Telegram Web Link
ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው!!
ክፍል 12
(የመጨረሻ ክፍል)

ጉንጬን ከነደሜ አንገቴን ይስመዋል። ከሰከንድ በፊት 'ምንዓይነቱ ነው?' ሲሉ የነበሩት 'ምፅ ምፅ ሲያሳዝን' አላሉም? በዚህ መሃል ማን መጣ ያ ያባለገኝ ልጅ ባልየው ልክ ሲያየው አወቀው መሰለኝ እኔን እንዳይለቅ እኔ ሆንኩበት ዝም እንዳይል እሱ ሆነበት። በቃ ቆንጆ ቲያትር ተፈጠረ።

"አንተ እናትህ ..... አገኝሃለሁ!!" ያኛው ለራሱ አንድ ሁለት ብሏል መደንፋት።

"ማነኝ ነው የምትለው?" የነበረው ተማሪ የተፈጠረው ሳይገባው ያኛውን ይይዛል ይመስለኛል። እኔ ለራሴ ምንም እንዳልል ልሳን ላይ ነኝ የባሌንና የልጁን ድምፅም መለየት እራሱ እየቸገረኝ ነበር። ፖሊስ መጥቶ እኔ ወደሆስፒታል እሱ ወደፖሊስ ጣቢያ ሄድን። አይኔ ስር ስቲች ተደረግኩ። (ይሄ ምልክት አሁንም ድረስ አይኔ ስር አለ። አዳሜ እየገባሽ ፎቶዬን ዙም አድርጊ አሉሽ!)

እና ከዚህ በኋላ ፍቅር ተወለደ ነው የምትዪው? አላችሁኣ? ግድ የላችሁም እንቀጥል። እኔኮ የብዙ ሰው ህይወት የኖርኩ ነው የሚመስለኝ የምላችሁ ለዚህ ነው።

በነገታው ማሚ እኔጋ ስትደውል ስልኬን አላነሳሁላትም አንድ ጓደኛዬጋ ስትደውል የተፈጠረውን ነገረቻት። እኔ መስማቷን እንኳን ከማወቄ ማሚ መጥታለች። ማታ አሳድረውት ፖሊሶቹ ለቀውት ነበር እሱን። ማሚ ቀወጠችው። ሴቶች ጉዳይም አይደለች? ደዋወለች። አሳሰረችው። እኔጋ ስትመጣ ግን ከፍቷት ነው የደረሰችው።

"ምነው?" ስላት

"ባልሽ ምን እንዳለኝ ታውቂያለሽ? "

"ምን አለሽ?" (ምንም ቢል የምገረም ይመስል)

ልጄን ይገድላታል ብላ ስትቀውጠው። "ሞታም ቢሆን ዘግይተሽ ነው የደረስሽውኮ ታዲያ አንቺ አታስጥያትም ማሚ በሷና በኔ መሃከል አትግቢ!" ብሏት ነው የምትብሰከሰከው። ትምህርት ቤት በዶርሜም አካባቢ ሆነ በክላሴ አካባቢ ብቻ እኔ ባለሁበት አቅራቢያ እንዳይገኝ ታገደ እና ከቀንት በኋላ ተለቀቀ። ሁሉም እንደነበረ ቀጠለ። ማሚም ተመለሰች። እኔም ትምህርቴን ቀጠልኩ። ከዛ ልጅጋም እንደነበረ (ምን እንደነበረ መድሃንያለም ይወቀው ) የነበረውን ቀጠልን። የሆነ ቀን ስልክ ደወልኩለት ለልጁ

"ና በናትህ ወክ እናድርግ!" አልኩት ስልኩን እንዳነሳ

"ገምቺ የት እንደሆንኩ?"

"እኔንጃ የት ትሆናለህ? መሽቷልኮ!"

"እቤትሽ ከባልሽ ጋር !" ቀልድም መሰለኝ።

"አንተ በማይቀለድ ነገር አትቀልድ!"

"እግዚአብሄርን የምሬን ነው።" ጠላታችሁ ክው ይበል። (አሁንም እማጅኑልኝ ያባለግኩት ልጅና ባሌን አንድ ቤት።)

"ይገድልሃል!! እየቀለድኩ አይደለም ይገድልሃል!" አልኩት

"እየጠበቅኩት ነው!.... ተፋጠን ነው ዛሬ የምናድረው!! ነገ ጊቢ ስመጣ ደውልልሻለሁ።" ይለኛል እየሳቀ

"እኔ አንተን ብሆን እዛች ቤት አላድርም።"
ስልኩን ዘግቼው ምን ማሰብ እንዳለብኝ ግራ ገባኝ። ምንድነው ሁለቱን አንድ ቤት የሚያሳድራቸው? ወይ አንደኛው አጋች አንደኛው ታጋች ሆነው ካልሆነ በቀደም እኔ እየደማው እናቶቻቸውን በብልግና ሲቀባበሉ የነበሩ ሰዎች አንድ ቤት ማደር? ይሄ በዓለምም የትኛው ልብ ወለድ ውስጥም የለም። ይሄ የተከሰተው እኔ ቤት ብቻ ነው። እንደ ቅዠትም እንደዱካክም እንደመባነንም እንልክፍትም ሲያደርገኝ አደርኩ።

በነገታው እንዳለውም ደወለልኝ። የምናወራው ጉዳይ አለ ብሎኝ ተያይዘን ፀጥ ያለቦታ ሄድን። ከትናንት ወዲያ ነገር ይኸው ራሱ ጉድ ወድጄሻለሁ ብሎኝ ነበርኮ ዛሬ መጥቶ "ከባልሽ ጋር ታረቂ!" ብሎኝ እርፍ!! ለልብወለድነት ሁላ አይሆንም አላልኳችሁም? የእውነት ዞረብኝ! ተጋድለው እሁድ ፖሊስ ፕሮግራም ላይ ቀርቤ "ሁለቱንምኮ እወዳቸው ነበር .... ጌታ ለእኔ ባይላቸው ነው ..... ፎሊስ ምን ታደርገዋለህ? " ምናምን ብዬ ቃሌን ሰጠሁ ስል አጅሬዎቹ ፍቅር በፍቅር ሆነው አይዞህ ሲባባሉብኝ ነው ያደሩት!

"ማንም ሰው እንዲህ አይወድም ሜሪዬ ግፍ ነው። በስመአብ እኔ እንዲህ ዓይነት ፍቅር አይቼ አላውቅም!! የትኛውም ወንድ ወንድነቱን ውጦ ከሚስቱጋ ያለ ወንድ አስታርቀኝ አይልም። የመጨረሻ ይወድሻል።"

"ሚስቱ አይደለሁም! ሚስትህ አይደለችም ስትለው የነበርከው አንተ አይደለህ እንዴ?"

"ለሱ አሁንም የሚወዳት ሚስቱ ነሽ!! ሜዬ አሁን አንቺን አጥቶ መኖር ምን ማለት እንደሆነ በጣም ተምሯልኮ አንድ እድል ስጪው!" በአንድ ለሊት ሚኒ ባሌን ሆኖ ብቅ አለልኝ። ስለሌላ ሰውም እያወራ ወይም እሱም ሌላ ሰው ነው የመሰለኝ ሳቅኩኝ

"በቀደም መስሎኝ በቦክስ ያነጠፈኝ .....ይታይሃል ? ፊቴ ገና አልጎደለም። ተለውጧል? ቆይ ምን ቢልህ ነው?"

"እንዴ እሱማ በቃ ቀንቶ ነው። ደግሞ የዛን ቀን የመጣው እኔን ሊጣላ እንጂ ካንቺጋ ሊጣላ አልነበረም። ከወንድ ጋር ሲያይሽ ደሙ ፈልቶ ነው በዛ ላይ አንቺ አጋጋልሽ! " (ወንዶችኮ ግን አትስማሙ።)

"እ........ሺ?" ደንቆኝ ነው የማየው። "የምልህ ቆይ አንተ በቀደም ወድጄሻለሁ ስትለኝ አልነበር? "

"እግዚአብሄርን ነው የምልሽ እሱ የሚወድሽን እሩቡን አልወድሽም። ደሞ ሀጥያት ነው እንደዛ እየሆነልሽ እያወቅኩ ለራሴ አላዳላም።"

ነግሬአችኋለሁኮ ከኔጋ አብረው ሲያለቅሱ የቆዩ ጓደኞቼ እሱ መጥቶ "እሷ ማለት ለእኔ የህይወቴ ካስማ ብሎ ..." እትት ብትት ሲል በግልምጫ የሚያፈርጡኝ ሰው ነኝ። የሚገርመኝ ያጠፋው እሱ ከሆነ ጥፋቱን አያስተባብልም። የሚናገርበት መንገድ ግን በቃ ለመኮነን አይመችም። የተፈጠረውም እንደዛ ነው። በጉልበት የሚሆን ነገር እንደሌለ ሲገባው ቢያንስ የተሻለ ብሎ ያሰበው መንገድ ይመስለኛል ልጁን ጠርቶ ማናገር ነው። ከዛ ያው ጠርቶ አጥምቆ ላከልኝ። ከቺኩጋ ተጣልቶ ትታው ሄዳለች።

ብቻ ለሌቱን ሙሉ ሲባባሉ ያደሩትን ሲነግረኝ እኛም ልናድር ሆነ። የታሸገ ነገር ሰጥቶኝ ተለያየን። ገብቼ ስከፍተው ቀለበቴ ነበር።

እዚህጋ የተሰማኝን ወይም የሚቀጥለውን እርምጃ እንዴት እንደተራመድኩ ምክንያቴን ልፅፍላችሁ የምሬን አሰብኩትኮ። አላውቅም! ምናልባት እዚህኛው ጊዜ ላይ ቡረቃም ህመምም ስለሌለው ይሆናል ትዝ አይለኝም ምን አስቤ እንደነበር። ኤጭ በሉና ተዘጋጁ አንዴ .......

የሆነ ቀን ልንመረቅ አንድ ወር ሲቀረን ይመስለኛል። እሱም የተወሰነ ኮርስ እየቀረው አብሮኝ ተመራቂ ነበር። ብድግ ብዬ ብቻ ቀለበቴን አደረግኩት። ተነስቼ እቤት ሄድኩ። በቃ ሄድኩ አልኩኮ .......

ምንም እንዳልተፈጠረ...... ይቅርታ የለ ...... መወቃቀስ የለ ....... ልክ ትናንት ተገናኝተን እንደነበር ሁላ ጨዋታ ጀመርን:: ስገባ ሲያየኝ የነበረው ፈንጠዝያ እንዳለ ሆኖ ...... ወላ

"ቺኳ ጎበዝ ናት አንተ ቤቴን አሪፍ አድርጋ ነው የያዘችው!" ሁላ አይነት ወሬ ነበረው። የገዛነውን መሬት እንደሸጠው ነገረኝ ሚስት ሚስት አልሰራራኝም። ይመችህ አልኩት።

"አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው እሱን የወደድሽው ሎቲ የሚያደርግ ወንድ አትወጂም አልነበር?"
(ሲቆይ ጆሮዬን ልበሳልሽ ከወደድሽ ብሎኛልኮ)

"አንተ ግን በጣም ከሳህኮ እህል አታበላህም ነበር እንዴ?" (እኔምኮ ከስቻለሁ ከዛ በላይ የሚከሳ ቀሪ ስጋ ስላልነበረኝ እንጂ)

"በቃ እስክንመረቅ ለምን አብረን አንሆንም?"

"እንዲህኮ ደስ ስንል" ምናምን ተባብለን ወደ ዶርም ተመለስኩ።

ምንም ሳይጨመር ሳይቀነስ በቃ እንዲህ ነው የሆነው። ዶርም ስመለስ ሁሉም ሊበላኝ በጣም የገረመኝ ማሚ ታብዳለች ብዬ ስጠብቃት።

"እንኳን ነገር አበረድሽ ቢያንስ ተረጋግተሽ ተመረቂ! እኔማ በእልህ ከአሁን አሁን የሆነ ነገር አደረጋት ብዬ
ሌት ተቀን አምላኬን ስወተውት ነው የማድረው!" አለችኝ። እንደባልና ሚስት ሳይሆን እንደ ፍቅረኞች ነገር ሆንን ..... ያለፀብ አለቀ እና ልንመረቅ አንድ ቀን ሲቀረን አብረን አደርን!!

በነገታው እነማሚ መጡ ልጃችን ልታስመርቀን መጣች። ተመረቅን!! እንደማንኛውም ተመራቂ ተማሪ ፊታችን እስኪገረጣ ፎቶ ስንነሳ ዋልን!! እንዳሰብኩት በማእረግ ባልመረቅም በሚያኮራ ውጤት ተመረቅኩ። በምወዳቸው ሁሉ ተከብቤ ያ የናፈቅኩት ቀን ሆነ!! በሚቀጥለው ቀን ቤተሰቦቼን ሸኝቼ ዶርም ተመለስኩ። ለማንም ምንም ሳልል እቃዬን ሸካክፌ ወደአዲስ አበባ ......... ለማሚ ያለሁበትን ለማንም እንዳይናገሩ አስጠነቀቅኩ። ብዙም ሳልቆይ የግል ዩንቨርስቲ ማስተማር ስራ ጀመርኩ።

በወሩ ደወልኩለት።

"ማወቅ ስላለብህ ልንገርህ ብዬ ነው። ፍቅርን አርግዣለሁ!" አልኩት። ደስ አለው። እብድ ናት በሉኝ በማርገዜ ደስታዬን ብታዩት። ከእርሱ ውጪ ከሌላ ወንድ ልጅ መውለድ አልፈልግማ!!

"የት ነሽ?" ቦረቀ። "ላግኝሽ? We can fix this eko ልጆቻችንን አብረን እናሳድጋለን አይደል? "

"ልጆቻችንን እናሳድጋለን። እኔና አንተ ግን አንድ ላይ ሆነን አይደለም። ልጅህን መጥተህ እንድታይ ስወልድ አሳውቅሃለሁ። በልጆችህ ህይወት ውስጥ እንደፈለግክ ሁን አባታቸው ነህ። በእኔ ህይወት ውስጥ ግን አይደለም።" አልኩት።

happily divorced

እና ዛሬ ላይ ለልጆቼ ሳወራላቸው እንዲህ ነው የምላቸው

"እንዳባታችሁ ያፈቀረኝ ወንድ የለም! ወደፊትም አይኖርም። እንዳባታችሁም ደግሞ የጎዳኝ ወንድም የለም። ....... አባታችሁ ጣኦቴ ነበር። በምድር ላይ ትልቁን ስጦታዎቼን እናንተን ሰጥቶኛል። በእናንተ ደግሞ ደስተኛ ሴት አድርጎኛል። መልካም ነገር ብቻ ይግጠመው።"

................ጨርሰናል ........

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Meri feleke
[መደነቃቀፋችን ዳንስ መስሎን ነበረ]
የስልኬ ሙዚቃ ማጫዎቻ ላይ ሙሉ ቀን እየተደጋገመ ሲዘፍን የዋለው የBen E.King 'stand by me' የሚል ዘፈን ነው። ሁልጊዜ ለምን እንደዛ እንደማደርግ አይገባኝም ፤ አንድ ሙዚቃ ደጋግሜ አደምጣለሁ። አንዳንዴ ለተከታታይ ቀናት ሌላ ዘፈን ሳልቀላቅል ካለማቋረጥ የምሰማቸው ዘፈኖች አሉ፤ ከወደድኩት ነገር ላይ ቶሎ መላቀቅ የሚከብደኝ ለዛ ነው በቃ ከያዝኩ እንደዚ ነኝ ስወድ አፍናለሁ ስወድ አስጨንቃለሁ፤ ለራሴ ራሱ የሚረብሸኝ ባህርዬ ነው እና አዲስ ለሚተዋወቁኝ ሁሉ መጀመሪያ የምናገረው ነገር "ስወድ አስጨንቃለሁ.....ስወድ ችግር አለብኝ"ን ነው። ዘፈኑ ደግሞ አሁን እንዲህ እየተስረቀረቀ ሩቅ ልውሰድሽ ይለኛል፤ ረስቼዋለሁ ትቼዋለሁ ወዳልኩት ትናንት አጅቤሽ ካልሄድን እያለ ያባብለኛል ....
"አሻቅበን ያየነው ሰማዩ ተገምሶ ላያችን ቢደፋ ፣ ወይ ደግሞ _ ግዙፍ ተራራ ተንዶ ከውቅያኖስ ገብቶ ቢጠፋ፣
ማልቀስ እርም ነው ለኔ _አንዲት ዘለላ እንባ እንኳ 'ካይኔ ጠብ አትል አትፈስ፣
አንተ አጠገቤ እስቆምክ ከጎኔ እስካለህ ድረስ፣" አሁን ላይ ሆኜ ሳስበው በአብሮነታችን ውስጥ የነበሩ እንደቀልድ ያለፍናቸው ፤ በእብደታችን ያሸበረቁ በሳቅ ያከበብናቸው በኩርፊያ ያጀብናቸው አያንዳንዱ ቅፅበታት እጅግ ውብ ቢሆኑም ልክ ናቸው ብዬ የማስብበት ዘመን አልፏልና ድጋሚ በጨረፍታም ላስባቸው አልፈልግም። በርግጥ አንዳንዴ ከነዚህ ቀናቶቻችን ጥቂት የእብደት ስራችን የጎላባቸውን
እያነሳሁ ለወዳጆቼ ስነግራቸው ( በትንሹ፤ ስለ ምሽት ባሌት ዳንሳንችን፣ ፀጉሬን ሰብስቦ በስርአት ስለሚያያይዝበት ሻጤ። በአብዛኛው ደግሞ ስለ ፍትወት፤ የቃምነው ጫት ገረባ ላይ ስለምንፈፅመው ሩካቤ፣ ማዕዳችንን ገፍተን ስላጧጧፍነው ወሲብ፣ ዝናብ እየዘነበ ጭቃ ላይ ስላደረግነው ፣ ምናምን) ወይ 'ያማችኋል ግን?' ወይም 'እብድ ናችሁ? ' ካልሆነ ደግሞ 'ይሄ ልክ አይደለም ! '
ይሉኛል። የምንወደው እብደት ውስጥ አብረን እንዋኝ እንደነበር፤ ነፃነት እና እውነት ከሰሩት እብደት በላይ ልክነት እንደሌለ ጨምሬ ልነግራቸው ፈልጌ በቸልታ ትከሻዬን ሰብቄ እተወዋለሁ። ግን እንደዛ ያሉኝ ዕለት አመሻሽ ላይ ናፍቆኛል ልቤ እስኪርድ ናፍቆኛል አለ አይደል የኔና የእርሱ አለም በራሳችን ህግ ተከልሎ በእብደታችን የቆመ ፍፁም ሌላ ፕላኔት ነበርና ማንም የሰራነውን አለም ልክ አይደለም ቢለን የምንሰማ አይነት አልነበርንም፤ አንዳችን ላንዳችን እስካለን
ድረስ የምንፈራው ምንም ነገር አልነበረም። "ምሽቱ በመጣ ጊዜ፤ ምድር ፅልመት ስትለብስ፣ ድቅድቅ ጨለማው መሃል ጨረቃ ብቻ ተግታ ብርሃኗን ለእኛ ስትለግስ፣ ፍፁም ልፈራ አልችልም _
አንተ አጠገቤ እስቆምክ ከጎኔ እስካለህ ድረስ፣" ከሆነ ጊዜ በፊት ወደ ኋላ ተመልሼ አመሻሻችን እንዴት እንደነበር ሳጤን ከሰርክ እለት ዑደታችን ( ስንራኮት ከዋልንበት ከእርሱ ቤት ወደ ቤቴ ሲሸኘኝ) በመንገዳችን አሳብረን የምናልፈው የኡሪዎች ኳስ ሜዳ ነበር፤ ልክ እዛ ስንደርስ ከላያችን የምታበራ ጨረቃ ጥላችንን ፍንትው አድርጋ ስታሳየን ከጥላዎቻችን ጋር የደነስንበት በምሽት ከደመቀ ውበቷ ላይ ቅርፁን ቀይሮ ብርሃኗ ዜማ ሆኖ በጆሮዎቻችን ተንቆርቁሮ እንደነበር አስቤ አውቃለሁ።
በፊት ላይ ሲናፍቀኝ ከሁሉ ከሁሉ በግድግዳው እና በአልጋው ክፍተት መካከል ከፀጉሬ ሾልካ የወደቀች የአንዲት የሻጤ ነገር ያሳስበኝ ነበር። ስለ እርሷ ያልተመለሱ ብዙ ጥያቄዎች ነበሩኝና ባገኘውና ብጠይቀው እወድ ነበር። ከኔ በኋላ ቤቱን እና ገላውን የጎበኘች እንስት ከአልጋ ተንሸራቶ በዚያ በኩል መሬት ያረፈ የውስጥ ሱሪዋን እጇን ሰዳ ስታስስ የፀጉሬ ሁለት ዘለላ
የተተበተበበት ያን ሻጤ ያገኘች እለት ምንድነው የሚሰማት? ምንስ ነው
የምታስበው? እርሱም ከእኔ ጋር እንደለመደው ፍቅር ሲሰሩ የተንጨፋረረ ፀጉሯን ከጉዳያቸው በኋላ ሰብስቦ ሊያስይዝላት አልጋቸው ላይ የተበታተ የፀጉሯን ማያያዣ ሲያስስ አንዱን ተሳስቶ ገፍቶ በቀደመው ክፍተት ቢልከው፤ አልጋ ስር የተገናኙ ሁለት ሻጤዎች እንደ ባለቤቶቻቸው በጣውንትነት ስም ይጠራሩ ይሆን? የየራሳቸውን የውድቀት ታሪክ እና የሴቶቹን እንዝህላልነት እያነሱ ይወያዩ ይሆን? ወይስ... ለየባለቤታቸው ወግነው ቀጫጫ ሽቦ አካላቸውን ለድብድብ ያነሳሉ? ወይስ... እዛው ባሉበት ብዙ ቀናትን አሳልፈው ቤት አፀዳለሁ በሚል ሰበብ አልጋ በምትጎትት ሶስተኛ ሴት እጅ ከወዳደቁበት ተነስተው የወረሳቸው ትቢያ እፍፍ ተብሎላቸው ድጋሚ አናት ላይ ይወጣሉ? እና የናፈቀኝ እለት ወይስ ...... ወይስ ... ወይስ እያልኩ ስለ ጥቃቅኗ ነገር ሁሉ በጥልቅ የማስበው እና የምብከነከነው ከእለታት ድሮ ቀን በወጣች ደንጋዛ እና ፈዛዛ ጨረቃ ደነስን ያልነው መደነቃቀፍ፣ በሌላ ጥንት በሚመስል ቀን ከፀጉሬ የወደቀ ወልጋዳ ሽቦ ምናምን የገዘፈ ጥቅም ኖሯቸው ሳይሆን ከእርሱ ጋር የነበሩኝን ቅንጣቶች በሙሉ ከቋጥኝ አግዝፌ ስለማይ ነበር።
አሁን ላይ ዛሬን በአሁን መለካት ሳይሆን በነገ መስፈር ስለለመድኩ እንደ ጥንቱ
ስወድ አላስጨንቅም፣ አሁን Ben E.King ሳምንት ሙሉ ልብ በሚበላ ብሉዝ ቢለምነኝ እንኳ የሚያንኳኳውን የትዝታ በር ለመክፈት የምጥር አይነት
አይደለሁም። ዘንድሮ ከተረት እና ከኩሸት የቻልኩትን ያህል ተምሪያለሁና ይሄ ይሄ ትዝ ሲለኝ የምለው "የሁሉንም ነገር ዋጋ በሰአቱ መረዳት ብንችል ህይወት እንዴት ውብ ይሆን ነበር" ነው። የማዝነው የማይገባቸውን ዋጋ ሰጥተን ላጡን እና ላጣናቸው ስናላዘን ስለተላለፉን ቀናት ነው።

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Elssa Mulugeta
ልጅ ስትወልድ ነው ቤተሰቦችህን የምታመሰግነው ከቤ :)
ህፃናት ቤትህን ሲያምሱት ህወሀት ማረኝ ትላለህ። ለምሳሌ ልጅህ የቤትህን ቴሌቪዥን ኩባያ ወርውሮ ሊሰብርብህ ይችላል ። ነገ ወሳኝ ስብሰባ አለኝ ብለህ በክብር ያኖርከውን የሱፍ ጃኬት ባሊ ውስጥ ነክሮ ሲያንቦራጭቅ ልታገኘው ትችላለህ ። ውዷ ባለቤትህ ናፍቃህ እቅፍ አድርገሀት ጉያህ ከመክተትህ ቅናት ያንገበገበው ፈልፈላህ ስኒ ወርውሮ ግንባርህን ይገምስሀል 😄 በተለይ ወንድ ልጅ ራሱን የቻለ ወያኔ ነው። ልጄን ቅዱስ ብዬ ከምጠራው ጌታቸው ረዳ ብዬ ለምን አልሰየምኩትም የሚል ቁጭት አንገብግቦኝ ያውቃል። ሌላው ልጅ ስትወልድ የምትረዳው የሴቶችን አስማት ነው። ሴት ልጅ ምትሀተኛ ናት። ሚስትህ የውጭውን ስራ ሰርታ ቤት ተፍተፍ ብላ ልጅህን እንደፀባዩ ስትይዝልህ የሴት ልጅን ተፈጥሮ ታደንቃለህ። ብዙ ወንዶች በባህሪያችን ስልቹ ነን። 10 ደቂቃ ልጅህን አቅፈህ ተቀምጠህ ትግል ሲጀምርልህ ትማረራለህ። አንዳንዴ ረዥም ገመድ አዘጋጅቼ ከጠረጴዛ ግርጌ ልሰረው ወይ ልትል ትችላለህ ።
ቢሆንም...ቢሆንም...ወንድም መላ አለው። ልጄ ሲረብሽ ጊልዶና ሳንቾ ትዝ ይሉኛል። ጊልዶ የሚደብረኝን ያህል መርቄው አውቃለሁ። የጊልዶ ባዶ ...ባዶ ሙዚቃ ቅንብሮች ልጄን ያስጨፍሩታል። የኤልያስ መልካ አጥንት እየወቀሰኝ ሳንቾን እከፍትለታለሁ። ሙዚቃው እስኪፈፀም የሰላም አየር እምጋለሁ። ሙዚቃው ሲፈፀም Phase 2 ጦርነት በይፋ ቤቴ ውስጥ ይጀመራል። ህወሀት ማነው ቅዱሴ ያንሰራራል። የቤቱ ህገመንግስት ተጣሰ ይለኛል። ወልቃይት ....(ወይኔ ጨለልኩ በቃ !)... አንተ የተቀመጥክበት ቦታ የኔ ነው ብሎ ያንባርቃል። እየተንጫነጭኩ ቦታዬን አስረክባለሁ ።
ከልጅህ ጋር ትንሽ ከተጎራበጥክ ባለቤትህ በግልምጫ ታነሳሀለች። ያልሰከነ ቡና ልትቀሳልህ ትችላለች...እንደ ጣና ሀይቅ በቀጠነ ሽሮም ልትመታ ትችላለህ። This is life brother!
....ፈጣሪ ላያስችል አይሰጥም ብለህ ስትማረር ብትውልም የልጅህ አንገት ስር ገብተህ ስትስመው አመፁን ትረሳዋለህ። ሌላ ልጅ መድገም ሁሉ ያምርሀል። ህፃናት ገነትን በአንገታቸው ይዘው ይዞራሉ። በስራ እየጦዝክ በመሀል ልጅህ ይናፍቅሀል። ብጥብጡ.. .አመፁ...ረብሻውም ለካ አንድ መሳጭ የህይወት ሂደት ነው አባዬ ! እየከነፍክ ቤትህ ትገባለህ.. .የሶስተኛው ዙር ጦርነት መለከት ይነፋል :)

@getem
@getem
@paappii

#mikael aschenaki
Forwarded from WORDS
“Express your love, we can't read minds. “

@words19
ዜማና ሰውነት
[ግዕዝ፤አሃዱ]
ሰዎች"እንዴት ነው ሰብራህ የሄደችው ?" ብለው ሲጠይቁኝ " ልቤ እስከሚያነክስ" ብዬ ከመለስኩላቸው ረጂም ጊዜ ቢያልፍም ድንገት ቀና ስል የጠራ የመስከረም ሰማይ አይቼ ናፈቀችኝ ።
ለእንቁጣጣሽ በፈካ ቢጫ አደይ ያቆጠቆጠ አረንጓዴ መስክ ላይ ይሄን ብራ ሰማያዊ ሰማይ ደርበን የተራከብን ነን። በሚያሳሳ የመስከረም ቀን መኻል
አፍላነት ያቀጣጠለው፤ ነፋስ ስሞ ያበረደው ገላችን ላይ ጣል ያደረግነው፤ የተጋፈፍነው ሰማይን ነው። ሽቅብ ያየሁበትን አይኔን ቶሎ ሰበርኩ እንጂ ባተኩር ከጭኗ የተላቀቀ የጠይምነቷን ባዘቶ ጉም ሰርቶ አየው ነበር። ሁሉ እንደዛሬ ስላይደለ ልብ ብዬ ባየው ህመሙ ነፍሴ ላይ ያረብባል እንጂ። በልጅነት ቀናቷ ድንግል ልቧን እና ነፍሷን የገረሰስኩ ተቀዳሚ ግዕዟ ነኝ። ማለት የመጀመሪያውን መሳም የትኛውም መሳም እንደማይሽረው፤ የመጀመሪያው ዜማ ድንቅነት በሌሎች እንደማይሸፈነው፤ በልቧ ቅኝት ላይ ተደላድዬ የተፃፍኩ ማንም የማይሰረዘኝ ዜማዋ ነኝ። ለመጣ ለሄደው ሳትሰለች የምትነግረኝ ገድሏ ከአንደበቷ የምወጣ ብቸኛ ተረኳ መሆን ትምክተኛ አድርጎኝ፤ ልታቅፈኝ የዘረጋቻቸው እጆቿ አየር ላይ
እንደተንከረፈፉ ትቻት ስነጉድ፤ በማንም ያልተሳሙ ለጋ ከንፈሮቿ ሊስሙኝ ሲተጉ
ስገፋ ተስፋ ቆረጠችና ያልቃል ብዬ ያልገመትኩትን ለኔ ያላትን ፍቅር ለሌላ አጋርታ አገኘኹዋት። በኔ ግዕዟ ላይ እዝል ደርባ የምታዜም ሆነች። ፀፀት ልቤን ሲበላኝ እስከዛሬ ትምክህት የሸበበው አንደበቴን ከፍቼ እንደምወዳት
ነገርኳት። ሁለተኛ ፍቅሯ ከኔ እንደማይበልጥባት አውቃ ይሁን የዘመናት ህልሟ ስለሆንኩ ብቻ ግን መውደዴን ስነግራት ደስ አላት አቅፋኝ አለቀሰች። "ሁሌም አለሁልህ "አለችኝ።
ፍቅሬ በእኔ በግዕዟ እና በሁለተኛዋ እዝሏ ዜማ የምትንገላታ አሳዛኝ አራራይ
ሆነች። በዚህ ዜማ የታመምን ሶስት ሰዎች ነበርን። ከእርሱ ጋር አሸብሽባ
እንደምትመጣ እያወኩ በቅዳሴዋ ልዘምም ደፋ ቀና ስል ከጠይም ገላዋ ላይ የሚነሳ የእዝሏ ጠረን፣ ከሴትነቷ የሚተን የእርሱ ጢስ ዜማዬን እና አቋቋሜን ቢያዛባውም። በ"የኔ ነበረች፤ ሁሌም የኔ ነች። " እምቢተኝነት በቅኝት መኻል ሽብርክ የሚል ልቤን ታቅፌ ወረቧ ላይ ከርሚያለሁ። አሁን ይሄን እኔ እና እርሷ የተጋፈፍነውን የመስከረም ብራ ሰማይ ቀና ብዬ ባይ በተመሳሳይ ቀን እኔ ጋር ከመምጣቷ በፊት ከእዝሏ ጋር የነበራትን ወረብ በበራሪ ኮከብ እንደ ስዕል አስቀምጦ ያሳየኛል። ግን አይኔን አቅንቼ ሰማዩን ሳይ ትዝ ባለችኝ ቅፅበት አንገቴን መልሼ እጄን ደረቴ ላይ አጣምሬ የልቤ ድሪቶ ውስጥ ቀበርኳት። ቢሆንም እኔ ምንም የልቤ ስርቻ ውስጥ እንደመነኛ ልጥላት ብሞክር በእርሷ ልብ ውስጥ ግን ያለኝን ቦታ አውቃለሁ፤ ብዙ ሁለተኞች ያልሻሩኝ የሁሉ ነገር አሃዱዋ ተቀዳሚ ግዕዟ ነኝ። [እዝል፤ ተደራቢ]
ትዝ የምትለኝ በእኩለ ሌሊት ነቅቼ ሲጋራዬን ለኩሼ ያጨስኩ ቀን ነው። ከሁሉ ከሁሉ የምትወደው ከንፈሬን ነው። ከንፈሬ ላይ ባለችው ጥቁር ነቁጥ ሁሉ ሳትቀር ትቀና ነበር "ማርያም ለምን ሌላ ቦታ አልሳመችህም?" ብላ ታኮርፈኛለች። ሌሊት እንዳልቀሰቅሳት ተጠንቅቄ ተነስቼ ወንበር ስቤ ተቀምጬ
ሲጋራዬን ስለኩስ ከእንቅልፏ ትነቃለች። በቅጡ ያልተከፈቱ አይኖቿን ገርበብ
አድርጋ " ጭሱን ከአፍህ ልውሰድ?" ትለኛለች። ቀጥላ ከመኝታዋ ተነስታ ጭኔ
መሃል ትንበረከክ እና አጭሼ የምተነፍሰውን ጭስ ከአፌ አንደ ወፍ ትቀበላለች። የዛኔ ከንፈሮቻችን ተጋጥመው ቅጡ በማይገባን ወረብ ቆመን መወዛወዝ እንጀምራለን።
ሁሉም እንደሚያውቀው ከኔ ቀድሞ በገጠማት ዜማ ያልተደሰተች ዘማሪ ነች እኔ አፍላነቷ ጎትቶ ከቀሚሷ ስር ከገላዋ ላይ ያዋለኝ እዝሏ ተደራቢ ዜማዋ ነኝ።
አለ አይደል በግዕዝ የጋለ እሳቷን አቀዝቅዤ አረጋጋታለሁ። ቀልበ ቢስ ቀልቃላ እና ሃይለኛ ቅላፄዋን ዳብሼ ገርቼ እመልስላታለሁ። የመጀመሪያዋ ነውና ለግዕዟ ያላትን ስሜት በአንዴ አውጥተሽ ጣይ ባልላትም። በኔ እርጋታ አገግማለች። ፍቅር ከጀመርን ከጥቂት ጊዜ በኹዋላ በወረባችን መኻል የቀደመ ትትርናዋን ችላ ብላ ሁሉ ነገሯ ሲቀየርብኝ ግራ ገባኝ ። ቆይቼ አስቸጋሪ ግዕዟን አስጣልኳት ያልኳት እርሷ የቀደመ ቅላፄዋን ሳትተው በእኔ ላይ ደርባ ማዜም መጀመሯን አወኩኝ ። ይህን ሳውቅ እውነቱን በልቤ ደብቄ ሸፋች ልቧን ላረጋጋ ርቃኗን አስተኝቼ ከላይ እስከ ታች በከንፈሬ እየዳበስኩ በእንባዬ አርጥቤ አጠብኳት። እንዲህ ሳደርግ በሃይለኛ እና እምቢተኛ የሚማረክ እርሷነቷ ለኔ መለማመጥ
ትኩረት መስጠት ተሳነው። እናም ያኔ የጀመርነው ለስላሳ ቅኝት ዜማችን
ተቆራረጠ። አሁን ዛሬ ላይ ስለ እርሷ ሳስብ ሃዘን በልቤ ያልፋል ። በህይወቷ ከተጣባት ጠንካራ ግዕዝ ላሳርፋት የጣርኩ ለስላሳ እዝሏ ብሆንም እዚያና እዚህ የሚረግጥ አሳዛኝ አራራይ ነፍሷ ግን ያን እንድታደርግ አልፈቀደም። ከብዙ ጊዜ በኹዋላም ቢሆን እኔ ላይ ካደረገችው ክህደት ይልቅ ለቅብዝብዝ እርሷነቷ እና በዚህ ምክንያት ለሚበላሹ ዜማዎቿ የማዝን ተደራቢ ዜማዋ እዝሏ ነኝ። [አራራይ፤ አሳዛኝ] ሰዎች በሰራኹዋቸው ነገሮች በሙሉ ይበሳጫሉ። ይበሳጩና ያዝናሉ።
የበደልኳቸው እንኳን ትንሽ ተበሳጭተውብኝ ቀጥሎ የሚያደርጉት ነገር ቢኖር ለእኔ ማዘን ነው። እኔነቴ ሰው ጨክኖ ጆሮ እንደ ማይነፍገው አሳዛኝ ዜማ ነው፤ እንደ አራራይ። ስለ ዜማ ሳስብ ስለ ሁለቱ የቀድሞ ፍቅረኞቼ አስባለሁ። የመጀመሪያው ግዕዜ
ነው ...... ልጅነቴን በጥበቃ የጨረሸ፤ የኮራብኝ፤ የተጀነነብኝ፣ ደጅ ያስጠናኝ፣
ያስለመነኝ፣ እልህ ያጋባኝ ፣ የፈተነኝ። ሁለተኛው ደግሞ እዝሌ ነው ......የደረብኩት ፣ ያረጋጋኝ ፣ያበረደኝ ፣የወደደኝ። ስለምነው የከረምኩት ግን የገፋኝ። በኋላም ከሚያሳርፈኝ ጋር እፎይ ማለቴን ሲያይ ስመኘው የኖርኩት ፍቅር ካልሰጠሁሽ ብሎ ፊቴ ቆመ። አመታት እርሱን የኔ በማድረግ ምኞት አልፈው በመጨረሻ ፊቴ ሲቆም አይሆንም ማለት አቅቶኝ፤ እዝሌንም በቃኸኝ ግዕዜን አግኝቻለሁ ብዬ እንዳልለው የምጠለልበት የምሰክንበት ጥጋቴ ነውና እንዳላጣው ፈርቼ በሁለት ቢላ የምበላ ሆንኩኝ ። ሁለቱንም በተለያዩ ምክንያቶች ሳላስባቸው ውዬ አላውቅም። ባስታወስኳቸው ቁጥር ግን ሃዘን ይከበኛል። ሁለቱም በመቅበዝበዝ እና በመንገብገብ ያበላሸኹዋቸው የህይወቴ ዋና ዋና ዜማዎች ናቸው። በእርግጥ ከነርሱ በኋላም ያማረብኝ ቅላፄ የተዋጣልኝ አቋቋም የለም ግን እንደ ሁለቱ ያበላሸሁት የለም። አሁን ላይ ከግዕዜና ከእዝሌ የተረፈኝን አራራይ ዜማ ለራሴ ወስጄ ሌት ተቀን እህህ እላለሁ።
ሁሉን የእኔ ይሁን የሚል ልጅነቴን ለተከተለ ደመነፍሴ ፣ በሁለት ዜማ አንድ ቅኝት ለናፈቀ ለጋነቴ ፣ ለባተልኩት ፣ ለባከንኩት ፣ ከሁሉ ከሁሉ በአንድ እለት ግዕዝም እዝልንም ለተቀበለ ሴትነቴ በአራራይ ዜማ እህህ እላለሁ ። በመጨረሻ የገባኝ ግን ሁሉ በአሳዛኝ ዜማ እንደሚቋጭ ነው ፤ ህይወት የሚባል ውብ ነገርም ቢሆን

@wegoch
@wegoch
@paappii

#elssa mulugeta
Forwarded from Sunset Hiking
#Sunsethiking is hosting a day hike to "DAMOCHA"

Damocha Mountain is an eroded volcanic crater with a jagged rim surrounding the valley floor far below. The valley features a drainage stream that comes out just to the right of the museum and provides an easy, well-worn route past the lower peaks that hide the real summit (from the vantage point of the park). This trail ends at a tiny mountain village.

📅Hiking Date :- Aug 15, 2021 (Nehase 9), 2013).

💵 Hiking #Cost:- 675 ETB only

🛫Departure: Piasa (Taitu Hotel)

Departure Time - 12:30 Am LT

🎉🎊Package includes🎋🎊
🚍 Transportation
🌲 Bottled water
🌺 Guide + scout
🍂 photography 📷
💐 Breakfast
🏖 lunch

NB.
🚫 Sanitizer & facemask mandatory!

👉 walking hour: 5 hour (up to 20 km of walking)

suitable for: HARD, basic skill required

for more join the

🔸channel @sunsethiking🍁
🔻📷 @sunsetphotography🍁

🎫 tickets available at
@Paappii ( +251922303747)
እውነት እብዱ ማነው?
(እውነተኛ ታሪክ)
#ክፍል አንድ

እነሆ… እውነት እብዱ ማን ነው…? ልክ የዛሬ ሶስት ዓመት በዕለተ ባለወልድ አጥቢያ (ሐምሌ 28 ለሐምሌ 29) ከሌቱ ስምንት ሰዓት ገደማ ጥቂት ቀሳውስት ለቅዳሴና ማህሌት ወደ ቤተክርስቲያኒቷ እየገቡ ሳለ አንደኛው ቄስ ከቅፅሩ ባሻገር የትኩስ ውልድ ሕጻን ልቅሶ ድምፅ ሰምቶ ቆም አለ፡፡ ‹‹ይሰማችኋል የሕጻን ልጅ ልቅሶ…›› አለ፡፡ ሌሎቹም ጆሮአቸውን ቀስረው ይሰማል የተባለውን ድምፅ ለመጋራት ቆም አሉ፡፡ እንዳለውም ወዲያው የሕጻን ድምጽ ልቅሶ በድጋሜ ሲሰማ እውነትም ከቤተክርስቲያኑ ቅፅር ጀርባ ከወደ መቃብር ቤቶቹ አካባቢ የሚሰማው ድምጽ በጉልህ የትኩስ ውልድ ሕጻን እንደሆነ አረጋገጡ። የሐምሌው ዝናብ እኝኝኝ… ማለቱን ከጀመረ ቆይቷል… ይበርዳል…!
ከየት ነው…? የማን ነው…? ተጥሎ ነው…? የምን ጉድ ነው…? ወዘተ የመሳሰሉ ጥያቄ እያመላለሱ ሳለ ከመሃከላቸው አንደኛው ትንግርቱን የሚፈታ መላ መታ፡፡ ‹‹እናንተ… ያቺ እብድ እኮ ነፍሰ-ጡር ነበረች… እሷ ወልዳ መሆን አለበት…›› አላቸው፡፡ ሌሎቹም የተሰጠውን መላምት ከግምት በላይ እርግጠኛ ሆነውበት ምንም ሳይነጋገሩ በጥቆማው ተግባብተው ድምጹ ወደሚሰማበት የቤተክርስቲያኑ ቅፅር ጀርባ እየተጣደፉ ዘለቁ፡፡ "ያቺ እብድ" የተባለችው ይቺ ሴት ግን ማን ናት…? መጀመሪያ እሷን በጥቂቱ ላስተዋውቃችሁ፡፡ ስሟ በሀገሬው ሕዝብ ዘንድ “እብዷ” ይባላል፡፡ በቃ ይሄ ነው መጠሪያዋ፡፡ ከጥቂት ዓመታት በፊት ምናልባትም ከሁለት ዓመት ገደማ በፊት ነው እዚህ ከተማ የተገኘችው፣ ወይም “አምጥተው የጣሏት” ይላሉ ነዋሪዎቹ፡፡ በነገራችን ላይ ለምን እንደሆነ ባይገባትም ከተማውን በደንብ የምታውቀው እህቴ እንደነገረችኝ ከሆነ ብዙ እብዶችን በመኪና እያመጡ እዚህ ከተማ መጣል የተለመደ ነገር ከሆነ ቆይቷል፡፡ “ለእብድ መኖሪያ የሚሆን ተመራጭ ከተማ…” የሚለው ግርምተ-ሃሳብ ውስጤ ተመላለሰ፡፡ አንዳች መልስ የማገኝለት ይመስል ሃሳቡ ለአፍታም ቢሆን ውስጤ መቆየቱ ለራሴ ፈገግ አሰኘኝና ተውኩት፡፡ ክረምት ይሁን በጋ፣ ቀን ይሁን ማታ፣ “እብዷ” እዚህ ከተማ ከታየችበት ቀን ጀምሮ እስካሁን እርቃኗን ነው የምትውለው፣ እርቃኗን ነው የምታድረው፡፡ አንዳንድ ደግ ሰዎች እንደምንም ብለው ልብስ ሲያለብሷት በደማቅ ፈገግታ ታጅባ ለጥቂት ደቂቃዎች ብቻ የለበሰችውን ልብስ እንደ አንዳች ትንግርት ዙሪያ ገባውን ትመለከተዋለች፡፡ ይገርማታል ያስቃታል…! ከዚያ ሰዎቹ ዘወር ካሉ በኋላ ወዲያው አውልቃ ትጥለውና የለመደችውን ነጻነት በድጋሜ ተጎናፅፋ መለ–መላዋን ትቀጥላለች፡፡ በየትኛውም ቋንቋ ቢያናግሯትና ቢጠይቋትም በጠያቂው ድምፅ ወይም ቋንቋ ወይም ንግግር ከመደመምና አጫ በረዶ የመሰለውን ጥርሷን ብልጭ እያደረገች ፈገግ ከማለት ውጪ መልስ የሚባል ነገር ሰጥታ አታውቅም፡፡ የማትናገረው በተፈጥሮዋ “መናገር የተሳናት” ሆና ይሁን ወይም “እብዷ” ካሰኛት
የአዕምሮ ጤና መታወክ የተነሳ አይታወቅም፡፡ በአጭሩ ከፈገግታ በቀር አትናገር አትጋገር አይነት ናት፡፡ “እብዷ” እዚህች ትንሽ የገጠር ከተማ ከመጣች ጀምሮ ሰው ተተናኩላ አታውቅም ይላሉ፡፡ የተወለደችበትን አካባቢ ወይም ነገደ-ቋንቋዋን የሚያውቅ የለም፡፡ የሚገምትም የለም፡፡ ቁመቷ ሎጋ፣ ቀለሟ ጥቁር የሚባል፣ ፀጉሯ ከርዳዳና አጭር፣ አፍንጫዋ ሰልከክ ያለ፣ ጥርሷ ድርድር ያለ ነጭ ነው፡፡ ይህ ነው ስጋዊ መገለጫዋ፡፡ ከዚህ ውጪ እሷ ማለት በቃ “እብዷ” ናት፡፡ እዚህች ትንሽ ከተማ “አምጥተው ከጣሏት” ጀምሮ እዚያችው ማርያም ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ገባ እየዋለች፣ በመረጠችው መቃብር ቤት እያደረች፣ ቀንም ሆነ ማታ እርቃኗን በመሆን በራሷ ዓለም መኖር ጀምራለች፡፡
አንድ ክፉ ቀን “ጤነኛ” የሚባል/የሚባሉ የሆነ አካባቢ ሰው/ሰዎች ነው/ናቸው
አሉ እስኪደፍራት/እስኪደፍሯት ድረስ…
በዚያም ሰበብ እስክትፀንስ ድረስ…
ለሐምሌ ባለወልድ አጥቢያ በድቅድቁ ጨለማ ራሷ ሽሏን እስከምትገላገል ድረስ…
÷÷÷
ቄሶቹ የሚሰሙትን የአራስ ሕጻን ልጅ ልቅሶ አቅጣጫ እየተከተሉ፣ ድምጹ ከሚመጣበት ቦታ አካባቢ ሲደርሱ እውነትም “እብዷ” እንደማንኛውም ውሎ
አዳሯ ሁሉ በዚያ በሐምሌ ጨለማ በሐምሌ ቁር… በሐምሌ ዝናብ… እርቃኗን በድቅድቁ ጨለማ ውስጥ ቆማለች፡፡ አይናቸውን አጥብበው በጣም ተጠግተው ሲመለከቷት ደግሞ ከደቂቃዎች በፊት እዚያው እመቃብር ቤቶች አካባቢ አምጣ የወለደቻትን ልጅ ለፈጣሪ መስዋዕትነት የምታቀርብ ይመስል፣ ሕጻኗን በአንድ እጇ ወደላይ ከፍ አድርጋ ይዛ እንደተለመደው ፈገግ ትላለች፡፡ የሕጻኗ እትብት ከሕጻኗ ሆድ ጀምሮ ወደታች እስከ እናትየው እግሮች መሃል ድረስ ይወዛወዛል፡፡ ከእናትየው መዳፍ ብዙም የማትተልቀው ሕጻን በዚያ ሐምሌ ቁር እና ዝናብ እየተቀጠቀጠች በእሪታ ትነዝራለች፡፡ [ቄሶቹ የፈጣሪን እና የቅዱሳንን ስም እየጠሩ ማማተባቸውና ማነብነባቸውን መገመት ቀላል ነው፡፡]
ቄሶቹ በወቅቱ ምን አስበው ይሁን መረጃው ባይኖርም፣ በወቅቱ የወሰኑት ውሳኔ ከቤተክርስቲያኗ ፊትለፊት የሚገኝ አንድ ግቢ አስገብተውና የግቢውን በር
ዘግተው መሄድ ነበር፡፡ ግቢው ደግሞ አንድ ደግ የአካባቢው ሰው ደካማ
አዛውንቶችን የሚያኖሩበትና የሚረዱበት ነው አሉ፡፡ ለማንኛውም ቄሶቹ እዚያ
ግቢ አስገብው ወደ ቅዳሴአቸው ሄደዋል፡፡ (እዚህ ጋር ቄሶቹ ያደረጉት ነገር መልካም ነው ብዬ ለማሰብ ተቸግሬአለሁ…)
÷÷÷
የሐምሌው ዝናብ ሌቱም አልበቃ ብሎት ንጋትም እንዲሁ ሲንዛዛ ስለ ነበር፣በግቢው ውስጥ የሚኖርና በጠዋት የተነሳ ማንም ሰው አልነበረም፡፡ ከጠዋቱ ወደ ሶስት ሰዓት ገደማ በግቢው ውስጥ ከሚኖሩት ተረጂ አዛውንቶች መካከል አንዳቸውን ለመጠየቅ መጀመሪያ ወደ ግቢው የዘለቀችው አንዲት ወጣት ልጅ
ነበረች፡፡ ልጅት ወደ ግቢው ስትገባ ዙሪያ ገባ ከሚገኙት ክፍሎች መካከል ከኩሽና
ያልተናነሰውና ክፍት ከነበረው አንደኛው ክፍል ደጃፍ ላይ "እብዷ" አንዳች በጭቃ ተጨማልቆ የተድበለበለ ነገር ይዛ ወደላይ እየወረወረችና እየቀለበች ስትጫወትበት ተመለከተች፡፡ ልጅት ያየችው ነገር ትንንሽ እጆችና እግሮች
ስላሉትና ከሆዱ ደግሞ አንዲት ትንሽዬ ቁራጭ የምትወዛወዝ ነገር ስላየች በጣም ደንግጣ ጩኸቷን አቀለጠችው፡፡
የተኛም ያልተኛም ከየቤቱ ወጥቶ ምን ሆንሽ ቢሏት…‹‹እብዷ… እብዷ… እብዷ…. የሆነ አውሬ መሰለኝ… የሆነ አውሬ ነገር ይዛ እየተጫወተችበት ነው…›› ብላ እየተንቀጠቀጠች በጣቷ ወደ “እብዷ”
ትጠቁማለች፡፡ ሰዎቹም እየተጣደፉ ቢጠጉ “እብዷ” አሁንም ፈገግታዋን እያጀበች ሌት በ8:00 ገደማ በወለደቻትና በጭቃ ስታንደባልላት ባደረችው ልጇ አሁንም ትጫወታለች፡፡ አሁን የሕጻኗ እትብት ከእናትየው ተለያይቶ ትንሽዬ የእትብት ቅሪት በሕጻኗ ሆድ ላይ ተንጠልጥላለች፡፡ ራሷ ነች አሉ በጥሳ የለየችው፡፡ በጭቃ ተለውሳ ከተጨማለቀችው ልጅ ምንም አይነት ድምፅ የለም፡፡ በግቢው የነበሩት ሰዎች ተረባርበው ልጅቷን ከእናትየው ነጥቀው መሬት ላይ አስተኝተው ይተረማመሳሉ፡፡
ግንባሯ ላይ ድፍት ያለው ፀጉሯ ፈረንጅ የሚያሰኛት… ከአንድ መዳፍ በላይ
የማትተልቅ አንዲት እፍኝ ሴት ሕጻን ልጅ ትኑር ትሙት ለማወቅ የሚሞክር
ጠፍቶ ሁሉም እርስበርሱ እንደተፈራራ የሆነች እራፊ ጨርቅ ላይ አስተኝተዋት
አሁንም ወዲህ ወዲያ ይዋዥቃሉ… ይጮሃሉ… ይንጫጫሉ… አንዱ ይገባል…
የሚያየውን ማመን አቅቶትና ዘግንኖት እየሮጠ ይወጣል… ሌላው የተፈጠረውን
ለመመልከት ወደ ግቢው እየሮጠ ይገባል… ሁሉም ወዲህ ወዲያ ይላል…
ዝናቡም እኝኝኝ… ይላል…
÷÷÷
አባዬ፣ አለወትሮዋ የጠዋቱ ብርድ እና ዝ
ናብ ከአልጋ አላላቅቅ ብሏት ተኝታለች። ሰዓቱን ስትመለከት ሶስት ሰዓት ገደማ ስለሆነ እንደምንም ብላ ተነስታ ወደ
ማርያም ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ሳያልቅ ለመድረስ ተጣድፋለች። በዚያ ላይ
ከልጆቿ መካከል አራቱን የወለደችው በባለወልድ ቀን ስለሆነ ለባለወልድ የተለየ ስሜት አላት። "አዬ የኔ ጉድ፣ ለዛውም በባለወልድ ቀን እንዲህ ላርፍድ?" እያለች ነጠላዋን ተከናንባ ከወጣቷ ልጇ ሚሚ ጋር አውራ መንገዱን ተሻግረው ወደ ማርያም የሚያስገባውን መንገድ ሲጀምሩ ከአንድ ግቢ ውስጥ የሚጮኹ፣ የሚንጫጩ፣ የሚተራመሱ ሰዎች ሲመለከቱ በድንጋጤ እየተጣደፉ ወደ ውስጥ ሲዘልቁ ሁለቱም በአይናቸው ያዩትን ማመን አልቻሉም…
÷÷÷

ይቀጥላል

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Tilahun abebe
#ወግ_ብቻ

💚#ናፍቆትህ ናፍቆኛል. .
©ትዝታዬ
.
" . . . ወሰን አልባው ፍቅርሽ ፣ ጠብቆኝ
በስስት ፣ አድርጎኛልና መንገዴን እንዳልስት።

ለአንኳኳለት ሁሉ ልቤ አይከፈትም ፣
እንኳንስ አካሌ ሃሳቤ አይሸፍትም።. . . ..
. . . "

ይኼን ሙዚቃ እንደ ዛሬ ብቻዬን ሳልቆዝምበት በፊት………ጮክ ብለን ዘፍነነዋል . . . ተለጣጥፈን አዳምጠነዋል. . . ተገባብዘነዋል. . . ትዝታ ፅፈንበታል. . . . .

ያኔ ……

ጥር ከመግባቱ በፊት ሳውቀው. . .

"ምወደው ጫካ አለ" አለኝ የመጀመርያ የአብሮነት ምሳችንን እየበላን ነበር. . .

"ትወስደኛለህ "

"ከፈለግሽ ደስ ይለኛል "

ካለንበት ዕሮብ ለቀጣዩ ዕሮብ አቀድን. . .

ፍቅሩን አንዴ ነው የጠጣሁት ለዚህም ነው አሁንም እንደ አማልክት ምኖረው. . .

የዓለምን ምስጢር የገለጠልኝ እውነት ነበር. . . ሚሆነውም እሱ ነው. .

አስፈሪው ጫካውን ሲያሳየኝ አልፈራውም ፣ አልደነገጥኩም. . . . አልተጨነኩም. . . . ነፍሴ ስትዘል . . . ስታመሰግን አየዋት . . . ያኔ ነው ያፈቀረችው መሰለኝ . . አክብራው ስታጎነብስ አይቻታለው. . . ነፃነቷን ሰቷት ነበር እና. . . .

ከዛ ቀን በኃላ ከንፈናል . . . ያለሱ ሚታየኝ ውበት፣ የሚጣፍጠኝ ስም አጣው. . . በረርኩ . . ልቡ ውስጥ ፣ ነፍሱ ውስጥ ፣ አዕምሮው ውስጥ . . በፍቅር ፈቀደልኝ. . .

ለኔ ደክሞት ፣ሰንፎ አያውቅም. . . ያፈቅረኛል!!
ፍቅሩን መላው አካላቱ ይናገራሉ. . .


ሊመሽ ሲል ከመለያየታችን በፊት መንገድ ዳር ሻይ እንጠጣለን. . . እኔ ችፕስ ወዳለው . . . እሱ ጨጓራውን ያመዋል . . . ቢሆንም ይበላልኛል. . .ቦታውን ወዶት እኮ አደለም ሚቀመጥልኝ እኔ ስላልኩት ነው. . . .

ማይወደውን ፣ ማይፈልገውን ሁሉ ለኔ ፣ ለፍቅራችን ሲል ፈልጎት ነበር . .

* * *


ዛሬ…………

ደክሞት ፣ ደክሞኝ ጠፍተናል. . . የዘረጋነውን እውነት በመቆሳሰል ደብቀነዋል. . . ያቀፈኝ ክንዱ ተሰብስቦዋል ፣ ጥጉ ፣ ጥጌ ላይ ነኝ. . . ህልሞቻችን ከቀኖቻችን ጋር ተኳርፈዋል . . . የራሱ ልብ ውስጥ ፣ የራሴ ነፍስ ውስጥ ተወታትፈናል. . . . ደምኖብናል . . .

እራሴን ጠይቃለው " ፍቅራችን እውነት አበቃ ?"

ይቆጨኛል. . . ሚቆጨኝ ስለሌለ ሳይሆን ያልነገርኩት ስላለ ነው. . .

"ያልኖርኩልክ የቀረኝ ሂወት አለኝ. . . ያላሳየሁክ ያልሆንኩልክ እውነት አለኝ ፣ ውሃን ልወልድልህ ፈልጋለው ፣ እስከ እድሜዬ አመሻሽ አንተን ነው ምፈልገው ፣ እንደ ደነስናቸው ዳንሶች ፣ እንደነበሩን ፀሃይና ጨረቃ ፣እደተሳሙት ከንፈሮቻችን ፣ እደተራመድንባቸው ጓዳናዎች ፣ እዳለቀስንበት ምሽት ፣በጅብ እንደፈራንበት ቀን ፣ እንደ ደበደበን ዝናብ ፣ እዳቃጠለን ሀሩር ፣ እንደ ጉርሻችን ፣ እንደ ሰጠከኝ አበቦች . . ተው ትዝታ አንሁን . . " ልለው ፈልጋለው!

"ከአንተ ጋር የአንዲት ሰዓት ሐሴት ዘላለማዊ ውድ ቅርፅ ነው።. . . ፍቅራችን ከዘመናት በፊት የጠፋውን ማሙዝ እንዲሆን አልፈልግም. . . የሳትነውን መንገድ እንመለስበት፣ ኑርልኝ፣ ልኑርልህ ፣ ና ፣ ልምጣ " ልለው እፈልጋለው

. . . . ግን አልለውም

አንዳንድ እውነቶች መነገር አይፈልጉም ፣ ቁጭትን እየወለዱ ቢሆን እንኳን በመደበቅ ይፀናሉ. . .

ቢሆንም ናፍቆትህ ዝም ብሎ ይናፍቀኛል ፣ ናፍቆ ያሰኘኛል. . . እንዳልመጣም ፣ እንድመጣም
ይመክረኛል!!

/ትዝታ /


|❀:✧๑♡๑✧❀|

@wegoch
@wegoch
@wegoch
ወጣቱ ልጅ የመጀመሪያ ደረጀ ት/ቤት አስተማሪውን በሆነ ሰርግ ላይ ያየዋል። ሮጦ ሄዶ በትህትናና በአድናቆት ሰላም ካለው በኃላ አስተማሪውን "አስታወስከኝ ወይ?" አለው።አስተማሪውም ግራ በመጋባት ውስጥ ሆኖ "ይቅርታ አላስታውስህም እንዴት እንደተዋወቅን ልትነግረኝ ትችላለህ?" አለው፤ወጣቱም ልጅ እንዲህ እያለ ተረከለት "3ኛ ክፍል እያለን ያንተ ተማሪ ነበርኩ፤ታዲያ አንድ ቀን የክፍል ጓደኛዬን ቆንጆና ልዩ የሆነውን የእጅ ሰዓቱን ሰርቄበት ነበር።እሱም እያለቀሰ ሄዶ የእጅ ሰዓቱ እንደተሰረቀበት ላንተ ሄዶ ይናገራል፤አንተም መጥተህ ልትፈትሸን ሁላችንም ክፍል ውስጥ ያለን ልጆች አይናችንን ጨፍነን እጃችንን ከፍ አድርገን ፍታችንን ወዴ ግድግዳ ኣዙረን እንድንቆም አዘዝከን።በዛን ጊዜ እኔ የፍተሻውን ውጤት እያሰብኩ በጣም ተረበሽኩ፤የሚገባበትን አጠሁ።አስበው ሰዓቱ በኔ ኪስ ውስጥ ተገኝቶ ሁሉም ተማሪ ሌባ እያለ ስሰድበኝ፤ ግቢ ውስጥ መጠቋቆሚያ ሲሆን፤ከት/ቤት ተባርሬ ወላጅ አምጣ ስባልና ወላጆቼ ይሄን አሳፋሪ ድርግቴን ስሰሙ።በዚህ ጭንቅ ውስጥ እያለሁ የፍተሻው ተራ ደርሶ እጅህ ወደ ኪሴ ስገባና ሰዓቱን ቀስ አድርገህ ከኪሴ ስታወጣ ተሰመኝ፤በቃ መጥፎ ዜናው ልነገር ነው አለቀልኝ ብዬ ስጠባበቅ አንተ ግን ምንም ሳትል የመጨረሻው ልጅ እስክትደርስ ፍተሻውን ቀጠልክ።ፍተሻውም ስያልቅ አይናችሁን ግለጡና ወደየቦታችሁ ተመለሱ አልከን።እኔ ግን መልሰህ ታስቆመኛለህ ብዬ መቀመጡን ፈራሁ።በጣም የሚገርመው አንተ ሰዓቱን አውጥተህ ለባለቤቱ መለስክለት፤ግን ከማን ኪስ ውስጥ እንዳገኛህና ማን እንደሰረቀበት ምንም አልተናገርክም ነበር።በት/ቤት ቆይታዬም ምን እንደተፈጠራ ማንም አላወቀብኝም ነበር፤አንተም ምንም ብለሃኝ አታውቅም።እኔ ግን ስሜንና ክብሬን እንዳደንክና ስብዕናዬ እንደጠበክልኝ ዛሬም ድረስ አስታውስሃለው።አንተም ይሄን ታሪክ ቶሎ ትረሳለህ ብዬ አልገምትም አሁንስ አስታወስከኝ?" አለው።አስተማሪውም በመገረም ውስጥ ሆኖ "ትንሽ ትንሽ አስታውሳለው በማን ኪስ ውስጥ እንዳገኛሁ ግን አላስታውስም፤ ምክንያቱም እኔም ስፈትሻችሁ የነበረው አይኔን ጨፍኜ ነበር!!"አለው።

# NB በህይወታችን ለሚናከናውናቸው ነገሮች ሁሉ ጥበብ ያስፈልገናል።እንደ አስተማሪ እንደ ወላጅ እንደ መሪ...ወዘተ ለአንዳንድ ነገሮች አይናችንን መጨፈን አለብን ምክንያቱም ሁሉም ጥፋቶች በቅጣት ብቻ አይታረሙም!!!!

@wegoch
@wegoch
@paappii

#ግጥም አብዮት
መቼም ጊዜ የማያሳየን ጉድ የለም።
ዛሬ የ you tube ከርስ ውስጥ ገብቼ አንጀቱን ሳማስል ቆየሁ። ከሁሉም ከሁሉም ግርምቴን የወሰደው የ 90 ዎቹ ሙዚቃ ነበር ። ሙዚቀኛ አቤል ነይ ማታ ማታ የሚለውን ሙዚቃ መለስ ብላችሁ እዩት እስቲ?
አቤሎ ያደረገው ከርፋፋ ሱፍ አነስ ያለ ዩንቨርስቲ ተምረው ለመመረቅ የተዘጋጁ 5 ተማሪዎችን ጥንቅቅ አድርጎ ያስመርቅ ነበር😊 ... አቤት የሱፍ ግፍ! ጓዶች በ 90 ዎቹ ጊዜማ የሱፍ ጨርቅ ላይ ግፍ አቆይተናል። እዛ የሰራነው ግፍ ነው ዛሬ ሱፍ ልብስንም የሱፍ ቆሎንም ያስወደደብን 😭
ወደ አቤሎ ሱሪ አዘቅዝቄ ተመለከትኩ።
ሱፍ ዑመር ዋሻማ ምን ይሰፋል? እንዝርት ለምታክል ቅልጥም የደብረ ብርሀን ብርድ ልብስ የሚያህል ጨርቅ ሱሪ ገድግዶበታል።
ወያኔ ምሽግ ሳይሰራ የቀረው እሱ ሱሪ ውስጥ ብቻ ነበር 😜
ደግሞ ሁሌ ሁሌ የሚል የሀይልዬ ክሊፕ አለ። በሰዓቱ ብዙ እይታ አድርጎ የሰቀለው ቪድዮ ላይ የሚደንሱ ሴቶች ሁለቴ ራመድ.. .ሶስቴ ወደ ኋላ መለስ እያሉ ይጨፍራሉ ። ደግሞ አሰላለፋቸው የኮንሶ ወረዳ ካዘጋጃቸው እርከኖች ፈፅሞ አይለይም።
ወደ ሌላ ሙዚቃ ተሸበለልኩ።
አሸንፈን...አሸንፈን...በማራቶን 😃
ወይኔ ወንድሜ ጆሲ !
የራሱ ትልቀትና የሰውነቱ ቅጥነት የሚመጠጠውን ከረሜላ ቁጭ!
ጀላቲም እንደመምሰል ይላል ። ፈረንጆች ይሄን አይተው ኖሯል ለካ እናንተ ጠኔያሞች ብለው የሚሞሸልቁን።
ነይ በክረምት የሚለው የመስፍኔ ሙዚቃ ለጥቆ መጣ ። የዳሎል ጨው !
ጭው ያለ ፊት ... የኢትዮጵያን መከራ የተሸከመ ፊት...ጦርነት ፊት ። ንግድ ባንክ ፊት ... ከዚህ እስከዛ ፊት ...ከዛ እስከዚህ ፊት 😄 ይሄም ቢሆን ግን የእናት አሜሪካ ውለታ ን መዘንጋት የለብንም። የማክዶናንድ በርገር አጋርነትን መርሳት የለብንም። መስፍኔ እንደገና ተወለደ ! መስፍኔ እንደገና አበበ ። መስፍኔ ከጨው ፊት ወደ ፓሎኒ ኳስ ፊት ያሸጋገርክልን ጌታ ክሪሺና ምስጋናህን ውሰድ 🙏
ትንሽ ቆየት ያለ የፍቅራዲስ ሙዚቃ ደግሞ ዠመረ ። ብትን ጨርቋ ብትንትን ብሎ መሬት ላይ ፍስስ.. .ስጋ ያልያዘ ፀጉራም ፍየል ቁጭ! ዛሬ እድሜ ለጊዜ ይሁንና የፍቅርዬ ቻፓ ወንዱን ሁሉ እያማለለው ይገኛል /አበበ ብርሀኔ አፉ ይበለኝና ቻፓዋ ግን ይመስጣል! /
ቴዲ አፍሮን ብነካ ጀማው ይነክሰኛል እንጅ የሆነ ዳፍንታም መነጥር አድርጎ ለማን ልማሽ እያለ መሞዘቁን ላሽ ልል አልፈልግም። ለዛ ክሊፕ ሳይሆን ለብረት ቤት ብየዳ አገልግሎት ነበር ያ መነጥር መዋል የነበረበት ።
ከአፍታ በኋላ ቴድዮ ከተፍ አለች ። ጡት ከጣለ ሳምንት ያልሞላው ምስኪን ራፐር ። የጉራጌ ቶን ምናምን 😁 ክሊፑ ላይ ሲደንስ ሳየው እንደ ወፍ እንዳይበር እንዴት እንደፈራሁለት ብታዩ!
በሰው ይሄን ያህል ስቄ ከ አራት ዓመታት በፊት የተነሳሁትን የራሴን ፎቶ አየሁት ።
በዛን ጊዜ ሉሲን አገኘኋት ያለው አንትሮፖሎጂስት እኔ አይቶ መሆንማ አለበት !
እህል ከቀመሰ ዓመታት ያስቆጠረ ነብይ ይሄን ያህል አይሞግግም። ስማር ነበር ወይስ ተማሪዎችን ፉጨት ሳስተምር ነበር ? በሚል ጥያቄ ትንሽ እንደተወዛገብኩ.. . የመሰረት መብራቴ ድራማ ሰተት ብሎ ላፕቶፔ ስክሪን ላይ ተገሰጠ ። መሲ የኔ Philps ከጥንት እስከ ጠዋት አንድ አይነት ፊት።
አባቴ በጋን ቁልፍ ጠርቅሞ ሲጠቀምበት የኖረው Philips ካውያ ዛሬም ድረስ አዲስ መሆኑን አስቤ ፈገግ አልኩኝ።
አባዬ ካውያውን ዝም ብሎ ሲያየው ይቆይና አይ የድሮ እቃ! ይላል በግርምት ። በነገራችን ላይ እሷን ካውያ የነካ አይደለም የቁም ሳጥኗን ቁልፍ በእጁ የያዘ የቤተሰቡ አባልን አባዬ በርግጫ እንደ ኳስ ያነጥረው ነበር ። ቀልቃላዋ ታናሽ እህቴ ስንት ጊዜ በረንዳውን ተሻግራ የግቢው አበባ ላይ እንዳረፈች እኔ ብቻ ነኝ የማውቀው !
ሸሚዙን ጠረጴዛ ላይ ጥሎ ካውያውን ከወዲህ ወድያ ሲያንገላታው መሲዬ ን ያሰቃያት እየመሰለኝ በልቤ አዝንበት ነበር :)

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Mikael aschenaki
Forwarded from WORDS
"The secret of your future is hidden in your daily routine."

@words19
#የህልም ፍታት - ከአመታት ወደ ቀናት

ክተታችን ደርሶ እየመታነው እንገኛለን። አዲስ ነገርን አስበን ብዙ አስበን ሩቅ አልመን ያዘጋጀነውን አጣፍጠን የሰራነውን ማዕድ ብትቀምሱ ለብርዱም ኩታችሁን ደርባችሁ የኪነ-ጥበብ ማዕድ ላይ ብትቋደሱ እያልን ስንጋብዝ። ገጣሚው ቃሉን ሰድሮ ሙዚቀኛውም ዜማውን ወጥሮ የሰራውን ማዕድ ቅመሱልኝ ብሎ ስለተጣራ ሁላችሁም በጠራነው ክተት ተከታችሁ ነሀሴ 23 ፒያሳ በሚገኘው hi5 coffe house እንድትገኙ እንላለን። ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ የእሽቅድምድም ጉዳይ እና ቀድሞ ብታ የማስያዙ ጉዳይ ይታሰብበት ልንል እንወዳለን። ኩታችሁን ደርባችሁ አልያ በሀገር ባህል ልብስ አሸብርቃችሁ ኑልን እኛም ጎንበስ ብለን እንቀበላለን።

ሁላችንም ግብዣውን እናድርስ
share
እውነት እብዱ ማነው?
ክፍል - ሁለት
(የመጨረሻ ክፍል)

አባዬ፣ አለወትሮዋ የጠዋቱ ብርድ እና ዝናብ ከአልጋ አላላቅቅ ብሏት ተኝታለች። ሰዓቱን
ስትመለከት ሶስት ሰዓት ገደማ ስለሆነ እንደምንም ብላ ተነስታ ወደ ማርያም ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ሳያልቅ ለመድረስ ተጣድፋለች። በዚያ ላይ ከልጆቿ መካከል አራቱን የወለደችው በባለወልድ ቀን ስለሆነ ለባለወልድ የተለየ ስሜት አላት። "አዬ የኔ ጉድ፣ ለዛውም በባለወልድ ቀን እንዲህ ላርፍድ?" እያለች ነጠላዋን ተከናንባ ከወጣቷ ልጇ ሚሚ ጋር አውራ መንገዱን ተሻግረው ወደ ማርያም የሚያስገባውን መንገድ ሲጀምሩ ከአንድ ግቢ ውስጥ የሚጮኹ፣ የሚንጫጩ፣ የሚተራመሱ ሰዎች ሲመለከቱ በድንጋጤ እየተጣደፉ ወደ ውስጥ ሲዘልቁ ሁለቱም በአይናቸው ያዩትን ማመን አልቻሉም…በግቢው ውስጥ ያለው አብዛኛው ሰው ፈራ-ተባ ባለበት ወቅት አባዬ አለፍ ብላ የማትናገር የማትንቀሳቀሰዋን ሕጻን አንስታ በሕይወት ትኑር ትሙት ለማወቅ ትንፋሿን ለማዳመጥ ሞከረች። ከሌቱ ስምንት ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ ሶስት ሰዓት ድረስ ለዘለቁት ሰባት ወይም ስምንት ሰዓታት ገደማ በዚያ አይነት ሁኔታ የቆየችው አራስ ልጅ አሁንም እስትንፋሷ አለ፡፡ በምን እንደተቆረጠ የማይታወቀው ቁራጭ እትብቷ አሁንም ሳይታሰር ጠልጠል እንዳለ ነው፡፡ አባዬ ሕጻኗን ለሚሚ ሰጥታ እየሮጠች ወደ ቤቷ ተመልሳ መጠራረጊያ እና ማቀፊያ የሚሆኑ ልብሶች ይዛ መጣች፡፡ ልጅቷን ሲጠራርጓት በጣም የገረማቸው ነገር ከጭቃ በቀረ ምንም አይነት ደም የቀላቀለ ነበር አልነበረባትም፡፡ ምናልባትም እናትየው ከወለደቻት በኋላ በዝናቡ ውስጥ መንገድ ላይ ዘለግ ላለ ጊዜ ይዛት ስለቆመች ዝናቡ አጥቧትም ሊሆን ይችላል፡፡ ያም ሆኖ ግን ጭቃዋ ሲጠራረግ ልቅም ያለች ቀይ ልጅ ብቅ አለች፡፡ ‹‹ፀጉሯ ግንባሯ ድረስ ድፍት ብሎ ቻይና ነበር እኮ የምትመስለው…›› ትላለች አባዬ ለኔ ባወራችኝ ጊዜ እንኳን ሶስት ዓመት ወደ ኋላ ተመልሳ በትዝታ፡፡ የግቢው ባለቤት፣ አባዬ እና ሚሚ ልጅቷን ከበው ምን እንደሚያደርጉ ለአፍታ መምከር ጀመሩ፡፡ ‹‹ለመንግስት እንስጣት ይሆን እንዴ…? ምን ይሻላል…? ምንስ እናድርግ…?›› ይላሉ
የግቢው ባለቤት፡፡ ‹‹አዪ ለመንግስት ብንሰጥስ ምን ይበጃታል ብለሽ ነው…? መጀመሪያ ግን ወደ ጤና ጣቢያ መውሰድ አለብን… ሌላውን በኋላ እናያለን…›› አሉ አባዬ ልባቸው የሚነግራቸው ሌላ መፍትሄ እንደሆነ በውስጣቸው እርግጠኛ ሆነው፡፡ መጀመሪያ ግን የልጅቷን ሕይወት ማትረፍ እንደሆነ ስለገባቸው ወደ ጤና ጣቢያ ለመውሰድ እየተሰናዱ፡፡ አባዬ በቃል አያውጡት እንጂ በልባቸው ያለውን አሳብ ምንም ሳይዘገይ ነበር ሚሚ ያቀበለችው፡፡ ይህ ሲሆን ሚሚ ነበረች የተጠራረገችውን ልጅ በማቀፊያ ይዛ የነበረችው፡፡ ‹‹አባዬ ይቺን ልጅማ ለማንም አንሰጥም… እኛው እናሳድጋታለን…›› አለች ፍጹም ፍርጥም ባለ እርግጠኝነት እና ስስት በእቅፏ ያለችውን አራስ ቁልቁል ትክ ብላ እያየች…‹‹ይሁን እኔም እንደሱ ነበር እያሰብኩ የነበረው… በይ ወደ ጤና ጣቢያ እንውሰዳት መጀመሪያ… በጣም ደክማለች…›› ብለው እየተጣደፉ ወደ ጤና ጣቢያ ሄዱ፡፡ ጤና ጣቢያ ደረሱ፡፡ ቁራጭ እትብቷም ተቋጠረ፡፡ ሙቀቷ 27 ዲግሪ ስለነበር በወቅቱ የነበረችው ሐኪም ወደ ማሞቂያ ክፍል እንድትገባ አደረገቻት፡፡ ሕጻኗ እየቆየች የበለጠ
ነፍስ እየዘራች ብትሄድም አንድም ጊዜ ስላልጠባች ጉዳት እየገጠማት ስለሆነ እነ አባዬ እብዷ ወዳለችበት ተመልሰው መጥተው እንዴት አድርገው እናትየውን አግባብተው በመውሰድ ልጅቷን እንድታጠባ ለማድረግ ከሰፈሩ ሰዎች ጋር ይመክራሉ፣ ይህ ሲሆን ተሲያት ሆኗል፡፡ የሚሚ ስልክ አቃጨለ፡፡ ሐኪሟ ነበረች… ‹‹ሐሎ አለች ሚሚ…›› ምናልባትም መጥፎ ዜና ልትነግራት የደወለች መስሏት እንደመደንገጥ ብላለች፡፡
‹‹ሐሎ… ምንድን ነው በዚያው የጠፋችሁት…እዚህ አምጥታችሁ ጥላችሁ የሄዳችሁትን
መጥታችሁ ውሰዱ እንጂ… ማን ላይ ጥላችሁ ለመሄድ አስባችሁ ነው…›› እያለች
አበሻቀጠቻት፡፡ ‹‹ስሚ የኔ እህት… እዚያ ጥለን የሄድነው ዕቃ አይደለም… የሰው ልጅ ነች እሺ…!?
እንዲህማ ልትናገሪ አትችዪም እሺ…! ለማንኛውም አሁን እንመጣለን ሌላ ትርፍ ነገር
አትናገሪ…›› ብላ እሷም አስታጠቀቻትና ወደ ጤና ጣቢያው ተመለሱ፡፡ እብዷም በዚህም በዚያም ተወስዳ ልጅቷን ባታጠባም ቢያንስ ኤች.አይ.ቪ እንድትመረመር ተደረገ፡፡ የፈጣሪ መልካምነት ማለቂያ አልነበረውምና እናትየው ከቫይረሱ ነፃ መሆኗን ሲያውቁ ለሁሉም ትልቅ እረፍት ነበር፡፡ ልጅቷን የማጥባቱ ነገር ግን የሚሆን ስላልሆነ
ከአመሻሹ 11፡00 ገደማ የፎርሙላ ዱቄት ወተት ተገዝቶና በጡጦ ተበጥብጦ ልጅት አፍ ላይ ሲደረግ በርሃብ ስትናጥ የነበረችው ሕጻን ወዲያው መጥባት ጀመረች፡፡ አባዬ ትልቅ
እረፍት እና ደስታ ተሰማት፡፡ የሚገባውን ጊዜ ወስደው፣ ልጅቷ በሙሉ ጤንነትና ጥንካሬ ላይ ስትሆን አባዬና ሚሚ ልጃቸውን ይዘው ወደ ቤታቸው ገቡ፡፡ ለአባዬ ትልቅ ትዝብት የነበረው ነገር እና እስካሁን ስታወራው እጅግ እየከነከናት ያለው ነገር አንዳንድ ሰዎች፣ የጤና ጣቢያዋን ሐኪም ጨምሮ የተናገሩት ነገር ተመሳሳይ እና እጅግ ኢሰብዓዊ የመሆኑ ነገር ነበር፡፡ ‹‹እንዲህ አይነቱ ልጅ ሲገኝስ ወስዶ ማሳደግ ነበር…! ግን ምን ዋጋ አለው… ሴት ሆነች እንጂ…! ወንድ ቢሆን ኖሮ ቢያንስ ቤት ይጠብቃል… ወይም ጥሩ እረኛ ይሆን ነበር… እያሉኝ እኔ ግን ልጄን ይዤ ስመጣ በጣም ነበር ደስ ያለኝ…›› ትላለች አባዬ አሁንም በጥልቅ ትዝብት የሰዎቹን ክፋት እየታዘበችና ወደኋላ እየተመለሰች፡፡ "ልጄ" ብላ ነው የምትጠራት። አባዬን ላስተዋውቃችሁ…?
አባዬ አክስቴ ነች… የእናቴ ታናሽ እህት… ከመንታ የማትተናነስ ቁርጥ እናቴን መሳይ…ከቁመና እስከ ፊት መልክ… ከድምጽ እስከ ውስጠ ስብዕና…! ላለፉት 14 ዓመታት አባዬን ባየሁ ቁጥር ስሜቱን ለማስተናገድ እጅግ ከባድ ነበር ለኔ፡፡ እናቴ ከሙታን ዓለም መጥታ የምታናግረኝ እስኪመስለኝ ድረስ ነበር መመሳሰላቸው… ድምጻቸው… ስብዕናቸው…እርጋታቸው… ጥርሳቸው… ጣቶቻቸው… ምኑ ቅጡ…!እናም አባዬን ለመጨረሻ ጊዜ ያየኋት ሌላኛዋ አክስቴ በሞተች ወቅት ለቀብር እዚያች ከተማ በሄድኩበት ጊዜ ነበር፡፡ እሱ ደግሞ ጊዜው ዘለግ እያለ ስለመጣ የሆነ ቀን ታላቅ እህቴን አብረን ሄደን እንደምንጠይቃት እንደዋዛ ቃል ገባሁላት፡፡ እህቴም የዋዛ አልነበረችም አውቃ ቀን አስቆረጠችኝ፡፡ እኔም ተስማማሁ፡፡ ቀኑ ደረሰና ከመጓዛችን በፊት ባለቤቴም የጉዞው ተሳታፊ እንደምትሆን አሳውቃን እጅግ ደስ የሚል ጉዞ አደረግን፡፡ አባዬን እና ሌላኛዋን አክስቴን እንዲሁም ዘመድ አዝማድን ከማየት እና ከመጠየቅ በዘለለ እንዲህ አይነት ተዓምረ ክስተት እመሰክራለሁ ብዬ ፍፁም አላሰብኩምም አልገመትኩምም ነበር፡፡ ቅዳሜ ተሲያት በኋላ ነበር የደረስነው፡፡ መምጣታችንን ቀድመን አሳውቀን ስለነበር ምንም ነገር ሳይጎድል ሁሉ ሙሉ ሆኖ ነበር የጠበቀን፡፡ ደስታው ልዩ ነበር፡፡ የአክስቶቼ ስስት የሚዘገን የሚታፈስ ነበር፡፡ እናቴን እያስታወሱ ለማለቃቀስ ሞከር አድርጓቸውም ነበር እኔ ኮምጨጭ ብዬ መለስኳቸው እንጂ፡፡ እነሱ እንደሁ እናቴን አንስተው ለማልቀስ ጥንጥዬ ነገር በቂያቸው ነች፡፡ በዛውም እንደ ወናፍ እስክወጠር ድረስ ‹ዘመድ ጠያቂና ቁምነገረኛ› መሆኔ ተደጋግሞ
ሲነገረኝ፣ ስመሰገን፣ አሁንም አሁንም ስመረቅ እንደ መነፋፋትም ቢጤ ሞክሮኝ ጎምለል ማለቴ አልቀረም፡፡ ቤቱ ውስጥ የአክሰቶቼ ልጆች፣ ጎረቤት፣ ተጨማሪ ዘመድ አዝማድ ውር ውር ይላል፡፡
ከሁሉም አይኔን የሳበችው ግን አንድ ጊዜ ‹እማዬ› አንድ ጊዜ ደግሞ ‹አባዬ› እያለች የምትጣራ እና ሙልቅቅ ብላ አባዬን አላንቀሳቅስና ከሰው አላስወራ የምትለው ሕጻን ልጅ ነበረች፡፡ ሕጻኗን የ3 ዓመት ልጅ ገደማ መሆኗን መገመት ከባድ አልነበረም። የሚገርመው ግን ከ10 ቀን በኋላ ልክ 3 ዓመት የሚሞላት ልጅ መሆኗ ነበር፡፡ እሷ ማለት ደግሞ ያቺው ከላይ የተረኩላችሁ ተዓምረ-እግዚአብሔር ናት… "ሚጡ" እንበላት ለወጋችን ያክል፡፡ አባዬ እናቴ በምትጠራኝ ስም ‹በልዬ› እያለች ነው የምትጠራኝ፡፡ ሌላኛዋ አክስቴ ደግሞ ‹ጥላሁን› ነው የምትለኝ፡፡ በውስጤ ጥያቄ እንዳለ የገባት የመሰላት አባዬ ከምሳ በኋላ ቡና እየጠጣን በጨዋታ መሃል…‹‹ይኸውልህ በልዬ በስተርጅና ይቺን የመሰለች ልጅ ወለድኩ…›› ብላ ወሬ ከመጀመሯ ተዓምሪቷ ሚጡ አሁንም አላስወራ አለቻትና ከወሬው አናጠበቻት፡፡ ወዲያውም ደግሞ ለጠየቃትም ላልጠየቃትም ስሟን እስከ አያቷ ድረስ ደጋግማ መጥራት ትይዛለች፡፡
‹‹ማነው ስምሽ አንቺ…›› ሲሏት…‹‹እኔ… ሚጡ… አቡሽ… አባባ…›› ትላለች አሁንም አሁንም የራሷንም፣ የአባቷንም፣ የአያቷንም ስም ሳታዛንፍ በልጅ አፍ በትንሹ ኩልትፍ እያለችና ፊደላቱን እየጠራች፡፡ በአባትነት የምትጠራው አቡሽ በጥቂት ዓመት የሚበልጠኝን የአባዬ የመጨረሻ ወንድ ልጅ ነው፣ በአያትነት ደግሞ የአባዬን ባል (የአቡሽን አባት)…! ግራ መጋባቴ ቀጥሏል፡፡ አቡሽ የሚኖረው አሜሪካ እንደሆነና ይቺ ልጅ ከመወለዷ ብዙ ዓመት በፊት አግብቶ ልጆች
እንደወለደም አውቃለሁ፡፡ ግራ ገባኝ፡፡ አባዬ ወደ ጓዳ ሄድ ስትል… እህቴ ላይ የጥያቄ ፊት ዘረገፍኩባት፡፡ ይህን ያወጋኋችሁን ታሪክ እህቴ ከሌላኛዋ አክስቴ ልጅ ጋር ሆነው ፈጠን ፈጠን እያሉ ተጋግዘው በአጭሩ ነገሩኝ፡፡ ግፋ ቢል ከአምስት ደቂቃ ባልበለጠ ጊዜ አጠናቀቁት፡፡
‹ይህንንማ ከራሷ ከአባዬ ሙሉ ዝርዝሩን ካልሰማሁ በቀር አይሆንም…› አልኩና ለምሽት የእራት ላይ ጨዋታ አቆየሁት፡፡ አላስቻለኝምና እራት ገና እራት መብላት እንደጀመርን አነሳሁላት…‹‹አባዬ… ምንድን ነው ቅድም እኮ ስለዚህች ሕጻን ልጅ እንዲህ እንዲህ አሉኝ… ኧረ
እንደው ሙሉውን ንገሪኝ አባይዬ…›› ብዬ ጀመርኩ፡፡ ‹‹አይ በልዬ… የሷ ነገርማ ተዓምር ነው፡፡ ይሄ እናንተ በምታነቡት መፅሐፍ ውስጥ ራሱ ቢፈለግ አይገኝም…!›› አለችና ጀመረች፡፡ ‹ይሄ የምታነቡት መፅሐፍ ውስጥ አይገኝም›
ማለቷ በልብ-ወለድ እንኳን የማይታሰብ ነው ለማለት ነው፡፡ የንጽጽሯ ጥልቀት የገባኝ ታሪኩን ከጨረሰችልኝ በኋላ ነበር፡፡ Stranger than fiction የሚልና በጣም ወድጄ የተመለከትኩትን አንድ የሆሊዉድ ፊልም አስታወሰኝ አገላለጿ፡፡ ድንቅ ነበር ንጽጽሩ…!ለታሪኩ ስክት ብሎ የሚገባ ጠቅላይ ዐረፍተ ነገር…!ከዚያም ቀስ እያለች እስከላይ ድረስ የነገርኳችሁን ተረከችልኝ፡፡ የሰሙት ሁሉ እንደ አዲስ አደመጡ፡፡ አንዳንዴም በየመሃሉ እየገቡ ጨማመሩበት፡፡ ባለቤቴ በተፈጥሮ ያላት ቦጅቧጃ ስብዕና ላይ እናትነት ተጨምሮበት ፊቷን ለመግለጽ በሚከብድ ስሜት አብራኝ አባዬ አፍ ላይ ተተክላለች፡፡ እኔም በየመሃሉ ለማመን የሚከብደኝን ነገር በጥያቄ ማጣደፌ አልቀረም፡፡ ደጋግሜ የምጠይቃት ግን እንዴት ከሌቱ ስምንት ሰዓት ጀምሮ እንደዚያ ሆና በሕይወት ተረፈች…? እንዴትስ እስከ ማታ 11፡00 ድረስ ጡት ሳትጠባ ልትተርፍ ቻለች…? እንዴትስ
እትብቷ በዚያ መልክ ተበጥሶ እና ሳይታሰር ተረፈች…? እናትየውስ እንዴት ተረፈች…? ማለቂያ አልነበረውም ጥያቄዬ፡፡ ‹‹አይ በልዬ እንደሚሉትማ እትብት በ30 ደቂቃ ወይም ቶሎ ተቆርጦ ካልተቋጠረ ልጅ ይሞታል ይባላል፡፡ በዚያ ላይ ብርዱ፣ ዝናቡ፣ ጡት አለመጥባቱ፣ እንደዛ በጭቃ እያድበለበለች ስትጫወትባት አድራ በሕይወት መትረፏ ሌላ ምን መልስ አለው በልዬ…የፈጣሪ ስራ ነው እንጂ! የእመቤቴ ማርያም ስራ ነው እንጂ! የባለወልድ ተዓምር ነው እንጂ በልዬ! የሚገድልም የሚያድንም አንድ ፈጣሪ እንጂ እንደ ሰው ግምትማ መች ትተርፍ ነበር…!» የሚል ነበር መልሷ። አባዬ ይህን ስትለኝ በወቅቱ አንቀጹ ትዝ ባይለኝም ድሮ መፅሐፍ ቅዱስ ላይ ያነበብኩት አንድ ጥቅስ ትዝ አለኝ፡፡
‹‹አሁንም እኔ ብቻዬን እኔ እንደ ሆንሁ፥ ከእኔም በቀር አምላክ እንደሌለ እዩ፤ እኔ እገድላለሁ፥ አድንማለሁ፤ እኔ እመታለሁ፥ እፈውስማለሁ፤ ከእጄም የሚያድን የለም።›› ዘዳግም ምዕ.32፣ ቁ.39፡፡ እውነትም ይህን ጥቅስ ከማመን ውጪ ሌላ ሰውኛ ማብራሪያ ለመስጠት ከባድ ነውና
እኔም በፈጣሪ የማያልቅ ተዓምር ተደምሜአለሁ፡፡ እኔ በማምነው መንገድ በፈጣሪ ላይ ያለኝን እምነቴንም ይበልጥ አጠናክሮታል፡፡ አባዬ ብዙ ካለችኝ በኋላ ታሪኩን እያጠቃለለች ነው፡፡ ‹‹እናልህ በልዬ… እቤት ከመጣን በኋላ አቡሽዬ ሲደውል ነገርኩት፡፡ ‹አቡሽዬ… ይኸውልህ
በስተርጅና ሴት ልጅ ወለድኩ› አልኩትና ታሪኩን ስነግረው እጅግ ተደስቶ ለየዘመዱ እየደወለ ‹አባዬ ልጅ ወልዳለችና እንኳን ማርያም ማረሽ በሏት…› እያለ ሰዉን ሁሉ ግራ አጋባው፡፡ ወዲያውም የሚያስፈልጋትን በሙሉ እሱ እንደሚያሟላ እና የአባትነት ኃላፊነቱን እንደሚወስድ ቃል ገብቶ ይኸውልህ ሚጡም በሱ ስም ትጠራለች… እሷም አባትሽ ማነው ስትባል አቡሽ ትላለች…›› አለችና ተነስታ ከፎቶ ማህደሯ ውስጥ ከልጅነቷ ከምሮ ያስነሳቻትን ፎቶዎች አምጥታ ሰጠችኝ፡፡ እየተቻኮልን እና እየተቀማማን ተመለከትነው፡፡ ገና የወር ዕድሜ ሳይሆናት ጀምሮ በየጊዜው የተነሳቻቸው ፎቶዎች ልዩ ናቸው፡፡ የአንድ ዓመት እና የሁለት ዓመት ልደቷ ሲከበር ድል ያለ ድግስ እንደነበረው መመስከር ይቻላል፡፡ ሁለት ፎቶዎች ትርፍ ቅጂ ስለነበራቸው አባዬን ለምኜ ፈቀደችልኝና ወሰድኳቸው፡፡ ከሁሉም ግን የልደት ፎቶዎቿ ይለያሉ…‹‹ይገርማል፣ በተለይ ለልደቶቿ ትልቅ ድግስ ነው ያደረግሽላት አባዬ…›› አልኩ፡፡ ‹‹እኔ አይደለሁም በልዬ… የሚገርምህ ልጅቷ ከዚህ ሁሉ ታሪኳ ቀጥሎ የሚገርመኝ በብዙ ነገር ዕድለኛ ነች፡፡›› አለችና በሁለቱ ልደቶቿ ወቅት ድግሱ እንዴት ሊያምርላት እንደቻለ የተከሰቱትን ድንገቴዎች አወራችኝ፡፡ ‹‹ይኸው አሁን ደግሞ ሶስተኛ ዓመት ልደቷ መጪው ባለወልድ ነው ከ11 ቀናት በኋላ፡፡ ነገር ግን ሚሚ መጪው ማክሰኞ ወደ አዲስ አበባ ስለምትሄድ ልደቷን ቀድመን እናክብር ብለን ነገ ልናከብርላት ወስነን ነበር፡፡ እኔም ቤት ባፈራው የሆነውን አደርጋለሁ ብዬ እንጂ በግ አርዳለሁ ብዬ አላሰብኩም ነበር፡፡ ይኸው ዕድለኛ ነች ብዬህ አልነበር… አምላክ ደግሞ ምንም የማታውቀውን አንተን በግ አስገዝቶ ላከላት… ታዲያ ከዚህ በላይ ዕድለኝነት
አለ…? ኧረ የሷስ ድንቅ ነው በልዬ…›› አለች፡፡
እንዳለችውም እኔ እጅ መንሻ ብዬ የወሰድኩላቸው በግ በነጋታው ዕለተ እሁድ ታርዶ፣ የልደት ግብዓቶች ሁሉ ተሟልተው ትልቅ ድግስ ሆኖ የሚጡ 3ኛ ዓመት ልደት በድምቀት
ተከበረ፡፡ ድንቅ እኛም እሁድን አድረን ሰኞ ወደ አዲስ አበባ ተመለስን…! ማክሰኞ ማታም ይህንን ታሪክ ማካፈል ጀመርን…!እነሆ ዛሬ ዕለተ ረቡዕም ለመደምደም እየተንደረደርን ነው…!
***
መውጪያ…
(እስቲ ደግሞ ጥቂት አብረን እንናደድ) እብዷን የደፈራት ሰው በአደባባይ የሚታወቅ ጤነኛ ሰው ነው መባሉን ስሰማ በመጀመሪያ የተሰማኝ ስሜት "ምናለ ፈጣሪ ያን የሚደፍራትን ሰው እጅ ከፍንጅ ቢያሲይዘኝ…" የሚል ነበር፡፡
‹‹እንዴት ነው ግን ከዚያስ በኋላ አንድ ሰው እንኳን ወይም የከተማው አስተዳደር ራሱ በግድም ቢሆን ወስዶ የወሊድ መቆጣጠሪያ የማያስደርግላት…! አሁንስ ቢሆን ምንድን ነው ዋስትናዋ በድጋሜ እንደማይደፍሯት?›› ብዬ ፈርጠም ብዬ ጠይቄ ነበር፡፡ አሁንም ያቺ ደግ አክስቴ ያደረገችውን ነገረችኝ፡፡ ‹‹አይ በልዬ… እሱማ ከዚያ በኋላ እንደምንም ብዬ ይሄ ክንድ ላይ የሚቀበረውን የ4 ዓመት የወሊድ መከላከያ አስደርጌላት ነበር፡፡ የሆነ ቀን ራሷ ቆፍራ አወጣችውና ጣለችው፡፡ ይኸው ይግረምህና… አሁንም ነፍጠ-ጡር ነች… ፈጣሪ የስራውን ይስጠው እንዲህ ያደረጋትን እንጂ ምን ይባላል…›› ብላ በቁጭት ተነፈሰች፡፡ እብዷ አሁንም ሁለተኛ ነፍሰ-ጡር ነች፡፡ ይህንን ስሰማ እንዴት እንደነዘረኝ የማውቀው እኔ ነኝ፡፡

"ጨርሰናል"

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Tilahun abebe
እስስት : ስትጎተትና : ስትቀያየር እንደምትጠላ : አታውቅም : አካሄዷም : ቢሆን ፥ አይኗ : ልቧን : ይመራዋል : እንጅ ልቧ : አይኗን : እንደሚከተለው : አታውቅም.....
ግንኮ : አይን : ያየውን : ለልብ : ካልነገረው : ልብም : አድምጦ : ካላመነበት : አይንን : ይከተለዋልን?

መቼም አንዴ ለጉዞ ፈጥሮኛልና መንገድም : እወድ የለ .....
በጉም : ላይ : እየተረማመድኩ : ሳለ ብቻዬን : አግዜሩን : አግኝቸው : ነበር : በምናባዊ : ፀዳል እንደምናስበው : አደለም : ኮስማና ነው።

እናተ : ሰዎች: ለምን : ትጠሉኛላችሁ : ስለምንስ ከክብሬ : ቁልቁል : አፈረጣችሁኝ : ማቅለላችሁ : ሳይቀር : ለሌሎች : መሳለቂያ : አረጋችሁኝ ፥ ከዙፋኔ እያለሁ : እንደሌለሁ : አበሸቀጣችሁኝ ለምን? ስለምንስ? ተጠራጣሪ : ሆናችሁ : በኔ ለምን? እንባ እንቅ እንባ እንቅ ,,,,,
እያረገው : ሶስት : የእንባ : ዘለላ :ከገፁ ፥ ሲረግፍ እየሁ።

እንባው ፥ ወደስቅለቱ : ትዝታ : እያላጋ : ወሰደን በስቅለቴ : ግዜ አንድ : ደንባራ : ወታደር : በጦር ጎኔን ሲወጋኝ : ህመሙን : አታውቅም : ይሁዳ : በከንፈሮቹ ሀሞት : ተጎንጭቶ : ጉንጨ : ላይ : ሲተፋብኝ : የተሰማኝን : አታውቅም : ጴጥሮስ : ሶስት : ግዜ : አንድ ለአብ አንድ ለወልድ አንድ ለመንፈስቅዱስ ለያንዳንዳችን : በአንድነት : የክህደትን : ኮሶ : ሲያግተን : ምሬቱን : አታውቅም።

40 ቀን 40 ለሊት ስፆም ሰይጣን በእባብ ተመስሎ ሲፈትነኝ የፈጠርኩትን መልሶ የኔ ሊያረጋቸው ሲደራደረኝ ቤተ መቅደሴን ሲሻቀጡበት እናቴን ከቁሻሻ መሀል ትቢያ እንደተደፋ ልቅላቂ ሲጠየፏት አታውቅም።

አዎ አታውቅም ........ እናት ሰዎች ህመሙን አታውቁም .........

የእግዜር እንባ ግን ምን አይነት ነው?

እኔም: ሆድ : ብሶኝ : የልቤን : ዘረገፍኩለት :ጌትዬ : በሁለት : አለም : ሰካር : ውስጥ: አየዳገርኩ: ለምን ዝም አልከኝ? አንተኮ: ብትታመምም : አምላክ ነህ የአምላክነትህ : ባህርይ ረቂቅ : ነው ያስችልሀል::

ግን ለምን ፈጠርከኝ? ማጥ: ረመጥ : ውስጥ : ከተትከኝ? እውነት አውጣኝ : ብዬ : ስለምንህ: ሳትሰማኝ : ቀርተህ ነው?
የህይወትስ ጣዕሙ በምን ይለካል ? በድን : አካልን አሸክመኸኝ : ለአመመታት : መክረሜን ዘንግተኸው ነውን?

እኔ : የነካሁት : ሁሉ : ርኩሰትን : እንዲላበስ : ሁሌ እንድሸሸግ : የምታረገኝ : ራሴን : በራሴው እንደ እፉኝን : ስውጥ አላሳዝንህምን?

የእናትህስ : ህመም : አንተን : ብቻ : የሚቆረቁርህ ይመስልሀል?
እሷኮ : አምጣ : አልወለደችህም : ደም : አልፈሰሳትም
ምነው_ቸሩ _መድሀኔ_አለም : የኔዋ : እናት: ወዝ ወዘናዋን : አጠንፍፋ : ባማጠች : የህመሟን ሲቃ ባስረቀረቀች : አኔን : ወልዳ : እንኳ_ማርያም : ማረችሽ ቢሏት : አንተው : የማርካት መሰለህ? በድኩም : አካሏ : ተንፏቃ : አፈር : ልሳ : ብትለምንህ : መች ምሬሻለው : አልካትና? የማርያም ልጅ...!!

አንተ : ብትፆም :ባህሪህ : ቅዱስ : ነህና : ይፈቅድልሀል እኛስ :አንጀታችን :ሲታለብ :ቆርቆሮ :ቤታችን :ውስጥ : በችጋር : ስንለበለብ :ዞር ብለህ : አይተኸናል : እንዴ?
ቅፅበታዊ : ደስታን : አሳይተህ : ዛላቂያዊ : ህመምን ከልባችን : የቸነከርከው : እውነት : ከሳዶርና ፣ አላዶር የሚተናነሱ : ይመስልሃልን?

ተው : እንጅ : ቤዛ ከሉ መድሀኔ አለም..... ተው እንጅ የማርያም ልጅ!!

ተስፋዬን : በምኞት : ደግፌ : ብጓዝ :ባንተ : አይደል የጨነገፈው : ማያዬ :መመልከቻ : አድማሴን : ባገኛት
ባንተም : አይደል : ያጣኃት? እንደኩታ : አይሽሞንሙነህ : ያለበስከኝ : ይህን :ማንነት አንተም አደል : የፈጠርከው ? ይኸው : እሷም /ወደመሸሹ አጋደለች....
እስቲ : ልወቀው : ጥፋቴን :ለምን : ግራ አርገህ ፈጠርከኝ?
ምን ትለኝ ይሆን? ምንስ ምላሽ ይኖርህ?

ግን ለምን አትወስደኝም? ኖሬ : የህይወት : ጣዕሙንስ በምን :ምላሴ : ላጣጥመው? ምላሴን : ቆርጠህብኝ ......ሳላጣጥመው : ኮመጠጠኝ።

ተፈጥሮ : ፊቱን : አጨፍግጎብኝ : ሳለ : ከነፍሴ የተጣባች : እንስትን : ወዳንተ : ልካኝ : ነበር። አንተ የምድርና ፣ የሰማይ : ጌታ : ሆይ : ቸኮሌት : ላክልኝ ብልሀለች።

ከጥሪው : መዝብ : ሳሟ :ሳይሰፍር : ወደኔ መታ የነበረችው : ማያዬን አወካት?

ለነገሩ : አንተ : ብታቅም : አላቅም :ከማለት : ወደኃላ አትልም...... ብቻ እሷ ታቅሀለች።

በቃና : ዘገሊላ :ግዜ : ውሀውን : ወይን : ጠጅ : አድገህ : ነበር : በሰው : ሰርግ : እንደዚ : የሆክ : በራህ : ሰርግ : እንዴት: ትሆን?
በስቅለትህ : ወቅት : ጎንህን : ሲወጉህ : ውሀ፣ ደም፣ ወተት : ፈሶህ ነበር ።

በመጀመሪያ :ቀን : ማያዬን : ሳገኛት : ውሀ ጠጥታ ነበር ።
በሁለተኛው : ቀን : ስንገናኝ : በተፈጥሮ : ደም እየፈሰሳት :ነበረ ።
በሶስተኛ : ቀን : ፈጣሪ : ቸኮሌት : በኔ : በኩል እንዲልክላት : ጠይቃኝ ነበር።

በቸኮሌት: ውስጥ : ወተቱን : ለማግኘት :ፈልጋለው ይሆናላ....


ቸኮሌቷን : አንድቀን : ይዤላት: እንምመጣ :ታውቅ ይሆን?

አታውመቅም.........

የእግዚአብሄርን : ልጅ : ሰርግ : አይቼ : ከድግሱ : በልቼ ጠጥቼ : መሞቴን : እንኳን : አታውቅም..........


አዎ አታውቅመም.....

አደራ
**ንገሩልኝ******

ሱራፌል ጌትነት (ሱራ ቢራቢሮ)

የግማሽ አለም ጣኦት

@wegoch
@wegoch
@wegoch
የተለየ ፍቅር አለ. በቃ ልዩ!... ይህ ፍቅር ሚመጣው ተስፋ ቆርጠህ ባለፈው ፍቅርህ ተደቁሰህ ሁለተኛ ላለመደቆስ ወስነህ ጥግህን ከያዝክ ቦሀላ ነው. መጀመርያ ቦታ አትሰጠውም ቀልድ ታደርገዋለህ ምክንያቱም ከጨዋታው ራስህን አግልለሀላ! ሲቀጥል እስቲ ልየው ብለህ በሶምሶማ የኧሯሯጥ ስልት ታስቀጥለዋለህ... መሀል ላይ የትላንት ቁ ስልህ ትዝ ይልህና ሶምሶማውን ወደ እርምጃ ትቀይረዋለህ. ውስጥህ ግን ይረበሻል.. እኔ ላይ ሆኖ የነበረውን እዚ ሰው ላይ እንደገምኩት ይሆንን? ብለህ... ከዛ ግን ህሊናህን አፍነህ ገድለህ ትረጋጋለህ. ያሰው ግን ሳይቀየር አንድ ቀለም ሆኖ ይቀጥላል. ወጣ ብለህ ትርዒቱን ስታይ እስስቱ ራስህ ሆነህ ታገኘዋለህ. ያሰው አሁንም ላንተ ደስታ ደፋ ቀና ይላል. እያስመሰለ ይሆንን? ደፍሬ ብገባ እጋጋጥ ይሆን? ወይስ ይህ ሰው የተሻለ ነው? እድል ልስጠው ይሆን እንዴ? ብለህ ብዙ ታወራርዳለህ? የዶ/ር እዮብ "የፍቅር ህይወት" ከሚለው መፅሀፍ ላይ ባገኘኸው መለኪያ ሁሉ ትለካዋለህ ከዛ ይመዝንብሀል.... "አይ ይሄ ነገር ይቅርብኝ" ብለህ ለደመነፍስህ እንዲወስን መሪውን ታቀብለዋለህ. ... ሁሉንም መንገድ መዝጋት ትጀምረህ... ትረሳዋልህ ሁላ... ማስተካከል የማይስማማው ጠማማ ትሆናለህ... ከብረት የጠነከረ ልብ ይኖርሀል... ያሰው ይጎዳል ስንት ለሊት ስንት ቀን ያነባል... በስተመጨረሻ "እያለቀስኩማ አልኖርም!" ብሎ የመንገዱን አቅጣጫ ይቀይራል. ድሮ ሲያደርግ የነበረውን ተቃራኒ እያቃረውም ቢሆን ያደርጋል.... ይሄኔ ነው ብረቱ ልብህ ወደ ቄጤማነት ሚለወጠው.... እሱ ያሳለፋት እያንዳንዷ ነገር በአስር ተባዝታ ትሰማሀለች.. የድሮ ህግህን ብትጠቀምም አይሰራልህ...... ተሸንፈሀላ! የድሮ ቁስልህ እንደገና ለመቁሰል ሙሉበሙሉ ይስማማል! ህመምህን ትወደዋለህ! በእብርክክህ እየዳኽክ የገፋኸውን ሰው ትፈልገዋለህ.... ልክ እንደ 'ህል ውሀ. አማራጭ የለህም ሄደህ ትናዘዛለህ! አበቃ! ያም ሰው አይጨክንም. "ለመቅረብ መራቅ!" ሚለን ህግ ተጠቅሞ ኖሮ ያንተን መመለስ ነበር ሚጠብቀማው ፈገግታውን እፊቱ ላይ ፍቅሩን እልቡ ላይ እንደእንጀራ አስፍቶ ይጠብቅሀል. አሁንማ ማን ይቻላቹ! አንድ ላይ ተበርራላቹ.....

ልዩ ፍቅር አለ ያላሰብከው ግዜ የሚመጣ... ህይወትህን ከስር መሰረቱ ጀምሮ በማር ሚለውስ ... ያለፈው ህይወቴ እንዴት እሬት ነበር ብልህ እንድትገረም የሚያደርግህ.... ግን ሳታስበው ሳትዘጋጅ እንዲው ስሜትህ ውርድ ባለበት ሰአት ይከሰትና ዋጋ ያስከፍልሀል.

#በMaggie
@getem
@getem
@paappii
ሻንጣው!
ድሮ አስረኛ ክፍል ተማሪ ሳለን ነፍሰ ቀጭኑ ኬሚስትሪ መምህራችን እንዲህ ሲሉ ጠየቁን ።
“ውሀ ከምን እና ከምን ንጥረ ነገሮች ነው የተፈጠረው ?”
ብዙ ተማሪዎች ይህችን ቀላል ጥያቄ ለመመለስ ተቅለበለብን ። መምህሩ ግን ከሁሉም ተማሪ ይልቅ
ትኩረታቸውን ስንሻው ላይ አድርገው እንዲመልስ አስገደዱት ።
ስንሻው ከእንቅልፉ የተነሳ ይመስል አይኑን አሻሽቶ ትንሽ ቆየና መምህሩ ጥያቄውን እንዲደግሙለት
ጠየቃቸው። /በነገራችን ላይ የስንሻው አባት ልጃቸው ትምህርት እንዳይገባው ተደግሞበታል ብለው
ስለሚያስቡ እሱን ይዘው ያልተንከራተቱበት ፀበል አልነበረም ። ኋላ ላይ ቢታክታቸው ጊዜ እርግፍ
አድርገው ተውት ! እርሱም ትምህርት አይንህን ላፈር ብሎ ማንበብ እና ማጥናቱን እርግፍ አድርጎ ተወው
/
"እኛ የምን ጠጣው ውሀ ከምንና ከምን ውህደት ተፈጠረ ? " ብለው ጥያቄውን ደገሙለት ።
ውሀ ልማት እና ቀበሌ ተዋህደው በገጠሙት የቧንቧ መስመር ነው የተፈጠረው ! ብሎ ሲመልስ ያልደነገጠ
ተማሪ አልነበረም ። ሁላችንም እያሾፈ ነው ብለን በትኩረት አየነው ።
እሱ እቴ !
ልቡ ደጭ እንኳ አላለም ! ሰው እንዴት ይሄን የሚያክል ተራራ ስህተት ሰርቶ ትንሽ ሀፍረት እንኳ
አይሸብበውም ?
“ስ ! ውይ ይቅርታ” አለን መልሶ .... በቃ ኦክሲጂንና ሀይድሮጂን ታውሰውት ነው ማለት ነው ብለን
ማስተካከያውን በጉጉት መጠባበቅ ያዝን ! ስንሻው እጅ አውጥቶ መልሶ ፣ የተሳሳተውን አውቆ ትክክለኛ
መልስ ከመለሰ ዘጠነኛው ሺህ አልፎ አስራ ዘጠነኛው ሺህ ገብቷል ማለት ነው በቃ !
ስንሻው ጉጉታችን ላይ በረዶውን ሊከለብስ
“ውሀ ልማት እና ሰሜን ሸዋ ዞን በመተባበር ነው 🙂“ ብሎ እርፍ አለው ።
ነፍሰ ቀጭኑ መምህራችን በንዴት ተነፋፍተው ነብር አከሉ ! አለ አይደል የቤት ውስጥ ድመት ስትቆጣ
እንዴት ነው ኩፍ የምትለው ?
መምህራችን ኩፍ አሉ ።
በስመአብ !
አስተማሪ ሲናደድ ለካ እንደዚህ ያስፈራል ?ከአስተማሪም ሁሉ ደግሞ ኬሚስትሪ አስተማሪ ሲናደድ በጣም ያስፈራል ። የሆነ ሰልፈሪክ አሲድ
ከላብራቶሪ አንስተው ፊቱ ላይ የሚከለብሱበት ሁሉ መሰለን ። የስንሻውና መምህራችህ መጨረሻ
የተዘጋው ዶሴ ሊሆን ነው ስንል ሰጋን !
“ተነስ !”
ስንሻው ተነሳ ። ደግሞ አነሳሱ እኮ እንደ ንጉስ ክቡር ዘበኛ ቀብረር ኮራ ብሎ ነው ። ግዳይ የጣለ ጀግና
የነብር ቆዳ ለብሶ ቢመጣ እንኳ መቼ ይሄን ያህል ይጀነናል ? ጅ ንን ን ን ቅብርርርርርርርርርርርር
ከሴሽን አንደኛ የሚወጣው ፍቅሩ የሚባለው ቸካይ ተማሪ እንኳ መምህር ሲያስነሳው አንገቱን ሰበር
ያደርጋል እኮ !
ስንሻው ተንጠራራ ........ ደረቱን ነፋ !
“እነ ሚካኤል ፣ እነ እዮብ እነ አቤል ኢንጅነር ወይ ዶክተር ሲሆኑ ሻንጣ ተሸካሚያቸው እንደምትሆን
አልጠራጠርም “ ብለው ሞራሉ ላይ ቀዝቃዛ ውሀቸውን ከለበሱበት ። በቃ ስንሻው ሊተነፍስ ነው አልን !
ደግሞ እኮ እንደፈራነው ከወራት በኋላ ስንሻው ማትሪክን ወደቀ ። እኛ ፈተናውን በጥሰን አለፍን ።
እኛ አስራ ሁለተኛ ክፍል አልፈን ለዩንቨርሲቲ ስንዘጋጅ ስንሻው የሆነ ትምህርት እንደከረሜላ አሽጎ የሚሸጥ
ኮሌጅ ዲፕሎማ መማር እንደጀመረ ሰማን ። አውቶቡስ ተራ አለመሄዱም የመምህሩ ትንቢት እውን
እንዳይሆን ስለሰጋ እንጂ የሱ መጨረሻ ከወያላነት ይዘላል ብሎ ማን ያስብ ነበር ?
ግቢ ሁለተኛ ዓመት ተማሪ ስንሆን ስንሻው ቀበሌ ስራ አጊንቶ መግባቱ ተነገረን ። ያኔ በሱ ሙድ ያልያዘ
አልነበረም ።
እንደውም አንድ ቀን ፍቅሩ የሚባለውቸካይ የነበረ ተማሪ ወደኔ ጠጋ ብሎ "ስንሻው በዚህ ከመሬት አልፎ
ማርስ የምትባል ፕላኔት ላይ እንኳ በማይገኝ ድድብናው ቀበሌ ስራ ማግኘቱም ተመስገን ነው ብሎ
ገለፈጠ ። "ስንሻው እኮ ቀን ስራ እንኳ ይበዛበታል ። እንደ ህንዶች ሰባቴ ቢፈጠር ሰባት ጊዜም ትምህርት
አይገባውም" አለኝ ቀጥሎ ።
ሁላችንም ጎበዝ ተብዬ ተማሪዎች ስንመረቅ ግን የነፍሰ ቀጭኑ ሰውዬ እርግማን ለስንሻው ምርቃት ሆኖ
እርፍ አለው ።
የከተማችን አስተዳደር ተመራቂ ተማሪዎች ተደራጅታችሁ ኮብልስቶን አንጥፉ ምናምን ብሎ በስብሰባ
ሰበብ ሲጀናጀነን ስንሻው ተከብሮ የከተማችን ከንቲባ ሆኖ ነበር ።
ጭራሽ እዛ አመዳችን ቡን ባለ ተመራቂ ተማሪዎች ፊት ቀርቦ ስለ ስራ ፈጠራ ሰፊ ማብራሪያ ሰጠን ።
አቤት የምላሱ ፍጥነት ! አቤት የቃላት ክሸናው ! አቤት የንግግሩ ስድርነት !መጥበሻ ሆኖ የተማሪውን ልብ አቀለጠው ። ከኔ ጎን ተቀምጣ የነበረችው ፀሀይ የምትባል ጓደኛችን
ዛሬውኑ ጀበና እና ስኒ ገዝቼ ስራ ካልጀመርኩ በሚል ሀሳብ ጦዛ ብንንን ብላ ጠፋች🤣
“ ኢንጅነር ነን ዶክተር ነን ብላችሁ አትኮፈሱ የጀበና ቡና ብታፈሉ ትችላላችሁ ። ለምሳሌ ሚካኤል እዮብ
አቤል በኢንጅነሪንግ እና ዶክትሬት ተመርቃችሁ ሰፈር ለሰፈር ከምታውደለድሉ የጀበና ቡና ብታፈሉ ምን
ችግር አለው ? ብሎ በምሳሌነት ጠቀሰን ። እኔ እንዳስተማረን ሳይሆን እንደ ሰደበን ቆጥሬው እሳት
እንደነካው ላስቲክ ተኮራመትሁኝ ።
አቤል ፣ እዮብ ፣ ሚኪ ምንም ጎበዝ ተማሪ ሆናችሁ ስታስጨንቁን ብትኖሩም አሁን ግን መጨረሻችሁ
እጣን እያጫጫሱ ሀላፊ አግዳሚውን መካደም ነው ማለቱም አይደለ ?
እዮቤ ጓደኛችን ፊቱ በርበሬ ሆኖ ቀላ !
አይ መንግስት የስራህን ይስጥህ ፤ አንድ የተከበርኩ ዶክተርን ለመንደር ስኩፒኒ አሳልፈህ ትሰጠኝ ? ብሎ
ክፉኛ ቆዘመ !
እኔም አነጋገሩ ትንሽ ሸንቆጥ ስላደረገኝ ከስብሰባው በሁላ ስንሻውን ለማናገር ከተቀመጥሁበት ተነስቼ
ተራመድኩኝ ።
ዛሬ ምንም ጉድ ይለይለታል !
በዛ ቢባል ከንቲባውን ገላመጥክ ተብዬ ብታሰርም አይደል ? የልጅነት ጓደኛዬ ስለሆነ ትንሽ ራሮት
ተሰምቶት ከሳምንት በኋላ ራሱም ሊያስፈታኝ ይችላል የሚል ድፍረት አደረብኝ ። ጀርባውን ተከትዬ
ተጠጋሁት ። በሰዓቱ ከየት መጣ ያልተባለ ጠባቂው በመዳፉ ጭብጦ አሽቀነጠረኝ ።
የጠባቂው መዳፍ ጎትቶ እዛው የተመረቅሁበት የዩንቨርስቲ ግቢ ሊዶለኝ ምን ቀረው ?
ቀና ብዬ አየሁት !
“ምን አጠፋሁ አለቃ?”
ፈርጣማው ጠባቂ በቁጣ ቱግ ብሎ እንዲህ አለኝ
“አንተ ምን አይነት ደፋር ነህ ባክህ ? ክቡር ከንቲባችንን ለመቅረብ አይደለም ሻንጣቸውን ለመሸከም
ብትመጣ እንኳ ማስፈቀድ ነበረብህ “
#ሚካኤል አስጨናቂ

@wegoch
@wegoch
@paappii
2024/09/23 09:24:41
Back to Top
HTML Embed Code: