Telegram Web Link
ራሴው ማበዴ ነው ... #7
(ሜሪ ፈለቀ)

እንባዋ ወደጆሮዎቿ ሲወርዱ ስትጠርጋቸው አየኋት። የእኔ መኖር ምቾት የሰጣት ስላልመሰለኝ ቀስ ብዬ ወጣሁ። እኚህ ሰዎች ሙድ ነው የሚይዙብኝ? ጭንቅላቴ ውስጥ ብዙ ጥያቄዎች እየተርመሰመሱ ቢሆንም ደምቆ የሚያቃጭልብኝ ‘መታመሟን ማን ነገረው?’ የሚለው ነው።

"እኔ ነኝ የነገርኩት።” አለኝ ካሳሁን ያሰብኩትን ያወቀብኝ መሰለኝ። ቀጠል አድርጎ "እነርሱ እስኪጨርሱ አንድ ቦታ ደርሰን እንምጣ?” ብሎኝ ተንቀሳቀሰ። ተከትዬው መኪናው ውስጥ ገባሁ። ብዙ ከተጓዝን በኋላተጀምሮ ያላለቀ ቤት ያለበት ጊቢ ይዞኝ ገባ። እያየሁት መንፈሱ ሲቀየር አስተዋልኩኝ። ሀዘን የተጫነው ሰውዬ ሆነ። ምንም ምንም ሳይለኝ ግድግዳውን ተደግፎ የተቀመጠ መጥረጊያ አንስቶ በጅምር ከቀረ የከራረመ የሚመስለውን ቤት ግድግዳና መሬት በጥንቃቄ ማፅዳት እና ማውራት ጀመረ።

"አበባ ጎበዝ አርክቴክት ነበረች። የፍትህ እናትን ማለቴ ነው። ለወደፊት ኑሯችን ራሷ ዲዛይን ያደረገችውን ቤት መገንባት ነበር የምትፈልገው። ይሄ ነበር የወደፊት ቤቷ ( መጥረጉን ቆም አድርጎ ቤቱን አመላከተኝ) ቤቷ ተሰርቶ ሳያልቅ እሷ ሞተች። ቤቱን አሰርቶ የመጨረስ ብርታቱ አልነበረኝም። በነበረበት ቆመ። ስትናፍቀኝ ላዋራት ፈልጌ መቃብሯ ጋር ስሄድ ሀዘኔ ይበረታል። ሙት መሆኗ በድን ያደርገኛል። እዚህ ስመጣ ግን እንደዛ አይሰማኝም። እዚህ የኔ አበባ ህይወት አላት። እዚህ ህልውናዋ ይሰማኛል። እና መቃብሯጋ መሄዴን ትቼ እዚህ መምጣት አዘወተርኩ። የሆነ ቀን እንደለመድኩት ስመጣ ፍትህ ቤቱን ሲያፀዳ አገኘሁት። ሁሌ ስመጣ ቦታው ፅዱ እንደነበር አስታወስኩ። ምንም አልተባባልንም። እስከትናንት ድረስም በዚህ ጉዳይ ቃላት ተለዋውጠን አናውቅም። ለ19 ዓመታት ይሄ ቦታ ፅዱ ነበር። እንዲህ ቆሽሾ አያውቅም። ሁሌም እሁድ ጠዋት መጥቶ እንደሚያፀዳው አውቃለሁ። አልመጣበትም። ሁሌም እሁድ ከሰአት እንደምመጣ ያውቃል። አይመጣብኝም። ትናንት ከዚህ በኋላ ወደዚህ ተመልሶ እንደማይመጣ ነገረኝ። በእናቱ ትዝታና ሀዘን መደበቅ እንደሚበቃው ነገረኝ። አየሽ ሁሌም የአዲስ ነገር ጅማሬ የአሮጌው መቋጫ ነው። ከአሮጌው ቅጥያ ከሆነ ምኑን አዲስ ሆነ?”

እየሆነ ያለው፣ የሰማሁት እና የማስበው ተፐውዟል። የካሳሁንና የአበባ ታሪክ ከእናትና አባቴ ታሪክ ጋር ይደባለቅብኛል። አባቴ ለእናቴ የፃፈላት ደብዳቤ ካሳሁን ለሚስቱ የፃፈላት ይመስለኛል። ደግሞ ስለፍትህ አስባለሁ። በፍፁም ለቅፅበት እንኳን ከፍቶት የሚያውቅ የማይመስለኝ ሰው ለነዚህ ሁሉ ዓመታት ይሄን ስቃይ እሹሩሩ ሲል ነበር የኖረው? እርስ በርሱ የተከላለሰ ነገር እያሰብኩ የቤቱ ደፍ ላይ ቁጭ አልኩ። መጥረጉን ሲጨርስ አጠገቤ መጥቶ ተቀመጠ።

"ታውቃለህ ከእናቴ በቀር የሚያውቀኝ ሰው ሳለቅስ አይቶኝ አያውቅም።” ካልኩት በኋላ እሱ ካወራው ልብ የሚቦረቡር ታሪክ ወይም እሱ ካለበት ስሜት ጋር በመልክም በቅርፅም የማይገናኝ ነገር ማውራቴ አሳፈረኝ።


"አየሽ አንዳንዴ ምንም ካልሰራንበት ዘመናችን ስህተት የሰራንበት ዘመን ይሻላል። ምክንያቱም ምንም ውስጥ ምንም የለም። ስህተት ውስጥ ቢያንስ የመሳሳቻ አንዱን መንገድ አውቀሽዋል። ደግመሽ በዚያ መንገድ መንደፋደፍ ወይም መንገድ መቀየር ያንቺ ምርጫ ይሆናል።” አለኝ። ለእኔ ያውራ ለራሱ ወይ ለሚስቱ አልገባኝም። ጭራሽ ያለውም አልገባኝም። ምን እየሆንን ነው? ጭራሽ እኔ የማወራው ነጭ እሱ የሚመልስልኝ ጥቁር!! እያበድን ነው እንዴ?… …ፀጥ ተባብለን ከቆየን በኋላ ተነሳ። ተመልሼ ሆስፒታል ስሄድ አባቴን ባላገኘው ደስ ስለሚለኝ መቆየታችንን ወድጄዋለሁ። ተከተልኩት። …… ቃል ሳንተነፍስ ሆስፒታል ደረስን።

"እኔ በቃ ወደቤት ልሂድ! ከቻልኩ በኋላ ብቅ እላለሁ።” አለኝ ከመኪናው ሳይወርድ። ተሰናብቼው ወደ እማዬ ክፍል እየሄድኩ ካሳሁንን ከጭንቅላቴ ማውጣት አልቻልኩም። መከፋት የተጫነውን ፊቱን ከሀሳቤ ማደብዘዝ አቃተኝ። እማዬና ፍትህ ከክፍሉ ውጪ የሚሰማ ሳቅ እየተሳሳቁ ደረስኩ። ሰላም ብያቸው ሳልጨርስ

"እኔ የምለው ጀብዱ ትወጃለሽኣ?” አለኝ ፍትህ የተጋነነ መገረም ባለው ድምፅ። የሰጠሁትን መረጃ አይቶት እንደሆነ ገብቶኛል።

“ማን ይጠላል?” አልኩት።

"እኔ!” አለኝ ኮስተር ብሎና አስረግጦ።

"ሃሃሃሃ ፈሪ ነህ ማለት ነዋ! ሊያውም የምትጠላው ጀብዱን አይደለም። የሚጠይቀውን ድፍረትና risk ነው። ” እያልኩት ፊቱ ላይ ስስት ያለበት ፈገግታ ተንሰራፋ…… እያወራን ካለበት ስሜት የማይገናኝ ዕይታ እያየኝ ነው። "ምንድነው?” አልኩት ግራ ሲያጋባኝ።

"ሳቅሽ!! ራሁ ድምፅ አውጥተሽ ሳቅሽ እኮ! ራስሽን ሰምተሽዋል?” እየፈነደቀ ነገር ነው ልበል? ድምፁ ውስጥ የምሰማው ነገር ምንድነው? ከመደሰት ያለፈ

"እና?”

"በፍፁም ድምፅ አውጥተሽ ስትስቂ ሰምቼሽ አላውቅማ።”
(ስቄ አላውቅም ይሆን? መቼ ነው ለመጨረሻ ጊዜ የሳቅኩት? መቼስ ይሆን የሚያስቅ ነገር የሰማሁት? ከሁልጊዜው በላይ እንባን በሚያዘንብ ሁኔታ ተከብቤ ዛሬ ምን አሳቀኝ?)
አሳፈረኝ። ያሳፈረኝ ዕይታው ይሁን አነጋገሩ አልገባኝም። ‘ተሽኮረመመች’ ተባብለው ከእማዬ ጋር ተሳሳቁብኝ። አፍንጫዬ አላበኝ። ጉንጬ የቀላም የነደደም መሰለኝ። ምንድነው እየሆንኩ ያለሁት? መቼ ነው እንዲህ የሆንኩት?
ድሮ ድሮ ድሮ ድሮ ድሮ ድሮ… ……....

"ይሄ ኬዝ እንዲህ ቀልብሽን የሳበው የትኛው ነጥብ ነው? ግልፅ ማስረጃ ነው የተያዘባት። ራሷም ድርጊቱን መፈፀሟን አምናለች።”

"ፍትህ ሰዎቹን ፈራሃቸው እንዴ?”

"በፍፁም ፈርቼ አይደለም። ከእነሱ ጋር ስለመያያዙም ገና መላምት ነው ያለሽ።”

ከፍትህ ጋር ሻይ እየጠጣን እየተነጋገርን ያለነው ስለትዝታ ነው። ትዝታ የ23 ዓመት ልጅ ናት። የአጎቷን ‘ፍቅረኛ’ በአጎቷ ሽጉጥ አራት ጊዜ ተኩሳ መግደሏን አምናለች። ለፖሊስ እጇን የሰጠችው ራሷ ናት። ለመግደል አበቃኝ ያለችው ምክንያት ለጥፊም የሚጋብዝ አይደለም። አጎት በአዲሳባችን ካሉ ባለሀብት አንዱ ነው። በተጨማሪም የሚንስቴር ወንድም ነው። ትዝታ አባቷ በ7 አመቷ ስለሞተ ያሳደጋት አጎቷ ነው። በ16 አመቷ ከጋብቻ ውጪ የወደቻትን ልጇንም እያሳደገላት ነው።

"ሰውየው ምንም ነገር የማድረግ አቅሙ ያለው ሆኖ ሳለ ጠበቃ እንኳን የቀጠሩላት የእናቷ ዘመዶች ናቸው። አስበው ትዝታ ልጁ ማለት ናት። ሌላው የሟች ጉዳይ ነው። ሟች የናጠጠ ሀብታም ሰውዬ ፍቅረኛ ሆና እናትና አባቷ ግን ከልጃቸው እጅ ስባሪ ሳንቲም ያልተለገሳቸው እና ለእለት ምግብ የሚቸግራቸው ሰዎች መሆናቸው ሲደመር ፍቅረኛ እንዳላትም አለማወቃቸው የሚጎረብጥ ነገር አለው። ትዝታ የሆነን ሰው እየተከላከለች እንደሆነ ነው የሚሰማኝ።"

"ማንን?”

"እሱን ማወቅ ያንተ ድርሻ ነው። እ? ገብተህበታል?”

"እሺ። ገብቼበታለሁ።” ይበለኝ እንጂ እንዳላመነበት ያስታውቅበታል።

"ፍትህ በህይወትህ ያልተለመደ ዓይነት ስኬት ላይ መድረስ ከፈለግክ ያልተለመደ ዓይነት ድፍረት ሊኖርህ ይገባል። ከተራ መንገድ ለመውጣት ማፈንገጥ አለብህ። ለእኔ ብለህ ብቻ እንድታደርገው አልፈልግም። አንዲት እርምጃ ከመራመድህ በፊት አንተ እንድታምንበት እፈልጋለሁ።” አልኩት።

"እስቲ መጀመሪያ ከትዝታ ጋር የምገናኝበትን መንገድ አመቻቺልኝ።”

"ሌላው ችግር ይሄ ነው። ጉዳዩን ውስብስብ እና አዳጋች የሚያደርገው ትዝታ ምንም አይነት መረጃ አትሰጥህም። መታሰር ነው የምትፈልገው። ጠበቃ እንዲኖራትም አትፈልግም። አንድ ሺህ ጊዜ ብትጠይቃት አንድ ሺህ ጊዜ የምትመልስልህ አንድ ዓይነት
መልስ ነው። ለማንኛውም ግን ነገ ቀጠሮ አለኝ እናገኛታለን።”

በዚህ ጉዳይ ላይ እርግጠኛ ባልሆንኩበት ምክንያት ፍትህ ጥሩ ሰርቶ ማየት እፈልጋለሁ። እንድኮራበት እፈልጋለሁ። አባቱ እንዲኮራበት እፈልጋለሁ። እሱም ራሱ በራሱ እንዲኮራ እፈልጋለሁ።

"ፍትህ አባትህ ዛሬ ደብሮታል። አንተ ወደ ቤት ሂድ። እኔ እማዬጋ ልመለስ።”

"ህምም እናቴጋ ሄዶ ነበር?”

"አዎን” አልኩት ሂሳብ እንዲቀበሉን አስተናጋጅ ለመጥራት እጄን እያነሳሁ። እጄን ለቀም አድርጎ ያዘኝ። ደንግጬ አየዋለሁ።

"ይቅርታ ራሁ አስደነገጥኩሽ። ትንሽ አብረሽኝ ቆዪ?” አለኝ ያያዘውን እጄን አጥብቆ እየያዘው። በጭንቅላቴ እሺ አልኩት። ዓይኖቹን ሳያርገበግብ ስላፈጠጠብኝ ተጨነቅኩ። ዓይኔን ከዓይኑ ብነቅልም እንዳፈጠጠብኝ ይታወቀኛል። ምራቄን ስውጥ ጉሮሮዬ ያስተጋባል። ያልያዘውን እጄን ጣቶች ከጠረጴዛው ስር አፍተለትላለሁ።

"ዓይኖቼን እንድታያቸው የግድ ስለስራ ነው ማውራት ያለብን?” ድምፁ ወፍራም ግን ለስላሳ ዓይነት ሆነ። የሰውነቴ ቆዳ ላይ እንደሆነ ሞገድ ሽው ሲል ይታወቀኛል።

"እያሳፈርከኝ ነው ፍትህ!” አልኩት። ባላየውም ፈገግ ማለቱን አውቄያለሁ። ባይናገርም አንደኛውን እጁን ዘርግቶ የጠየቀኝ ሌላኛውን እጄን መሆኑን ስላወቅኩ አቀበልኩት። እጆቼን ዘርግቶ ጣቶቼን እያያቸው ቀና ይላል።

"ጣቶችሽ ያምራሉ።” ባለኝ ቅፅበት ተራ በተራ ሁለቱንም እጆቼን ጣቶቼጋ ሳማቸው። ሆነ ብሎ ከንፈሮቹን ጣቶቼ ላይ አቆይቶ የተሰማኝን ለማወቅ ዓይኖቼን ይፈልጋል። በርግጌ ተነስቼ ልቆም ትንሽ ነበር የቀረኝ። ‘አገኘሁሽ’ አይነት ፈገግታ ፈገግ አለ።

"ፍትህ ሰው እያየንኮ ነው?”

"እና እኔ ምንአገባኝ? ዓይኑን የሚያሳርፍበት ቆንጆ ጎኑ ባይኖር ነው።” ብሎኝ የእጆቼን መዳፍ ተራ በተራ ሳማቸው። አይኔን ጨፈንኩ ልበል?

"ስለአንቺ የማላውቀውን አንድ ነገር ንገሪኝ?” አለኝ ወደእኔ እየሰገገ ተጠግቶኝ።

"ምንም አታውቅምኮ። ስለምንድነው ማወቅ የፈለግከው?”

"አሁን እኔ ማወቅ ስለሚገባኝ ነገር” ድምፁ ልክ የሆነ ስሜት አይሰጥም። እንኳን ቃላት ሰካክቼ በስርዓቱ ላወራ የማስበውን እንኳን ይበትንብኛል።

"ማለት?”

"አሁን መስማትም ማወቅም የምፈልገው እነዚህን እጆች የሚጨብጣቸው ሰው አለመኖሩን ነው።(እጆቹ እጆቼ ላይ አስማታዊ መርመስመሳቸውን አያቆሙም።) ፤ ፀጉርሽ ውስጥ ጣቶቹን ሰክቶ የአንገትሽን ጠረን የሚምግ፣ ከንፈሮችሽን ጎርሶ በትንፋሽሽ እድሜውን የሚቀጥል፣ (ዓይኖቹ የሚጠራቸው የሰውነት አካሌ ላይ በስድ እይታ ያርፋሉ። እኔን ግን ምን እየነካኝ ነው? የምሰማው ድርጊት እየሆነ ያለ ያህል ይሞቀኛል።) በአይኖችሽ መስለምለም ቀኖቹን የሚያደምቅ፣ የሸሚዞችሽን ቁልፍ ከፍቶ… ”

"እረፍ ፍትህ! እረፍ በቃህ! ማንም የለም!” አስቤ የተናገርኩት አልነበረም። አሁንም የቅድሙን ፈገግታ ደገመልኝ። እጆቼን ስለለቀቀልኝ ተነፈስኩ። ሆስፒታል ሸኝቶኝ ተመለሰ። ካፌ ተቀምጠን ያደረገውን እንዳላደረገ በቅጡ እንኳን ሳይጨብጠኝ ነው የሄደው። ተናደድኩ ልበል? ምን እየሆንኩ ነው? ምን እንዲያደርግ ነበር የፈለግኩት? ምናልባት የሚያደርገው ሁሉ ለብዙ ሌሎች ሴቶች ያደረገው ለእርሱ ምኑም ያልሆነ ይሆን? ምንዓይነቷ ቀሽም ነኝ?

እማዬ አስር ጊዜ “ምን ሆነሻል?” ስትለኝ ራሴን ገስፃለሁ። እየሆንኩ ያለሁት በግሳፄ ማቆም የምችለው ጉዳይ ግን አልሆነም።

"አባትሽ ስለመጣ ተናደሻል?” እማዬ ስትጠይቀኝ በራሴ በሸቅኩ። ምንም የኑሮ ማገር እንዳላፈነገጠብኝ ስለፍትህ በዚህ ጥልቀት ማሰቤ አናደደኝ።

"ኸረ እማዬ… … ለምን እናደዳለሁ? አንቺ ደስ ካለሽ የኔ ደስታ ያ ነው።”

"እንደምትጠዪው አውቃለሁ። አንቺን ደስ ካላለሽ ድጋሚ እንዳይመጣ እነግረዋለሁ።”

"እማዬ አንደኛ አልጠላውም። አልወደውም ማለት እጠላዋለሁ ማለት አይደለም። ከመጥላትና ከመውደድ ፅንፍ መሃል ምንም ስሜት ማጣት አለ። እንደዛ ነው ለሱ ያለኝ ስሜት። ሁለተኛ የአንቺ ፈቃድ ይሁን እንጂ በተመቸው ሰዓት መጥቶ ሊያይሽ ይችላል።”

የአባቴን ጉዳይ በጤነኛ ጭንቅላቷ ስትሆን ደፍራ አታወራኝም። በዚህ ሁሉ ስቃይዋ እሱን ማፍቀሯ እኔን መበደል የሚመስላት ይመስለኛል። ለእኔ አንዳችም የአባት ርህራሄ ያላሳየኝን ሰው ጭንቅላቷ እስኪዛባ ማፍቀሯ እኔ ለእርሷ ያደረግኩትን መልካምነት መደለዝ ይመስላታል መሰለኝ። ስለእውነቱ ሰውየውን አልወደውም። እሷ ስለምታፈቅረው ግን አልናደድባትም። ያንን ደግሞ ያስተማረችኝ ራሷ ናት። ‘ኩታ በየፈርጁ ይለበሳል።’ ትለኛለች። ለእሱ ያላት ፍቅርና ለእኔ ያላት ቦታ የሚጋጭም ፣አንዱ ሲጨምር ሌላው የሚቀንስም ፣ የሚወዳደርም አይደለም። ስለዚህ እኔንና እሱን ለምርጫ አላቀርብላትም። ሁለታችንንም በልቧ መያዝ ትችላለች።

"እማዬ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ? ካልፈለግሽ አለመመለስ ትችያለሽ። ”

"ጠይቂኝ!”

"የእውነትሽን ያደረገሽን ነገር ረስተሽለት ነው? ይቅር ብለሽው ነው?”

ኸረ ኡኡኡ አሁንም አልጨረስንም

@wegoch
@wegoch
@paappii
~ ራሴው ማበዴ ነው ..... #8 ~
(ሜሪ ፈለቀ)


"በእርግጥ ይቅር ብዬው ነው። ያ ማለት ያደረገኝን ረስቼው ነው ማለት አይደለም። አየሽ ሚሚሾ በደንብ ስሚኝ ከመስከረም እስከ ነሃሴ በፍቅሩ ከልሎ ፣ በርህራሄው ከብቦሽ፣ በሀዘንሽ አልቅሶ፣ በደስታሽ ፈንጥዞ ፣ በጉያው አሙቆ…… ያከረመሽ ሰው ጳጉሜ 5 ላይ ቢበድልሽ የቱን ትቆጥሪበታለሽ? ብዙ ፍቅሩን ወይስ አንዲት በደሉን? ሰዎች ስሪታችን ሆኖ ከፍቅር ይልቅ በደል በደማችን ቶሎ ይሰርፃል። እኔ የመረጥኩት ብዙ ፍቅሩን ነው። ፍቅሩ በደሉን ይከድንብኛል። ለነፍሴም ሰላም የሚሰጠኝ ያ ነው።” አለችኝ በጣም በተረጋጋ መንፈስ። በልቤ ይዣት መኖር የምፈልገው ይህቺን እናቴን ነው። በብዙ ምክሯና ፍቅሯ በማይነቃነቅ የሞራል አለት ላይ የተከለችኝ እናቴን።

"እሺ!” ከማለት ውጪ እሷ ላለችበት የፍቅር ልእልና መልስ አልነበረኝም።

"ደግሞም ልጄ የተበደልነው ህመም ከበደልነው በላይ የሚጠዘጥዝ እንደሆነ ስለሚሰማን የተደረገብን እንጂ ያደረግነው የሚፈጥረው ቁስል አያመንም እንጂ አባትሽን ከበደለኝ በላይ በድዬዋለሁ። ምናልባትም እኔ ካለፍኩት ስቃይ ያለፈ ተሰቃይቷል።” አለችኝ ቀጥላ። ‘አንቺ በየሆስፒታሉ ስትሰቃዪ እሱ ሚስት አግብቶ ወልዷል። የወለዳትን ልጅ ድሯል። እንዴት ተሰቃየ?’ ልላት ነበር ያሰብኩት። እንደ እማዬ ፍቅርና ቅንነት የሞላበት ሀሳብ ባልታደልም ይሄን ማለት ቅን ሀሳቧን በክፋት የመበረዝ ሀጢያት ስለመሰለኝ ዝምታን መረጥኩ።

በሰዎች የእለት ተዕለት ኑሮ ውስጥ የማይቀየር አንድ ህግ አለ። የሰዎች ድርጊት የሀሳባቸው ልጅ ነው። ልምዳቸው ደግሞ የሀሳባቸው የልጅ ልጅ ነው። ታስባለህ– ታደርጋለህ– ልምድህ ይሆናል። ድርጊትህ ወይም የየዕለት ልምድህ በሀሳብህ ያረገዝከውን አንኳር ይመስላል።

በሚቀጥለው ቀን አባቴ እናቴን ሊያያት ሲመጣ እኔና ፍትህ ትዝታን ልናያት ሄድን።

"እኔ የማንም እርዳታ አያስፈልገኝም። አንቺንም እሱንም አልፈልግም።” አለችኝ ትዝታ ከዛሬ በኋላ ጠበቃዋ ፍትህ መሆኑን ስነግራት። ከብዙ ልመና ቀረሽ ንግግር በኋላ ፍትህ ጠበቃ እንዲሆን በ‘ምንቸገረኝ’ ተስማማች። ትቻቸው ልወጣ ስል

"ጠበቃ ልጅ አለሽ?” አለችኝ።

"የለኝም። ምነው ጠየቅሽኝ? ትዝታ በልጅሽ እያስፈራራሽ ያለ ሰው አለ? ንገሪኝ? ማንም ቢሆን ከህግ አያመልጥም። በእኔ ልትተማመኚብኝ ትችያለሽ እባክሽ ንገሪኝ።” ከዚህ በኋላ ምንም ቃል አልተናገረችም። ትቻቸው ወጥቼ እንኳን የኔ ጭንቅላት ግን በሀሳብ እዚህና እዚያ መርገጡን አላቆመም።

ከዚህ ቀን በኋላ አባቴ በየቀኑ እናቴጋ ይመጣል፣ ፍትህ በትዝታ ጉዳይ አዲስ ነገር ለማግኘት ቀን ሲሯሯጥ ይውላል… … አመሻሹን እማዬጋ መጥቶ አይቶን ወደቤቱ ይሄዳል ወይ ያድራል ፣ ካሳሁን በተመቸው ሰዓት ሁሉ ከእኔና ከእማዬ ጎን ይሆናል… ፤ እኔ የፍትህ ክፍል ማደሬን ትቼ ፍትህ ሆስፒታል የሚያድር ቀን እቤቴ አድራለሁ። ሌላውን ቀን ከእማዬጋር። ……
በአንዱ ቀን አባቴ በትንሽዬ ካርቶን ያለ ነገር ሰጥቶኝ ሄደ። እቤቴ ገብቼ አየሁት። ደብዳቤዎች ናቸው። እማዬጋ የሌሉ እሱ የፃፈላት ደብዳቤዎች። አንብቤያቸው ስጨርስ አንድ ነገር ገባኝ። እማዬጋ ያሉት በሙሉ የፍቅር ደብዳቤዎች ናቸው። እሱጋ ያሉት ግን ቅሬታና በደል የተፃፈባቸው ናቸው። እንደ እማዬ አባባል እሱ አንዲትን በደል መርጧል። እሷ ለዘመናት የፍቅር ደብዳቤዎቹን ስታነብ እሱ ለዘመናት በደሉን እያነበበ ቂም ሲደምር ኖሯል። …… እሷ ከመስከረም እስከ ነሃሴ ላይ ናት። እሱ ግን ጳጉሜ 5 ላይ ነው። በሬ ሲንኳኳ ነው የባነንኩት

"ፍትህ? እማዬ ምን ሆነች?”

"ኸረ ምንም አልሆነችም። አባትሽ እሷጋ ሊያድር ነው። ወደቤት ከመግባቴ በፊት ስለትዝታ አንዳንድ ነገር ላውራሽ ብዬ ነው የመጣሁት።”

"ነገ መድረስ የማይችል ጉዳይ ነው?”

"ወሬው ይደርሳል። ……” ብሎኝ እጆቹን በአንገቴ ስር አሳልፎ ፀጉሬ መሀከል ጣቶቹን ሰክቶ ወደራሱ አስጠጋኝ። አንገቴ ስር ስሞኝ በሹክሹክታ "… ይሄ ግን ለነገ ማደር አይችልም ነበር።” አለኝ።

በሰላሳ አንድ ዓመቴ ማንም ወንድ ነክቷት የማታውቅ ድንግል ሴት መሆን የሚያኮራ ነገር ይሁን የሚያሳፍር አላውቅም። (‘ድንግል’ የሚለውን ቃል እጠላዋለሁ። ቃሉን እንጂ ነገርየውን አይደለም። በእርግጥ ነገርየውንም ልውደደው ልጥላው እርግጠኛ አይደለሁም። ቃሉ ግን የሆነ አፍ ላይ ሲባል ራሱ ድንግል፣ ደናግል፣ ድንጉላ……… ድንዝና አለበት።) እውነታው እግሮቼ መሃል ካለ ነገር ድፍንነት ወይ ጠባብነት በላይ ዓይኖቼን የማያስነቅሉ የኔን ትኩረት የሚሹ አሳሳቢ የዕለት ተዕለት ጉዳዮች የከበቡኝ ሴት ሆኜ በመኖሬ ትርጉሙም ጣዕሙም አይገባኝም። ድንገት እንኳን በሀሳቤ ሽው ካለ የማልም የነበረው አቅፎኝ የሚያድር የሆነ የማላውቀው ፈርጣማ ወንድ ሰውነት ነው። ማቀፍ ብቻ!! ሌላውን ‘ፓኬጅ’ አላስበውም። እኔ እና እማዬ ብቻችን መኖር የጀመርን ዓመት እማዬ ሲነሳባት ለሊቶቹ ይረዝሙብኛል። ምን እንደምፈራ አላውቅም ግን ስለምፈራ ዓይኔን አልከድንም። ጨለማው፣ ኮሽታው፣ ፀጥታው…… ሁሉም ያስፈራኛል። እጅግ ጥልቅ ፍርሃት እፈራለሁ። ድፍረት የፍርሃት ተቃራኒ አይደለም። የፍርሃት ሌላ ተቃራኒ ሊኖረው ይገባል። ምክንያቱም ድፍረት አለመፍራት አይደለማ። ይልቁንስ ድፍረት ፍርሃትን መጋፈጥ ነው። ድፍረት ፍርሃት እንዳያስቆምህ እየተንቀጠቀጥክም ሆነ እየዳህክ በፍርሃትህ ጫካ ውስጥ ሰንጥቀህ ማለፍ ነው።

እማዬ እና አባቴ ከተለያዩ በኋላ ከታላቅ እህቷ (ከአክስቴ) ጋር ነበር የምንኖረው። የአስራ ሁለተኛ ክፍል ትምህርቴን ጨርሼ ውጤት እየጠበቅኩ በነበረበት ክረምት አክስቴ ትኖር የነበረበትን ትልቅነቱ እና ፀጥታው የሚያስፈራ ቤቷንና ቢያንስ በዓመት ሶስቴ እብደቷ የሚነሳባት እህቷን (እናቴን) አስተዳድሪ ብላኝ አውስትራሊያ ከሄዱ ከእኔ እድሜ በላይ ያስቆጠሩ ቤተሰቦቻቸውን ተቀላቀለች። ከእርሷ በቀር ሀገር ውስጥ የቀረ የቅርብ ዘመድ ያልነበራት እናቴ ብዙም ሳትቆይ የበረራ ቁጥሯን መቁጠር ጀመረች። እንኳን እሷን ላረጋጋት እኔ ከርሷ ብሼ እጅና እግሬ እየተንቀጠቀጠ አለቅሳለሁ። መድሃኒቷን በስቃይ ወስዳ ስታንቀላፋልኝ። እያንዳንዱ የቆዳዬ ነጠብጣብ ቀዳዳ ፍርሃትን እየማገ ወደሰውነቴ ሲነዛው እየተሰማኝ ተስፋ ላለመቁረጥ እና ላለመውደቅ እታገላለሁ። ለፍርሃት እጅ ላለመስጠት!! ያ ነው ድፍረት ማለት። መታገል!! በነዚህ ጊዜያት ነበር በእቅፉ የሚከልለኝ ሰውነት የምመኘው!! ሰውነቱን እንጂ ሰውየውን አልሜ አላውቅም። ሰፊ ትከሻ፣ ሰፊ ደረት፣ ፈርጣማ ጡንቻ፣ ረዥም ቁመት…… ለውበት ሳይሆን ከፍርሃቴ ለመከለያ፤ ለስሜት ሳይሆን ለመደበቂያ፤ ለመፈንጠዣ ሳይሆን ለመወሸቂያ… …ከአንገቱ በላይ ባይኖረውም አልያም ምንም ቢመስልም አስቤው አላውቅም።

"ራሁ? እየሰማሽኝ እኮ አይደለም። ምን ሆነሻል? ከቅድም ጀምሮ ላጫውትሽ እሞክራለሁ። ከእኔ ጋር አይደለሽም።”

"ይቅርታ ፍትህ ትንሽ ራሴን አሞኛል።”

"ምን ላድርግልሽ? ሀኪም ቤት ልውሰድሽ? (እጁን ግንባሬ ላይ አድርጎ ማተኮሴን ያረጋግጣል። በጭንቅላቴ ንቅናቄ መሄድ ያለመፈለጌን ነገርኩት።) እሺ በቃ ነገ ይደርሳል ነገ አወራሻለሁ።እረፍት አድርጊ!” ብሎኝ ተነሳ። ምን አስቤ እንደሆነ እንኳን ለመረዳት ከራሴ ተማክሬ ያላደረግኩትን ድርጊት ተስፈንጥሬ እጁን ይዤ አሰቆምኩት። ቀጥዬ ለምን እንዳስቆምኩት የምሰጠው ምክንያት አልነበረኝም።

"ወዬ? ምን ላድርግልሽ? እንዲህ አድርግልኝ በይኝ። እ ራሁ? (ተመልሶ ተቀምጦ ይዞ ያስቀረውን እጄን እያሻሸ ፣ዓይን ዓይኔን እያ
የ እና ሁሉም የስሜት ህዋሳቶቼ በሚገባቸው ድምፅ ተንሾካሾከ።) ልታወሪልኝ የምትፈልጊው ነገር አለ? እ? እሺ እንዳድርልሽ ትፈልጊያለሽ?”

"አይይይ አልፈልግም።” አልኩት። አጠገቤ እንዲሆን እኮ እፈልጋለሁ። ሲነካኝ ግን እበረግጋለሁ። እጆቼን ሲያሻሽ ፣ ቅድም እንዳደረገው አንገቴ ስር ሲስመኝ ፣ ዓይኖቼን በሚለማመጡ ዓይኖቹ ሲያያቸው…… መሸሽ እፈልጋለሁ። እንዲህ ሲያደርግ የሚሰማኝን ስሜት ስለምጠላው አይደለም። ስለምወደው እንጂ። ነገር ግን ደስ የሚለኝ አዲስ ስሜት ያስፈራኛል። ሁሌም ቢሆን ያልተለማመድነው አዲስ ነገር፣ አዲስ ሀሳብ፣ አዲስ ስሜት……… ብቻ አዲስ ልምድ መጠኑ ቢለያይም ፍርሃት ያጅበዋል። ምክንያቱ ደግሞ ውጤቱ ከግምት ያለፈ ማረጋገጫ የለውም። ለዚህ ይመስለኛል የብዙ ሰዎች ኑሮ የተለመደ እና የተደጋገመ የሚሆነው። ከአዲስ ነገር ጋር አብሮ ብልጭ የሚለውን ፍርሃት መጋፈጥ የቻሉ ጥቂት ደፋሮች ለአለማችን አዳዲስ ሀሳቦች እና ፈጠራዎች አበርክተዋል።

"እሺ እኛ ቤት እንሂድ? ከካስዬ ጋር ስትጫወቺ ይለቅሻል። እንሂድ?”

"አይ… … ስለትዝታ የደረስኩበት ነገር አለኝ አላልክም ነበር? እሱን እንድትነግረኝ ነው።” የሚል ምክንያት ነበር የመጣልኝ

"ስለትዝታ ልትጠይቂኝ ነው እጅሽ የሚያልብሽ?( ያላበው መዳፌን በእጁ እየጠረገ ያደርቃል። ይሄኔ እኮ ድምፅ ከጆሮ ውጪ በሌላ የስሜት ህዋስ እንዴት ይተረጎማል? ብሎ የሚጠይቅ አላዋቂ አይጠፋም። አሁን ፍትህ እያወራ ያለበት ባለጣዕም ድምፅ ቀላል ይጣፍጣል?) ስለትዝታ ልትጠይቂኝ ነው ዓይንሽ የሚሸሸኝ? (ይሄን ያለበት ድምፅስ ቀላል የሚያውድ መዓዛ አለው?) ስለትዝታ ልትጠይቂኝ ነው ጉንጭሽ የቀላው? (ይሄኛው ቀለማት አሉት። ዓይን የሚይዝ የቀለም ስብጥር) ስለትዝታ ልትጠይቂኝ ነው ቃላት ለማውጣት ያማጥሽው?( ይሄኛው እንደሚያባብል የውሃ ዳር ንፋስ በቆዳዬ ላይ ሽውውውው እያለ ይዳብሰኛል።)" ጭራሽ የማወራው ጠፋብኝ። በዛው ድምፅ ቀጠለ

"ስለስራ ስታወሪ ዓይኖችሽ ዓይኖቼን ያሳድዳሉ ፣ አንገትሽን ቀና አድርገሽ የምትናገሪው ተፅፎ የተሰጠሽ አይነት ‘articulated’ ነው፣ በጥያቄሽ ብዛት እኔን ያልበኛል። …… ንገሪኝ ምን ልትዪኝ ነበር እጄን የያዝሽኝ?” (ይሄንን ድምፅ ጥፍሬ እና ፀጉሮቼ እንኳን ላይሰሙት አይችሉም።)

"ምንም!! ምንም የምልህ ነገር ኖሮኝ አይደለም። …… በቃ እንድትቆይ ብቻ ፈልጌ ነው።”

"እሺ (ያልከለለውን ፀጉሬን ወደኋላ እያደረገ) እሺ እንድቆይልሽ እስከምትፈልጊው ጊዜ ሙሉ የእድሜዬን ቁጥርም ቢሆን እቆይልሻለሁ። ምን እያደረግኩልሽ እንድቆይ ነው የምትፈልጊው?”

"አላውቅም!! ፍትህ የተሰማኝን ስለነገርኩህ እንዳፍር እያደረግከኝ ነው።" ስለው ፈገግ ማለቱን ሳላየው በምን አወቅኩ? ምራቄን እየደጋገምኩ በሚያስተጋባ ጉሮሮዬ የምውጠው ምን ሆኜ ነው? አፍንጫዬ ሳይቀር የሚያልበኝስ?

"እሺ!!” ብሎኝ እጄን ለቀቀኝ። ከሶፋው ላይ ትንሽዬዋን ትራስ አንስቶ እኔ ከተቀመጥኩበት በተቃራኒ ጥግ ተቀመጠ።ትራሷን ጭኑ ላይ ካስቀመጠ በኋላ በእጁ እየመታ ጠቆመኝ። ጀርባዬን ሰጥቼው እግሬን ሰቅዬ እሱን ተንተርሼ ተጋደምኩ።

"ፊትሽን አትከልዪኝ። ወደዚህ ዙሪና ከፈለግሽ ዓይንሽን ጨፍኚ።” አለኝ ቀጠለና። እንዳለኝ አደረግኩ። ዓይኔን ግን አልጨፈንኩም። ፀጉሬን በጣቱ እያበጠረ ለደቂቃዎች ካለምንም የቃላት ልውውጥ ከቆየን በኋላ።

"እንቅልፍሽ ከመጣ መተኛት ትችያለሽ።” አለኝ

"ከዛስ? አንተስ?”

"ያላደለው ጨለማ ላይ አፍጥጦ ያድር የለ? አንቺን የመሰለ ውበት ላይ አፍጥጦ ማደር ተገኝቶ ነው? ውብ’ኮ ነሽ ካስዬ ይሙት! (እጄን የማስቀምጥበት አጥቼ አቅበዘበዝኩት።) እፍረትሽ መጣ?” ብሎኝ ሳቅ ሲል በጨረፍታ አየሁት።

" አንዳንድ ነገር ሳጣራ ነበር። ምን ያህል እንደሚጠቅመኝ ባላውቅም አንዳንድ መረጃዎች ……”

"እስኪ ንገረኝ።"

"የሟች ታሪክ ትዝታ ካለችው የራቀ ነው። ሟች የሰውየው ፍቅረኛ አልነበረችም። ከዚያ ቀን በፊትም ተያይተው አያውቁም። የምትማርበት ትምህርት ቤት ጓደኞቿ የሞተች ዕለት መጥቶ ከትምህርት ቤቷ ወሰዳት ያሉትን ሰው አገኘሁት።”

"እና?” ከተጋደምኩበት ቀና ብዬ ለመልሱ አቆበቆብኩ። ፈገግ አለ። ‘ስለስራ ሲሆንማ እንዲህ ነው የምትሆኚው’ የሚል ትዝብት ያለበት ዓይነት ፈገግታ።

"ወንጀሉን መሸፈኛ ስራው ትዳር ፈላጊ አገናኝ ነው። ዋነኛ ስራው ተማሪ ህፃናትና ወጣት ሴቶችን ለከተማችን ዋልጌ ሀብታም ሽማግሌዎች ማቅረብ ነው። ‘ሀብታም የሆነ ባል ፈልጋለሁ ስላለችኝ ነው ያገናኘኋት።’ ባይ ነው። ትዝታ ለመጀመሪያ ጊዜ እቤታቸው የመጣችን ሴት ‘ልጄን በጥፊ ስለመታቻት’ በሚል ቀሽም ምክንያት ትገድላታለች ብሎ ማመን ይከብዳል። ካልሆነስ ማንን እየተከላከለች ነው? ሰውየውን? እሱስ ቢሆን ከዚያን ቀን በፊት አይቷት የማያውቃትን ሴት ለመግደል ምን በቂ ምክንያት ይኖረዋል?”

"አንድ የሆነ ነገር ግን አለ። ልጅ አለሽ ወይ ብላ የጠየቀችኝ ቀን በደንብ አስተውለሃታል? አነጋገሯ ለልጇ ብላ እየከፈለች ያለችው መስዋዕትነት እንደሆነ ነገር ነው።”

"ሌላው ነገር… …ማንም የሚያውቀው ሰው ክፉ ስለማያወራለት አጎቷ አንድ ትኩረቴን የሳበ መረጃ ሰማሁ። የትዝታ ፍቅረኛ ፣ የልጇ አባት ትዝታ እርጉዝ በነበረችበት ወቅት እቤታቸው ድረስ መጥቶ አጎትየውን ደብድቦት ሄደ። ከዚያ ቀን በኋላ ልጁን አየሁት የሚል ሰው የለም። ትዝታም ምንም ልትነግረኝ ፈቃደኛ አይደለችም። አጎትየው በሁለቱ ግንኙነት ደስተኛ ካልነበረ ጥቃት ሊያደርስ የሚገባው እሱ ሆኖ የተገላቢጦሽ እንዴት ሆነ?”

"እሱን እያሰብኩ ነበር። ጎብዘኻል ግን ደስ ብሎኛል።” አልኩት ለጊዜውም ቢሆን ያ የሚያሽኮረምመኝ ፍትህ ተዘንግቶኝ ዓይን ዓይኑን እያየሁ።

"በልብሽ ደምቄ ለመፃፍ የሚያስከፍለኝ ጉብዝናን ከሆነ እተጋለሁዋ ምን አማራጭ አለኝ?” አለኝ እሽኩርምሚቴን በሚያመጣው ድምፁ። ተመልሼ እንደመጀመሪያው እላዩ ላይ ተጋደምኩ እና ዓይኔን ጨፈንኩ።

★ አልጨረስንም ካላችሁ አልጨረስንም★
★ጨርሰናል ካላችሁም አልጨረስንም.....

@wegoch
@wegoch
@paappii
~ ራሴው ማበዴ ነው .....#9~
(ሜሪ ፈለቀ)

ፀጉሬን በጣቶቹ እያበጠረ መነሻም ማረፊያም የሌለው ወሬ እያወራኝ ለምን ያህል ደቂቃ እንደቆየ አላውቅም። እንቅልፍ ወስዶኝ የነቃሁት ለሊት ዘጠኝ ሰዓት ነው። የሶፋውን መደገፊያ ተደግፎ በተቀመጠበት እንቅልፍ ወስዶታል። ጣቶቹ ከፀጉሬ መሃል አልወጡም። በሁለት የሶፋ ትራስ እግሬን ሸፍኖ ከብርድ ከልሎልኛል። ሆስፒታል ለማደር አስቦ ስለነበር የወጣው ቱታ ሱሪና ጃኬት ነበር የለበሰው። ጃኬቱን አውልቆት እጄን አልብሶኝ በ‘ፓክ አውት’ ነበር። ቀሰቀስኩት።

" ፍትህ ተነስ በስርዓቱ ተኛ አንገትህን ያምሃል። ተነስ እኔ መኝታ ቤት ተኛ። እኔ እማዬ ክፍል እተኛለሁ።” ይሄን የሚለው በምክንያትና በእውቀት ካላመንኩ የሚለው ጭንቅላቴ ነው። ልቤ ግን ከአጠገቡ መራቅን አልፈለገም።

"ከአንቺጋ እንድተኛ ካልፈቀድሽልኝ እዚሁ ሶፋ ላይ የምለብሰው ስጪኝና እተኛለሁ።” አለኝ አይኑን እንኳን አስተካክሎ ሳይገልጥ። ግራ ገባኝ ምን እንደምለው። ያንን እሱም ያወቀ መሰለኝ

"አብረን ተኝተን ነበር እኮ! አልጋ ላይ ሲሆን ምኑ ይለያል? ራሁ ስወድሽ አታወሳስቢው።”

"እሺ!” እያልኩት ወደመኝታዬ ገባሁ። ተከትሎኝ ገብቶ ጫማውን ብቻ አውልቆ ቀድሞኝ አልጋ ልብሶቹ ውስጥ ገብቶ በጀርባው ተኛ። አይኑን ጨፍኖ እጁን ለማቀፍ ዘረጋልኝ። አለማወሳሰብ ይሔ መሆኑን እየገመትኩ እቅፉ ውስጥ ገባሁ። በሁለቱም እጆቹ ደረቱ ላይ አጣብቆ አቅፎኝ ተኛ።… … አፌን እየሞላ እና ጉሮሮዬ ውስጥ የገደል ማሚቶ እየሰራ የሚያልፈውን ምራቄን እየዋጥኩ፤ ድው ድውታው ለእርሱ የሚሰማውን ልቤን ለመቆጣጠር እየታገልኩ የሚቀጥለውን እንቅስቃሴ ጠበቅኩ።… … ጠበቅኩ። …… ጠበቅኩ። …ተኝቷል። …… እንቅልፍ ወስዶታል። ካለፍርሃት ተኛሁ።
.
.
.

"አገኘሁት! ራሁ አገኘሁት!” ይለኛል የሆስፒታሉ ኮሪደር መሃል እየደነሰ

"ምኑን? እስኪ አንዴ ዳንስህን አቁመህ ንገረኝ!”

"የትዝታን ፍቅረኛ አገኘሁት!”

"በጣም ጥሩ! የሚጠቅም መረጃ አገኘህ?”

"ገና ነው። ደቡብ አፍሪካ ነው ያለው። ከሀገር እንዲወጣ ያደረገው ማን እንደሆን ገምቺ? የትዝታ አጎት! አስፈራርተውት ነው ከሀገር እንዲወጣ ያደረጉት።”

"ለምን?”

"ትዝታን ለሌላ ለተከበረ ሰው ሊድሯት እንደሆነና ከሷ ህይወት እንዲወጣ እንዳስፈራሩት ጓደኛው ነው መረጃ የሰጠኝ። የሚደውልለትን ስልክ ሰጥቶኝ ደውዬለት ነበር።”

"እና?”

" በዚህ ርቀት ሆኖ እንኳን ይፈራቸዋል። ገና ስለትዝታ ሳነሳበት ‘ሰውየው አረመኔ ነው። አታውቁትም። ትንፍሽ ብል ይገድለኛል።’ አለኝ። ትዝታ ያለችበትን ሁኔታ አስረዳሁት። ልጁ ያለእናትና አባት መቅረቷ መሆኑን ስነግረው ስራ ቦታ መሆኑን እና መልሶ እንደሚደውልልኝ ነግሮኝ ስልኩን ዘጋው።”

"በቃ?”

"ለጊዜው አዎን በቃ!”

“እና የሚያስደንስህ ይሄ ነው? ገና የመፅሃፉን ሽፋን እየገለጥክ እንደሆነ አልገባህም ልበል? ገና ገፅ አንድን እንኳን አላነበብክም እኮ!”

"ራሁዬ ገፅ አንድ ላይ ነኝ ማለት ታዲያ ቢያንስ ትክክለኛውን ትራክ አጊንቻለሁ ማለት አይደል? የተሳሳተ መፅሃፍ ካልገለጥኩ am good ማለት ነው። ሌላው የውልሽ ትዝታን አናገርኳት። ‘ተወኝ’ ከሚል ቃል ውጪ ትንፍሽ ብላ የማታውቅ ልጅ። የልጇን አባት እንዳገኘሁት ስነግራት ከመቀመጫዋ ዘላ ተነስታ ‘በህይወት አለ?’ ብላ ነበር የጠየቀችኝ። ደስ ያላት ትመስላለች። ሞቷል ብላ አስባ ነበር ማለት ነው። ከዚህ ተጨማሪ ነገር ልትናገር አልፈለገችም። ይልቅ ያሰብሽውን ንገሪኝ።”

"የማስበውማ እንዴትም ብለህ ድጋሚ ልታናግረው ይገባል! ስለሰውየው የሚያውቀው ነገር የሚያስገድለው ወይም ከሀገር የሚያሰድደው ከሆነ ሰውየው እንዴት ያለ ወንጀል ውስጥ የዘቀጠ ቢሆን ነው? ስለሰውየው ተጨማሪ መረጃዎች መሰብሰብ አለብህ። የማስበው ዜሮ ላይ እንዳለን ነው።”

በእርግጥ ለእርሱ ይሄን ልበለው እንጂ በትዝታ ጉዳይ የሚገኙት መረጃዎች ብጥቅጣቂና ለማስረጃነት የማይበቁ ምስክርነቶች መሆናቸው ተስፋ አስቆራጭ ሆኖ እንኳን በየቀኑ መረጃ ለማግኘት የሚያደርገው ጥረት እያስገረመኝ ነው። ካሳሁን በሁኔታው መደሰቱን እያመሰገነኝ ነግሮኛል።

"እሺ እማዬን ተሰናብቻት ልውጣ!” ብሎኝ አልፎኝ ወደ ውስጥ ገባ። እማዬ ዛሬ ጠዋት እንዲህ ብላኝ ነበር።

"ሚሚሾ ወጣትነትሽን ለእኔ ብለሽ ገብረሻል። ለራስሽ መኖር ያለብሽ ጊዜ የደረሰ ይመስለኛል። ፍትህ መልካም ሰው ነው። ይወድሻል። አትግፊው።”

"በምን አወቅሽ?” ስላት ሳቀችብኝ። …… ፍትህን እንደወደደችው አውቃለሁ። ከእርሱም ጋር ሆነ ከካሳሁን ጋር ስትጫወት ያለስስት ነው። እነሱ አጠገቧ ሲኖሩ ደስተኛ ናት።…… ካሳሁን ሲኖር ፍትህን ያበሽቀዋል። እኔና እማዬ እንስቅበታለን። እሱ ሳይኖር እማዬና ፍትህ በእኔ ሙድ እየያዙ ይስቃሉ። …… ሆስፒታል ያለን አይመስልም… …… ወደሞት እየተንደረደረች ያለች እማዬን የከበብን አንመስልም። አዲስ ህፃን ወደቤተሰቡ የቀላቀለች እናት ከበን የምንደሰት ነው የምንመስለው። አባቴም በየቀኑ መምጣቱን አላቆመም። እሱ ሲመጣ እኔ እወጣለሁ። ላናግረው እንደማልፈልግ እርሱም ያውቃል። አይሞክርም። ከእኔ ይልቅ ከፍትህ ጋር ያወራሉ። እንዲህ እየሆነ እማዬ ሆስፒታል ከገባች አንድ ወር አልፏታል።

" ፍቅር ብርሃን ነው ሚሚሾ አይደበቅም። በምንም ልትከልዪው ብትሞክሪ የብርሃን ፍንጣቂዎቹ ቀዳዳ እየፈለጉ ያበራሉ። እንደሚወድሽ ትጠራጠሪያለሽ?” አለችኝ።

"አላውቅም እማ! ገና አጭር ጊዜ ነው ካወቅኩት እንኳን። አላውቀውም!” ከማለት ውጪ ግራ ስለሚያጋባኝ ድርጊቱ ለሷ ማውራት አልችልም። አንዴ በፍቅር አክናፍ አፈናጦኝ አርያም የደረስኩ እንዲሰማኝ ያደርገኝና መልሶ ለቀናት በመሃከላችን ከጓደኝነት የዘለለ ነገር እንደሌለ ያስመስላል። ባለፈው ለት አቅፎኝ አድሮ ጠዋት ስነቃ አጠገቤ ካለመኖሩ በላይ ሳገኘው ማታ እቅፉ ውስጥ እንዳልነበርኩ ያስመስላል። አላውቅም! እንዴትስ ማወቅ እችላለሁ? አዝኖልኝ ይሆን ወዶኝ ራሱ ካልነገረኝ በምን አውቃለሁ?

"ሚሚሾዬ የምትፈልጊውን ነገር ለማግኘት ምቹ ጊዜ እስኪመጣ ወይም ጊዜው የምትፈልጊውን ይዞ እስኪመጣ ቁጭ ብለሽ ለመጠበቅ ህይወት በጣም አጭር ናት። በእጅሽ ያለውን ጊዜ ምቹ አድርጊው።” አለችኝ የተዘጋጀ ምግብ እንደመጉረስ ቀላል ነገር የተናገረች ይመስል ልዝብ ብላ።

በቆምኩበት ሀሳብ ሳመነዥክ ፍትህ ተመልሶ መጣ።
“ባለፈው እማዬ ራሷን የጎዳች ቀን ስናወራ የእህቴን ሰርግ ላለመሄድ እና ለአባቴ ጥብቅና ላለመቆም በምላሹ አንድ ነገር እንዳደርግልህ ጠይቀኸኝ ነበር። ታስታውሳለህ? ምን ነበር?” አልኩት ለመሄድ እየተጣደፈ ስለነበረ ላቆየው ፈልግያለሁ።

"እኔ እንጃ! ብዬሽ ነበር? ትዝ አይለኝም።” አለኝ ጥድፈቱን ሳያቆም ትከሻዬን ጨበጥ አድርጎኝ በቆምኩበት ትቶኝ ሄደ። ከፋኝ። የሚናገረውንና የሚያደርገውን ነገር በፍቅር የምተረጉመው ብቻዬን እንደሆነ ተሰማኝ።ለእርሱ ከቀን ተቀን የተለመደ ድርጊትና ንግግር በላይ ዋጋ ያለው ነገር አልነበረም ማለት ነው። እግሬን እየጎተትኩ እማዬጋ ተመለስኩ። እማዬ እየደጋገመች ምን እንደሆንኩ ትጠይቀኛለች። እየደጋገምኩ የሆንኩት ያለመኖሩን እመልስላታለሁ። ሲመሻሽ ካሳሁን ቢመጣም እንደሌላው ቀን መደሰት አልቻልኩም። አንድ የሰውነቴ አካል የከዳኝ መሰለኝ። በሩ በተከፈተ ቁጥር እሱ እየመሰለኝ አፈጣለሁ። አባቴ ሊያድር ስለመጣ እኔና ካሳሁን ወደየቤታችን ሄድን። ጭራሽ ያለወትሮው ስልክም ሳይደውልልኝ አደረ። በሚቀጥለው ቀን ምሽት ሆስፒታል እማዬጋ ቁጭ ብዬ ደውሎልኝ
ሊያገኘኝ እንደሚፈልግ ነገረኝ።

"ታዲዎስ ተገድሏል!” አለኝ የተቀጣጠርንበት ካፌ ደርሼ ገና ሳልቀመጥ። ያለኝ ገብቶኝ ሳያልቅ ቀጠለ "ያልታወቁ ሰዎች በጩቤ ወግተውት መንገድ ላይ ወድቆ ነው የተገኘው።” ተስፋ የቆረጠ፣ የተናደደ፣ ያዘነ… … ብዙ ዓይነት ስሜት ነው የሚፈራረቅበት። "…… ጓደኛው ነው ደውሎ የነገረኝ። ምን እንዳለኝ ታውቂያለሽ? ‘በሰላም ይኖር የነበረውን ልጅ አስገደልከው። አንተ ነህ ያስገደልከው።’ አለኝ።” የተፈጠረው ነገር በጣም ስሜታዊ ስላደረገው ቅደም ተከተሉን ያልጠበቀ ወሬ ነው የሚያወራኝ።

የትዝታ ፍቅረኛ ታዲዎስ ባልታወቁ ሰዎች ተገድሎ ለቤተሰቡ መርዶ ተረድቷቸው አስክሬን እየጠበቁ ነው። ፍትህ በተደጋጋሚ ደውሎለት ስልኩ እንቢ ብሎት ነበር። የትዝታ አባት ትንፍሽ ቢል እንደሚገድለው ለፍትህ በተናገረ ማግስት ሞቶ መገኘቱ አጋጣሚ ሊሆን አይችልም። ግን ማስረጃ የለም። አጋጣሚ ግጥምጥሞሽም ሊሆን ይችላል። የሟች ጓደኛ ሞቱ ከፍትህ ጋር ከማውራቱ ጋር የተያያዘ መሆኑን በምን እርግጠኛ ሊሆን ቻለ?

"ትዝታ አንቺን ማግኘት ትፈልጋለች።” አለኝ በጎርናና ድምፅ "ምናልባት የምትነግርሽ ነገር ሳይኖር አይቀርም። የታዲዎስን አሟሟት ስነግራት ኩርምት ብላ ነበር የተንሰቀሰቀችው። እሷም ‘አስገደልከው’ አለችኝ። ማን? ለምን? ለሚለው ጥያቄዬ ግን መልሷ ዝምታ ነበር።” ሀዘናቸው ተጋብቶበታል። እሱም አስክሬን የሚጠብቅ ለቀስተኛ መስሏል።

"እሺ! አንተ ተረጋጋ እና ወዴት እንደሚወስደን እናስብ።”

"አይታይሽም? ወዴትም መሄጃ የለም።”

"ገና ከአሁኑ ተስፋ ቆርጫለሁ እንዳትለኝ? ገና ሳትጀምረው ይሄ ጉዳይ የተወሳሰበ ሊሆን እንደሚችል ነግሬህ ነበር። ገና ከመጀመርህ እጅ መስጠትህ ነው?” ስለው በቃል አልመለሰልኝም። ሁኔታው ግን የመሸነፍ ነው። ላፅናናው አልሞከርኩም። ምን እያሰበ እንደሆነ አላውቅም። እኔም በሀሳብ ተጠምጃለሁ። …… ሆስፒታል ማደር የእርሱ ተራ ነበረ።

"ወደቤት ሄደህ እረፍ! እማዬጋ እኔ እሆናለሁ።" አልኩት። ሄደ። እስከ ሶስት ቀን አልተመለሰም። ስልኩም ዝግ ነበር።

"ምን ሆኖ ነው? አስቀየምሽው እንዴ? ንገሪኝ ምን ተፈጥሮ ነው?” እማዬ ሶስት ቀን ስላላያት በጥያቄ ልትደፋኝ ነው። በስራ ምክንያት መሆኑን ብነግራትም አላመነችኝም። ካሳሁን ሲመጣም ተመሳሳይ መልስ ቢሰጣትም አላመነችም። አባቴ እንኳን ‘ምነው ጠፋ?’ ብሎ ጠየቀኝ።

ትዝታን ላገኛት ቀጠሮ አስይዤ አገኘኋት። አልቅሳ የሷን ጉዳይ እንድንተወው ለመነችኝ።

"ነገር መቆፈራችሁን ካልተዋችሁ ሌላ ተጨማሪ ሰው ይጎዳል።” አለችኝ ቃል በቃል።

"ተጨማሪ ማለት ከታዲዎስ ሌላ ማለትሽ ነው? ማነው የሚጎዳው? ልጅሽ? አጎትሽ? ሌላ ማን?” ከዚህ በኋላ ለጠየቅኳት ብዙ ጥያቄ መልስ አልሰጠችኝም።

"የልጅሽ አባት በሰው ነው የተገደለው። በእርግጠኝነት የምታውቂው ነገር አለ። መናገር ግን አትፈልጊም። ማንን ነው እየተከላከልሽ ያለሽው? ለልጅሽ ስታድግ ምን ምላሽ ይኖርሻል? አባቴስ ስትልሽ ምንድነው የምትያት? የአባቷን ገዳይ በነፃነት እንዲኖር የፈቀድሽበትን ምክንያት ታስረጃታለሽ? አባቷን በግፍ ላጣች ልጅ በቂ ምክንያትስ ይመስልሻል? ወይስ የአባቷን አሟሟት ትዋሻታለሽ? እስከመቼ? እውነት ቢረፍድም አንድ ቀን መውጣቷኮ አይቀርም።……… ” ምንም ቢሆን እናት ናትና ደካማ ጎኗ ልጇ ናት። ትዝታ ግን አልተሸነፈችም። ልወጣ ቦርሳዬን ሳነሳ

"የሱ ልጅ አይደለችም። አባቷ አይደለም።” አለችኝ። ከዛ በላይ ግን ልትነግረኝ አልፈለገችም።

★ ኸረ ወየው አያልቅም እንዴ? 😂

@wegoch
@wegoch
@paappii
~ ራሴው ማበዴ ነው…… #10~
(ሜሪ ፈለቀ)

«የሱ ልጅ አይደለችም። አባቷ አይደለም።” አለችኝ። ከዛ በላይ ግን ልትነግረኝ አልፈለገችም። እየወጣሁ ለፍትህ ደወልኩለት እና ተገናኘን። ከትዝታ ጋር ያወራሁትን ነገርኩት። ሞቶ የነበረው መነቃቃቱ አንሰራርቶ መላምቶቹን ይነግረኝ ጀመር።

"የልጇ አባት እሱ ያለመሆኑን የተናገረችው እውነት ከሆነ ትዝታ ከሌላ ሰው ጋር ግንኙነት ነበራት። ምናልባትም አጎቷ ልድራት ነው ካለው ሰውጋ… … አንዱ ባለስልጣን ወይም አንዱ ሀብታም ይሆናል። ምናልባት ሟች በሆነ መንገድ ከዚህ ሰው ጋር ተያያዥነት ሊኖራት ይችላል። …… ምናልባት…… በስመአብ ወ ወልድ… … እኔ ያሰብኩትን አስበሻል?”

"በትክክል!!…… እያሰብኩ ያለሁት እንደሱ ነው!” አልኩት ያሰብኩት እየዘገነንኝ::

የገዛ ሚስትህ በአደባባይ አብረሃት እየሄድክ ጡቶቿን የከለላቸውን ጨርቆች ገፋ ሳምልኝ ብትልህ ብልግና ይሆንብሃል። በሷ ድርጊት አንተ ትሸማቀቃለህ። መኝታ ቤታችሁ ውስጥ ራቁቷን ሆና ያንኑ ነገር ብትልህ ለቦታው የሚገባ ቅድስና አድርገህ ልትቆጥረው ትችላለህ። ምናልባትም ከዛ በላይ ‘ስድ’ ብትሆንልህ ያምርሃል።

በመንፈሳዊው ዓለም የመጀመሪያው ለሰው ልጆች የተሰጠ የተፃፈ ህግ አስርቱ ትዕዛዛት ናቸው። አትግደል የሚል ህግ ፅፎ ሰጥቷቸዋል። ጠላት በተነሳባቸው ጊዜ ግን አሳልፌ ሰጥቻችኋለሁና ዝመቱባቸው ብሎ እልፎች ያስገድላል።

በምድረኛው ህግም መግደል ወንጀል ነው ይልሃል። አንዳንድ ወንጀሎች ግን በዛው ህግ በሞት ያስቀጣሉ። እናም ፍትህ ነው ይልሃል። በተመሳሳይ በቀል ሀጢያት ነው ይሉሃል። የበደለህን ሰው አስጠፍንገህ ወህኒ ማስወርወር ግን በቀል ሳይሆን ፍትህ ነው ትባላለህ። ምናልባት አንተም ከዛ በላይ የምታደርገው ላይኖር ይችል ይሆናል እኮ!

አየህ በዚህኛው አለም ስትኖር ሀጢያት ወይ ፅድቅ፣ ልክ ወይ ስህተት፣ መልካም ወይም ክፉ፣ ብልግና ወይ ጨዋነት… … እነዚህ አንዱ ከሌላኛው ተቃራኒ ዋልታ የሚገኝ መቼም የማይስማሙ ሊመስል ይችላል። አይደለም! እንደውም አንዱ በአንደኛው የሚተካካበት ቦታ አለ። በመሃከላቸው የተሰመረ የሚመስልህን ቀይ መስመር ስታልፍ ከአንደኛው ክልል ወደሌላኛው አልተሻገርክም። ጊዜ፣ ቦታና ሁኔታ…… ምናልባትም ሌላ ተጨማሪ ገቢር ትርጉማቸውን ያፋልሰዋል።

በዚህ ተረክ ውስጥ ማለትም የሆነውን ለመረዳት(ለመዳኘት አላልኩም) ከነዚህ ሁለት ተቃራኒ ፅንፍ ከሚመስሉ ሀሳቦች መሃከል በሀሳባችን በምናሰምረው መሃል መስመር ላይ እንቁም! ወደየትኛውም እቅፍ ተጠግተን አንሙቅ።

እናማ ከአባቴና ከእናቴ ደብዳቤ .. ከተነገሩኝ እና ከነበርኩበት ተነስቼ የሆነው በአጭሩ ሲደበለል እንዲህ ነው…………

አንድ
የውብ ዳር አባቴን እና እናቴን ለያይታ አባቴን ያገባችው ስላፈቀረችው አልነበረም። ለበቀል እንጂ! የውብዳርና እማዬ ከልጅነት ጀምሮ ጓደኛሞች ነበሩ። የውብዳር ወንድም ያፈቀራትን እናቴን ማግባት የነፍስም የስጋም ፍፃሜያዊ ትልሙ ነበር። እና እናቴ ከአባቴ ጋር ፍቅር ስትጀምር ለምናልባቱ ያስቀመጡት የባይሆን ጭላንጭል የሌላቸው ስጋና ነፍሱ አድመው በዚህ ዓለም ዓለመኖርን መረጡ። የውብዳር ለብቸኛ ታላቅ ወንድሟ መርዝ ጠጥቶ መሞት ተጠያቂዋ ጓደኛዋ መሆኗን ብታምንም በራሷ እጅ ፍትህን ካላደረገች በቀር በየትኛውም ህግ እንደማትዳኝ ታውቃለች። (እዚህጋ የእማዬን ሚና በትክክል አላውቅም። ‘ከዳችው’ የሚለውን የየውብዳርን ቃል ወይም ‘ምንም አልነበረንም’ የሚለውን የእማዬን ቃል የትኛውን እንደማምን አላውቅም።) የሆነው ሆነና እናትና አባቴ ሲጋቡ የእናቴ ሚዜዋ የውብዳር ነበረች። በዓል ሆኖ እኛ ቤት ያልመጣችበት ቀን የለም።(እናቴ ስራ የሆነችባቸውን በዓላት የእመቤትነት ስርዓቱን የምትከውነው እሷ ነበረች።) እኔ ወይ አባዬ ታመን እማዬ ከሌለች እያደረች የምታስተዳድረን እሷ ነበረች። ልደቴ ሲከበር የሚያጓጓኝ የእርሷ ስጦታ ነበር። በቤታችን የፎቶ አልበም ውስጥ እሷ የሌለችበት ፎቶ ውስን እንደሆነው ሁሉ በኑሯችን ውስጥም እሷ የሌለችበት ገፅ ውስን ነበር።

ዘጠኝ ዓመት እስኪሆነኝ ድረስ አባትና እናቴ ሲሳሳሙ ወይ ሲላፍ ደርሼባቸው በሀፍረት ጉንጫቸው ቀልቶ አስደንግጫቸው ይሆናል እንጂ ተጣልተው ሲጨቃጨቁ ከእንቅልፌ ነቅቼ ያውም እናቴ አባቴን በጥፊ ስትለው አይቼ በመጮሄ አስደንግጫቸው አላውቅም። በሰዓቱ የፀቡ መንስኤ እማዬ የሴት ፓንት መኝታ ቤት ማግኘቷ መሆኑን ብሰማም አባዬ ከየውብዳር ጋር መማገጡን እሱ ከሰጠኝ ደብዳቤዎች ነው የተረዳሁት። (በደብዳቤው ላይ ጠጥቶ እንደነበር እና ስህተት እንደሆነ ፅፎ ይቅርታ ይለምናታል። የውብዳር ፓንቷን መኝታ ቤት ጥላ መሄዷ ያሰበችበት ተንኮል ነበረ።) ከዚህ በኋላ በብዙ ላብና እድሜ የከመሩትን ጡብ በአንድ ቀን እንደማፍረስ ሁሉ ቤታችን የፈረሰው ተምዘግዝጎ ነበር። እማዬ የበለጠ የጎዳት ከሌላ ሴት ጋር መተኛቱ አይደለም። ከምትወዳት ጓደኛዋ ጋር መተኛቱ እንጂ…… የየውዳር በቀል የገባት ሲቆይ ነው።

እዚህ ተረክ ውስጥ ማናቸውም ጥሩ አይደሉም። ማናቸውም ክፉ አይደሉም። እንደማንኛውም ሰው ባበዙት ድርጊት ይጠሩበታል። ቤታችን በየእለቱ ጭቅጭቅ ሆነ። እማዬ አባቴን ጥላ ከእኔጋ ማደር ጀመረች። በነዚህ ሁሉ ጊዜያት የይቅርታ ደብዳቤ ፅፎላታል። ብዙም ሳይቆይ የውብዳር ማርገዟ ታወቀ። እናቴ ከልጁና ከእሷ እንዲመርጥ ነገረችው። ይሄን ከሰማች በኋላ እማዬ አንድ ቀን ከስራ ውጪ ሌላ ቦታ አደረች። ከሌላ ሰው ጋር… … አባቴ አወቀ። …… የአባቴ በደል ወይስ የራሷ ፀፀት .... ትዳሯ ሊፈርስ መንደርደሩ ... አላውቅም ብቻ ብዙ ሳይቆይ በአዕምሮ መታወክ ስራዋን አጣች። እህቷ ፀበል ይዛት ትኳትን ጀመር። አባቴ መምረጥ ነበረበት። እብድ ሚስቱን ወይም በፍቅርህ ሞትኩ የምትለውን የውብዳርን፤ በደሏን በራሱ በደል አጣፍቶ ይቅር ማለት እና ከእናቴ ጋር መኖር (ይሄ ያልተወለደች ልጁን ችላ ማለትን ያካትታል።) ወይም አዲስ ህይወት መጀመር።

አየህ ክልል ብሎ ፍልስፍና እንደሌለ? ያበደች ሚስቱን ትቶ ገና ተወልዳ ያላያትን ልጁን መምረጥ ልክ አይደለም። ለፍቅሩና ለሚስቱ አድልቶ በእነርሱ በደል ምንም የማታውቀውን ልጁን ቤተሰብ መንሳትም ልክ አይሆንም። ግድ ሲሆን ግን ከሁለት ስህተት አንዱን ስህተት መምረጥ ልክ ይሆናላ!

ትልቅ የሚባል ስኬት ፣ ፍፁም የሚባል ፍቅር ፣ ግዙፍ የሚባል እምነት ፣ የማይረታ የሚባል አንድነት…… ለመውደቅ ‘ትልቅ ምክንያት’ ሊያንገዳግደው ግድ አይደለም። ብዙ ትንሽ ምክንያቶች ከስሩ መንግለው ይደፉታል።

ሁለት
ቤተሰቦቼ በራሳቸው ጡዘት ሲጦዙ ዕጣ ፈንታዬ ምን እንደሚሆን አርቀው ያላሰቡልኝ እኔ እነርሱ በበሉት የተበላሸ ምግብ እኔ ስቀዝን ኖርኩ። እነርሱ በበሉት የተበላሸ ፍሬ የእኔ ጥርስ በለዘ። እናቴ በከፊል ጤነኛ በሆነ ጭንቅላቷ በከፊል በእህቷ ጭንቅላት ከአባቴ ጋር ላለመኖር ወሰነች። አባቴ የውብዳርን አገባ። ከአባቴ እና ከእንጀራ እናቴጋ ሁለት ዓመት ኖርኩ። ያጣሁት እናቴን ብቻ አልነበረም። አባቴም በዝምታና በድባቴ የተከበበ እኔ ከማውቀው ሳቅና ፍቅር ከሞላው አባቴ የተለየ ሌላ ሰው ሆነ። አብዛኛውን ምሽት አምሽቶ ጠጥቶ ስለሚገባ አላገኘውም። የቤቱ አዛዥ ሚስቱ ናት! እሱ ደግሞ ለሚሆነው ሁሉ መልሱ ዝምታ ነው። አክስቴ ስትወስደኝ ሚስቱ ምን ያህል እንደምትከፋብኝ ስለሚያውቅ አባቴ አልተቃወመም።

እዚህጋ ስህተትም ልክም ፅድቅም ሀጢያትም… … መልካምነትም ክፋትም… … ሁሉም ቦታ የላቸውም። ምክንያቱም ለእነዚህ ሁሉ ክስተቶች አንዲት ጥሬ ዘር ያላበረከትኩ
እኔ ጎተራ ሙሉ መራራ ፍሬ ሳጭድ በየትኛው ሚዛን ተዳኝቶ ከአንዳቸው ይመደባል?

"ብትጠይኝ አልፈርድብሽም። በዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ የተጎዳሽው አንቺ ነሽ።” አለኝ አባቴ ከዘመናት በኋላ ዛሬ ላይ

"ስለእውነት እንደክህደትህ ብጠላህ ደስ ይለኛል። ከቤትህ አውጥተህ እንደጣልከው ቆሻሻ ስለረሳኸኝ አስከፍልህ ነበር። እድሜ ለእናቴ በል በሷ ልብ ውስጥ ስላነገሰችው ማንነትህ ስል እንደማንኛውም በህይወቴ ትርጉም እንደሌለው ሰው ቆጥሬሃለሁ።”

"ምንም ብልሽ ላንቺ በቂ የሚሆን ምክንያት ልሰጥሽ አልችልም። ግን አልከዳሁሽም። አንድም ቀን ረስቼሽም አላውቅም። አንቺንም ሆነ እናትሽን እንዳላያችሁ አክስትሽ በህግ አስከልክላኛለች። አንቺን ከእናትሽ መንጠቁ ደግሞ
እናትሽን እንደመግደል ነበር።”

አያችሁ…… ትልቅ ምክንያት አያስፈልግም። አባት ልጁን ለመተው እንኳን ቢሆን ትንንሽ ብዙ ምክንያቶች ሀያል ጉልበት አላቸው። እናቴን በማጣቱ መጎዳቱ፣ ሌላኛዋንም ልጁን እንደእኔ የተመሳቀለ ህይወት እንዳይኖራት ለመከላከል፣ የአክስቴ ሀይለኛነት፣ የእኔ እማዬጋ ለመኖር መፈለግ፣ የእንጀራ እናቴ ክፋት……… አንዳቸው ለብቻቸው ምንም የማይሆኑ ሲደማመሩ በኔና በሱ መሀከል ያለውን ትስስር መበጠስ የቻሉ ምክንያቶች ናቸው።

አሁን ደግሞ ሚስቱን ሊፈታት ነው። ምክንያቱ ልጁ ስላገባች ከየውዳር ጋር የሚያኖር ምክንያት እንደሌለው ስለሚያስብ።

"ይቅርታ ልጄ! አሁን ይቅርታዬ ያለፍሽበትን ነገር እንደማይሽር አውቃለሁ። አስቤሽ ሁሌም እንደምታመም ግን እወቂ።”

"አሁን ዋናው ነገር የእማዬ ደስታ ነው። በቀራት ጊዜ ደስተኛ እንድትሆንልኝ እፈልጋለሁ።” አልኩት አንድ ቀን መጥቶ ይጠይቀኛል ብዬ የጠበቅኳቸው ቀናት እንዳልነበሩ፣ ከእኔና ከእናቴ የውዳርንና እህቴን በመምረጡ በእህቴ እንዳልቀናሁ፣ እነርሱን ትቶ ከእኛጋር እንዲኖር ልለምነው አስቤ እንደማላውቅ: …………

ሶስት
ፍትህ ፍርዱ ልክ እንዳልሆነ እያወቀ ትዝታ 25 ዓመት ሲፈረድባት እጅ ሰጥቶ መቀመጥን መረጠ። ምክንያቱ ደግሞ የነበረው ምርጫ ማሸነፍ ወይ መሸነፍ አልነበረም። ይሄ ቀሽም የአንደኛ ደረጃ መምህር ያዘጋጀው ዓይነት ምርጫ ቀላል በሆነለት ነበር። ሁለት የማይመረጡ ምርጫዎች ነበሩት። ትዝታን ማዳን ወይ ቤተሰቡን ማዳን!! ትዝታን መርጦ ከሚወዳቸው አንዳችንን ማጣት ለእርሱ በምንም ስሌት ልክ አይሆንም። የሚወዳቸውን መርጦ ትዝታን መክዳትም በሂሳብም በሳይንስም ልክ አይሆንም። አየህ ድንበር ብሎ ፈሊጥ እንደሌለ? ግድ ሲሆን ከሁለት ስህተት አንዱን ስህተት መምረጥ ልክ የሚሆንበት አጋጣሚ ይፈጠራል። ቆይ ቆይ…… እንዲህ ቀላልና ምክንያታዊ ውሳኔ አልነበረም። ሁላችንንም ዋጋ ያስከፈ እንጂ…… ከስሩ እንጀምር.........

እንደውም ትዝታን ማዳን የሚለው ምርጫ አይደለም። ትዝታ መዳን አትፈልግም። ደፍሯታል ወይም አታሏታል…… ልጅን ያህል ነገር ወልዳለች። ለምን ለዚህ ሰው ትከላከልለታለች? የልጇ አባት አጎቷ መሆኑን ፍትህ ሲጠይቃት ድንጋጤዋ እውነቱን ቢያሳብቅባትም ካደች።

"በቅቶኛል። ራሁ ይህቺ ልጅ ምንም መስዋዕትነት የሚገባት አይደለችም።” አለኝ ፍትህ።

"ፍትህ ለእርሷ ብለህ ነው ወይስ ለሙያህ? ለእውነት? ለፍትህ?”

"የሆነ ሰው አርፌ ካልተቀመጥኩ አንቺን፣ ካስዬን ወይ እማዬን እንደሚያስከፍለኝ አስጠንቅቆኛል። ማስፈራሪያ ብቻ አይደለም።" አለኝ በሰጋ ልብ። እሱ ይሄን ከማለቱ ከአንድ ሰዓት በፊት የማላውቀው ሰው ሆስፒታሉ መግቢያ ጋር አስቁሞኝ ተመሳሳይ ማስጠንቀቂያ ለእኔም ሰጥቶኛል።

★ ለመጨረስ ሳንቃረብ አልቀረንም ★

@wegoch
@wegoch
@paappii
~ ራሴው ማበዴ ነው… #11 ~
(የመጨረሻ ክፍል)
(ሜሪ ፈለቀ)

[አልነገርኩትም። የማላውቀው ሰው የሆስፒታሉ መግቢያ በርጋ ጠብቆኝ የትዝታን ጉዳይ ማነፍነፍ ካላቆምኩ ከምወዳቸው ሰዎች አንዳቸውን እንደማጣ እንዳስጠነቀቀኝ አልነገርኩትም። ብዙ ነገር አልነገርኩትም። እንዲያውም ምንም አልነገርኩትም። እማዬ ከዚህ በኋላ ህክምና የሚፈይድላት ነገር ስለሌለ ወደቤቷ ወስደናት ዓይን ዓይኗን እያየሁ የምትሞትበትን ቀን መጠበቅ ትኩስ ቁስል ላይ ሚጥሚጣ እንደመበተን እየለበለበኝ እንደሆነ አልነገርኩትም። እቅፉ ውስጥ ሆኜ እዬዬ ብዬ ማልቀስ እንደምፈልግም። ከሰሞኑ አባቴን ሆስፒታል በማድረስ ሰበብ አዘውትረው ሲመጡ እህቴና ባሏን ማየት ልቤን በደም ፈንታ ቅናት እንደሚያስረጨው አልነገርኩትም። በእኔና በእርሱ መሃል ምንም ነገር እንደሌለ የሚሆነው መሆን እየከፋኝ አልቅሺ አልቅሺ እንደሚለኝ አልነገርኩትም። በዚህ ሁሉ ማጥ ውስጥ አቅፎኝ ያደረ ቀን የማግኩት ጠረኑን እርሱ አጠገቤ ሳይኖር እንኳን ካለበት ንፋሱ እያንጓለለ ለአፍንጫዬ እንደሚያቀብለው አልነገርኩትም። አጠገቤ ሆኖ ስለስራ እያወራኝ ልነካው እንደምፈልግ፣ ልስመው እንደምጎመዥ፣ እርሱ የኔ ቢሆንና በፈለግኩት ቁልምጫ ልጠራው እንደምመኝ… … አልነገርኩትም።]

"ማንናቸው?" አለኝ ዓይኔን ተከትሎ መኪና ውስጥ ያሉትን እህቴንና ባሏን እያያቸው

"እህምም…… እህቴ ናት! ባሏ ነው። አባቴን ወደቤት ሊያደርሱት እየጠበቁት ነው።” አልኩት አንገቴን ሰብሬ

"ታዲያ ምን?” አለኝ ዓይኔን እየፈለገ

"ምን?”

"ለምንድነው ስታያቸው በነበረው እይታ የምታያቸው? ምንድነው እሱ?"

"ኸረ ምንም አይደለም። በቃ ከእህቴ ጋር ስለማንነጋገር ነው።"

"አይደለም ራሁ። እያየሁሽ እኮ ነው። ቆይ ምንባደርግ ነው የተሰማሽን ልትነግሪኝ የምታምኚኝ? የበለጠ የቀረብኩሽ በመሰለኝ ቁጥር ለአካልሽ እንጂ ለልብሽ አልቀርብሽም። አብሬሽ ውዬ ባድር ቅርበቴ አይሰማሽም።…”

"ፍቅረኛዬ ነበረ። እህቴ ያገባችው ሰው…” ወቀሳውን እንዲያቆምልኝ ይሆን ለልቤ መቅረቡን እንዲያውቅልኝ አላውቅም። ነገርኩት!!

[ ዘጠነኛ ክፍል ስገባ አንድ ወንበር ላይ ከተቀመጥን ጀምሮ ብቸኛ ጓደኛዬ ዓለማየሁ እንደነበረ ግን አልነገርኩትም። የአስረኛ ክፍል ፈተና ተፈትነን ከተማሪዎች ጋር ከከተማ የወጣን ጊዜ ከንፈሬን ሲስመኝ ከርሱ ውጪ ያለውን ዓለም እንደረሳሁ አልነገርኩትም። በመከራ ከተከበበው ኑሮዬ የተረፈኝን ሰዓት ከርሱ ጋር ማሳለፌ በነገ ተስፋ እንዳልቆርጥ መፅናኛዬ ሆኖ በጥሩ ውጤት አብረን ዩንቨርስቲ እንደገባን አልነገርኩትም። ብዙ ጊዜ ‘ድብቅ ነሽ አላውቅሽም’ እያለ ቢነጫነጭም ይተወኛል ብዬ ለአፍታ አስቤ ባለማወቄ ሲተወኝ ከእማዬጋ አብሬ ማበድ ዳድቶኝ እንደነበረም አልነገርኩትም። የባሰው ደግሞ ከዓመታት በኋላ እሱ ዩንቨርስቲ አስተማሪ ሆኖ ተማሪው ከሆነችው እህቴ ጋር በአጋጣሚ ይሁን አስቦበት እስከአሁንም በማይገባኝ ሁናቴ ግንኙነት መጀመራቸውን ሆነ ብሎ ደውሎ የነገረኝ ማታ ራሴን ልስት እንደነበረ አልነገርኩትም። እህቴ ከዩንቨርስቲ በተባረረች በወራት ውስጥ የሰርጋቸው ጥሪ ካርድ ሲደርሰኝ ራሴን ባለመፈለግ ስሜት ውስጥ አዝቅጬው መብሰክሰኬን አልነገርኩትም። ከዓለማየሁ በፊትም በኋላም ሌላ ፍቅር እንደማላውቅም አልነገርኩትም።]

"እና አሁንም ድረስ ትወጂዋለሽ? እየቀናሽ ነው?” አለኝ

"አይይይ ለሱ ምንም ስሜት የለኝም። በሱ አልቀናም።”

"በሷ?" እያለኝ በጣም ተጠጋኝ። ትንፋሹ ጉንጮቼ ላይ እያቃጠለኝ አስቤ የተሰደሩ ቃላት መናገር አልችልም ነበር። በጭንቅላቴ ንቅናቄ ‘አዎን’ አልኩት። አልበቃውም እንድቀጥልለት ይጠብቃል። ምራቄ እያነቀኝ ነው።

"አባቴ ከእኔ እሷን ነበር የመረጠው። ፍቅረኛዬም… …” አላስጨረሰኝም ከንፈሬን በከንፈሩ ከደነው። መሳሙ ቀለምም ነበረው፣ ሽታም ነበረው፣ ጣዕምም ነበረው……

"በሚፈጠሩ ክስተቶች ውስጥ ራስሽን እየከተትሽ አትስፈሪ። ሁኔታዎች ሁሉ አንቺን ሚዛን ላይ አስቀምጠው አይለኩም።” አለኝ ለምን ያህል ደቂቃ እንደሆነ ስሞኝ ሲያበቃ… … ሰምቼዋለሁ? ገብቶኛልስ? መሳሙን እያጣጣምኩ ነበር።

"ተያቸው! እርሻቸው!” አለኝ ወደእነእህቴ እያየ። እያየኋቸው ነበር። የልጅ ስሜት ቢመስልም አዎን ሲስመኝ ማየታቸውን ለማረጋገጥ ነበር የማያቸው። አለ አይደለ እኔም ሰው አለኝ አይነት! አልጎዳችሁኝም አይነት! እንዳዩኝ በማወቄም በከፊል የታባታችሁ አይነት ስሜት……

በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት ብዙ ነገር ተቀየረ። እንደውም ሁሉም ነገር!! እማዬ ወደቤት መጣች። ካስዬና አባቴ እቤታችን እየመጡ እናቴን መጠየቅ ጀመሩ። እኔና ፍትህ ቤተሰቦቻችን እስኪያውቁ እንደፍቅረኛሞች ገብተን መውጣት ጀመርን። ፍትህ የትዝታን ጉዳይ ተለዋጭ ቀጠሮ ሊጠይቅ በተዘጋጀበት ወቅት እጅ ያሰጠው ሁናቴ ተፈጠረ። ሁላችንንም ሁሉንም የሚቀይር ነገር ተፈጠረ:: አባቴ ሞቶ ተገኘ።
.
.
.
አዎ አባቴ ....


ቆይ ቆይ ፍትህ በትዝታ ጉዳይ ተስፋ መቁረጡ እና 25 ዓመት ሲፈረድባት መዋጡ ቀላል አልነበረም። ቤተሰቡን በሙሉ ያስከፈለ መስዋዕትነት እንጂ… …… ካልንበት እንቀጥል። አባቴ ተገደለ! ይቅርታ እንዳደርግለት ሲለማመጠኝ የነበረው አባቴ አንድስ እንኳን በጎ ቃል ሳልነግረው ሞተ። አልጠላህም ሳልለው.... አንድ ቀን በወጉ ሰላም ሳልለው...... በሱ ምትክ ከካስዬ ጋር እንደልጅ እና አባት ስንሆን ሲቀና ሰንብቶ ..,,,,በራሴው ጉዳይ እርሱ አንዲት ጠጠር ባላበረከተበት የነገር ካብ ህይወቱን አጣ!! ለፍትህ ይሄ የመጀመሪያው መሆኑ እና ካላረፈ ሌሎቻችንም ተራ ጠባቂዎች መሆናችን እና ቀጣይዋ እኔ መሆኔ ማስጠንቀቂያ ደረሰው። ይሄኔ ነው እጅ የሰጠው! ከእኔ በላይ ሁሉ የተጎዳ መሰለኝ።

"በፍፁም አንቺን ለምርጫ ማቅረብ አልችልም። አንቺን ማጣት አልችልም።” ይለኛል እየደጋገመ። ለማን እንዳለቀሰ ያልገባኝን ለቅሶ በአባቴ ቀብር ላይ ምርር ብሎ አለቀሰ። ግራ የገባው ስሜት ውስጥ ጠለቅኩ። አንዱ አካሌ ሽባ የሆነ ነገር ይመስለኛል። ከሬሳው ጋር የቀበርኩት ነገር ያለ ይመስል የሆነ ስሜቴ ወደአባቴ መቃብር ይጎትተኛል።

የባሰው ነገር ለእናቴ የፍቅሯን ሞት ማርዳት ነበር። በየቀኑ እየመጣ ሲያያት የከረመውን ሰው በምንም ሰበብ ቀረ ልንላት አንችልም። እንደገና እንደተዋት በምንም ምክንያት ሰንገን ብንነግራት ጤነኛ አትሆንም። መሞቱንም ብታውቅ ጤነኛ አትሆንም። ቢያንስ ግን ከመከዳት ስሜት ፍቅረኛዋ እያፈቀራት መሞቱን ማወቋ ይሻላል በሚል ተስማምተን የተሻለ ሁኔታ ላይ ያለው ካስዬ ነገራት። ዝም አለች። ለሁለት ሰዓታት ዝም አለች። እኔን የምታይበትን መንገድ አልወደድኩትም። ያንቺ ጦስ ነው ፍቅሬን ያሳጣኝ አይነት መልዕክት አለው። ድንገት ከየት ባመጣችው ጉልበት እንደሆነ እንጃ ተስፈንጥራ ተነስታ ቀብሩን እሄዳለሁ ብላ አመሰችን። ካስሽ ይዟት ሄደ። ካስሽ ደግፏት ፍቅሯ አፈር ሲገባ አነባች። አለቃቀሷ ግጥምም ቃልም ሳይኖረው ዜማ አለው። እያየኋት ለአባቴ ይሁን ለእርሷ ብቻ አነባሁ! ስለእውነት የውብዳር እንኳን ስታለቅስ አሳዘነችኝ። በየመሃሉ ለሞቱ ተጠያቂ መሆኔን ልትነግረኝ አንዳንድ ሀረግ ትመዛለች። እህቴ አፈሩ ላይ ተልሞሰሞሰች። ትንፋሽ አጥሮኝ ደረቴ ላይ ሲያፍነኝ ነው ቀብሩ ያበቃው እና ወደቤታችን የተመለስነው።

እቤት ከመግባታችን እማዬ "ይሄ የበረራ ቁጥር… …” ማለት ጀመረች። መሬቷ ያንሳፈፈችኝ አይነት ስሜት ተሰማኝ። ግራቪቲ የከዳኝ! ያልበላሁት ምግብ ወደ ላይ ወደላይ አለኝ። እሪሪሪ ብዬ ማልቀስ እፈልጋለሁ። ግን ጉሮሮዬም
ደረቴም የታፈነ ይመስለኛል።


"እኔ አለሁ አንቺ እረፊ!” አለኝ ካስዬ። እንዳለውም ከዚያን ቀን በኋላ ኖረ። ምክንያቱም በሚቀጥሉት ቀናት እናቴ ማነሽ? ማለት ጀመረች። ፍትህንም ስታይ መበርገግ ጀመረች። የሚገርመው ካስዬን በባሏ ስም አንድዬ እያለች መጥራት ጀመረች። ከእርሱ ውጪ ማንንም አታስጠጋም። (ሀኪሟ እሷ እንኳን ሳታውቀው ለካስዬ የሆነ የተለየ ስሜት እንደነበራት እና ሲያማት ከፍቅሯ ጋር እንደተማታባት ሳይኮሎጂ ጠቅሶ መላ ምት መታ።) ፍትህ በኔ ልመናና ጭቅጨቃ ይግባኝ በመጠየቁ ስጋቱ ሊያሳብደው ደርሶ ራቅ ያለ ቦታ አዲስ ቤት ተከራይተን አብረን መኖር ጀመርን።

" 20 ዓመት ሙሉ ያላየሁት አባቴ ለወራት ካጠገቤ ነበረ። ይቅር በይኝ እያለኝ ፣ እንደምጠላው እያሰበ… አልጠላህም ሳልለው፣ ስናፍቅህ ነው የኖርኩት ሳልለው፣ ይቅር ብዬሃለሁ ሳልለው ነው የገደሉት……” እንባዬን ማስቆም ተስኖኝ በመሃከላችን ባለው ርቀት እንዲሰማት ጮክ እያልኩ ለትዝታ ነው የምነግራት። አትመልስልኝም። የአባቴ መሞትም የእኔ እንባም ስሜት የሰጣት አትመስልም።

"እናቴ ልትሞትብኝ ነው። በሰዎችሽ ጦስ አዕምሮዋ ተቃውሶ እኔን ልጇን እንኳን አታውቀኝም። ያ ምን ማለት እንደሆነ ታውቂያለሽ? ማን እንደሆንኩ ሳታውቅ ሳትሰናበተኝ እማዬ ትሞትብኛለች ማለት ነው።” ብዙ የሀሳብ ድሮች ያደሩበት በሚመስል ጠባብ እይታ ታየኛለች እንጂ አትመልስልኝም።

"ፍቅረኛሽን አስገድለውታል። አንቺንም ለማይሆን ህይወት ዳርገውሻል። ሀያ አምስት ዓመት ወህኒ እንድትበሰብሺ አጨብጭበው ሸኝተውሻል።ልጅሽም ነገ እጣዋ ምን እንደሆነ አይታወቅም። እና አሁንም ለእነርሱ ትከራከሪያለሽ! ምንድነው ችግርሽ? አሁን ካለሽበት የባሰ ምን እንዳይመጣ ነው?…… ” ለፍልፌ ሳበቃ

"እወደዋለሁ።” አለችኝ

"ማንን?” የማስበው እውነት ባይሆንና ብንንን ብሎ ቢጠፋ እየተመኘሁ

"ሰለሞንን!”(አጎቷ ነው) ደነዘዝኩ። ከሁለት አንዳችን ጤነኛ ባንሆን ነው። ለተከታዮቹ ደቂቃዎች እሷ ተናጋሪ እኔ በድን ሰሚ ሆንን። ትቻት ስወጣም በድኔን እየጎተትኩ ነበር። ጭንቅላቴ ውስጥ የሀሳብ መዘውር ያለ ይመስለኛል። አንዱ ሀሳብ ሌላውን እያስከተለ በመዘውሩ የሚፈጭ…… ርርርርር የሚል የሞተር ድምፅ ያለው መዘውር።

ሰውየው አስገድዷት አይደለም። ገና ከ12 አመቷ ጀምሮ እያባበለ ያስለመዳት የስድ ጨዋታ ነው። ለምዳዋለች። ልምዱን አልጠላችውም። እንደውም ስታወራኝ እንኳን ከሚወዱት ፍቅረኛ ጋር እንዳሳለፉት ጣፋጭ ጊዜ የፊቷ ፀዳል እየበራ ነው። በመጀመሪያ ፊልሞች ያሳያታል። እያንገላቱ፣ እያሰቃዩና እየገረፉ የሚረኩ ወንዶች ፊልም… … በስቃዩ ውስጥ የተሳመች ያህል በማቃሰት የምታብድ… … እንዲያሰቃያት የምትለምን ሴት ያለችበት ፊልም… … ቀስ በቀስ አለማመዳት። ጤነኛ ሰው ሊወደው የማይችለውን sex torture እንደ ሱስ ለመደችው። ደስ ብሏትና ፈልጋ የምታደርገው ቅውሰት ሆነ። አጎትየውን ከሴት ጋር ስላገኘችው በእልህ ታዲዎስን ፍቅረኛዋ አደረገችው። ሰላማዊው ታዲዎስ አጎቷ የሚነዳትን የእብደት ቁልቁለት ሊያንቆለቁላት አይችልምና ሱስ እንዳባዘተው ወመኔ በሱስ ጥም አዛጋች። ከሁለቱም ጋር ሆነች። በዚህ መሃል የአጎቷን ልጅ አረገዘች። ታዲዎስ የእኔ ልጅ ነው ብሎ ቁምስቅሏን ሲያሳያት ነው እውነቱን የነገረችውና የዘመኑ ቁጥር በአጎቷ በጎ ፈቃደኝነት እንዲወሰን የፈረደችበት። ከዛ የቫንፓየር ወይ የማርስ ፍጡሮች ተረት እንጂ ሰውነት የማይመስል አኗኗር ሰውየው ከወንድሙ ልጅጋር እንደባልና ሚስት ኖሩ።… … የዛን ዕለት ምሽት ሴት ይዞ እቤት መጣ! በቅናት የነደደ አካሏ ያዘዛትን አደረገች። ምንም የማታውቅ ንፁህ ነፍስ ጠፋች።

"ልጄ ከአጎቴ እንደወለድኳት እንድታውቅ አልፈልግም። ሶልም ይሄ ነገሩ ቢታወቅ ስሙ ይጠፋል፣ ይታሰራል። የወንድሙም ስም አብሮ ይነሳል(ባለስልጣን ወንድሙን ማለቷ ነው።) ሶልን እወደዋለሁ። መጥፎ ነገር እንዲደርስበት አልፈልግም።” አለችኝ የሆነ ልክ የሆነ ነገር እንደነገረችኝ ሁሉ ሀፍረት ሳይሰማት። ዘገነነችኝ። በእርግጥ አሳዘነችኝም። የሆነ አይነት በሽታ እንደሚሆን አሰብኩ። የገዛ ሰውነቴ እየሸከከኝ ወጣሁ። ጭንቅላቴ ውስጥ ያለው መዘውር አልቆመም።

የኑሯችን መዘውር የሚዞረው በሚገጥሙን ክስተቶች ግብዓትነት አይደለም እያልኩ አስባለሁ። ይልቅስ በገጠሙን ክስተቶች ላይ በወሰንነው ውሳኔና በዘረጋነው እርምጃ እንጂ…… ኑሯችን የውሳኔያችን ውጤት እንጂ ያጋጠሙን መከራና ፍሰሃ ውጤት አይደለም። ……

“ literally she is sick, serious ህክምና ያስፈልጋታል።” አለኝ ፍትህ ነገሩን ስነግረው እየሰቀጠጠው።

"ከአሁን በኋላ የትዝታ ኬዝ አይደለም። አባቷን በስድ ግፈኞች የተቀማች ልጅ ኬዝ ነው። የራሴ ጉዳይ ነው።" አልኩኝ ከመናገሬ በፊት ያሰብኩት ያልመሰለኝን ንግግር! …………

አሁን አልጨረስንም ብትሉም ጨርሰናል::

@wegoch
@wegoch
@paappiii
{{{ ቡና እና እሷ }}}
*****
(ተፃፈ ለቡና ደጋፊዎች ማለቴ ተጠቃሚዎች😜)

ቡና አልወድም . . .!!
ጥቁረቱን ሳይ ከሰይጣን ደም የተቀዳ ይመስለኝ ነበር - ቡና!!
ጥቁር ደም!! ጥቁረቱ ከጨለማ የገዘፈ፡፡ እራሱ ሰይጣንን የመሰለ፡፡ እንደውም ቡና መቆላት ሲጀምር ሰይጣን በጠረኑ ተስቦ የሚመጣ ይመስለኛል፡፡ ልክ ሲወገጥ፣ ስራውን በማን ልቦና ላይ ሰፍሮ፣ በማን ልሳን አንበልብሎ፣ ማንን መውገጥ እንዳለበት የሚያስብ ይመስለኛል፡፡ እሳት ላይ ተጥዶ እስኪፈላ የስራውን እቅድ የሚነድፍ፤ ፈልቶ እስኪሰክን ሲዘቀዘቅ ደግሞ በየሰው ምላስ ለመወንጨፍ በተጠንቀቅ የተንበረከከ አትሌት ይመስለኛል፡፡
የመሰለኝ ሁሉ መስሎኝ አልቀረም፡፡ እናቴ ቡናዋን ቀድታ ለአጣጪዎቿ ካከፋፈለችና እነሱም ከተጎነጩ በኋላ፤ ሰይጣን ደሙን በደማቸው አስርጾ ማሳማት ይጀምራል፡፡
‹ውይ የእንትና ልጅ እኮ ሳታረግዝ አልቀረችም፡፡ ደግሞ ምናለ ከደህና ሰው ቢሆን…›
‹ኤዲያ! እሱ ሰው መስሎሻል፤ ሚስትና ልጁን ቤት ቁጭ አድርጎ ሲልከሰከስ አይደል እንዴ የሚያመሽ፡፡›
‹‹እኔኮ ግርም የሚለኝ…›
‹እሷን ሰው ብለሻት…›
‹ድንቄም አዋቂ!! በፎርጅድ ነው አሉኮ ባለ ድግሪ የሆነው…›
‹ማን እሷ!...›

ቡና አልወድም!...... ነበር፤ ማርታን እስካገኝ፡፡
ማርታን ባወቅኩ ቅፅበት እውነቴና እውቀቴ ተገለባበጠብኝ፡፡ ቡና የሰይጣን ሳይሆን የፈጣሪ መሆኑ ተገለጠልኝ፡፡ እንደውም ለአዳም፣ ጥረህ ግረህ ብላ ተብሎ የተነገረው ቃል፤ በደንብ ተግባራዊ ሚሆነው በቡና ላይ ነው፡፡ ቡና ተቆርጦ፣ ተፈልፍሎ፣ ተለቅሞ፣ ታጥቦ፣ ተቆልቶ፣ ተወግጦ፣ ተፈልቶ፣ ተቀድቶ . . . ይህን ሁሉ የስራ ሂደት አልፎ ነው ለመጠጥነት የሚበቃው፡፡
‹‹ምነው ሞቅ ሞቅ ሳላደርገው፣ በቅጡ እንኳ ሳልጀምር መጣህሳ?›› ትላለች ማርታ፤ የቡና ሲኒዎቿን እየደረደረች፣ ከሰሏን እያያዘች፣ ያን ድንቅ ፈገግታዋን በፊቷ እያፈገገች፡፡ ፊቷን ሳይ የከሰሉ መፍገግና የሲነዎች ንጻት ከጥርሷና ከፈገግታዋ እጅግ በጣም ያንስብኛል፡፡
የቡና ሱስ እያንከለከለ በጠዋት የሚያመጣኝ ይመስላታል፡፡ ከቡናዋ በላይ ከፊቷ የሚፈሰውን ፈገግታ ጠጥቼ ነበር ቀኔን ብሩህ የማደርገው፡፡ ቡናዋን፣ ገበያዋን ለመክፈትና እሷን ለማግኘት ስል ነበር መጠቀም የጀመርኩ፡፡ እየቆየሁ ስሄድ ግን የቡና ሱስ አናቴን ተቆጣጠረው፡፡ በማርታ ፈገግታ ብቻ ቀኔ አልፈካ ሲለኝ፤ ‹‹ማርቲዬ እስቲ የተለመደችውን ጣፋጭ ቡናሽን ቅጅልኝ!›› ማለት ጀመርኩ፤ ገና ወንበር ላይ ቂጤን ሳላሳርፍ፡፡

አንድ ቀን ጠዋት እንደተለመደው የማርታን ፈገግታ በቡና የማጣጣም ሱሴን ለማስታገስ ብቅ አልኩ፡፡ ማርታ ግን አልነበረችም፡፡ ቡናዋም የቡና እቃዎቿም አልነበሩም፡፡ ማርታን ጥበቃ ቆሜ ባለሁበት፣ ፀሀይ በምስራቅ በኩል ብቅ ብላ ቀኑን ሙሉ እያረፈች ተጉዛ በምዕራብ በኩል ሰመጠች፡፡ እኔ አይኔን በተለያየ አቅጣጫ እየወረወርኩ፣ አፌን ሱሱ ባዛጋኝ ቁጥር ከፍቼ እየደረገምኩ ጠበቅኳት፡፡ ብቅ ግን አላለችም፡፡ በማግስቱም በጠዋት መጣሁ፤ የለችም፡፡ በማግስቱ ማግስትም መጣሁ፣ በማግስቱ ማግስት ማግስትም መጣሁ፣ ከዛ በኋላም ለተከታታይ ሶስት ቀን መጣሁ፤ ማርታ ግን የውኃ ሽታ ሁናለች፡፡ እኔን የቡናና የፈገግታ ሱሰኛ አድርጋኝ ጠፍታለች፡፡
ማርታንና ቡናዋን ፍለጋ ተንከራተትኩ፡፡ ማርታን ሳጣ ቡና ለመጠጣት አንዲት ቡና አፍይ ዘንድ ቀርቤ አዘዝኩ፡፡ ቡናው ከጉሮሮዬ አልወርድ አለኝ፡፡ ጣዕሙ ለጉሮሮዬ ሰቀጠጠኝ፡፡ ትቼው ወጣሁ፡፡ "ለካ እስከዛሬ ቡናን ለጉሮሮዬ ያጣፈጠው የማርታ ፈገግታ ነው" ስል አሰብኩ፡፡ እውነቴም፣ እውቀቴም አፈነገጠ፡፡
‹‹ቡና የሰይጣንም የፈጣሪም ሳይሆን የማርታ ነው፡፡ የማርታ!!›› እያልኩ፤ ለቡና ተጠቃሚዎች እየሰበኩ፤ ማርታንና ቡናዋን ፍለጋ ዛሬም እንከራተታለሁ፡፡

እውነቴን ነው!! የማርታን ቡና በፈገግታዋ አጣጥመው ሳይጠጡ፤ ቡና ጠጣሁ ብለው አያውሩ፡፡

ዳንኤል ከበደ (#ኤልዳን_ለእኔ)

@wegoch
@wegoch
@wegoch
ዛሬ ስንሻውን አገኘሁት !🙂
_________________________

መጀመርያ ላይ የመኪናውን ክላክስ ሰምቼ ስዞር የማላውቀው ሰው ሊጠራኝ አይችልም በሚል እምነት ብቻ ጉዞዬን ልቀጥል ነበር ! ሚኪ ብሎ ጠራኝ ! ጌታ ሆይ ይሄን መሳይ የኮራ የደራ መኪና እያሽከረከረ ያለው እኔ በልጅነቴ የማውቀው ፣ ያ ትምህርት እሱን ከሚገባው ሶስት ግመሎች ተቃቅፈው በመርፌ ቀዳዳ ቢሾልኩ ይቀላል የሚባልበት ስንሻው እንዳይሆን ብቻ !
ዞር አልሁኝ !
ራሱ ስንሻው ነው ። ፊቱ እንደ ዓለም ካርታ ሉል መስሎ ተድቦልቡሏል ፣ ከላይ ያደረገው ነጭ ሸሚዙን የሚያምር ቅርፅ ያለው ሰውነቱ ይበልጥ ውበት እና ፍካት ሰቶታል ። በግራ እጁ ላይ ያደረገው ሰዓት ለግሉ ብቻ የሚገለገልበት ሳይሆን ለዓለም ህዝቦች ሁሉ ጊዜ የሚያውጅበት ይመስላል ።
አይኔን ብጠራጠርም ቀረብሁት ። ፈገግ ሲል በፍንጭቱ ይበልጥ እርግጠኛነቴ ጨመረ ። ልጅ ሆኖ ተደባዳቢ ነበር ።
እሱ የመቀጣቀጥ ሙዱ ከመጣ ለምን መሬቱን በሀይል እየረገጥህ ትሄዳለህ በሚል ተልካሻ ምክንያት ሁሉ ሳይቀር ለፀብ ይጋበዛል ።
እሱን የማይፈራ የክፍላችን ተማሪ አልነበረም ። ከእሱ የባሰ ረባሽ ተማሪም ክፍላችን ውስጥ አልነበረም ፣ ከእሱ የሚብስ ፎርፌ የሚቀጣ ተማሪ ጮርናቄ ለመብላት በክፍል መስኮቶች የሚዘል አንዳችስ እንኳ አልነበረም ።
እንደውም ትዝ የሚለኝ ቲቸር ንጉስ የሚባሉ መምህራችን አንተ በዚህ ከቀጠልህ” እነ ሚኪ ተምረው ዶክተር አልያም ኢንጅነር ሲሆኑ አንተ ሻንጣ ተቀባይ ወዛደር ትሆናለህ“ ብለው አሟርተውበት ነበር ።
እሱ ግን ይኸው በማላውቀው ምክንያት ዛሬ ከኔ የተሻለ ወዝና ንብረት ይዞ ክላክስ አደረገልኝ !
ይኸው የቲቸር ንጉስ ሟርት አቅጣጫውን ስቶ እኔ ላይ አረፈ !እሱን ወዛደር ብለውት ወዛም ሆኖ አረፈው ! እኔ ተምሬ እሳቸው እንዳሉት ኢንጅነር ሆንኩ ኝ (ስም ብቻ ተረፈኝ ) ስንሻው ሳይማር (ተምሮም ሊሆን ይችላል ) እሳቸው እንዳላሉት ከበርቴ ሆነ ።
'ስንሻው ?"
"ሚኩ ቸካይ ? አንተ እንዴት ነህ ? ምነው ደግሞ ሾለክህ ?" አለኝ
ለምን ከሳህ ማለቱ ነው ! ለምን ሆድህና ጀርባህ ተጣበቀ ምነው የቂጥህ ዋንጫ ወለቀ ምነው ምን ላርግልህ የሚለውን ነጠላ ዜማ እኔ ነኝ ሂዩማን ሄር አድርጌ የለቀቅሁት አልህ ? ማለቱ ነው ።
ይበለኝ !የ አርባ ቀን እድሌ ነው ።
“ደግሞ ደክሞሀል ! ላብህ ” ወደ ብብቴ አመላከተኝ ። ብብቴ አካባቢ ክረምት ገብቷል ። መንገድ እና ድንጋጤ ተባብረው ባህራቸውን ብብቴ መሀል አንጣለውት ነበር ።
ስንሻው መኪናውን ከፍቶልኝ ገባሁ ። እሱ የተቀባው ሽቶ መዓዛ ከመቅደስ እጣን ይልቃል ብል ፈጣሪ ይቀየመኛል ብዬ እንጂ እውነቱስ እንደዛ ነበር ።
መኪና ውስጥ የሽታ ማኪያቶ ተፈጠረ ! ድሮ ማኪያቶ ሲባል ለመጠጥነት ለሚውለው የቡናና ወተት ድብልቅ ይመስለኝ ነበር ።
ለካ የግም እና የጥኡም መዓዛም ማኪያቶ አለ ።
”አይ ሚኩ ትንሽ ከመጥቆርህ እና ከመክሳትህ ውጪ የድሮ መልክህ ቅልብጭ እንዳለ ነው“ አለኝ ለጥቆ !
አንተ አክሱም ተገትረህ የምትቀር ድንጋይ ሊለኝ እንደሆነ ገብቶኛል ! ባጭሩ ይሄ ሰው አንተ ኢትዮጲያ ቢለኝ እኮ ቅኔው ይገባኝ ነበር ። ከዚህ በኋላ የታሪክህን ያህል ሶስት ሺህ ዘመን ያህል ቢጨመርልህም የምትለወጥ አይመስለኝም ሊለኝ እንደሆነ እኮ ማንም ያውቀዋል ።
በኢንጅነሪንግ ነው አይደል የተመረቅኸው ? ጠየቀኝ
ምኑን ተመረቅሁት ? ተረገምኩኝ በለው ልለው ነበር ። ባይሆን በእውቀቴ ልኩራራ ብዬ እንዴታ አልኩት ወሬዬን ላሳምር ።
የት ነው የምትሰራው ?
የምሰራበትን ድርጅት ነገርሁት ።
በለበጣ ፈገግ ብሎ ኡኡይ ተቀጣሪ ነሀ ? አይዞህ በርታ ብሎ መለሰልኝ ።
አንተስ እንዴት ነህ ? ምን እየሰራህ ነው ?
ስንሻው መኪናውን እያሽከረከረ “ እኔማ እድሜ ለቲቸር ንጉስ አንድ ጊዜ የማይረሳ የንግግር ማስጠንቀቂያ ሰቶኝ ነበር ። አንተ ረስተኸው ይሆናል (አይ ጅሉ እኔማ ይሄን ጉድ እያየሁ እንዴት ረሳዋለሁ ?)
....እኔም ታድያ ያቺን ነገር በልቤ ይዤ ከዛ ትምህርት ቤት ስለቅ ወጣሪ ተማሪ ሆንኩኝ ። የውጭ እድልም አጊንቼ እዛ ው ተምሬ ትልቅ ድርጅት ውስጥ ተቀጥሬ መስራት ጀመርኩኝ ። አሁን በጎን ሀገሬ ላይምኢንቨስት ማድረግ ጀምሬያለሁ ። ባይሆን በሙያህ እኔ ጋር ቀጥሬህ ታግዘኛለህ“ አለኝ ።
የልቤ ምት ፍጥነት እሱ ከሚነዳው መኪና እኩል ፈጥኖ ሲረባበሽ ይታወቀኛል !
እሺም እንቢም አላልኩትም ። በልቤ የቲቸር ንጉስን ትንቢት አስቤ እየተሸማቀቅሁ ነበር ።🙂

@wegoch
@wegoch
@paappii

#Michael Aschenaki
ባያፍራ የኢቡዎች ህልም
______________________
(አይሰምርም አይጨነግፍም?
በሚልየን የሚቆጠሩ ኢቡዎች ደም ፈሷል። ሽንፈትና ውርደትን ተከናንበዋል።
ዛሬም እንደተሸናፊ ጎሳዎች ዝቅ ተደርገው ይታያሉ። ሀገር አልባዎቹ ኢቡዎች በናይጄሪያ ዘላለማዊ ግዞት ተጠፍንገው ዛሬም ሳይወዱ በግዳቸው ይኖራሉ። ነገሩ እንዲህ ነው። ሀገረ ናይጄርያ የተመሰረተችው በእንግሊዝ ፍላጎት ነው። ሰሜናዊ ናይጄሪያ የሀውሳ ጎሳ፣ ደቡብ ምዕራብ ዩርቡን፣ ደቡብ ምስራቅ ደግሞ ዛሬ ከንፈር የምንመጥላቸው ኢግቡዎች በስፋት ይኖሩበታል። እነዚህ በምንም የማይቀራረቡ ጎሳዎችን ለማእድንና ነዳጅ ፍላጎቷና ለቅኝ አገዛዟ እንዲመቻት
እንግሊዝ ናይጄሪያ የሚል ሀገር መሰረተች። ሲፈርድባቸው ኢግቡዎች አዕምሯቸው ብሩህ ነው። ሲጥልባቸው ስራ ፈጣሪነትን ተክነዋል። የተፈጥሮ ነገር የነፃነት ታጋይነት በደማቸው አለና እንግሊዝ ከሀገራቸው እንድትወጣ የነፃነት ትግልን መርተዋል። ቀናነት ተፈጥሯቸው ነው በመላው ናይጄሪያ ተበትነው ሀብት ንብረት አፍርተው መኖሩ ጀመሩ። ናይጄሪያ ፀሀይ ወጣላት። ነፃነቷን ተቀዳጀች። ቅኝ ገዢዋ እንግሊዝ ናይጄሪያን ለቅቄ ወጣሁ አለች። ነገር ግን ወጥታ አልወጣችም። አዲስ በሚመሰረተው ነፃ ሀገር ላይ አሻራዋን ለማኖር እንቅስቃሴ ጀመረች። በአዲሱ ሀገረ ምስረታ ላይ ኢግቡዎች እንዳይሳተፉ ተደረጉ። የመጀመርያው የናይጄሪያ ጠቅላይሚኒስተርም
ከሰሜን ናይጄሪያ የመጣ የሀውሳ ጎሳ አባል ሆነ። ሌሎች ትልልቅ ስልጣኖችም
በሀውሳዎች ተያዘ። በዚህ ቅሬታ ያላቸው ኢግቡዎች ሁሉን ነገር ዳር ሆነው
ይታዘቡ ነበር። ዓመታት ተቆጠሩ። አዲሷ ናይጄሪያ ገና ዳዴ ከማለቷ ባለስልጣኖቿ በሙስና፣ አድሎ፣ ዝርፊያና ህገወጥ ስራዎች ላይ ተዘፈቁ። መጀመርያውንም በመንግስት ምስረታ ላይ ቅሬታ ያላቸው ኢቦዎች መፈንቅለ መንግስት አደረጉ። ወታደራዊውን መፈንቅለ መንግስት ቹኩማ ኒዙጉ እየመራ በሰሜናዊይኑ ቁጥጥር ስር የነበረውን ስልጣን ተረከበ። በሙስና የተዘፈቁ ባለስልጣኖችም የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው ተገደሉ። እዚህ ጋ ቹኩማ የሰራው ስህተት አለ። ከባለስልጣኖቹ መሀከል የኢቡ
ጎሳዎችን አልነካቸውም ነበር። ይሄም መሪዎቹ የተገደሉበት የሀውሳ ጎሳ
በአከባቢው ያሉትን ኢቡዎችን ከመኖሪያ በማፈናቀልና ቀመግደል ቁጣውን
ገለፀ። ነገሮች ተባባሱ። ርእሰ ብሔሩ የኢቡ ጎሳ አባል ቢሆንም አንድ ኢቡ የሆነ ወጣት በሰላም ተኝቶ ማደር የሚናፍቀው ህልሙ ሆነ። ስጋት ከበባቸው። ሞት የእለት ተእለት ዜናቸው ሆነ። ይባስ ብሎ መሪው ቹኩማ መፈንቅለ መንግስት ተደረገበት። በሰፈረው ቁና ተሰፈረ። የኢቡዎች ሰቆቃ ተባባሰ። በመላው ሀገሪቱ ተበትነው ያሉት ኢቡዎች ወደመነሻቸው ደቡብ ምስራቅ አከባቢ ተሰበሰቡ። ቤታችን ገባን ብለው እፎይ አሉ። እንደውም እኛ ናይጄሪያ አደለንም የራሳችን ግዛት መመስረት አለብን በሚል መርህ የዛሬ ህልማቸውን ቢያፍራን መሰረቱ። የተቀረው የናይጅሪያ ክፍል የተበተነው ኢቡ ሁሉ የቢያፍራ ግዛትውስጥ ተሰበሰበ። ተይ ባይ የሌላት እንግሊዝ የቢያፍራን ነገር አልወደደችውም። ሰሜናዊያኑን ሀውሳዎች በማስተባበር ወደቢያፍራ ዘመቱ። እልቂት በኢቡዎች ላይ ሆነ። ሚልየኖች ረገፉ። ሆስፒታል፣ ትምህርት ቤትና የንግድ ማእከሎች በአውሮፕላን በሚጣሉ ቦንቦች ጋዩ። ህፃናትና እናቶች በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ። የአልም ትኩረት ተነፈጋቸው። ኢቡዎች ተሸነፉ። ነፃ ምድር ቢያፍራ ቅዠት ሆና አከተመች። ጦርነቱ አበቃ። አንድ ናይጄሪያ በድጋሚ ቀጠለች። በኢቦች ደም ናይጄሪያ ቀጠለች። የተረፉት ኢቡዎች ግን አሁንም ጥያቄ አላቸው። "እቺ ሀገር የኛ አይደለችም። ጦርነቱን ተሸንፈናል። የዘር ጭፍጨፋ ነው የተረደገብን። ሀገሪቱ የኛ አይደለችም። ዛሬ እኔ እድሜዬ ገፍቷል፣ ባያፍራ እውን ሆና ላልመለከታት እችላለሁ። የልጅ ልጆቼ ግን ህልሜን እውን ያደርጉታል። ነፃ ምድር ባያፍራ ትመሰረታለች። እኛ ናይጄሪያዊያን አይደለንም!" ይላሉ የኢቡ ጎሳ ተወካይ። ዛሬም ይሄ እንቅስቃሴ አለ። ቢያፍራን የመመስረት ትግል ህልም ወይስ ቅዠት?

@wegoch
@wegoch
@paappii

#muaz jemal
#Hike with your #talent.

Sunset Hiking Team is proudly hosting another epic hiking #Dinbaro (Menlik's Window)

(#Free #Outdoor_Photography, #Lunch, #Water, #Snack and much more).

Join us:
@sunsethiking or @sunsetphotography

Register
@chere_daregot(0919296071) by writing your name and talent!
#ገበታ ወ ባሻ !
(ሚካኤል አስጨናቂ)
አከራዬ ባሻ ሰሞኑን እጅግ የበዛ ወከባ ላይ ናቸው ። የግቢውን ብልፅግና ማረጋገጥ አለብኝ ብለው ደፋ ቀናውን ተያይዘውታል ።
እነሆ.. .የዛሬ ሳምንት ታድያ ወደ ቢሮ ለመሄድ ስጣደፍ ከየት መጡ ሳይባል ፊትለፊቴ ተገጨሩ :)
"ሚኪያሴ" አሉኝ! (እውነቱን ለመናገር ቤት አከራዮች ሲያቆላምጡኝ የቆነጠጡኝ ያህል ያመኛል )... ዝናዬ አከራይህ ዛሬ እከል ዬ ብሎ ከጠራህ ነገ የሆነ ጨላ ልትበጥስ ወይም ቤትኪራይ ሊጨመርብህ መሆኑን ልብ በል !
"አቤት ባሻ "
"ገበታ ለግቢያችን የሚል መርሀግብር በዚህ ሰሞን ተዘጋጅቷልና.. . (ንግግራቸውን ሳይጨርሱ የምድረ አዳም ሀጥያት የተከተበበት የመልዓክ መዝገብ የመሰለ የወረቀት መዓት ከጃኬታቸው ኪስ ውስጥ አውጥተው አቀበሉኝ) ...
ከዛ ሁሉ ዝብዝብ የፅሁፍ ብዛት መዋጮ የሚለውን የብሩን መጠን ሾፌ ቆሽቴ ጨሰ።.በየወሩ የምከፍለው የቤት ኪራይ ሳያንስ ገበታ ለግቢ የሚል የ 250 ብር መዋጮ ቀኔን ሰርቆኝ ዋለ ።
እነሆ ከባሻ ጋር በተገናኘን ማግስት ደግሞ ባለቤታቸው እመት ውድነሽ (ኑሮ ውድ ሆኖ ቦክስ እንጋጠም ብሎዋቸዋል መሰል ) ... እንዳኮረፈ ዝንጀሮ ለምቦጫቸውን ጥለውት አየሁ ። (እናቴ እኔን ! ማዘር ጁሱ ተመጦ የተጣለ ላስቲክ ይመስል ተኮራምተው የለ እንዴ?) ...ደግሞ እውነቱን ለመናገር ማዘር እንኲን አኩርፈው ፈገግ ብለው እንኳ አምሮባቸው አያውቅም። ፊታቸው የኬጂ ተማሪ የሚለማመድበት የስዕል ደብተር ይመስል እዚህም እዛም ተዥጎርጉሮ የኬንያ ባንዲራን ይመስላል።
"ማዘር ሰላም ነው?"
ምን ሰላም አለ ልጄ?
ምነው ... ምን ገጠሞት?
"ይሄ የሽማግሌ ህጣን ሰላሜን ነሳኝ :) ሰው እንዴት ቤቱ ውስጥ ያለውን የእህል ዘር አይጥ እየበላበት የግቢ ብረት በር ገዝቶ ያስመርቃል ? ተገቢ ነው መኮንን? ...ማነው ሚካኤል :)
..."እ ህ ህ.. ." የምመልሰው ጠፍቶኝ ተንተባተብሁ ።
" ልክ አይደለም !" ራሳቸው መልሰው ቀጠሉ ...ሶስቱ ልጆቻችን ርስበርሳቸው ጠብ ላይ ሆነው... "
"እዚህ ቤት የተጣላ ሰው አለ እንዴ?"
"እንዴታ ሚካኤል !...ያ ጥቁር ልጄ ሹሼ ከበደን እንዳይሆን አድርጎ ቀጥቅጦት የለ እንዴ? ይሄን ጠብ መፍታት ነው ወይስ ግቢው ውስጥ ችግኝ መትከል ነው የሚቀድመው ?...ቤቴ ውስጥ አይጥ እንደ አብርሀም ዘሮች በዝቶ ተባዝቶ የውጭ በር ሰራ አልሰራ ምን ይጠቅመኛል? እኔ የማወራው ስለ BBC እሱ የሚያወራው ስለ EBC! ...አልተገናኝቶም ልጄ! " የእመት ውድነሽ እንባ ኮለል ብሎ ሲወርድ አንጀቴ ተላወሰ ። በዚህን ጊዜ ባሻ ከየት መጡ ሳይባል ጀርባዬን መታ መታ አድርገው ...
"አየህ ልጄ ባለቤቴ ግቢው ሲያምርበት እኮ ደስ ብሏት ነው የምታነባው " :)
ቀና ብዬ ውድነሽን አየኋቸው።
የሽሙጥ ፈገግታ ፈገግ ብለው ራሳቸውን ከታች ወደ ላይ ሰበቁ ።
"ገና ምን አይተሽ ቤታችን እንደ አማዞን ጫካ ነብርና አንበሳ እንዲሁም ዝሆንና ጎሽ ይመላለሱበታል። "
ባሻ ይሄን የሚሉት በኩራት አካፋና ዶማቸውን ይዘው ሌላ ችግኝ ለመትከል ከስራችን እየተንቀሳቀሱ ነበር :)

@wegoch
@wegoch
@paappii
ቅቤ አምራች ገበሬና ዳቦ አምራች ነጋዴ እንደ አጋጣሚ ድግስ ላይ ተገናኝተው ያወራሉ፡፡ በጨዋታቸው በጣም ስለተግባቡ ከዚህ በኋላ አጋጣሚ ፈጥረው ለመገናኘት ይስማማሉ፡፡ ነጋዴው ጠዋት ጠዋት 300 ግራም ዳቦ ሲልክለት ገበሬው ደግሞ ማታ ማታ 300 ግራም ቅቤ ሊልክለት ተስማሙ፡፡ በዚህ መልኩ ብዙ ጊዜ ከቆዩ በኋላ ነጋዴ የቅቤ መጠን እየቀነሰ መሄዱን አየ። በመጨረሻም ሚዛን ላይ ሲያስቀምጠው 150 ግራም ሆኖ አገኘው፡፡ በዚህም በጣም አዘነ፤ ተበሳጨም፡፡ ገበሬውንም አስጠራው፡፡ ሌሎች ሰዎች እንዲያዳምጡት አድርጎ ‹ከተስማማነው ውጭ የቅቤውን መጠን ለምን ቀነስከው?› ሲል ጠየቀው፡፡ ገበሬውም ‹እኔ ፈጽሞ አልቀነስኩትም› ሲል በአግራሞት መለሰ፡፡ ነጋዴውም ቅቤውን በሚዛን ለክቶ አሳየው፡፡ 150 ግራም ነው፡፡ ገበሬውም አዘነ፡፡ ‹እኔ ቤት ውስጥ የ300 ግራም መለኪያ የለኝም፡፡ አንተ ጠዋት ዳቦውን ስትልክልኝ በእጅ ሚዛኑ አንደኛው ሰሐን ላይ አደርገዋለሁ፤ ከዚያም ቅቤውን በሌላኛው ሚዛን አስቀምጠዋለሁ፡፡ ልክ ከዳቦው ጋር እኩል ሲመዝኑ በዕቃ አዘጋጅቼ እልክልሃለሁ› አለው፡፡ ወዲያውም ጠዋት የላከለትን ዳቦ አውጥቶ ሚዛኑ ላይ አስቀመጠው፡፡ ዳቦው 150 ግራም ነበር የሚመዝነው፡፡ ነጋዴው አፈረ፡፡
‹የምታገኘው ለሌላው ባደረግከው ልክ ነው፡፡ 150 ሰጥተህ 300 ልታገኝ
አትችልም፤ እባብ ሰጥተህ ርግብ፣ ድንጋይ ሰጥተህ ዳቦ፣ እሬት ሰጥተህ ማር ልታገኝ አትችልም፤ አንተ ብቻ ብልጥ ልትሆን አትችልም፤ ማሾውን አጥፍተህ
ብርሃን ልታገኝ አትችልም፤ ሌላው ገድለህ አንተ በሰላም ልትኖር አትችልም›
አለው ገበሬው፡፡ ማንኛውም ድርጊት ተመሳሳይና ተመጣጣኝ የሆነ ምላሽ አለው፡፡ አንተ እዚህ ለብቻህ ቤትህ ውስጥ ሆነህ ክፉ ስታደርግ ሌላውም በቤቱ ብቻውን ሆኖ ክፉውን ይመልስሃል፡፡ ‹እዛም ቤት እሳት አለ› እንዳሉት ነው አለቃ ገብረ ሐና፡፡ አንተ ጎመድ ይዘህ ከወጣህ ሌላውም አያቅተውም፤ አንተ ገጀራህን ከሳልክ ሌላውም ይስላል፤ አንተ የሌላውን ወገን ስታፈናቅል፣ ያኛውም ያንተን ወገን
ያፈናቅላል፡፡ ዛፍ ቆርጠህ ዝናብ፣ በካይ ጋዝ እየለቀቅክ የተስተካከለ የአየር ንብረት አትጠብቅ፡፡ ተፈጥሮም በሰጠሃት መጠን ነው የምትመልስህ፡፡ በዓለም
ላይ ሚዛኑ አንድ ነው፤ ተመዛኞቹ ግን ይለያያሉ፡፡ እዚህ ካጎደልክ፣ እዚያም
ያጎድሉብሃል፡፡ እዚህኛው ዩኒቨርሲቲ የዚያኛው ልጅ አለ፤ እዚያኛው ዩኒቨርሲቲም የአንተ ልጅ ይገኛል፡፡ እዚህ የአንተ ወገን ብዙኃኑን ይዟል፣ እዚያ ግን አናሳ ነው፡፡ እዚህ አናሳ የሆነው ደግሞ እዚያ ብዙ ይሆናል፡፡ የብዙኃን ወገን በሆንክበት ቦታ አናሳው ካሰቃየህ፣ አናሳ በሆንክበት ቦታ ደግሞ ብዙኃን ያሰቃዩሃል፡፡ እዚህ ባለ ሥልጣን እንደሆንከው እዚያ ተራ ትሆናልህ፡፡ የሚያዋጣው በሚዛኑ ልክ ትክክለኛውን ማድረግ ብቻ ነው፡፡

@wegoch
@wegoch
@paappii

#eled aymen(elediye)
This is huletegna events and promotion. we are a team of people who love to sing. Also you can showoff your talents by performing on our upcoming acoustic night. 2thegna is the place to be.

Venue: velvet lounge, bole Tk building rooftop

Telegram: @huletgna
Instagram: @hulegna
Join and share.

Call 0900651327 if you want to perform or save a seat.
for more
@MsChanandlerBond
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1495ኛው የነብዩ መሐመድ የልደት በዓል አደረሳችሁ!

Mawlid Al Nabil Al Sharif
@seiloch
@getem
@wegoch
#ቆዳ እና #ሸራ ላይ የወደዱትን ፎቶ ለማሳል
በ +251984740577
ወይም @gebriel_19 ላይ ፎቶ በመላክ ማዘዝ ይችላሉ ።

🎨ለ ልደት
🎨ለፍቅረኛ
🎨ለ ሰርግ እና
🎨የቤተሰብ ፎቶግራፍ ማሳል ለምትፈልጉ ሁሉ

Join @seiloch
2024/09/24 11:15:37
Back to Top
HTML Embed Code: