው የምንጠጣው፡፡
ሁሌም አንዳቸው እንዳለቀሱ ነው፡ ሁሌም አንዳቸው ካንዳቸው እንደተጣሉ ነው፡፡ አንዳቸውም ደብተራቸው የት እንዳለ አያውቁም፡ ወይ ደግሞ ካለሲያቸው ይጠፋባቸዋል፡፡ ወይ ደግሞ ፓንታቸው፡፡ ወይ ሸራ ጫማቸው፡፡ ሁሌም የሆነ ነገር ላይ እንደተንጠለጠሉ ነው፡፡ ‹‹ውረድ…ውረዱ…!›› እያልኩ ከጣራ በላይ ብጮህም እነሱ እቴ! እንደ ሰው በመሬት ላይ ከመሄድ እንደ ጦጣ
ባገኙት ነገር ላይ መንጠላጠልን ይመርጣሉ፡፡ ቲቪው ከተከፈተ- ማለት ቲቪ በሚፈቀድላቸው ሰአት- ድምፁ ከጣራ በላይ ነው፡፡ ግን ማንም በጨዋ ደምብ ቁጭ አያየውም፡፡ ሁሌም ይሄኛውን እንይ…ይሄኛውን አናይም እያሉ ጣቢያ ለመቀየር የኔ ተራ ነው በሚል እንደተናቆሩ ነው፡፡ ጠብ መገላገል፣፡ አንዳቸውን ማባበል፣ አንዳቸውን ማስፈራራት የነጋ ጠባ ስራዬ ነው፡ ሁሌም እህትና ወንድም እኮ ናችሁ…መዋደድ አለባችሁ እያልኩ እመክራለሁ፡፡ ወይ የሆነ ነገር ሸርክቶት የሚደማ እጅ ይዤ ኡፍፍ እያልኩ ፕላስተር አደርጋለሁ፡፡ እስከዛሬ የከፋ ነገር ገጥሞኝ ሃኪም ቤት ሮጬ የሄድኩት ለሁለት ነገር ነው፡፡ አንድ ጊዜ ያንዳቸው እጅ ተሰብሮ፣ አንዴ ደግሞ አንደኛው ሳንቲም ውጦ፡፡ አምስት ልጆች ስላሉኝ የልደት በአል ቶሎ ቶሎ፣ ተከታትሎ ነው የሚመጣው፡፡ እንደገና ሌላ መአት ሻማ፣ እንደገና ሃው ኦልድ አር ዩ ናው እያሉ መዘፈን፣ እንደገና ኬክ መግዛት (የምገዛው ኬክ ሁሌም መጠኑ አንድ አይነት ነው፡፡ አንዱን ካንዱ ያስበለጥኩ እንዳይመስል)፡፡ በዚህ ሁሉ ትርምስ መሃከል አንደኛው ልጄ ሁልጊዜም ጡሩምባውን እንደነፋ ነው፡፡ ትንፋሽ እስኪያጥረው፣ ከመጠን በላይ
ጮህ አድርጎ ነው የሚነፋው፡፡ (ወይ ትኩረት እንድንሰጠው ወይ ደግሞ
ሊያናድደን)፡፡ የሚያወጣው ‹‹ሙዚቃ›› ጭራ እና ቀንድ የሌለው ታምቡር የሚፍቅ ድምፅ ነው፡፡ ያናድደኛል ግን ልጄ ነውና ሳምባው እስኪፈነዳ መንፋት ይችላል፡፡ ምናልባት ከልምምድ ብዛት ችሎታው ሊሻሻል ይችላል፡፡ ለጊዜው ግን የምሰማው ነገር ስሪያ ላይ ያለች ዝሆን የምታወጣው አይነት ነው፡፡
እናት ነኝ፡፡ የእናትነት አለም ይሄ ነው፡፡ ለጤና ጥሩ አይደለም፡፡ ፀጥታ እና የጥሞና ሰአት ካገኘሁ ብዙ ጊዜ ሆኖኛል፡፡ የራሴ ጊዜ እና እረፍት ካገኘሁ አመታት ተቆጥረዋል፡፡ በባዶ እግር የሚሞቅ የባህር ዳርቻ አሸዋ ላይ መቆም የሚሰጠውን ስሜት አላውቀውም፡፡ መዋኛ ገንዳ አጠገብ አለሃሳብ በጀርባ ጋለል ብሎ ‹‹ልጆቼ የት ይሆኑ›› ከሚል ጭንቀት ተላቅቆ ዘና ማለት ምን ምን እንደሚል አላውቀም፡፡
እንደምንም ብዬ ከምሳ ሰአትe በኋላ ለጥቂት ደቂቃ አይኔን የመክደኛ ጊዜ ባገኝ እንኳን ለሳምንት ከእንቅልፌ የምነቃ አይመስለኝም፡፡ አንዳንዴ 17ኛ ፎቅ ላይ ከሚገኘው ቢሮአችን ማታ አንድ ሰአት ላይ ወጥቼ ለብቻዬ ሊፍት ውስጥ ስገባ ጭንቅላቴን ከቀዝቃዛው የሊፍቱ ግድግዳ ላይ ደገፍ አደርግና፣ ይህቺን አጭር እና ጣፋጭ የፀጥታ ሰአት አጣጥማታለሁ፡፡ መኪናዬ ውስጥ ሬዲዮ ከፍቼ አላውቅም፡፡ ሁሌም የምነዳው በፍፁም ፀጥታ ታጅቤ ነው፡፡ ይሄን ሁሉ ስላችሁ ግን እናት በመሆኔ እንደከፋኝ እና እየተማረርኩ እንደሆነ እንዳታስቡ፡፡
እናት መሆኔን እወደዋለሁ፡፡ ልጆቼን እወዳለሁ፡፡ ቤታችን በፍቅርና በበረከት የተሞላው በእነሱ ምክንያት ነው፡ እናትነት እጣ ፈንታዬ፣ አምላክ የሰጠኝ ፀጋ እና ማእረጌ ነው፡፡ ልጆቼን መንከባከብ እና እድገታቸውን ማየት በምንም የማልቀይረው ደስታዬ ነው፡፡ አንዳንዴ እራት አቀርብላቸውና ዝም ብዬ ቁጭ ብዬ እያየኋቸው በልቤ፣ ‹‹እነዚህ ሁሉ ልጆች የማን ናቸው…ከየትስ መጡ?›› እያልኩ በደስታ እሞላለሁ፡፡
----
ለእናትና አባቴ ብቸኛ ልጅ ነበርኩ፡ቤታችን ትልቅ የድንጋይ ቤት ነበር፡፡ እናት እና አባቴ ቤቱን በፍቅር ሊሞሉት ቢሞክሩም እኔ ግን ብቸኝነት ያጠቃኝ ነበር፡፡ የራሴ ክፍል ነበረኝ፡፡ ገና ከልጅነቴ
ጀምሮ፡፡ በልብስ ወይ ደግሞ በቲቪ ሪሞት ኮንትሮል ከማንም ጋር ተጣልቼ አላውቅም፡፡ የሚያስፈልገኝ ነገር ሁሉ ነበረኝ- ከወንድም ወይ ከእህት በስተቀር፡፡ የወንድም ወይ የእህት ፍላጎት ያንገበግበኝ ነበር፡፡ የትምህርት ቤት ጓደኞቼ ከወንድም እና እህቶቻቸው ጋር ተጠባብቀው ታክሲ ውስጥ ሲገቡ በሃይል እቀና ነበር፡፡ ምሳ እቃ ከፍተው አብረው ሲበሉ፣ እረፍት ላይ አብረው ለመጫወት አንዳቸው አንዳቸውን ሲጠብቁ ሳይ እቀና ነበር፡፡ ምንም
ነገር ቢደርስብኝ ከሁሉም ሰው በፊት ሊያድነኝ እና ሊጠብቀኝ የሚችል፣ በደም
የሚዛመደኝ ሰው ክፉኛ እናፍቅ ነበር፡፡ አስታውሳለሁ፤ አንዴ ትምህርት ቤታችን
በከፊል ሲቃጠል ሁሉም ልጆች ወንድም እና እህታቸውን ፍለጋ ሲሯሯጡ እኔን ብሎ የመጣ ማንም ልጅ አልነበረም፡፡
ለዚህ ነው ብዙ ልጆች እንዲኖሩኝ እመኝ የነበረው፡፡ የዛሬ ባሌን የማግባት እድሌ ሃምሳ በመቶ ነበር፡፡ አሜሪካ ለትምህርት የሄደውን እጮኛዬን የማግባት እድሌ ደግሞ ሃምሳ በመቶ ፡፡ ልቤ ሁለቱንም ይወድ ነበር፡፡ በእርግጥ መጀመሪያ የወደድኩት የመጀመሪያውን፣ አሜሪካ የሄደውን እጮኛዬን ነበር፡፡ ልቤ ለሁለተኛው የተከፈተው አሜሪካ የሄደው እጮኛዬን መጠበቅ ከሰማይ መና የመጠበቅ ያህል ስለሆነብኝ ነው፡፡
እዚህ ሃገር ኢንጂነር መሆን የማይቻል ይመስል አሜሪካ ሄጄ ኢንጂነሪንግ ልማር
ብሎ በጣም ረጅም ጊዜ ቆየ፡፡ የዚያን ጊዜ ኢንተርኔት ጨጓራ የሚልጥና ቀርፋፋ ስለነበር በዚያ ጎታታ ኢንተርኔት
በስካይፕ መገናኘት አቸከኝ፡፡ በቪዲዮ እያወራን አንድ አረፍተ ነገር ሳይጨርስ
ምስሉ ስክሪኑ ላይ ደርቆ ይቀራል፡አንዳንዴ አፉ አጓጉል ተከፍቶ እያለ ነው እንዲህ የሚሆነው፡፡ ታዲያ ይሄን ጊዜ ዝም ብዬ ይሄንን ምስሉን አይና ጠዋት ከእንቅልፉ ሲነሳ ምን እንደሚመስል ማሰብ እጀምራለሁ፡፡ ጠዋት ሲነሳ ምን እንደሚመስል የማላውቀውን ሰው ለማግባት ማሰቤ ያስፈራኛል፡፡ ሴቶች የሚያገቡት ሰው ጠዋት እንደተነሳ ምን እንደሚመስል ማወቅ አለባቸው ባይ ነኝ፡፡ ከእንቅልፋቸው ሲነሱ ነፍሰ ገዳይ የሚመስሉ ፍቅረኞቸ ነበሩኝ፡፡ በዚያ ምክንያት የተውኳቸው፡፡ ባሌን የተዋወቅኩት ከግብርና ጋር የተያያዘ ስብሰባ ላይ ነው፡፡ ስለ ማዳበሪያ፣ ምርጥ ዘር ምናምን የሚያወራ ስልጠና ነገር ነበር፡፡ ወደፊት ገበሬ የመሆን ሃሳብ
ነበረኝ፡፡ ከፕላስቲክ የተሰሩት ወንበሮች ላይ ጎን ለጎን ነበር የተቀመጥነው፡፡ ካሮት የሚመስሉ የእጆቹን ጣቶች ሰረቅ እያደረግኩ ሳይ ትዝ ይለኛል፡፡ ከዚያ
ማውራት ጀመርን- ስለ እንጆሬ፡፡ የእንጆሬ እርሻ ነበር እንዲኖረኝ የምመኘው፡፡ በኋላ ለሻይ ቡና ስንንናኝ አሜሪካ ስላለው እጮኛዬ ነገርኩት፡፡ ‹‹በዱር ካሉ ሁለት ወፎች በእጅ ያለ አንድ ወፍ ይበልጣል›› አይለኝም? ተረት እና ምሳሌያዊ አነጋገር፣ ፈሊጥ ምናምን የሚገባኝ አይነት ሴት አይደለሁም ግን እሱ ነው የሚያዋጣሽ ማለቱ መሰለኝ፡፡ የሚገርመው ግን እንዲህ ማለቱ ልቤ
እንዲፈልገው አደረገ፡፡ አለ አይደል…የሴት እልህ…‹‹ምናባቱ ቆርጦት ነው ለሌላ ወንድ አሳልፎ የሚሰጠኘኝ?›› አይነት ነገር፡፡ ከአመት ተኩል በኋላ በሰርግ ተጋባን፡፡ አሜሪካ ያለው እጮኛዬን ልብ እንደ መስታወት ያደቀቀ እና መቶ ሰዎች ብቻ የተጋበዙበት ቀለል ያለ ሰርግ ነበር፡፡ ባሌ በጥቁር ሱፍ አምሮበት- ሰፊ ትከሻው ኮቱን ወጥሮት- የሚጣፍጥ የአፍተር ሼቩ መአዛ እያወደኝ፡፡ አፍተር ሼቭ የሚጠቀም ወንድ ደስ ይለኛል፡፡ ከሰርጉ ጥቂት ወራት በፊት አርግዤ ነበር፡፡ ግን ሆዴ ስላልገፋ ብዙ አያስታውቅም ነበር፡የእናቴን ውብ ሃብል አድርጌ. አባቴ እጄን ጥብቅ አድርጎ ይዞኝ…..ስለሰርጌ የማስታውሰው ይሄንን ነው፡፡ የአባዬ እጄን አጨማመቅ…. ብዙ ሳልቆይ ልጄን ወለድኩ፡፡ ብዙ ሳልቆይ ስል ሰርጌ ላይ ኬኩ እንደተቆረሰ ማለቴ ሳይሆን ከጥቂት ወራት በኋላ፡፡ ከዚያ በኋላ በተከታታይ መውለድ ቀጠልኩ፡፡ እንደ እኔ ፍላጎት ቢሆን ቤቴን ሆስፒታሉ ውስጥ አድርጌ መመላለሱ ይቀርልኝ ነበር፡፡ ዝም ብዬ መውለድ ቀጠልኩ፡፡
ሶስተኛው ልጃችን እንደተወለደ ባሌ ‹‹አሁን ይበቃናል›› አለ፡፡ ይበቃናል? ይቀልዳል እንዴ? ከቁብ ሳልቆጥረው ሁለት ልጆችን ጨመርኩ፡፡ ልጆች ድንቅ ስጦታዎች ናቸው፡፤ ግን ሰውነትን እንዳልነበር ነው የሚያደርጉት፡የመጀመሪያዎቹ ሁለት ልጆቼ ሰውነቴን ፈጽሞ ቀይረውት ነበር፡፤ ከዚያ በኋላ ግን ለውጡ እምብዛም ነው፡፡ አሁን ሳስበው በሰርጌ እለት ከነበረኝ አቋም አሁን ሳልሻል አልቀርም፡፡ እንደዚያ
ጊዜ ወደ ላይ አይለኝ፡፡ ከዚያ ጊዜ ይልቅ አሁን ሞላ፣ ሰፋ ብያለሁ፡፡ ዳሌዬ ሰፍቷል፡፡ ከበፊት ይልቅ ያሁኑ ሰውነቴ ያኮራኛል፡፡ ያው ወገቤ አከባቤ ትርፍ ስጋ አይጠፋም ግን ለማስተካከል እየታተርኩ ነው፡፡ ደረጃ ስወጣ የሚንቀጠቀጥ ትልቅና የላላ መቀመጫዬ ሊኖረኝ ይችላል፡፡ ግን ያም ሆኖ አማላይ ቢጤ ነኝ፡፡ ….ለምሳሌ መቼ እለት መስሪያ ቤታችን በተለማማጅነት የተቀጠረ የ ሃያ አንድ አመት ጎረምሳ፣( በእድሜ እጥፍ የምበልጠው ጉብል - ወደ ጠረጴዛዬ መጥቶ የባጡንም የቆጡንም ሲቀባጥር ቆይቶ ምን ቢለኝ ጥሩ ነው? ‹‹ነገ…ከቢሮ ወጣ ብለን ሻይ ቡና ብንል ምን ይመስልሻል?›› እውይ፡፡
‹‹በጣም ደስ ይለኝ ነበር …›› አልኩና ግራ እጄን አንስቼ የጋብቻ ቀለበቴን እየጠቆምኩ ‹‹ግን ባለትዳር ነኝ›› አልኩት፡፡ ‹‹ውይ…ይቅርታ…ግን በጣም ቆንጆ ነሽ›› አለኝ፡፡ እውይ፡፡ እድሜው ሰላሳ ሁለት ቢሆንና ከእናቱ ጋር የማይኖር ቢሆን ቡናውን እጋበዝለት ነበር፡፡ አሁን አሁን ከተማው ውስጥ እንደእሱ አይነቶቹ በዝተዋል- ከእናታቸው
ወይ ደግሞ እንደ እናት ከሚሰራቸው ሴቶች ጋር የሚኖሩ ወጣት ወንዶች፡፡
ግብዣውን እቀበል የነበረው ባለትዳር ብሆንም ላጤ ስለሆንኩ ነው፡፡ ትዳሬ ጣእሙን መለወጥ የጀመረው ከአምስት አመታት በኋላ ነበር፡፡ ትዳሬ የተለወጠው ባሌ ስለተለወጠ ነው፡፡ ሁላችንም ተለውጠናል፡፡ ግን ለውጡ ቀ……ስ ያለ ነበር፡፡ …አለ አይደል…ምን የመሰለ የአትክልት ስፍራ ውስጥ እንደሚታይ ትንሽ አረም….መጀመሪያ ስታዩት ያን ያህል ትልቅ ነገር አይመስልም፡፡ ቀስ በቀስ ተስፋፍቶ አትክልትና አበቦቻችሁን ውርር እስኪያደርግ እና አንድ በአንድ ማነቅ እስኪጀምር፡፡
---ይቀጥላል-----

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሴት እና ትዳር- ‹‹እርቃን››- ክፍል ሁለት
------------------------
ትዳራችን ይነፍስበት የጀመረው እዚህ ግባ በማይባሉ ጥቃቅን ነገሮች መነሻነት
ነበር፡፡ አለ አይደል…ጠዋት ከእንቅልፋችን ስንነቃ እንዴት አደርሽ ማለት ሲተው… (ባሎች፣ እባካችሁ..ሁሌም ሚስቶቻችሁን እንዴት አደርሽ ብላችሁ ጠይቁ….በክር ከተሰራች አሻንጉሊት ጋር አይደለም እኮ ተኝታችሁ ያደራችሁት! አንድ ቀን እንዴት አደርሽ ብላችሁ መጠየቅ ስትረሱ ነገም አታስታውሱም…ከዚያ ይለምድባችሁና
ልክ አዳሪ ትምህርት ቤት እንደሚኖር ተማሪ ብድግ ብላችሁ ካልጋ መውጣት
ትጀምራላችሁ፡፡ ) እና እንዳልኳችሁ ጠዋት መነሳትና ሰላም ሳይለኝ ወደ ሽንት ቤት መሄድ ጀመረ፡፡ ሁልጊዜ እንዴት አደርህ የምለው እኔ ሆንኩ፡፡ ከዚያ እኔ ብቻ እንዴት አደርህ ማለቱ ታከተኝ፡፡ እየቆየ ሲሄድ ጠዋት ጠዋት እኔን ማየት እንኳን እንዳቆመ ማስተዋል ጀመርኩ፡፡ ልብስ እየለባበስን ስናወራ እንኳን ጭራሽ አያየኝም፡፡ ለማየት የማስቀይም አይደለሁም፤ ሁሌም ራሴን በመስታወት ስለምመለከት ይሄንን አውቃለሁ፡፡ እና ታዲያ ምን ሆኖ ነው የማያየኝ? እኔ ደግሞ ሰው ካላየኝ ኖርኩ አልኖርኩ ግድ እንደሌለው ነው የሚሰማኝ፡፡ ካላየኸኝ የለሁም ማለት ነው…ድምጽ ብቻ ያላት መንፈስ ሆንኩ ማለት ነው…(.ወንዶች፣ እባካችሁ ሚስቶቻቸሁን እዩ፡፡ ) ጠዋት ጠዋት ሰላም ማደሬን ባይጠይቀኝም፣ ባያየኝም ግን ትዳራችን ጥሩ የሚባል ነበር፡፡ ቤቱን ማስተዳደር ላይ አልሰነፈም፡፡ ለልጆቹ መጫወቻ እና ልብስ ይገዛል፡፡ አንዳንዴም አብሯቸው ይጫወታል፡፡ ከዚያ ሕይወት በማይታሰብ ፍጥነት መክነፍ ጀመረች፡፡ ልጆቻችን ትምህርት ቤት ሲገቡ የትምህርት ቤት ክፍያ ራስ ምታት እና ለነገ ጥሪት የመቋጠር ጭንቀት ይወጥረን ጀመር፡፡ ባለቤቴ ትልልቆቹን ወጪዎች ሲችል እኔ ደግሞ ጥቃቅን የቤት ቀዳዳዎችን እየደፈንሁ ኑሮ ቀጠለ፡፡ ከዚያ ሳይታወቀን ሁለታችንም በየራሳችን ዛቢያ የምንሽከረከር፣ በማይገናኙ መንገዶቻችን አለእረፍት የምንሮጥ እና የምንባዝን ሰዎች ሆንን፡፡ እሱ ቤት ከሚኖርበት ጊዜ ስራ ላይ የሚያሳልፈው ጊዜ እየበዛ፣ ቤት ሲመጣም በድካም ብትንትን ብሎ እና ልጆቹን እንኳን ማናገር እንዳይችል ሆኖ፣ ለመኝታ
ብቻ ሆነ፡፡ እሁድ እሁድ ቤት ይሆናል ግን ከቅዳሜ የዞረ የመጠጥ ድምሩን ስለሚያወራራድ እንዳለ አይቆጠርም፡፡ ሁሌም በስራ ደክሞ ስለሚገባ ልጆቼን ብስክሌት መንዳት እንኳን ያስተማርኳቸው እኔ ነኝ፡፡ ለነገሩ ጭራሽም ለማድረግ አልሞከረ፡፡ እያደር እሱ ሊያከናውናቸው የሚገቡ ስራዎችን ፣ ሊወጣቸው የሚገቡ ሃላፊነቶችን እኔ ማድረግና መወጣት ጀመርኩ፡፡ የቧንቧ ሰራተኛ ፈልጎ ማግኘት…የልጆቹን ትምህርት ቤት መምረጥ፡፡ ልጆቻችን እያደጉ ሲሄዱ አብሯቸው ማሳለፍ ያለበትን ጊዜ ሳያሳልፍ እድሜያቸው
እንዳያልፍና እንዳይቆጨው ብዬ ጊዜ እንዲሰጣቸው የምችለውን ሁሉ ጣርኩ፡፡
እስቲ መናፈሻ ወይ መጫወቻ ቦታ ውሰዳቸው…ብስክሌት አብረሃቸው ጋልብ….አዋራቸው፣ ወንዶቹን ደግሞ እንዴት አይነት ወንድ…እንዴት አይነት አባት መሆን እንዳለባቸው አሳያቸው ስል ወተወትኩት፡፡ እሱ ግን ሁሌም ጊዜውን የሚሻማ ነገር አያጣም፡፡ ሁሌም ከዚህ የሚበልጥበት ነገር አይጠፋም፡፡ ከዚያ የቤተሰቡ ራስ እኔ ሆንኩ፣ ውሳኔ አሳላፊዋ ሆኜ አረፍኩ፡፡ ከጊዜ በኋላ የትምህርት ቤት ክፍያ በጊዜ መክፈል አቆመ፡፡ ጭራሽ ትምህርት ቤቱ ደውሎ
ክፍያ ይጠይቀኝ ጀመር፡፡ ያን ጊዜ የዚያኛውን ሴሚስተር ራሴ እከፍልና
የሚቀጥለውን እንዲከፍል ባየው ባየው እሱ እቴ!
---
አባቴ ለእናቴ ምን አይነት ባል እንደነበር አላውቀም፡- ምናልባት እንደ ባል ያጎደለባት ነገር ይኖር ይሆን አላውቅም፡፡፡ ለእኔ ግን ምን አይነት አባት እንደነበር ጠንቅቄ አውቃለሁ፡፡ ሃላፊነቱን የሚያውቅና በአግባቡ የሚወጣ አባት ነበር፡፡ በዚያ ላይ ኩሩ ነበር- የእኔ አባት፡፡
አንዴ አስታውሳለሁ- አስር ወይ አስራ አንድ አመቴ እያለ- ቅዳሜ ቀን ነው…. ጠዋት ቁርስ እየበላን በልጅነት አእምሮዬ ያኔ- ምክንያቱ አልገባኝም ግን የሆኑ የባንክ ሰራተኞች ወደ ቤታችን መጡ፡፡ አባዬ እኔና እማዬን ካለንበት ትቶን
ሊያናግራቸው ይሄዳል፡፡ በሳሎኑ መጋረጃ ውስጥ ውጭ ቆሞ ሲያዋራቸው አያለሁ፡፡ ከአጥራችን ውጪ
የቆመው የጭነት መኪና የቤት እቃችንን በሙሉ ለቃቅሞ ለመሄድ የጓጓ ይመስላል፡፡ እማዬ ከተቀመጠችበት ሳትነሳ፣ አንዴ እንኳን ሳትንቀሳቀስ፣ ተነስታ ወደ አባዬ ሳትሄድ እዛው ቁጭ ብላለች፡፡ የእሷ ተረጋግቶ መቀመጥ እኔንም ሲያረጋጋኝ አስታውሳለሁ፡፡ እሷ እንደዛ ረጋ ብላ ቁጭ ካለች ውጪ እየሆነ ያለው (መጥፎ ነገር ይመስላል) ምንም ነገር ቢሆን አባዬ መላ እንደማያጣለት እና ወደ ቁርሱ እንደሚመለስ ነገረኝ፡፡ እናም ልክ እንዳሰብኩት ሆነ፡፡ አባዬ ያንን ቀን ልክ ሌሎች ቀኖችን እንደሚያሳልፈን በብልሃት አሳለፈን፡፡ ከዚያ በኋላ ስለ ወንድነት ያለኝ ግምት አባቴን ተደግፎ የተሳለ ሆነ፡፡ ወንድ ልጅ፣አባወራ ሲሆን ቤተሰቡ የሚገጥመውን ችግርን ወጥቶ እንደ ወንድ መጋፈጥ እንዳለበት፣ ከዚያም በኩራትና በልበ ሙሉነት መቆም እንዳለበት ከአባዬ ተማርኩ፡፡
.
እናትና ሚስት ሆኜ ቤቴን ማስተዳደር ምኞቴ ነበር፡፡ ባሏን የምትከተል፣ ታታሪና ጨዋ ሚስት መሆን ነበር ፍላጎቴ፡ሚስት፡፡ ቀስ በቀስ ግን የአባወራውን ስራ መረከብ ጀመርኩ፡፡ ባል ሆንኩ፡፡ እሱ መወሰን ያለበትን ነገር መወሰን፡፡ የልጆቹን ትምህርት ቤት ክፍያ መክፈል፡፡
ያን ጊዜ በሌላ አይን እመለከተው ጀመር፡፡ በፊት የምመካበት እና የማደንቀው ወንድ መሆኑን አቆመ፡፡ አቅጣጫው ጠፍቶበት የሚማስን ሰው ሆኖ አገኘሁት፣ አቅጣጫው የጠፋበት ሰውን ደግሞ መከትል አልችልም፡፡ ከጊዜ በኋላ አንዳችን ለአንዳችን ጭራሹን ባእድ ሰዎች ሆነን አረፍነው፡፡ የባል እና ሚስት ወጋችን እንደ በርሃ ዝናብ በጭንቅ የሚመጣ እና በስንት ጊዜ
የሚከሰት ነገር ሆነ፡፡ ከስንት አንዴ ሆኖልን ፍቅር ስንሰራ እንኳን ሃሳቤ ወደማልመው የእንጆሬ እርሻዬ
እየሄደ ያስቸግረኛል፡፡ ስናወራ ከሌላ አለም እንደመጣ ሁሉ፣ ሁሉ ነገሩ እንግዳ ይሆንብኝ ጀመር፡፡ የማላውቀውን ቋንቋ እንደሚናገር እንግዳ ሰው፡፡ ይሄ ሁሉ የሆነው አሪፍ ሚስት መሆኔን ስላቆምኩ ይሆናል፡፡ እንደ በፊቱ አምሽቶ ሲመጣ እና እራት እየበላ የዚያን እለት ቢሮ ስለተፈጠሩ አስደናቂ ነገሮች ሲያወራኝ እያዳመጥኩ፣ ቁጭ ብዬ አላየውም፡፡ ይልቅ ለጥቂት ቀናት ፊልድ ሲሄድ ልቤ ጮቤ ይረግጣል፡፡፡ ያን ጊዜ ቤቱ ይሰፋኛል፣ ክፍሎቹ ወደ ጎን ልጥጥ ይላሉ… ያኔ.መተንፈስ እችላለሁ፡፡ ከፊልድ የሚመለስ ቀን ቀድሜው ገብቼ ደህና የሚበላ ነገር አዘጋጅቼ (ድሮ ቢሆን የምበላው ነገር እኔ ነበርኩ!) ለመጠበቅ አልቸኩልም፡፡ በፊት በፊት በየትኛው አውሮፕላን እንደሚመጣ፣ ትራንዚቱ የት እንደሆነ፣ ስንት ሰአት የት እንደሚደርስ አውቅ ነበር፡፡ አንዳንዴማ ኤርፖርት ሁሉ ሄጄ እቀበለው ነበር- ያውም ምን እንደሚናፍቀው ስለማውቅ ትኩስ ቡና በፔርሙስ ይዤ! አሁንስ? አሁንማ ደስ የሚለኝ ሲሄድልኝ ነው፡፡ ምክንያቱም ቤት ውስጥ ሆኖ ልክ እንደ ወንዶቹ፣ ልክ እንደ ቤተሰብ አስተዳዳሪ፣ እንደ ደህና አባወራ ወዲህ ወዲያ ሲል ላየው ስለማልፈልግ ነው፡፡ በዚያ ላይ…የሚያገኘውን ገንዘብ የት እንደሚያደርገው ሳላውቅ ወይ ሳይነግረኝ… ቤተዘመድ ጋር አብረን ስንሄድ ግን እንደ መልካም ሚስት- እናት እና አባቱ እንደሚፈልጓት አይነት- እሆንና ምግብ አቀርበለታለሁ፡፡ እናቱ ልጃቸው እንዲህች አይነት ድንቅ ሚስት አግብቶና በትዳሩ ተደላድሎ ስለሚኖር ኩራት ኩራት
ይላቸዋል፡፡ የማያደንቀን ሰው የለም፡፡ ‹‹ድንቅ ጥንዶች›› ይሉናል አንዳንዶቹ፡እውነታው ግን የተገላቢጦሽ ነው፡፡
አናወራም፡፡ አንጣላም- ለጠብ የሚሆን ጉልበት እንኳን አልነበረንም፡፡ ውድቅት ላይ ቤት ቢመጣ ግድ አይሰጠኝም፡፡
ውጪ ያስቀመጣት ሴት ብትኖር እንኳን ደንታ የለኝም፡፡ ያስቀመጣት ካለችውም የወንድ ቅርፊት እንጅ ደህና ወንድ እንዳላገኘች ስለማውቅ አይቆረቁረኝም፡፡ የወንድ ልጣጭ ነው ያገኘችው፡፡ የወንድ ጭራ፡፡ የባለቤቷን ጉድለቶች አንድ በአንድ የምትቆጥር፣ ኩንታል ስህተቶቹን ተሸክማ የምትኖር፣ የወንድነት ጥላ የራቀው እርቃን እና ደካማ ባሏን አብጠርጥራ የምታውቅ ሚስት ሆኛለሁ፡፡ እርግጥ ነው- እኔም ደካማ ጎን አለኝ- ምን ጥያቄ አለው? እዚህና እዚያ ምላሴን ያዳልጠኝ ይሆናል፡፡ ነገረኛ ብጤም ሳልሆን አልቀርም፡፡ እሱም ከአንዴም ሁለት ሶስቴ ጨቅጫቃ መሆኔን ነግሮኛል፡፡ እንዲህ ስለመሆኑ እና እንዲህ እንዲሆን ምክንያት ስለሆኑት ነገሮች የማወቅ አንዳችም ፍላጎት ግን የለኝም፡፡ አንዴ የሆነ አውሮፓ ያለ ኤርፖርት ውስጥ ሆኜ በጉዞ የተዳከሙ እና ጥውልግ- ትክት ያሉ ሰዎች- አይኖቻቸውን ባዶ አየር ላይ ተክለው-- ዝም ብሎ በራሱ የሚሄደው ተንቀሳቃሽ ደረጃ ላይ በደመነፍስ ሲሳፈሩና በድንዛዜ ሲሄዱ ሳይ ‹‹ትዳሬ ልክ እንደዚህ ነው››› ስል ትዝ ይለኛል፡በቅርቡ የሆነ ደረሰኝ ኪሱ ውስጥ አግኝቼ ነበር፡፡ ከጓደኞቹ ጋር ሲዝናና አምሽቶ የከፈለበት ነው፡፡ ለአንድ ጠርሙስ ውስኪ እና ለሚበላ ነገር ሰባት ሺህ አምስት መቶ ብር ከፍሏል፡፡ በአንድ ምሽት ሰባት ሺህ አምስት መቶ ብር ያውም በአዘቦት ቀን፡፡ ደረሰኙን ሳይ ልቤ በጩቤ የተወጋ መሰለኝ፡፡ የልጆቹን ትምህርት ቤት ክፍያ አልከፍልም የሚል ግን ለመጠጥ ይሄን ያህል ብር የሚያወጣ ወንድ ሆኗል፡፡ ስለ ልጆቹ ጉብዝና ለወላጆቹ፣ ለዘመድ አዝማድ የሚጎርር ግን ተማሩ አልተማሩ ግን የማይሰጠው ሰው ሆኗል፡፡ ያውም ከእኔ በስንት እጥፍ የሚበልጥ ደሞዝ
እየበላ፡፡ እርግጥ ነው እንዳሻው እንዲሆን ፈቅጄለታለሁ፡፡ የውሸት እንዲኖር ተባብሬዋለሁ፡፡ ጥሩ አባት እና መልካም ባል ነኝ ብሎ የሚያምንበትን የቁጩ አለም ገንብቶ የውሸት እንዲኖር ይሁንታዬን ሰጥቼዋለሁ፡፡ እዋሽለታለሁ፡፡ ከዚህ ሁሉ ነገር የሚስጠላው ነገር ግን የእሱ ውሸታምነት እኔንም የውሸት የምኖር ውሸታም ማድረጉ ነው፡ ሁለመናዬ ውሸት የሆነ ሰው
አድርጎኛል፡፡ ምናልባት ጠርጥራችሁ ከሆነ ከሌላ ሰው ጋር መውጣት አልጀመርኩም፡፡ ሰው ጠፍቶ አይይለም፡፡ መግቢያ መውጫ ያሳጡ ብዙ ወትዋቾች አሉኝ፡፡ ግን በህግ ባለትዳር ነኝ፣ ትዳር ያለኝ ላጤ ብሆንም፡ ከባለቤቴ ጋር ‹‹ትዳር›› የሚባል ለትርፍ የተቋቋመ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የምንመራ ሁለት ሰዎች ብንሆንም፡፡ እንደሚስት በምንም ነገር እንዲያግዘኝ መጠየቅ ካቆምኩ ቆየሁ፡፡ እንደ ቤቱ ራስ፣ እንደ አባዋራ እሱን መከተል ከተውኩ ቆየሁ- መምራት አቁሟላ! ግርማ ሞገሱ ጠፍቶ አይኔ ላይ ከኮሰሰ፣ ለእሱ ያለኝ ክብር ብን ብሎ ከጠፋ ሰነባበተ፡፡ በፊት በፊት ያማልለኝ የነበረ ያ ወንዳወንድነቱ….ለምሳሌ ጠዋት ጠዋት ከወገቡ በላይ ራቁቱን ሆኖ ጥርሱን ሲፍቅ ሳየው የሚሰማኝ ሞቅታ በፀፀት ተተክቷል፡፡ እስከ መቼ ነው እንደዚህ የምኖረው ግን? እኔስ እስኪያንገሸግሸኝ፣ እስኪያቅተኝ ድረስ እዚህ ያጋደለ፣ ጣራው የሚያፈስ ጎጆ
ውስጥ መኖር እችላለሁ፡፡ ከሁሉ የሚያንገበግበኝ ግን ልጆቼ የአባታቸውን ሁኔታ መረዳት መጀመራቸው ነው፡ አባታቸው ለቤተሰቡ ጥላ ከለላ የሚሆን ጠንካራ አባወራ አለመሆኑን ማየት መጀመራቸው ነው፡፡በተለይ ለወንድ ልጆቼ አብዝቼ እጨነቃለሁ፡፡ የአባወራ ምሳሌ አድርገው ለሚስሉት ምስኪን ልጆቼ፡፡ የወንድነት አርአያ አድርገው የሚቆጥሩት - እሱን በሆንኩ የሚሉት ሰው ይሄ በመሆኑ፣ ልጆቼ አውላላ ሜዳ ላይ ስለቀሩብኝ አዝናለሁ፡፡ ስለ ልጆቼ እጣ ፈንታ የምጨነቀው እኔ ብቻ፣ ለቤተሰቤ የምወጋው እኔ ብቻ መሆኔ ልቤን በሃዘን ያደማዋል፡፡ ውስጤን ይሰረስረዋል፡፡ ያበግነኛል፡፡ ከዚህ ግራ የገባው ሁኔታ እንዴት ማምለጥ እንዳለብኝ አላውቀም፡ምክንያቱም….የቤቴን ወጪ መሸፈን እችል ይሆናል፣ ከልጆቼ ጋር ማውራት እና መጫወት እችል ይሆናል፣ የቤት ሥራቸውን አብሬያቸው መስራት፣ ሲጎብዙ ማበረታታት፣ እንደ እናት ስለ እነሱ መፀለይ አያቅተኝ ይሆናል፡፡ ግን እንዴት መልካም አባወራ መሆን እንዳለባቸው ላሳያቸው፣ አርአያ ሆኜ ልመራቸው አልችልም፡፡ ያንን ሊያደርግ የሚችለው አባወራው ብቻ ነው፡፡ የእኔ አባ ወራ ተብዬ ደግሞ ሃላፊነቱን አሽቀንጥሮ ጥሎ፣ ወንድነቱን እንደ አሮጌ ካፖርት አውልቆ ወንበር ላይ ማንጠልጠልን መርጧል፡፡
-----አበቃ------

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Hiwot_Emishaw
- ወንድ ልጅ ሹገር ማሚ ጠብሶ መኪና ሲገዛ ጀብድ ነው ሴት ልጅ መኪና ያለው
ወጣት ወንድ ስትጠብስ ጎልድዲገር ትባላለች ? ከተማው ውስጥ ስንት የአሮጊት ሴቶችን ጭን ሲያሞቁ የሚውሉ የወንድ ጡረተኞች እንዳሉ አናውቅምና ነው ?

- ለወንድ ልጅ ሴት መቀያየር ማዕረጉ ነው ሴት ልጅ ቦይፍሬንድ ስትቀያይር ይች አተራማሽ ቤተሠብ አሠዳቢ ትባላለች !

- ወንድ ልጅ ትዳር እያለው ችት ቢያደርግ ሚስቱን ታገሽውና ለልጆችሽ ስትይ ሁሉን ችለሽ ኑሪ ትባላለች ሚስት ችት ብታደርግ ከቤትህ አባራት ይባላል :: መጥፎ ነገርን ስታወግዙ ለሴት ወንድ ብላችሁ ሣይሆን ድርጊቱን አውግዙ መጥፎ ነገሮች ለሴት ልጅ ብቻ እንደተሠጡ ነው ይሄ Dysfunctional culture በራሡ ለሴት ልጅ ያለው አመለካከት የወረደ ነው ሴት ሁሌም የወንድ ጥገኛ ናት ሴት መኪና ትወዳለች ሴት ብር ትወዳለች :

- ህይዎት ፊልም ላይ እንዳለው አንዲት የሃብታም ልጅ የጋራዥ ሠራተኛ አፍቅራ
ምናምን አይደለም፡፡ ሁሉም ሲያስመስል ነው ማንም ቢሆን የተሻለ ነገር ቢያገኝ አይጠላም !

- youtube ላይ ብር ለመለቃቀም ሲባል ጎልድ ዲገር ምናምን እያሉ የሴት ልጅን ክብር የሚነካ ነገር የሚሠሩ ምድረ ዱቄታም ኮልኮሌ ማነው ፈቶ የለቀቃቸው ? ምንድነው PHD የሠራሁት በስግጥና ነው ማለት ! ችግርህን ለማራገፍ ሴት ልጅን አሸማቆ ገንዘብ ከማግኘት በላይ ድድብና ከየት ተገኝቶ

- በስፖኪዮ የሴት ልጅ ቂጥ ለማየት 360° ዲግሪ አናቱ የሚዞር ወንድ ሁላ ሴት ልጅ ጥቅመኛ ናት የሚል ቪዲዮ ሠርቶ ይለቃል ህዝቡም እንዲህ አይነት ነገር ይመቸዋል ያያል ። ከዛ እሷን አሸማቆ እሡ ገንዘብ ያገኛል ። ይሄ የምርጫ ጉዳይ ነው መኪና ያለው ወንድ ነው የምፈልገው የምትል ሴት ካለች መብቷ ነው ።

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Bethlehem Habtie
ውብ እግሮች ያሏት ቀይ ሴት ትስበኝ ነበር። ሞላ ያለች፣ ጠጉሯን ቁጥርጥር
የምትሰራ፣ ደስ ሲላት ጂጂ ፍሪዝ የምታንጨባርር፣ መብራት ሲጠፋ የምትበራ፣ ሞቅ ሲለኝ ጠብቃ የምትደውልና “ስሞትልህ ግጥም አንብብልኝ” እያለች የምትስቅ ልጅ ትስበኝ ነበር። “የጥበብ ሰው አስተዋይ ነው” በማለት ራሷን ለጅንጀና ያመቻቸች ሴት ትስበኝ ነበር። “የእንትናን መድበል አነበብክ ዎይ? ሳድስ ያበዛል እንጅ፣ እንዴት ጎበዝ መሰለህ” እያለች፣ ጥቁር ማኪያቶ… ከካፌ ጠረጴዛ ወደ ከንፈሬ የሚያደርገውን ተንሳፋፊ ጉዞ በጨዋታ የምታቋርጥ አይነት ልጅ ትመቸኝ ነበር… ነበር…የኔ ተንከሲስ መጣችና ምርጫዬን ፐወዘችው! ብዙ ከተዜመላቸው ወገን ናት። ጠይም መልከ መልካም፣ ዐይኗ ጎላ ያለ። ካልከፋት አትስቅም። አይከፋትም ደግሞ። ህይወትን እንደ ቼዝ በስሌት ነው
የምትጫወታት። በአንድ ቢጫ ረፋድ፣ ካፌ ዘና ብላ ስፕራይት እየጠጣች ነበር።
በመሃል ስልኳ ጠራ። ቀጥሎ ያደረገችው ፈፅሞ የማይጠበቅ ነው በውነቱ አነሳችዋ ስልኳን! የደወለችላት ጓደኛዋ ምን እንዳለች እንጃ… እንዲህ መለሰች…“ኤዲያ… ግጥም ደግሞ ምን ያደርጋል? ስጠላ!” በያዝኩት መፅሄት አስመስዬ ፈገግ አልኩ… ደስ አለቺኝ… ስልክ አናግራ ስትጨርስ ሄድኩና አጠገቧ ወንበር ሳብኩ…“ሰዓት ይዘሻል የኔ እህት?” “ሃሃ ይቺ ሙድ አልፎባታል… አልሰማህም?” “የመረጥኳት ለምን ሆነና? ይገርምሻል ብዙ ጀንጃኞች ያለፈባቸውን አባባሎች አቅም አሳንሰው ያያሉ… እና አዲስ አቀራረብ ለመፍጠር ይንገላታሉ… ድከሙ ሲላቸው!” “ጋሽ ምኒሊክ ወስናቸውን ታውቃቸዋለህ?”
“አዲስ ጅንጀና ከመፍጠር የተረሱትን መልሶ መጠቀም አይሻልም ብለሽ ነው?”
“‘የእንጆሪ ፍሬ’ የሚል ውብ ዘፈን አላቸው… እንዴት ያምራል መሰለህ… ለምን እንደተዜመ ብነግርህ አታምንም”
ምን ዓይነቷ ቀውስ ላይ ጣለኝ ዛሬ ደግሞ… አልኩና፣ እንደ ስምንተኛው ንጉስ በግራ እጄ አማተብኩ… “ሃይማኖት እባላለሁ… ሰባት ተኩል ሊሆን ነው…” እንዲቹ እየተደናቆርን ሁለት አመት አብረን ቆየን!
____
ሁለት መሃንዲሶች ወዳጅ ቢሆኑ አይሰለችም? ስለምን ሊጨዋወቱ ነው? ስለምን ዝም ሊባባሉ ነው? የተግባቡ ሰሞን ስለ አገራቸው መንገዶች ጥራት
መጓደል ያወሩ ይሆናል። ምናልባት በእርዳታ ብር ተጀምሮ፣ በዘረፋ ሰበብ ስለተጓተተ ‘ደረጃውን የጠበቀ’ መንገድ ያወሩ ይሆናል፣ ያ ሲሰለቻቸው ተማሪ
እያሉ ስለወሰዱት ‘ብሪጅ’ የተባለ ኮርስ ይወያዩ ይሆናል… ከዛስ? “መንገድ ዐይኑ ይጥፋ አይባልም ደርሶ የወሰደውን ሰው ያመጣል መልሶ” ይሉ ይሆናል አንዳቸው
“አቦ ባለፈው አወራንበት እሱን… አዲስ ጨዋታ የለም?”
_
እኔና እሷን ሁለት አመት ያኖረን ልዩነት ነበር። ግጥም ደስ ይለኛል። ግጥም ያስቃታል። ካልከፋት የማትስቀው ጉድ ግጥም ሳነብላት ትስቃለች። ግጥሙ
እያስከፋት ይሆናል እንግዲህ። ተናዳ ከሆነ ደግሞ ግጥም ይበልጥ ያበግናታል። ሁለት አመት ያጣመረን ልዩነትም ሰለቸን መሰል ጭቅጭቅ አመጣን። ጥንዶች ጭቅጭቅን ችለው የሚቀጥሉት አብረው ስለሚተኙ ሳይሆን አይቀርም። እሱም እስኪሰለች። በሆነ ባልሆነው እየጨቀጨቀች አንጎል አደረገችኝ። ለንዝንዟ ምላሽ ባለመስጠት አበሳጨሁዋት። ባንድ ክፉ ማክሰኞ ከንቅልፏ ተነሳች፣ ከአልጋችን ወረደች፣ ፊቷን ታጠበች፣ ጥርሷን ቦረሸችና ጀበና ወርውራ ሳተቺኝ… በስመአብ! ከየት አመጣችው? ሰው ‘የሚፈነከት አይጠፋም’ ብሎ፣ ጀበና ገዝቶ ይደብቃል? ደሞ ሰው በጀበና ለመፈንከት ጥርስ መቦረሽ ያስፈልጋል? እንደ ዲስከስ ወርዋሪ በቅንፍ ቅርፅ ነበር
ጀበናውን የወረወረችው፣ ስቶኝና ግድግዳውን ነርቶ፣ ስብርባሪዎቹ ወደ መሬት ሲወድቁ፣ አንድ ኮሜዲያን ስለ ፍቅርና መዋደድ የተናገረውን እያሰብኩ ነበር… “የምን ፍቅር? መዋደድ ይበቃል! ፍቅር መጨረሻው ጠላትነት ነው! ”በድርጊቷ ተናደድኩ! እንዴት እንደምጎዳት እያሰብኩ፣ ስንደረደር ወደ ጆሮ ግንዷ ተጠጋሁና፣ ሁለት መስመር ግጥም አነበብኩላት… አለቀሰች ተለያየን።
_
ጊዜአት አለፉ… ድንገት የተገናኘነው ከሶስት ዓመት በኋላ ነበር። አምሮባታል። ሲፋቱን የሚያምርባቸው ነገር አለ። የማይታመን… እየሳቀች ነበር! ልቦለድ ፀሃፊ ጠብሳ ይሆናል እንግዲህ። “አ……ንተ…?” አለች እየሳቀች… “እንዴት ነሽ?” “ደህና ነህ? አገባህ? ደህና ነህ? አዲስ ጀበና ገዛህ ዎይ?” “አሃ… ያኛውንም አንቺ ነበርሽ እኮ የገዛሽው… ረሳሽ?” “ያ ይሆናል… ደህና ነህ?” “አለሁ” “በቃ ቻው… ስብሰባ አለብኝ… ልሂድ” እየተራመደች ስትርቀኝ… ከተለያየን ጀምሮ ሲከነክነኝ የኖረ ጥያቄ ታወሰኝ…
“እኔ ምልሽ?”
“ወዬ”
አለችና
ተመለሰች…
“ጋሽ ምኒሊክ ወስናቸው ‘የእንጆሪ ፍሬ’ን ያዜመው ለማን ነበር?”
“ለእውነት”
“የምርሽን?”
“በእውነት!”

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Yonas Angesom Kidane
2024/09/24 06:26:37
Back to Top
HTML Embed Code: