Telegram Web Link
አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #3

የእኔ አሸናፊ ሊሆን አይችልም! እሱ እንዲህ ሊደፍረኝ ድፍረቱ ሊኖረው አይችልም። የእኔ አሸናፊ ቢሆን ደግሞስ ለሚስቱ ማናት ብሎ ነው የሚነግራት? ምንስ ቢላት ደግሞ የአደጋ ጊዜ ተጠሪዋ አድርጋ ትፅፈኛለች? መቼም እህቴ ናት አይላትም ዘንድሮ ወንዱ ብሶበታል እናቴ ናትስ ብሏት ቢሆን? ወይ አክስቴ ………. አይሆንም እንዲሁ ራሴን ሳስጨንቅ ነው። አሸናፊ የሚባል ሀበሻ አሸን አይደል?

ለማንም ምንም ሳልተነፍስ ልጄንና ባባን እነእማዬጋ ትቼ ቦታው ደረስኩ። ለእነእማዬ ስሙን ብጠራባቸው ቄስ ጠርተው ነው እንዳልሄድ የሚያስገዝቱኝ። ልቤ ሲደልቅ በለበስኩት ሹራብ ላይ ይታያል። ሰዎቹን ምን እንደምጠይቃቸው አላውቅም። ብቻ መልሳቸው የእኔ አሸናፊ አለመሆኑን እንዲያረጋግጥልኝ አምላኬን እለምናለሁ። አብረሃምና ግሩም ሰዎቹ ቤት ተቀምጠው እየጠበቁኝ ነበር። አከራዮቹ ስገባ አስቀድመው ተነግሯቸው ስለነበር እንደሚያውቀኝ ሰው ሰላም አሉኝ። ‘ፈስ ያለበት’ ሆኖ ያውቁኝ ይሆን እንዴ ? ብዬ አሰብኩ።

“ይኸው እኛ ቤት መኖር ከጀመሩ አስራ ሁለት ዓመታቸው ነው። መጥቶ የሚጠይቃቸው ቋሚ ጓደኛ እንኳን የላቸውም እንኳን ቤተሰብ። ሁለቱም ቤተሰቦቻቸውን አያውቋቸውም። ምንድነው ስሙ ጠፋብኝ ……. ሁሌ ያወሩት ነበር ….. የሆነ የህፃናት ማሳደጊያ ነው አብረው ያደጉት።”

የውስጥ እጄን አላበኝ። አሸናፊ ማሳደጊያ ነው ያደገው:: ከዚህ በላይ እስኪነግሩኝ መጠበቅ ራሴን ማሰቃየት መሰለኝ።

"የአባቱን ስም ያውቁታል? አሸናፊ ማነው የሚባለው?"

"ማን ነበር አንቺዬ ? አሸናፊ ......" ብለው ሊያስታውሱ ሲታገሉ አባወራው ቀለብ አድርገው "አሸናፊ ታዬ ነው። እርግጠኛ ነኝ።"አሉ።

አፌ ውስጥ ሞልቶ የነበረው ምራቅ ደረቀ። ፀጥ አልኩ። የሰማሁትን እርስ በርሱ ሳጋባው ጭንቅላቴ ውስጥ ወዲያ ማዶ እጅግ ርቆ የተቀበረ ስም ትዝ አለኝ ሄለን!!

"ታናሽ እህቴ በያት! አብረን ስላደግን ሳናወራ እንግባባለን። በዚህ ምድር ላይ እንደርሷ የሚያውቀኝ ሰው የለም ነበር ያለኝ" ያኔ።

ራሷ ናት! አረብ ሀገር ነበረች ያኔ! በጠና ታማ ወደሀገር ቤት ስትመለስ ክንፏ እንደተሰበረች ወፍ እየተጥመለመለ በእንባ ሲነግረኝ አባዬን "ቤት ልገዛ ብር አንሶኝ ነው" ብዬ ዋሽቼ ብር ተቀብዬ ሰጥቼዋለሁ። ለአብሮ አደግ እህቱ ማን ያውቃል እኔንም ታላቅ እህቴ በያት ብሎ ይሆናል የነገራት። ምናለ ብትነቃ እና በጠየቅኳት

"ታውቂዋለሽ?" አለ ግሩም የፈሰሰ ፊቴን አይቶ

"መሰለኝ። አሸናፊ ታዬ የሚባል ሰው ከረዥም ጊዜ በፊት አውቃለሁ። የሚስቱ መታወቂያ ላይ ስሜን የሚያፅፍ አይነት መተዋወቅ አይደለም እንጂ ...."

"ምናልባት ቁልፍ ካላችሁ እቤታቸው የፎቶ አልበም አይጠፋ ይሆናል። እዛው እናንተ በቆማችሁበት ማየት ብንችል?" አለ አብርሃም

"የታሰረበትን እስር ቤት ታውቁታላችሁ?" ጭንቅላቴ ውስጥ ያሰብኩት ጥያቄ አይደለም። እኔም ከአፌ ሲወጣ ነው የሰማሁት። ብቻ ዓይኔን እያየ እንዲነግረኝ የምፈልገው ብዙ ነገር ነበረ

"እዚህ እያለ እንጠይቀው ነበር። ከ6 ወር በፊት ወደ ሸዋሮቢት ተዛውሯል። ከዛ በኋላ ጠይቀነውም አናውቅ። እሷም እግር ስናበዛ ደስ አይላትም።" አሉ ሰውየው የሆነ ቅሬታ ባለው ድምፅ

"የታሰረበትን ምክንያት ያውቁታል?" አልኩኝ መልሱ ምን እንደሚሰራልኝ ሳላውቅ

"ምኑን አውቀነው። ሚስጥር ነው እናቴ! እንድናውቅ አልፈለጉም። ሁለቱም እንደልጆቻችን ነበሩ። እሱ ከታሰረ በኋላ እሷ ጭራሽ ሌላ ሰው ሆነች። አንድ ጊቢ ሆነን የማንገጣጠም ሆንን" አሉ ሴትየዋ

"እንግዲህ ካላችሁ ቤቱን ልክፈትላችኋ!" አሉ ሰውየው ወሬውን መቀየር የፈለጉ ይመስላሉ።

እግሬ መቆም የሚችል ሁሉ አልመስልሽ አለኝ። አሁንም እሱ ባልሆነ እላለሁ ደጋግሜ

"ይቅርታ እኔ እዚህ ልቆይ እናንተ አልበም ካገኛችሁ አምጡልኝ እቤት አልግባ?" አልኩኝ ልምምጥ በሚመስል። የቤቱ አባወራ እና አብርሃም ሲሄዱ ግሩም አጠገቤ መጥቶ

"ይቅርታ በጥሩ የምታስታውሺው ሰው አይደለም መሰለኝ" አለኝ

"በጭራሽ!" ለጥሩ የቀረበ ምናምኒት ትዝታ እንኳን የለኝም። ..... ያልገባኝ ስሜን እንኳን ለማውሳት የሚያስችል ድፍረት እንዴት እንደኖረው ነው። እፍ እፍ ብሎ ቀብሮኝ የሄደ ሰው ነው:: " አልኩት ልክ ዛሬ የሆነ ይመስል እያርገፈገፈኝ። ለማያውቀኝ ሰው የማይነገር ስሜት እያወራሁ እንደሆነ ሲገባኝ

"ይቅርታ የማይባል አልኩ!" አልኩት መልሼ

"በፍፁም የማይባል አላልሽም። ማውራት ከፈለግሽ ጥሩ ሰሚ ነኝ::" አለኝ ትከሻዬን በአይዞኝ ደለቅ ደለቅ እያደረገ

"ማውራትስ የሚሆንልኝ ሰው አይደለሁም።" አልኩት። እነአብርሃም አንድ ያረጀ የፎቶ አልበም ይዘው ብቅ አሉ። ልቤ እሱ መሆኑን እያወቀ። ፎቶው ላይ ያለው ሰው ሌላ ሰው ቢሆን እላለሁ። እጄን ለመዘርጋት አልታዘዝልሽ እንዳለኝ ገብቶት ነው መሰለኝ ግሩም አልበሙን ተቀበላቸው። እንደማራገፍ ካደረገው በኋላ

"ዝግጁ ነሽ?" አለኝ ለመክፈት እጁን አዘጋጅቶ በጭንቅላቴ አይደለሁምና ነውን እንዳምታተሁ እየገባኝ። ወደላይም ወደጎንም ጭንቅላቴን ወዘወዝኩት። ገለጠው። ....... ራሱ ነው።

ትቶኝ ሲሄድ በአካል ሊነግረኝ እንኳን ያላከበረኝ አሸናፊ። ..... በብጣሽ ወረቀት እንደተወኝ : አብረን የገነባነውን ዓለም የኔ ዓለም አይደለም ያለኝ ..... አሸናፊ ! ትቶኝ ለመሄዱ ምክንያት እኔ ልጅ መውለዱን እናዘግየው ማለቴ መሆኑን አሳምኖኝ በፀፀት ያነደደኝ አሸናፊ ...... በብጣሽ ወረቀት የሶስት ዓመት ፍቅራችንን ....... ሙሽራዬ ተብዬ ደስታ እና ወዙ ሳይደበዝዝ የዓመት ትዳራችንን ....... እንደ ብናኝ ብትንንንን ያደረገው አሸናፊ !! ከሀገር ወጥቻለሁ አትፈልጊኝ ነበር ያለኝ። ...... ፎቶዎቹ ላይ ደስተኛ ይመስላሉ። ሰው እንዴት እንዲህ ክፉ ይሆናል? ሰው እንዴት እንዲህ ያለ ቅጥፈት ይቀጥፋል? እኔን ባይወደኝ ለእኔ ባያስብ ሰው የዘራውን እንደሚያጭድ እንዴት ነገውን አልፈራም? ትቶኝ መሄዱ ሳያንሰው ለትዳራችን መፍረስ ምክንያቷ እኔ መሆኔን አምኜ እንድተክን እንዴት ይፈርድብኛል?

"ሸዋሮቢት እሄዳለሁ!" አልኩኝ ሳላስበው። ማንም ምንም ሳይል ደቂቃ ከቆዩ በኃላ

"ዛሬ መሽቷል። ነገም ሰንበት ነው። ሰኞ በጠዋት እኔ አደርስሻለሁ ከፈለግሽ። እስከእዛ ድረስ ደግሞ ምን እንደሚፈጠር አይታወቅም። እናትየው ትነቃም ይሆናል።" አለኝ አብርሃም። እየሆነ ያለው ነገር ምን እንደሆነ ባያውቅም ሲኦል ነክ ነገር መሆኑ ሳይገለጥለት አልቀረም። ህመሜ እንደአዲስ ልቤን ሲሰቅዘኝ ታወቀኝ ልክ እንደያኔው ትቶኝ እንደሄደ ጊዜ ....... መንገር አፍሬ ብቻዬን ለወራት እንደቆሰልኩት ለማንም አገኘሁት ሳልል መታመምን በወደድኩ ......

"እቤትሽ እናድርስሽ?" አለ ግሩም መደንዘዜ ገብቶት። ያላለቀውን አልበም እየገጠመው። የእነእማዬ ቤት አቅጣጫ በየት መሆኑን ከማመልከት ውጪ ቃል ሳልተነፍስ እነእማዬጋ ደረስኩ። ባባ ከእንቅልፉ ነቅቶ ከጠዋቱ በተሻለ ነቃ ብሎ ከወንድሜ ልጆችጋ እየተጫወተ ነበር።
መጥፎ ሴት አይደለሁም። ግን ደግሞ መልዓክም አይደለሁም። የአሸናፊን ልጅ ልንከባከብ? ራሴን ፈራሁት። እኔ እኮ በእርሱ ምክንያት ማንንም የማላምን ደንባራ ሴት ሆኛለሁ። ሙሽራዋ ከአንድ ዓመት በላይ አብሯት ለመዝለቅ ያልፈለጋት ምንም የሆነች ዓይነት ሴት እንደሆንኩ እየተሰማኝ ታምሜያለሁ። እኔኮ በእርሱ ምክንያት ፍቅርንም ሰው ማመንንም ሰው መቅረብንም አጠገቤ እንዳይደርሱ አርቄ ቀብሬያቸዋለሁ። የእርሱን ልጅ ላሳድግ? እናቱ አይበለውና ብትሞት እናቱ እሆናለሁ? ራሴን ፈራሁት ......

"እማዬስ?" አለኝ ባባ ሳሎን ገብቼ የደነዘዘ ሰውነቴን ሶፋው ላይ እንደጣልኩት። 'እናትህማ እኔን ፍም ላይ ማግዳኝ ሆስፒታል ተኝታለች' ብለው ደስ ባለኝ።

"ምነው እማ? ምን ሆንሽ?" አለችኝ ልጄ ተከትላ ..... እንደአዲስ ክው ብዬ ደነገጥኩ .... ምንድነው የምላት???

ምንም ከማለቴ በፊት ባባ

"እማዬጋ ውሰጂኝ!" ብሎ እሪታውን አቀለጠው።

ይቀጥላል። ...........

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #4

ልነግረው ነበር እኮ ደስታ አቅሌን አስቶኝ እቤት የደረስኩት። "አርግዣለሁ እኮ" ልለው።

"ቤት ፣መኪና ፣ የተሻለ ስራ ...... ምናባቱ! አንተን ሙሉ የሚያደርግህ ልጅ መውለድ ከሆነ ሁሉንም ትቼዋለሁ።"ልለው ነበር እቤት ስደርስ

"የእኔ እቅድ አንተን ካስከፋብኝ ባላቅድስ ያንተን ፍላጎት ልኑርልህ" ልለው ነበር። ከመፈንጠዙ የተነሳ ምድር ትጠበዋለች ብዬ እያሰብኩ ከሀኪም ቤት እንደህፃን ዝግዛግ እየረገጥኩ መደነስ እየቃጣኝ እቤት የደረስኩት። እሱ አልነበረም! ብጣሽ ወረቀት አስቀምጦልኝ ሄዷል።

እስከዛች ቀን ድረስ የዓለምን ክፋት በመልካምነት መብለጥ እችላለሁ ብዬ የማምን ጅል ነበርኩ። ከሰዎች ውስጥ ጥሩነታቸውን ለማድመቅ የምጋጋጥ .... ለክፋታቸው ምክንያት እየፈለግኩ ይቅር ማለት የምችል ጀለገግ ነበርኩ። የማንም ክፋት እንዳይሰብረኝ ሆኜ በእድሜዬ በስያለሁ ብዬ የማምን ገልቱ !!! .... ክፋት በምሳሳለት ሰው ተመስሎ ሲመጣ ተሰብስቤ እንዳልገጣጠም ሆኜ ተሰባበርኩ እንጂ.... ለሰዓታት ቁጭ ብዬ እየደጋገምኩ ወረቀቱን አነበብኩት።

"ፌቪዬ አንቺ ቤተሰብ መመስረት እንዳያጓጓሽ በሚወዱሽ ቤተሰቦች ተከበሽ ነው ያደግሽው። መጉደልን አታውቂውም! እኔ የሌለኝን አባት ለልጄ መሆን እፈልጋለሁ። በህይወቴ የተመኘሁት ብቸኛ ነገር የራሴን ቤተሰብ መመስረት እንጂ ቤት መገንባት ወይም ሀብት ማጠራቀም አልነበረም። እንድትረጂኝ አልጠብቅም! አንቺ የተመቻቸ ህይወትም ቤተሰብም ኖሮሽ ስላደግሽ የተመቻቸ ህይወት ሳይኖረን መውለድ አትፈልጊም። ላስጨንቅሽ አልፈልግም! ደስተኛ እንደሆንኩ እያስመሰልኩ አብሬሽ መሆኑንም አልፈልግም። በራሴ ምክንያት በትዳራችን ደስተኛ አይደለሁምና ከሀገር ለመውጣት ወስኜ ፕሮሰሱን ጨርሻለሁ። እንዳትፈልጊኝ። ደስተኛ ሁኚ!

በቃ! በዝህች ሙንጭርጭር ነው 'ደስተኛ ሁኚ' ብሎ ተሳልቆ ደስታዬን ይዞት እብስ ያለው። እያንዳንዱን ዓረፍተነገር እየደጋገምኩ አመነዥካለሁ። ስለልጅ ያወራነውኮ ሁለቴ ነበር። 'ለልጃችን የተስተካከለ ህይወት አበጅተንለት ብናመጣው አይሻልም?' ነበር ያልኩትኮ።

ከመረዳት አልፌ እነማዬጋ ስንሄድ በዝምታ ስለሚያሳልፍ ይከፋው ይሆናል ፣ጉድለቱን ያስታውሰው ይሆናል ብዬ እነማዬን ላለማየት ሰበብ የምደረድር ሰው ነበርኩኮ። ትቶኝ ቢሄድ እንኳን ቢያንስ በአካል ቢነግረኝ ምን ነበረበት? ከእቅዴና ከፍቅራችን የቱ እንደሚበልጥብኝ ለመረዳት እድሉን እንዴት አይሰጠኝም?? ሰዓታት? ሰዓታት ታግሶኝ ቢሆን "ልጃችንን በሆዴ ይዣለሁ!" ልለው አልነበር?

ሁሉም ክስተት እንደአዲስ ውስጤ እየተገላበጠ ያምሰኝ ገባ! የወረቀቱ ሻካራነት እንኳን ጣቶቼ ላይ ይሰማኛል። በእንባዬ የተኮማተሩት ፊደላት .... ደብዳቤው የነበረበት ጠረጴዛ ..... እኔ የተቀመጥኩበት ረዥም ወንበር ...... ቀን ላይ ተሰርቶ የበላነው የነበረው ሳሎኑን ያፈነው የቀይወጥ ሽታ ....... ልክ እንደአሁን ይንጠኝ ጀመር። ረዥም ሳግ የቀላቀለው ትንፋሽ ተፈስኩ።

ወደ ሸዋሮቢት እየሄድን ነው። ከግሩም እና ከአባቱ ጋር ። ሳገኘው ምን እንደሚሰማኝ ማሰብ አልፈልግም። ትቶኝ የሄደበት ምክንያት ልጅ ያለመሆኑን ብቻ ነግሮኝ ራሴን ይቅር እንድለው ነው ጥድፊያዬ። ዓመታቱን እጎነጉናለሁ። ከመታሰሩ በፊት 10 ዓመት አብሯት ኖሯል። ልጅ የወለዱት ምናልባት ከ8 ዓመት በኋላ ነው። ፎቷቸው ያስታውቃል ደስተኛ ነበረ። ከሀገር ወጥቻለሁ ያለኝም ጭራሽ ውሸቱን ይሆናል አይደል? እንዳልወደደኝ ማወቅ ወይም ምክንያቱ ልጅ እንዳልነበር ማወቅ የቱ የበለጠ እንደሚሳምም ማመዛዘን አልቻልኩም።

ለማንም ምንም አልተናገርኩም። ሰኞ እስኪደርስ እንዳልፈነዳ ስፈራ ነበር ሰኞ የነጋልኝ። የዛን ቀን እነእማዬጋ ካደርኩ ጥያቄያቸውን ስለማልችለው ባባንና ልጄን ይዤ ወደቤቴ ተመለስኩ። ልጄ በእኔ ፈንታ አባብላ ዝም ባታስብልልኝ በነበርኩበት ሁኔታ ባባን ማረጋጋት ፈታኝ ነበር። እሁድ ቀን ወደሆስፒታል የሄድኩት ጥያቄዎቼን እንድትመልስልኝ ይሁን ወይም በጥሩነት እንድትድን ፈልጌ ይሁን ሳላውቅ ነው። እሷ እቴ! የትናንት ህመሜን ፣ ስድስት ማትሪክ የሚወጣቸው ዳሽ ሙላ ጥያቄዎች እና ባባን አስታቅፋኝ ....... ለሽሽሽ ብላለች።

ልጄ ለወትሮ ክፍሏ ከገባች ብጠራት የማትሰማኝ ከስር ከስሬ እያለች

"እማ ምንድነው የሆንሽው? እንደዚህኮ ሆነሽ አታውቂም ምንድነው?" ትለኛለች።

"ምንም አልሆንኩም!" እላታለሁ እየደጋገምኩ። ምልስ ብላ ያበረታችኝ መስሏት

"ባባ አሳስቦሽ ነው? አንቺ እንኳን ለአንድ ልጅ ለአንድ መዋዕለ ህፃናት ልጆችኮ እናት መሆን የምትችዪ ምርጥዬ እናት ነሽ!" ስትለኝ ሲንቀለቀል ዓይኔን የሞላውን እንባዬን እንዳታየው ዘልዬ ወደመታጠቢያ ቤት ገባሁ።

እንዴት ነው አይደለምኮ አባትሽን አገኘሁት!! ባባ ወንድምሽ ነውስ የምላት? ለእኔ ለትልቋ ሴት መሸከም ከብዶኝ እያንገታገተኝ ያለሁትን ጉድ በምን ለውሼ ብነግራት ነው ህመሟን የሚያለዝበው?

"አባቴን ማወቅ እፈልጋለሁ!፣ አባቴ ማነው? ለምንድነው የማይፈልገኝ?" ብላ ስትሰፋኝ

"አባትሽ አንቺን ማርገዜን ሳያውቅ ነው ተጣልተን ትቶኝ የሄደው። ቆይተን እንውለድ ስላልኩት ነው የተጣላኝ ..... አየሽ በተዘዋዋሪ አንቺን ስላልሰጠሁት ነው የተጣላኝ እንጂማ ልጁን ቢያውቅሽ ኖሮ ይኖርልሽ ነበር። ምርጥ አባት ይሆንሽ ነበር። ላልወለዳት ልጁ በፍቅር ያበደ ነበር" ብዬ ከነገርኳት ዓመት እንኳን አልሆነምኮ። ለራሴ እንኳን በቅጡ ያልገባኝን ትርምስምስ ምን ብዬ ልንገራት?

"ደህና ነሽ? የምትፈልጊው ነገር አለ?" አለኝ አብርሃም። ለካ መኪናው ቆሟል። ስሙን ለማወቅ ግድ ያልሰጠኝ የሆነኛው ከተማ ደርሰናል።

"አይ ደህና ነኝ። ምንም አልፈልግም" አልኩኝ።

የምፈልገው ግን ከቅዳሜ በፊት የነበሩት ቀኖቼ ላይ መመለስ ነበር።
ስራ ቦታ ...... የአንድ ባንክ ቅርንጫፍ ሀላፊ የሆነች ፣ ባል የሌላት ፣ 'ይህቺ ሴት ቆማ መቅረቷ ነው' እያሉ ሲያዝኑልኝ ..... ገሚሱም ሲመክረኝ ገሚሱም 'ችግር ቢኖርባት ነው' እያለ ሲያማኝ ከስራዬ ውጪ ከማንም በጥብቅ ሳልጋመድ የምትውለዋን ያቺን ሴት .......

እቤት ስመለስ .......ከልጄ ጋር የቤት ስራዋን ስንሰራ፣ ስለጓደኞቿ ስታወራኝ ፣ በሳምንት ሁለት ቀን ፊልም አብረን ስናይ፣ በሳምንት ሁለት ቀን ተራ በተራ መፅሃፍ ስናነብ፣ ክፍሏ ገብታ ስትቀርብኝ ለመጥራት ሰብብ ስፈልግ፣ የቀረውን ጊዜ ጓዳ እኔ ምግብ ሳበስል እየመጣች የእድሜዋን ጥያቄ እየጠየቀች ልቤን ድክም ስታደርገኝ የምታሳልፈዋን ያቺን ሴት.....

ቅዳሜና እሁድን ...... ከልጄ ጋር ቤተሰቦቼጋ ሄደን በቀን ለማይቆጠር ጊዜ ቡና ስናፈላ፣ ጉንጫችን እስኪዝል የባጥ የቆጡን ስናወራ፣ የእማዬን ጣፋጭ ምግብ ቁንጣን እስኪይዘን ስንበላ ፣ አባዬ በልጅ ልጆቹ ሩጫና ጩኸት ሲያማርር እየሳቅን የምታሳልፈዋን ሴት ......

ሁሉ ባይኖረኝም ባለኝ የማመሰግን። ህመሜን ባልረሳውም ከህመሜ ጋር እንዴት ተከባብረን ተላምደን መኖር እንዳለን የተማርኩኝ ያቺን ሴት......

አርብ ከመተኛቴ በፊት የነበርኳትን ሴት መሆን ነው የምፈልግ የነበረው። እንደብዙ ሰውኮ ብዙ አልጠየቅኩም አይደል እንዴ?

"ደርሰናል። ግን እርግጠኛ ነሽ ልታገኚው ትፈልጊያለሽ?" ሲለኝ ነው አሁንም መኪናው መቆሙን ያስተዋልኩት። ከኋላ ብቻዬን ነበር የተቀመጥኩት።
"እ? አዎ አይ እርግጠኛ ነኝ! ችግር የለውም!" አልኩኝ ደረቴን በርቅሳ ልትወጣ ይመስል የምትደልቅ ልቤን እንዳያዩብኝ ልብሴን እየነካካሁ። ምንም ባልናገርም ፊቱን ማየት እንደሞት እንዳስፈራኝ ከሁኔታዬ ገብቷቸዋል።

አባትየው ለአንደኛው ፖሊስ ሲያስረዳ ሲጨቃጨቁ አጠገባቸው ሆኜ እንደእሩቅ ድምፅ ነው የሚሰማኝ። የማስበው ሳየው ምን እንደምለው ነው! ሊመልስልኝ የሚችለውን መልስ መላ እመታለሁ። ልጅ እኔጋኮ ልጅ አለህ ስለው ይደነግጥ ይሆን? ይፀፀት ይሆን? እና? ቢለኝስ?

የሆነ ስም ጠርቶ እገሌ ይጠራልኝ ብሎ አባትየው ሲቀውጠው ፖሊሶቹ አልፈቅድ ብለው እንደሆነ ገባኝ። ከመምጣታችን በፊት አጣርቶ ነው ማለት ነው? ፍርሃቴ ከማየሉ የተነሳ እዚህ ድረስ ከመጣሁ በኋላ እንቢ ብለው ሳላገኘው ብመለስ ብዬ አስቤ ለቅፅበት ደስ እንደሚለኝ ተሰማኝ። ትልቁን ፍርሃቴን ተጋፍጬ ከእውነት ከመጋፈጥ መሸሽ!! የሰው ልጅ በብዙ እንደዛ አይደለ? ፍርሃቱን በመሸሽ ውስጥ ያለውን መንገድ ያውቀዋል። ቢወደውም ቢጠላውም ስለለመደው ይኖራል። ፍርሃቱን ሲጋፈጥ ከተራራው ጀርባ ያለውን ግን አያውቀውም። ሳያውቀው ይፈራዋል። አልለመደውማ! ስለዚህ ፍርሃቱን እሹሩሩ እያለ የለመደውን የተለመደ ህይወት ይኖራል።

የተባለው ሰው ተጠርቶ ተጨባብጠው። ሁኔታውን በእርጋታ ከተረዳዱ በኋላ ተስማሙ። ሰውየው አሸናፊ እንዲጠራ ትእዛዝ ሲሰጥ መሮጥ ሁሉ አማረኝ። ብቻ እነግሩም ስለተንቀሳቀሱ እግሬን ወደፊት እየዘረጋሁ ዘለቅኩ። ተጠርቶ ሲመጣ የሚቆምበት ቦታ የሆነ ፖሊስ ነገር እየመራ ወስዶ ሲያደርሰኝ እነ ግሩም ወደኋላ ቀሩ

ከጀርባው ለእኔ ከማይታየኝ ከሆነ ሰው ጋር እያወራ እየሳቀ ብቅ አለ። ሲያየኝ እንደመቆም አለ። ፊቱ ግን የገረመው አይመስልም ነበር። የሆነ ቀን እንደምመጣ የሚያውቅ ዓይነት መረጋጋት ነው ያለው። በረዥሙ ቢተነፍስ ትንፋሹ በሚሞቀኝ ዓይነት ርቀት ላይ ደርሶ ሲቆም ለምን ላገኘሁ እንደመጣሁ ፣ ምን ልጠይቀው እንደነበር ሀሳቤ ሁሉ ጭንቅላቴ ውስጥ ተደነባበረ። እልህ ፣እንባ ፣ላለመሸነፍ ትንቅንቅ ..... አፈነኝ። ወዲያው ደግሞ በራሴ ተበሳጨሁ። እንዴት ያለሁ ልፍስፍስ ነኝ ከዚህ ሁሉ ዓመታት በኋላ እንኳን የበደለኝን ሰው ሳየው ጎብዞ መታየት የሚከብደኝ? እኔ እስካወራ ድረስ ከንፈሩን አላላቀቀም። አይኖቹን እንኳን አልሰበራቸውም። ሳይነቅል ከማየቱ የተነሳ በአይኑ እየቦረቦረኝ ያለ ዓይነት ስሜት ሁላ ነው የተሰማኝ። ለደቂቃ ትንፋሼን ውጬ አይኖቼን አይኖቹ ውስጥ ዘፈዘፍኳቸው። አፌን ለቆ ሲወጣ የሰማሁት ዓረፍተ ነገር

"አብረን በነበርንበት ጊዜ ወደኸኝ ታውቅ ነበር?" የሚል ነው።

ይቀጥላል እንግዲህ......

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
አላየሁትም ነበር ።ጠራኝ። ወደ ተጠራሁበት ዞሬ ተመለከትኩ ዘመናዊ መኪና ውስጥ ያለ
ሰው ነው ። ኮስተር ብዬ ስመለከት አበጀ ነው ። በፈገግታ ወደ መኪናው ሄድኩ ።በቶሎ
ከመኪናው ወረደ ተቃቅፈን ሰላምታ ተለዋወጥን ተመችቶታል ።
አይኔ ላይ ተመችቶታል እያልኩ እንዳየሁት ያስታውቃል ። አይኑ ላይ አልተመቸክም አይነት
እያየኝ እንዳለ ገብቶኛል ።
"ምነው በእግርህ መኪና እስካሁን አልገዛህም" አለኝ አዎ ባክህ አልገዛሁም አልኩት ።
ቀጠለ ወፍራም ሳቅ እየሳቀ "ደሞ እግረኛነት ቦርጭህን ከመገበድ ኣላዳነውም"
ሁለታችንም ሳቅን ።
ቀጠለ "አረ ዱብ ዱብ እማ በል አለኝ" ኑሮ ዱብ ዱብ እያደረገኝ ደሞ ሌላ ዱብ ዱብ
ስለው ወፍራም ሳቅ ሳቀ ።
በራሴ ቀልድ እኔም በስሱ ሳቅኩኝ. ።
"አሁንም አዛው የድሮ ቦታ መብራት ሃይል ነው
ነው የምትሰራው"?? አዎ እዛው ነኝ ።
"እና በተረፈ?"
አለው
"አላገባህም?"
አዎ አላገባሁም አልኩት ትከሻዬን ቸብ አድርጎ "አግባ እንጂ በዚህ አያያዝህ የኔ ልጅ ቤቢ
ይቀድምሀል"። ሌላ ወፍራም ሳቅ
በዝባዝንኬ ወሬው ከሱ ጋ ማሽካካት ደከመኝ
በቃ ቻው አልኩት ። "ወዴት ነህ "አለኝ ወደ ቢሮ አልኩት ልሸኝህ አለኝ አይ የምጠብቀው
ሰው አለ እዚህ አካባቢ አልኩት
ቤት አንደገዛ፤ ለቤተሰቦች ምን ምን
እንዳደረገ፤ እንዴት እንደተሳካለት ለጨዋታው ማዋዣ የእኔን እያጣቀሰ እንዲያፌዝበት
ለምን እድል እሰጠዋለሁ ?!
ደመቅ አድርጎ "ቻው አትጥፋ እንደዋወል አለኝ" ወፍራም ፈገግታ ታጅቦ ። ቀዝቀዝ ባለ ፊት
ፈገግታ አልባ ስንብት ሰጥቼው ተሰነባበትን።
ቻው አልኩት ።
ቅር አለኝ። ሰው በዚህ መጠን ለምን ይታበያል ?
ያለን ከሚያስፈልገን አንፃር አይደል ብዙ እና ትንሽ የሚሆነው ።
የሰው ስኬት መለኪያው ገንዘብ ብቻ ነው?? የሰው ስኬት ከአምላኩ ጋ ባለው ታማኝነት
አይለካም ??
የሰው ሰኬት ከቤተሰቡ ጋ ባለው ሰላም አይለካም ? የሰው ስኬት ከራሱ እቅድ እና ፍላጎት
አንፃር አይለካም?? የሰው ስኬት መመዘኛው ንዋይ ብቻ ነው ??
ይሁን እሺ !!!
ሰው በየአጋጣሚው እና ባገኘው አጋጣሚ
እኔ ... እኔ ...እኔ ...እኔ ማለት አለበት ??
ይበል እሺ !!
ስኬቴ ብሎ ሲቀባጥር ለማን እንደሚያወራ እና የሚያወራው ሰው በምን ሁኔታ ላይ
እንዳለ መረዳት የለበትም ?
ሃጠራው !!
ከሴተኛ አዳሪነት ለመውጣት ታግላ የወጣች እንስት አና በድንግልና ለማግባት አልማ
አቅዳ የተሳካላት እንስት ደስታቸው ለራሳቸው እኮ ግዙፍ ነው።
የሰው ስኬት ሁሉ ለባለቤቱ ትልቅ ነው። ባንተ ስኬት እቅድ የሰው መንገድ አታንኳስስ!!
ማስታወሻ ፦ ፩
ያንተ ማግኘት ላንተ ነው
በአንተ ማግኘት ከቻልክ ማገዝ ካልቻልክ ኑራቸውን እንዲያማርሩ ምክንያት አትሁን ።
ማስታወሻ፦ ፪
ባገኘህው አጋጣሚ የተሳካልህን ጉዳይ እየዘበዘብክ ሰው ትግል ላይ ማላገጥ ጠላት
ማፍራት ነው።

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Adhanom Mitiku
አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #5

አፌን ለቆ ሲወጣ የሰማሁት ዓረፍተ ነገር
"አብረን በነበርንበት ጊዜ ወደኸኝ ታውቅ ነበር?" የሚል ነው። ጥያቄዬ አፌን ለቆ ወጥቶ ሳያልቅ በፊት

"ባባ ደህና ነው?" የሚለው የእርሱ ጥያቄ ዓለሜን አዞረብኝ። ለመጠየቅ መልሱን ፈርቶ እያማጠ እንደያዘው ያስታውቅ ነበር። እኔ ሳየው የ15 ዓመት ቁስሌን ነው የጠዘጠዘኝ። ለካስ የእኔ መከሰት ለእሱ የቤተሰቡ ህልውና አደጋ ላይ መውደቅ ማመላከቻ መርዶ ነው። ራስ ወዳድ እንደሆንኩ ተሰማኝ።

"እሱ ደህና ነው። እኔጋ ነው!" አልኩት። በረዥሙ ከሆዱ እስከ ጭንቅላቱ የናጠው የመገላገል ትንፋሽ ተነፈሰ።

"እሷስ?" አለኝና መልሶ "ተይው አትንገሪኝ!" አለኝ። ለሆነ ደቂቃ ስረግመው የኖርኩት አሸናፊ መሆኑን ረሳሁት። የምመልስለትም የምጠይቀውም ተወነባበደብኝ።

"ሞታ ነው አይደል? በህይወት እያለች ላንቺ እንዲደወል አታደርግም።" አጠያየቁ እንድመልስለት የፈለገ አይደለም።

"በህይወት አለች!" አልኩት:: ሲቃ አይሉት ለቅሶ አይሉት ያለየለት ድምፅ አሰምቶ በዛ ቁመቱ ግንድስ ብሎ መሬቱ ላይ ዘፍ ብሎ ተቀመጠ። ላለማልቀስ እየታገለ ግን እንባ ሳይወጣው እያለቀሰ እንደሆነ ያስታውቅበታል። ዝም ብሎ ከማየት ውጪ ማድረግ የቻልኩት ነገር የለም። ድንገት የሆነ ነገር ትዝ እንዳለው ነገር በጥያቄ እያየኝ ከተቀመጠበት ተስፈንጥሮ ተነስቶ

"ቆይ ቆይ ታዲያ ህሉ በህይወት ካለች ባባ አንቺጋ ምን ይሰራል? እ ...እ ... በፍፁም! ህሉ ትንፋሿ እያለ ልጇን አሳልፋ አትሰጥም!" ተቁነጠነጠ። የተፈጠረውን ነገር ስነግረው ጭንቅላቱን በእጆቹ ይዞ ጀርባውን ሰጥቶኝ ቆመ። ምልስ ብሎ

"አንቺ ውሸት አትችዪበትም። እውነቱን ንገሪኝ! ትድናለች?" ሲለኝ የእኔ እንባ ምን ቤት ነው ከእርሱ ቀድሞ የተዘረገፈው?

"አላውቅም!! ሀምሳ ሀምሳ ነው የመንቃት እድሏ ነው ያሉት ሀኪሞቹ።"

እዚህ ደቂቃ ላይ ስለራሴ ምንም እንደማልጠይቀው አወቅኩ። ጥያቄዎቼን መልሼ አዝያቸው ልሄድ ወሰንኩ። ቤተሰብ ለእሱ ዓለሙ ነው። ዓለሙ ፈርሷል። የእኔን ህመም እርሱ ካለበት ሁኔታ ጋር ማነፃፀር አልፈለግኩም። ዝም አልኩ።

"ከሞተች። (ሲቃ እያነቀው ቃሉን ሲለው እንደዘገነነው ያስታውቃል።) ለልጄ እናቱ እንደሞተች አትንገሪው። ሲቆይ ይረሳታል። "

"እንዴ?" ብዬ ጮህኩኝ ሳላስበው።

"ልግባ?" አለኝ ለመሄድ ፊቱን እያዞረ። ግራ ገባኝ። እንዲህ ሁሉ ነገር እጄ ላይ ጥሎ እንዴት ነው የሚገባው? ባባን ምን ላድርገው? እሺ ልጄንስ ምን ልበላት? እሺ ሚስቱን የገጨበትን ሰው በህግ ልጠይቀው በሽማግሌ? እሺ ሚስቱንስ ምን ላድርጋት? ዥውውውው አለብኝ። ይሄን ሁሉ መከራ እላዬ ላይ ጥሎማ አይገባም! ግን የቱን አስቀድሜ የቱን እንደማስከትል እንጃ!

"አዎ እያንዳንዱን ቀን ወድጄሽ ነበር።" አለኝ ለመሄድ እየተንቀሳቀሰ። ማለት የምፈልግ የነበረው ብዙ ነበር። ለምን ብዬ የምጠይቃቸው እልፍ ጥያቄዎች ነበሩ። ፊቱ ላይ ካለው ስቃይ ጋር ሲነፃፀር የእኔ ጥያቄ ገለባ ሆነብኝ። መርዶ ይሁን የምስራች ሳይገባኝ

"እርጉዝ ነበርኩ። ያኔ ..... " ብዬ 'ትተኸኝ ስትሄድ' ልል ነበር። የምጎዳው ነገር መሰለኝና ሌላ የሚተካው ቃል ስፈልግ....

"እና? " አለኝ። ሊሄድ ከነበረበት ተመልሶ በጉጉት

"15 ዓመቷን ባለፈው ሰኔ 6 አከበረች::" አልኩት። ሳቅና ለቅሶ ፊቱ ላይ ተሳከረበት። ወደፊት ወደኋላ ከዛ ወደጎን ተንቆራጠጠ። እጁን አንዴ ጭንቅላቱ ላይ አንዴ ወደኋላ አንዴ ጉንጩ ላይ ያቅበዘብዘዋል።

"ታውቂያለሽ ....." ብሎ ዝም አለ

"አውቃለሁ። ብታውቅ ልጅህን ያለአባት እንድታድግ አታደርጋትም። ልነግርህ ነበር። ልነግርህ ስመጣ አንተ ሄደሃል።" አልኩት። ልክ እንደቅድሙ መሬቱ ላይ ዘጭ ብሎ ተቀመጠ። ግን እንደቅድሙ ለቅሶ ብቻ አይደለም። ፈገግ እያለ ነው የሚያለቅሰው። ቅስስ ብሎ ከመሬቱ ላይ ተነሳ መደሰት ይሁን ማዘን ያለበት ግራ የገባው ይመስላል።

"አባቷ ?...." ብሎ እንዴት መጠየቅ እንዳለበት ግራ ሲገባው

"ታውቃለች። እውነቱን ነው የነገርኳት። የአሁኑን እንዴት እንደምነግራት ነው ግራ የገባኝ።"

ሰዓታችን ማለቁን ደጋግመው እየገገሩን ነው። እንደማሰብ ካለ በኋላ ...... እስከአሁን የሆነውን መሆን እንዳልሆነ ...... ክፉ ዜና እንዳልሰማ ...... ምንም ዝንፍ ያለ ነገር እንዳልተፈጠረ ..... ተረጋግቶ ከፊቱ ላይ እንባውን ካበሰ በኋላ በሰከነ ዝግተኛ ድምፅ

"ጥያቄዎችሽን ሁሉ ብመልስልሽ : የሆነውን ሁሉ አንድ በአንድ ባስረዳሽ ደስ ይለኛል። ምናልባት እድሉን ካገኘሁ የሆነ ቀን ያደረግኩትን ለምን እንዳደረግኩ እነግርሻለሁ። ያ ማለት አንቺ ያ ይገባሻል ማለት አይደለም። እመኚኝ አንቺን ከጎዳሁሽ በላይ ባሰብኩሽ ቁጥር እቀጣበታለሁ። ይገባኛል ብዬም አይደለም የምጠይቅሽ ግን በዓመታት ብዛት ሊከፋ የማይችል ደግ ልብ እንዳለሽ አውቃለሁ። ልጄ ቤተሰብ እንዲኖረው እፈልጋለሁ። ካንቺ የተሻለ ብዙ ፍቅር ያለው ሰው አላውቅም!! እኔ የኖርኩትን ህይወት እንዲኖር አልፈልግም። የተፈረደብኝ ቀን ለሄሉ ድንገት የማትወጣው ነገር ውስጥ ከገባች ላንቺ እንድትደውልልሽ ነገርኳት። ታውቂያለሽ ሁለታችንም ቤተሰብ የለንም። 'በህይወት እያለሁ አላደርገውም ድንገት እኔ የሆነ ነገር ከሆንኩ ግን ልጄ በፍቅር የሚያድግበት ቤተሰብ ያስፈልገዋል።' አለችኝ:: ለዛ ነው መታወቂያዋ ላይ ያንቺ ስም የኖረው። "

ከዚህ በላይ መቆየት አይችልም ነበር። "እሺ አደጋ ያደረሰባትን ሰው ......" ብዬ ሳልጨርስ

"ምን እንደምታደርጊ አንቺ ታውቂያለሽ!! ካንቺ የተሻለ ምክንያታዊ ሆኖ የሚወስን ሰው አላውቅም !" አለኝ ፊቱን አዙሮ እየሄደ።

በቃ! ??? ስመጣ የሆነ ከባድ ሸክም ላራግፍ ...... የሆነ የሚስጥር መፍቻ ቁልፍ ላገኝ ........ የሆነ ያልኖርኩትን መኖር ልጀምር ....... የሆነ ከበሽታዬ የምፈወስ ........ የሆነ ጥያቄዬ ሁሉ የሚመለስ ዓይነት አልነበር የነበርኝ ስሜት?

ጥያቄዬ ግማሹ እንኳን መልስ ሳያገኝ ይባሱኑ ልሸሸው እንደማልሞክር የማውቀውን ሀላፊነት አሸክሞኝ ገባ! ተገተርኩ ለደቂቃ! ልክ እሱ መሬቱ ላይ ዘጭ ብሎ እንደተቀመጠው ንጥፍ ማለት አማረኝ። ራሴን ምን ውስጥ ነው የከተትኩት? ምኑን ከምኑ ነው የማዛምደው? ጭራሽ ልጠይቀው ያላሰብኩት ጥያቄ ትዝ አለኝ። ምን አድርጎ ነው የታሰረው? ምን ያህል ዓመት ይሆን የሚቆየው? ለልጄ እውነቱን ከነገርኳት ቢያንስ ይሄን ማወቅ አለብኝ። እንደገባኝ ከሆነ የግሩም አባት መረጃዎችን በአቋራጭ የማግኘት መክሊት አለው። እግሬ መሬቱ ላይ የተተከለ ይመስል ከተገተርኩበት ተስፈንጥሬ አጠገባቸው ደረስኩ። እንደሆነ ሊፈነዳ እንደተቀባበለ መዓት የምለውን ለመስማት ጠበቁኝ።

"አንድ ውለታ ዋሉልኝ!" ስላቸው ሁለቱም ግራ ገብቷቸው ያዩኛል።

"የታሰረበትን ምክንያትና ምን ያህል እንደተፈረደበት ማወቅ አለብኝ!" ስላቸው ፍፁም የጠበቁት ጥያቄ አለመሆኑ ያስታውቅባቸዋል። አባትየው ከድንጋጤው መለስ ብሎ

"ስልኮች እደዋውላለሁ። " አለኝ።

ወደአዲስአበባ እየተመለስን ጭንቅላቴን የጨመደደው ሀሳብ የታሰረው ክፉ ነገር አድርጎ ቢሆን ለልጄ እንዴት ብዬ እንደምነግራት ነበር። በመስኮቱ አሻግሬ እያየሁ ውስጤ ያለው ስሜት ቅድም ስሄድ የነበረው ዓይነት እንዳልሆነ ገባኝ ..... ምን አጊንቼ ነው የቀለለኝ??

"እርቦኛል:: የሆነ ቦታ ምግብ እንብላ?" አልኩኝ
"ባንቺ ሁኔታ ስለምግብ ማውራት ቅንጦት ስለመሰለኝ እንጂ ቁርስ እንኳን ሳንበላ ነውኮ ጠዋት የወጣነው!" አለኝ ግሩም!

ይቀጥላል ......

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
አንዳንድ ቀን ይበለኝ የደስታዬ ጠላት እኔ ነኝ እላለሁ ።የማፈቅራት ልጅ ነበረች ፤ ቅብጥ
ያለች ፤ ጨዋታ አዋቂ ነፍሷ በጥንጥ ነገር የሚደሰት ። ቁም ነገሬ ለምለው ነገር ያላት
ቸልታ ነገ ለምመሰርተው ኑሮ ተፅዕኖ እንዳለው እጠረጥራለሁ ። ጥርጣርዬ ግንኙነታችን
ወደ ትዳር እንዳያድግ አገደኝ ።
መልክ አይቼ፤ ዳሌ አይቼ ፤ ሳቄን ብዬ እንዴት ኑሮ እመሰርታለሁ ብዬ ነው የተውኳት።
አብረን ሆነን ስኮምክ እንደትንሽ ልጅ አፏን ከፍታ ደረቴ ላይ ተለጥፋ ታሽካካዋለች ፤ አሳሳቋ
የድብርት ፤ኩርፍያን ይገነብራል።
እኔ ጅንኑ ከእሷ ጋ ስሆን ነፃነቷን ታፈናጥርብኛለች ፤ እላፋታለሁ ፤ ተው እያለችኝ ለልፊያ
እራሷን ታዘጋጃለች ፤ ስታገላት እየሳቀች በሳቋ መሃል "ጅል ነህ እንዴ"? ትለኛለች
ጅል ላልሆነ ሰው ጅል ሲባል የበለጠ ያስቃል የበለጠ ያጃጅላል።
ኩርፊያዋ አይቆይም ፤ ረስታው ታወራኛለች እያወራች መሃል ላይ "ኤጭ ለካ አኩርፌ ነበር
በቃ ምስኪን ስለሆንኩ ትጫወትብኛለህ ኣ"? ትለኛለች አንገቷ ስር ሽጉጥ ብዬ ስስማት
"እሰ..ይ" ትለኛለች ።
እንስቃለን ።
ቁጠባ፤ እቅድ ፤ ነገር ማወሳሰብ ጠላቷ ነው አትችልበትም ። ጫማሽን እንሽጠው እና
እንጠጣበት ብላት አረ ? ጥሩ ሃሳብ ከማለት ውጪ አትግደረደርም ።
አውጥቼ ፤ አውርጄ ፤ ብልጣ ብልጥነቴን ተጠቅሜ ተውኳት።
ሌላ ጠበስኩ
አገባሁ።
ጨዋ ፤ ጠንካራ ፤ነብሴ ከነብሷ የማይናበብ
ሰው ስለወደደልኝ ፤ ጨዋ ነች ብዬ ስላሰብኩ አገባኋት ።
ባለ መነፅር ፤ እርግት ያለች ፤ ለእያንዳንዱ ነገር ማብራሪያ ያላት ጎበዝ ታታሪ ነች ሚስቴ ።
ደስ አለኝ ራሷን የቻለች ልጅ፤ ትጉህ ሰራተኛ እና የሚጠቅማት ላይ የምትመሰጥ በመሆኗ
ነው የመርጥኳት ።
ነገር ግን
ድሮ ቀልድ እችል እንደነበረ ሁላ ነው ያጠፋችብኝ ። ኑሮዬ ሎጂክ ሆነ ። እሷ ጋ ሁሉ ነገር
ቁምነገር ነው። ልለውጣት ብሞክር ብጣጣር ከሆነችው ነገር ፈቀቅ አልል አለች ።
ረጅም ማሽካካት ፤ ልግጫ ፤ ልፍያ ፤ ቀልድ ድራሹ ጠፋ ።
ከስራ መልስ ሌላ ስራ ነው። እራት ይቀርባል ፤ እንበላለን። ቀስ ብለን ልክ እንደ ምግብ
ተሰናድተን ልክ ለደሞዝ እንደሚሰራ ስራ አንዳንዴ እንዋሰባለን።
ወሲባችን ልፍያ የለው ፤ ግፍያ የለው ፤ ችኮላ የለው፤ መላላስ የለው ፤ መቀባጠር የለው ፤
ሁካታ የለው፤ ቅድመ ወሲብ እና ድህረ ወሲብ በወሲቡ ዙርያ ቀደዳ የለ፤ ሁሉ ነገር እሷ ጋ
ቁምነገር ነው ።
ቁጥብ ያለ ነው ሁሉ ነገሯ ።
በቃ ኑሮን ካለ እቅዴ ኮስተር ብሎ ከሚኖሩት ውስጥ ተቀላቀልኩ ። ጭምትር ማለቷን
ላላቅቃት ሞከርኩ ። በሙከራዎቼ መንፈሳዊ ጥቅሶች ፤ ባህል፤ እሴት፤ ወግ እየሞጀረች
ኩም ታደርገኛለች ።
ዝግጁ ያልሆነን ሰው እና ፍቃድ የሌለው ፍጡርን እንደ መቀየር ከባድ ነገር የለም ።
ብዙ ጭቅጭቅ የለ ፤ ብዙ ንዝንዝ የለ ። የማሽን ኑሮ እየኖርኩ ነው።
አንዳንዴ
ምን አለ የድሮ ፍቅረኛዬን ባገባት ኖሮ እላለሁ። እሺ ይሁን እጣ ፈንታችን አልገጠመም ።
ያን የመሰለ ማሽካካት ፤ልፊያ ፤ልግጫ ፤ ቡረቃ አይቼው ባልነበር ፤ ዛሬ እንደዚህ መች
አይኔ ላይ ውል ይለኝ ነበር?!
እጦትን ከሚያጎሉ ነገሮች አንደኛው አግኝቶ ማጣት ነው ።
ቁም ነገረኛዋን ሚስቴን ማግባቴ ትክክል ነኝ አይደለሁም አላቅም።
ኑሮዬ ስራ ሲሆን የድሮ ኑሮዬ ንፍቅ ይናፍቀኛል።
ሚስቴ ጋ ከጓደኛ ጋ መሰብሰብ ፤ ማምሸት መቀምቀም ምቾት አይሰጣትም በዚህም
ምክንያት በአጋጣሚ ካልሆነ አላመሽም አልሰበሰብም አልቀመቅምም።
ጥንካሬዋ እና ጉበዝናዋ የኑሮ ሸክሜን ስታቀልልኝ አይ እሰይ እንኳን ያገባኋት እላለሁ።
ነፃ መሆን ፤መፍታታት ፤መሽካካት ነፃ አበላለግ ከአጋሬ ጋ ሲያምረኝ የትላንቷ እጮኛዬ
ትናፍቀኛለች ።
ማስታወሻ
እጅግ የበዛ እጅግ እንዳነሰ ያህል ነው ።


@getem
@getem
@paappii

#Adhanom Mitiku
ልጅነት...
*
በልጅነታችን ሁላችንም ለወላጆቻችን ጨዋ ነበርን። ሼባዎቹ ጠጅ ቤት በተጣሉ ቁጥር
<<ከእገሌ ልጅ ጋር አትዋል!!>> የሚል ሀርድ ይበጨቁብናል። ጥሎብን ደግሞ
የተከለከልነውን ጓደኝነት ነፍሳችን አጥብቃ ትሻለች። በልጅነቴ ኩኩሻ ከተባለ ልጅ ጋር
እንዳልውል ማዕቀብ ተጥሎብኛል። እሱም እንደኔው ከእኔ ጋር እንዳይውል ማስጠንቀቂያ
ተሰጥቶታል። በእዚህ ምክንያት ለአባቶቻችን <<ጦጣው>> የሚል የጋራ ቅጽል ስም
አውጥተንላቸው በድብቅ እንገናኝ ነበር።
አንድ ቀን ጨፌ ኳስ ልጫወት የጨርቅ ኳሴን ታቅፌ በበራቸው ላይ እያለፍኩ ሳለ
ከግቢያቸው ውስጥ የኩኩሻን ድምጽ የሰማኹ መሰለኝ።
<<ኩኩሻ!>> ብዬ ተጣራሁ።
ከግቢው ውስጥ <<እ!>> የሚል ድምጽ ሰማሁ።
<<ኳስ አትጫወትም? ጨፌ እየሄድኩ ነው!>>
መልስ ሳጣ በድጋሚ <<ምነው? ጦጣው አለ እንዴ?>> ብዬ ጠየቅኹ።
ይሄኔ ከግቢው ውስጥ <<ኧረ አለሁ..አለሁ...ግባ!>> የሚል የአባትየውን ጎርናና ድምጽ
ተሰማ።
ከእዚያ በኋላ እንዴት ነፍሴ እስክትወጣ በርሬ ቤት እንደገባሁ እኔና እግሬ ብቻ ነን
የምናውቀው። ሁለቱ ሼባዎች እስኪታረቁ ድረስ የእኔና የኩኩሻ ጓደኝነትም ተቋርጦ ቆየ።
**

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Tilahun girma ango
አክስቶቼ እና ላሞቻቸው
-----
ጸሐፊ: አፈንዲ ሙተቂ
------
ስለሁለት አክስቶቼ ላወጋችሁ ነው። አሚና ኢብራሂም (በቀኝ) እና ሐኒፋ ሼኽ ሙሐመድ ረሺድ ይባላሉ፡፡ “ሐኒፋ” የአባቴ እህት ስትሆን መላው ዘመዶቿ እና የሰፈሩ ህዝብ “አዴ” እያለ ነው የሚጠራት፡፡ ከዚህ ቀደም “ኦነግ እና ኢህአዴግ በአንድ ቀን ጦርነት” በሚል ርዕስ በጻፍኩት ጽሑፍ ያወጋኋችሁ ጦርነት የተጀመረው በርሷ ግቢ ውስጥ ነው፡፡ አሚና ኢብራሂምም የስጋ ዘመዴ ናት፡፡ ይሁንና አያቴ (ሼኽ ሙሐመድ ረሺድ) ያገቧት የመጨረሻ ሚስት እርሷ በመሆኗ የሼኽ ሙሐመድ ረሺድ ልጆች “አዮ አሚና” እያሉ ነው የሚጠሯት፡፡ እኛም የአባቶቻችንን ልማድ በመከተል “አዮ አሚና” እያልን እንጠራታለን፡፡

እነዚህ አክስቶቼ ልጅ በነበርኩበት ዘመን በርካታ ከብቶች ነበሯቸው፡፡ በግቢዎቻቸው ጥግም ለከብቶች የተሰሩ ሰፋፊ በረቶች ነበሯቸው፡፡ ባለፈው በጥቅምት ወር 2008 ስዘይራቸው ግን የሁለቱም በረት በቦታው አልነበረም፡፡ “ከብቶቹ ወዴት ጠፉ?” ብዬ ስጠይቃቸው ልዩ ልዩ ምክንያቶችን ዘረዘሩልኝ፡፡ ዋነኛው ምክንያታቸው “ድሮ የግጦሽ ስፍራ የነበሩት መስኮች በሙሉ ወደ እርሻ ማሳነት ተቀይረዋል፤ ስለዚህ ከብቶቹን ለማብላት ወደ ሩቅ ስፍራዎች መሰማራት ግድ ይላል፤ አሁን ባለው ሁኔታ ግን ያንን ማድረግ አንችልም፤ በመሆኑም ከብቶቹን ለመሸጥ ተገደድናል” የሚል ነው፡፡ ምክንያታቸው አሳማኝ ቢሆንም ከሁለቱ ቤቶች እንደ ድሮው ትኩስ ወተት በ“ቀቤ” ለመጠጣት ባለመቻሌ አዘንኩ! እስቲ ስለነዚያ ከብቶች ያለኝን ትዝታ በትንሹ ላውጋችሁ፡፡
*
በዚያ ዘመን በሰፈሩ የሚኖረው እያንዳንዱ ቤተሰብ ጥቂት የማይባሉ ከብቶች ነበሩት፡፡ በዘመኑ ወግ መሰረት ሴት ከብቶች (ላም እና ጊደር ) እና ጥጆች ባለቤትነታቸው የእመወራዎች ነው፡፡ ከነዚያ እመራዎች ሁሉ በከብቶች ብዛት የምትበልጠው ደግሞ “አዮ አሚና” ነበረች፡፡ በበረቷ ከሚያድሩት ላሞች መካከል በአንድ ጊዜ የሚታለቡት ብቻ አስራ አምስት ያህል ይሆናሉ፡፡ በመሆኑም ከቤቷ ወተት፣ ቅቤ እና እርጎ ጠፍተው አያውቁም፡፡ አያቴን ሊዘይሩ ለሚመጡ እንግዶች የሚቀርበው “ሆጃ” የሚፈላው በአብዛኛው ከርሷ ቤት በሚታለበው ወተት ነበር፡፡ ልጆች በቤታቸው እንጀራ እና ቂጣ ብቻ አግኝተው ማባያ ሲያጡ ወደርሷ ይመጡና ወተትና እርጎ ይጠይቃሉ፡፡ ለልጃገረዶችም ጸጉራቸውን የሚሰሩበትን ቅቤ ትሰጣቸው ነበር፡፡

በዘመኑ ወግ መሰረት ከብቶችን በስም እየለዩ መጥራት የተለመደ ነው፡፡ ታዲያ ለከብቶች የሚሰጠው ስም በአብዛኛው የከብቱን ቀለም እና ቁመና የተከተለ ነው፡፡ የ“አዮ አሚና” ስም አሰያየም ግን ከዘመኑ ልማድ ወጣ ያለ ነው፡፡ “መጋል” እና “ጉራቻ” ከተሰኙት ሁለት ላሞች በስተቀር ሌሎቹ ከብቶች ለየት ባሉ ስሞች ነበር የሚጠሩት፡፡ ለምሳሌ “ደንገሹ”፣ “ኩሜ”፣ “ባቲ”፣ "መገርቱ" ፣ “ሂና” “ኩሊ”፣ “ኩሪ”፣ "ዱኮ" ወዘተ…. በመሳሰሉ ስሞች የሚጠሩ ከብቶች ነበሯት፡፡ ስያሜዎቹን እንዴት እንደምታወጣቸው አላውቅም፡፡ ታዲያ አዮ አሚና ከብቶቿን ስታነጋግራቸው ዋዛ እንዳትመስላችሁ!! እያንዳንዱን ከብት እያከከችው እንደ ሰው ልጅ ታዋራው ነበር፡፡
*
የአዴ (ሐኒፋ ሼኽ ሙሐመድ ረሺድ) ከብቶች በብዛት የአሚናን ያህል አይደሉም፡፡ ይሁንና ከሰፈሩ ከብቶች ሁሉ ለኔ በጣም የሚታወሱኝ እነርሱ ነበሩ፡፡ ምክንያቱም ነፍስ ካወቅኩ በኋላ ወደሰፈሩ በምሄድበት ወቅት የማርፈው እርሷ ዘንድ ስለሆነ ነው፡፡

ከነዚያ ከብቶች መካከል በጣም ቁጡዋ “ዳለቲ” ትባላለች፡፡ “ዳለቲ” ቀንድ የላትም፡፡ ሆኖም በድቡልቡል ጭንቅላቷ በቴስታ “ገጭ” እያደረገችን ከመሬት ላይ ትፈጠፍጠን ነበር፡፡ ከልጅነት እስከ ጉልምስና ዘመኗ ድረስ የምታውቃት አክስቴ እንኳ ቀኑ ሲመሽ ዳለቲን ይዛ በማደሪያ ስፍራዋ ላይ አስራ አታውቅም፡፡ “ዳለቲ” የማትነካቸው ሁለት ልጆችን ብቻ ነው፡፡ አንደኛው ሙሐመድ አሕመድ (ነጋሺ) የሚባለው የራሷ (የአክስቴ) ልጅ ሲሆን ሌላኛው “ናጂ በደው” ይባላል፡፡ ስለዚህ ዳለቲን ለማሰር ከተፈለገ እነዚያ ልጆች የግድ መገኘት ነበረባቸው፡፡
“ዳለቲ”ን የወደለቻት “ጋሬ” የምትባል ላም ናት፡፡ ይህቺ ጋሬ “ጄብሎ” የተሰኘ ሌላ ላምም ወልዳለች፡፡ ታዲያ ይህቺ “ጄብሎ” በውጊያ እናቷን ታሸንፋታለች፡፡ አክስቴ የቡና አተላ (ረጃ) እና ድርቆሽ ለጋሬ በምትሰጥበት ጊዜ “ጄብሎ” እያባረረቻት ትነጥቃለች፡፡ ሆኖም “ጄብሎ” ምንም ቀንድ ያልነበራትን ዳለቲን አትችላትም፡፡ በመሆኑም ዳለቲ ከእናቷ አፍ ድርቆሹን የነጠቀችውን “ጄብሎ”ን ታባርርና ለራሷ መብላት ትጀምራለች፡፡ ይሄኔ ግን የድርቆሹ የመጀመሪያ ባለቤት የሆነችው “ጋሬ” ከተፍ ትላለች! ምክንያቱም እርሷ ጄብሎን ባትችላትም ቀንዳ አልባ ለሆነችው ዳለቲ ትበረታለችና! እናም ከጅምሩ ለርሷ የተሰጠውን ድርቆሽ ያስመለሰችው “ጋሬ” ዘና ብላ መመገብ ትጀምራለች፡፡ ይሁንና ምንም ያህል ሳይቆይ “ጄብሎ” እንደገና ከተፍ ትልና እንደለመደችው “ጋሬ”ን በማባረር ድርቆሹን መብላት ትጀምራለች፡፡ አንድ ጊዜ ያህል ዋጥ ካደረገች በኋላ ግን “ዳለቲ” ከተፍ ትልና ድርቆሹን ትነጥቃታለች፡፡ “ዳለቲ” መብላት ስትጀምር ደግሞ እንደገና “ጋሬ” ትመጣለች፡፡ እንደገና “ጄብሎ”፤ እንደገና “ዳለቲ”፤ እንደገና “ጋሬ”!
አክስቴ ለሶስቱ ከብቶች በተለያየ ቦታ ድርቆሽ ብታስቀምጥላቸው እንኳ ላሞቹ ጥላቸውን አይተውም፡፡ አንደኛው ከብት ለርሱ የተሰጠውን ከማላመጥ ይልቅ ሌላኛውን ነጥቆ መብላቱ ያስደስተዋል፡፡ ስለዚህ አክስቴ የከብቶቹን ጥል ለማስቀረት ሌላ ዘዴ ፈጠረች፡፡ ላሞቹ ከማደሪያቸው ሳይፈቱ ድርቆሽና ውሃቸውን መስጠት!! በዚህ ዘዴ ሁሉም ተስተካከለ፡፡ ሆኖም አንዳንዴ አክስቴ በቤቷ በሌለችበት ጊዜ የአክስቴ ልጆች የሶስቱን ከብቶች ጥል ለማየት ሲሉ ብቻ መመሪያውን እየጣሱ ከብቶቹን ይፈቷቸው ነበር፡፡ እናም ጋሬ፣ ዳለቲ እና ጄብሎ ለረጃ እና ለድርቆሽ ሲሉ እየተቁነጠነጡ ውጊያ ይገጥማሉ፡፡

ይህ የሶስቱ ላሞች ጥል ለረጅም ጊዜ ሲገርመኝ ነበር፡፡ አንዱ ከብት አንደኛውን ብቻ ይችለዋል፤ ሌላኛውን ለማባረር ግን ወኔ የለውም፡፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው እንዴት ነው…? ሁለቱንም ላሞች የወለደችው “ጋሬ” ሌሎቹን ማሸነፍ ያልቻለችበት ምክንያትስ ምንድነው…? ቀንድ ያላት “ጄብሎ” ቀንድ አልባዋን “ዳለቲ”ን የምትፈራበት ምክንያትስ ምንድን ነበር….?

መልሱን በጭራሽ አላውቀውም!! ይሁንና በኋለኛው ህይወቴ ተመሳሳይ አጋጣሚዎችን በማይበት ጊዜ ሁሉ የነዚያ ከብቶች ጥል ወደ አዕምሮዬ ይመጣል፡፡
*
የአዴ” (አክስቴ) ከብቶች የሚጠሩባቸው ስሞች ከአዮ አሚናም ይበልጥ ያስገርማሉ፡፡ ለምሳሌ ከላይ የጠቀስኳት “ጋሬ”ን እና “ጋሬ” የወለደቻቸውን ብቻ በስም ላስተዋውቃችሁ፡፡

በሀረርጌ ኦሮሞ ባህል መሰረት “ጋሬ” የሚባለው ሰውነቱ በጥቁር ወይም ቀይ ቆዳ ተሸፍኖ በጭንቅላቱ ላይ ብቻ ነጭ የሆነ ከብት ነው፡፡ “ጋሬ” ግን ሙሉ በሙሉ ቀይ ነበረች፡፡ በዚህ ረገድ ከሌሎች ጋሬዎች ሁሉ የተለየችው እርሷ ብቻ ነበረች፡፡ አክስቴ ለምን ከህዝቡ ልማድ ውጪ ለላሚቱ “ጋሬ” የሚል ስም እንዳወጣች ስጠይቃት “ጋሬ የእናቷ ስም ነበር፤ እናቷን በጣም እወዳት ነበር፤ ብዙ ወተት ያለስስት የሰጠችኝ ላም ናት፤ ነገር ግን የአባ ጎርባ በሽታ ገደለብኝ፤ ስለዚህ እርሷን ለማስታወስ ብዬ ለልጇ “ጋሬ” የሚል ስም አወጣሁ” አለችኝ፡፡
(ከላይ ካለው ጽሑፍ የቀጠለ)
----
“ጋሬ” የወለደቻት የመጀመሪያ ከብት “ቤጆ” ትባላለች፡፡ “ፔጆ 404” የምትባለው የቤት መኪና “ፋሽን” በነበረችበት ዘመን ስለተወለደች ነው እንዲህ ተብላ የተጠራችው፡፡ ሁለተኛዋ ቀንድ አልባዋ “ዳለቲ” ናት፡፡ ይህችኛዋ በቀለሟ “ዳለቻ” ስለነበረች ነው እንዲያ የተባለችው፡፡ ሶስተኛዋ “ጄብሎ” ናት፡፡ አክስቴ ስሙን ከየት እንዳመጣችው አላውቅም፡፡ ሆኖም ወደ ከተማ መጥታ “ጀብሎ” የሚባሉ ሲጋራ አዟሪዎችን ካየች በኋላ ስሙን ለከብቷ እንዳወጣችው እጠረጥራለሁ፡፡ አራተኛው “ሌንጮ” ይባላል፡፡ ይህኛው ወይፈን ነው፡፡ “ሌንጮ” በልጅነቱ የተለየ ስም የነበረው አይመስለኝም፡፡ በሂደት ግን የሰፈሩን በሬዎች እየገጠመ ስላሸነፋቸው “ሌንጮ” የሚለውን ስም አግኝቷል (“ሌንጮ” በአማርኛ “አንበሳው” እንደማለት ነው)፡፡

አምስተኛዋ “ዲምቱ” ትባላለች፡፡ “ቀዮ” እንደማለት ነው፡፡ ይህቺኛዋ “ኦነግ እና ኢህአዴግ በአንድ ቀን ጦርነት” በሚል ርዕስ በተጻፈው ተከታታይ ጽሑፍ ውስጥ ያስተዋወቅኳችሁ ላም ናት፡፡ በዕለቱ በግቢው ከነበሩት ከብቶች መካከል በጥይት ተመትታ ለመሞት የበቃችው እርሷ ብቻ ናት፡፡ ስድስተኛዋ አንዲት ብስል ቀይ ጥጃ ናት፡፡ ይህቺኛዋ “ደሃቦ” የሚል ስም የነበራት ሲሆን ስሙን የሰጣት ደግሞ በወቅቱ ከብቶቹን ያግድ የነበረው “ሙሐመድ አሕመድ” (ነጋሺ) የተባለው የአክስቴ ልጅ ነው፡፡ ሆኖም በዚህ ስም ላይ ከባድ ውዝግብ ተቀስቅሷል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡
ስያሜው በቅድሚያ የተሰጠው ከቢር ያሕያ የተባለ የአክስቴ ጎረቤት ለወለዳት አንዲት ቀይ ልጅ ነው፡፡ መሐመድ አሕመድ ግን ስሙ በጣም ደስ አሰኘውና በዚያው ሰሞን “ጋሬ” ለወለደቻት ጥጃ ሸለማት፡፡ የከቢር ያሕያ ሚስት ይህንን ስትሰማ ተቆጣች!! “እንዴት በልጄ ስም ከብቱን ይጠራል?” በማለት መንደሩን ቀወጠችው፡፡ መሐመድ አሕመድ ጥጃዋን በዚያ ስም መጥራቱን እንዲተው ቢነገረው “እምቢ” አለ፡፡ አክስቴ ብትለምነው፣ ብታስፈራራው፣ ብትገርፈው ልጁ በእምቢታው ጸና፡፡ የከቢር ያህያ ሚስት አክስቴ “ሆን ብላ ያደረገችው ነው” ባይ ሆነች፡፡ አክስቴ ሐቁን ብታስረዳት በጭራሽ አልሰማ አለች፡፡ በመጨረሻም ሽማግሌዎች በነገሩ ገብተው መሐመድን ገሰጹት፡፡ መሐመድም ለጊዜው ግሳጼውን የተቀበለ መሰለ፡፡ ነገር ግን በዚያ ስም ፍቅር ስለተለከፈ አንድ መላ ፈጠረ፡፡ ደሃቦን በአማርኛ መንዝሮ “ወርቄ” በሚል ስልት ጥጃዋን መጥራት ጀመረ፡፡ አማርኛ የማትሰማው የከቢር ያህያ ሚስትም ከቁጣዋ ረገብ አለች፡፡ መሐመድ አሕመድም ለ“ደሃቦ” የነበረውን ፍቅር በ“ወርቄ” በኩል ተወጣ (“ደሃብ” በዐረብኛ ወርቅ ማለት ነው፤ ሶማሊዎች ስሙን ሲያቆላምጡት “ደሃቦ” ይላሉ”)፡፡
-----
እነዚያ በፍቅር እያናወዙ ጎረቤት የሚያጣሉ ከብቶች ዛሬ የሉም፡፡ ወተት “በሽበሽ” የነበረበትን ያንን ደግ ዘመን አልፈን የገጠሩ ህዝብም እንደ ከተሜው ገበያ እየሄደ ወተት በኩባያ ከሚገዛበት ዘመን ላይ ደረስን፡፡ ይህም እንግዲህ ኑሮ ነውና “አልሓምዱሊላህ” እንላለን፡፡

በነገራችን ላይ "አዮ አሚና" አሁን በሕይወት የለችም። ይህንን ጽሑፍ ከጻፍኩ በኋላ በጥር ወር 2010 አርፋለች። አላህ ይርሓማት። "አዴ" ግን ዛሬም አለች። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ድሬ ዳዋ ከከተመው ልጇ ዘንድ እየኖረች ነው። ረጅም ዕድሜ ይስጣት።
እኛንም ቸር ያቆየን!
-----
አፈንዲ ሙተቂ
ጥቅምት 30/2008 ተጻፈ።
ገለምሶ- ምዕራብ ሀረርጌ

@wegoch
@wegoch
@paappii
አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #6

“ማት? አንተ እኔን ብትሆን ምን ታደርግ ነበር ?" አልኩት ወንድሜን የሆነውን አንድ በአንድ ከነገርኩት በኋላ።

"እኔ አንቺን ልሆን አልችልም! ኸረ ማንም አንቺን ሊሆን አይችልም! እህቴ ማንም ያንቺ ልብ የለውምኮ!! ግን አያድርገውና ባንቺ ቦታ ብሆን ታውቂኛለሽ እዛው አንድ አይኑን በቦክስ ጠብቼው ሁለት ስንቅ ታመላልሺ ነበር።" አለኝ እየሳቀ።

"ማት የምሬን ጨንቆኝኮ ነው!"

"እህቴ ? " አለኝ ..... አለው የሆነ የሚያየኝ አስተያየት .... የስስት ዓይነት! በስሜ ጠርቶኝ አያውቅም። 'እህቴ' ነው የሚለኝ።

"ያለሽ እውነቱን ነው። ካንቺ የተሻለ ምክንያታዊ ሆኖ የሚወስን ሰው እኔም በአቅራቢያዬ አላውቅም! የሆነማኮ እነእማዬ ከእኔ ተደብቃው ያስተማሩሽ ጉብዝና አለ"

"አያድርገውና ብትሞትስ?" አልኩት

"ብትሞት ነው ወይስ ብትድን ይበልጥ ያስፈራሽ?"

"ማለት? "

"ማለትማ ገብቶሻል! ቅድም ከባባ ጋር ስትሆኚ የነበረውን አይቻለሁ። ውስጡ ካለነው በአንድ ጣት የማንሞላ ሰዎችሽ ውጪ ማንም እንዳይገባበት ደራርበሽ ያጠርሽውን አጥር ዘው ብሎ ገብቶብሻል። ያን አጥርሽን ሲያልፉ .... ስስት አታውቂም ነፍስሽንም : ያለሽንም ትሰጫለሽ! ከዛ ሲሄድብሽ ያለውን መሰበር ትፈሪዋለሽ!"

እሱ ክሽን አድርጎ በቃላት ሲያስቀምጠው የሆነ ያሳከከኝን ቦታ በትክክል ያገኘው 'አዎ !...እሱጋ' የሚያስብል አይነት ስሜት ተሰማኝ። የገለፀበት መንገድ ገርሞኝ

"አይገርምም! ፈሪ አድርጎኛል!" አልኩኝ

"እሱ ነው ፈሪ ያደረገሽ? እሱም በግድ አጥርሽን አልፎ አይደለም ውስጥ ያገኘሽው? ስታውቂው ውጣልኝ የማትዪበት ደረጃ ደርሶ አይደለም የተቀበልሽው? አስቢው እህቴ? መቼ ነው ከቤተሰብ ውጪ ለመጨረሻ ጊዜ ጓደኛ ኖሮሽ የሚያውቀው? ከአቢ በኋላ ሁሌም እንዲህ ነበርሽ። "

አቢ የአባዬ ታናሽ እህት የአክስቴ ልጅ ናት። እሷ እኛ ቤት ከመምጣቷ በፊት ምን ዓይነት ልጅ እንደነበርኩ አላስታውስም። አክስቴ በልጅነቷ ከትዳር ውጪ ነበር የወለደቻት። ጣሊያን ቪዛ አጊንታ ስትሄድ አቢ እኛ ቤት ስትመጣ 14 ዓመቴ ነው። በወራት ነበር የምትበልጠኝ። እህትም ጓደኛም አገኘሁ። እኔ የምማርበት ትምህርት ቤት ገባች። ለአራት ዓመት ከእርሷ ተለይቼ የሄድኩበትን ቦታ፣ ከእርሷ ተለይቼ የበላሁትን ምግብ፣ ሰምቼ ወይ አድርጌ እሷ የማታውቀው ነገር አላስታውስም። ውጤት አምጥተን የተለያየ ዩንቨርስቲ ሲደርሰን አይኖቼ እስኪፈርጡ አለቀስኩ። በዚህ መሃል እናቷ መጣች። እናቷ ስትመጣ በተደጋጋሚ ከእናቷ ጋር ለብቻ ማሳለፍ ሲጀምሩ የምሰራው ጠፋኝ። እሷ ሳትኖር ምንድነበር የማደርገው? ማሰብ አቃተኝ። የሆነ ቀን ግራ ሲገባኝ እማዬጋ ሱቅ ሄጄ ዋልኩ። ስመለስ አቢ አልነበረችም። ሻንጣዋን ይዛ ሄዳለች። ቻው እንኳን አላለችኝም። አባዬና ማት ሳሎን ቁጭ ብለው ነበር።

"አቢስ?" አልኩኝ

"አቢ ከእናቷ ጋር ሄዳለች!" አለኝ አባዬ

"ልታድር? " አልኩኝ ማደሯ እየከፋኝ

"አይደለም ልጄ! ተመልሳ አትመጣም! ከእናቷ ጋር ወደውጪ ሄዳለች። ዛሬ ነው በረራቸው !" አለኝ ምንም እንዳልሆነ ቀለል አድርጎ።

ያውቁ ነበር እንደምትሄድ። ራሷ ትንገራት ብለው ነበር ዝም ያሉኝ። እሷ ልትነግረኝም ..... ቻው ልትለኝም ግድ አልሰጣትም። ማልቀስ እየፈለግኩ ግን አላለቀስኩም። ዝም አልኩኝ። ለቀናት ዝም አልኩኝ። ለእኔ ብዙ ነገሬ ናት ብዬ ለማስባት ሴት ለሷ ምኗም አልነበርኩም ብዬ ሳስብ ልቤን ክብድ ይለኛል። እኔና እሷ የምንቀመጥበት የነበረ ካፌ ብቻዬን ቁጭ ብዬ 'የምሯን ነው ግን? አብረን የሳቅነውን፣ ያለቀስነውን፣ አብረን የሰራነውን ተንኮል፣ የተማከርነውን ....የምሯን ረስታው ነው?' እላለሁ። ከወር በኋላ ደውላ

"ቻው ያላልኩሽ ፈርቼሽ ነው!" ከማለት የተሻለ ማብራሪያ እንኳን አልሰጠችኝም። በቃ ህይወቷን ቀጠለች። እኔ ግን ጎደለችብኝ። የሆነ ቀን ከቤት ደወልኩላት። ከኢትዮጵያ ጣሊያን! በቅጡ ሰላም እንኳን ሳትለኝ "ፌቪዬ ልወጣ ስል ነው የደወልሽው እደውልልሻለሁ!" ብላ ዘጋችው። የእኔ በህይወቷ መጉደል ቁርስ የመዝለል ያህል እንኳን ሳይከብዳት ህይወቷን ቀጠለች:: ..... ጠበቅኳት። የሆነ ቀን 'ናፈቅሽኝ' ትለኛለች ብዬ ...... የሆነ ቀን የሄደችበት ሀገር የገጠማትን ልታወራኝ መልሳ ትደውላለች ብዬ ........ ጊቢ ሸበላ ወንድ አይቼ እንደው ደውላ ታበሽቀኛለች ብዬ ....... ቢያንስ ለልደቴ እንኳን አትረሳኝም ብዬ ......... ከዓመታት በኋላ ወደሀገር ቤት እስከተመለሰችበት ጊዜ ድረስ አልደወለችም። .....

"የህይወት አንዱ አካል ነው። ሰዎች ወደ ህይወትሽ ይመጣሉ ይሄዳሉ። የሆነው መንገድሽ ላይ መቀበልንም መሸኘትንም መልመድ የለብሽም?" አለኝ ማት በሀሳብ መጋለቤን እያስተዋለ። ስልኬ ሲጠራ አየውና በጥያቄ አየኝ

"ባክህ ባለመኪናው ነው። የገጫት!" አልኩት ግሩም የሚለውን ሲያይ ሌላ ነገር አስቦ እንደሆነ እየገባኝ።

"እኔ ተናግሪያለሁ!" አለኝ በተንኮል። ስልኩን አነሳሁትና ግሩም ሊያገኘኝ እንደሚፈልግ ነግሮኝ ልጄ ከትምህርት ቤት ከተመለሰች በኃላ ባባን ለሷ ትቼው ልንገኛኝ ተቀጣጥረን ዘጋሁት።

"አባቷ ምንም አድርጎ ቢሆን እውነቱን እንዳለ ማወቅ አለባት። ሳይዘገይ ብታውቅ ደግሞ ጥሩ ይመስለኛል።" አለ ማት ግሩም ስለአሸናፊ ሊነግረኝ በአካል ቢሆን ይሻላል እንዳለኝ ስነግረው።

"አውቃለሁ። ግን..."

"አንቺ አለሽላት ምንም አትሆንም! እያወቅሽ እንዳልነገርሻት ከምታውቅ እውነቱ ምንም ያህል ከባድ ቢሆን እሱን ብታውቅ ይሻላል። "

ማት ቤቴን ለቆ ከወጣ በኋላ ብዙም ሳይቆይ ባባ ከእንቅልፉ ነቅቶ አጠገቤ መጣ። አይኖቹን እያሻሸ በቅጡ ሳይገልጥ የተቀመጥኩበት ሶፋ ላይ እግሮቹን አውጥቶ ጭንቅላቱን ጭኔ ላይ አስደግፎ ተጋደመ። ልምድ እንደሆነ ነገር ........ ብዙ ጊዜ አድርጎት እንደሚያውቅ ነገር.......ለቀናት ሳይሆን ብዙ ጊዜ እንደሚያውቀኝ ነገር። ሳላስበው ፈገግ አልኩ።

ሊሄድብኝ እንደሚችል እያወቅኩም ቢሆን ያለስስት ልወደው፣ ልጠብቀው፣ የእኔ እስከማይሆን ቀን ድረስ የእኔ ላደርገው ለራሴ ቃል ገባሁ። ቀኑ ደርሶ ትቶኝ ሲሄድ አምኜ እቀበላለሁ! አልኩ። ልጄ ስትመጣ እዛው እግሬ ላይ እሱ እንቅልፍ ወስዶት በተቀመጥኩበት ሶፋውን ደገፍ ብዬ ሸለብ አድርጎኝ ነበር።

"ነፍስ አጥፍቶ ነው!" አለኝ ግሩም አንዱ ካፌ በተቀመጥንበት ሊነግረኝ ሲታሽ ቆይቶ!

"አሸናፊ በሌላ በምንም ሊታሰር ይችላል። ነፍስ ማጥፋት? በፍፁም!" አልኩኝ የሰማሁትን እንኳን ለማብሰልሰል ሰከንድ ሳልወስድ እርግጠኛ ሆኜ :: መደንገጥ ነበር የነበረብኝ አይደል? እንደዛ አይደለም የተሰማኝ

"እኔ እንጃ! ሰዎች እኮ ይቀየራሉ! አንቺ የምታውቂው ሰው ላይሆን ይችላል አሁን"አለኝ

"ትናንት ያየሁት አሸናፊ ምንም አልተቀየረም! የዛሬ 15 ዓመት የማውቀው አሸናፊ ነው።" ካልኩት በኋላ ነው ዓይኖቹን አፍጥጦ በመገረም ሲያየኝ ስለእኔና ስለአሸናፊ የሚያውቀው ነገር እንደሌለ ያስታወስኩት።

"የልጄ አባት ነው!" ካልኩት በኋላ ለማስረዳት ብዙ እንደሚፈጅ ሲገባኝ ተውኩት። እሱም አልጠየቀኝም። "እሺ ስንት ዓመት ነው የተፈረደበት? "

"አስራ አራት"

"በፍፁም እርግጠኛ ሆኜ የምነግርህ አሸናፊ እንኳን ሰው ለመግደል ለጥፊ እጁን አያነሳም።"

"እኔ ስለማላውቀው ምንም ልልሽ አልችልም ሰዎች ግን አይደለም በ15 ዓመት በ15 ቀን ሊቀይራቸው የሚችል አጋጣሚ ይፈጠራል።"

"ሟች ምን አይነት ሰው ነው? መረጃ አለህ?"
"አብሮት ማሳደጊያ ያደገ ጓደኛው የነበረ ሰው እንደነበር ? ከሀገር ውጪ ነበር መሰለኝ ለእረፍት በመጣበት ነው የተገደለው።"

"ገደለው?" አልኩኝ ሳላስበው።

"ምነው ታውቂዋለሽ?"

"አዎ! ማለቴ አላውቀውም ግን አሸናፊ ሲያወራ ሰምቻለሁ:: እርግጠኛ ነኝ እሱ ነው!! " አልኩኝ ደሜ ቀዝቅዞ

ይቀጥላል እኮ ....

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
የአብዮት ፍሬ ነኝ!

ብዙ ነገሮች ይናፍቁኛል። ብዙ ነገሮች በትዝታ ይመልሱኛል። በዚህች አጭር የእድሜ ልዩነት ይሄን ሁሉ ለውጥ ካየው በኔ ልጅ ዘመን ነገሮች ምን ያህል እንደሚለወጡ ሳስብ እንደ መደንገጥም እላለሁ።

ለውጥ 1

የድሮ መምህራኖች ማለት ...

አብዮት ፍሬ ነው የተማርኩት ። ይቅርታ አብዮት ፍሬ ነው ያደግሁት ...ሰላሳ አባትና ሰላሳ እናቶች ነበሩኝ።

የድሮ መምህራን እንደ ልጅ ይሳሱልሀል...እግር በእግር ይከታተሉሀል...ያፎካክሩሀል...ይመክሩሀል።

አይረሳኝም

መምህርት ብርቱኬ እኛ ከበናቸው.. .ግርማ ሞገሳቸው መቼም የእቴጌ መነን ነው። ኩርት ያሉ ቀብራራ...ሲኮሳተሩ ምድር ሆይ መቼ ነው የምትውጭኝ እንላላን....ሲንከባከቡን ደግሞ የእናታችንን ስም ለጊዜው እንዘነጋለን።

ታሪክ ሲተርኩልን በምናባችን እንጋልባላን...ከሚኒልክ ጋር እንዘምታላን...ጥልያንን አሳሩን እናበላዋለን መቼም !

የአድዋን ታሪክ ያፅፉናል...(ንግስታችንን ከበናል ... የባህርዛፉ ውዝዋዜ ራሱን የቻለ ዜማ ነው) .... አጤ ሚኒልክም...

አጤ ሚኒልክም (እንፅፋለን)...በመሀል የመምህራችን ንግግር አምልጧት የነበረችው ማርቲ ጔደኛችን ኤጭ!  አለች ጮክ ብላ ።

ኤጭ?????!

በስመአብ !

መብረቅ የወረደብን ያህል ክው አልን። ማርቲ በቃ ዛሬ እንደበርበሬ ልትደለዝ ነው ብለን ስናስብ መምህራችን ነገሩን ወደ ቀልድ ቀየሩት

"በባዶ ቤት ያንጫጫሽ! "

አጤ ምኒልክ አልኩሽ እኮ.. ..ሳቅ ተጥለቀለቀ....

አሁን ያሉትን መምህራን አሰብኳቸው።

ኤጭ ለማለት አትሳቀቅም...አብረውህ ይቅማሉ...አብረውህ ይጠጣሉ...ፌስቡክ ቲክቶክ ላይ አብረውህ ይለፋደዳሉ...ግርማ ሞገስ የላቸውም።

ለውጥ 2

አምስተኛ ክፍል ስገባ አብዮት ፍሬ ውስጥ እናቴ የለሽም። ከ 1-4 ክፍል ነበር ያኔ የምታስታምር...ዛሬ ሀይስኩሉን ትሾፍረዋለች።

መንጠራ ትምህርት ቤት ሳለው የመምህር ልጅ የሚል አክብሮት ይቸረኛል። በእረፍት ሰዓት እንደ ንጉስ ከቆምኩበት ሆኜ ጮርናቄና ብርቱካን ይመጣልኛል። የትኛውም ልብ አለኝ የሚል ውሪ ቀና ብሎ አያየኝም።

አብዮት ፍሬ ስገባ ብቸኛ ነበርኩና በአይን ከማውቃቸው የምዳሰ ሰፈር ጀለሶቼ ጋር ተቀላቀልኩ።

አንዳንድ ግብረ ገብ ያልሆነ ነገራቸው ግን አማረረኝ። አንዱ ደህና ኩርኩም አልሶኝ ዞር ስል ከየት መጣ ያልተባለ ሌላ ኩርኩም አናቴን ይፈልሰኛል።

ጭራሽ ደግሞ የሆነች ጌምህን ካላመጣህ ብለው ወጠሩኝ።

ያቺ ጌም ያን ጊዜ ከ I phone 13 በላይ ክብር ነበራት ።

26 ነፍስን የሚያስቱ ጨዋታዎች ነበሯት። በተለይ የአውሮፕላን ውድድሩ ይምጣብኝ 😍

ያቺን ጌም ይዣት ክፍል መጣሁ (ይዣት ባልመጣ እንደ ፊኛ ነፍተው ይጠልዙኛላ)

ምድረ ውሪ ከሌላ ፕላኔት እንደመጣ ፍጥረት ከበቡኝ።

ጭዌው ተጀመረ.. .ጌሟ ስትከፈት የሆነ ሰቅጣጭ ድምፅ ደግሞ አላት ...

ዲምዲሪሪሪንንንንንን...

ደግሞ ለክፋቱ ሂሳብ መምህራችን ጋሽ በሌ ከተፍ !

ጋሽ በሌ አበዱ ...

ጭራሽ ጌም ይዛችሁ ክፍል ውስጥ? (ይታያችሁ የዛሬ ተማሪ እኮ ብሉቱዝ ኤርፎኑን ሰክቶ ፖርን ፊልሙን ይለባልባል🙄)

ጌሙ የማነው?

ከዚህች ጥያቄ በኋላ ውሪው ሀዋሪያት ጌታን በከዱበት ፍጥነት ከዱኝ። በተለይ ዮሀንስ ሶስት ጊዜ ጮሆ ሸመጠጠኝ። ይሁዳው ቦጌ በጣቱ ጠቆመኝ።

ቲቸር ወላጅ ካላመጣህ አትገባም አሉኝ።

አቤት ድንጋጤ!

አባቴ ተጠርቶ ጌም ይዤ ክፍል እንደገባሁ ሲነገረው አሰብኩት ። አንበርክኮ በዛ የአዞ ቆዳ ቀበቶው ሲያርገፈግፈኝ ሳልሁት (ቀበቶዋ ደግሞ አስጨናቂ ሳህለ ሚካኤል የሚል ጥሁፍ ተነቅሶባታል ።) እውነትም አስጨናቂ...

ያኔ እኔ ታማሚ ነኝ ብዬ አወጅኩ። ትምህርት ቤት ቅርት!

ሀኪም ዘንድ ሂድ እንቢ

ፀበል ሂድ ኸረ ምን በወጣኝ! ...እናቴ ተሸበረች...

ከሶስት ቀን በኋላ በራችን ተቆረቆረ ።

ጋሼ ሄዶ ሲከፍተው ጋሽ በሌ!

የኔ እየሱስ የጠፋሁባቸውን በግ ለመፈለግ መጡ።

ሚኪ ትንሽ አጥፍቶ ተቆጥቼው ነበር አሉ...

አስቡት ጌምን ለዛውም ጩኸቱ ከመድፍ የሚልቅ ጌም ይዤ ክፍል መግባት ትንሽ ጥፋት ሲሆን 😑

ደንግጦ ቀርቶ ነው ብለው ቤተሰቦቼን አረጋጉልኝ ። ጥፋቴን እንኳ ሹክ አላሉም እኮ.. .ነገሮች ተድበሰበሱልኝ።

ከቀበቶ ውርጅብኝ አርነት ወጣሁ። በነጋታው ክፍል ስደርስ ከነዛ ቦዘኔ ውሪዎች አርቀው እዮብ የሚባል ጎበዝ ተማሪ ዘንድ አስቀመጡኝ።

ተመልከት የድሮ መምህር ጓደኛ ሰውን ምን ያህል ሊቀይር እንደሚችል የገባቸው ነበሩ።

እጅ ፅሁፌ ሲታይ ደብተሬ ላይ ዶሮዎች ፓርቲ ያዘጋጁ ይመስል ነበር ። እዮቤን እያየሁ እጄን ገራሁ !

የደብተሬ ልባድ የእብድ ቡትቶ ይመስላል ።

በጊዜ ሂደት ደብተሬን በወጉ መሸከፍ ጀመርኩ። ጭራሽ የመጀመርያው ገፅ ላይ ያለ ተሰጦዬ አበባ ሳልኩበት። አሁን ላይ ሆኜ ያን አበባ ሳየው ሳማም እንደመምሰል ይላል 😄

የዛሬን ተማሪ አሰብኩት.. .

ወላጅ ሲባል ገና ሪሲኒንግ አስቦ ይዞ ከተፍ ይላል

የዛሬን ወላጅ አሰብኩት ...

የተማሪ ነፃነት...መብት ምናምን በሚል ማልያ መምህሩን ለመክሰስ ሲሯሯጥ...

የዛሬን መምህር አሰብኩት ...

የበደለውን ተማሪ ከማስተማር ይልቅ ለመጣል ሲጋጋጥ.. .

ይቀጥላል! 

@wegoch
@wegoch
@wegoch
አክስቶቼ እና ላሞቻቸው
-----
ጸሐፊ: አፈንዲ ሙተቂ
------
ስለሁለት አክስቶቼ ላወጋችሁ ነው። አሚና ኢብራሂም (በቀኝ) እና ሐኒፋ ሼኽ ሙሐመድ ረሺድ ይባላሉ፡፡ “ሐኒፋ” የአባቴ እህት ስትሆን መላው ዘመዶቿ እና የሰፈሩ ህዝብ “አዴ” እያለ ነው የሚጠራት፡፡ ከዚህ ቀደም “ኦነግ እና ኢህአዴግ በአንድ ቀን ጦርነት” በሚል ርዕስ በጻፍኩት ጽሑፍ ያወጋኋችሁ ጦርነት የተጀመረው በርሷ ግቢ ውስጥ ነው፡፡ አሚና ኢብራሂምም የስጋ ዘመዴ ናት፡፡ ይሁንና አያቴ (ሼኽ ሙሐመድ ረሺድ) ያገቧት የመጨረሻ ሚስት እርሷ በመሆኗ የሼኽ ሙሐመድ ረሺድ ልጆች “አዮ አሚና” እያሉ ነው የሚጠሯት፡፡ እኛም የአባቶቻችንን ልማድ በመከተል “አዮ አሚና” እያልን እንጠራታለን፡፡

እነዚህ አክስቶቼ ልጅ በነበርኩበት ዘመን በርካታ ከብቶች ነበሯቸው፡፡ በግቢዎቻቸው ጥግም ለከብቶች የተሰሩ ሰፋፊ በረቶች ነበሯቸው፡፡ ባለፈው በጥቅምት ወር 2008 ስዘይራቸው ግን የሁለቱም በረት በቦታው አልነበረም፡፡ “ከብቶቹ ወዴት ጠፉ?” ብዬ ስጠይቃቸው ልዩ ልዩ ምክንያቶችን ዘረዘሩልኝ፡፡ ዋነኛው ምክንያታቸው “ድሮ የግጦሽ ስፍራ የነበሩት መስኮች በሙሉ ወደ እርሻ ማሳነት ተቀይረዋል፤ ስለዚህ ከብቶቹን ለማብላት ወደ ሩቅ ስፍራዎች መሰማራት ግድ ይላል፤ አሁን ባለው ሁኔታ ግን ያንን ማድረግ አንችልም፤ በመሆኑም ከብቶቹን ለመሸጥ ተገደድናል” የሚል ነው፡፡ ምክንያታቸው አሳማኝ ቢሆንም ከሁለቱ ቤቶች እንደ ድሮው ትኩስ ወተት በ“ቀቤ” ለመጠጣት ባለመቻሌ አዘንኩ! እስቲ ስለነዚያ ከብቶች ያለኝን ትዝታ በትንሹ ላውጋችሁ፡፡
*
በዚያ ዘመን በሰፈሩ የሚኖረው እያንዳንዱ ቤተሰብ ጥቂት የማይባሉ ከብቶች ነበሩት፡፡ በዘመኑ ወግ መሰረት ሴት ከብቶች (ላም እና ጊደር ) እና ጥጆች ባለቤትነታቸው የእመወራዎች ነው፡፡ ከነዚያ እመራዎች ሁሉ በከብቶች ብዛት የምትበልጠው ደግሞ “አዮ አሚና” ነበረች፡፡ በበረቷ ከሚያድሩት ላሞች መካከል በአንድ ጊዜ የሚታለቡት ብቻ አስራ አምስት ያህል ይሆናሉ፡፡ በመሆኑም ከቤቷ ወተት፣ ቅቤ እና እርጎ ጠፍተው አያውቁም፡፡ አያቴን ሊዘይሩ ለሚመጡ እንግዶች የሚቀርበው “ሆጃ” የሚፈላው በአብዛኛው ከርሷ ቤት በሚታለበው ወተት ነበር፡፡ ልጆች በቤታቸው እንጀራ እና ቂጣ ብቻ አግኝተው ማባያ ሲያጡ ወደርሷ ይመጡና ወተትና እርጎ ይጠይቃሉ፡፡ ለልጃገረዶችም ጸጉራቸውን የሚሰሩበትን ቅቤ ትሰጣቸው ነበር፡፡

በዘመኑ ወግ መሰረት ከብቶችን በስም እየለዩ መጥራት የተለመደ ነው፡፡ ታዲያ ለከብቶች የሚሰጠው ስም በአብዛኛው የከብቱን ቀለም እና ቁመና የተከተለ ነው፡፡ የ“አዮ አሚና” ስም አሰያየም ግን ከዘመኑ ልማድ ወጣ ያለ ነው፡፡ “መጋል” እና “ጉራቻ” ከተሰኙት ሁለት ላሞች በስተቀር ሌሎቹ ከብቶች ለየት ባሉ ስሞች ነበር የሚጠሩት፡፡ ለምሳሌ “ደንገሹ”፣ “ኩሜ”፣ “ባቲ”፣ "መገርቱ" ፣ “ሂና” “ኩሊ”፣ “ኩሪ”፣ "ዱኮ" ወዘተ…. በመሳሰሉ ስሞች የሚጠሩ ከብቶች ነበሯት፡፡ ስያሜዎቹን እንዴት እንደምታወጣቸው አላውቅም፡፡ ታዲያ አዮ አሚና ከብቶቿን ስታነጋግራቸው ዋዛ እንዳትመስላችሁ!! እያንዳንዱን ከብት እያከከችው እንደ ሰው ልጅ ታዋራው ነበር፡፡
*
የአዴ (ሐኒፋ ሼኽ ሙሐመድ ረሺድ) ከብቶች በብዛት የአሚናን ያህል አይደሉም፡፡ ይሁንና ከሰፈሩ ከብቶች ሁሉ ለኔ በጣም የሚታወሱኝ እነርሱ ነበሩ፡፡ ምክንያቱም ነፍስ ካወቅኩ በኋላ ወደሰፈሩ በምሄድበት ወቅት የማርፈው እርሷ ዘንድ ስለሆነ ነው፡፡

ከነዚያ ከብቶች መካከል በጣም ቁጡዋ “ዳለቲ” ትባላለች፡፡ “ዳለቲ” ቀንድ የላትም፡፡ ሆኖም በድቡልቡል ጭንቅላቷ በቴስታ “ገጭ” እያደረገችን ከመሬት ላይ ትፈጠፍጠን ነበር፡፡ ከልጅነት እስከ ጉልምስና ዘመኗ ድረስ የምታውቃት አክስቴ እንኳ ቀኑ ሲመሽ ዳለቲን ይዛ በማደሪያ ስፍራዋ ላይ አስራ አታውቅም፡፡ “ዳለቲ” የማትነካቸው ሁለት ልጆችን ብቻ ነው፡፡ አንደኛው ሙሐመድ አሕመድ (ነጋሺ) የሚባለው የራሷ (የአክስቴ) ልጅ ሲሆን ሌላኛው “ናጂ በደው” ይባላል፡፡ ስለዚህ ዳለቲን ለማሰር ከተፈለገ እነዚያ ልጆች የግድ መገኘት ነበረባቸው፡፡
“ዳለቲ”ን የወደለቻት “ጋሬ” የምትባል ላም ናት፡፡ ይህቺ ጋሬ “ጄብሎ” የተሰኘ ሌላ ላምም ወልዳለች፡፡ ታዲያ ይህቺ “ጄብሎ” በውጊያ እናቷን ታሸንፋታለች፡፡ አክስቴ የቡና አተላ (ረጃ) እና ድርቆሽ ለጋሬ በምትሰጥበት ጊዜ “ጄብሎ” እያባረረቻት ትነጥቃለች፡፡ ሆኖም “ጄብሎ” ምንም ቀንድ ያልነበራትን ዳለቲን አትችላትም፡፡ በመሆኑም ዳለቲ ከእናቷ አፍ ድርቆሹን የነጠቀችውን “ጄብሎ”ን ታባርርና ለራሷ መብላት ትጀምራለች፡፡ ይሄኔ ግን የድርቆሹ የመጀመሪያ ባለቤት የሆነችው “ጋሬ” ከተፍ ትላለች! ምክንያቱም እርሷ ጄብሎን ባትችላትም ቀንዳ አልባ ለሆነችው ዳለቲ ትበረታለችና! እናም ከጅምሩ ለርሷ የተሰጠውን ድርቆሽ ያስመለሰችው “ጋሬ” ዘና ብላ መመገብ ትጀምራለች፡፡ ይሁንና ምንም ያህል ሳይቆይ “ጄብሎ” እንደገና ከተፍ ትልና እንደለመደችው “ጋሬ”ን በማባረር ድርቆሹን መብላት ትጀምራለች፡፡ አንድ ጊዜ ያህል ዋጥ ካደረገች በኋላ ግን “ዳለቲ” ከተፍ ትልና ድርቆሹን ትነጥቃታለች፡፡ “ዳለቲ” መብላት ስትጀምር ደግሞ እንደገና “ጋሬ” ትመጣለች፡፡ እንደገና “ጄብሎ”፤ እንደገና “ዳለቲ”፤ እንደገና “ጋሬ”!
አክስቴ ለሶስቱ ከብቶች በተለያየ ቦታ ድርቆሽ ብታስቀምጥላቸው እንኳ ላሞቹ ጥላቸውን አይተውም፡፡ አንደኛው ከብት ለርሱ የተሰጠውን ከማላመጥ ይልቅ ሌላኛውን ነጥቆ መብላቱ ያስደስተዋል፡፡ ስለዚህ አክስቴ የከብቶቹን ጥል ለማስቀረት ሌላ ዘዴ ፈጠረች፡፡ ላሞቹ ከማደሪያቸው ሳይፈቱ ድርቆሽና ውሃቸውን መስጠት!! በዚህ ዘዴ ሁሉም ተስተካከለ፡፡ ሆኖም አንዳንዴ አክስቴ በቤቷ በሌለችበት ጊዜ የአክስቴ ልጆች የሶስቱን ከብቶች ጥል ለማየት ሲሉ ብቻ መመሪያውን እየጣሱ ከብቶቹን ይፈቷቸው ነበር፡፡ እናም ጋሬ፣ ዳለቲ እና ጄብሎ ለረጃ እና ለድርቆሽ ሲሉ እየተቁነጠነጡ ውጊያ ይገጥማሉ፡፡

ይህ የሶስቱ ላሞች ጥል ለረጅም ጊዜ ሲገርመኝ ነበር፡፡ አንዱ ከብት አንደኛውን ብቻ ይችለዋል፤ ሌላኛውን ለማባረር ግን ወኔ የለውም፡፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው እንዴት ነው…? ሁለቱንም ላሞች የወለደችው “ጋሬ” ሌሎቹን ማሸነፍ ያልቻለችበት ምክንያትስ ምንድነው…? ቀንድ ያላት “ጄብሎ” ቀንድ አልባዋን “ዳለቲ”ን የምትፈራበት ምክንያትስ ምንድን ነበር….?

መልሱን በጭራሽ አላውቀውም!! ይሁንና በኋለኛው ህይወቴ ተመሳሳይ አጋጣሚዎችን በማይበት ጊዜ ሁሉ የነዚያ ከብቶች ጥል ወደ አዕምሮዬ ይመጣል፡፡
*
የአዴ” (አክስቴ) ከብቶች የሚጠሩባቸው ስሞች ከአዮ አሚናም ይበልጥ ያስገርማሉ፡፡ ለምሳሌ ከላይ የጠቀስኳት “ጋሬ”ን እና “ጋሬ” የወለደቻቸውን ብቻ በስም ላስተዋውቃችሁ፡፡

በሀረርጌ ኦሮሞ ባህል መሰረት “ጋሬ” የሚባለው ሰውነቱ በጥቁር ወይም ቀይ ቆዳ ተሸፍኖ በጭንቅላቱ ላይ ብቻ ነጭ የሆነ ከብት ነው፡፡ “ጋሬ” ግን ሙሉ በሙሉ ቀይ ነበረች፡፡ በዚህ ረገድ ከሌሎች ጋሬዎች ሁሉ የተለየችው እርሷ ብቻ ነበረች፡፡ አክስቴ ለምን ከህዝቡ ልማድ ውጪ ለላሚቱ “ጋሬ” የሚል ስም እንዳወጣች ስጠይቃት “ጋሬ የእናቷ ስም ነበር፤ እናቷን በጣም እወዳት ነበር፤ ብዙ ወተት ያለስስት የሰጠችኝ ላም ናት፤ ነገር ግን የአባ ጎርባ በሽታ ገደለብኝ፤ ስለዚህ እርሷን ለማስታወስ ብዬ ለልጇ “ጋሬ” የሚል ስም አወጣሁ” አለችኝ፡፡
(ከላይ ካለው ጽሑፍ የቀጠለ)
----
“ጋሬ” የወለደቻት የመጀመሪያ ከብት “ቤጆ” ትባላለች፡፡ “ፔጆ 404” የምትባለው የቤት መኪና “ፋሽን” በነበረችበት ዘመን ስለተወለደች ነው እንዲህ ተብላ የተጠራችው፡፡ ሁለተኛዋ ቀንድ አልባዋ “ዳለቲ” ናት፡፡ ይህችኛዋ በቀለሟ “ዳለቻ” ስለነበረች ነው እንዲያ የተባለችው፡፡ ሶስተኛዋ “ጄብሎ” ናት፡፡ አክስቴ ስሙን ከየት እንዳመጣችው አላውቅም፡፡ ሆኖም ወደ ከተማ መጥታ “ጀብሎ” የሚባሉ ሲጋራ አዟሪዎችን ካየች በኋላ ስሙን ለከብቷ እንዳወጣችው እጠረጥራለሁ፡፡ አራተኛው “ሌንጮ” ይባላል፡፡ ይህኛው ወይፈን ነው፡፡ “ሌንጮ” በልጅነቱ የተለየ ስም የነበረው አይመስለኝም፡፡ በሂደት ግን የሰፈሩን በሬዎች እየገጠመ ስላሸነፋቸው “ሌንጮ” የሚለውን ስም አግኝቷል (“ሌንጮ” በአማርኛ “አንበሳው” እንደማለት ነው)፡፡

አምስተኛዋ “ዲምቱ” ትባላለች፡፡ “ቀዮ” እንደማለት ነው፡፡ ይህቺኛዋ “ኦነግ እና ኢህአዴግ በአንድ ቀን ጦርነት” በሚል ርዕስ በተጻፈው ተከታታይ ጽሑፍ ውስጥ ያስተዋወቅኳችሁ ላም ናት፡፡ በዕለቱ በግቢው ከነበሩት ከብቶች መካከል በጥይት ተመትታ ለመሞት የበቃችው እርሷ ብቻ ናት፡፡ ስድስተኛዋ አንዲት ብስል ቀይ ጥጃ ናት፡፡ ይህቺኛዋ “ደሃቦ” የሚል ስም የነበራት ሲሆን ስሙን የሰጣት ደግሞ በወቅቱ ከብቶቹን ያግድ የነበረው “ሙሐመድ አሕመድ” (ነጋሺ) የተባለው የአክስቴ ልጅ ነው፡፡ ሆኖም በዚህ ስም ላይ ከባድ ውዝግብ ተቀስቅሷል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡
ስያሜው በቅድሚያ የተሰጠው ከቢር ያሕያ የተባለ የአክስቴ ጎረቤት ለወለዳት አንዲት ቀይ ልጅ ነው፡፡ መሐመድ አሕመድ ግን ስሙ በጣም ደስ አሰኘውና በዚያው ሰሞን “ጋሬ” ለወለደቻት ጥጃ ሸለማት፡፡ የከቢር ያሕያ ሚስት ይህንን ስትሰማ ተቆጣች!! “እንዴት በልጄ ስም ከብቱን ይጠራል?” በማለት መንደሩን ቀወጠችው፡፡ መሐመድ አሕመድ ጥጃዋን በዚያ ስም መጥራቱን እንዲተው ቢነገረው “እምቢ” አለ፡፡ አክስቴ ብትለምነው፣ ብታስፈራራው፣ ብትገርፈው ልጁ በእምቢታው ጸና፡፡ የከቢር ያህያ ሚስት አክስቴ “ሆን ብላ ያደረገችው ነው” ባይ ሆነች፡፡ አክስቴ ሐቁን ብታስረዳት በጭራሽ አልሰማ አለች፡፡ በመጨረሻም ሽማግሌዎች በነገሩ ገብተው መሐመድን ገሰጹት፡፡ መሐመድም ለጊዜው ግሳጼውን የተቀበለ መሰለ፡፡ ነገር ግን በዚያ ስም ፍቅር ስለተለከፈ አንድ መላ ፈጠረ፡፡ ደሃቦን በአማርኛ መንዝሮ “ወርቄ” በሚል ስልት ጥጃዋን መጥራት ጀመረ፡፡ አማርኛ የማትሰማው የከቢር ያህያ ሚስትም ከቁጣዋ ረገብ አለች፡፡ መሐመድ አሕመድም ለ“ደሃቦ” የነበረውን ፍቅር በ“ወርቄ” በኩል ተወጣ (“ደሃብ” በዐረብኛ ወርቅ ማለት ነው፤ ሶማሊዎች ስሙን ሲያቆላምጡት “ደሃቦ” ይላሉ”)፡፡
-----
እነዚያ በፍቅር እያናወዙ ጎረቤት የሚያጣሉ ከብቶች ዛሬ የሉም፡፡ ወተት “በሽበሽ” የነበረበትን ያንን ደግ ዘመን አልፈን የገጠሩ ህዝብም እንደ ከተሜው ገበያ እየሄደ ወተት በኩባያ ከሚገዛበት ዘመን ላይ ደረስን፡፡ ይህም እንግዲህ ኑሮ ነውና “አልሓምዱሊላህ” እንላለን፡፡

በነገራችን ላይ "አዮ አሚና" አሁን በሕይወት የለችም። ይህንን ጽሑፍ ከጻፍኩ በኋላ በጥር ወር 2010 አርፋለች። አላህ ይርሓማት። "አዴ" ግን ዛሬም አለች። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ድሬ ዳዋ ከከተመው ልጇ ዘንድ እየኖረች ነው። ረጅም ዕድሜ ይስጣት።
እኛንም ቸር ያቆየን!
-----
አፈንዲ ሙተቂ
ጥቅምት 30/2008 ተጻፈ።
ገለምሶ- ምዕራብ ሀረርጌ

@wegoch
@wegoch
@paappii
.. አስደሳች ጨዋታዎች

(ከተስፋዬ ገብረአብ )
-------
ተስፋዬ ገብረ-አብ “በጋዜጠኛው ማስታወሻ” በርካታ ፖለቲካ-ነክ ወጎችን አውግቶናል፡፡ እኔ እዚህ የምጽፍላችሁ ግን ፖለቲካውን ሳይሆን ተደጋግመው ቢነገሩ የማይሰለቹ ሌሎች ጨዋታዎቹን ነው፡፡ (እኒህን ጨዋታዎች የቀዳሁት ከዚያው መጽሐፍ ነው)፡፡

===አቶ ፍሬው ለምለም እና የቼክ እደላው===

አቶ ፍሬው ለምለም ደግ አዛውንት ነበሩ፡፡ የብሄራዊ ሎተሪ ተጠባባቂ ስራ አስኪያጅ ሆነው የተመደቡ ሰሞን እንደ አንበጣ ወረርናቸው፡፡ የመንግሥትና የኢህአዴግ ሚዲያዎች ሁሉ ማስታወቂያ ይሰጡአቸው ዘንድ የሽያጭ ወኪሎቻቸውን ላኩባቸው፡፡ ከቴሌቪዥን፣ ከሬድዮ፣ ከአዲስ ዘመንና ከበሪሳ ጋዜጦች ለመጡት ሁሉ ይሉኝታ ይዞአቸው ቼክ ፈረሙ፡፡ ቀጥሎም “አብዮታዊ ዲሞክራሲ” ጋዜጣ መጣ፡፡ እምቢ ማለት አልቻሉም፡፡ የሾማቸው ኢህአዴግ ነውና ቼክ ፈረሙ፡፡ ከ“ማህቶት” ጋዜጣ ለመጣው ግን ላለመስጠት አንገራግረው ነበር፡፡ “በአማራው ክልል ዋና የሎተሪ ደንበኞች ዘንድ እንደርሳለን” እያለ ሲለፈልፍባቸው ለመገላገል ብለው ቼኩን ፈረሙ፡፡ በነጋታው የኦሮሚያ ጋዜጣ ወኪል መጣ፡፡ “ለአማራው ፈርመህ ለኦሮሞ ያልፈረምከው ነፍጠኛ ስለሆንክ ነው” እንዳይባሉ ቼክ ፈረሙ፡፡ ከደቡብና ከትግራይ መጡባቸው፡፡ ከነገር ለመሸሽና ላለመነካካት ሲሉ ፈረሙላቸው፡፡ በመጨረሻም እኛ ሄድን-ከእፎይታ መጽሔት፡፡ ዐርብ ጠዋት የሽያጭ ሰራተኛውን አስከትዬ ከቢሮአቸው ስገባ ግስላ ሆነው ጠበቁኝ፡፡

“ምን ፈለጋችሁ እናንተ ደ’ሞ?!” ሲሉ ጮኹ፡፡ “አታፍሩም እንዴ? ፍሬው ለምለም እንደ ጠበል ጠዲቅ ገንዘብ እየመዠረጠ ይሰጣል ያላችሁ ማን ነው? ምንጣፉንም ጠቅልሉትና ውሰዱታ! ጠረጴዛውንም ጫኑ! እሱ ነው የቀራችሁ:: ነውር አይደለም እንዴ?”
ካረጋጋናቸው በኋላ ሳምንቱን በሙሉ የደረሰባቸውን አጫውተውን ሲያበቁ እንዲህ አሉ፡፡
“እስኪ ይሁን እንግዲህ… ዳግመኛ አትምጡብኝ እንጂ ለዛሬው ባዶ እጃችሁን አልመልሳችሁም”::

===መለስ እና ደበበ እሸቱ===

እውቁ ተዋናይ ደበበ እሸቱ በምርጫ-97 ተወዳድሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡ እናም ጠ/ሚ/ መለስ እንዲህ ተጠይቀው ነበር አሉ፡፡

ጋዜጠኛ፡ ኢህአዴግ በምርጫው ድራማ ሰርቷል ይባላል፡፡ እውነት በምርጫው ድራማ ተሰርቶ ነበር እንዴ?
ጠ/ሚ/ መለስ፡ የተሰራ ድራማ የለም፡፡ ምናልባት በምርጫው ደበበ እሸቱ ስለተሳተፈ ድራማ የመሰላቸው ካሉ ተሳስተዋል”፡፡

(ሆኖም ይህቺ የድረ-ገጾች ፈጠራ ናት ይለናል- ተስፋዬ ገብረ አብ)

===ስብሐትና ቦነስ===

ለጋሽ ስብሐት ገብረ እግዚአብሄር ለስድስት ዓመታት ያህል አለቃው ሆኜ ብንሰራም በአንዳንድ ነገሮች ላይ እርሱ ነበር የሚያዘኝ፡፡ አንድ ቀን እንዲህ ሲል ጠይቆኛል፡፡
“ላማክርህ ነበር የመጣሁት”
“እሺ ጋሽ ስብሐት ምን ነበር?”
“ገንዘብ ቸግሮኛል”
ዝም አልኩ፡፡ ምክንያቱም የመጪዎቹን ሁለት ወራት ደመወዙን ከወዲሁ ወስዶ ነበርና ምን እንደማደርግ ግራ ሊገባኝ ጀምሮ ነበር፡፡ እሱም ይህንን ተገንዝቦ ኖሮ ፈጥኖ ንግግሩን ቀጠለ፡፡
“ደመወዜን ቀድመህ ስጠኝ ልልህ አልችልም፡፡ ወስጄዋለሁና፡፡ አሁን ሳስብበት ቆየሁና አንድ ሌላ ዘዴ መጣልኝ፡፡
“ምን ዘዴ አገኘህ ጋሽ ስብሐት?”
“ታታሪ ሰራተኛ በሚል ለምን ቦነስ አትሰጠኝም?”

===ፈረሰኛው ባህሩ===

የግንቦት ሀያ አንደኛ ዓመት በዓል እየተከበረ ነው፡፡ ብዙ ህዝብ በመስቀል አደባባይ ታድሞአል፡፡ ሁሉም እንደ አቅሙ ሸልሏል፡፡ ከዚያ ህዝብ መሀል አንድ ፈረሰኛ አባት ትኩረቴን ሳቡት፡፡ ፈረሳቸው ተንቆጥቁጧል፡፡ እሳቸውም ፈረሳቸውን መስለዋል፡፡ እኒህ ሽማግሌ ያቅራራሉ፡፡ ጃሎታውን ያስነኩታል፡፡ ምናልባት ደርግ ብዙ ጋሻ መሬት የወረሰባቸው ይሆን? ወደርሳቸው ቀርቤ ምክንያቱን ብጠይቅ የተሻለ ነው በማለት ለቃለ መጠይቅ ጋበዝኳቸው፡፡
“አባት ስምዎትን ማን ልበል?”
“ባህሩ ከበደ”
“አቶ ባህሩ ዛሬ እንዲህ አምረው በሰንጋ ፈረስዎ እየጋለቡ ወደዚህ አደባባይ የመጡት ለምንድነው?”
“እኔ ከኃይለ ስላሴ ዘመን ጀምሮ፣ በደርግም ጭምር፣ አሁን ወያኔ ከመጣ ወዲህም ሰልፍ የሚባል አምልጦኝ አያውቅም፤ ሰልፍ አለ ከተባለ የክት ልብሴን ለብሼ ሰንጋ ፈረሴን ጭኜ ከተፍ ነው”

===ወይዘሮ ኢትዮጵያ===

ደርባን በምትባል ከተማ ላይ የተዋወቅኩት ኤርትራዊ ጋዜጠኛ ያጫወተኝ ነው፡፡
ኤርትራ የነጻነት በዓሏን እያከበረች ነው። ህዝቡ በሳባ ስታድየም ታድሟል። ወታደሮች የሰልፍ ትርኢት ያሳያሉ። እናቶች ሹሩባ ተሰርተው በእልልታና በእስክስታ ክብረ በዓሉን አድምቀውታል። ኤርትራዊው ጋዜጠኛም የአንድ ደማም ኤርትራዊት እናት የእስክስታ አወራረድ ስለማረከው ለቃለ መጠይቅ ጋበዛቸው።
“እናት! እንኳን ደስ አለዎት”
“እንኳን አብሮ ደስ አለን፡፡ ኤርትራ ሀገራችን ከኢትዮጵያ አገዛዝ ነጻ በመውጣቷ ደስ ብሎናል፡፡ የዛሬዋ ዕለት የልደት ቀናችን ናት”
“ስምዎትን ማን ልበል?”
“ወይዘሮ ኢትዮጵያ እባላለሁ”
-------
(ተስፋዬ ገብረ አብ፣ የጋዜጠኛው ማስታወሻ፣ 2001/2009 G.C.)

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Afendi mutaki
እማሆይ ረታ ነጠረች_ ቅዱስ_አርዮስ
<unknown>
እማሆይ ረታ ነጠረች

ተራኪ
ቅዱስ አርዮስ ና ዳናዊት

ፅሁፍ አርዮሱ


@wegoch
@wegoch
@paappii
አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #7

“ምን አድርጎት ነው የገደለው?” ነበር ያለችኝ።

በየትኛው ቃል፣ በየትኛው ዓረፍተ ነገር፣ በየትኛው ሰዓት፣ የት ቦታ ፣ እንዴት እንደምነግራት ስጨነቅ እና ሳምጥ ቀናት ካለፉ በኋላ ለልጄ ስለአባቷ ስነግራት!! ያልጠበቅኩት ምላሽ ስለነበር ፈራኋት። ምናልባት በጣም ደንግጣ ይሆን ምንም ዓይነት መረበሽ ያላሳየችኝ?

“የእኔ ልጅ ሁሉንም በአንዴ ስደራርብሽ ይበዛብሽል። ሌላ ጊዜ ደግሞ ነገሮችን በሰከነ ጭንቅላት ሆነን እነግርሻለሁ። አንድ ነገር ግን በእርግጠኝነት ልንገርሽ አባትሽ መጥፎ ሰው አይደለም!” አልኳት

“እማ እኔ እንደምታስቢው ህፃን ልጅ አይደለሁም! ስለአባቴ እውነቱን የነገርሽኝ ትችለዋለች ብለሽ ስላመንሽብኝ አይደል? ከነገርሽኝ አይቀር ሁሉንም ማወቅ እፈልጋለሁ። እና ደግሞ እንኳንም ነገርሽኝ!” ብላ ጉንጬን ሳመችኝ። ከኔ በተሻለ ነገሩን በእርጋታ የተቀበለችበት መንገድ ጤነኝነት እስከማይመስለኝ ድረስ ተገረምኩ። ዝም ማለቴን ስታይ ቀጠል አድርጋ

“ቆይ በህይወቴ ሁሉ ጭራሽ ያልነበረ አባቴ ድንገት እስር ቤት እንደሆነ ከማወቅ ያውም ሰው ገድሎ፣ እናቴን ትቶ ሌላ አግብቶ የወለደው ወንድም እንዳለኝ ከማወቅ የባሰ አለው? የለውም እኮ እማ! ንገሪኝ ሁሉንም!!” እውነቷን ነው የባሰ የለውም!

“የለውም!” አልኳት እንዲህ መብሰሏ እየገረመኝ

“ንገሪኛ! ምን አድርጎት ነው የገደለው?”

“የአባትሽን ህይወት ያበላሸበት ሰው ነው። የእሱን ብቻም አይደለም። የባባን እናትም ህይወት ያበላሸ ሰው ነው። አባትሽ ያልኖረውን ህይወት ስኬታማ ሆኖ በመበቀል የሚያምን ሰው ነበር። በትምህርቱም ጎበዝ ተማሪ ነበር። ጥሩ ውጤት አምጥቶ ተምሮ ስራ ይዞ አግብቶ ወልዶ የሚኖርለት ቤተሰብ እንዲኖረው ነበር ምኞቱ። ስሙን ረስቼዋለሁ ……… ሟች ….. አብሯቸው ማሳደጊያ የነበረ ልጅ ነበር። በባህሪው ባለጌ በጉልበት የሚያምን ነበር። የባባን እናት ፍቅረኛዬ ካልሆንሽ ብሎ ያስቸግራት ነበር። የሆነ ቀን አባትሽ ‘ተዋት አትፈልግህም!’ ስላለው ይጣላሉ። ይደባደባሉ። የዛን እለት ማታ አባትሽ ወደማደሪያው ሲመለስ ሎከሩ ውስጥ መጠኑ ብዙ የሆነ አደንዛዥ እፅ በጥቆማ ተገኝቶበት ተከሰሰ። የአስራሁለተኛ ክፍል ትምህርቱን ሊጨርስ አንድ ዓመት ነበር የቀረው። ከዛ በፊት በጥሩ ስነምግባር : ልጆችን በማስጠናት : በቅን ልብ የሚታወቅ ልጅ በመሆኑ ቅጣቱ ቀሎለት 1 ዓመት ነበር የተፈረደበት። ከዛ ግን ህይወት ከቆመችበት አልቀጠለችለትም። እሱ ባልነበረበት ጊዜ ይሄው ልጅ የባባን እናት አታሎ ከጊቢ ውጪ አስጠርቶ ደፈራት። ለማንም መንገር ፈርታ ለአባትሽ የተፈጠረውን ነግራው ማሳደጊያውን ጥላ ጠፍታ አረብ ሀገር ሄደች። አባትሽ ከራሱ መታሰርና ህይወቱ እንደቀድሞ ካለመሆኑ በላይ እርሷን ሊጠብቃት ያለመቻሉ እኔ እስከማውቀው ድረስ ይጠዘጥዘው ነበር። አቅመ ቢስነት ይሰማው ነበር።”

“አባቴና እሷ ያኔ ፍቅረኛሞች ነበሩ? “

“እሱ እንደነገረኝ ከሆነ አልነበሩም። እንደእህትና ወንድም ነበር የሚጠባበቁት። ካምፑ ውስጥ ከነበሩ ልጆች በሙሉ ሁለቱ በተለየ ይቀራረቡና ይጠባበቁ ነበር። እንደታናሽ እህቱ ይሳሳላት እንደነበር ነው የነገረኝ።”

“እሺ ከዛስ?”

“ከዛ አባትሽ ቅጣቱን ጨርሶ ሲወጣ እሷም የለችም። ልጁም በህገወጥ መንገድ ከሀገር ወጥቷል። ከመታሰሩ በላይ ከፍተኛው ቅጣት ወደማሳደጊያ ጣቢያው መመለስ እንዳይችል የተጣለበት ማዕቀብ ነበር። ከዛ ጊቢ ውጪ ሰውም ህይወትም አልነበረውም። የትም ሆኖ ትምህርቱን መቀጠል አይችልም ነበር። ስራ እንኳን ለመቀጠር ተያዥ የሚሆነው ሰው የለውም ነበር። ብቻ እስር ቤት በነበረበት ጊዜ ተምሮ በነበረው የእጅ ሙያ አንድ ፈርኒቸር ቤት ስራ እስኪያገኝ ድረስ ብዙ አስከፊ ህይወት አሳልፏል።”

“እና ሰውየውን በመግደሉ ልክ ነው ብለሽ ነው የምታስቢው?” አለችኝ

“ልክ ነው ብዬ አላስብም ። አንዳንዴ ግን ሰዎች ሁሉ ልክ ያልሆነ ነገር እናደርጋለን። አባትሽ ያደረገው ልክ ባይሆንም። ያደረገበትን ምክንያት ግን በመጠኑም ቢሆን እረዳለሁ።”

“ትጠይዋለሽ? ማለቴ አባቴን ትጠይዋለሽ? ሰው በመግደሉ ሳይሆን አንቺን ባደረገሽ ነገር?”

“አልጠላውም የእኔ ልጅ!! ግን ተቀይሜዋለሁ። በጣም ብዙ ተቀይሜዋለሁ። ጥላቻ ሳይሆን መከፋት! ቅያሜ ነው ያለኝ!! ብዙ ቅያሜ!!”

“ይቅርታ ቢልሽስ?”

“ከይቅርታው ይልቅ ያደረገበትን ምክንያት መረዳት ብችል ምናልባት ቅያሜዬን እተወው ይሆናል። አላውቅም! እስከማውቀው ድረስ አባትሽ ያለበቂ ምክንያት ማንንም ሰው ቢሆን የሚጎዳ ነገር የሚያደርግ ሰው አልነበረም! ቢያንስ እኔ እንደዛ ነው የማስበው!”

“ስታገኚው አልጠየቅሽውም?”

“ከእኔ ጥያቄ የሚበልጥ መጎዳት ውስጥ ስለነበር መታገስን መረጥኩ የእኔ ልጅ!”

“አትናደጂም?” አለችኝ የእሷ እድሜ በማይመስል ጠንካራ ድምፀት

“በምኑ?”

“ደግነትሽን እንደጂልነት ሲቆጥሩብሽ? ምንም አድርጎሽ ቢሆን እንደምትረጂው ስለሚያውቅ ለምን ትቶሽ እንደሄደ እንኳን ምክንያቱን ሳይነግርሽ ጥሩነትሽን ይጠቀምበታል። እንቢ እንደማትዪው ያውቃል። ምክንያቱም ክፉ ልብ የለሽም አይደል?” ይሄን ያለችበት መንገድ ጉዳዩ ስለእኔ ብቻ እንዳልሆነ ገባኝ። የሆነ እያለፈችበት ያለ ነገር አለ ማለት ነው። የሆነችው ነገር። ንግግሯ የ15 ዓመት ልጅ ንግግር አይደለም።

“እንደዛ እንዲሰማሽ ያደረገሽ ሰው አለ? መልካምነትሽን እንደጅልነት የቆጠረብሽ ሰው አለ? ደግ ሆነሽለት ብልጥ ሆኖ የተጠቀመብሽ ዓይነት ስሜት እንዲሰማሽ ያደረገሽ ሰው አለ?”

“ብዙ ጊዜ። ጓደኞቼ የምላቸው የሆነ ነገር ከእኔ ሲፈልጉ የሚወዱኝ ይመስላሉ። እያወቅሁ የፈለጉትን የምችለው ከሆነ አድርግላቸዋለሁ። እነሱ ግን የሚመስላቸው የሸወዱኝ ነው።”

“ወይኔ ጉዴ!! መቼ ነው እንደዚህ ያደግሽው? በ15 ዓመት እንዲህ አይበሰልምኮ የእኔ ልጅ?”

“ያንቺ ልጅ አይደለሁ?”

“የውልሽ የእኔ ልጅ! ጥሩ መሆን፣ ለሰዎች ሁሉ ቅን ነገር ማድረግ፣ የቻልሽውን ሁሉ መርዳት ጥሩ ነገር ነው። የሰው ልጅ ሁሉ የሚያጭደው የዘራውን ነውና የዘራሽው ደግነት ባላሰብሽው መንገድ ጎተራሽን ሞልቶ ታገኚዋለሽ!! ያ ማለት ግን ቅን ልብሽን ተጠቅመው ባገኙት አጋጣሚ ሊጠቀሙብሽ ለሚፈልጉ ብልጥ ነን ብለው ለሚያስቡ ከንቱዎች ሁሌ መጠቀሚያ መሆን አለብሽ ማለት አይደለም። ዝምታ የሚገባው ብልህ ሰው ብቻ ነው። አንዳንዱ ሰው ከንቱነቱ ሊነገረው ይገባል። ለራስሽ ቁሚ! ‘እስከዛሬ ዝም ያልኩህ እንደእኔ ጥሩነት እንጂ እንዳንተ ከንቱነት አይደለም’ ማለት አለብሽ” ስላት ድክም ብላ ትስቃለች። ለዛሬ ንግግራችንን የጨረስን መሰለኝ። ውስጤ ሽጉጥ ብላ

“እወድሻለሁ እኮ! ምርጥዬ እናት ነሽ! እንዳንቺ ዓይነት እናት ባትኖረኝ እኔም ከከንቱዎቹ አንዷ እሆን ነበር።” አለችኝ

በሳል እንደሆነች ድሮም አውቃለሁ። ዛሬ ግን ከአዕምሮዬ በላይ ሆነችብኝ። እኔ በሷ እድሜ አባዬ እና እማዬ ሲጨቃጨቁ ሰምቼ እናትና አባቴ ተጣሉ ብዬ እንደ ተዓምር ለማቲና ለአቢ እያለቀስኩ መናገሬን አስታውሳለሁ። በእኛ ፊት አያደርጉትም እንጂ ለብቻቸው ሲሆኑ እንደማንኛውም ባለትዳር የሚጨቃጨቁበት ጉዳይ ሊኖራቸው እንደሚችል የገባኝ መቼ እንደሆነ እንኳን እንጃ ...... እሷ ከእኔ ተሽላ በእርጋታ ነገሮችን የተቀበለችበት መንገድ እየቆየ 'ሆ'ያስብለኝ ገባ።
ለተወሰኑ ቀናት ነገሮች እንደዛው ባሉበት ቀጠሉ። ልጄ ምንም እንኳን ስለአባቷ ያለውን ነገር ብትቀበልም ለጊዜው ልታገኘው እንደማትፈልግ አስረግጣ ነገረችኝ። እኔ ግን ላገኘው እፈልጋለሁ!! አሁንም የቀረኝ ነገር እንዳለ ነው የሚሰማኝ!! ባገኘው ፣ የሄለንን ያህል እንኳን ወዶኝ ባይሆን አብረን ያሳለፍነው ጊዜ በልቡ ውስጥ የሆነ ቦታ እንደነበረው ማወቅ ከሆነ መታሰሬ የሚፈታኝ ነገር ይመስለኛል። ለልጄ ያልኳት ከልቤ ነው። ይቅርታ እንዲለኝ አይደለም መሻቴ ምክንያቱ እኔን ትቶ ለመሄድ ውሃ ያነሳ እንደነበር ነው ማወቅ የምፈልገው። በሌላ ቋንቋ እሱጋ የነበረኝን ዋጋ ነው ማወቅ የፈለግኩት።

በቻልኩት አጋጣሚ እና ጊዜ የባባን እናት እየሄድኩ አያታለሁ። ምንም ለውጥ የላትም። እነግሩም የህክምና ወጪዋን እየሸፈኑ ቢሆንም ከዛ ባለፈ የተነጋገርነው ነገር የለም። ምንም ከመወሰኔ በፊት ሄለን ብትነቃ ውሳኔውን ለሷ ለመስጠት ፈልጌ ይመስለኛል በዝምታ ቀናት ያስቆጠርኩት።

አሸናፊ ለባባ ስለእናቱ እንዳልነግረው ቢነግረኝም ያን ማድረጉ ልክ መስሎ ስላልታየኝ ለባባ በእድሜው ሊገባው በሚችል መልኩ እናቱ ለጊዜው መታመሟን ነግሬው የተወሰነ ቀንም ይዤው ሄጄ አሳይቼዋለሁ። ምናልባት እሷ ብታልፍ እንኳን ዋሽቼው ልጄ አላደርገውም። እናቱ እንደሞተች አውቆ ከልጄ ለይቼ የማላየው እናቱ እንደሆንኩ አሳየዋለሁ። እናት እሆነዋለሁ!! የማትዋሸው እናት!! መጀመሪያ የወሰድኩት ቀን እንድትነቃለት ስሟን እየጠራ ሲያለቅስ እንደህፃን አብሬው አልቅሻለሁ!! የዛን ቀን እንቅልፉን ተኝቶ ሁሉ እየቃዠ ይጠራት ነበር። አልጋዬ ላይ አምጥቼው አጠገቤ አስተኝቼው በጭንቀት እና በላብ የተጠመቀ ትንሽዬ ፊቱን እያየሁት ለረዥም ሰዓት እንቅልፍ አልወሰደኝም። እቅፌ ውስጥ ሲሆን እንደምጠብቀው ልቡ ነግሮት ነው መሰለኝ ለጥ ብሎ ተኛ!!

ከተከታዮቹ ቀን በአንዱ ከስራ ተመልሼ ከልጄ እና ከባባ ጋር መክሰሳችንን እየበላን በሬ ተንኳኳ። የግሩም እናት ነበሩ። ከመጀመሪያው ቀን በኋላ አይቻቸው ስለማላውቅ እየገረመኝ ወደውስጥ እንዲገቡ ጋበዛኳቸው።

"ላናግርሽ ፈልጌ ነበር። በልጆቹ ፊት ባይሆን ጥሩ ነው!" አሉኝ ወንበሩ ላይ እየተቀመጡ። ልጄ እኔ ምንም ከማለቴ በፊት ባባን ይዛው ወደክፍሏ ሄደች።

"ምንድነው ሀሳብሽ? ውሳኔሽን ማወቅ እፈልጋለሁ! ልጄ ከዛ ቀን በኋላ ተረጋግቶ ምንም ነገር ማድረግ አልቻለም! ስራውን እንኳን በትክክል እየሰራ አይደለም! እሱ ዓመት ሙሉ ዝም ብትዪም እንደማይጠይቅሽ ስለማውቅ ነው ራሴ የመጣሁት! እየሆነ ያለው ነገር ምንም አልገባኝም! 'እሷ ለራሷም አልተረጋጋችም!' ይለኛል እሱ። መቼ ነው የምትረጋጊው? አንቺ እስክትረጋጊ ከዛሬ ነገ ፖሊስ መጥቶ በሬን አንኳኳ : ልጄን ወሰደብኝ እያልኩ መሳቀቅ ገደለኝ" አሉኝ ያነገቱትን ቦርሳ እንኳን ከትከሻቸው ሳያወርዱ

ይቀጥላል .......

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
2024/09/23 05:20:53
Back to Top
HTML Embed Code: