Telegram Web Link
K ቅንድል ቅፅ 2 ቁጥር-2_edited8.pdf
6.8 MB
ቅንድል ዲጂታል መፅሔት
#ቅፅ-2 #ቁጥር-2


#ልዩ እትም
#ሚያሸልሙ_ጥያቄዎች_የተካተቱበት



💵ፓኬጅ ከገዙ 60 ሳንቲም ብቻ💵

ቅን ፣ ምክንያታዊ እና ሀገር ወዳድ ትውልድ ለኢትዮጵያችን !!!
@KendelM
@KendelM
💧💧ቂም የሸፈነው እውነት💧💧
ክፍል ሁለት

የደስታዬ ጫፍ ይሆናል ብዬ የማስበው ቀን ሲመጣ እርካታን ሳይሆን ባዶነትን ተሸክሞ ነው የመጣው፡፡ የምፈልገው ሁሉ ኖረኝ፡፡የማስበው ሁሉ ሰመረልኝ፡፡ ግን ትርጉም አልባ፣ ደስታ የለሽ ሙት ሆነብኝ፡፡

                                                 ******
እንደማንም ያልነበረው ልጅነቴ፡-
ሰዎች ስለልጅነታቸው ሲያወሩ ‘እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ…..’ ሲሉ እገረማለሁ:: ‘ማንኛውም ኢትዮጵያዊ’ እኔን ያቀፈ ማዕቀፍ ይሆንን?

በቀን አንዴ ትርፍራፊ ለመቅመስ መስገብገብ፣ ጎዳና ላይ በገነባቻት የላስቲክ ቤት አጠገብ ተቀምጣ የምትለምን ወፈፍ የሚያደርጋት እናት፣መለመኛ የሆኑ መንታ ታናናሽ እህትና ወንድም፣ አስር ሳንቲም ለመመፅወት የሚመፃደቅ ሂያጅ፣ በባዶ እግርና በእኮዮች ምፀት ታጅቤ የምዳክርበት ትምህርት ቤት…….. ከማንኛውም ኢትዮጵያዊ የተለየ ልጅነት ነው፡፡

ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እናቱ ልመናን ተናዛለት አባት አልባ ህፃናት መንገድ ዳር አስታቅፋው አልሞተችም፡፡

ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እናቱ የሚበር መኪና ውስጥ ገብታ ስትሞት የሚሰማውን ከእብደት ያልተለየ ስሜት አያውቀውም፡፡

የኔ ልጅነት ‘እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ’ የሚባለው ማዕቀፍ ውስጥ የማይገባው ልጅነት የሚባለው ዘመኔ በአስር ዓመቴ አክትሞ የሁለት አመት ጨቅላ መንታ ታናናሾቼን እየለመንኩ ማሳደግ ግዴታዬ ስለነበር ነው። ዓለም ስትከረፋብኝ፣ በርሃብ ከሚጮሁ ታናናሾቼ ጋር ኡኡኡ ብዬ ሳለቅስ “እንደእናቷ ጠሸሸች” እተባልኩ አራት ዓመታትን ጎዳና መግፋቴ ነበር፡፡

አንድ ምሽት ታናናሾቼን አስተኝቼ ነትቦ እርቃኔን ያጋለጠውን ልብሴን እየሳብኩ ከላስቲክ ጎጆአችን ፊት ለፊት ቆሚያለሁ፡፡ መኪና ሲጢጥ ብሎ ሲቆም ሰማሁ፡፡ የሰከረ ወንድ ድምፅ ተከትሎ ተሰማኝ፡፡

“እሙዬ ነይ እስኪ……”

“እሙዬ ነይ እስኪ……”

“ምን ፈለግክ?”

“አንቺን”

“ሸርሙጣ አይደለሁም፡፡”

“ታዲያ እዚህ ምን ይገትርሻል?”

“ቤቴ ነዋ…..” ብዬ የላስቲክ ቤቴን በእጄ ጠቆምኩት።

“ስንት ዓመትሽ ነው?”

“አስራ አራት” ከመኪናው ወርዶ እየተንገዳገደ ተጠጋኝ፡፡

“300 ብር እሰጥሻለሁ፡፡”

“ሸርሙጣ አይደለሁም አልኩህ እኮ……”

“ሸርሙጣ ነሽ ማን አለሽ? ጎዳና እያደርሽ ምንም አልቀመስኩም ለማለት ነው?” እዚያ ጎዳና ላይ ስኖር ከዛ በላይ ፀያፍ ቃላቶች ሰምቼ አውቃለሁ፡፡ የዛን እለት ግን ሰውየው የተናገረው ንግግር ሰቀጠጠኝ፡፡ አጠገቤ ያገኘሁትን ድንጋይ አንስቼ ከፍ አደረግኩ

“በዚህ አናትህን ሳልከፍልህ ሂድ ከዚህ ጥፋ”

“ምንም የማታውቂ ከሆነ 1000 ብር እሰጥሻለሁ”

ደጋግሜ የብሩን መጠን ለራሴ አነበነብኩት፡፡ በህልሜ እንኳን አስቤው የማላውቅ ዓይነት ነበር፡፡ ምን ያህል ፍርሃት ቢያርደኝም ከብሩ መጠን ጋር ሲወዳደር ቀለለኝ፡፡ በዛው ቅፅበት ምን እንደማደርግ እቅድ አወጣሁ፡፡ ጭንቅላቴ እጄን አላዘዘውም፡፡ የመኪናውን በር ከፍቼ ገባሁ፡፡ ሲኦልን የዛን ምሽት አየኋት፡፡ በአለም ላይ ካሉ አስቀያሚ እና ጨካኝ ፍጥረታት መሃከል ዋነኞቹ ወንዶች መሆናቸውም የዛን እለት ገባኝ፡፡ ገና የ14 ዓመት ልጅ ነበርኩ፣ በችግር ሰውነቴ ደቆ የእድሜዬን ያህል ያላደግኩ፣ ምንም የማላውቅ………… ሰው እንዴት በህፃን ህመም ይደሰታል? እየተሰቃየሁ በፈሰሰኝ ደም እንዴት ድል እንዳደረገ ይፈነጫል? እሱ ወዙን ሲያዘንብ እኔ እንባዬ ሲዘንብ እንዴት ሰብዓዊነት አይሰማውም? እንዴት በ1000 ብሩ ስቃዬን ይገዛል? እንዴትስ ያ ደስተኛ ያደርገዋል? ይኼ ፍጡር ወንድ ነው።……  በስቃይና በተስፋ ተሰቅዤ ሊነጋ አካባቢ ወደ ላስቲክ ቤቴ ተመለስኩ፡፡ እነ አቢን ቀሰቀስኳቸው፡፡ …………… ርሃብ የለም፡፡ ልመናም የለም፡፡ ገበያ ይዣቸው ወጣሁ፡፡ ለብሰውት የማያውቁትን ልብስ ገዛሁላቸው፡፡ ካፌ ወስጄ ኬክ አበላኋቸው፡፡ ጠግበን ዋልን፡፡

በዚያው ሰሞን በተረፈኝ ገንዘብ መንገድ ላይ ሲቆሙ የማያቸው ሴቶች የሚለብሷቸውን የመሳሰሉ አልባሳት ገዛሁ፡፡ ያደርጉታል ብዬ ያሰብኩትን አደረግኩ፡፡ ይመስላሉ ብዬ ያሰብኩትን መሰልኩ። ዘወትር ማታ ሲዖል ደርሶ መልስ የኑሮዬ አንድ ክፍል ሆነ። ገንዘብ እየተቀበልኩ ስቃዬን መጨጥ (ለወንዶቹ እርካታቸውን) የየቀን ስራዬ ሆነ። አሁን ገንዘብ ማግኘት ቻልኩ፡፡ እንዳቅማችን ቤት ተከራየን፡፡ እህትና ወንድሜ ትምህርት ቤት ገቡ፡፡

ወንዶችን አልወድም ገንዘባቸውን እንጂ። ከወንድነታቸው የሚተርፈኝ ስቃይና ላባቸው ነው፡፡ ገንዘባቸው ግን የማልፈውን ሲኦል ያስረሳኛል፡፡ መንገድ መቆሙን ትቼ ትልልቅ ሆቴል ውስጥ መስራት ጀመርኩ፡፡ እንደዋዛ ትልቅ ሴት ሆንኩ፡፡ ሃያ አንድ ዓመት ሞላኝ፡፡ በዚህ ወቅት ነው ካሳሁንን ያገኘሁት፡፡ የሆቴሉ ደንበኛ ነው፡፡

“ቆንጆ እኮ ነሽ እዚህ ቦታ መገኘት አልነበረብሽም::” አለኝ።

“አየህ ተፈጥሮ ቁንጅናን እንጂ የተደላደለ ህይወትን አብራ አልሰጠችኝም::” መለስኩለት።

“የዛሬ ገቢሽን ልስጥሽና እቤትሽ አርፈሽ ተኚ?”

… አሁንም አልጨረስንም…

@wegoch
@wegoch
@paappii

#meri feleke
💧💧ቂም የሸፈነው እውነት💧💧
የመጨረሻ ክፍል

“የዛሬ ገቢሽን ልስጥሽና እቤትሽ አርፈሽ ተኚ?”

“ይበዛብሃል::”

“እጥፍ ላድርግልሽ!!”

በራሱ መኪና እቤቴ አደረሰኝ፡፡የጠየቅኩትን ገንዘብ ሳያቅማማ ሰጠኝ፡፡ በተደጋጋሚ እንዲህ አደረገ፡፡ ለዘመናት የሆቴሉ ደንበኛ ሲሆን ከሆቴሉ ሴቶች ጋር ስሙ ተነስቶ እንደማያውቅ ሰማሁ። ከአመታት በፊት ብቸኛ ወንድሙ ከእርሱ ጋር ተጣልቶ በባህር አቋርጦ ወደውጪ ሀገር ሊሄድ ሲሞክር የመሞቱን መርዶ ከሰማ ጀምሮ በየምሽቱ ይመጣል፣ እራቱን ይበላል፣ ይጠጣል፣ ለሴቶቹ ይጋብዛቸዋል፣… … ወደቤቱ ይሄዳል። ከቀናት በኋላ አብሬው እንዳድር በትህትና ጠየቀኝ፡፡ እቤቱ ነበር ይዞኝ የሄደው፡፡ ከሱ ጋር ካደርኩ በኋላ ወደ ሆቴል ተመልሼ መሄድ አላስፈለገኝም፡፡ በየእለቱ ማታ እቤቱ እጠብቀዋለሁ፡፡ ሲነጋ ወደቤቴ እመለሳለሁ፡፡

እንዳገባው የጠየቀኝ ቀን እብደት የቀላቀለው ስሜት ነበር የተሰማኝ፡፡ ምክንያቱ ባል ማግኘቴ አይደለም፡፡ ባል ወንድ ነው ወንድ ደግሞ የገንዘብ ምንጭ ነው። ከዛ ያለፈ አይደለም ለኔ፡፡ ካሳሁን ብዙዎች የሚያውቁት ሀብታም ነጋዴ ነው፡፡ …… በቃ!! ብር አገኛለሁ፡፡ የትኛውም ወንድ እንደሸቀጥ የሚገዛት ሴት መሆኔ ይቀራል፣ እነ አቢዬ ያለስጋት ትምህርታቸውን ይማራሉ፣ በለውጥ ገላዬን እሰጠዋለሁ፡፡ ልቤ ያውቀዋል እንደምፈታው፡፡ ተጋባን፡፡ እህትና ወንድሜን ይዤ እኔ ገንዘብን እሱ ትዳሩን ስንጠብቅ ኖርን፡፡
                                      
  *

ሳምንታት አለፉ፡፡ ሲመቸው ለቤቱ ፕሮሰስ እንደሚመጣ ቢነግረኝም  ካሳሁን አልመጣም ፡፡ አልደወለም፡፡  በቤቱ ምክንያት ቢመጣና ባየው ተመኘሁ፡፡ቤቱ አስክሬን የወጣበት ቤት መስሎ ረጭ አለ፡፡

የቤቱ ድምቀት፡- ትልቅነቱ፣ የቀለማቱ ስብጥር፣ በውስጡ ያጨቀው ውድ እቃ አልነበረም፡፡ ሞገሱን ተገፏል፡፡ ካሳሁን የለበትም፡፡

የምግቡ ጣዕም የሰራተኛዋ ጥበብ አልነበረም፡፡ ከካሳሁን ጋር የምግብ ጠረጴዛው ላይ መታደሙ እንጂ።

የእንቅልፉ መጣፈጥ የአልጋው ምቾት አልነበረም በካሳሁን እቅፍ ውስጥ ማደሩ እንጂ።

ይሄ ሁሉ የገባኝ አምስት ዓመታት ዘግይቶ ሆነ፡፡ የህይወት ዘመን ልምዴንና እውቀቴን ያስከነዳው እውነት ካሳሁን ‘ሴት ልጅ ለገንዘብህ ስትል ትወድሃለች’ ብለው እንደሚያስቡ ወንዶች አልነበረም፡፡ ገንዘቡን እንደወደድኩት እንጂ ለእሱ ግድ እንደሌለኝ ያውቃል፡፡ ራሱን እንድወደው ነበር አምስት ዓመት ሙሉ ሲጥር የነበረው፡፡ የፈለግኩትን ሁሉ እንኳን አጊንቼ እሱ ከሌለበት ባዶ መሆኑን ነበር ያሳየኝ፡፡ እድሜውን ካፈራው ንብረት እንደበለጥኩበት አሳይቶኝ እድሜዬን ሙሉ የጓጓሁለት ሀብታምነት ከንቱ መሆኑን ነገረኝ፡፡ አብሬው ስኖር ያላየሁት እውነት ያ ነበር፡፡

“ ማንም የኔን ያህል አውቆሽ አያውቅም፡፡” ይለኝ ነበር ሁሌም ሳበሳጨው፡፡ አሁን ነው ምን ያህል እንደሚያውቀኝ የገባኝ፡፡ ባዶነቴ በፍቅር እንጂ በገንዘብ እንደማይሞላ ያውቅ ነበር፡፡ እሱ ብቻ ይሄን ያውቅ ነበር።

ስልኬን አንስቼ ደወልኩለት፡፡

“ሰብሊ ይቅርታ ደንበኞች እያናገርኩ ነው፡፡ ቆይቼ እደውላለሁ፡፡” ብሎኝ ስልኩን ዘጋው፡፡ ‘ቆይቼ’ ያለው ሰዓት ዘላለም መሰለኝ፡፡ ሲሊፐር እንዳጠለቅኩ ተነስቼ ከቤት ወጣሁ፡፡ እንዲህ ላብድ የሚመስለኝ ሰዓት እብደቴን የማስታግሰው እህትና ወንድሜ ጋር ስሆን ነበር፡፡ አሁን እነሱ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች ናቸው፡፡ እንድረብሻቸው አልፈልገኩም፡፡ ደግሞም ካሳሁንን የአባታቸው ያህል ነው የሚወዱት። በቀስታ እየተራመድኩ ማሰብ ጀመርኩ፡፡ አሁን ያለኝን ሁሉ አጥቼ ካሳሁንን ብቻ ማግኘት ተመኘሁ፡፡ እግሬን ጭንቅላቴ አላዘዘውም፡፡ ወደካሳሁን ቢሮ ሮጥኩ። ርቀቱ፣ አለባበሴ፣ የፀጉሬ መንጨፍረር…….. ምኑም ግድ አልሰጠኝም፡፡ ትንፍሼ ቁርጥ ቁርጥ እያለ በሩን ከፍቼ ገባሁ፡፡ ሁኔታዬ ያስደነገጣት ፀሃፊው መውጣቱን ነገረችኝ፡፡ በደከመ ነፍሴ ወደቤቴ ማዝገም ጀመርኩ፡፡ የመጣሁት መንገድ ርቀቱ የታወቀኝ ስመለስ ነው። ብዙ መንገድ ሮጫለሁ፡፡ መንገዱ ዳር ድንጋይ ላይ ተቀመጥኩ፡፡ ለብዙ ቀናት የረባ ምግብ ያለመብላቴን፣ እረፍት ያለው እንቅልፍ ያለመተኛቴን አሁን ነው ያስታወስኩት፡፡ ላዳ ይዤ ወደቤቴ ሄድኩኝ፡፡ በሩ ላይ የካሳሁንን መኪና ቆሞ ሳየው ‘እሪሪሪሪረ……’ ማለት አማረኝ፡፡ በሩጋ ስደርስ እሱ እየወጣ ነበር፡፡ ከላይ እስከታች እያስተዋለኝ

“ስደውልልሽ አታነሺም?”



“ስልኬን ጥዬው ነው የወጣሁት፡፡ ቢሮህ እኮ ሄጄ…..”

“አሁን መጥታ ነበር ሲሉኝ ነው ወደቤት የመጣሁት። ሰላም አይደለሽም?” ይዞኝ የመጣው ታክሲ ጥሩንባውን አስጮኸው፡፡

“አልከፈልሽውም እንዴ?” ብሎ እጁን ኪሱ ውስጥ እየከተተ ወደታክሲው አመራ፡፡ በዛው የማይመለስ መሰለኝ፡፡ ድጋሚ ለሳምንታት የማላየው መሰለኝ፡፡ ምን እንዳደረግኩ የገባኝ ካደረግኩት በኋላ ነው፡፡ አፌን ጭንቅላቴ አላዘዘውም፡፡

“እሪሪሪሪሪሪ…….” ብዬ አቀለጥኩት፡፡ በታክሲውና በኔ መሃከል ባለ እኩል እርቀት መሃል ደንግጦ ዞረ፡፡

“ምን ሆንሽ?” አጠገቤ ዘሎ ደረሰ፡፡ ምን እንደምለው ግን ግራ ገባኝ፡፡ የእንባዬ ጠብታ መሬቱ ላይ ተከታተለ፡፡ ባለታክሲው በጩኸቴ ተደናግጦ መውረዱን ሳይ ደነገጥኩ፡፡

“ምንም አልፈልግም፡፡ ሁሉም ይቅርብኝና አትሂድብኝ!!” እንባዬን እየታገልኩ ያወጣሁት ቃል ይሄ ነው፡፡

“አልሄድኩም እኮ ታክሲውን ልሸኘው ነው::”

“አልፈልግም እኮ ነው የምልህ፡፡ ቤቱንም ብሩንም ምኑንም አልፈልግም፡፡ ሁሉንም አልፈልግም። አልፈልግም በቃ!!” በእንባዬ ታጅቤ አምባረቅኩኝ፡፡

ያልኩት እንዳልገረመው ፤ እንዲህ እንደሚሆን እንደሚያውቅ ሁሉ ፈገግ እንደማለት ብሎ ወደታክሲው ሹፌር ፊቱን አዞረ፡፡ መሬት ላይ እየተንከባለልኩ መጮህ አማረኝ፡፡ ብሩን ሰጥቶት ሲመለስ በእንባ በተጋረደ ዓይኔ አየዋለሁ፡፡

“ላቆሰልኩህ ቁስል በሌላ በፈለግከው ነገር ቅጣኝ እባክህ ትተኸኝ አት….” ያልኩትን የሰማ አይመስልም፡፡ አጠገቤ ከመድረሱ ከንፈሮቼን ጎረሳቸው።

አምስት ዓመት ሙሉ እንዲህ ነበር የሳመኝ?

ጨርሰናል!!

@wegoch
@wegoch
@paappii

#meri feleke
ለቀናችኹ ይህን አድምጡማ
@Wegoch
@Wegoch
@Wegoch
ደግሞ ለምሽታችኹ ይኽን ያዙ
@Wegoch
@Wegoch
@Wegoch
ለሌላኛዉ ቀናችኹ ይኾን ዘንድ
@Wegoch
@Wegoch
@Wegoch
ለቅዳሚታ'ችኹ ከጀመርነዉ ላይ ይኽን ያዙ
@Wegoch
@Wegoch
@Wegoch
"በብዙ ምክንያት፣ ሰው ቢያሳምመኝም፤
ከሰው የተሻለም፣ መድኃኒት የለኝም።"
-----/መላኩ አላምረው/-----
"የመወለድ ብልጫው ምንድነው?"
--->-->->
ከዓመታት በፊት የሥነ ፍጥረት ኮርስ ሳስተምር "አምላክ ሰውን በመፍጠሩ ተፀፀተ" የሚለውን ጠቅሼ "ይህ የተጻፈልን እውን አምላክ የመፀፀት ባሕርይ ኖሮት ነውን? አይደለም። ይህ ጥቅስ የሰውን ልጅ ክፉነትና በተፈጠረበት ዓላማ አለመኖሩን፣ አፈንጋጭነቱን፣ ከጽድቅ ሸሽቶ ኃጢኣት ቆፋሪነቱን... በአጠቃላይ የሰው ልጅ የክፋት ጥግ አምላክ የሚፀፀት ባሕርይ ቢኖረው ኖሮ በትክክል ለፀፀት የሚያበቃ መሆኑን ለማጠየቅ ነው" እያልሁ እያስረዳሁ እያለ ከሰንበት ተማሪዎች አንዱ እጁን አወጣና እንዲህ አለ። "በእኔ እምነትና መረዳት በመፈጠሩ መፀፀት መቆጨት ያለበት ራሱ የሰው እንጅ አምላክ አይደለም ሰውን በመፍጠሩ መፀፀት የነበረበት። ምክንያቱም የሰው ልጅ ወደዚህች ምድር በመምጣቱ የሚያገኘው አኗኗሪ ያው በክፋት የተሞላውን የሰውን ልጅ ነው። ምድርን የስቃይ ዓለም አድርጎ በሴራና ተንኮል ተሞልቶ ለመኖር የተፈጠረው የሰው ልጅ ነው ለእንዲህ ያለ ኑሮ በመምጣቱ መፀፀት ያለበት። እኔ በበኩሌ በመወለዴ እፀፀታለሁ።"
እንዲህ ተናግሮ እንደተቀመጠ በፈገግታ እያየሁት መለስሁለት። "ወንድሜ አመክንዮህ አያስኬድም። ሲጀመር አንድ ሰው የመፀፀት ዕድል የሚኖረው ራሱ ባደረገው ድርጊት ነው። ራሱ ምንም ድርሻ ባላዋጣበትና በሌላ አካል በተከወነ ነገር በውጤቱ ምንስ መሆን ለምን ይፀፀታል? ባይሆን ሊያማርር ይችላል። ሰው በአምላክ ተፈጠረ እንጅ ራሱን ስላልፈጠረ ብቸኛ መብቱ 'ለምን ተፈጠርሁ?' እያለ የማማረር እንጅ 'መፈጠር አልነበረብኝም፣ ተሳስቻለሁ' ብሎ የመፀፀት ዕድል የለውም። መፀፀት የአድራጊ/ተግባሪ/ከዋኝ ድርሻ ነው። የአምላክ የመፍጠር ክዋኔ ውጤት የሆነው ሰው ሊፀፀት የሚችልበት አመክንዮ/Logic የለም። ልፈጠር ብሎ እንኳን ፍላጎቱን የመግለፅ ዕድል አልነበረውምና።" አልኩት።
ተማሪው መለሰ። "እንጃ ብቻ... እኔ በመፈጠሬ እፀፀታለሁ። የተወለድሁባትን ቀንም ረግማለሁ። የክፋትን ዓለም የኃጢአትን ምድር አይ ዘንድ ለምን ተወለድሁ? እ...."
አቋረጥሁት።
"እየውልህ ወዳጄ! አንተ በክፉዎች መሃል በጎ ሰው የመሆን ዕድል እያለህ፣ በኃጢአተኞች መካከል ጻድቅ ሆነህ መኖር እየተቻለህ ስለምን ክፋትና ኃጢአት ስለበዙ ብቻ መወለድህን ትርገማለህ? አምላክህን ስለፈጠረህ የምታማርረው እርሱ ክፋትን ፈጥሯልን? ኃጢአት ከክፉ ሰው አእምሮ ታስቦ ከርጉም ልብ ይወለዳል እንጅ በአምላክ ተገድደን የተሰጠን ነው እንዴ? አምላክ ለሰው ልጅ የማሰብና ምንም ነገር የመተግበር ፀጋን ሰጠ። በዚህ የአእምሮ የመፍጠር ፀጋ መልካም ነገርን ብቻ ማሰብና መተግበር እየቻለ ስለምን በክፉ ምግባር ይፀፀታል? ኃጢአትን ወዶና ፈቅዶ እንጅ ተገዶ የሚያደርግ አለ? ንፁህ ሆነህ የመኖር ምርጫና አቅም እያለህ በቆሻሻ መኖር ማማረር ምን ይሉታል? መፀፀት ካለብህ መልካም ነገር ማድረግ እየቻልህ ለበጎ ተግባር ዋጋ ሳይጠየቅብህ የክፋትን መንገድ በነፃ ፈቃድህ መርጠህ ለምድር መርገምን ከጨመርህ ነው።"
መልስ አልሰጠኝም።
--->->
ከዚህ ጊዜ በኋላ የተወለድሁበት ቀን (ግንቦት 27) በመጣ ቁጥር ከልጁ ጋር የነበረን ውይይት ትዝ ይለኛል። በተለይ ዘንድሮ በደንብ ነው ትዝ ያለኝ። ምን አልባት የሰውን ልጅ የክፋት ጥግ ከመቼውም ጊዜ በላይ ያለፉት ሁለት ዓመታት የመረዳት ዕድል ስለሰጡኝ በተግባርም ስላሳዩኝ ይሆናል። ሰው ወዶ አያማርርም። አንዳንዴ መኖር በራሱ ያስጠላና ፈጣሪን ያለ አግባብ የማማረር ከንቱነት ውስጥ ሁሉ ይከታል። ግን ትርጉምም ትርፍም መፍትሔም የሌለው ማማረር።
ብቻ ግን አንድን ጥያቄ በአግባቡ ጠይቀን መልስ ለራሳችን ማግኘት ይኖርብናል።
"የመወለድ ብልጫው ምንድነው? መወለድ ካለመወለድ በምን ይሻላል? ባንወለድ ምን ይቀርብን ነበር? በመወለድ ምን ተጠቀምን? ለመጣንባት ዓለም ምን በጎ ድርሻ አለን? እስካሁን ምን መልካም አስተውልፅኦ አበረከትን? ነገስ? ለምን እንኖራለን? ለምድር በክፋት ተፀንሶ በሴራ የሚወለድን መርገም ለመጨመር? ወይስ ለችግሯ መፍትሔ ለማውጣት? በምድር ላይ መልካም ነገርን ተግብሮ በጎ አሻራን አስቀምጦ ከማለፍ በስተቀር የመወለድ ብልጫው ምንድነው? እኛ ባንወለድ ይህች ምድር የሚቀርባት መልካም ነገር አለ? ወይስ የሚቀርላት መከራ? በእውኑ መወለዳችን ካለመወለዳችን ብልጫው ምንድነው? ክፋት ወይስ መልካምነት? ኃጢአት ወይስ ጽድቅ? በመወለዳችን አለመወለዳችንን በምንድነው የምንበልጠው? ችግር በመጨመር ወይስ መፍትሔ በማዋጣት?"
--->->
ለማንኛውም በእኔ በኩል እንኳንም ተወለድሁ ባይ ነኝ።
የሰውን ልጅ የክፋት ጥግም ቢሆን አይቼ እመሰክር ዘንድ መወለድ ነበረብኝ። ፈጣሪውን በመፍጠሩ ያሳዘነውን የሰውን ልጅ ብሽቅነት፣ ውለታ ቢስነት፣ አማራሪነት፣ ምስጋና ቢስነት አይቼ እረዳ ዘንድ እንኳንም ሰው ሆኜ ተፈጠርሁ። በመወለዴ ልፀፀት እንዴ? በፍፁም። ባይሆን ከክፋት መሃል ጥቂት በጎነትን፣ ከጥላቻ መሃል ጭላንጭል ፍቅርን እየፈለግሁ ልኑር እንጅ።
እርግጥ ነው ምድርን በክፉ ሰዎች ክፋት ልክ ብቻ ከተመለከክናት ደንበኛ ሲኦል ናት። ፈጣሪንም ለምን በሲኦል ፈጠረኝ ማለታችን አይቀርም። ነገር ግን መልካምነቷን እንመርምር። ምን በመንፈስ ተራቀን ረቂቅ ምሥጢራዊ በረከቷን ባንመረምር ቢያንስ በሥጋ እይታ ምድራችን ያላት በረከት ቢቆጠር መወለዳችን ልክ ነበር። ንፁህ ውሃን ከሆዷ አፍልቃ የምታጠጣን፣
ኦክስጅንን ከእፅዋቷ እያመነጨች ሕይወት የምትሰጥን ገነት ማየት አልነበረብንም?
በአበቦቿ አሸብርቃ፣ በማዕድኖቿ አብረቅርቃ የምታስውብን ይህችን ውብ ምድር ሲኦል ብቻ ናት ብለን የገነትነት ገጿን መሰረዝ ልክ ነው? በፍፁም። ሕይወታችንን የምሬትና የሀዘን ብቻ ሆኖ እንዲያልፍ ካልፈረድንበት በቀር በደስታ ውስጥ ሆነን ፈጣሪን የምናመሰግንበት ብዙ ጸጋና በረከትም ምድር ይዛለች።
ደግሞስ ከተፈጠሩ ወዲያ ለምን ተፈጠርሁ ብሎ ማማረር ምን የሚሉት ከንቱነት ነው? ባይሆን የተፈጠሩበትን ዓላማና ሊያበረክቱት የሚገባን በጎ ድርሻ ለይቶ ለእርሱ መድከም እንጅ። መቼም አምላክ ቅዱስ ነው ለርኩስ አላማ አይፈጥረንም። መልካም ነውና ለክፉ ድርሻ አላመጣንም። የመክፋት ነፃነታችንን ያከብርልናል ማለት ክፋታችንን ይፈልገዋል ማለትም አይደለም።
መልካምን እያሰቡ በጎ ነገርን የመተግበር ሙሉ መብት እያለን በተቃራኒው ጎን መድከምን ከመረጥን ምን ያድርግ? ነፃነት ባይኖረንም መከራ ነው። ሰው ነፃ ፈቃዱን ቢያጣ ከግዑዝ ዓለም ወይም ከደመ ነፍስ እንስሳት በምን ይለያል? ክፋትንም በጎነትንም የመሥራት ነፃነት ባይኖረኝ ማለት ግዐዝነትን/እንስሳትን መምረጥ ነው።
--->-->->
ወዳጄ የሰውን ልጅ የክፋት ገፁን ብቻ እያሰብህ የምትብሰከሰክ ከሆነ ጤነኛ አትሆንም። የሰው ክፋቱ ምኑ ይተረካል? የክፋት አሠራር፣ የሴራ አኗኗር ሕይወት ሆኖን የለ?! ራሳችን የምኖረውን ሕይወት ለማን እንተርከው?
አብዛኛው ሰው እኮ (በዚህ ባለንበት ዘመን በተለይም በፖለቲካው ዓለም) ሰብዓዊ ባሕርይውን በፈቃዱ ጥሎ ሌላ ነገር የሆነ እስኪመስል ድረስ ክፉ ሆኗል። ሁሉንም ነገር በክፋት ያያል። ሁሉንም ነገር ሴራ ያደርገዋል። "ሁሉም ነገር የሴራ ውጤት እንጅ ምንም ነገር አጋጣሚ አይደለም" በሚል የሴራ ንድፈ ሐሳብ ልቡ የተነደፈ ትውልድ አንተ መልአክም ብትሆን ሰይጣን ያደርግሃል።
በቃ ይኸው ነው።
👆ከላይኛው የቀጠለ
.

መስቀል ይዘህ ልትባርከው ብትሄድ "የዋህ ካህን መስሎ መስቀል እያሳዬ ሊገድለኝ የመጣ እባብ ነው። መስቀሉን የሚይዘው እኔን ወግቶ ለመግደል እንጅ ሊባርከኝ አይደለም" እያለ ካህኑን ሰይጣን ያደርግሃል። ወደኸው ብትቀርበው "በጣም ስለሚጠላኝ በፍቅር ቃላት እየሸነገለ ቀርቦ አስብቶ ሊያርደኝ ነው።" ይላል። አብዛኛው የአዳም ዘር (በዚህ ባለንበት ዘመን በተለይም በፖለቲካው ዓለም) ክፋት ብቻ ካልሆነ በቀር መልካምነትን ላያይ ዓይነ ልቦናው የታወረ፣ እዝነ ልቦናው የደነቆረ ነው። ሲጀመር ክፉ ሰው አንተን በራሱ ልክ ነው የሚያስብህ። እርሱ ልቡ ጥላቻን አእምሬው ሴራን የተሞላ ስለሆነ በቃ ያንተ ምንም ነገር ለእርሱ የተሰወረ ክፋት ነው። መስቀልህ ጦሩ፣ ፍቅርህ ፀሩ ነው። ያንገትህን ማተብ እንኳን "እኔን አንቆ ለመግደል ነው አስሮት ሚዞር" ሊልህ ይችላል። አደግ ያለ ጥፍር ካለህም የእርሱ መውጊያ ነው። ሻርብ ብትለብስ ማነቂያ ነው።
ከእናት አባትህ፣ ከወንድሞችህ፣ ከአብሮ አደግ ጓደኞችህ ሁሉ ጋር ሰብሰብ ብለህ ስትጫወት "እርሱን ለማጥፋት ከሆኑ ጠላቶቹ ጋር እየመከርህ ነው።"
እና ይህን ሁሉ ስታይ ሰው የሌለበት ዓለም ይናፍቅሃል። መወለድህም መርገም ሆኖ ሊታይህ ይችላል። ግን አስተውል።
ከዚህች ምድር በዚህ ሰዓት መድኃኒት ሆነው የሚፈውስህ ሰውም አለ። ሞትህን የሚሞትልህ፣ መከራህን የሚሸከምልህ ሰው በዙሪያህ አለ። ለዚህ ሰው ስትል ብቻ መኖር የለብህም? ምን በክፉዎች ተከበህ ብትኖር በዚህ ሁሉ መሃል በደግነት ጥግ ለሚኖሩ ለመልካም ሰዎች ስትል መኖር ላኖራቸውም ማመስገን የለብህም? ክፉን ብቻ እየቆጠርህ የበጎ ሰዎችን ድርሻ በዜሮ ማባዛትህ ከክፉዎች አያስመድብህም?
ይልቅ እንዲህ በል።
"በብዙ ምክንያት፣ ሰው ቢያሳምመኝም፤
ከሰው የተሻለም፣ መድኃኒት የለኝም።"

@wegoch
@wegoch
(በእውቀቱ ስዮም)
.
ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ አገሪቱን በልምላሜ ለማላበስ የሚያደርገው ጥረት እሚደነቅ ነው፤ ይህንን አረንጉዋዴ ዘመቻ ደግፌ መዳፌ ወንፊት እስኪሆን ሳጨበጭብ ቆይቻለሁ!!
የሰሞኑ አልገባኝም! ህልውናችን ክንብል ድፍት ሊል ጫፍ ላይ በሆነበት ጊዜ ላይ ለችግኝ ተከላ ዘመቻ ህዝብን መጥራት አስፈላጊ ነው?
አገራችን ማንም ያላገኘውን እድል አግኝታ በማባከን የሚደርስባት የለም ! ታሪኳ እንደዚያ ነው! ለኮሮና ያሳየነው ንቀት አንዱ ማሳያ ይመስለኛል፤ ባለፈ ነገር ላይ መወቃቀስ ስለማይጠቅም ነው እንጂ ብዙ እምለው ነበረኝ!
ለማንኛውም አሁን መንግስት፤
1)ለህክምና አርበኞች የሚያስፈልጋቸውን ስንቅ እና ትጥቅ እያቀረበ ነው?
2) የምግብ እጥረት በሚከሰትበት ጊዜ ለህዝቡ የሚነዛው ምግብ በጎተራው እያጠራቀመ ነው ?
3. ለኮሮና ቫይረስ መዳኒት ወይም ክትባት ቢገኝ ኢትዮጵያ የምታገኝበት መንገድ አስቦበታል? ‘፤ በቸርነቱ የሚደርስልን የአለም የጤና ድርጅት በትራምፕ ንፍገት ምክንያት ቺስታ ሆኗል! መንግስት ይሄንን ጉድለት የሚሞላበት ነገር አዘጋጅቷል?
መልሱ አዎ ከሆነ ይመቸው! ካልሆነ ግን ለዚህ ጣጣ መፍትሄ ሳያገኙ የችግኝ ዘመቻ ላይ ጉልበት መጨረስ አያዋጣም እላለሁ:: ወይራ ተከላው ከስምንት ወር በሁዋላ ይደረስበታል ! እስከዚያ ግን በህይወት መቆየት አለብን ‘ እህል የሚደርስ የፍልሰታ እኔ እምሞት ዛሬ ማታ “ ይላሉ ባልቴቶች ሲተርቱ!
በመጨረሻም፤ ድሮ በዘመነ ወረሼህ የነበረች አንዲት አሚና ከዙረት ወደ አገሯ ስትመለስ ያንጎራጎረችው እንዳይደርስብን እመኛለሁ!
“አስቲ ወደ አገሬ ልዝለቅ ወደ አፋፉ
ሰውስ አልቋልና እንደምነው ዛፉ “

@wegoch
@wegoch
Cyborea: The Mother of Judas
(Pp76)

የይሁዳ እናት Kahlil Gibran በፃፈው "Jesus The Son of Man " ውስጥ ስለ ልጇ ቀጣዩን ያናግራታል

"ልጄ ይሁዳ ትሁትና ፃድቅ ሰው ነበር። ለኔ ለእናቱ የነበረው አዘኔታና ርህራሄ መቼም ልረሳው አልችልም።

…ሮማውያን ያልዘሩትን የሚያጭዱ፣ በአይሁድ ሃብትም የከበሩ መሆናቸውን ዘወትር ሲናገር እሰማ ነበር።
ልጄ በአንድ አይሁዳዊ ወታደር ላይ ቀስቱን በመወርወር አቁስሎት እንደነበር ትዝ ይለኛል። ይሄም ወንጀል ሆኖ ሲታሰር ዕድሜው 17 ነበር።
በዚያ እድሜው የአይሁዳዊያንን ወጣቶች ልብ ሲያነቃቃና ሲያደፋፍር ይውላል። የእስራኤልንም ክብር በየአደባባዩ ይመሰክር ነበር።


የልጄን ሞት አውቃለሁ በዚያው ልክ ግን ማንንም እንዳልከዳ እና እንዳላታለለም ጭምር አውቃለሁ።
ልጄ የዘወትር ፍላጎቱ የእስራኤልን ከፍታ ማየት ነበር፣ በአፉም ይሄ አይለየውም ፣ በተግባሩም አሳይቷል።

አንድ ቀን በጎዳና ላይ ስንሄድ ይሄ አሁን ከዳው የሚባለውን ኢየሱስን አገኘነውና እኔን ጥሎ እሱን ተከትሎ ሄደ። ልቤ ግን ይህን ማድረግ እንደማይገባው ያውቅ ነበር።
ተመልሶ ሰላም ሁኚ በማለት ሲሰናበተኝ መሳሳቱን ነግሬው ነበር ግና አላደመጠኝም።


ከእንግዲህ ስለልጄ አትጠይቁኝ

ከይሁዳ እናት በላይ ክብር ወዳገኙት እናቶች ሂዱና እነሱን ጠይቁ።
ወደ ኢየሱስ እናት ሂዱ። በእኔ ልብ ያለፈው ልጅን የማጣት ሰይፍ በእርሷም አልፏልና የሚሰማኝን በሚገባ ልትገልፅላችሁ ይቻላታል፣ ያንጊዜ ትረዱኝ ይሆናል።"

ንባብ- Jesus The Son of Man by Kahlil Gibran
ትርጉም - በሱራፌል አየለ
@wegoch
@wegoch
Forwarded from Mikiyas Liyew Tadesse
ከጀመርነዉ 'ሚቀጥል
አድምጡማ
@Wegoch
@Wegoch
@Wegoch
የጀመርነዉ ኹሉ መባቻ ሲበጅለት
@Wegoch
@Wegoch
@Wegoch
#ወግ_ብቻ
.
ኔልሰን ማንዴላ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የህግ ትምህርት በሚማሩበት ጊዜ ነጭ
ፕሮፌሰር አስተማሪ ነበራቸው። ስሙም ፒተር

አንድ ቀን ፕሮፌሰር ፒተር በአንድ ምግብ ቤት ምግባቸውን እየበሉ ሳለ
ማንዴላ
በአጋጣሚ ምግብ ይዘው ከአጠገባቸው ይቀመጣሉ። ዘረኛው ፒተርም "አቶ
ማንዴላ! አሳማና 'ርግብ ለመብል አብረው አይቀመጡም!" ሲላቸው ብልሁ
ማንዴላም
"አይጨነቁ ፕሮፌሰር በርሬ እሄዳለሁ" ብሏቸው ሌላ ወንበር ላይ ይቀመጣሉ።

በዚህ የተናደደው ፒተር በሌላ ቀን ቂሙን ሊወጣበት ያስባል። አንድ ቀንም
ፕሮፌሰሩ ክላስ ውስጥ እያስተማሩ

" ማንዴላ በመንገድ ላይ እየሄድክ ሁለት ቦርሳዎችን ብታገኝና በአንደኛው
ቦርሳ
'ገንዘብ' በሌላኛው ቦርሳ ደግሞ 'ጥበብ' ቢኖር የትኛውን ትወስዳለህ?" ብሎ
ማንዴላን ሲጠይቀው

ማንዴላም"ገንዘቡን እወስደዋለሁ" …ብሎ መለሰለት። ፕሮፌሰሩም በድል
አድራጊነት
"አንተ ሞኝ ነህ እኔ አንተን ብሆን ኖሮ ጥበብ ያለበትን ቦርሳ እወስድ ነበር"
ሲለው ማንዴላ ፈገግ እያለ
"ልክ ነህ ማንም የሌለውን ነው የሚወስደው" አለው።
በዚህ ሁሉ ነገር የተበሳጨው ፕሮፌሰር ፒተር የማንዴላ የፈተና ወረቀት ላይ
'ደደብ' ብሎ ይፅፋል። ሌሎች ተማሪዎች የታረመላቸውን የፈተና ወረቀት
ሲያዩ
ማንዴላ ደደብ
የሚለውን ፅሁፍ ከወረቀቱ ላይ አየና ተገረመ ከዛም ወደ ፕሮፌሰሩ ሄዶ

"ይቅርታ ቲቸር ፊርማህን ብቻ ነው ያስቀመጥክልኝ ውጤቴን ረስተኸዋል"
ብሎት እርፍ ፡፡

ካነበብኩት
@Wegoch
@Wegoch

Creadit yeneta
Forwarded from ወግ ብቻ (ልዑል) via @Qualitymovbot
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ወግ_ብቻ
ሥጋ ነፍስን ሲያሸንፍ ኃጢአተኛ፤
ነፍስ ደግሞ ሥጋን ሲያሸንፍ ፃድቅ ትሆናለህ።
----------------------
የሚስቲሲዝም እምነት አራማጆች አንድን ነገር በጥልቀት ማሰብ፣ ማሰላሰል ከዚያም በነገሩ ውስጥ መዋሐድ ነው ይላሉ።
ጠቢቡ ሰለሞን ‹‹ሰው በልቡ እንዳሰበ እንደዚያው ነው... /As the man thinks, so is he...›› ይላል። የምታስበውን፣ የምታሰላስለውን ትሆነዋለህ፤ ለምን ቢሉ ከማሰብ ማመን ይመጣልና፤ በአመኑት ነገር መኖር ደግሞ የሰው ባህርይ ነው።

ሚስቲሲዝም ጅማሬው ሃይማኖት ነው። በጥልቅ የምታሰላስለው አንድ ነገር አለ። በዚያ ነገር ልብህን ታፀዳለህ፤ ዕውቀትን ትቀስማለህ፤ ራስህን ወደ ሌላ ዓለም ታሸጋግራለህ። በዚህም ግብህ አንድ ነው። የምታሰላስለው ነገር ላይ መድረስ። ያ ነገርም ፈጣሪ ነው ይላሉ።
. . . . .
--------
አንድ የቻይና መነኩሴ ከፍተኛውን የሚስቲሲዝም ደረጃ ይጨብጥ ዘንድ ወደ ታዋቂው የዜን መምህር ሄደ። በዚያም ጥሩ አቀባበል ተደርጎለት በነጋታው ወደ ልምምዱ ገባ። በጥልቀትና በፀጥታ ማሰላሰልን ተነግሮትም ይህንኑ ጀመረ።

በመጀመሪያዎቹ አስራ ሁለት ዓመታት ከአንደበቱ የወጣ ቃል ቢኖር፦ ‹‹የምተኛበት አልጋ አልተመቸኝም...›› በማለት ለመምህሩ መናገሩ ነበር።
መምህሩ አሁንም መነኩሴው በተመስጦ ማሰላሰሉን እንዲቀጥል ነገሩትና አስራ ሁለት ዓመት ጨመረ።

በእነዚህ ቀጣይ አስራ ሁለት ዓመታት ደግሞ አሁንም መነኩሴው ከአንደበቱ የወጣ ቃል ቢኖር አንድ ብቻ ሲሆን ይኸውም ‹‹ምግቡ አልተስማማኝም›› የሚል ነበር። መምህሩ ሌላ አስራ ሁለት ዓመት አዘዙለት።

በእነዚህ አስራ ሁለት ዓመታት ደግሞ ይበልጥ ፀጥታና ማሰላሰልን ቢያጠናክርም በመጨረሻው ዓመት ግን አንዲት ቃል ወጣው፦ ‹‹በቃኝ!›› የሚል ነበር።

መምህሩም ይኽን ሲሰሙ፦ ‹‹እውነትህን ነው። እዚህ ባሳለፍካቸው ሰላሳ ስድስት ዓመታት ውስጥ የኖርከው በማጉረምረም ነው። በዚህም ምክንያት የመጀመሪያውን ደረጃ እንኳን ማለፍ አልቻልክምና ቢበቃህ ጥሩ ነው...›› በማለት አሰናበቱት።
. . . . .
በሌላ ጊዜ አንድ ወጣት መነኩሴ ወደ ዜኑ መምህር መጣና በተመስጦ ለማሰላሰልና የእውነትን ጫፍ ለመጨበጥ ያደረበትን ፍላጎት ነገራቸው። ከመምህሩ ያገኘው መልስ ግን ጩኸት የተቀላቀለበት ሳቅ ነበር።

በዚህም ተደናግጦ ወደ ቤቱ በሐዘን አመራ። በነጋታው ተመልሶ ወደ መምህሩ በመሄድ፦
‹‹መምህር ሆይ፤ ትናንት መጥቼ ስለ ሚስቲሲዝም በምጠይቅዎ ሰዓት በሳቅዎ አባረሩኝ። ጥፋቴን ሊነግሩኝ ይችላሉ?›› አለ።

መምህሩም መሳቃቸውን ጀመሩ። ቢሆንም እንደ ትናንቱ አልገፉበትም። ሳቃቸውን አቋርጠው፦
‹‹አንተ ከጥጃ አትሻልም›› አሉት። መነኩሴው ከትናንቱ ይልቅ ዛሬ ደነገጠ።
‹‹እንዴት ከጥጃ አልሻልም?›› አላቸው።
‹‹የእኔን ሳቅ ጥጃ ብትሰማ እየቦረቀች ትዘል ነበር፤ አብራም ትስቅ ነበር ... አንተ ግን ከመደንገጥህ የማዘንህ...›› አሉት።

መነኩሴው ከጥጃ የማነሱን ጉዳይ በዚሁ ማሰላሰል ጀመረ። መምህሩም አስራ ሁለት የማሰላሰያ ዓመት አዘዙለት።
-----------------------------
📓 "ጥ በ ብ"
🖌 ከ ጲ ላ ጦ ስ
(ኃይለጊዮርጊስ ማሞ)
📖 📖 📖 📖 📖 📖
#ወግ_ብቻ
.
የጠቢቧ ሴት ድንጋይ
——
ጠቢቧ ሴት በተራሮች መካከል ስትጓዝ ወንዙ ላይ አንድ የከበረ ድንጋይ አገኘች። በቀጣዩ ቀን ደግሞ አንድ የተራበ ሌላ ተጓዥ አገኘች፡፡ ጠቢቧ ሴትም የያዘችውን ስንቅ ከፍታ እንዲመገብ አደረገችው፡፡

የተራበው መንገደኛም ምግቡ ይብቃኝ ብሎ ከመሄድ ይልቅ ያገኘችውን የከበረ ድንጋይ ተመለከተውና የከበረውን ድንጋይ እንድትሰጠው ጠየቃት፡፡ የከበረውን ድንጋይም ያለምንም ማቅማማት ሰጠችው፡፡

ተጓዡም ዕድል ፋንታውን እያሰበ እያመሰገነ ጉዞውን ቀጠለ። የከበረው ድንጋይ ሙሉ ሕይወቱን ያለምንም ሥራ በተድላ እና በደስታ ማሳለፍ እንዲችል እንደሚያደርገው ያውቅ ነበር፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ ግን ድንጋዩን ለመመለስ ወደ ጠቢቧ ሴት ተመልሶ መጣ፡፡

"እያሰብኩበት ነበር" አለ "ድንጋዩ ምን ያህል የከበረ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን ከዚህ የበለጠ የከበረ ነገር ትሰጭኛለሽ ብዬ ተስፋ ስላደረኩ ለመመለስ ወስኛለሁ፡፡ እጅግ የከበሩ ነገሮችን ለመስጠት የሚያስችልሽን የበለጠ የከበረ ነገር እንድትሰጭኝ እሻለሁ፡፡ ይህን ክቡር ድንጋይ እንድትሰጭኝ ያደረገሽን የከበረ ነገር ስጭኝ፡፡"
***
በምድር ላይ የጥበብ ሁሉ ጥበብ ራስን መግዛት ነው፡፡ ራሳችንን መግዛት የሚያስችለንን የከበረውን ጥበብ ከከበሩ ቁሶች በላይ አንሻ፡፡ ደስታ የሚገኘው በከበሩ ቁሶች ሳይሆን በከበረ ማንነት እንጂ።
የከበረ ማንነት ደግሞ ራስን መግዛት ነው፡፡
@wegoch
@wegoch
@wegoch
#ወግ_ብቻ
.
አንድ ወፍ ዛፍ ላይ አለች። አንተ ደግሞ ርቦሀል። ወፏን ገድለህ መመገብ ወይንም ሌላ አማራጭ መፈለግ አለብህ? ይህንን ምርጫህን ለመወሰን ሳይንስ አያገለግልህም። ወፏን ለመብላት ከፈለክ ወንጭፍ ወይም ባላ ለመስራት ከወሰንክ ግን... ሳይንስ ወደፍላጎትህ ለመድረስ ጣልቃ ይገባል።

ወፏን ከዛፍ ላይ በወንጭፍ አማካይነት ከመታሃት በኋላ አሳዘነችህ እንበል። ልታድናት ፈለክ። ማዳን መወሰንህ ምርጫ ነው። ምርጫህ የሚወሰነው እንደ እምነትህ ነው። እምነትህ ከሀይማኖት ጋር የተሳሰረም የተፋታም ሊሆን ይችላል። እንደመሰለህ የምትወስነው ነው። ወፏን ለማዳን ከፈለግህ የእንስሳት ሀኪም ዘንድ ጠአቅፈህ ትወስዳታለህ። የእንስሳት ሀኪሙ ሳይንስን ነው በአንተ ውሳኔ ላይ ጣልቃ የሚያስገባው። ሳይንስ ለመግደል ስትወስን የጦር መሳሪያን በመስራት፣ ለማዳን ስትፈልግ ሀኪምን ተመስሎ ይመጣል። ወደ ምርጫህ ማቋረጫውን እንጂ የቅድመ ምርጫ ሚዛንህ አይሆንም። ሚዛንህ እምነትህ ነው። ስሜትህ ነው። ስሜትህ እንጂ... ተጠባጩ እውነታ አይደለም ግብረ ገባዊ እሴትህን (moral value) የሚሰራልህ።


ከሌሊሳ ግርማ ነፀብራቅ ገፅ 79 የተቀነጨበ
@wegoch
@wegoch
@wegoch
#ወግ_ብቻ
.
መገናኛ ጋር ነው። ለታክሲ ሰልፍ ተሰልፌያለሁ። ከፊቴ እናትና ልጅ ቆመዋል። በመሐል አንዱ መፅሀፍ አዟሪ መጣ። በእጁ ብዙ መፅሀፍት ይዟል።

"የልጆች መፅሀፍ በ20 ብር ብቻ" አለ ጮክ ብሎ።

"ግዢልኝ ግዢልኝ" አለች ትንሿ ልጅ እናቷን።

"አታርፊም አንቺ!" አለች እናቷ ኮስትር ብላ።

"የልጆች መፅሀፍ በ20 ብር ብቻ" አለ በድጋሚ።

ልጅቷ "እማዬ ተይ ግዢልኝ" ስትል በቁንጥጫ ልምዝግ አደረገቻት። ልጅቷ ማልቀስ ስትጀምር መፅሀፍ አዟሪውን ጠራሁት። የተረት መፅሀፉን ተቀብዬ 20 ብር ከፈልኩኝ። መፅሀፉን ስሰጣት ልጅቷ በፈገግታ ስትቀበለኝ እናትየው በግልምጫ አነሳችኝ። እኔ ግን በልቤ ለራሴ እንዲህ አልኩ፦

"ይኼኔ መጫወቻ ቢሆን አስር ትገዛላት ነበር። ለልጆቻችን ለምን "ቁምነገር" አንገዛም?! ቢያንስ የአርቴፊሻል ሽጉጥን ያህል ስነልቡናዊ ቀውስ አያስከትሉም"

ሱራፌል አየለ
@wegoch
@wegoch
#ወግ_ብቻ
.
ፈላስስፎችና የተፈጥሮ መልስ

ሾፐንሃወር የተባለው ፈላስፋ ለሴቶች የተንሸዋረረ አመለካከት ነበረው። እንደውም በፍልስፍና ፅሁፉ ሴት ሰው አይደለችም እስከማለት ደርሷል። ታዲያ ከዚህ ፍልስፍናው በኋላ አንዲት ሴት ይወዳል። ይሁን እንጂ ሰው አይደለችም ብሎ የፈረጃት ሴት ፊት ነሳችው። ሴት ሰው ናት ወይ የሚለውን ጥያቄ ተፈጥሮ ራሷ መለሰችው።

ኒቼ ታላቅ ፈላስፋ ነው። የእግዚአብሔርን ሞት ያረዳን ኒቼ ነበር። በእርግጥ ኒቼ ወፈፍ ያደርገው ነበር። እናም እግዚአብሔርም በተራው የኒቼን ሞት አረዳን። ከተፈጥሮ ጋር ታግሎ ያሸነፈ የለም። ከተፈጥሮ የበለጠ ጠቢብ የለም። የአዋቂዎች ጥበብ ከንቱ ነው።

ዲዎጋን ተፈጥሮ ባይሆንም የሱን ልጨምርላችሁ፦

ፕሌቶ(አፍላጦን) ለተማሪዎቹ ሰው ማለት ሁለት እግር ያለው ክንፍ አልባ እንስሳ ነው ብሎ አስተማረ። በማግስቱ ዲዎጋን ክንፉ የተነቀለ ዶሮ ይዞ መጥቶ "ይኸውላችሁ የፕሌቶ ሰው" ብሎ በተማሪዎቹ አስቆበታል።

ምንም ያህል ብልህ ብትሆኑ የበለጠ ብልህ አለ!
ቴዎድሮስ ሸዋንግዛው
@wegoch
@wegoch
2024/09/24 21:31:01
Back to Top
HTML Embed Code: