Telegram Web Link
ነብስያህን አድምጥ! ራስህን ሁን!!

ብትወዱኝም ብትጠሉኝም ሁለቱም ይመቸኛል። ብትወዱኝ ልባችሁ ውስጥ ነኝ ብትጠሉኝ
ደግሞ ጭንቅላታችሁ ውስጥ ነኝ..!
እኔ አይደለሁም ያልኩት፤ ዊልያም ሼክስፒር ነው የተናገረው ሀሳቡ ግን ፈገግ ያደርጋል።😊😊😊


ሽቶን ስጦታ ብለህ ስትሰጠው ...!!! ሸተሃል ለማለት ፈልገህ ነው....ከሚል ሰው ጋ እንዴት ነው የምንግባባው ጃል??....!!..!!ደግሞም አንዳንድ ሰው አለ ጨረቃን በጣትህ እያሳየሀው ከጨረቃ ይልቅ ጣትህን የሚያይ..!!!


ከራስ ጋር!!!

ፊት ለፊት ስንገናኝ መተቃቀፍ ወደየቤታችን ስንሄድ እንደ kappa ማስታወቂያ ጀርባ ለጀርባ
መሆን ምንም አያዋጣንም. ..ጠራቢዬ ሆይ ወዴት አለህ /ሽ?ሁሉንም ፅሁፎቼን ስጽፍ የነበረው
ፈገግ እያልኩ ነው ይሄንን ግን ኮስተር ብዬ ነው።እዚህ ውስጥ እኮ አስተማሪዎቼ ትንሽ
ናቸው ተማሪዎች ግን የሉኝም...የማትረዳኝ/ ሆይ ይሄንን በማምበብ ጊዜህን አታጥፋ/ፊ !!!


ይቅርታ ለማድረግ አሰቀድሞ መቁሰል ግድ፣ይላል፣ቆስሎ ይቅርታ ለማድረግም ደግሞ ኩራትን በውስጥ መሸከም ግድ ነው።ከልብ የሆነ ልግስና ለመፈፀም አስቀድሞ "እኔ" የሚለውን ወይም "የእኔነት" አስተሳሰብ አውጥቶ መጣል ብቸኛው መፍትሔ ነው!!....ስለ እኛ እያወራህ ስለ ራስህ ራስህን ነፃ ለማውጣት ነው ከተባልክ ምን ታረገዋለህ......የምትናገረው ነገር ልክ መሆን ወይም አለመሆንህ ሚረጋገጠው....እንደሰውየው አረዳድ ነው......ያ ማለት ግን አንተ ልክ አይደለህም ወይም እሱ ልክ አይደለም ማለት ላይሆን ይችላል...😊

ካህሊል ጅብራል የልቧ ሰው ምን ይላል....."ከጥንቸሎች የበለጠ ኤሊዎች መንገድ ያውቃሉ"....

ቴድ አፍሮ..የልቧ ሰው ምን ይላል......ተመልከትልኝ



ቀላል ይሆናል
.......
ዳገቱ ላይ አትዛል ጉልበቴ
የተራራው ጫፍ ፍቅር ናት እርስቴ
ቀላል ይሆናል ቀና አርገኝ ፅናቴ
ቀላል ይሆናል(4)
ቀላል ይሆናል
ደመና ሲያይ መስሎት የጨለመ
አለ ቂል ሰው ሁሉም አከተመ
ደቂቃ ተስፋን ካየናት አርቀን
ነገ ሌላ ይሆናል ጥሩ ቀን
ቀላል ይሆናል (8)
ቀላል ይሆናል
ፈራን
ፍቅርን ፈራን
ልጅነት የለገሰንን
የፍቅር አምላክ በጥበቡ በረቂቅ ያለበሰንን
በመለኮት የቀባንን
እውነት ፈራን...ፍቅር ፈራን
አሄ አሄሄሄሄ (8)
ዳገቱ ላይ አትዛል ጉልበቴ ይላል.......ዳገቱ አንድም የህይወት መስመራችን ኑሯችንን ነው..ውጣውረዱን እንቅፋቱን ፈርተን ዳገት ላይ እንዳንቀር ...ስልቹ ሆነን ተስፋ አጥተን ለዳገቱና ለፈተናው ተሸንፈን እንዳንቀር ሲል አትዛል ጉልበቴ በማለት የሚመክር ዜማ ነው...። መጽሐፍ ቅዱሱም ቢሆን ፈተና በበዛባት አለም ላይ እንደምንኖር ያትታል...የየእለት ፀሎታችንም ቢሆን ...ወደፈተናም አታግባን ከክፉ ሁሉ አድነን እንጅ የሚል ነው....ስለዚህ ይሄ ሁሉ የሚያመላክተን ምንኛ የዚህ አለም ኑሮ ፈታኝ እንደሆነ ነው.....ይሄን ፈተና ደግሞ በፅናት መወጣት ያስፈልጋል....ዳገቱን መፍራት የለብንም ሲል ነው አትዛል ጉልበቴ ያለው ይመስለኛል። ብሎም የህይወትን የዳገት አለም ፅናት እስካለን ድረስ እናልፈዋለን ሲል ቀላል ይሆናል ቀና አርገኝ ፅናቴ በማለት ከገዛ ፅናቱ ጋር ይነጋገራል። ይሄ በጣም ግልፅ እና ፊትለፊት የምናኘው መልዕክቱ ነው ወይንም ሰሙ ነው....ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ ጀርባ ያለው ወርቁ ይመስለኛል።
ከዚህ ከምናየው ከተረዳነው ጀርባ ያለ ሌላ ሃሳብ ያለ ይመስለኛል። የአለምን ዳገቱን ካለፍን ውጣ ውረዱን ከሸኘን በስቲያ ያለ እጣፈንታን የሚያስቃኝ ቅኔ ነው። የተራራው ጫፍ ርስታችን ፍቅር ነው ሲል ይተርካል....የተራራው ጫፍ የሚለው ክርስቶስን ወይንም አላህን ወይንም በአጠቃላይ ፈጣሪን ይመስለኛል። ፍቅር እንደ ርስት...ፍቅር እንደ ቡራኬ ፅድቅ....ፍቅር እንደ ትልቅ የህይወት ግብ የሚሰበከውና የሚሰጠው በፈጣሪ ዘንድ ብቻ ነው ብል አላጋነንኩም.....ፈጣሪ ደግሞ ያለው ከውጣውረዱ ከዳገቱ በላይ ነው....በተራራው አናት ላይ ነው ክርስቶስ ያለው...እናም የተራራው ጫፍ ፍቅር ናት ርስቴ ይለናል ብላቴናው።
ደመና ሲያይ መስሎት የጨለመ
አለ ቂል ሰው ሁሉም አከተመ
....ትንሿን የፈጣሪ ፈተና አይቶ ሁሉም የሚጋረድበትና በቃ ሁሉም ነገር አከተመለት ብሎ ተስፋ ስለሚቆርጥ ቂል ሰውም ያትታል። በተለይ የአምላክን ድርጊትና የመለኮትን ህልውና ለማወቅ ዘለግ ያለ ጠለቅ ያለ እይታና ጥበብን ያሻል ለዛም ነው ይህን በቀላሉ ተስፋ ቆራጩን ሰው ቂል ነው ያለው። እዚህ ላይ ድንቁ ሎሬት በእሳት ወይ አበባው መግቢያ ላይ ካላት ጋር ትመሳሰልብኛለች።
"እና እንደኔና እንዳንቺው የውበት ዓይኑን የታወረ
እግረ ሕሊናው የከረረ
ባሕረ-ሃሳቡን ያልታደለ
የውበት ዓይኑ የሰለለ
ሰማይ ጨለማ ነው እንጅ አበባ እኮ አደለም አለ
ያልታደለ።" ይለናል ሎሬቱ.....እዚህ ላይ በትርጉም ቀጥታ ካነሳነው ሃሳብ ጋር ባይሄድም ቴዲ ቂል ሰው ያለበትና ጋሽ ፀግሽ እግረ ሕሊናው የከረረ ያለበት መስመር ይገናኛል...ሁለቱም ለተለያየ ጉዳይ ይበሉት እንጅ ጭብጡ ግን በምናብ ርቀን መጥቀን...በተመስጦ ከአምላክ ጋር ካልተገናኘን ...በጥበብና በከፍታ አይን መመስጠር ካልቻልን ቴዲ እንዳለው ቂል በቀላሉ ሁሉም አከተመ እንላለን ማለት ነው...ለዚያም ነው እኮ ገና ትንሿን ደመና ሲያይ...ደመና መና መሆኑን...ደመና የእርገት መሰላል መሆኑን....ደመና መገለጫ መሆኑን ሳያመሰጥር ቂሉ የጨለመ የመሰለው።
....ደቂቃ ተስፋን ካየናት አርቀን
ነገ ሌላ ይሆናል ጥሩ ቀን
ደቂቀ ተስፋ ያላት የሚመስለኝ ....እምነትን ነው...የሰናፍጭ ታክል እምነት ቢኖራችሁ ይህንን ተራራ ማንቀሳቀስ ትችላላችሁ.. .የሚል በቀጥታም ባይሆን የመፅሐፍ ቅዱስ አባባል አለ። እንግዲህ ትንሿ ደቃቃዋ የተባለችው የሰናፍጭ ታክሏ እምነት ናት....እምነት ደግሞ በራሱ በፈጣሪ ላይ ያለን ተስፋ ማለት ነው አይደል....? ስለዚህ እምነት ካለ ነገ ሌላ ቀን ነው ይለናል.....አሁንም እኛ ካሻን በአለማዊም መጠቀም እንችላለን ምክንያቱም ለሁለቱም እንዲያስኬድ ተደርጎ የተሰነደ ቅኔ ነውና...ነገር ግን ነገ ሌላ ይሆናል ጥሩ ቀን ያለው....ቅድም እንዳልነው ከላይ የተራራው ጫፍ ክርስቶስ ነው ፍቅር የተባለው ካልን...ደቂቀ ተስፋው እምነት ነው ካልን በእምነታችን ጉልበት የተራራውን ጫፍ ፍቅር ማግኘት የምንችለው በሌላኛው አለም....ስጋ ሞትን ከሞትን በስቲያ ይመስለኛል ። ስለዚህ ነገ ሌላ ይሆናል ጥሩ ቀን የተባለው ጥሩ ቀኑ ያኛው አለም መንግስተ ሰማያት ይመስለኛል። አይ በፈጣሪ ከታመንን የነገ አለማዊ ቀናችንን ያሳምርልናል ማለቱ ነው ብላችሁ መረዳትም መብታችሁ ነው ይቻላል።
ከዚያ ዝቅ ይልና ብላቴናው ማንን ወዲህ ተውሶ አመጣ ሃሳቡን ደህና አርጎ የሚያስተሳስርለትን ሎሬቱን.....
ፈራን
ፍቅርን ፈራን
ልጅነት የለገሰንን
የፍቅር አምላክ በጥበቡ በረቂቅ ያለበሰንን
በመለኮት የቀባንን
እውነት ፈራን...ፍቅርን ፈራን
ሲል የህልውናችንን መናጋት...የነፍሳችንን ፈተና...የስጋችንን ብክነት ያትታል።
ፈጣሪ ፍቅርን በረቂቅ አልብሶናል...ለዚያም በልጅነት ጊዜ የኖርነው ኑሮ ምሳሌ ነው..ህፃንነት እኮ ውበት ነው የዋህነት ነው...አሁን ተጣልተን አሁን እንታረቃለን.....


ቅዱስ ቁርአን ምን ይላል መሰለህ......."ከችግር ቦኃላ ምቾት አለ ""



በብቻነት ኑሮ ብቻ ይወደዳል በብቻነት ኑሮ ብቻ የሚለው ቃል...ብቻ ይወደዳል ...

የፀጥታ ዜማ ቅኝት ይወለዳል!!!

ሁላችሁንም ለነበረኝ ግዜ በጣም አመሰግናለሁ...
Forwarded from Natnael Fikru (Natnael Fikru)
እንግዲህ ለዚች ወተን ስለመመለሳችን እርግጠኛ ላልሆንበት ህይወት ነው ክልሌ ....... እንትን የኔ ናት እንትን የኔ ነው ...... የእንትን ብሔር ይውጣ እያልን የምንባለው እርስበእርስ የምንገዳደለው የምንከፋፋው ........ ቢገባን ዛሬ የሆነው ሁሉ ፈጣሪ ሊያስተምርን ያረገው ነው .........
ፓለቲከኛ አደለውም ! ስለፓለቲካ መፃፍም አልፈልግም (አለወድም) !!! አሳቤን ለማካፈል ነው ፡፡
ህይወታቸውን ላጡት መላው ተሳፋሪ ቤተሰብ እና ወገኖች መፅናናትን እመኛለው ! 🙏😞
ፖለቲካ አስጠላኝ ፍቅር ናፈቀኝ😢😢
@wegoch
Barcho ባርቾ Ethiopian Fiction Narration By Samrawit Kebede 2019
netb tube ነጥብ ቲዩብ
Watch "‹‹ደብዳቤው›› DEBDABEW by samrawit kebede 2019" on YouTube
https://youtu.be/-JXPNUQg9PE

@wegoch
@wegoch
Forwarded from ቅንድል ኢትዮጵያ (Ermiyas Dejene)
ቀንዲል Digital Magazine(1).pdf
4.9 MB
#ቀንዲል ዲጂታል መፅሔት

ቅፅ 1- ቁጥር2

💰ፓኬጅ ከገዙ 0.60 ሳንቲም ብቻ💰

@kendilM
@kendilM
ዳቦ ቤት በራፍ ላይ በራብ የሞተው ሰው😔😔😔
ከደምሰው መርሻ በሶፊ
Worth to share
👉👂👏
@wegoch
@wegoch
@bestletters
ይቀጥላል

እኛ ኢትዮጵያንኮ በአንድ አቅማዳ ውስጥ የተከተትን የተለያየን ዘሮች ድምር ነን፡፡ ከሚያጣላን ይልቅ የሚያፍቅረን፣ ከሚያለያየን ይልቅ አንድ የሚያደርገን ብዙ ነገር አለን፡፡ እኛኮ በአንድ ክረምት፣ በአንድ በጋ፣ በአንድእለት፣ በአንድ የጊዜ ቀመር የምንኖር ልዮ ሕዝቦች ነን፡፡ ማጉ ቢለያይ፣ ድሩ ቢለያይ፣ ሸማኔው ቢለያይ፣ ቋጪው ቢለያይ ሁላችንም የምንለብሰው ልብስ ግን አንድ ነው፡፡ ....አዋ አንድነው እዉነት እላቹሃለው የምንረግጠው አፈር፣ ቀና ብለን ስናይ በቀሰተ ደመናው የፈካው ሰንደቅ አላማችን፣ በብዙ ሕዝቦች አንደበት የተቀመረው ቋንቋችን፣ በሰለጠነ ትምህርት ሳይሆን በበሰለ አይምሮ ፣በበለፀገ ቴክኖሎጂ ሳይሆን በጠንካራ እጆች አሻራ የተነደፈበት የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶቻችን፣ የሰው ልጅ እኔማንነኝ፡? ከየትስ መጣው? ብሎ ሲጠይቅ የማንነቱን ጥያቄ የሚያገኝበት ሀገር <ኢትዮጽያ>ናት፡፡እኛ ኢትዮጽዊያን ትናንት ለአለም ሁሉ መነሻ ነበርን .......

ዛሬም ነገም....


ይቀጥላል



ከ አሸናፈፍቃዱ/1050/

@wegoch
@wegoch
@lula_al_greeko
አራተኛ ዙር መሠናዶ ሲሆን ወግ ፣መነባነብ፣ግጥም፣ተውኔት እና ሌሎችም በዋሽንት፣ ክራር ፣መሠንቆ እና ኪቦርድ ጋር ተዋዝቶ የፊታችን እሁድ ምሽት12:00 በዝዋይ ቱሪስት ሆቴል አዳራሽ

@getem
@wegoch
የጥበብ ምሽት ከአንጋፋ አርቲስቶች ጋር
🔰ዕንቁላል ፋብሪካ
ከእምቢልታ ሆቴል ከፍ ብሎ በሚገኘው ገነት መናፈሻ እንድቅትዮን
(የብርሃን ዕለት) በወሩ የመጨረሻ ማክሰኞ መጋቢት ፳፬-፳፻፲፩
ዓ.ም. የጥበብ ድግሱን አሰናድቶ ይጠብቆታል.

@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
@getem
በአንድ መንደር ውስጥ የሚኖር አንድ ሰው ነበር።

ይህ ሰው ውሀ ከወንዝ እየቀዳ ቤተ-መንግስት ዘወትር ያመላልስ ነበር። ውሀ
የሚያመላልስባቸው ሁለት እንስራዎችም ነበሩት በነዚህ እንስራዎች
ውሀ እየሞላ ወደ ቤተመንግስት ይውስድባቸው ነበር። ከሁለቱ እንስራዎች አንዱ
ግን ቀዳዳ ነበረው፤ እና ምንም እንኳን ከወንዙ ሁለቱንም እኩል
ውሀ ሞልቷቸው ቢሄድም ቤተመንግስት ሲደርስ ግን አንደኛው እንስራ ሙሉ፤
ቀዳዳ ያለበት እንስራ ደግሞ ጎዶሎ ይሆን ነበር። በዚህ ሁኔታ ሰውዬው
በሁለቱ እንስራዎች አንድ ሙሉ እንስራ ውሀ፤ በሌላኛው ደግሞ ጎዶሎ ውሀ
እያመላለሰ ለረጅም ጊዚያት ቆየ።
ከእለታት አንድ ቀን ታዲያ ቀዳዳ ያለበት እና ዘወትር እያንጠባጠበ የሚሄደው
እንስራ እንዲህ ሲል ለሰውዬው አቤቱታ አቀረበ፡፡
እንስራው፦ "እኔን እና ጓደኛዬን እየተሸከምክ ውሀ ማመላለስ ከጀመርክ እንሆ
ቆየህ።
ሰባራ ሆኜም እንኳን ስታመላልስብኝ ሰነበትክ አሁን ግን ዘወትር ከጌታዬ ፊት
ጎዶሎ ውሀ እየያዝኩኝ መቅረብ አሳፈረኝ። ጓደኛዬ ዘወትር ሙሉ ውሀ ሲወስድ
እኔ ግን ሁሌ ጎዶሎ ማቅረቡ አንገቴን አስደፈኝ። እናም በኔ ውሀ ማመላለሱ
ቢበቃህ ይሻላል።" አለው። ይህን የእንስራውን አሳዛኝ ንግግር የሰማው ሰውዬ
በማስተዋል ቀዳዳውን
እንስራ እየተመለከተ፡-
ሰውዬው፦ "ዛሬ ውሀ ቀድተን ስንመለስ አንድ ነገር አሳይሀልሁ" ሲል ነገረው።
ውሀ ቀድተው ሲመለሱ ሰውዬው የሚያንጠባጥበውን እንስራ ወደ መሬት
እያስተዋለ እንዲሄድ ነገረው። እንስራውም እንደተባለው አደረገ።
በእሱ በኩል እጽዋቶችን ተመለከተ ፍሬ ያፈሩ አትክልቶችን አስተዋለ
የሚያማምሩ አበባዎችን አየ። በዛኛው እንስራ በኩል ግን ምንም አልነበረም።
ምንም እንኳን ዘወትር በተመሳሳይ መንገድ ቢሄዱም እንደዛሬው አስተውሎ
አያውቅም ነበር።
ሰውዬው፦ "አየህ ወደጄ አንተ እንደምታንጠባጥብ ሳውቅ ባንተ በኩል ዘሮችን
ዘራሁ፤ ዘወትር ካንተ በሚንጠባጠበው ውሀ ጥማታቸውን አራሱ፣ ፍሬ አፈሩ፣
አበቡም። ይህ የምትመለከተው አትክልት ሁላ ባንተ በኩል ብቻ ነው ያለው
ሌላኛውን
እንስራ በምሸከምበት በኩል ምንም ነገር የለም እናም ጥቅም የለኝም አትበል።
ሌላው ቢቀር ደካማ ጎንህ እንኳን ለሌሎች ጥቅም አለው" ሲል አስረዳው።
አንዳንዴ ልዩነታችንን አይተን፤ በንጽጽር ብቻ ጥቅም የለኝም እርባና ቢስ ነኝ
ብለን እናስብ ይሆናል። ሌላው ሰው የቻለውን እኛ ባለመቻላችን ብቻ ጎዶሎ
እንደሆንን እናስባለን።
የሌሎች ብርሀን እንጂ የኛ ስለማይታየን ከጨለማ መውጣት ያቅተናል።
ሰባራው እንስራ ሌላኛው እንስራ ሙሉ ውሀ መውሰዱን ተመለከተ እንጂ
በሱ ውሀ ስንት የእጽዋት ነፍስ እንደበቀለ አላስተዋለም።
እኛም እንዲህ ነን የየራሳችን ብርሀን አለን ነገር ግን የሌላው ሰው
ጭላንጭል ያስቀናናል።
ሌሎች ሙሉ ውሀ መሸከም ቢችሉ እንዳንተ ነፍስ መዝራት አይችሉም።
አንተ
እንደነሱ ሙሉ ውሀ መሸከም ቢያቅትህ ጉድለትህ ሌሎች እንዲያብቡ ያደርጋል።
@wegoch
@teku_melanin
********
This is a story about a lonely, lonely man
He lived in a lonely house
On a lonely street
In a lonely part of the world
But, of course, he had the internet
The internet, as you know, was his friend
You could say, his best friend
They would play with each other every day
Watching videos of humans doing all sorts of things
Having sex with each other
Informing people on what was wrong with them and their life
Playing games with young children at home with their parents

The internet looked at him and said, "Yes, I love you very, very, very, very, very, very much. I am your best friend. In fact, I love you so much that I never, ever want us to be apart ever again ever"
"I would like that," said the man
And so they embarked on a life together
Wherever the man went, he took his friend
The man and the internet went everywhere together, except of course the places where the internet could not go
They went to the countryside
They went to birthday parties of the children of some of his less important friends
Different countries
Even the moon
When the man got sad, his friend had so many clever ways to make him feel better
He would get him cooked animals, and show him the people having sex again, and he would always, always agree with him
This one was the man's favourite, and it made him very happy
The man trusted his friend so much
"I feel like I could tell you anything," he said, on a particularly lonely day
"You can. You can tell me anything. I'm your best friend. Anything you say to me will stay strictly between you and the internet"

And so he did
The man shared everything with his friend
All of his fears and desires
All of his loves – past and present
All of the places he had been and was going, and pictures of his penis
He would tell himself, "Man does not live by bread alone"

And then he died
In his lonely house
On the lonely street
In that lonely part of the world 🖤

@wegoch
@teku_melanin
'ተ'ነ'ፋ'ፍ'ቀ'ው'
.
( ዴቭ)
.
ናፈቃት እሷም ናፈቀችው
ፈለጋት እሷም ፈለገችው
በናፈቀው አይኗ የናፈቃት ፊቱን ልታየው ወደደች…በናፈቀው ጆሮዋ
ያን ስርቅርቅ ድምጹን ልትሰማው ከጀለች…በናፈቀው አፍንጫዋ
ወንድነቱን ልታሸት ናፈቀች…በናፈቀው ከንፈሯ ከንፈሩን ልትስም
ናፈቀች…በእጆቹ ሲዳስሳት በሃሳብ ተሰማት፡፡
.
.
እሱም ፈለጋት በናፈቁት አይኖቹ ዳሌዋን ሊያማትር ፈለገ…በናፈቃት
ጆሮው ትንፋሿን መስማት ናፈቀ…በናፈቁት እጆቹ ጡቶቿን ሊዳስስ
አማረው…ሰውነቱን ከሰውነቷ አጣብቆ ሲይዛት ተሰማው…በጀርባው
በኩል ጥብቅ አድርጋ ስታቅፈው በሃሳቡ ውል አለበት፡፡
.
.
ልክ እንደለመደው በግርግዳ ስልክ አልፎ ሂያጇን ጠርቶ
እንድታወራለት አስማምቶ ደውሎ አስጠራት ያ ቁጠኛ አባቷ ቢያገኙት
ምን ሊያደርጉት እንደሚችሉ አላሰበም አሁን
ማሰቢያው እሷ ጋር ነው፡፡
.
.
እንገናኝ ሲላት በደስታ ልቧ ደለቀ የናፍቆቷን ረሃብ እስከሚተርፋት
ልታጣጥም ሞልቶ እስከሚተርፋት ስንቅ አድርጋ ልትወስደው
ቋመጠች፡፡ የለበሰችውን ቢጃማ አወላልቃ የሚወደውን ሮዝ አጭር
ጉርድ ከሚወደው ጠቆር ያለ ኮት ጋር አመሳስላ ለበሰች፡፡ ሁሌ ልበሽ
የሚላትን ፍላት ትንሽየ ጫማ አጠለቀች የገዛላትን ሮዝ ሊፕስቲክ
በስሱ ተቀባች ጸጉሯን እሱ እንደሚወደው አስተካከለች፡፡ከፊቷ
በቆመው መስታወት ራሷን ተመለከተች እሱ የሚወዳትን መሰለች
እሱን እሱን እንድትሆን ትሻለች እና፡፡
.
.
የወዳደቁት የቆሸሹ እና ያልቆሸሹ ካልሲዎች ሰበሰበ ተጠርጎ
የማያውቀውን አቧራ የሞላውን ቤቱን አፀዳዳ የተመነቀረውን አልጋ
በወጉ በወጉ አስተካከለ ትንሿን ቤቱን በሰንደል ጭስ አመጋት ጥሩ
ሽቶ ጨመረባት እሷን ይፈልጋል እና የቀጠሮውን ሰአት አየ መምጫዋ
ሲደርስ ልቡ መምታቷን ጨመረች፡፡
.
.
በትንፋሿ መቆራረጥ በአካሄዷ መሮጥ በናፍቆት መረገጥ ልቧ ክፉኛ
መታ ሰውነቷን የማታውቀው ስሜት ወረራት እሱ ጋር ለመድረስ……
እየደረሰች ናፈቀች……እናፈቀች ተጓዘች……እየተጓዘች ደረሰች፡፡
ስትደርስለት ደስ አለው ተቃቀፉ አንገቱ ስር ሽጉጥ አለች አይኖቿን
ጨፍና በባቢሎን ግንብ እንደታጠረች በሽህ ሰራዊት እንደተከበበች
ቆጠረች ምንም መቶ ከዛ ግንብ ሊያስወጣት እንደማይችል
ደመደመች፡፡
.
.
እንዳቀፋት ሰውነቱ ሞቀ ከፀጉር እስከጥፍሩ በማያውቀው ስሜት
ሰውነቶቹ ቆሙ…እንዳቀፋት አልጋ ላይ ወደቁ…እንደ እንዝርት
አሾራት……እንደ ዳርት ወረወራት……እንደ እንዝርት ሾረች እንደዳርት
ተወረወረች እሳት ሆነ ክሰል ሆነች……ክብሪት ሆነ ጭድ ሆነች ……
አራገባት ነደደች በነደደው ገላዋ መልሳ አቃጠለችው……እንደፈለገው
ሆነችለት አመማት ደስ አለው አቃሰተች ጨመረ ክብሯን ሰጠችው
ክብሯን ወሰደ፡፡
.
.
ደስ የሚል ስቃይ አመማት እሱ ግን ከፋው መውደዷ ጨመረ ሌላ
ሴት አሰበ አብራው መኖር ፈለገች ከቤቱ ሊያስወጣት ወሰነ በፍቅሩ
ተጎዳች ያደረገውን ጀብዱ ለጓደኞቹ ነገረ እነሱም አደነቁት ከዛን ግዜ
በኋላ የማታውቀው የሴት ድምጽ አልሰማችም ቀጠሮም አልያዘችም
ቤት ውስጥ ዘግታ ተቀመጠች ወንዶች እንደዚህ ናቸው አለች
መቅረብ አልፈልግም ብላ ሁሉንም ኮነነች ሴትነቷን የሚፈልግ ወንድ
አግኝቷት ወንዶችን ሁሉ ጠላች እሱም ስራውን
ተያይዞታል እሷም ወንዶችን መውቀስ መጥላት ቀጥላለች፡፡
.
.
ወሰነች ማድረግ አለብኝ አለች የአባቷን ሽጉጥ ሰረቀች ወደ ቤቱ
ሄደች የዛን ግዜ የነበረው ሽታ አሁንም አለ የዛን ግዜው ሰንደል
ከውጭ ይሸታል ልክ የዛን ግዜ እንደነበረው የሲቃ ድምጽ……
ከፍታው ገባች ራቁቱን አየችው…እንደገና ሌላ ራቁት አየች
አላመነታችም ሽጉጧን አወጣች አቀባበለችው……
.
.
ከነመለመሉ ስለወንድ ልጅ ብሎ ለመነ እሷ ግን
አልሰማችውምየጥይት ጩኸት አካባውን ረበሸው ወፎች በድምጹ
ደንግጠው በረሩ……
አቅፏት አለቀሰ ባደረገው ነገር ፀፀት ውስጡን ተቆጣጠረው ልጅቷ
ራሷን አጠፋች
ለወደደችው ፍቅር ልታስፈራራው ይዛው የመጣችውን ማስፈራሪያ
ራሷን ገደለችበት፡፡
እስር ቤት እራሱን ዘጋ ከህይወት ገጽም እስኪሰረዝ መጠበቅ
አልፈለገም ሞትን በሞቷ አብሯት ሊሞት በቁሙ ሞተ ………
ህይወት ግን አታቆምም አሁንም የሚሸኙትን ትሸኛለች የሚተኩትን
ትተካለች ፡፡

@wegoch
@wegoch
@gebriel_19
Forwarded from Melkam74 Digital Magazine
Melkam74 ቅፅ ፩ ቁጥር 4.pdf
4.5 MB
📠 Melkam74 ቅፅ 1 ቁጥር 4

💰 ፓኬጅ ከገዙ በብር 1.27 ብቻ 💰
Fight autism home teacher for autistic children በኦቲዝም ለታመሙ ልጆች ብቻ:

በኦቲዝም ለተጠቃ/ች ልጅ ድጋፍ፣ ክትትል እና የቤት ዉስጥ ትምህርት ይፈልጋሉ?
ኦቲዝም ምንድን ነው?
ኦቲዝም በህፃናት/ልጆች የነርቭና የእድገት ሂደት ላይ ውስንነትን በማስከተል ልጆቹ ከሰዉ ጋር የሚኖራቸውን ግንኙነትና የመግባባት ክህሎት እንዲሁም የመረዳት ችሎታ የሚጎዳ/የሚቀንስ ህመም ነዉ።
ኦቲዝም ለሁለንተናዊ የህፃናት/የልጆች እድገት አስፈላጊ የሆኑ ማህበራዊ ግንኙነቶችን እንዲሁም የልጆቹን ግለሰባዊ ባህሪያቶች ይጎዳል።
መፍትሄው ምንድን ነው?

ምንም እንኳ እስከ አሁን ድረስ ኦቲዝምን ፈፅሞ ሊያድን የሚችል ህክምና ባይኖርም ልጅዎ ላይ የሚታዩትን የህመም ምልክቶች በመቀነስ የልጅዎን እድገትና የትምህርት አቀባበል ሁኔታ ማሻሻል ይቻላል።
ይህንንም የልጁ/ቷን ማህበረዊ፣ የመግባባት ክህሎትና ባህሪ ላይ አትኩረው በሚሰሩ ባለሙያዎች በሚተገበሩ ተከታታይ እና የተዋጣላቸዉ መርሃግብሮች ማሳካት ይቻላል።
ከምንሰጣቸው ድጋፍ፣ ክትትል እና ትምህርት መካከል፦
የመግባባት ክህሎት፦ የኦቲዝም ተጠቂ ልጅን የማህበራዊ እና የቋንቋ ችግሮች ላይ በመሥራት የመግባባት ክህሎትን ማጎልበት።
የባህሪ ለዉጥ፡- የኦቲዝም ተጠቂ ልጅ ሊኖሩት/ዋት የሚችሉትን አስቸጋሪ ባህሪያትን በመቀነስ እና መልካም ሥነምግባርን በማስረፅ ተፈላጊ የባህሪ ለዉጥ ማምጣት።

ትምህርት፡- ኦቲዝም ላለባቸዉ ህፃናት በጥናት በተቀረፀ የትምህርት መርኃግብር እና ለዚሁ አላማ በተዘጋጁ የትምህርት መርጃ መሳርያዎች በመታገዝ የቤት ውስጥ ተጨማሪ ትምህርት በመስጠት የልጆቹን የትምህርት አቀባበል ማሳደግ።

ቤተሰብ ተኮር ድጋፍ፡- ወላጆችና ሌሎች የቤተሰቡ አባላት የኦቲዝም ተጠቂ ልጅን የመግባባት ክህሎት እና ችግሮችን የመፍታት ችሎታ ለማዳበር በምን መልኩ መቅረብ እና አብረዉ መጫወት እንዳላባቸው ማስተማር።

ለበለጠ መረጃ በሚከተሉት የስልክ ቁጥሮች ይደውሉ፦
0913011134
0910916602

@wegoch
@gebriel_19
*********
ህይወት ተከታትለው የሚመጡ ተፈጥሮአዊ ድንገተኛ ለውጦች ድምር ናት፡፡
ለውጦችን ለመታገል እና ለቋቋም አትጣሩ፡፡በራሳችሁ ላይ ሀዘን ከመጥራት በቀር የምታተርፉት ነገር የለም እውነታ እውነታ ይሆን ዘንድ ተውት
ነገሮች ሁሉ ተፈጥሮአዊ መንገዳቸውን ተከትለው
እንደፈቀዱት እንዲፈሱ እድል ስጡዋቸው ሁሉም ነገር ባለበት ሁኔታ ደስ
ይበላችሁ፡፡
ይህን ስትረዱ መኖር ይቀላችኋል፡፡

🖋በሄደው አትናደድ፤ በመጣውም አይግረምህ፤
ዛሬ የመጣውም ነገ ይሄዳል።
ትላንት የሄደውም ነገ ይመጣል።
ሁሉም እንደ ሰአቱ ይለዋወጣል።
አንተ ግን ቅንነትህን አትጣል!"😊

🖍 ከታዋቂነት ከዝና ይልቅ ልትጨነቅ የሚገባህ ለባህርይህ ነው
ምክንያቱም ዝና ሌሎች አንተ ነህ ብለው የሚያስቡት ነገር ሲሆን ባህሪ ግን አንተ በትክክል የሆንከው ነገር ነው ።

🖌ከእርቃን ሰውነት ይልቅ እርቃን ነብስ ታሳዝነኛለች!
ገላን በብጣሽ ጨርቅ መሸፈን ይቻላል
ባዶ ነብስ መሸፈን መሙላት ግን ከባድ ነው።

@wegoch
@words19 💖
የሚስቴ ሰርግ ማስታወሻ(ልዑል ሀይሌ)
......................................................
ውዴ! ምንም እንኳ ቁመቴ አጥሮ ለሌላ ሲድሩሽ አማትሬ ማየትቢሳነኝም
በቤታችሁ አጥር ተንጠላጥዬ ናፍቆቴን ልገልፅልሽ እንደምንም የደረሰውን እጄን
አወዛውዤ ነበር።ነገር ግን የአባትሽ ከዘራ ከአንቺ የናፍቆት ምላሽ ቀድሞ እጄን
ስለሰበረኝ ካንቺ በፊት ስለ አባትሽ ከዘራ ልፅፍ ቀሪዋን ግራ እጄን
አለማምጃለሁ!(ለካ አሁን ሲገባኝ የቀኝ እጅ የቀለም ቀንድ የግራ እጅ መሃይም ኖሪያለሁ)...እውነት ውዴ!..አባትሽ አባትሽ ባይሆኑ እንዲህ እላቸው ነበር። "ምነው እጄን ነሱኝ ልጆን ሰላም ልላት አንድ እጄን ሳነሳ፤ ከዘራዎት ነው ወይ
ለልጆ የተዳረ ያ ጎበዝ ጎልማሳ።"
.
እውነት ውዴ አባትሽ አባትሽ ባይሆኑ እንዲህ እላቸው ነበር
"ይኸው ዕድሜ ለእርሶ
ዱላዎት ሰብሮኛል፤
ለድብደባ ሱሶ ነገ ልምጣሎት ወይ አንድ እግሬ ቀርቶኛል።"
ነገር ግን የአባትሽን አባት መሆን ልሽር አይቻለኝምና።ወደ ከዘራው
ተሸጋግሬ
ልወቅሰው ተነሳሁ። ውዴ! ያ ከዘራ የአባትሽ ሆነ እንጂ ሌላ ከዘራ ቢሆን
እንዲህ
ብዬ ቅስሙን ልሰብረው ተነስቼ ነበር(አ
ይጣል የከዘራ ቅስም!)
"ምን አይተህ ነው ከ`ጄ
አጥንት የሰበርከው
ሲቀር ተከፋህ ወይ
አምና የለመድከው"
ዳሩ ምን ያደርጋል ከዘራው የአባትሽ ስለሆነ ትቼዋለሁ...ለነገሩ ምን
አለፋኝ
አጥር ዘልዬ እጄን እንዳነሳ፤ አባትሽም ከዘራቸውን እንዲያነሱ ምክንያት
የሆንሺው አንቺ አለሽ አይደል?! ብዬ ወዳንቺ ልዞር አሰብኩኝ። እውነት
ውዴ!...አንቺ አንቺን ባትሆኚ እንዲህ ብዬ ባለማመድኳት ግራ እጄ
ልፅፍልሽ
አስቤ ነበር
"ናፍቆት አንገብግቦኝ እጄን ባነሳልሽ፤
የአምናው ክህደት ዳዴ
በአባትሽ ከዘራ እግ፡ር አወጣልሽ፤
ክህደትሽስ ይሁን ይቁም እግር ያውጣ፤
ልብ ይሰበራል ወይ
ፍቅሩን ሊገልፅልሽ ለሰርግሽ ለመጣ።"
ምን ዋጋ አለው?! አንቺ አንቺ ሆነሻል...
ምን ያደርጋል!?..ከዘራውን መንካት አባትሽን፤ አባትሽን መንካት አንቺን፤
አንቺን
መንካት የገዛ ራሴን ህመም መቀስቀስ ስለሚሆንብኝ ልተወው
ተገድጄአለሁ! ...ምክንያቱም አፈቅርሻለሁ!!..የፍቅሬ ልክ ክደሽኝ ሄደሽ
እንኳ
በሰርግሽ ዕለት በአጥራችሁ ተንጠልጥዬ የአባትሽ ከዘራ ሲሳይ ሆኜ
በመመለስ
ገልጫለሁ። ያወዛወዝኩትን እጄን በቅፅበት አይተሽው ከሆነ ለስንብት
እንዳነሳሁት ታውቂልኝ ዘንድ አሳውቅሻለሁ...(የሚቀጥል...)


፲፰-፩-፳፻፲፩
ከለሊቱ ፭ ሰዓት ከ ፲፭

@wegoch
@wegoch
@gebriel_19
ሲገባኝ ከታች ያሉት ጥያቄዎች ነጋችንን ያሳያሉ!
ከማን ጋር ነው የምትውሉት?
የት ነው ምትውሉት?
ምን እያወራችሁ ነው የምትውሉት?
እሱ ነገር ሊያሳስበን ይገባል!

@hanahailu
@wegoch
🔝


"ኢትዮጵያን አናውቃትም"

**** **** ****
*ኢትዮጵያን አናውቃትም! አውቃታለሁ የሚል ደፋር ነው። ከምናስባት ሁሉ በላይ የማትገመት ሀገር ናት።
እኛኮ ያልሞከርነው ክፋት የለም። እንደ ሂትለር ዘር ተኮር ስብከትን አስፋፍተናል። እንደ አይሁድ ሰውን እርቃኑን ሰቅለናል፤ በድንጋይ ወግረን ገድለናል። እንደ ስታሊን ቁልቁል ሰቅለን ገርፈናል፤ አሰቃይተናል።
*እኛ ኢትዮጵያውያን ሩዋንዳን ከበተነው የዘር ተኮር ጥላቻ ስብከት በላይ ተሰብከናል፤ ሶማሊያን መንግሥት አልባ ካደረገው በላይ ችግር ተፈጽሞብናል፤ ሶሪያን ካፈራረሰው በላይ ሴራና ግጭት ተከናውኖብናል። ተከፋፍለንና ተበታትነን እንድንጠፋ እስከመገንጠል መብት ተሰጥቶናል። ይህ ሁሉ ተሞክሮም ግን አለን። ይህችን ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር ልዩ ምሥጢር ካልሆነ በቀር ማነው የሚያኖራት?
*ሳስበው ክፋትን ሁሉ ሞክረን ስለጨረስን አሁን መልካም ነገር የሚሞከርበት ጊዜ ላይ ነው። ካሁን በኋላ በዚህች ሀገር ላይ ያልተሞከረ አዲስ ክፋት ፈልጎ ሊያገኝ የሚችል ስለማይኖር ሁሉም በጎ በጎውን ማሰብና መሥራት መጀመሩ አይቀርም። ለኢትዮጵያ የተሻለ ጊዜ እየመጣ ነው።
*"ኢትዮጵያን አውቃታለሁ" የሚል ሰው ድፍረቱ ይገርመኛል። እኔ እንደማላውቃት ነው ማውቀው። ኢትዮጵያን አናውቃትም። ፈጽሞ አላስተዋልናትም። ኢትዮጵያ የራሷ ማንነት ያላት ሀገር ስለሆነች ከሌላ ሀገር በተቀዳ ሐሳብ ልትመራ አትችልም። ማንም ሀገር የሌለው የራሷ የሆነ ጥበብና እውቀት አላት። በድህነት መነፅር ስለምናያት ነው እንጅ... ልዩና ማንም የሚመኛት ሀገር ናት።
*አንዳንዱ "የኢትዮጵያ ሕዝብ ያውቀኛል፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ነው የምታገለው፣ ሕዝቡ ከእኔ ጋር ነው..." ሲል ይሰማል። ምን ማለቱ ነው? የትኛው ሕዝብ? ፌስቡክ ላይ ያለው? ሚዲያ ያለው? ፖለቲከኛው? ሃይማኖተኛው? ወይስ የቱ? መለየት አለበት። ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚያውቀውም የሚሰማውም ሰው ያለ አይመስለኝም። እያስተዋልን እንናገር።"

# ዶክተር ዓለማየሁ ዋሴ
የእመጓ ዝጎራ እና መርበብት ደራሲ
ኅዳር 5/2011 ዓ/ም በራስ ሆቴል አዳራሽ ከተናገሩት የተወሰደ

@wegoch
"አዲስ ባሬስታ እንጂ ለውጥ መቼ መጣ!" [Arts Tv World] 16k
ጦቢያ ግጥምን በጃዝ #92-02 | በኃይሉ ገ/እግዚአብሔር
"አዲስ ባሬስታ እንጂ ለውጥ መቼ መጣ!" (Arts Tv World)
👤 ጦቢያ ግጥምን በጃዝ #92-02 | በኃይሉ ገ/እግዚአብሔር

🕜 11:50
💾 10.97 MB

ግጥም ብቻ

@wegoch
@wegoch
@gebriel_19
2024/09/28 07:26:53
Back to Top
HTML Embed Code: