Telegram Web Link
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኛ⬇️

እባክህ ወንድሜ ጩኸታችንን አሰማልን።🙏 በኢትዮጵያ አየር መንገድ አቆጣጠር ዶ/ር አብይ ገና ስልጣን ላይ አልወጣም።

በጣም ይገርማል። አየር መንገዱ ሊሸጥ ነው የሚባል ወሬ ሲናፈስ ዶ/ር አብይን ጨምሮ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንዴት ይሆናል በሚለው ጉዳይ በስፋት ሲያወሩበት ሰንብቷል። ጥሩ ነው። ነገር ግን  ለአየር መንገዱ ሰራተኞችስ የሚቆረቆረው ማን ነው? ምናልባትም በአሁን ሰዓት ሀገሪቱ ውስጥ ካሉት መስሪያ ቤቶች ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት ቀጥሎ ከባድ የመብት ጥሰት የሚደረግበት ጊቢ የኢትዮጵያ አየር መንገድ መሆኑን መላው የጊቢው ሰራተኛ የሚስማማበት ጉዳይ ነው።

በመስሪያ ቤቱ ከሚታዩ ረገጣዎች በጣም በጥቂቱ፦

1:- ላለፋት 3 ዓመታት ስልክ ይዘን እንዳንገባ እና ምንም አይነት ማስረጃዎችን እንዳንይዝ ተደርገናል።

2:- መብታችንን በአግባቡ ስንጠይቅ ማስፈራርያ እና ዛቻ ይደርስብናል፤ ካልፈለጋችሁ መውጣት ትችላላችሁ እንባላለን፤ የተለያዩ ቅጣቶች ይደርሱብናል።

3:- ድንገት አንድ ሱፍ የለበሰ ሰው በር ላይ ቆሞ የራሱን ምክንያት ፈጥሮ ሊያባርርህ ይችላል። በዚህም ምክንያት ስራችን የዛፍ ላይ እንቅልፍ ሆኖብናል።

4:- ስለጊቢው የተሰማንን እና እየተደረገ ያለውን ነገር በነፃነት መናገር እና በማህበራዊ ድህረ ገፆች ማሳወቅ አንችልም። በዚህ ምክንያት ከስራቸው የተባረሩ ሰራተኞች ቤት ይቁጠራቸው።

5:- በአቪዬሽን አካዳሚ ከሰለጠንንበት ሙያ ውጪ እንድንሰራ አንገደዳለን። ይህ እንዴት ይሆናል ብለን በምንጠይቅበት ጊዜ "ሌላ ሰው ከጀርባችሁ አለ፤ የእገሌ ተላላኪ ናችሁ " ተብለን እንቀጣለን። ከባሰም ከስራ እስከመሰናበት እንደርሳለን።

6:- ሰራተኞች human error ሰራችሁ ተብለው ማዕከላዊ ገብተው መገረፋቸው የአደባባይ ምስጢር ነው።

6:- 7 እና 8 አመት የሰሩ ሰራተኞች እያሉ 3 ዓመት በቅጡ ያልሰራ ብሄር ተመርጦ ከሀገር ውጪ (out station) ሄዶ እንዲሰራ ይደረጋል።

7:- በእረፍት ቀናችን እና በትርፍ ሰዓት በግድ  እንድንሰራ እንደረጋለን በምትኩም ክፈሉን ወይም ተመጣጣኝ እረፍት ስጡን ብለን ስንጠይቅ ለመክፈል ፈቃደኞች አይሆኑም እረፍትም አይሰጡንም ጭራሽ ሌላ ማስፈራርያ ይደርስብናል።

8:- መስፈርቱን የማያሟሉ ሴቶች በሴትነታቸው ብቻ ተጠቅመው ሆስተስ ሲሆኑ ተመልክተናል።

9:- ይህን ሁሉ ተቋቁመን በሰላም እንኑር ስንል ደግሞ የጥበቃ ሰራተኞች ድንገት የሆነ ሰዓት ላይ አለባበሳችሁን ቀይሩ ይሄ ጠበበ ይሄ ሰፋ፤ ፀጉራችሁን እንዲህ ካላደረጋችሁ እይሉ ከልክ በላይ የሆነ ጫና እያሳደሩብን ቁም ስቅላችንን ያሳዩናል።

10:- KPI (Key Performance Indicator) በሚባል የስራ አፈፃፀም መገምገሚያን ሽፋን በማድረግ በብሄር እና በሃይማኖት የሚሰራውን መድሎ እና ኢ ፍትሃዊነትንማ ታግለን ታግለን ስላቃተን ተስፋ ቆርጠን ትተነዋል።

በነዚህ እና ሌሎች ባልጠቀስኳቸው እጅግ በጣም ብዙ ምክንያቶች ሰራተኛው ተስፋ በመቁረጥ ውስጥ ሆኖ ቀኑን እየገፋ ይገኛል።  ከ 80% በላይ የሚሆን ትኩስ እና የተማረ የወጣት ሀይል በጥቂት ለራሳቸው እና ለብሄራቸው በወገኑ አስተዳዳሪዎች ምክንያት ተስፋ ቢስ እና ሀገሩን የሚጠላ ሆኗል።

ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ከሀገር እየወጣ የቀረውንም ቤት ይቁጠረው።   እናም ሳይቃጠል በቅጠል ነውና አሁን መላው አለም ያጨበጨበለት አየር መንገድ ሰራተኛውን ረግጦ የአሸዋ ላይ ህንፃ ሆኗል እና በኋላ አይሆኑ አወዳደቅ ወድቆ አለም ከመሳቁና ጠላት ከመደሰቱ በፊት የሚመለከትቸው አካላት በተለይም የትራንስፖርት ሚንስቴር እና በየአመቱ ያተረፍነውን ትርፍ እየተሰበሰቡ የሚቀራመቱት የቦርድ አባላት የቀን ጅቦች ቆም ብለው ሊያስቡበት ይገባል። "ባረጀ አስተሳሰብ አዲስ ትውልድ አይመራም"። ሰራተኛው ጥሩ ስሜት ላይ አይደለም። ጥሩ እያሰበ አይደለም። ሰራተኛን ንቆ እና ረግጦ የትም መድረስ አይቻልም።

ስሜቴን እንደምንም ተቆጣጥሬው የፃፍኩት። ኪ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኛ!

ከቲክቫህ ገፅ ላይ የተወሰደ

@wegoch
@wegoch
ንብረታችን አይደለም ወይ????


አማራ ጠላቶቹ ያረከሱትን እቃ ጠበል ረጭቶ ጻ ርኩስ
መንፈስ ብሎ ይደግምበትና እቃውን ለበጎ አላማ
ያውለዋል ።ጣሊያን የሰራውን መንገድና ህንጻ ከመጻነት
በሃላ ላፍርስ ልገንድስ አላለም ። ጠበሉን እየረጨ
ካሚዩንና ትሬንታ ኳትሮ ነዳበት እንጅ ። ምን ማለት
ፈልጌ የደረሰብን ግፍ ብዙ ቢሆንም ያውም በገዛ
ገንዘባችን የተሰራውን ሃብት ማውደም ከአማራነት
ብልህነት ጋር ይመጣጠን ይሆን???ብየ መጠየቄ
አልቀረም ። ምናልባት በበረከት መኪና ላይ
የተወሰደው እርምጃ ከብሶት አንጻር ብዙ ነው ባይባልም
እንደ ሃገር አንጡራ ሃብት ግን ያስቆጫል ። በተረፈ ግን
በባለሃብቶቹ ሆቴሎች ላይ የተወሰደው እርምጃ ግን
አማራዊ ሚዛን የጠበቀ ነው ወይ ?ብየ መጠየቄ
አልቀረም ። ገና ለገና ያጣነውን ለማግኘት በመመኘት
የያዝነውን ማጥፋት እጥፍ ዋጋ አያስከፍልም ወይ????
ወገኖቼ ነገሮችን በማስተዋልና በማስተንተን
እናድርጋቸው !!!

@Balmbaras
@wegoch
@wegoch
ለውጥ በሕግና በሥርዓት ካልተመራ፡ ሕዝብ በርጋታና
በማስተዋል ካልተጓዘ፡ ከምትለወጥ ሀገር ይልቅ
የመረቀነች ሀገር እንፈጥራለን፡፡ ምርቃና ደግሞ
ከዕውቀት ይልቅ ለስሜት፡ ከጤና ይልቅ ለዕብደት
ይቀርባል፡፡ ሀገር እንዳትመረቅን ስክነት፡ መረጋጋትና
ሕግ አክባሪነት ወሳኞች ናቸው፡፡ ጊዜው ይህን
ይጠይቀናል፡፡


((( ዳንኤል ክብረት )))

@balmbaras
@wegoch
@wegoch
ናቲ😂

ሂውማን ሄር ፣ አርቲ ፣ ሜካፕ ምናምን የምትጠቀሙ ሰው መሰል
አሻንጉሊቶቻችን ሆይ : እናንተኮ ስትሞቱ ኢትዮጵያ አትሆኑም…
ኢትዮጲስ ነው የምትሆኑት

@wegoch
@wegoch
*ይድረስ ለአዲስ ተመራቂ ተማሪዎች*

በዚህ አመት ለተመረቃችሁ ተማሪዎች ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ።ትምህርት የሚያልቅ ባይሆንም የመጀመሪያውን ማዕረግ (ዲፕሎማ፣ዲግሪ...) ለመረከብ መብቃት አንድ ስኬት ነው።የሰው ልጅ ህይወት ከመጽሐፍ ጋር በጣሙን ይመሳሰላል።በእርግጥም ህይወታችን ራሱ መጽሐፍ ይወጣዋል።ተወልደን ይህችን ዓለም መቀላቀላችን እና የእድገታችን ሂደት አንደኛው እና ዋናው ምእራፍ ነው። መማር እና ተምረን መመረቅ ሁለተኛው የህይወታችን ምእራፍ ነው። ወደስራው ዓለም ገብተን ከኑሮ ጋር ከባድ ትግል የምንፋለምበት ረጅሙ እና ሦስተኛው ምእራፍ ነው።ማግባት፣መውለድ...እና መሞት በተራቸው ምእራፉን ይሞሉት እና አንድ ወጥ መጽሐፍ ይወጣዋል። እናም ይሄ የትምህርት ዓለም ቆይታችሁን ምእራፍ ዘግታችሁ ሌላ አዲስ ምእራፍ ልትጀምሩ ነው።
ዛሬ ለአዲስ ተመራቂ ተማሪዎች ከራሴ ከህይወት ተሞክሮዬ(ትንሽም ብትሆን) የተማርኩትን ላካፍላችሁ ወደድኩ።ይረዳችኋል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።

ልነግራችሁ የፈለኩት ዋናው ቁምነገር "የትምህርቱ ዓለም እና አሁን የምትገቡበት የስራው ዓለም በጣም የተለያዩ "ሆድ እና ጀርባ"መሆናቸውን ስለሆነ አካላዊም ስነ ልቦናዊም ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ ነው #keep your expectation low# ።" በትምህርት ዓለም የነበራችሁ ጥረት፣ተወዳጅነት፣ሰቃይነት፣ግብረ-ገብነት፣ ስኬት ወዘት.. በስራው ዓለም ሙሉ ለሙሉ ላይረዷችሁ ይችላሉ።እኔም እንደማንኛውም ተማሪ በነበርኩበት ኮሌጅ በስነ-ምግባር በጣም የተመሰገንኩ፣የተማሪዎች መሪ(representative)፣ ተቋሙን ወክዬ ብዙ መድረኮች ላይ የቆምኩ፣የሜዳልያ ተመራቂ ወዘተ...ነበርኩ።ያም ወደስራው ዓለም ስገባ ህይወቴን እንደሚለውጥ ተስፋ ሰጥቶኝ ነበር።የምርቃቴም ቀን ሜዳልያውን ስሸለም ብዙ ድርጅቶች የቢዝነስ ካርድ እየሰጡ "pls አብረን እንስራ" ብለውኝ ነበር።ግን ያ ሁሉ 90% ውሸት ነበር።(ይሄ እድል እና ፍላጎት እንደ ሰኔና ሰኞ የገጠመላቸውን ጥቂት ተማሪዎች አይመለከትም።በርግጥ በጣም ከብዙ በጥቂቱ አንዳንድ እድል ይሁን አጋጣሚ ባላውቅም ከመጀመሪያው የሚሳካላቸው ልጆች እንዳሉ አስተውያለሁ።) ተመርቄ ከወጣው በኋላ ወደስራው ዓለም ስገባ ያ የነበረኝ ተፈላጊነት፣ስም፣ሜዳልያ...እዛው ካምፓስ ነው የቀረው።እንደ አዲስ ነው መጀመር የነበረብኝ።even የመጀመሪያ ደሞዜም 1000 ብር ነበር።(የማወራው ከ3 ተኩል በፊት ስለሆነ ነገር ነው።) በዚህ ደሞዝ ቤት ኪራይ፣ምግብ፣ታክሲ...ብቻ ከባድ ነበር።

ሁለት ዓመት ድርጅት እየቀያየርኩ የተሻለ ነገር ፈለኩ።ግን ተቀጥሮ እስከተሰራ ድረስ ያው ነው።ከባድ ጥረት እና ጊዜ ይፈልጋል።
እናም ቁም ነገሮቹን ባጭሩ ላስቀምጥላችሁ።

1፦ልክ በካምፓስ እንዳለው የተማሪ ለተማሪ ፉክክር ሁሉ በስራውም ዓለም ከባድ የሆነ ፉክክር አለ።ሰዎች ራሳቸውን ለማሳደግ ከባድ የሆነ ትግል ያደርጋሉ።እናም አዲስ የተማረ የሰው ኃይል ገበያው ላይ ሲጨመር ፉክክሩን ይበልጥ ያከረዋል።በዚም የቅጥር ገበያው (employment market) ላይ ያሉ ሰዎች በትንሽ ደሞዝ ፣ ብዙ ስራ፣ ለረጅም ሰአት፣ ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ይሰራሉ። ይህ ደሞ ለአዲሱ ተመራቂ ከዛም በታች ወርዶ እንዲሰራ ይዳርጋል።የሆነም ነገር ነው።እናም ባጭሩ ብዙ ነገር expect ማድረግ ሞራልን ይጎዳል።ጠንክሮ ለመስራት እና ተፎካካሪ ለመሆን መዘጋጀት ያስፈልጋል።

2፦ሁልጊዜም ራሳችሁን ማሳደግ ላይ (personal development) መስራት አትርሱ።ባላችሁበት መርገጥ በገቢም በእውቀትም ወደኋላ ያስቀራል።ውሃም አንድ ቦታ ሲረጋ ይሸታል።በማንበብ፣ለሚድያዎች ቅርብ በመሆን፣ በመጠየቅ፣ ከሰዎች ጋር መረጃ በመለዋወጥ፣ በመማር ራሳችሁን በየለቱ አሳድጉ።ያኔ ተፈላጊነትም ይመጣል። የሀገሪቱም (የዓለምም) ኢኮኖሚ በየሳምንቱ እና በየወሩ ይዋዥቃል።እናም ከኢኮኖሚካል ጥቅሙ ለመጠቀም ፤ከጉዳቱም ለማምለጥ መረጃ ወሳኝ ነው።በዚህ አንድ ዓመት ውስጥ እንኳን የ"ብር" ዋጋ ምን ያህል inflate እንዳደረገ ማየት ይቻላል።ስለሰራተኞች ደሞዝም ብትጠይቁ እንዲሁ ነው።ስለዚህ በእውቀትም በሙያም ሁሌም ራሳችሁን ገንቡ።አንድ ቦታ ብቻ ተቀጥሮ መስራት አንድ ሙያ ብቻ ነው የሚያስጨብጣችሁ፤ ስራ ስትቀያይሩ ግን እውቀትም ታገኛላችሁ፤ሰውም ትተዋወቃላችሁ፤የስራውን ገበያም ታውቁታላችሁ።

3፦ማንኛውንም ስራ ለመስራት ተዘጋጁ።ስራ አይናቅም።ብዙ ሰዎች በተመረቁበት field አደለም እየሰሩ ያሉት።እናም "በተመረኩበት ካልሰራሁ" ካላችሁ መቸገራችሁ አይቀርም።ያገኛችሁትን ስራ እየሰራችሁ የምትፈልጉትን ስራ በዛው ታፈላልጋላችሁ። "Love what youመሄድን do,'till you do what you love" እንደሚባለው።

4፦ሁልጊዜም ለወርቁ ሩጡ (Go for the gold)። ለምቾት ሳይሆን ለስኬት ስሩ፤ ለብር ሳይሆን ለመስራት ስሩ።ስራችሁን ጥንቅቅ አድርጋችሁ ከሰራችሁ "ብር" ራሱ ወደእናንተ ይመጣል።ትንሽ ነገር ስታገኙ ራሳችሁን እዛው አትገድቡት፤ dig for more። የእኔ ጓደኞች ከተመረቅን በኋላ በየገቡበት ድርጅት እንደገቡ "በቃን" ብለው ከ4000 ብር ባልበለጠ ደሞዝ ለማብቃቃት እየሞከሩ አሁንም እዛው ናቸው።ከዛ በላይ አልሞከሩም።እኔ ግን በተቻለኝ መጠን ብዙ ቦታዎች ሞከርኩ።በርግጥ ከባድ risk አለው።ያላችሁን ነገር ታጡ ይሆናል።የቤት ኪራይ ምከፍለው አጥቼ ተባርሬ አውቃለሁ።ኪሴ ባዶ ሆኖ ብዙ ቀናት ጾም አድሬአለሁ።ከስራ ስራ ስቀይር ነገሮች ዝብርቅርቅ ብለውብኛል።ያ ግን ለስኬቴ ግብዓት እና ጥንካሬ ሆኖኛል።ዛሬ ባለአምስት አሃዝ ደሞዝ አገኛለሁ።ንብረትም(Asset) እየገነባሁ ነው።ይሄ የሆነው ሩጫዬ ለወርቁ ስለነበር ነው።እናም እግዚአብሔር በተፈጥሮ ትልቅ አቅም ሰጥቶናል። dont wast it by stucking somewhere.

5፦በመጨረሻም የምታገኙትን ገንዘብ በአግባቡ manage ማድረግ መልመድ ያስፈልጋል።ብዙ...በጣም ብዙ ሰራተኞች የሚቸገሩበት ጉዳይ ነው።ደሞዝ ከወር እስከ ወር አልደርስ ይላል።ደሞዛቹህ እጃቹህ ከመግባቱ በፊት እቅድያገኛችሁትን አውጡለት፤መድቡት።ከዛ እጃቹህ ውስጥ ሲገባ ወደተመደበለት ቦታ አውሉት።በምንም ተአምር ገንዘብ ከቁጥጥራችሁ ውጭ እንዳይሆን፤እንዲቆጣጠራችሁ አታድርጉ።አንዴ ከቁጥጥራችሁ ውጭ ከሆነ በጣም አስቸጋሪ ነው።መጨረሻችሁ ተበዳሪ መሆን ነው።
በእኔ እምነት "ገንዘብ" ከእድሜያችን ጋር ይገናኛል።ገንዘብ/ደሞዝ ለማግኘት ከህይወታችን ላይ 30 ሙሉ ቀናትን ሰጥተን በምትኩ የምናገኘው "የእድሜያችን ቅያሪ" ነው።እናም ይህን ያህል የእድሜያችንን portion የወሰደ ነገር እንዴት ያለአግባብ እናወጣዋለን?!?! ስለዚህ ለፍታችሁ ሰርታችሁ የልፋታችሁን ዋጋ ቁም ነገር ላይ ማዋል ይገባል። ለዚህ ደግሞ በጣም recommend የማደርገው እቁብን ነው።እቁብ ስትጥሉ save እያደረጋችሁ ነው።ብሩ ተጠራቅሞ ሲመጣ አቅም ይሰጣችኋል።ያኔ ጠንከር ያለ ነገር ማድረግ ትችላላችሁ።ሌላው...ጥሬ ገንዘብን(cash) ወደ ቁሳቁስ መቀየርም አንዱ ብርን ማዳኛ እና ለረጅም ጊዜ ማቆያ ዘዴ ነው።ባጭሩ የምታገኟትን እያንዳንዷን ገንዘብ save ማድረግ እና ቁምነገር ላይ ማዋል ነው።

6፦last but not least...በየሃይማኖታችሁ ፈጣሪ በጥረታችሁ እንዲያግዛችሁ፣ትርጉም ያለው ኑሮ መኖርን እንዲያሳያችሁ፣ ለሰዎች መሰናክል ሳይሆን አርአያ እንድትሆኑ፣ ኑሯችሁ እንዲባረክ መጸለይ በጣም ይረዳል።ጸሎት ልክ እንደ leverage ነው።ጥረታችንን በ
እጥፍ ያባ
ዛው

እና ስኬታችንን ቅርብ ያደርገዋል።

ከራሴም ህይወት፣ ከብዙ ሰዎች የህይወት ተሞክሮ እና የሚያሰሙት ቅሬታ እና ከተለያዩ መጽሐፍት ላይ የተረዳኋቸው ቁም ነገሮች ከብዙ በትንሹ እነዚህ ናቸው።ብዙ ብጽፍ እና ይበልጥ ብገልጸው ደስ ይለኝ ነበር።ረዝሞ እንዳያሰለች ሰጋሁና በዚሁ ቋጨሁት። እነዚህን መጽሐፍት ብታነቡ ስራን እና ኑሮን እንዴት አስማምታችሁ መሔድ እንዳለባችሁ እውቀትን ያስጨብጧችኋል።

@ሰባቱ የስኬታማ ሰዎች ባህሪያት
@25 የስኬት ቁልፎች(ዶ/ር ኢዮብ ማሞ)
@Rich dad Poor dad(robert kiyosaki)
@The monk who sold his ferrari(robin sharma)
@You can win (shiv keyra)

ጽሑፉ ይረዳችኋል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።

መልካም የስራ ዘመን! መልካም እድል!!!

@Fafi_G21
@wegoch
@wegoch
ልጓም!!!!!


መብትን ያለ አንጻራዊ ግዴታ ለመጠቀም ሲታሰብ
ህዝብ መረን ይሆናል ። ሃገርም ባንድ ጀምበር ይናዳል
። ያኔ መብት ወደ መባላት ይለወጣል ። የህግ ሰዎችም
every right has its own implied duty ይላሉ ።
መብትና ነጻነት ያለ ህግና ስርአት ሲከወን ነገሩ ሁሉ
ልጓም እንደሌለው ፈረስ ይሆንና ማሳረጊያው ገደል
መግባት ይሆናል ። አናርኪዝም (( ህግና ስርአት
አልባነት) ልቅ ከሆነ ነጻነት ማህጸን ውስጥ ነው
የሚፈለፈለው ።ስለሆነም ልጓማችንን ሳንጥል
ነጻነታችንን እናጣጥም ለማለት ፈልጌ ነው።

@Balmbaras
@wegoch
@wegoch
for Daily motivational quotes and messages
@words19
@words19
@words19
@words19
የአትሌቲክስ ፌደሬሽኑ እኔስ በምን ከእግር ኳስ ፌደሬሽኑ
አንሳለሁ በሚል እያሳፈረን ይገኛል፡፡
የሰሞኑ የነዮሚ ቀጀልቻ የመጠላለፍ አባዜ አሳፍሮን
ሳናበቃ የ16 ዓመት ወጣት ተብላ በዓለም አደባባይ የነሃስ
ሜዳሊያ አስገኘች የተባለችው አትሌት ግርማዊት ገ/
እግዚአብሔር የዕድሜ ጉዳይ " የሴት ልጅ እድሜና
የወንድ ልጅ ደመወዝ አይጠየቅም" ከሚለው ትዝብት
አዘል አባባል እጅግ ያለፈ ነው፡፡
ለማንኛውም የሴትዮዋን ፎቶ ሳይ ዕድሜሽ ስንት ነው
ስልሽ አሽላሾሽት ያልሽኝ ልጅ እንደው ባያሌው እንደምን
አለሽ? አሁንስ አላሻሻልሽውም? ነው ወይስ በዛው
እንጠናሽ ነው?
እኔ እምለው የሮጡት የ16 ዓመቷ ልጅ ሞግዚት ይሆኑ
ይሆን??? ተደናጊረኮ! ወይ መዓልቲ!
Big Shame!

@Balmbaras
@wegoch
@wegoch
ከኖሩ አይቀር !!!!


የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አመራሮችን ጉዳይ
በጀግንነት ሲፋለም የቆየው ጠበቃ ተማም አባ ቡልጎ ምን
ያህል ለሃቅ የቆመ ጠበቃ እንደነበር አረጋግጠናል ።
የአምባገነኖች ቁጣና ግልምጫ ሳይበግረው ስለ ፍትህና
ስለ ሙያው ክብር ጥቅሙንና እንጀራውን አሳልፎ የሰጠ
ጀግና ነው ። እነሆ የሱ ሙግት ሃቀኛ እንደነበር በጠቅላይ
ሚኒስትሩ አንደበት በዘወርዋራ መምገድም ቢሆን እነ
አቡበከርን ቤተ መንግስት ጠርተው ባነጋገሩ ጊዜ
ተረድተናል ። አምባገነኖች የነጠቁትን የጥብቅና ፈቃድ
ዛሬ እንደተመለሰለት በሰማን ጊዜ ለእውነት ኑሮ ማለፍ
በገንዘብ የማይገዙት ጸጋ በመሆኑ በመንፈስ ቅናት
ሰክረናል ።
የዛሬውን የጁማ በረካ ጠቅልለን ለተማም አባ ቡልጎ
ብንረዝቅ ማን ከልካይ አለን !!!! ማንም!!!!!!

@Balmbaras
@wegoch
@wegoch
ሞራል????


ኮሌጅ ስንመረቅ፤ የስራ ዝውውር ስናደርግ ፤ዘመድ ወዳጅ
፤ጒደኞች የጣት ቀለበት ሸልመውናል ። ስንበላ ፤ስንታጠብ
፤ ስንሄድ ስንመጣ ያን የጣት ቀለበት እያየን ለቀለበቱ
መደረግ ምክንያት የሆነውን ጉዳይ እናስታውሳለን ።
ለቃላችን መታሰራችንን ማረጋገጫ ምልክት ነው ። ዋናው
ጉዳይ ቀለበቱ ሳይሆን ቀለበቱ የተደረገበት ምክንያት
ለመረዳት መጣር ጤነኝነት ይጠይቃል ። ቀለበት
ለማድረግ ምክንያቶቹ የትየለሌ ናቸው ። አንዱን ጠርዝ
ይዞ መንደቅደቅ የሞራል ሹቀት እንዳይሆንብን ። አበቃ ።

@Balmbaras
@wegoch
@wegoch
ጊዜ ጠባቂ ቦንብ 16k
ዳንኤ ክብረት On Zeru
° ጊዜ ጠባቂ ቦንብ 😊
ዳንኤል ክብረት

፨ ጥዑም ወግ
፨ መጠን 0.9 MB

አዘጋጅ @Zerusoutlying
@wegoch @wegoch @wegoch
( ሁለቱ መንደሮች )

(ሚኪያስ ልየው) @Mykey21

አንድ ግዙፍ ከተማ ውስጥ አንድ ትልቅ እና አንድ ደግሞ ትንሽ የገጠር መንደሮች ይኖሩ ነበር። እነዚህ መንደሮች ምንም እንኳን የአንድ ከተማ መንደሮች ቢሆኑም ለአንድም ቀን ተነጋግረው አያውቁም ነበር።
የአንዱ መንደር ነዋሪ አንዱ ጋር አይደርስም በመካከላቸው ጥላቻ ፣ ክፋት ፣ ከፍተኛ መራራቅ ብቻ ሆነ። ትልቁ መንደር ትንሹን መንደር ትንሽ በትንሽነቱ መቀመጥ አለበት እኛ ሁሌም ትልቅ ነን በማለት ያንቋሽሿቸው ነበር።
እኛ በርካታ መሬቶች በርካታ ከብቶች አሉን እንሱ ግን የደረቁ ደረቆች ናቸው በማለት ይሳለቁባቸው ነበር።
ትልቁ መንደር ውስጥ ከፍተኛ የሰው ቁጥር በመኖሩ ምክንያት ህዝብ የለት ተለት ስራውን እንደ ልብ ለማከናወነት ተቸገረ ገበሬው የእርሻ መሬቴ ላይ አረስክ በማለት ከወዳጁ ጋር መጋጨት ጀመር።
ከብት የሚጠብቁ እረኞች ደግሞ የኔ በግ አንተ ጋር ገብትዋል ይሄ የኔ አደለም በሚል እና በተለያዩ የጎሳ ግጭቶች እርስ በርስ ተጋጩ።
ሸንጎውም ችግሩ ከአቅሙ በላይ ሲሆንበት የእርቁን ጉዳይ በይደር እያቆየው ችግሩም እየተባባሰ መጣ። በዚህም ምክንያት ከቀን ወደቀን የትልቁ መንደር ነዋሪዎች ስራቸውን በቅጡ መስራት አልቻሉም ነገሩ እየተባባሰ ከአቅማቸው በላይ ሲሆንና እርስ በርስ መተላለቅ ፤ ሊሰራ በሰላም ከቤቱ የወጣውም ወደቤቱ እየተመለሰ ስላልሆነ በመንደሪቱ ሁሉ ሁሉም ነዋሪ ስራ ማቆምን ምርጫቸው አደረጉ።
ለመስራት የሚፈልግ ካለ እኔ እቤት ተጎልቼ አንተ ማን ስለሆንክ ነው በሚል እና በሌሎችም በርካታ ምክንያቶች እርስ በርስ መገዳደል መጠፋፋት መጣ። በዚህም በመንደሪቱ ውስጥ ረሃብ ተከተሰ ገበሬው የዘራውን መሰብሰብ አልቻለም። ሰዉ አንድ በአንድ በረሃብ እና በእርስ በእርስ ግጭት መሞት ጀመረ።

ታድያ ይሄ ሁሉ ነገር ሲሆን የትንሹ መንደር ነዋሪዎች ምንም ሳይሆኑ በድሎትና በጥጋብ ይኖሩ ነበር።
የዚህ መንደር ነዋሪዎች በነዋሪ ብዛት ከዛኛው መንደር ቢለዩም በማህበረሰቡ ውስጥ ግን በርካታ አስተዋይና ብልህ ሰዎች ይኖሩ ነበር።
ታድያ እነዚህ ሰዎች ብልህዎች ስለነበሩ አንድ ቀን የሃገር ሽማግሌዎችን በመሰብሰብ ለህዝቡ የምንጠይቀው ነገር አለ በማለት ለሃገር ሽማግሌዎቹ ጥያቄ ያቀርባሉ።
ሽማግሌዎቹም ጥያቄውን እንዲቀጥሉ ይነግሯቸዋል።
ብልህዎቹም ሰዎች እንዲ በማለት ጥያቄያቸውን ያቀርባሉ።
እኛ መቼም ምንም እንኳን በመካከላችን ጥላቻና ክፋት ቢኖርም የሃገራችን ሰዎች ናቸው። የትልቁ መንደር ነዋሪዎች በረሃብ በችግር ብሎም በግጭት ሲሰቃዩ እያየን ዝም ብሎ የሚያስችል ልቦና የለንም ስለዚህም ልንደርስላቸው ፣ ልንታደጋቸው ይገባል በማለት ጥያቄያቸውን ለመንደሩ የሃገር ሽማግሌዎች ያቀርባሉ። ሽማግሌዎቹም ይሄ በእነሱ ስለማይወሰን የትንሽዋን መንደር ነዋሪዎች ጠይቀው እንደሚነግሯቸው የሃገር ሽማግሌዎቹ ጥያቄውን ላቀረቡላቸው ብልህ ሰዎች ይነግሯቸውና ይለያያሉ።
በሌላ ቀን ታድያ የሃገር ሽማግሌዎቹ የመንደሩን ነዋሪዎች በሙሉ ሰብስበው ብልህዎቹ ሰዎች ያቀረቡላቸውን ጥያቄ ይነግሯቸዋል
ከሁሉ የሚያስገርመው ነገር የመንደሩ ነዋሪዎች የሃገር ሽማግሌዎቹን ንግግር አላስጨረሷቸውም። ሁሉም ያለ አንድ ማቅማማት ተስማሙ የትንሿ መንደር ነዋሪዎች ያላቸውን እየገለበጡ ለትልቁ መንደር ነዋሪዎች ሰጧቸው የትልቁ መንደር ነዋሪዎችም ከጥቂቶቹም በስተቀር በረሃብ ከማለቅ ተረፉ።
በመጨረሻም ያለ ማንም ጥያቄ ሁለቱ መንደሮች ውስጥ የነበረውን ትንሽ እና ትልቅ የሚለው ን ስያሜ እርግፍ አድርገው በመተው አንድ ግዙፍ መንደር መስርተው እርቅን በማውረድ አብረው በፍቅር መኖር ጀመሩ።

ተደመሩ ማለት ነው እንግዲህ
ወዳጄ

@wegoch
@wegoch
@wegoch
የ አለም ዋንጫ ሩሲያ አዘጋጅታ
ዶ/ር አብይ በላው
🔶 At prime Minister Dr.ABIY for Nobel Prize.
ጉዞ ጀምረናል!!!!!!!


ውሾች እንዲህ ሲሉ ተናገሩ፣ " እስከ ዛሬ ድረስ " ውሾቹ
ይጮሃሉ፣ ግመሉ ግን ወደፊት ይሄዳል!!!!!!!" ያላችሁት
እውነት ነበር!!!!!!! ይኸው ስንት ዘመን ያናፋነው ያ ሁሉ
የጩኸት ክምር የግመሉን መስገር ሊያቋርጠው
አልቻለም። እንዲያውም አያ ግመል እያደር ወደ ጀመረው
ረጅም ጉዞ መገስገሱን ተያያዘው። እኛም የተጓዡን ወኔና
ጉዞ መስበር ባለመቻላችንና በማይበገረውና ፍንክች
በማይለው የግመል ፅናት ተማርከን የራሳችንን ጉዞ
ጀምረናል። ጉዞው አድካሚና ፈታኝ ቢሆንም ከባዶ ጩኸት
የማይሻል ጉዞ የለም ብለን ጉዞውን ተያይዘነዋል። ውሾች
በግመል ላይ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ማንባረቁን ትተን፣
የራሳችንን ጉዞ ጥርሳችንን ነክሰን ጀምረነዋል !!!!! Bon
voyage!!!!!!
ጩኸት ሆይ ደህና ሰንብት!!!!!!" እያሉ ከግመል ጎን ለጎን
ሲጓዙ የተመለከተው አያ ግመል ቁልቁል በግርምት
እያያቸው """ እነ ውሾ፣ ይኸ የጉዞ ፉከራችሁ በራሱ
ጩኸት ነው !!!!! አትጩኹ!!!! ብዙ የሚሄድና ብዙ
የሚጓዝ አይጮህም!!!!! ብሎ ከገረመማቸው በዃላ
በበረሃው ገላ ላይ በጥልቁ ዝምታው ተውጦ ይገማሸር
ጀመር።

ሸጋ ሸጊቱ ቀን!!!!...


@balmbaras
@wegoch
@wegoch
​​~~~ ከእውነት አንሽሽ ~~~
መድረክ መሪው ለቴዲ መጀመሪያ ባለህበት ወደ መስኮት ና ሲለው ወድያው በ2ቱ እጆቹ ሰላም ቢልም የቲቪ ካሜራው ግን ሌላ ቦታ ያሳያል፡፡ ደጋግሞ ግን ና ና ና ይላል፡፡

ይህ 1ሴራ እንዳለ ያሳያል ገና ወደ መድረክ ከመምጣቱ ምን እንደሚያደርግ ሳይጠይቁት ኢትዮጵያ የሚለው ክላሲካል ጀመሩበት፡፡ይህ 2ኛ ሴራ ነው መድረክ መሪው እንደማንኛው ሰው ቤቱ ሆኖም እንደሚያደርገው ቴዲም እንደዛ ለሰላም ታግሏል ብሎ ዝቅ ለማድረግ ሲጥር ነበር፡ይህ 3ኛ ሴራ ነው፡፡

ሆኖም ህዝቡ ሰላም ካለ በኀላ እጁና ፊቱ ወደ መሳሪያ ተጫዋቾች እያሳየ ለዛሬ አልተዘጋጀሁም ብሎ እውነታው ገለፀ፡፡ አቡጊዳ ባንድ አልነበሩማ፡፡ ሚስጢሩ ያልገባው ታዳሚም አንዴ ዝፈን ብሎ ሲጮህ የዝግጅቱ የሚስማማዉ ፊዮሪና -አስመራ እያለ ዘፈነ፡፡

ከጨረሰ በኀላ ግን መድረክ መሪው እንዲዘፍን እዳልተጋበዘ፡ከአሜሪካ እንደገባ እንደነበረ ሌላው እውነትም መናገር ነበረበት፡፡ቴዲ ግን ኢትዮጵያ ነው፡፡

ቪድዮው በደንብ ተከታተሉት፡፡

ትዝብት ከ
@ZeruHackGod
@wegoch
@wegoch
2024/09/30 23:28:54
Back to Top
HTML Embed Code: