Telegram Web Link
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#COVID19

ባለፈው ሳምንት ከፕሬዝዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴና ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ጋር የተገናኙ 2 የአውሮፓ ህብረት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በኮሮና ስጋት ራሳቸውን ማግለላቸውን 'ኢትዮጵያ ኢንሳይደር' ድረገፅ አስነበበ።

ባለስልጣናቱ ራሳቸውን ያገለሉት አብረዋቸው ወደ ኢትዮጵያ ከተጓዙ የልዑካን ቡድን አባላት መካከል አንዱ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው በምርመራ ከተረጋገጠ በኋላ ነው።

ከትናንት ጀምሮ ራሳቸውን ማግለላቸውን የገለጹት የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ እና የጸጥታ ፖሊሲ ከፍተኛ ተወካይ ጆሴፕ ቦሬል እና የህብረቱ የቀውስ አስተዳደር ኮሚሽነር ያኔዝ ሌናርቺች ናቸው።

ባለፈው ሳምንት ሐሙስ መስከረም 28/2013 ዓ/ም ከጠ/ሚ አቢይ አህመድ ጋር የተገናኙት ባለስልጣናቱ ፤ በማግስቱ ከፕሬዝዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ጋርም ተወያይተዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#UPDATE

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ማስቀጠያና ቅድመ ዝግጅት ማጠቃለያን እንዲሁም የኮቪድ-19ን ወረርሽኝ ምላሽ ተግባራት ዝግጅት በተመለከተ ተቋማት የደርሱበትን ደረጃ ሊገመግም ነው።

በዚህ መድረክ ፦

• የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች
• የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቋሚ ኮሚታ ሰብሳቢዎች
• የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣
• በከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ቁልፍ ሚኒ ያላቸው መንግስታዊ ተቋማት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ይገኛሉ።

ከጥቅምት 6 እስከ 8 በሀዋሳ ከተማ በሚካሄደው መድረክ ላይ ፦

- ኮቪድ-19 በመከላከልና ሰላማዊ የመማር ማስተማርን በማረጋገጥ ላይ የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ሚና ፤

- በኮቪድ-19 ወቅት ትምህርትና ስልጠና ለማቀጠል የሚወሰዱ ክልከላዎች እና እርምጃዎች ፤

እንዲሁም ከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና እንደገና ለማስጀመር ተቋማት የደረሱበትን ደረጃ በመገምገም ላይ የሚገኘው ግብረኃይል ሪፖርት መሰረት ወይይት ተደርጎ ውሳኔና ቀጣይ አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#UPDATE

በሰሜን ወሎ ዞን ከ18 ሺህ ሄክታር በላይ በጤፍ ፣ ማሽላና ማሾ የተሸፈነ ማሳ በአንበጣ መንጋ ሙሉ በሙሉ መውደሙን ዞኑ ለetv አስታውቋል።

የአንበጣ መንጋውን ለመከላከል በሰው ኃይልና በአውሮፕላን ርጭት እየተካሄደ ቢሆንም አንበጣው በብዛት በመፈልፈሉ እና በተደጋጋሚ በመከሠቱ ጉዳቱ እየከፋ መምጣቱን ዞኑ ገልጿል።

የአንበጣ መንጋው ተጨማሪ ጉዳት እንዳያደርስ ህብረተሰቡ እንዲሁም የመከላከያ ሠራዊት እና የክልሉ ልዩ ኃይል አባላት የደረሱ ሰብሎችን በመሰብሰብ አርሶ አደሮችን እየደገፉ ነው።

በደረሰው ጉዳት ምክንያት ከ34 ሺህ በላይ ዜጎች ለችግር እንደሚዳረጉ ተገልጿል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#MoE

የትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር ገረመው ሁሉቃ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ ተከታዮቹን ነጥቦች አንስተዋል ፦

- የመምህራን እጥረትን ለመቅረፍ ከዚህ ቀደም /በፊት የማስተማር ልምድ ያላቸው እና አዲስ ተመራቂ ተማሪዎች ሀገራዊ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።

- ተመራቂዎች በመምህርነት ስራ የመቀጠል ፍላጎት ካላቸው በቀጣይ ቅጥር በሚካሄድበት ጊዜ ቅድሚያ ይሰጣቸዋል።

- የመማር ማስተማር ሂደቱን በፈረቃ ለማስቀጠል የተያዘው እቅድ እንደየአካባቢው ነባራዊ ሁኔታ የሚወሰን ይሆናል፡፡

- ጥሪ የተደረገላቸው መምህራን በበጎ ፍቃድ አገልግሎት የሚሳተፉ እንጂ ቅጥር የሚፈፅሙ አይደሉም።

- መደበኛ አስተማሪዎች ከዚህ ቀደም ከሚያስተምሩት ክፍለ ጊዜ በተጨማሪ አምስት ክፍለ ጊዜ በበጎ ፈቃድ እንዲያስተምሩ የሚደረግ ይሆናል።

- የመማሪያ ክፍል እጥረትን ለማስወገድ የአርሶ አደር ማሰልጠኛ ጣቢያዎችን፣ የቀበሌ ፅህፈት ቤቶችን እና የሃይማኖት ተቋማት አገልግሎሎት እንዲሰጡ ይደረጋል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
ችሎት !

በአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የሚገኙት 4ቱ ተጠርጣሪዎች ፦

- ጥላሁን ያሚ፣
- ከበደ ገመቹ፣
- አብዲ አለማየሁ እንዲሁም ላምሮት ከማል እያንዳንዳቸው "ወንጀሉን አልፈጸምንም፤ ጥፋትም የለንም" በማለት ዛሬ ለፍርድ ቤት ተናግረዋል።

ተጠርጣሪዎቹ ይህን ያሉት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሕግ እና ጸረ ሽብር ችሎት ዛሬ ረቡዕ በቀረቡበት ወቅት ነው።

የተከሳሾች ጠበቃ ተከሳሾቹ የክስ መከላከያ እንደሌላቸው ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል።

ዐቃቤ ሕግ ፖሊስ መስክሮችን እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ይሰጠ ሲል ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

ፍርድ ቤቱ ግን ዐቃቤ ሕግ ራሱ መስክሮቹን ፍርድ ቤት እንዲያቀርብ አዟል።

በዚሁ መሠረት ከኅዳር 23 እስከ 25/2013 ዓ.ም ምስክሮቹን ይዞ እንዲቀርብ ፍርድ ቤቱ ተዕዛዝ ሰጥቷል።

Via BBC
@tikvahethiopiaBot
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#ATTENTION📣

በምዕራብ ሀረርጌ ውስጥ ወጥ የሆነ ትልቅ የማሽላ ምርት የሚገኘው ከጉባ ቆርቻ ወረዳ ፣ ኦዳ አነኒ የሚባል ቀበሌ ነው።

ዘንድሮ ጥሩ ዝናብ አግኝተው ትልቅ ምርት ይጠብቁ ነበር ፤ ነገር ግን የአምበጣ መንጋ መጥቶ ወሮባቸዋል፤ ይኸው ሁኔታ እጅግ ሀዘን ውስጥ ከቷቸዋል።

የመንጋው እዛው ወረዳ ላይ የተለያዩ ቀበሌዎችንም ወሯል ፣ ኦዳ ዲማ ፣ እና ወደ ቆላማው ያሉትን ቀበሌዎች እጅጉን ጎድቷቸዋል።

በአጠቃላይ በወረዳው የሚገኙ አስራ አራት ቀበሌዎች እስካሁኗ ሰዓት ድረስ አንበጣ መንጋ ተከስቷል።

የሚጮህላቸው አክቲቪስትም ሆነ ሚድያ ስለሌላቸው እጅጉን ችላ ተብለዋል። የሚመለከተው አካል ሁሉ አስፈላጊውን ማድረግ ይኖርበታል።

እዮብ ወንዱ
ጥቅምት 4/2013 ዓ/ም

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
በትግራይ የኬሚካል ርጭት ተካሂዷል ?

በግብርና ሚንስቴር የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ አበራ ለማ ፦

"የአንበጣ መንጋውን ለመዋጋት ሚኒስቴሩ አውሮፕላኖችን ጨምሮ የአንበጣ መከላከያ መሳሪያዎችን ቢያዘጋጅም የትግራይ ክልል ግብርና ቢሮም ይሁን እስከ ወረዳ ያሉት መዋቅሮች የአንበጣውን መገኛ አሳውቆ እርጭት እንዲደረግ የፍቃደኝነት ችግር ስላለ እስካሁን ርጭት አልተካሄደም።

አሁንም ቢሆን ከክልሉ ወረዳዎች ጋር በስልክ እየተገናኘም ነው ፤ የአንበጣ መንጋው የተከሰተበትን ቦታ ለይተው የሚያሳወቁ ከሆነ በአውሮፕላን የኬሚካል ርጭት ማድረግ ይቻላል።

የገበሬዎች ምርት ከፖለቲካ የተለየ ነገር ነው ፤ ፋይዳውን አይተው ፤ ለሕብረተሰቡ አስበው መረጃውን የሚሰጡ ከሆነ የፌደራል መንግሥት የኬሚካል ርጭቱን ለማካሄድ ዝግጅቱም ሆነ ፍላጎቱ አለው።"

-

በትግራይ ክልል የእርሻና ገጠር ልማት ቢሮ የተምች መከላከልና ቁጥጥር፣ የዕፅዋት ኳራንታይን ዳይሬክተር አቶ መብራህቶም ገብረኪዳን ፦

"የግብርና ሚንስቴር በአውሮፕላን አማካኝነት የኬሚካል እርጭት ለማካሄድ እንደሚረዱን ገልጸውልናል።

አውሮፕላን እንዲልኩና የሚረጭበት አካባቢ እንድናሳውቃቸው በነገሩን መሠረት ስምምነት ላይ ደርሰናል፤ ቢሆንም ግን እምነት የለንም።

ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ ከዚህ ቀደም በአውሮፕላን የኬሚካል እርጭት እናካሂዳለን ተብሎ ከግብርና ሚንስቴር እንድንዘጋጅ ተነግሮን ብንጠብቅም ዋጃ አጠገብ ድንበር ላይ ረጭተው ተምልሰዋል።

አውሮፕላን የትም ቦታ ኬሚካል አይረጭም። ለምሳሌ በመንደር ውስጥ ፣ ውሃ ላይ እንዲሁም ተራራማና ሸለቆ ውስጥ መርጨት የለበትም ወይም ለመርጨት አይመቸውም።

ግብር ሚኒስቴር ቢያግዘን ጥሩ ነው ካልሆነም በራሳችን እንሰራዋለን።" (BBC)

@tikvahethiopiaBOT
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
የሰሜን ወሎ ዞን አርሶ አደሮች ጥሪ ፦

(በአብመድ)

ዛሬ በአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር ዶክተር ፋንታ ማንደፍሮ የተመራ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን የበርሃ አንበጣ መንጋ የመከላከል እንቅስቃሴውን በቦታው በመገኘት ተከታትሏል።

ልዑኩ ከአርሶ አደሮች እና ባለሙያዎች ጋርም ተነጋግሯል።

ልዑኩ የበርሃ አንበጣ መንጋው የተከሰተባቸው የራያ ቆቦ ወረዳ ሁለት ቀበሌዎች 41 አዲስ ዓለም እና 06 መንደፈራ ተገኝቶ የመከላከል ሥራውን ምልከታ አካሂዷል፡፡

በቀበሌዎቹ አንበጣው በጤፍና ማሽላ ሰብሎች ላይ ጉዳት አድርሷል፡፡

አርሶ አደሮች ኅብረተሰቡን ያሳተፈ መከላከል ሥራ ቢጠናከር የተሻለ እንደሆነ የመፍትሔ ሐሳብ አቅርበዋል፡፡

የፀጥታ አካላት ፣ ተማሪዎች ፣ በጎ ፈቃደኛ የሆኑ ወጣቶች እንዲሳተፉና የደረሱ ሰብሎችን በመሰብሰብ እንዲተባበሯቸው ማስተባበር እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ👏

የአርሶ አደሩን ህይወት መታደግ የራስን ህይወት መታደግ ነው !

የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ አመራሮች ፣ ሰራተኞች ፣ መምህራን እንዲሁም የደብረ ብርሃን ወጣቶች ትላንት በቀወት ወረዳ የደረሱ የአርሶ አደር ሰብሎችን በመሰብሰብ የአንበጣ መንጋ የሚያደርሰውን ጉዳት የመከላከል ሥራ አከናውነዋል።

የአርሶ አደሩ ህይወት አደጋ ላይ ነው ማለት የከተማው ነዋሪ የመኖር ህልውና አደጋ ላይ እንደሆነ መረዳት ተገቢ ነው ሲሉ የዘመቻው አስተባባሪ ዶ/ር ታምራት ቸሩ ተናግረዋል።

ዘመቻው በአጭር ጊዜ የታቀደ ቢሆንም ውጤታማ እንደነበር ተገልጿል። በቀጣይም ይህ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ አሳውቋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በፖሊስ መወሰዱ ተሰማ !

ዛሬ 8:00 አካባቢ ቁጥራቸው በርከት ያሉ ፖሊሶች ' ፍትህ መፅሄት ' የሚገኝበት ቢሮ በመገኘት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በወቅቱ ቢሮ ስላልነበር ካለበት በስልክ በመጥራት ይዘውት እንደሄዱ ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ ገልጿል።

ባሳለፍነው ቅዳሜ በፍትሕ መጽሔት ላይ ' አባ ብላ ገመዳ ' በሚል ርዕስ በተጻፈ ጹሑፍ ዙሪያ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ለብሮድካስት ባለስልጣን የቅሬታ ደብዳቤ ጽፎ ነበር፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#UPDATE

ጋዜጠኛ ተመስገን ታስሮ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እንደገባ ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ አሳውቋል !

ታሪኩ ደሳለኝ ተከታዩን ብሏል ፦

"ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን መታሰሩን በር ላይ ያሉት ፖሊሶች ነግረውናል።

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከቢሮ መወሰዱን እንደሰማን ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ያመራን ሲሆን እዛ በር ላይ ያሉት ፖሊሶች ተመስገንና የመፅሔቱ አዘጋጅ ምስጋን ዝናቤ ተይዘው መግባታቸውን ገልፀውልናል።

ከዚያ ውጪ ምንም ዓይነት መረጃን ያላገኘን ሲሆን ምናልባት ምግብና ልብስ ካመጣን ለማስገባት እንደሚተባበሩን ነግረውናል።"

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
ጥቅምት 4/2013 ዓ/ም

የኢትዮጵያ ኮቪድ-19 መረጃዎች ፦

#Somali

በሶማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 146 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ በቫይረሱ መያዙ የተረጋገጠ ሰው አልተገኘም።

#BenishangulGumuz

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 85 የላብራቶሪ ምርመራ ተራደርጎ 27 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#Amhara

በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 765 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 76 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። የ2 ሰው ህይወት አልፏል (1 ከእንጅባራ ህክምና ማዕከል፣ 1 ከሃይቅ)

#Oromia

በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 579 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 102 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል። የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል።

#DireDawa

በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 142 የላብራቶሪ ምርመራ 54 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#Harari

በሐረሪ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 94 የላብራቶሪ ምርመራ 13 ሰዎች በቫረረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#SNNPRS

በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 1304 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 55 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።

#AddisAbaba

በአ/አ ባለፉት 24 ሰዓት 3,246 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 308 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል፤ የ2 ሰዎች ህይወት አልፏል።

* ያልተካከቱ የክልል ሪፖርቶችን ቆይት ብላችሁ ይህንኑ ፖስት ተመልከቱ !

@tikvahethiopiaBOT
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
በኢትዮጵያ ከኮቪድ-19 ያገገሙ ሰዎች ከ40 ሺህ አለፉ!

በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 7,121 የላብራቶሪ ምርመራ 712 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ የ7 ሰዎች ህይወት አልፏል። በተጨማሪ በትላንትናው ዕለት 858 ሰዎች አገግመዋል።

በአጠቃላይ በሀገራችን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 86,430 የደረሱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 1,312 ደርሷል ፤ ከበሽታው ያገገሙ አጠቃላይ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 40,165 ደርሷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
ኒኮላስ የተሰኘው የመቐለ ልዩ ት/ቤት ወጣት የኬሚስትሪ እና የስነ ህይወት ባለሙያዎች አዲስ የአንበጣ ማጥፍያ ኬሚካል ሰሩ።

ከ3-5 ደቂቃ ባለዉ ጊዜ አንበጣ ይገድላል የተባለዉ ኬሚካል ከሰሞኑን በመስክ ተሞክሮ ውጤታማ መሆኑን ባለሙያዎች አረጋግጠዋል።

ወጣቶቹ ምርምር ማድረግ የጀመሩት የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት (FAO) ሥለ አንበጣ መንጋ ሥርጭትና አደገኛነት ያወጣውን ማስጠንቀቂያ አከል ትንበያ በመስማታቸው ነው።

አዲሱ ፀረ አንበጣ ኬሚካል በቅርብ ከሚገኙ ዕፅዋት የተቀመመ ፣ በብዛት ሊመረት የሚችል እና የተፈጥሮ አካባቢን የማይጎዳ ነው ተብሏል። (DW)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
ሹመት !

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጥቅምት 04 ቀን 2013 ዶ/ር አረጋዊ በርሔን የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብ/ም/ቤት ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አድርገው ሾመዋል።

#PMOEthiopia
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
#UPDATE

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ (የፍትህ ማናጂንግ ዳይሬክተር) ከእስር መፈታቱን ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ ከደቂቃዎች በፊት አሳውቋል።

ከዚህ በተጨማሪ የፍትህ መጽሔት ዋና አዘጋጅ ምስጋን ዝናቤም ከእስር መፈታቱ ተሰምቷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
2024/09/21 07:30:27
Back to Top
HTML Embed Code: