Telegram Web Link
ከክልሎቻችን የሚሻለው እስር ቤታችን
(አሳዬ ደርቤ)
ባንዲት አገር ውስጥ ተቻችለው ለመኖር የተቸገሩ ፖለቲከኞች በገባቸውና ባልገባቸው ምክንያት በቁጥጥር ስር ውለው በአንድ ክፍል ውስጥ ታድመዋል፡፡ ከእነዚህም መሃከል እስክንድር ነጋ፣ በቀለ ገርባ፣ ጃዋር መሃመድ፣ ኢንጂነር ይልቃልና ስንታየሁ ቸኮል ይገኙበታል፡፡ (መንግሥት አቀላቅሎ ያሰራቸው ሁለቱ ሕዝቦች በአንድ አገርና ክልል ቀርቶ በአንድ ክፍል ውስጥም መኖር እንደሚችሉ ለማሳየት ሳይሆን አይቀርም፡፡)
.
የሆነው ሆኖ እስረኞቹ ከተከላካይነትና ከአጥቂነት ስሜት ጸድተው፣ ተረኛና ነፍጠኛ መባባላቸውን ትተው… ለአንዱ የመጣውን ምግብ በጋራ ይበላሉ፡፡ እርስ በእርስ እየተቀላለዱ መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ስቀውት በማያውቁትን ሳቅ እስር
ቤቱን ያደምቁታል፡፡ ከጃዋር ውጭ ያሉት አብዛኞቹ ተጠርጣሪዎች ሲታሰሩና ሲፈቱ የኖሩ በመሆናቸው ያሉበትን ሁኔታ ለመበቀል አላዳገታቸውም፡፡ በተለይ ደግሞ እስክንድር ለተወሰነ ጊዜ ያህል ባለቤቱን እና ልጆቹን ጎብኝቶ ከመመለስ ባለፈ ተፈትቶ አያውቅም፡፡ እሱ ግን በዚህ አባባል አይስማማም፡፡ ‹‹መቼ ታስሬ ነው የምፈታው?›› በማለት የእሥራትን ትርጓሜ ከፍርሐት ጋር ያዛምደዋል፡፡
.
እስረኞቹ የሚተኙት ተደራራቢ በሆኑ አልጋዎች ላይ ነው፡፡ በመሆኑም ይሄን ቀደዳ ልጽፍ ወደ ክፍላቸው ስገባ ከጃዋር ስር ካለው አልጋ ላይ እስክንድር ተኝቶ ነበር፡፡ ከይልቃል ስር ካለው አልጋ ደግሞ በቀለ ገርባ ጋደም ብሏል፡፡ በቄ አብሮ ለመኖር እንጂ አብሮ ለመታሰር የሚመች ሰው በመሆኑ በየደቂቃው የሆነ ቀልድ እያወራ ያዝናናቸዋል፡፡ በዚያን ቀንም ናፕ ለመውሰድ አስበው አረፍ ከማለታቸው ‹‹የአማራ የበላይነት እዚህ ድረስ ተከትሎን መምጣቱ ያሳዝናል›› ማለት ጀመረ፡፡ ‹‹እኮ እንዴት?›› ተብሎ ሲጠየቅም ‹‹ከእኔ በላይ ያለውን አልጋ የተቆጣጠረውን ሰው አታዩም እንዴ?›› በማለት ወደ ኢንጂነር ይልቃል አልጋ ሲያመለክታቸው መተኛታቸውን ትተው መሳቅ ጀመሩ፡፡ በሳቁ መሃከልም እስክንድር ጣልቃ ገባና ‹‹እኔስ ምን ልበል?›› የሚል ጥያቄ ሲያቀርብ ‹‹አንተ ደግሞ ምን ሆንክ?›› በማለት በቀለ ጠየቀው፡፡ ‹‹አትላስ ከተሸከማት መሬት በላይ የሚከብድ መንግሥት ተሸክሜ ነው እኮ የማድረገው›› ብሎ ወደ ጃዋር አልጋ በጣቱ ባሳያቸው ጊዜም የቀዘቀዘው ሳቃቸው እንደ አዲስ ተሟሟቀ፡፡ ጃዋርም በእስክንድር ወሬ ሲስቅ ከቆየ በኋላ ‹‹እስኬው ለካ እንዲህ ተጫዋች ነህ እንዴ?›› በማለት ሲጠይቀው ‹‹ታዲያስ! ተከትየህ የመጣሁት እኮ ጨዋታ አዋቂ መሆኔን የሚያውቀው መንግሥት ጃዋርን አጫውትልኝ ስላለኝ ነው›› የሚል መልስ በመስጠት እያሳቃቸው ሳለ የክፍላቸው በር ተከፈተና አዲስ እንግዳ ገባ፡፡ የእንግዳውን ማንነት ሲመለከቱም ሁሉም ከአልጋቸው ላይ ተነስተው በጭብጨባና በጩኸት ተቀበሉት፡፡
.
ይሄም እንግዳ አቶ ልደቱ አያሌው ሲሆን ከክፍሉ በር ላይ ቆሞ በጭብጭባና በፈገግታ የተቀበሉትን ጓዶች ሲመለከት እሥር ቤት ሳይሆን ቤተ- መንግሥት
የገባ መሰለው፡፡ ከሰላምታ በኋላም ‹‹በምን ጥፋት ተጠርጥረህ ነው?›› አለ ጃዋር ለመሳቅ እየተዘጋጀ፡፡ ‹‹ደብረ ዘይት ላይ ቄሮዎችን አደራጅቼ ብጥብጥ ላስነሳ ስል…›› በሳቃቸው አቋረጡት፡፡ ‹‹ለሁለት ወራት ያህል አብረን ልንከርም ነዋ?›› እስክንድር ተናገረ፡፡ ‹‹ከዚያ በኋላስ?›› ጃዋር ጠየቀ፡፡ እስኬውም ‹‹ከዚያ በኋላማ መስከረም ሰላሳ ስለሚደርስ በመንግሥት የማይታዘዙትን ፖሊሶች ተከትለን ወደ ቤታችን እንሄዳለን›› የሚል መልስ በመስጠት ጃዋርና ልደቱን ሲተርባቸው በቄ ሳቁን አቋርጦ ‹‹ወደ ቤታችን ሳይሆን ወደ ቤተ-መንግሥታችን ተብሎ ይስተካከል›› የሚል እርማት ሰጠ፡.በተደረገለት አቀባበል የመዝናናት ስሜት የተሰማው አቶ ልደቱም ‹‹በሉ አልጋየን አሳዩኝና አረፍ ልበል›› ብሏቸው ወደ ውስጥ ሊገባ ሲል ‹‹የሻማ ሳትከፍል አትገባም›› በማለት በቀለ አስቆመው፡፡ በዚህም ጥያቄ ልደቱ ግር እየተሰኘ ‹‹መብራት የለም እንዴ?›› የሚል ጥያቄ ሲያቀርብ ‹‹ሰውዬ ፖለቲካ እያወራህ ከመንግሥት ጋር አታነካካን›› እያሉ ኪሱን ይዳብሱት ጀመር፡፡

@wegoch
@wegoch
@paappii
የባለቅኔው (የገጣሚው) ድምፅ
#ክፍል አንድ
ለጋስነት በልቤ ውስጥ ተዘርታለች፡፡ ክምር ስንዴ አመረትኩ፤ ለተራቡም አካፈልኩ፡፡
ነብሴ ለወይን ፍሬ ሕይወት ትሰጣለች፡፡ ወይኑን ጨምቄ ለተጠሙ አጠጣሁ፡፡
ፋኖሴን ዘይት ሞልቼ መስኮቴ ላይ አኖርኩ፡፡ በጭለማ ለሚጓዙ እንግዶችም መንገዱን አበራሁ፡፡
ይህንን ሁሉ የማደርገው በእነዚህ ድርጊቶቼ ውስጥ ስለምኖር ነው፡፡ የህይወት እጣ ለጋስ እጆቼን ብታስርብኝ ሞትን እመርጣለሁ፡፡ ገጣሚ ነኝና መለገስ ካልቻልኩ ፈፅሞ አልቀበልም፡፡

የሰው ልጅ ቁጣ እንደ አውሎ ነፋስ ያጓራል፡፡ እኔ ግን በዝምታ እተነፍሳለሁ፡፡ ምክንያቱም ትንፋሼ ፈጣሪ ጋር ሲደርስ ወጀቡ በሙሉ ይቆማልና፡፡
ሰዎች ምድራዊ ነገሮች ላይ ይንጠለጠላሉ፡፡ የእኔ መሻት ግን የፍቅር ችቦ ናት፡፡ በብርሃኗ የልቤን ኢ-ሰብአዊነት ታነፃልኛለች፡፡
ሰዎች በዘር፣ በቀለምና በሃይማኖት ተከፋፍለዋል፡፡ እኔ ደግሞ በሁሉም አገር እንግዳ ነኝ - ከየትኛውም ወገን አይደለሁም፡፡
ሥነ-ፍጥረት( ዩኒቨርስ) አገሬ ስትሆን ጎሳዬ ደግሞ ሁሉም የሰው ልጅ ነው፡፡
የሰው ልጆች አቅመ-ቢስ ሆነውም የተከፋፈሉ ናቸው፡፡ በየጊዜው የምትጠበውን ምድር በግዛትና አገራት መሰነጣጠቅ አላዋቂነት ነው፡፡
የሰው ልጆች እጅ ለእጅ የሚያያዙት የነብስን ቤተ-መቅደስ ለማፍረስና ምድራዊ ድልድይ ለመገንባት ብቻ ነው፡፡ ብቻዬን ቆሜ እንዲህ የሚል የውስጥ ድምፄ ተሰማኝ "ፍቅር በህመም ለሰው ልብ ሕይወት እንደምትሰጥ ሁሉ ድንቁርና ደግሞ የእውቀትን መንገድ ያሳየዋል፡፡" ሕመምና ድንቁርና ወደ ታላቅ ደስታ ይመራሉ:- ምክንያቱም ፈጣሪ ከፀሀይ በታች ለሰው ልጅ መከራን አልፈጠረም፡፡

ይቀጥላል.........
#መናፍቁ ካህሊል እና ሌሎችም

@wegoch
@wegoch
@paappii
የባለቅኔው...........

#ክፍል ሁለት

ውቧ አገሬ ዘወትር ትናፍቀኛለች፡፡ ጎስቋላ ሕዝቧንም ከልቤ እወዳቸዋለሁ፡፡ ሆኖም ግን የአገሬ ሰዎች "የአገር ፍቅር" በሚሉት የአብዮተኝነት ስሜት ተገፋፍተው ጎረቤት አገር በመውረር በሰዎች ላይ ግፍ ቢፈፅሙ ሕዝቤንና አገሬን ለመጥላት እገደዳለሁ፡፡

የትውልድ መንደሬንና ያደግሁበትን ቤት እናፍቃለሁ፡፡ ሆኖም የአገሬ ሰዎች ለምስኪን መንገደኛ መጠለያ ቢከለክሉ ናፍቆቴን በመተው እረሳቸዋለሁ፡፡ ለመንገደኛ መጠለያ ያልሆነ ቤት ቢፈርስ ይሻላል፡፡ የትውልድ መንደሬን አገሬን በምወድበት ኃይል እወዳታለሁ፡፡ አገሬን ደሞ ከምዶር እኩል እወዳታለሁ፡፡

የሰው ልጅ የፈጣሪ መንፈስ ምድር ላይ የሚወከልባቸው ፍጡራን ናቸው፡፡ እነዚያ የመንፈስ ልጆች ዛሬ በፈረስ መንደር ላይ ቆመው እያለቀሱ ለልጆቻቸው የድረሱልኝ ጩኸት ያሰማሉ፡፡ ልጆቻቸው ግን የጎሰኝነት መዝሙር በመዘመርና ጎረቤቶቻቸውን መግደያ ሰይፍ በመሳል ሥራ ተወጥረው የእናቶቻቸውን የለቅሶ ጥሪ አይሰሙም፡፡

ሰብአዊነት ልጆቿን ትጠራለች፤ ሆኖም ድምጿን የሰማት የለም፡፡ አንድ ሰው የእናቱን ጥሪ ሰምቶ እንባዋን ቢያብስላት ሌሎች "ደካማ ፤ ቡቡ!" ሲሉ ይሰድቡታል፡፡

የሰው ልጅ የፈጣሪ መንፈስ መገለጫ ነው፡፡ ፈጣሪ ደግሞ ፍቅርና በጎነትን ይሰብካል፡፡ ሆኖም ይህ ትምህርት የሰዎች ማሾፊያ ብቻ ነው፡፡ የናዝሬቱ እየሱስ ያንን ስብከት በማድመጡ ተሰቀለ ፤ ሶቅራጥስ ድምፁን ሰምቶ በመከተሉ መከራ ደረሰበት፡፡ የእየሱና የሶቅራጥስ ተከታዮች በአምላክ ያምናሉ፡፡ የነርሱ አማልክት በሰው እንደማይገደሉ ስለሚያምኑ በሁለቱ ስብከት ላይ አፌዘ፡፡ ፌዝ ደግሞ ከግድያ የበለጠ መራራ ናት፡፡

ሆኖም ግን እየሩሳሌም እየሱስን፤ አቴንስ ደግሞ ሶቅራጥስን መግደል አይችሉም፡፡ ሁለቱም ለዘላለም ይኖራሉ፡፡ በአምላክ የሚያምኑ ሁሉ በፌዝ አይሸነፉም፡፡
ለዘላለም ይኖራሉ ፤ ያድጋሉ፡፡

ይቀጥላል........

#መናፍቁ ካህሊል እና ሌሎች

@wegoch
@wegoch
@paappii
የባለቅኔው........

#ክፍል ሦሥት

የሰው ልጅ በመሆንህ ወንድሜ ነህ፡፡ ሁለታችንም የቅዱስ መንፈስ ልጆች ነን፡፡ ከአንዲት ምድር የተሰራን ፍጡራን፡፡

በሕይወት ጎዳና አብረኸኝ ትጓዝ ዘንድና የእውነታን ምሥጢር እንድረዳ ታግዘኝ ዘንድ ጓደኛዬ ነህ፡፡ 'የሰው ልጅ ነህ' ይህ ለኔ በቂዬ ነው፡፡ እንደ ወንድሜ እወድሃለሁ፡፡ አንተ እንደፈቀድህ ልትናገረኝ ትችላለህ፡፡ ነገ ሲደርስ ንግግርህን እንደማስረጃ ቆጥሮ ይፈርድብሃል፡፡

ንብረቴን ልትቀማኝ ትችላለህ፡፡ ስግብግብ በመሆኔ ያካበትኩት ሀብት ካስደሰተህ ውሰደው፡፡ የፈቀድከውን ልታደርገን ትችላለህ፡፡ ነገር ግን 'እውነቴን' ልትነካት አትችልም ፡፡ ደሜን ማፍሰስ ፤ ስጋዬን ማቃጠል ትችላለህ፡፡ ሆኖም መንፈሴን መጉዳት አትችልም፡፡

እግርና እጄን በሰንሰለት አስረህ ጭለማ ውስጥ ልታሥረኝ ትችላለህ፡፡ ሆኖም ግን ነፃ አስተሳሰቤ በሰፊው ሰማይ ላይ ትንሳፈፋለችና ማን ሊያስራት ይችላል?

ወንድሜ ነህና እወድሃለሁ፡፡ ባንተ ቤተ-ክርስቲያን አመልካለሁ ፤ በመቅደስህ እንበረከካለሁ ፤ በመስኪድህ እሰግዳለሁ፡፡ እኔና አንተ የአንድ ሃይማኖት ልጆች ነን፡፡ የሃይማኖት መንገዳችን ቢለያይም መንገዶቻችን በሙሉ የአንድ ፈጣሪ እጅ ጣቶች ናቸው፡፡ የፈጣሪ እጅ ለሁላችን ሙላትና የመንፈስ ስጦታ የተዘረጋ ነው፡፡

በእውቀት ዐይኔ ባላየውም ስለ እውነታህ ስል እወድሃለሁ፡፡ የሁለታችን እውነቶች በሚመጣው ዓለም እጅ ለእጅ ተያይዘው አንድ ዘላለማዊ እውነት በመሆን ይጣመራሉ፡፡ በፍቅርና በውበት ለዘላለም ይኖራሉ፡፡

በጨቋኝህ ፊት ደካማ ፤ በስግብግብ ባለፀጋ ፊት ደግሞ ደሃ በመሆንህ እወድሃለሁ፡፡ በዚህ ምክንያት እያነባሁ አቅፍሀለሁ፡፡ ከእንባዬ ጀርባ የፍትህን እጅ አቅፈህ የፈረዱብህን ይቅር ስትል አይሃለሁ፡፡ ወንድሜ ነህና እወድሃለሁ፡፡

ይቀጥላል...........

#መናፍቁ ካህሊል እና ሌሎች

@wegoch
@wegoch
@paappii
ታድለህ
(በእውቀቱ ስዩም)
.
’ስለኢትዮጵያ ዝም አንልም “ የተባለው ድርጅት ሊቀመንበር በቀደምለት በዝነኛ ተዋናይቶች ታጅቦ ባወጣው ያቋም መግለጫ እንዲህ አለ:-
“ አርቴፊሻል የወንድ ብልት መጠቀም፤ ራስን በራስ ማርካት እና የአፍ ዝሙት በወንጀል ህግ እንዲካተት (መንግስትን ) እንጠይቃለን “
ገራሚ ነው!
“ ራስን በራስ ማጥፋትም ፤ ራስን በራስ ማርካትም ተከልክሎ እንዴት ነው የሚኖረው? አለ ጉዋደኛየ በየነ ይህንን መግለጫ የሰማ ቀን::
እኔ እምለው! አንዲት ላጤ ሴት ፤ ብቸኝነት ሲቀፈድዳት ኳረንቲን ሲያዝጋት : አልፎ አልፎ ራሷን ብታረካ ምን ጣጣ አለው? ! በርግጥ በወንዱ ጉዳይ ላይ በስሱም ቢሆን እስማማለሁ!! በየቀኑ ደከመኝ ስለቸኝ ሳይል “የሚመታ “ ጎረምሳ፤ በዘር ማጥፋት ወንጀል ቢከሰስ ችግር የለብኝም ! አንዲሁም፤ ራሱን በራሱ ለማርካት አንድ ደርዘን ሳሙና የሚፈጅ ጎልማሳ ያገር ሃብትን አላግባብ በማባከን ቢከሰስ ሲያንሰው ነው!
ግን አንድ ሰው ምኝታቤቱን ዘግቶ ብቻውን ለሚሰራው ስራ ከሳሹ ማን ሊሆን ነው? ምናልባት፤ጎረቤቱ?
ከገዛ እጁ ጋራ ሲዳራ ፤ እጅ ከፍንጅ ተይዞ ልደታ ፍርድ ቤት የሚቀርብ ተጠርጣሪ በአእምሮዋችሁ ሳሉት ፤
ዳኛው “ ጎረቤትህ ሴጋ ሲመታ በቀዳዳ አይቸዋለሁ ብሎ መስክሮብሃል፤ በዚህ ጉዳይ ምን ትላለህ?’
“ ክብር ፍርድቤት! ሽንቴን ከሸናሁ በሁዋላ ዘለግ ላለ ጊዜ ሳራግፍ አይቶኝ ይሆናል እንጂ እንዲህ አይነት ድርጊት ለመፈፀም አስተዳደጌ አይፈቅድልኝም" አርቴፊሻል የወንድ ብልትን አቅርቦትንስ መንግስት በምን መንገድ ነው መቆጣጠር የሚችለው?!
ማህበሩ በዚህ ጉዳይ ላይ ከወዲሁ ቢያስብበት ጥሩ ነው! ምናልባት ፤ፌዴራል ፖሊስ በላጤ ሴቶች መኖርያ ቤት ውስጥ ድንገተኛ ብርበራ ሊያደርግ ይችላል!
ከዚያ ፖሊሱ ከተጠርጣሪዋ ሴት ራስጌ የሆነ ነገር ጎትቶ እያወጣ
“ አንቺ ይሄ ምንድነው?
“ ያልጋው አምስተኛ እግር ነው!! ኮንስታብል"
" ካልጋው ጋር እንዴት አልተገናኘም ታድያ?"
" በ wirelessም ይሰራል"
ሌላው በወንጀል ህግ እንዲካተት የታጨው ተግባር “ኦራል ሴክስ “ ወይም በማህበሩ አጠራር "ያፍ ዝሙት" ነው!
ወደፊት የሚሆነውን አስቡት! ማለዳ ላይ አንድ ጨዋ ዜጋ ባቅራቢያው ወደሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ጎራ ይልና፤
“ ወንጀል ፈፅሜ ፤ በፈቃዴ እጄ ልሰጥ ነው የመጣሁት” ይላል፤
ተረኛው ፖሊስ ;-“ የሰራኸው ወንጀል ምንድነው?”
ወጣቱ “ ትናንት ማታ ፍቅረኛየን አስዘፍኛለሁ "
ይሄኔ ፖሊሱ ምን ይላል

@wegoch
@wegoch
@wegoch
የባለቅኔው........

#ክፍል አራት

ወንድሜ ሆነህ ሳለህ ለምን ትጣላኛለህ? ክብር የሚሹ አለቆችህን ለማስደሰት ብለህ ለምን አገሬን በመውረር ታንበረክከኛለህ? ሚስትና ልጆችህን ጥለህ በደምህና በእናትህ እንባ ክብርና ሥልጣን ለሚገነቡ ሰዎች ስትል ስለምን ደምህን ለማፍሰስ ወደሩቅ አገር ትሄዳለህ?

ወንድም ወንድሙን ቢገድል ክብር ይሆንለታል? ከሆነ ደግሞ ወንድሙን ሊገድለው ቃዬል ሃውልት ሊቆምለት ይገባል ማለት ነው፡፡

"የመኖር ጉጉት የሌሎችን መብት እንድንነጥቅ አስገድዶናል" በማለት የምታምን መሪ ወንድሜ ሆይ ስማ፡፡ የሌሎችን መብት ማስከበር እጅግ ታላቅ ተግባር ነው፡፡ የእኔ መኖር ሌሎችን በመግደል ላይ የተመሰረተ ከሆነ ሞቴን እመርጣለሁ፡፡ የሚገድለኝ እንኳን ባጣ ከዘላለማዊነት መምጣት በፊት ለዘላለማዊነት ስል ራሴን አጠፋለሁ፡፡

ወንድሜ ሆይ #ራስ-ወዳድነት የበላይነትን ትፈጥራለች፡፡ የበላይነት ደግሞ በተራዋ ጎሰኝነትን ስትፈጥር ከጎሰኝነት ደግሞ ሌሎችን የማንበርከክ የሥልጣን ጥማት ትመጣለች፡፡

ነብስ በእውቀትና በፍትህ ታምናለች፡፡ ድንቁርናና ብዝበዛን የሚያመጣ ሥልጣንን ደግሞ ትክዳለች፡፡ ባቢሎንን ያፈረሳት ፤ የእየሩሳሌምን መሠረት ያናጋውና ሮምን ያወደማት ይኸው ሥልጣን ነበር፡፡ እኔ የማከብረው ብቸኛው ሥልጣን የተፈጥሮን ፍትህ የሚጠብቅና የሚያከብር ዕውቀትን ነው፡፡

ገዳይን በመግደልና ዘራፊን በማሰር ምን ዐይነት ፍትህ እናመጣለን? ጎረቤትን በመውረር ሕዝብን መግደልስ ምን ዐይነት ፍትህ ነው? አንድ ገዳይ ሌላውን ገዳይ የሚቀጣበትን ሥልጣን ፍትህ ምን ትለው ይሆን? ሌባ ሌላው ሌባ ላይ የሚፈርድበትንስ?

ወንድሜ ነህ እወድሃለሁ፡፡ የምወድህም በሙሉ ክብርና ፍቅር በምትገለፅ በፍትህ ስም ነው፡፡ ዘርህንና ማህበረሰብህን ሳልመለከት እወድሃለሁ፡፡ ይህንን ውዴታዬን ፍትህ ባትደግፍልኝ በውስጤ አስቀያሚ ራስ-ወዳድነት ደብቄያለሁና ከሃዲ ነኝ፡፡

@wegoch
@wegoch
@paappii
እስልምና ለምን ደስ ይልሀል ? ያላችሁኝ እንደሆን.. .
(ሚካኤል አስጨናቂ)
በእምነቴ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ተከታይ ነኝ።
ሀይማኖቴን ብዙ በመረመርኩት ቁጥር የበለጠ የእድለኝነት ስሜት ይሰማኛል።.
ያደግሁት አንድ መስጂድ እና ጥቂት ሙስሊሞች በነበሩባት ሰላሌ ፍቼ ከተማ ውስጥ ነው።
እንደውም ለረመዳንም ይሁን ለአረፋ ክብለ በዓል ጊዜ ነጭ በነጩን ለብሶ ጎልቶ የሚታየን አብድል የሚባል የዳቦ ቤት ባለቤት ብቻ ነበር። ስለ ሙስሊሞች ማወቅ እና ህይወታቸውን መከታተል የጀመርሁት ጅማ ዩንቨርስቲ ተማሪ በነበርሁበት ጊዜ ነው።
የጅማ ሙስሊሞች አክራሪ ተብለው ቢወነጀሉም እኔ በቅርበት አውቃቸው ስለነበር ትክክለኛ ማንነታቸውን እረዳው ነበር። የጅማ ሙስሊሞች እንግዳ ተቀባይና ፍቅሮች ናቸው። ከማንም ሰው ጋር ተቻችሎ ሳይሆን ተፋቅሮ ለመኖር ሀጃ የለባቸውም (አክራሪነት ህዝብ ጋር ሳይሆን መሀይማን ምሁሮች ባሉበት ብቻ የነገሰ ጣዖት ነው።
ብዙ የግቢ ጓደኞቼ ከቤት ቀርተን በበዓል ወቅቶቻችን ቅንጣት ሳይከፋን ራሳችን አርደን ባዘጋጀነው ስጋ ዘና ብለን አክብረን እናውቃለን ።
ዶሮ ወጥ ሰርተው ያበሉንን እትዬ ን ማን ይረሳቸዋል? (Wing 5 ቡና እንጠጣባት የነበረችውን ቤት ባለቤት አንድም የኪቶ ፉርዲሳ የኢንጂነሪንግ ተማሪዎች አንረሳቸውም)
እንደውም.. .
እዚህ ጋር አንዴ ታክሲ ውስጥ ያጋጠመኝን ሌላ እውነት ላጨዋውታችሁማ :)
ወሩ ታህሳስ ነበር...የጌታ ልደትን ለማክበር ሽር ጉዱ ጦፏል... ጅማ ከተማዋ በአሪቲና ጉዝጓዝ መዓዛዎች ታውዳለች። ብዙው ተማሪ ወደ ሀገሩ ተጉዞ በዓልን ሊያከብር መንቀሳቀስ ጀምሯል። ከአንድ ቀን በዓል ወከባ የማይወዱ የእኔ ቢጤዎች ደግሞ እዛ ጭር ባለ ግቢ ውስጥ ቀርተናል ...
ታክሲ ውስጥ ተሳፋሪው ሞልቶ ሊንቀሳቀስ ሲል ጀማል የሚባል ግለሰብ ገባ። በእጁ የገዛትን ዶሮ ይዟል።
"ጀማል " አለው...አንድ የአካባቢው ነዋሪ..
"ሀዬ " ብሎ ዞር አለ ...
"ዶሮዋ ምንድናት? "
ጀማል ፈገግ አለ ... (የድዱ ውቅራት ደስ የሚል ውበት አጎናፅፎታል )
"በዓል አይደል እንዴ? "
የታክሲዋ ተሳፋሪ ሁሉ በአግራሞት ጀማልን አየነው።
"እና ታድያ የክርስትያን በዓል እኮ ነው "
ጀማል ፈርጠም ብሎ መለሰ...
"አቦ ተዋ ! ፍቅር ካለ የወንድሜ በዓል ለኔ የማይተርፍበት ምክንያት የለም። ዶሮዬን ሸፍ አድርጌ ረሀ ሆኜ ማሳለፍ ነው የምፈልገው።
ገናን እወደዋለሁ ። አቦ አንተም ከቻልክ በኋላ ቤት መተህ ዱአ እያደረግን እንዋል ።"
የሰማሁትን ማመን አልቻልኩም ነበር...ድሮውንም የጅማ ሙስሊሞች ይመቹኝ ነበር...ፍቅሬ የበለጠ ጨመረብኝ።
ሙስሊሞችን ሳያቸው ነጠላ አጣፍቶ ቤተክርስትያን የሚሄዱ ክርስትያኖች ያህል ይቀሉኛል።
ሀይማኖታቸው ...ስርዓት አለው። ስርዓትና ምግባር በኦርቶዶክስ ቤት ብቻ ሳይሆን ሙስሊሞችም ጋር ያለ ስለሆነ እወዳቸዋለሁ ። አብዛኛው ሴቶቻቸው እንደ እሳት ሰንሰለት የሚጋረፍ ውበት ቢኖራቸውም ለማንም የማይገለጥ ምትሀት እንደሆነ አውቃለሁ። እንደው ለአንድ ቀን ፊትን ሸፍኖ መንቀሳቀስ ቢታገዱና ብናያቸው ኢትዮጵያ ውስጥ የህንድ ሴቶች ሊወሩን መተዋል የምንል ይመስለኛል 😃
ባሎቻቸው ያንን ለህዝብ የተሸሸገ ውበት ቤታቸው ውስጥ ገላልጠው እያዩ ሚስታቸውን ከጎናቸው ሸጉጠው ጋደም ሲሉ ምን ይሰማቸው ይሆን?
እኔ በግሌ ለአንድ የኦርቶዶክስ ቤተመቅደስ ያለኝ ክብርን ያህል ለሙስሊም መስጂዶችም ክብር አለኝ። እንደው ለአመል ያህል በአፌ ቧልት እያወራሁ የምጓዝ እንኳ ቢሆን መስጂድ ደጆች ላይ ስደርስ ሀፍረት ይሸብበኛል።
ሰዎች በስሜታችን የከፋፈልነው ነገር እንጂ ፈጣሪ ለሁላችንም ፀሎትና እምነት ዋጋ እንደሚሰጥ ይሰማኛል።
አቦ በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ

@wegoch
@wegoch
@wegoch
‹‹እንደትዳር ደባሪ ነገር የለም ››
(አሌክስ አብርሃም)
‹‹በእኔና አንተ መሃል ይቅር እንጅ እንደትዳር ደባሪ ነገር የለም ›› ትለኛለች!
ድንገት በአጋጣሚ ደውላ እያወራንኮ ነው! ድል ባለ ሰርግ ካገባች ገና አንድ
ዓመቷ !
‹‹ምነው ባለቤትሽ ጋር ሰላም አይደላችሁም እንዴ ?››
‹‹አንዱ የትዳር ደባሪ ነገሩኮ እሱ ነው …ሰላም ሁን አትሁን አታውቀውም ፀብ
የለም ግን ትበሳጫለህ ›› ትነጫነጫለች !
‹‹ምን ሆንሽ አሪፍ ልጅ ነው ያገባሽው... ማለቴ አይጠጣም ፣አያጨስም ፣
አይቅምም ፣ ፌስቡክ አይጠቀምም፣ እና ሌላ ሴት ቀና ብሎ አያይም
ይወድሻል.... ››
‹‹ኡፍፍፍ ባልቴቶች እንደሚያወሩት ነው የምታፅናናኝ! …ታውቃለህ ?
….መጀመሪያ ልትጋባ ስትወስን የሆነ በቃ ግርግር ነው ….ሚስት መሆን የሆነ
አስማት ነገር ይመስልሃል ፣በምድር ላይ ካሉ ሴቶች ሁሉ በሆነ ተዓምር ተለይተህ
የተመረጥክ ነገር … ትዳር ከውጭ ሁነህ ስታስበው ውስጡ እንጀሆቫ ዊትነስ
መፅሄት አበባ ወንዝ ልጅህን ቸቸ ብለው የሚያጫውቱ አንበሶች… ቁርስ
የሚያቀርቡ ነብሮች ምናምን ያሉበት ይመስልሃል ! …
ከዛ ሰርግ አለ …ግርግሩ ድግሱ ልብስ መግዛቱ ሰው መጥራቱ በቃ የሰማው
ሰው ሁሉ ልታገባ ነው ምናምን ለወግ ማረግ በቃች እያለ ማውራቱ … ቬሎው
ፎቶው ፍሸናው …ሚዜው አጀቡ ልእልት የሆንክ ነው የሚመስልህ …ከዛ ደግሞ
ምላሹ አለ …ባህላዊ ቅራቅምቦው ቅሉ ፎሌው ሞሰቡ ሹርባው … ስትመላለስ
የምትኖር ነው የሚመስልህ… ከዛ በኋላ በቃ ራት የትም ስትጠራ መድረክ
የሚዘጋጅልህ ነገር ….ጫጉላ አለ … ከተሳካልህ ወጣ ብለህ ምናምን ቱሪስት
የሆንክ መስሎ እስኪሰማህ …ቀለበት መንገድ ላይ መኪና ኮፈን ላይ ቁመህ
እንደታይታኒክ ተቃቅፈህ እጅህን መዘርጋት ሁሉ ይቃጠሃል... ያገኙህ ሁሉ አዲስ
ተጋቢ መሆንህን ሲያውቁ ፈገግ ይሉልሃል …
ተጋብተህ በመጀመሪያወቹ ሳምንቶች ገና ከማሸጊያቸው የወጡ አዳዲስ
ፒጃማዎች ፣ ሽቶዎች ከቤትህ አይጠፉም …ጧት ስትነሳ ፈገግታው …በቃ
ስትወጣ አዲስ ተጋቢዎች ናቸውኮ ምናምን መባሉ …ፊልም ላይ ያየሀቸውን
ፊክሽን ላይ ያነበብካቸውን የፍቅር ሲኖች የምትደግም ነው የሚመስልህ …ጧት
ቁርስ መስራቱ … የስጦታ አዲስ ሰሃን ፣ የስጦታ አዲስ ብርጭቆ ፣ የስጦታ
አዲስ ማንኪያ …ሁሉ ነገር አዲስ ነው …ሲም ካርድህ ሁሉ አዲስ ሊሆን
ይችላል ! መሸት ሲል የስጦታ አዲስ ጋቢ ጣል አድርገህ ሶፋ ላይ ….ባል ከውጭ
ሲመጣ ለማስደመም ምናምን ቡና ማፍላት … ያሳለፍከውን ታሪክ ማውራት
ከዛስ በለኝ ….
ከዛስ?
በቃ ትዳር ማለት.... ጭርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርር
ርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርር
ርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርር
ርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርር
ርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርር
ርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርርር
ጓደኞችህ ራሱ የታባታቸው እንደሚጠፉ ግራ ይገበሃል …የሆነ ባል ሳይሆን
የሚናከስ ውሻ ያገባህ ይመስል እነዛ በቀን ስድስት ጊዜ የሚደውሉ ጓደኞችህ
ድራሻቸው ነው የሚጠፋው ‹‹ስፔስ እንስጣችሁ ብለን ›› ምናምን ይሉሃል !
ስፔስ አባታቸው ይውጣ !… ባገባና ባላገባ መካከል ክላስ መፈጠሩ ነው እንጅ …
በእውነት መገፋት ሁሉ ነው የሚሰማህ ! ባንዴ ያረጀህ እስኪመስልህ !
‹‹ፍቅር ካለ …››
‹‹ኦፋ …ፍቅር ትላለህ እንዴ? ቀለበቱ ጣትህ ላይ ሲገባ ፍቅር ከልብህ ላይ ክንፍ
አውጥቶ ነው የሚበረው መሰል …ባልህ ራሱ ታላቅ ወንድምህ ነው
የሚመስልህ ! በቃ የሆነ ስልችት ይልሃል …‹‹ሃኒ ከረቫቴ የት ነው …ሃኒ
ሰማያዊው ሸሚዜን የት አደረግሽው …ሃኒ እስኪ ደውይልኝ ስለኬን የት አደረኩት
…. ሃኒ ቻርጀር ወሰድሽ እንዴ ….ሃኒ ዛሬ ያየሁት ህልም …ሰፊፊፊፊፊፊፊፊ ባህር
ይመስለኛል …..በቃ ህልም ፈች ሁሉ ትሆናለህ! አልጋ ላይ ራሱ እንደበፊቱ
አትሆንም … መሄጃ ስለሌለህና አንድ አልጋ ላይ ስለምትገናኝ ስራ ከምፍታት
ምናምን ብለህ እንጅ ይሰለችሀል …ደግሞ ሙቀቱ …ባል ጋር ሲሆን ሰሀራ ነው
የሚሆነው አልጋው !
ከቤት ስትወጣ ‹‹ዋው ትዳር ተስማምቶሻል›› ለመባል እንደበፊቱ ብድግ ብለህ
አትወጣም! ለማማር ፍዳህን ትበላለህ ! ቁርስ ፣ ምሳ ፣ራት …መተኛት …ከዛ
ቁርስ ምሳ ራት …ከዛ ቁርስ ምሳ ራት … ወክ ! ከዛ ቁም ነገር ቁም ነገር
ማውራት …ሶፋ ብንቀይር …ሌላ ቤት ብንከራይ …ዕቁብ ገብተን የሆነች ከከተማ
ወጣ ያለች ቦታ ብንገዛና ሰርቪስ ነገር ብንቀልስ …አይ እዳው ያለቀ
ኮንዶሚኒየም ብንገዛ …ምናምን ማለት ትጀምራለህ …ስትወጣ ቦርሳና ጥላ
መያዝ ትጀምራለህ ! ወይ ታረግዛለህ እርፍ !! ሌላ ረዥም የገንፎና የዳይፐር ወሬ
….
‹‹እና ምን ተሻለ… ?››
በቃ የሆነ ጊዜ ላይ ድንገት በደረቅ ሌሊት ተነስተህ የድሮ ቦይ ፍሬንድህን ቀልድ
እያስታወስክ መሳቅ ትጀምራለህ …ወይ ደግሞ ያበሳጨህን እያስታወስክ
ትረግመዋለህ ! ‹‹እግዜር የኔን ቀን ይስጠው ,,,አዳልጦት ትዳር ውስጥ ይግባ
፣አልጋው ሰሀራ ይሁንበት›› እያልክ ! እንዲህም እያልክ ግን አሁን ማን ጋር ይሆን
እያልክ መቅናት ልትጀምር ሁሉ ትችላለህ … በቃ እዚህ ፌዝ ላይ ስትደርስ
ፌስቡክ ላይ መጀመሪያ ሰርች የምታደርገው የድሮ ቦይፍሬንድህንና ጓደኞችህን
ስታተስ ነው …
እኔ የምልህ አንተ ግን እንዴት ነህ ?… ያሳለፍነው ጊዜ ትዝ ይልሃል ወይስ
ረስተኸዋል …?
‹‹አሁን ነው ማምለጥ! ›› እላለሁ !

@wegoch
@wegoch
@paappii
#ማጠቃለያ

ነብሴ በሃዘኔ ወቅት አፅናኝ የልብ ወዳጄ ነው፡፡ ነብሱን ወዳጁ ማድረግ የማይችል ሁሉ የሰብአዊነት ጠላት ነው፡፡ የሰብአዊነትን መሪነት ያላገኘ ደግሞ ይጠፋል፡፡ ህይወት የምትፈጠረው ከውስጣችን እንጂ ከአካባቢያችን አይደለም፡፡

አንዲት ቃል ለመናገር መጥቻለሁ፡፡ ሆኖም ግን ሞት እስትንፋሴን ቢያቋርጣት ቃሌ ነገ ትናገራለች፡፡ ምክንያቱም ነገ ምሥጢርን በዘላለማዊነት መፅሐፍ ላይ አትተውምና፡፡

የፈጣሪ ነፀብራቅ በሆነ ብርሃንና ፍቅር ሥር ለመኖር መጥቻለሁ፡፡ ሰዎች ሕይወቴን ሊያጠፏት አይችሉምና እየኖርኩ ነው፡፡ ዐይኖቼን ቢያወጧቸው እንኳን የፍቅርና የውበትን ዜማ ጆሮዎቼ ይሰማሉ፡፡
ጆሮዎቼን ቢደፍኗቸው ደግሞ የተፈጥሮን ውብ ልስላሴ በመዳሰስና መዓዛውን በማሽተት እደሰታለሁ፡፡

ባዶ ቤት ውስጥ ቢያስሩኝ እንኳን የፍቅርና የውበት ልጅ ከሆነችው ነብሴ ጋር እኖራለሁ፡፡

እዚህ የመጣሁት ለሁሉምና ከሁሉም ጋር ለመሆን ነው፡፡ ዛሬ በብቸኝነት የማደርገው ነገር ሁሉ ነገ ደግሞ ለሁሉም ሰው ያስተጋባል፡፡

<< ዛሬ በአንድ ልብ የምንናገር ነገ በብዙ ልቦች ይነገራል>>


📯📜📯📜አለቀ📯📜📯📜

#መናፍቁ ካህሊል እና ሌሎች

@wegoch
@wegoch
@paappii
አምስት ሆነን እራት እየበላን ሳለ ከቀጠሮው ሰአት አርፍዶ ስድስተኛው መጣ።
ከመቀመጡ ቢራ እያዘዘ ስላረፈደበት ሁኔታ ማስረዳት ጀመረ።
"አታምኑኝም ከማን ጋር እንደነበርኩ" ሲል ጀመረ።
ከዚያም ማስታወሻ ደብተሩን አወጣና "እከሊት ናት የፃፈችልኝ" ብሎ በሚያምር
የእጅ ፅሁፍ የተፃፈ አንድ ገፅ ፅሁፍ አሳየን። ፅሁፉ ላይ ልጅቷ ምን ያህል
እንደምትወደው የሚገልፅ ሃተታ ይገኛል። ልጅቷን በስምና በመልክ ሁላችንም
እናውቃታለን።
"ጓደኛ ነበራችሁ?" አልነው።
"አዎ ተጣብሰን ነበር። ግን የቁምነገር አይደለም። ሴክስ ላይ በጣም ጎበዝ ናት
ሞክሯት" አለን።
ወዲያውም ስልክ ተደወለለትና ወጣ። ከዚያን ቀን በኋላ ባለው ሶስት አመት
ውስጥ አይቼው አላውቅም።
በተለያየ ጊዜ ስንገናኝ ከአምስታችን አራቱ መሞከራቸውን እና የተወራው
ጉብዝናዋ እውነት እንደሆነ እና ለማንም እንደማትከለክል ተናገሩ። የቀረሁት
እኔም እድሌን እንድሞክር ተነገረኝ። የማውቃቸው ሰዎች የደረሱበት መድረስ
እንደሚደብረኝ ስለሚያውቁ የተጫነኝ አልነበረም።
ይህ ከተፈጠረና ያ የጓደኞች ስብስብ ከተበተነ ከረጅም ጊዜ በኋላ ልጀቷ በስራ
ጉዳይ እኛ ሰፈር እንደምትመላለስ አወቅሁ። ተዋወቅን እና ቀስ በቀስ ተግባባን።
ፍቅረኛሞችም ሆንን።
ነግራኝ ያላመንኩት በኋላ ሳውቅ የገረመኝ ግን ልጅቷ ወንድ ያላወቃት ነበረች።
እሷ ራሱ ሁል ጊዜ የምትተርተው ተረት አላት " ብዙ የሚበላው ልጅ ስለ መብላቱ
የማይናገረው ነው " የሚል።
በቅርቡ ልንጋባ ነው።

@wegoch
@wegoch
@wegoch

#by_Haileleul_Aph
ቦይንግ 747-8፣ ለመገጣጠም ብቻ 4 ወር የፈጀ አውሮፕላን ነው፡፡ ስድስት
ሚሊዮን የሚገጣጠሙ ክፍሎች አሉት፡፡ በተለያየ የዓለም ክፍሎች ሆነው
ከጥቃቅን እስከ ግዙፍ፣ ከመካኒካል እስከ ኤሌክትሪካል የሚያመርቱ ከ30 ሺ
በላይ ሠራተኞች ይሳተፉበታል፡፡ ከእነዚህ መካከል የሚተዋወቁት ጥቂቶች
ናቸው፡፡ ብዙዎቹ የአንዱን መኖር ሌላው አያውቀውም፡፡ በእድሜ፣ በዜግነት፣
በጾታ፣ በእምነት፣ በመልክና በዘር ይለያያሉ፡፡ የሚከፈላቸው ክፍያ ይለያያል፡፡
የሚያመርቱትም የአውሮፕላኑን አንድ ክፍል እንጂ ጠቅላላውን አውሮፕላን
አይደለም፡፡
ሁሉንም አንድ የሚያደርጓቸው ሁለት ነገሮች ናቸው፡፡ የሚሠሩት ለአንድ ኩባንያ
መሆኑና የሚሠሩበት ዓላማ አንድ መሆኑ፡፡ እነዚህን ሁሉ ስድስት ሚሊዮን
ተገጣጣሚ አካላት የሚያመርቱት ባለሞያዎች ቦይንግ ለሚባል ኩባንያ የሚሠሩ
ናቸው፡፡ ንኡስ ኮንትራት ወስደው የሚሠሩት እንኳን ለዚሁ ኩባንያ እንደሚሠሩ
ያውቃሉ፡፡ ሁለተኛው ነገር ደግሞ የሁሉም ዓላማ አውሮፕላን መሥራት መሆኑ
ነው፡፡ በዓይን ለማየት አስቸጋሪ የሆነቺው ብሎን ከሚሠራ ጀምሮ ትልልቁን አካል
እስከሚያመርተው ድረስ ዓላማቸው ብሎን፣ ክንፍ፣ በር፣ ሞተር፣ ጎማ፣ ወንበር፣
መሥራት አይደለም፡፡ አውሮፕላን መሥራት ነው፡፡ ያ በሰማይ ሲበር የሚያዩት
አውሮፕላን እንደየዐቅማቸው ተሳትፈው እነርሱ የሠሩት አንድ አውሮፕላን ነው፡፡
ምናልባትም የመጨረሻውን ቅርጽ ሲይዝ ብዙዎቹ ላይገኙ ይችላሉ፡፡ ይህ
የሚፈጸመው ሲያትል ፓይነ በተባለው ሜዳ በሚገኘው የቦይንግ ኤቨረት ፋብሪካ
ነው፡፡ 13.4 ሚሊዮን ኪውቢክ ሜትር የሚጠጋው ይህ መገጣጠሚያ
በፕላኔታችን ላይ ለአውሮፕላን ከተሠሩ መገጣጠሚያዎች ሁሉ መሰል የሌለው
ነው፡፡ እዚህ ቦታ አውሮፕላኑ ተገጣጥሞ የመጨረሻውን ቅርጽ ሲይዝ ብዙዎቹ
ሠራተኞቹ የሉም፡፡ በአንድ ነገር ግን ርግጠኞች ናቸው፡፡ እነርሱ ያመረቱት አካል
ተገጣጥሞ አስደናቂውን የቦይንግ አውሮፕላን እንደሚፈጥረው፡፡
ሀገር የምትገነባው እንደዚህ ነው፡፡ በየዘመናቱ፣ በተለያየ ድርሻ፣ ሞያና
አስተዋጽዖ የሚችሉትን በሚያበረክቱ ዜጎች፡፡ በአሜሪካም ይሁኑ በጃፓን፣
በአውስትራልያም ይሁኑ በካናዳ፣ በአውሮፓም ይሁኑ በእስያ፣ በአፍሪካም ይሁኑ
በዐረቡ ዓለም ለአንዲት ኢትዮጵያ በሚሠሩ ዜጎች፡፡ የሚሠሩት ሥራ እጅግ
አነስተኛ መስሎ ይታይ ይሆናል፤ ወይም ደግሞ ገዝፎ የሚታይ ጉልሕ ይመስላል፡፡
ግን ኢትዮጵያ ለምትባል አንዲት ዓላማ፣ ኢትዮጵያዊነት በሚባል አንድ ኩባንያ
ውስጥ ሆነው የሚያመርቱ ዜጎች ናቸው ኢትዮጵያን የሚገነቧት፡፡ ምናልባትም
አንዳንዶች የእነርሱ አስተዋጽዖ የመጨረሻው ሥዕል ምን እንደሆነ አላዩም፣
ወደፊት አያዩ ይሆናል፡፡ ግን በአንድ ነገር ርግጠኞች ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ በሁሉም
አስተዋጽዖ ትገነባለች፡፡
የእያንዳንዱ ቅንጣት በጥራትና በብቃት መመረት ለአውሮፕላኑ ጥራትና ብቃት
ወሳኝ ነው፡፡ እያንዳንዳችን በተሠማራንበት ቦታ የምንሠራው፣ የምናስበው፣
የምንጽፈው፣ የምንወስነው፣ የምናካሂደው ነገር ጥራትና ብቃት እንዲኖረው
ከተደረገ ሀገራችን የጠራችና የበቃች ትሆናለች፡፡ እያንዳንዱ የቦይንግ
አውሮፕላን ቅንጣቶችን አምራች ባለሞያ የሚሠራው ነገር ከሌሎች ጋር
ተጋጥሞ፣ ተስማምቶና ተዋድዶ አንድ አውሮፕላን ካልፈጠረ ሥራው ዋጋ
የለውም፡፡ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በየቦታውና በየዘመናቱ የሚሠራው ሥራ
ከሌላው ጋር ተጋጥሞ፣ ተስማምቶና ተዋድዶ አንዲት ኢትዮጵያን ካልፈጠረ
ትርፉ ድካም ነው፡፡
ኢትዮጵያን በጋራ ለመገንባት ሁላችንም መተዋወቅ የለብንም፡፡ ለአንድ ዓላማ
እስከሠራን ድረስ የትም ሆነን፣ ማንም ሆነን በግንባታው ላይ መሳተፍ
እንችላለን፡፡ አንድ ዓይነት መሆንም የለብንም፡፡ የተለያየ እምነት፣ ዘርና ፖለቲካ
ይዘን፣ በተለያየ ዘመንና ቦታ ሆነን መገንባት እንችላለን፡፡ ብቻ ለአንድ ዓላማ
እንሰለፍ፡፡ ለማፍረስ ያይደለ፣ ለመገንባት፡፡
ማንም ብቻውን አውሮፕላኑን አያመርተውም፡፡ እያንዳንዱ ባለሞያ ለአንድ ዓላማ
ተሠማርቶ በሚቻለውና በተሰጠው መጠን ይገነባል እንጂ፡፡ ኢትዮጵያም እንዲሁ
ናት፡፡ ማንም ብቻውን አይገነባትም፡፡ ሁላችንም በተሰጠን መጠንና በቻልነው
ያህል አሻራችንን እያሳረፍን እንገነባታለን፡፡
ኑ፣ በጋራ አገር እንገንባ፣ አኮብኩባ ስትበርም እንያት፡፡

@wegoch
@wegoch
@paappii

#ዳንኤል ክብረት
ምክር እስከመቃብር
(ከኣልፎ ሂያጁ ማስታወሻ የተቀነጨበ)

እንደምነሽ ሸገር
እንደምነሽ ሸገር
የቤት ኣከራየ የጋሽ ጣሰው ኣገር
እየመጣሁ ነው፡፡ወደ ኣዲስ ኣበባ እየመጣሁ ነው፡፡እናቶች
ኣባቶች ልጆች ኦርጅናሎች ሰልቫጆች! እኔ ሳልመጣ ውጊያውን
እንዳትጀምሩት ኣደራ፡፡ ኣጭርና ጣፋጭ ይሁን እንጂ
በማንኛውም ትግል ላይ ለመሳተፍ ዝገጁ ነኝ፡፡የጥይት መከላከያ
ቆብ ሹራብና ሱሪ እንዲሁም ፈንጅ የማይበትነው ጫማ
ከተሰጠኝ ኣንድ ሻለቃ እመራለሁ፡፡ኣነሰ ከተባለ ኣንዲት ኮረብታ
እቆጣጠራለሁ፡፡ በጦር ምህንድስና ላይ እሳተፋለሁ፡፡ ባሩድ
ኣገነፋለሁ፡፡ የታንክ ጎማ እነፋለሁ፡፡በሰላሙ ቀን ለሞባይል፤
በቀውጢው ቀን ለሽጉጥ ማስቀመጫ የሚሆን ሰገባ እሰፋለሁ፡፡
ይሄም ኣላዋጣ ካለ የኤፍሬም ይሳቅን ቡድን የሚፎካከር
ኣስታራቂ ቡድን ኣቋቁሜ” ኣንተም ተው ኣንተም ተው፤
ያስታረቅሁበትን ኪሴ ውስጥ ክተተው” የሚል ኣገልግሎት
እሰጣለሁ፡፡ቃሌ ነው፡፡የተናገርኩት ከሚጠፋ በቅርቡ የገዛሁት
ጋላክሲ ሙባይል ይጥፋ(በዝች ንግግር ውስጥ የተደበቀ ጉራ
እንዳለ እናንተ ሳትሉኝ ኣውቀዋለሁ)
ገና ለገና ካሜሪካ ሊመጣነው በማለት ማጅራቴን ለመመታት
እያሟሟቃችሁ ያላችሁ ዱርየዎች እንዲሁም ከዱላ የተረፈች
ማጅራቴን በማሸት ትርፍ ለማጋበስ የተሰናዳችሁ ወጌሻዎች
ተስፋ ቁረጡ ፡፡ ቤሳቢስትን የለኝም፡፡(ማጅራት መምታት ሲነሳ
ፋሲል ደመወዝ ትዝ ኣለኝ፡፡እንኳን እግዜር ማረህ ልለው ብደውል
ከዲሲ በርሮ ኣትላንታ እንደገባ ነገረኝ፡፡ለኮንሰርት ይሁን
ለስልታዊ ማፈግፈግ ኣልነገረኝም፡፡ ወይ ኣበሳ!እኛ
ኢትዮጵያውያንኮ ምስኪን ነን ፤ ኣገር በቀል- ዱላ ሸሽተን ስንሄድ
የውጭ ኣገር ዱላ ይጠብቀናል፡፡
ኣሜሪካ ሁለት ወር ስቆይ ያተረፍኩት ነገር ቢኖር ግብዣና ምክር
ነው፡፡ዲታው ቢራ ጋብዞ ወደ ኣገርቤት ይዣት የምመለስ ቦርጭ
ያወጣልኛል፡፡ቺስታው ቦርጬ እንዴት እንደምቀንስ ይመክረኛል፡፡
ኣሜሪካ ፍሪሽ የሆነ ሰው ኑሮው ምክር እስከመቃብር ነው፡፡
ከኢትዮጵያ ወደ ኣሜሪካ ገንዘብ የተላከለት የመጀመርያው ሰው
ሳልሆን እቀራለሁ?
ለምሳሌ ጺም ለመቆረጥ ኣስር ዶላር መከስከስ ነበረብኝ፡፡
ፈርዶብኝ ኣሜሪካ ስገባ ጺሜ ያለወትሮው ቶሎቶሎ ማደግ
ጀመረ፡፡ኣዲኣበባ እያለሁ ጺም ኣልነበረኝም፡፡እንዲያውም” ይሄ
ልጅ ጺሚ የሚባል ነገር የለውም ስልብ ነው እንዴ?” የሚል
ኣሜት በመንደራችን ይናፈስ ነበር፡፡ስልብ ኣለመሆኔን ለማሳየት
ኣንድ ሁለት ቀን መንገድ ዳር ሸንቻለሁ፡፡
እንደልማዴ ከቀናኝ የሚጋብዘኝ ከፈረደብኝ የሚመክረኝ ኣላጣም
በማለት Fenton መንገድ ላይ ወደሚገኝ ያበሻ ምግብ ቤት
ጎራ ኣልኩ፡፡ ኣንዱ መድረክ ላይ የሱዳን ዘፈን ይዘፍናል፡፡
ከተስተናጋጆች ውስጥ ኣንድም የሚያዳምጠው የለም፡፡ሁሉም
ሙባይሉ ላይ ኣቀርቅሯል፡፡የታደለው ከፍቅረኛው በቫይበር
የተላከለትን የክንፈር ምስል እያየ በደስታ ይዋኛል ፡፡
ያልታደለው”የትምርት ቤት ክፍያ እየደረሰብኝ ስለሆነ ቶሎ
ላክልኝ እንጅ”የሚል ካገር ቤት የተላከ መልክት እያነበበ
ተክዟል፡፡ ሌላው ግድግዳው ላይ በተንጠለጠለው ቲቪ ላይ
የሚተላለፈውን ያሜሪካ እግርኳስ እየተመለከተ ምድር ጠቦታል፡፡
ያሜሪካ እግርኳስ ቢሏችሁ እንደ ዋናው እግርኳስ እንዳይ
መስላችሁ፡፡ ኣንዱ ጠብደል ጥቁር ሙልሙል ኳስ ይዞ
ይሮጣል፡፡ሌላው ኣሳድዶ ይደርስበትና ዘርጥጦ ይጥለዋል፡፡ ለኔ
ይህ ጨዋታ ሳይሆን ህጋዊ እውቅና ያለው ኣምባጓሮ ነው፡፡
በዚህ መሃል ዘፋኙ “ከ እኔ ጋ ናችሁ?” እያለ ኣስሬ ቢጣራም
ማንም ተጉዳይ ኣልጣፈውም፡፡ ልምምድ ላይ ያለ ይመስል
ለራሱ ዘፍኖ ወረደ ፡፡ስላሳዘነኝ ባንኮኒውን እንደመቋሚያ ተደግፌ
በጥሞና ኣዳመጥሁት፡፡ድምጹ ከዛፍ ላይ ኣምፖል ያረግፋል፡፡ ቢሆንም ዘፈኑን ኣለቅጥ ያስረዝመዋል፡፡የሱን የሱዳን ዘፈን ታግሶ
መጨረስ ሱዳንን በእግር እንደማቋረጥ ነው፡፡
ጥግ ላይ ክበበው ገዳ ተቀምጧል፡፡ ወንበር ስቤ ኣጠገቡ
ተሰየምሁ፡፡ ራት ይጋብዘኛል ብየ ስጠብቅ ከራት ጋር የተያያዘ
ገጠመኝ ጋበዘኝ፡፡
ክበበው ገዳ ጎረምሳ እያለ የለቅሶ ቤት እራት ኣያመልጠው
ነበር፡፡ እንድያውም እንዲያባላኝ እያለ ቃሪያ በኪሱ ይዞ መዞር
ጀምሮ ነበር፡፡ ኣንድ ለቅሶ ላይ ታድያ እራት ሲቀርብ ክበበው
ከቤቱ ይዞት የመጣውን ቃርያ ከኪሱ ኣውጥቶ ኮርሸም ሲያደርግ
የተመለከተ የሰፈር ልጅ ወደ ኣስተናጋጆች እያጨበጨበ “እዚህ
ጋ ቃርያ ኣልደረሰኝም” ብሎ ጮከ፡፡
ኣለፍ ብሎ፤ የጃንሆይ ኣምባሳደር ዘውዴ ረታና ያሬድ ጥበቡ
ቁጭ ብለዋል፡፡ያሬድ ተራሮችን ያንቀጠቀጠ ትውልድ ሲሆን
ዘውዴ የተንቀጠቀጠው ተራራ ነው፡፡ኣሁን ዲማሚቱና ተራራውም
ባንድ ጠረጴዛ ዙርያ ተቀምው ሳያቸው ገረመኝ፡፡
ከማጅራቴ ኣካባቢ “ልትጽፍ ነው የመጣህ ኣይደል”የሚል
ሹክሽክታ ሰማሁ፡፡ወይንሸት ናት፡፡ ባለፈው ኣመት ከባህል
ቡድናችን ጋር ስትመጣ ኮከብ ድምጻዊ ነበረች፡፡ኣሁን እዚሁ
ቀርታ ኮከብ ኣስተናጋጅ ሆናለች፡፡ኣፍንጫዋ ላይ የወርቅ ቡግር
የመሰለ ሎቲ ለጥፋለች፡፡እዚህ ኣገር ሴቶች ሎቲ
የሚያንጠለጥሉት ጆሮኣቸው ላይ ሳይሆን ኣፍንጫቸው ላይ ነው፡፡
ስለወይንሸት በሌላ ምእራፍ እተርካለሁ፡፡
በሩ ኣጠገብ ተኬን ኣየሁት፡፡ ተኬ በደርግ ዘመን ካይሮ ላይ
ከጠፋው የብሄራዊ ቡድናችን ገንዘብ- ያዥ ነበር፡፡ኢትዮጵያ
ከግብጽ ጋር ባደረገችው በግጥምያ ዋዜማ ላይ በረኛውን
ጨምሮ ብዙ ተጫዋቾች ስለኮበለሉ እሱ የበረኛውን ቦታ ተክቶ
ተሰልፏል፡፡ ከተቃራኒ ቡድን የተለጋች ኳስ ወደእሱ ኣቅጣጫ
ስትመጣ በገንዘብ ቆጠራው ለምዶበት ጣቱን በምላሱ እያጣቀሰ
ሲርበደበድ ፤ ኣስራ ሰባት ጎል ገበቶበታል፡፡ (ምንጭ፡
የይድነቃቸው ተሰማ ሪፖርት)ተኬ ጉዳዩ ሲነሳበት
ያማርራል፤“ይሄ ውለታ ቢስ ህዝብ የገባብኝን ኣስራ ሰባት ጎል
እንጂ ያዳንሁትን ሰባት መቶ ጎል ኣላሰበልኝም” ይላል፡፡ካገሩ
ወጥቶ መቅረት ኣሳብ ፈጽሞ ኣልነበረውም፡፡ይሁን እንጅ ይህን
ሽንፈት ይዞ ጓድ መንግስቱ ፊት መቆም የሚያመጣውን ነገር
ኣስቦ በዛው” ነካው“፡፡
ኣሁን በሩ ኣጠገብ ቁጭ ብሎ ”ብሉ ሙን“ ቢራ ይጠጣል፡፡
የቢራ ጠርሙሱን በጥርሱ ከፍቶ ቆርኪውን ጠረጴዛ ልይ ተፋው፡፡
ቢራ መክፈቻ ቢቀርብለትም ተጠቅሞበት ኣያውቅም፡፡እግዜር
መንጋጋን የፈጠረው ሲርብህ ኣጥንት እንድትቆረጥምበት
ሲጠማህ የቢራ ጠርሙስ እንድትከፍትበት ነው ይላል፡፡ ————በበእውቀቱ ሥዩም————

@wegoch @wegoch @wegoch
ሽምቅ ውጊያ ማ ነው !

(ሚካኤል አስጨናቂ)

ዝግጅቱ ተጧጡፎ ነበር ። እኔን ጨምሮ ሁሉም የሰፈር ጓደኞቼ ከቄሮ የሚያስንቅ አጣና አዘጋጅተን ሽር ጉድ እያልን ነው። 

ደፌ ፣ ኩሜ ፣ ታሪኩ እና ይርጋለም ሽመላቸውን አስውበው ያወዳድራሉ። ከእኔ ሽመል በስተቀር የሁሉም ጓደኞቼ ዱላ በቆርኪ አክሊል ተውበው ቀጭን ልዑል መስለዋል ። ጭራሽ ደፌና ኩሜማ በሽቦ የተሰራ ፅናፅል ተሸክመው ደንበኛ የደብር ዳቆን መስለዋል :) ከሁሉም የእኔ ዱላ ብቻ ተጣሞ የአዝማሪ ማሲንቆ ይመስል የነበረው። 

ስብሰባው ተጀመረ ...

ይርጋለም ገንዘብ ያዥ... እኔ ድምፅ ባይኖረኝም የተሻለ ግጥም ይችላል በሚል እምነት ዘፈን አውራጅ...ታሪኩ ተጠባባቂ ዘፋኝ ...ደፌ የስንዴ ሽልጦ ተሸካሚ.. .ኩሜ ደግሞ የፍርኖዱቄት ዳቦ ተቀባይ😊 ሆነን ተሿሿምን ። የሹመቱ መቀያየር ፍጥነት ከብልፅግና ፓርቲ ቢያስንቅ እንጅ የሚተናነስ እንኳ አልነበረም 😂

ጭፈራው ተጀመረ.. . ጭፈራውን ደግሞ የጀመርነው ማልደን ስለነበር ብዙ ቤት ሰዓት ገና 9 ሰዓት አልሆነም በሚል ሰበብ ኩም አድርገው መለሱን። እስከ ስድስት ሰዓት በነበረው ጭፈራ ጥቂት ገንዘብና ሁለት የፍርኖ ዱቄት ዳቦዎችን አተረፍን። በጭፈራው የመክሰር ስሜት ቢሰማንም ሁለቱን ሽሌ ተከፋፍለን ስንገምጥ ወድያው ሀሳባችንን ቀይረን ፊታችን በደስታ በራ።

ጎን ለጎን እስከ ዘጠኝ ስንፆም የነበርነውን የፍስለታ ፆም ወደ ስድስት ሰዓት አዙረን ከእግዜር ተኳረፍን ።

የከሰዓቱ ፕሮግራም ላይ ከገንዘብ ያዡ ይርጋለም በስተቀር የሁላችንም ሹመት ተቀያየረ /ብልፅግና ስታይል 😉/

የከሰዓቱ የመጀመርያ ዙር ጭፈራ ላይ ...

እዛ ማዶ

 ሆ 

አንድ ትሪ

ሆ 

እዚህ ማዶ 

ሆ 

ሌላ ትሪ

የኔማ ደጀኔ 

ሆ 

ባለ ማስተርስ ድግሪ የሚል ግጥም ያዘለ ሙገሳ ያደረስነው ቀን ሰራተኛው ደጀኔ በደስታ ሰክሮ አምስት ብር ለቀቀብን። 

ይሄ ብር ነዳጅ ሆኖን ፍጥነት ጨምረን ተርገበገብን...እስከ 10 ሰዓትም ድረስ ዜማና ግጥም እያሰናኘን የማህበረሰቡን የሙገሳ ጥም ስለቆረጥን በገንዘብና ሽልጦ ናዳ ተመተን በድሎት ተሰቃየን።

10 ሰዓት ላይ እኔን ጨምሮ የጓደኞቼም ጉሮሮ የካሴት ክር እንደነከሰ ቴፕ መነፋነፍ ያዘ። 

ጥቂቶች ሁኔታችንን ሲያዩ ስላዘኑልን.. .ዘፈን በቅጡ ባናወርድም እርጥባን ሲቸሩን ቆዩ ...ከ ጣሰው ቤት በስተቀር ።

ጣሰው የቀረችንን እንጥፍጣፊ ጉልበት አሟጦ ከሰለቀጠ በኋላ በዘመኑ ቋንቋ ላሽ አለን...

እዛ ማዶ



አንድ ከረባት 

ሆ 

እዚህ ማዶ



አንድ ከረባት 



የኔማ ጣሰው 



ክቡር ባላባት 

ሆ.... 

ብር ወፍ የለም :) ..... ሁሉም ማጉረምረም ያዘ ... በተለይ ከሁላችንም የተንኮል ሊቅ የነበረው ይርጋለም ጣሰውን እንስደበው የሚል ሴራ ጠነሰሰ ...

እዛ ማዶ .... ብሎ አስጀመረን.. .

ሆ ብለን ተቀበልነው

አንድ ገበያ 

ሆ 

እዚ ማዶ

ሆ 

አንድ አህያ

ሆ ..

የኔማ ጣሰው ...

ሆ ...

ደደብ አህያ !

(ከዚህ ግጥም በኋላ በቅፅበት ከየት መጣ ያልተባለ የጥፊ ድምፅ ተሰማ...ገንዘብ ሊሰጠን እየመጣ የነበረው ጣሰው ...በገንዘቡ ፈንታ በካልቾ እየጠለዘ እንደ ኳስ አንጥሮን ተበታተንን)

...

ሁላችንም ላባችን ጠብ እስከሚል ሮጠን ካበቃን በኋላ.. . እያለከለክን ተሰበሰብን...ሁላችንም ብንሰበሰብም ይርጋለም ግን በመሀከላችን አልነበረም። ቆይቶ እያለከለከ ስራችን ተከሰተ ...ፊቱን ዘፍዝፎ አንድ ከባድ መርዶ አረዳን...

ጣሰው የሰበሰብነውን ብር በሙሉ ተቀብሎታል።

ሀዘኑ እንደዚህ በቃላት የሚነገር አልነበረም...የሁላችንም ልብ ክፉኛ ቆሰለ ።

አዘንን ...ተከዝን....

ህመሙ ና ስብራቱ ቀኑ አልፎ አድረን እንኳ አልፋታ ብሎን በፅኑ ቆዘምን። በተለይ ታሪኩ ነጠላ አዘቅዝቆ ገቢው ውስጥ የለቅሶ ድንኳን ማስተከል ብቻ ነበር የቀረው።

ይሁንና ... ከቀናት በኋላ ይርጋለም ከስራችን ብን ብሎ ጠፋ ... ዘወትር ቸኮሌትና ፓስቲ እየገዛ እንደሚዝናና የሚጠቁሙ የወሬ ፍንጣሪዎች ደረሱን ። 

በርግጥም ይርጋለም ጣሰው ገንዘብ ተቀብሎኛል በሚል ሙድ የቀኑን ገንዘብ ለራሱ መደበርያ አውሎት ነበር :)

@wegoch
@wegoch
@paappii
#ከግድግዳው_ባሻገር

#በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰርቶ #የተፃፈ

“ደንበል..ሸዋ ዳቦ…ስቴዲየም…ሜክሲኮ…ኸ..ትሔዳላቹ….?”
ወትሮም በእዚህ ሰዓት የታክሲው ግፊያ አስቸጋሪ ነው፡፡ ሰዉ ተገፋፍቶ ከጠባቧ የታክሲ በር ሾልኮ ተሰገሰገ፡፡ ከወንበሮቹ መካከል አራት ሰዎችን ከሚያስቀምጠው የመጨረሻ ረድፍ ላይ በቀኝ ጥግ ተቀመጥኩኝ፡፡ በተከፈተው የታክሲው መስኮት አልፎ የሚመጣው ቀዝቀዝ ያለ የጠዋት አየር ከፊቴ ደርሶ ሲጎበኘኝ ፊቴ ፈካ አለ፡፡
አፍታም ሳይቆይ ቁመቷ መካከለኛ የሆነ፣ ቀጠን ያለች ወጣት ሴት “ልትጠጋልኝ ትችላለህ?” አለችኝ፡፡ ሰምቻታለው ነገር ግን አይኔ ከመስታወቱ ባሻገር ስለነበረ መልስ ሳልሰጥ ወደ መስኮት ጥግ ሰውነቴን ሰብሰብ አድርጌ ተቀመጥኩኝ፡፡ የተቀባችው ሽቶ የታክሲውን አየር ተቆጣጥሮታል፡፡ ዘወር ብዬ የግርፍት እይታ ገረመምኳት፡፡ የተተኮሰው ፀጉሯ እዚህም እዛም ተበታትኗል፡፡ ደግሜ በጥልቀት ተመለከትኳት፡፡ ፊቷ የተረበሸ ከተማ ይመስላል፡፡ ጉንጮቿ ከፊቷ መቅላት ጋር አብሮ የቀላ ፍም ምድጃ ሆነዋል፡፡ የቀጠለችው ሰው ሰራሽ አልያም የሌላ ሰው ፀጉር ስፌት ከተተከለበት አናቷ ላይ በግልጥ ይታያል፡፡ ከንፈሯ ውሀ እንደተጠማ የደረቁ፡፡ በተደጋጋሚ ጣቶቿን እየሰደደች የቀሉ አይኖቿን ታሻቸዋለች፡፡ የደረቁት የኩል ፍርፋሪዎች ከአይኗ ሽፋሽፍት ላይ ከተጣበቁት አይናሮች ጋር እየተቀላቀሉ በጣቶቿ ከፊቷ ቆዳ ላይ ትዳምጣቸዋለች፡፡ በስራ አልያም በአንዳች ምክኒያት እንደተዳከመች ገብቶኛል፡፡
ታክሲው ደንበል ጋር እንደደረሰ ከተናገረ በኋላ ወራጅ መኖር አለመኖሩን በመጠየቅ የላይኛውን የቀለበት መንገድ በጎን ትቶ የውስጠኛውን የቀለበት መንገድ ቁልቁል ይዞ ከነፈ፡፡ ስልኬን ከፍቼ ቁጥሮቹን ከጎነቆልኳቸው በኋላ ወደ ቀኙ ጆሮዬ አስጠግቼ ጥሪውን እስኪያነሳ መጠባበቅ ጀመርኩኝ፡፡ ሁለት ሶስቴ ከጠራ በኋላ አነሳው፡፡ ሰላምታ ተለዋውጠን እዛው ስታዲየም እንደምጠብቀው ነገርኩት፡፡
“ትንሽ ስለማረፍድብህ ትንሽ ታገሰኝ ሻይ ቡና እያልክ፡፡” አለኝ በሰዐቱ መድረስ የተሳነው አንድ ጓደኛዬ፡፡
“መቼ ይሆን አንተም በሰዓትህ ምትገኘው?”
“ጥሩ ትኮምካለህ ባክህ! በል ዲዛይኖቹን በፍላሽ ሬዲ አርግልኝ እና ፕሪንት እናረጋቸዋለን እንደመጣው፡፡”
“አንተ ብቻ ቶሎ ና እሱን እቤት ገልብጬዋለው፡፡” ሰላምታ ተለዋውጠን ስልኩን ዘጋሁት፡፡ በግራ ትከሻዬ ከበድ ሲለኝ ተሰማኝ፡፡ ዘወር አልኩ፡፡ እኔ ላይ ደገፍ ብላ እንቅልፍ ሸለብ አድርጓታል፡፡ ደንገጥ አልኩኝ፡፡ ምናልባት ነቃ እንድትል በማሰብ ሰውነቴን ነቅነቅ አድርጌ ጠጋ ብዬ ተቀመጥኩኝ፡፡ ትንሽ እንደ መንቃት ብላ መልሳ ተኛችብኝ፡፡
አሳዘነችኝ፡፡ ታክሲው የአብዮት ትራፊክ መበራት ይዞት ቆሟል፡፡ ከቀዩ የትራፊክ መብራት የአንድ ደቂቃ ተኩል ቆይታ በኋላ ተንቀሳቀስን፡፡ መውረጃዬ ተቃርቧል፡፡ እንደተሸገረ የስታድየም ታክሲዎች ከተኮሉበት የታክሲ ማውረጃ እና መጫኛ ደረስን፡፡
“ስታድየም መጨረሻ፡፡” የታክሲው ረዳት ለፈፈ፡፡ ጥቂት የታክሲው ተሳፋሪዎች ወረዱ፡፡ እኔም አንደኛው ወራጅ ነበርኩኝ፡፡ አልወረድኩም፡፡ ልጅቷ ከትከሻዬ ጭንቅላቷን ሸብረክ አድርጋ እንደተኛች ነች፡፡ ከበስተ መጨረሻው ረድፍ ከተቀመጥነው አንዳችንም አልወረድንም፡፡ ረዳቱ የታክሲውን ጠባብ በር በክንዱ ገፍቶ አጋጠመው፡፡ ታክሲው ተንቀሳቀሰ፡፡ ከመውረጃዬ አለፍኩኝ፡፡ የይሉንታ ግዞተኛ መሆኔን ስረዳው አበሸቀኝ፡፡ ዘወር ብዬ ተመለከትኳት፡፡ የተከደኑ አይኖቿን በተበታተኑት ፀጉሮቿ መሀከል ስመለከታቸው አሳዘኑኝ፡፡ ምነኛ እንደደከማት ከደረቁት ከንፈሮቿ መሀከል የሚወጣው የሞቀ ትንፋሽ ልጆሮዬ ሹክ አሉት፡፡ እጆቿ በጭኖቿ መሀከል ተሸንቁረዋል፡፡
#ይቀጥላል
ስለሺ ሳልስ ዑመር
©SVC2017

@wegoch
@wegoch
@wegoch
እዛ ማዶ ጭስ ይጨሳል
አብዮተኛ ይደግሳል😊
ነሐሴ ➋➌
#የግጥም_አብዮት 🙏

ቦታ ☞ አ.አ ደምበል ህንፃ ጀርባ ወረዳ 9 የወጣቶች ማዕከል አዳራሽ ውስጥ ነው፡፡

⭕️ 400 ሰው ብቻ!

📍100 ብር 👌
ተቃርኖ ((ጆኒ ሀብቴ))



ወጥቷል፡፡
ወደዓለም፡፡ለዓለም፡፡
ሊኖር ነው፡፡
ከዓለመኞች ጋር፡፡
ዓለመኞች ቆንጆ መሳይ ናቸው፡፡ተጣዳፊዎች፡፡ለሁሉ የሚሮጡ፡፡የሞላላቸው መሳዮች ግን በማብቂያው ፥ ምንም ያልያዙ መናጢዎች፡፡
ያፈቅራሉ፡፡
ቸኩለው ልብ ይሰጣሉ፡፡ተጣድፈው ሁሉን ተሰጣጥተው ይጨርሳሉ፡፡በንጥቀት ይሰለቻቻሉ፡፡
ደሞ ወደሌላ ይሮጣሉ፡፡መሬት ላይ ይሮጣሉ፡፡አልጋ ላይ ይሮጣሉ፡፡አየር ላይ ይሮጣሉ፡፡ፍቅር ላይ ፥ ጥላቻ ላይ ይሮጣሉ፡፡ሳቅ እንባ ላይ ይሮጣሉ፡፡
ሁሉ ላይ ይሮጣሉ፡፡ረግተው ካየሀቸው ለሌላ እሩጫ እያደቡ እንጂ እርጋታን አውቀውት አይደለም፡፡በዚህ ሁሉ ጥድፈታቸው ውሸታሞች ፥ ቀጣፊዎች ፥ አጭበርባሪዎች ሆነው ይታዩታል፡፡
"አትሩጥ፡፡ለምንም ነገር አትፍጠን፡፡ያንተ ያንተ ነው፡፡ላንተ ያለው እንጀራ ሻግቶ ይወድቃል እንጂ ማንም አይበላው" ይለው ነበረ እረኛ እያለ የሚያግደው በጉ፡፡
የታደለ ረኛ ነበረ፡፡የሚያወራ በግ የነበረው፡፡ይሄ ከሚሊዮን እረኛ አንዱ ብቻ የሚያገኘው እጣ ነው፡፡ወርቅ እንቁላል እንደምትጥለው ዶሮ ነው ይሄ በግ፡፡አይገኝም፡፡ሲገኝም በዘመን አንዴ ነው፡፡
አዋቂ ነው፡፡ልሳን አለው፡፡የጣፈጠ አንደበቱ እውቀቱን አሳምሮ ይናገራል፡፡
" ዛሬ ዛሬ ሁሉ ይሮጣል፡፡አንተ ግን ዝግ በል፡፡የሮጠውን ያህል ማንም አያገኝም፡፡በማብቂያው ሁሉ በሮጠው መጠን እርካታ የለውም....." ይለዋል ተናጋሪ በጉ፡፡
" እኔና አንተ ያለነው እልም ያለ ገጠር ፥ ለምን ስለከተሜው ታወራኛለህ?የት ታውቀዋለህ?"
ሳቅ ይልና " ዝም ብዬ የምታረድ በግ አልምሰልህ፡፡እሱ የአብርሐም በግ ነው፡፡እኔ ብታረድም አዋቂ በግ ነኝ " ይለዋል፡፡
" እሺ ይሄ ወሬ ለኔ ምን ይረባኛል!?"
"ቀንህ ሲደርስ ከተሜ ነህ፡፡በጊዜህ ከተሜኛ ነህ፡፡ለዛ ጊዜ የሚሆንህን ነው ዛሬ የምነግርህ፡፡"
ወጥቷል፡፡
ያየው ደነቀው፡፡ግራ ገባው፡፡
ይሄ ሕይወት እንቀልፍ አልባ ነው፡፡ንቃት ግን የለውም፡፡ረፍት አልባ ነው፡፡ስራው ግን አጥጋቢ አይደለም፡፡ይኳኳላል፡፡ግን ውብ አይደለም፡፡ያነጣጥራል፡፡ኢላማ ግን ይስታል፡፡ደስተኛ ነኝ ይላል፡፡ግን ብስክስክ ብሶቱን ታቅፎ ነዋሪ ነው፡፡ይብለጨለጫል፡፡ግን አያበራም፡፡
መጥታ ያቀፈችው ማን ነበረች!?
አዎ!!
ሔርሜላ ነች፡፡
ብዙ ሳቅ ያላት ሔርሜላ፡፡ብዙ ድምፅ ፥ ምንም ዝምታ የሌላት ሔርሜላ፡፡እየሳቀች እዛው የምታለቅስ፡፡እኩል በእኩል ሳቋም እንባዋም የበዙ፡፡
እንዴት ወደሱ መጣች!?
ከየት ወደሱ መጣች!?
ለምን እሱን አቀፈችው!?
ሁሉ ተሳከረበት፡፡ብብብብብብብብዥዥዥዥዥዥዥዥዥዥዥዥዥ ያለ ሆነበት፡፡አልጠራ ያለ መደፍረስ፡፡አያጥቡት ግን የሁሌ ጭቃ፡፡ተወቅጦ የላመ ፥ የደቀቀ ውሃ፡፡
" የኔ ፍቅር !?" አለች ሔርሜላ፡፡
እ!?
" ወይዬ " አለ እሱም፡፡
እ!?
" ልሄድ ነው በቃ፡፡ "
ከአይኑ የእንባ ኳሶች አንከባለለ፡፡ጉንጩን አብዶ ሰርቶ ፥ አፍንጫውን በሎጬ አታልሎ ፥ ሪዙን አብዶ ሰርቶ የእንባ ኳሶቹን ቁልቁል ወደመሬት ጎሉ በሹት ጠለዘው፡፡
" እሺ በቃ ሂጂ " አለ እንደምንም ብሎ፡፡
መቼ መጥታ!?
መቼ ልትሄድ!?
አሁን አቀፈችው አልተባለም እንዴ!?
አሁን ሳቀች ሲባል አልነበረ እንዴ!?
ምን ጉድ ነው ይሄ!?
እያለቀሰ ፥ እያለቀሰች ተቋጨች፡፡አከተመች፡፡ተቋጩ፡፡አከተሙ፡፡
" አለህልኝ የኔ ፍቅር!?" እያለች ከንፈሯን ከንፈሩ ላይ አተመች፡፡
" የኔ ኮኪዬ " አለ ከንፈሯን እያጣጣመ፡፡
ኮኪ ማን ነች ደሞ!?
የኔ የኔ ከተባባሉ የእነሱ የራሳቸው ናቸው፡፡እሱ የእሷ ፥ እሷ የእሱ፡፡
ፍቅረኛሞች ናቸው፡፡
ሽቅርቅር ያለች፡፡የሽቅርቅሯ መርቀቅ ከአጠገቧ ያለን ሁሉ አፈር ድሜ አስበልቶ የሚያስረሳ፡፡ሁሉ ነገሯ አይን ይጠራል፡፡አይን ማራኪ ጀግና መሽቀርቅር ፥ አይን ጎታች ማግኔት መሽቀርቀር ፥ አይን ጋባዥ ለጋስ መሽቀርቀር ነው ያላት፡፡
ያያት ሁሉ ይስቃል፡፡እሷን እያየ አብሯት ያለን ይረሳል፡፡ሲያያት ይደሰታል፡፡ከተሜ ቅብ ደስታ፡፡ጥድፊያ ውስዋስ ደስታ፡፡
" በጣም ነው የማዝነው የኔ ፍቅር፡፡"
" ይገባኛል፡፡"
" ግዴታ ስለሆነብኝ ነው፡፡መሄድ አለብኝ፡፡"
የእንባ ኳሱ.....የለቅሶ ግጥሚያው....የእንባ ሊጉ.....የዚህ ዘመኑ ውድድር ኮኪ ነበረች፡፡የመለየት ዋንጫውን አብልታውና ሸልማው ሄደች፡፡
ያ በጉ ታውሰው፡፡ሊያወራው ፈለገ፡፡
እንዲህ አይነት ወሬ....
"የማዝነው...
ክፉዎች ባሸነፉበት ዓለም ላይ በመኖሬ አይደለም!!!
"ቅዱሳኖቹ ተለይተው ስላልታወቁ እንጂ!!!
የሚከፋኝ...
"ዋናው እርኩስ ታውቆ ፥ ታላቁ ቅዱስ በማይታወቅበት ዓለም ላይ ስላለሁ ነው
የሚያስጠላኝ...
"እኔ ለማን ፥ ማን ለኔ እንደቆምን አለማወቃችን ነው...." ሊለው ፈለገ፡፡
ግን አይለውም፡፡ሊለው አይችልም፡፡ሰንቆታላ፡፡ከገጠር ወደከተማ ሲገባ፡፡
" እረደኝ፡፡ግን ፈጥነህ አትግፈፈኝ፡፡ቃሌን ለማቋረጥ በጥድፊያ ካራ አትሳል...." እያለው ከሚሊዮን አንድ እጣውን በፈጥነት ፈጣጥሞት ከተማ መግቢያ ስንቁ አድርጎታል፡፡
ምን አይነት ዓለም ላይ ነው የወጣው!?
ሰውዬው ከእንስሳው የሚያንስበት ፥ እረኛውን ከብቱ በሚያግድበት ፥ ጠባቂውን ተጠባቂው ተግቶ ዘብ የሚቆምለት ዓለም ላይ ነው የወጣው፡፡

@wegoch
@wegoch
#ከግድግው_ባሻገር
በእውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተፃፈ
ክፍል ሁለት
ጥቂት ደቂቃዎች አልፈዋል፡፡ ቡናና ሻይ እንደደረስን ሜክሲኮ ከመድረሳችን በፊት መቀስቀስ እንዳለብኝ አሰብኩኝ፡፡ ባልቀሰቅሳት፣ ቀኑን ሙሉ ብታርፍብኝ ምነኛ ደስ ባለኝ፡፡ ምናልባት አዳሯ ከባድ ሆኖ ይሆናል፡፡ ምናልባት እንቅልፍ የተጠማች የእንቅልፍ ባዳ ትሆን ይሆናል፡፡ ምናልባት ህይወትም ምትም ትርጉም አልባ ሆነውባት በተኛውበት ብሞት ብላ በመመኘት የተኛች ይሆናል፡፡ ምናልባት የተመቸው የቤቷ ፍራሽ ሳይመቻት የደረቀውን የኔን ትከሻ መርጣ ይሆናል፡፡ መቋጫ የሌላቸው የትየለሌ ምናልባቶች በህሊናዬ እየተንሸራሸሩ ከትከሻዬ ሸርተት ማለት ጀመረች፡፡ ወደ ጥልቅ የእንቅልፍ ባህር እየቀዘፈች ነበር፡፡ ነገር ግን የእኔ ትከሻ እሷ በምናቧ እንደተመለከተችው የውቅያኖስ ያክል አይሰፋም ነበር፤ ቢመቻትም አይበቃትም፤ ቢበቃትም አያዛልቃትም፡፡ ለደቂቃዎችም ቢሆን እረፍት ውስጥ ነበረች፡፡ ጭንቅላቷ ከነበረበት ትከሻ ቁልቁል ተንሸራቶ አየር ቀዝፎ እንደገና ሽቅብ ተመለሰ፡፡ ነቃች፡፡
ዘወር ብላ ተመለከተችኝ፡፡ ደንግጣለች፡፡ እንደ ማፈር አረጋት፤ ከነበረችበት ሰፊ የነፃነት አለም ወደ ጠባቧ፣ ጎርባጯና አስቀያሚዋ አለም መመለስዋ አላስደሰታትም፡፡
“ይቅርታ! አስቸገርኩህ፡፡” በተስለመለመ አንደበት አንገቷን ሸብረክ አድርጋ ይቅርታዋን አቀረበች፡፡
“የቤርጎ አላስከፍልም፡፡ ትከሻዬን ግን ስብርብሩን ነው ያወጣሽው፡፡ ያገር ወጌሻ ቢያሸኝ ሚመለስም አይመስለኝም፡፡” ፊቴን አጨማድጄ በማስመሰል መለስኩላት፡፡
“ዖ ማይ ጋድ! አንተ ላይ ነበር የተኛውት? ወይኔ በጣም ይቅርታ አላወኩም ነበር፡፡” የእጆቿን መዳፍ በአፏ ላይ አድርጋ የጨረፍታ ተመለከተችኝ፡፡
“ገና ጠዋት ነው፤ ከባድ ለሊት ነበር መሰለኝ ያሳለፍሺው፡፡”
ቀና ብላ አየችኝ፡፡ መልስ አልሰጠችኝም፡፡ “ሜክሲኮ መጨረሻ፡፡” ረዳቱ ጠባቧን በር እየበረገደ እንድንወርድ ጋበዘን፡፡ ውስጤ ምን እንደምትሰራ ለማወቅ በጣም ጓጉቷል፡፡ ቀደም ብዬ ከታክሲው የወረድኩት እኔ ነበርኩኝ፡፡ ከአፈታ በኋላ ወረደች፡፡
“በጠዋቱ እኔ ላይ ከተኛሽ ቀኑን ሙሉማ ስንቱ ላይ እንደምተኚ ሳስበው እቺ ልጅ ቡና ያስፈልጋታል አለበለዚያ የሰውን ትከሻ ሰባብራ ነው ምጨርሰው ብዬ አሰብኩኝ፡፡ ለምን ቡና አንጠጣም፡፡” ድፍረት የተሞላበት ግብዣ ነበር፡፡
“መተኛት አለብኝ ገብቼ…ግን ውለታህን እዚሁ ለመክፈል እዚሁ አካባቢ መጠጣት እንችላለን፡፡” እያንገራገረች እሺታዋን ገለፀችልኝ፡፡
እዛው አካባቢ አንድ ካፌ ከተምን፡፡ ካፌው ግርግር ያልበዛበት በጥሩ ቅንብር ሙዚቃ የታጀበ ጥሩ ድባብ ያለው ቤት ነው፡፡ ክብ ሰርተው ከተደረደሩት ወንበር እና ጠረጴዛ መሀከል ከአንዱ ተቀመጥን፡፡ ምርጫዋን ጥቁር ማኪያቶ እና ለኔም ሻይ አዘን ወደ ጨዋታችን ተመለስን፡፡
“መቀስቀስ ትችል ነበር እኮ ስተኛብህ፡፡”
“አይ እኔ እንኳን የሰውን የመተኛት ሰበዊ መብት አልጋፋም ብዬ ነው፡፡” ፈገግ አለች፡፡
“ከመቼ ወዲህ ነው መተኛት ሰባዊ መብት የሆነው አንተ?” የግርምት እየተመለከተችኝ ጠየቀች፡፡
“መኖር ሰባዊ መብት እንደሆነ እንደዛው ሁሉ በመተኛት ውስጥም ሌላ መኖር አለ፡፡”
“ውይ ፍልስፍና ላይ ብዙም አይደለሁም፡፡ ከስራ ግን አስፈታሁ፤ ስራ እየገባህ ነው እንዴ?”
“በእርግጥ ለስራ ነው የወጣሁት፡፡ ግን ጓደኛዬ ትንሽ አርፋጅ ስለሆነ ችግር የለውም፡፡”
“እዚሁ ነው ምትገናኙት ወይስ ሌላ ቦታ?” ትንሽ ፈገግ አልኩኝ፤ ይሉኝታ ይዞኝ እንደመጣው ባላወቀች፡፡
“መውረጃዬ ስታዲየም ነበር፡፡ ያው…ግን ሳይሽ ከባድ እንቅልፍ ላይ ነበርሽ፤ መቀስቀስ አልፈለኩኝም፡፡ ለሊት አልተኛሽም ነበር?” ጥያቄው ጠጠር እንዳለባት ከፊቷ መቀያየር በቀላሉ ማንበብ ይቻላል፡፡ አንድ ሁለቴ ማኪያቶዋን ማግ ካደረገች በኋላ ትንሽ ተከዝ አለች፡፡ ጥቂት በዝምታ ተዋጠች፡፡ አንዳችም አልተናገርኩም፡፡ ቀጣዩን ንግግር ለማዳመጥ ግን ጓጉቻለው፡፡
“ከስራ ነው ምመጣው፡፡” ፊቷ ኮሶ የጠጣች ያክል ተጨማደደ፡፡ አሁንም በትካዜ ውስጥ ነች፡፡
“በደለኛነት ተሰምቶህ ያውቃል?” ከምናወራው ነገር ጋር ጭራሽ የማይገናኝ ጥያቄ፡፡
“አዎ! አንዳንድ ጊዜ እኔ የማይገባኝን ነገር ሳደርግ አልያም በማይገባኝ አከሔድ ስኖር በደለኛነት ይሰማኛል፡፡ ለምን ጠየቅሽኝ?”
“እኔ እየተሰማኝ ስለሆነ፡፡ አየህ በህይወት ስትኖር ሶስት ነገሮች የህይወት ባላንስህን ይጠብቁልሀል፡፡ ያመንከው ፈጣሪ ውይም የምታምነው ነገር፣ ህሊናህ እና በዙሪያ ያሉት ሰዎች፡፡ ለእነዚህ ነገሮች ያለህ ቦታ የተዛባ ከሆነ የበደለኝነት ስሜት ይኖርሀል፡፡”
“ታዲያ የምትሰሪው ስራ እነኚህን ነገሮች አዛባቸው?” አይኖቿ እንባን አቅረዋል፡፡
“አዎ! አሁን ግን የፀፀተኝነቱም ስሜቴ የሞተ ይመስለኛል፡፡”
“ስራሽን ማወቅ እችላለው?”
ይቀጥላል….
ስለሺ ሳልስ ዑመር
©SVC2017

@wegoch
@wegoch
2024/09/24 13:29:10
Back to Top
HTML Embed Code: